የገቢዎች ሚኒስቴርና የጉምሩክ ኮሚሽን 1 ቢሊየን 47 ሚሊየን 909 ሺህ 135 ብር የሚያወጡ የተለያዩ የምግብና አልባሳት ቁሳቁስ ድጋፍ አደረጉ።
ድጋፉ ለዘጠኙም ክልሎች እና ለሁለቱ የከተማ አስተዳደሮች እንዲሁም ለ26 በጎ አድራጎት ማህበራት የተበረከተ ነው። የገቢዎች ሚኒስትር አቶ ላቀ አያሌው የኮሮና ቫይረስ እያሳደረ የመጣውን ተፅዕኖ በጋራና በአብሮነት ለመከላከል እርዳታው አስፈላጊ መሆኑን በመጥቀስ ለሁለተኛ ጊዜ መደረጉን ተናግረዋል።
የተደረገው ድጋፍ በተለያየ ጊዜ በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች በኮንትሮባንድ መልክ የተያዙ መሆናቸው በርክክቡ ወቅት ተገልጿል።ድጋፉን የየክልሉ አመራሮች እንዲሁም የሚመለከታቸው ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች ከአቶ ላቀ አያሌው እና ከጉምሩክ ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ደበሌ ቃበታ እጅ ተረክበዋል።
Via FBC
@YeneTube @FikerAssefa
ድጋፉ ለዘጠኙም ክልሎች እና ለሁለቱ የከተማ አስተዳደሮች እንዲሁም ለ26 በጎ አድራጎት ማህበራት የተበረከተ ነው። የገቢዎች ሚኒስትር አቶ ላቀ አያሌው የኮሮና ቫይረስ እያሳደረ የመጣውን ተፅዕኖ በጋራና በአብሮነት ለመከላከል እርዳታው አስፈላጊ መሆኑን በመጥቀስ ለሁለተኛ ጊዜ መደረጉን ተናግረዋል።
የተደረገው ድጋፍ በተለያየ ጊዜ በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች በኮንትሮባንድ መልክ የተያዙ መሆናቸው በርክክቡ ወቅት ተገልጿል።ድጋፉን የየክልሉ አመራሮች እንዲሁም የሚመለከታቸው ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች ከአቶ ላቀ አያሌው እና ከጉምሩክ ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ደበሌ ቃበታ እጅ ተረክበዋል።
Via FBC
@YeneTube @FikerAssefa
በአዲስ አበባ ከተማ የቤት ለቤት የኮሮናቫይረስ ምርመራ ሊጀመር ነው
ምክትል ከንቲባው ታከለ ኡማ እንደገለጹት ከሚቀጥለው ሳምንት ጀምሮ በአዲስ አበባ ሁሉም ወረዳዎች የኮሮናቫይረስ ምርመራ ይጀመራል።
ምርመራው ተጋላጭ ሊሆኑ ይችላሉ ተብለው ከተለዩ ወረዳዎች የሚጀምር መሆኑን ገልጸው በመዲናዋ 117ቱም ወረዳዎች ይከናወናል ብለዋል።
ለምርመራው ጡረታ ላይ የነበሩና በሞያው ልምድ ያላቸው ከ1 ሺህ 200 በላይ ሃኪሞች የመንግስትን ጥሪ ተቀብለው ካሉት ሃኪሞች ጋር ተጨማሪ ሃይል በመሆን ዝግጁ መሆናቸውንም ከንቲባው ገልጸዋል።
ከቤት ለቤት ምርመራው በተጨማሪ በሚቀጥለው ሳምንት ተማሪዎች በያሉበት ሆነው ትምህርት እንደሚጀምሩና የምገባ መርሃ ግብሩም እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
በተያዘው መርሃ ግብር መሰረት ከ7ኛ ክፍል በታች የሚማሩ ተማሪዎች ትምህርቱን በሬዲዮ የሚከታታሉ ይሆናል።
ከ7ኛ እስከ 12ኛ ክፍል የሚማሩ ተማሪዎች ደግሞ ትምህርታቸውን በፕላዝማ የሚከታተሉ ይሆናል።በዚህ ሂደት ተማሪዎችና መምህራን የተለያዩ መረጃዎችን የሚለዋወጡበት የአሰራር ስርአትም መሰርጋቱ ተገልጿል።
የተማሪዎች ምገባ መርሃ ግብርም በተለያዩ አካባቢዎች 1 ሺህ 200 ተማሪዎች የሚመገቡባቸው የምግብ ባንኮች ተዘጋጅተዋል፤ ለምግብ አቅርቦቱም 30 ሺህ ወጣቶች ዝግጁ ሆነዋል ተብሏል።
ምንጭ: ኢዜአ
@Yenetube @Fikerassefa
ምክትል ከንቲባው ታከለ ኡማ እንደገለጹት ከሚቀጥለው ሳምንት ጀምሮ በአዲስ አበባ ሁሉም ወረዳዎች የኮሮናቫይረስ ምርመራ ይጀመራል።
ምርመራው ተጋላጭ ሊሆኑ ይችላሉ ተብለው ከተለዩ ወረዳዎች የሚጀምር መሆኑን ገልጸው በመዲናዋ 117ቱም ወረዳዎች ይከናወናል ብለዋል።
ለምርመራው ጡረታ ላይ የነበሩና በሞያው ልምድ ያላቸው ከ1 ሺህ 200 በላይ ሃኪሞች የመንግስትን ጥሪ ተቀብለው ካሉት ሃኪሞች ጋር ተጨማሪ ሃይል በመሆን ዝግጁ መሆናቸውንም ከንቲባው ገልጸዋል።
ከቤት ለቤት ምርመራው በተጨማሪ በሚቀጥለው ሳምንት ተማሪዎች በያሉበት ሆነው ትምህርት እንደሚጀምሩና የምገባ መርሃ ግብሩም እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
በተያዘው መርሃ ግብር መሰረት ከ7ኛ ክፍል በታች የሚማሩ ተማሪዎች ትምህርቱን በሬዲዮ የሚከታታሉ ይሆናል።
ከ7ኛ እስከ 12ኛ ክፍል የሚማሩ ተማሪዎች ደግሞ ትምህርታቸውን በፕላዝማ የሚከታተሉ ይሆናል።በዚህ ሂደት ተማሪዎችና መምህራን የተለያዩ መረጃዎችን የሚለዋወጡበት የአሰራር ስርአትም መሰርጋቱ ተገልጿል።
የተማሪዎች ምገባ መርሃ ግብርም በተለያዩ አካባቢዎች 1 ሺህ 200 ተማሪዎች የሚመገቡባቸው የምግብ ባንኮች ተዘጋጅተዋል፤ ለምግብ አቅርቦቱም 30 ሺህ ወጣቶች ዝግጁ ሆነዋል ተብሏል።
ምንጭ: ኢዜአ
@Yenetube @Fikerassefa
በአዲስ አበባ 1200 የሚጠጉ የምግብ ባንኮች ተቋቁመዋል።
የምግብ ባንኮቹ ከኮሮና ቫይረስ ጋር በተያያዘ ችግር የሚገጥማቸው ዜጎችን ለመደገፍ ነው ብለዋል ኢ/ር ታከለ ኡማ።ኢ/ር ታከለ በመስጠት ላይ ባሉት መግለጫቸው ነዋሪዎች በየአካባቢው በተዘጋጁት የምግብ ባንኮች ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል።
Via ENA
@YeneTube @FikerAssefa
የምግብ ባንኮቹ ከኮሮና ቫይረስ ጋር በተያያዘ ችግር የሚገጥማቸው ዜጎችን ለመደገፍ ነው ብለዋል ኢ/ር ታከለ ኡማ።ኢ/ር ታከለ በመስጠት ላይ ባሉት መግለጫቸው ነዋሪዎች በየአካባቢው በተዘጋጁት የምግብ ባንኮች ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል።
Via ENA
@YeneTube @FikerAssefa
ለኢትዮጵያ ገበያ ሊቀርቡ ጅቡቲ ወደብ ላይ ደርሰው ከነበሩ የምግብ ሸቀጥ እና ዘይቶች ውስጥ የጅቡቲ መንግስት የተወሰኑት እዚያው በሀገሩ ገበያ ላይ እንዲቀርቡ ማዘዙን ሸገር ኤፍ ኤም ሰምቻለው ብሏል፡፡
ወደ ኢትዮጵያ ሊገቡ የነበሩ መኮረኒ እና ፓስታ የመሳሰሉ የምግብ ሸቀጦች የጅቡቲ መንግስት የምግብ እጥረት በሀገሩ ሊኖር ይችላል በሚል እዚያው ለሽያጭ እንዲውሉ ማዘዙ ታውቋል፡፡መረጃውን ለማጣራት ሸገር በጅቡቲ የኢትዮጵያ ጉምሩክ ሀላፊ የሆኑት አቶ አሊ አብደላ ጋር ደውሏል፡፡እሳቸውም ጉዳዩ በሁለቱ ሀገራት ከፍተኛ የመንግስት ሀላፊዎች ደረጃ ንግግር እየተደረገበት መሆኑን በመጠቆም ዝርዝር መረጃ ከመስጠት ተቆጥበዋል፡፡
ምንጭ: ሸገር ኤፍ ኤም
@YeneTube @FikerAssefa
ወደ ኢትዮጵያ ሊገቡ የነበሩ መኮረኒ እና ፓስታ የመሳሰሉ የምግብ ሸቀጦች የጅቡቲ መንግስት የምግብ እጥረት በሀገሩ ሊኖር ይችላል በሚል እዚያው ለሽያጭ እንዲውሉ ማዘዙ ታውቋል፡፡መረጃውን ለማጣራት ሸገር በጅቡቲ የኢትዮጵያ ጉምሩክ ሀላፊ የሆኑት አቶ አሊ አብደላ ጋር ደውሏል፡፡እሳቸውም ጉዳዩ በሁለቱ ሀገራት ከፍተኛ የመንግስት ሀላፊዎች ደረጃ ንግግር እየተደረገበት መሆኑን በመጠቆም ዝርዝር መረጃ ከመስጠት ተቆጥበዋል፡፡
ምንጭ: ሸገር ኤፍ ኤም
@YeneTube @FikerAssefa
#69
4 ሰዎች ዛሬ በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል።
ባለፉት 24 ሰዐታት ውስጥ በተደረገው ተጨማሪ ምርመራ 345 ተመርምረው 4 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸውን ተረጋግጧል።
@Yenetube @Fikerassefa
4 ሰዎች ዛሬ በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል።
ባለፉት 24 ሰዐታት ውስጥ በተደረገው ተጨማሪ ምርመራ 345 ተመርምረው 4 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸውን ተረጋግጧል።
@Yenetube @Fikerassefa
የታማሚዎቹ ሁኔታ :-
ታማሚ 1 :- እድሜ 33 : ዜግነት ኢትዮጵያ ሴት ስትሆን ከአሜሪካ የመጣች ናት በለይቶ ማቆያ ያለች
ታማሚ 2 :- እድሜ 30 : ዜግነት ኢትዮጵያ ሴት ስትሆን ከዱባይ የመጣች ናት በለይቶ ማቆያ ያለች
ታማሚ 3 :- እድሜ 29 : ዜግነት ኢትዮጵያ ወንድ ሲሆን ከዱባይ የመጣ ነው በለይቶ ማቆያ ያለች
ታማሚ 4 :-እድሜ 42 : ዜግነት ኢትዮጵያ የጉዞ ታሪክ የለውም
@Yenetube @Fikerassefa
ታማሚ 1 :- እድሜ 33 : ዜግነት ኢትዮጵያ ሴት ስትሆን ከአሜሪካ የመጣች ናት በለይቶ ማቆያ ያለች
ታማሚ 2 :- እድሜ 30 : ዜግነት ኢትዮጵያ ሴት ስትሆን ከዱባይ የመጣች ናት በለይቶ ማቆያ ያለች
ታማሚ 3 :- እድሜ 29 : ዜግነት ኢትዮጵያ ወንድ ሲሆን ከዱባይ የመጣ ነው በለይቶ ማቆያ ያለች
ታማሚ 4 :-እድሜ 42 : ዜግነት ኢትዮጵያ የጉዞ ታሪክ የለውም
@Yenetube @Fikerassefa
10 ሰው አገግሟል!
በኢትዮጵያ ተጨማሪ ስድስት ግለሰቦች ከኮሮና ቫይረስ አገግመዋል።
በአጠቃላይ በኢትዮጵያ ያገገሙ ሰዎች ቁጥር 10 ደርሷል።
@Yenetube @FikerAssefa
በኢትዮጵያ ተጨማሪ ስድስት ግለሰቦች ከኮሮና ቫይረስ አገግመዋል።
በአጠቃላይ በኢትዮጵያ ያገገሙ ሰዎች ቁጥር 10 ደርሷል።
@Yenetube @FikerAssefa
ሀዋሳ የሚገኘው ኬር አውድ ኢንተርናሽናል ሆቴል (በአራት ኮኮብ ሆቴል) በሀዋሳ ከተማ ላይ ኮሮና ቫይረስ ከተከሰተ ለአንድ መቶ የህክምና ባለሙያዎች ለአንድ ወር የምሳ አገልግሎት እንደሚሰጥ እንዲሁም በሻሸመኔ ከተማ በንግድ ሱቃቸው ተከራይተው ለሚሰሩ ደንበኞች የአንድ ወር የቤት ኪራይ ነፃ ያደረጉ መሆኑን በተለይም ለየኔቲዩብ ተናግሯል።
@Yenetube @Fikerassefa
@Yenetube @Fikerassefa
በኬንያ የኢፌዲሪ ኤምባሲ ኬንያ ውስጥ ታስረው የነበሩ 19 ዜጎች ከአገሪቱ የኢሚግሬሽን ባለስልጣን ጋር በመተባብር ዛሬ ሚያዝያ 3 ቀን 2012 ዓ.ም ሞያሌ አድርሷል።
ከ16-25 ዓመት ዕድሜ ያላቸው ዜጎች የተያዙት ኬንያን አቋርጠው ወደ ደቡብ አፍሪካ ለመሄድ ሲሞክሩ ያለጉዞ ሰነድ በመገኘታቸው ነው ።በኢትዮጵያ መንግስትና የዓለም የፍልሰት ድርጅት (IOM) ጤንነታቸውን ጠብቆ ለቤተሰባቸው ለማብቃት የኮሮና ለይቶ መቆያ ገብተዋል።ቀደም ሲል በተመሳሳይ ለይቶ ማቆያ የነበሩ 64 ዜጎቻችን ጤናቸው ተረጋግጦ ወደ ቤተሰቦቻቸው ተሸኝተዋል።
ምንጭ: በኬንያ የኢትዮጵያ ኤምባሲ
@YeneTube @FikerAssefa
ከ16-25 ዓመት ዕድሜ ያላቸው ዜጎች የተያዙት ኬንያን አቋርጠው ወደ ደቡብ አፍሪካ ለመሄድ ሲሞክሩ ያለጉዞ ሰነድ በመገኘታቸው ነው ።በኢትዮጵያ መንግስትና የዓለም የፍልሰት ድርጅት (IOM) ጤንነታቸውን ጠብቆ ለቤተሰባቸው ለማብቃት የኮሮና ለይቶ መቆያ ገብተዋል።ቀደም ሲል በተመሳሳይ ለይቶ ማቆያ የነበሩ 64 ዜጎቻችን ጤናቸው ተረጋግጦ ወደ ቤተሰቦቻቸው ተሸኝተዋል።
ምንጭ: በኬንያ የኢትዮጵያ ኤምባሲ
@YeneTube @FikerAssefa
ጅቡቲ በኮሮና ቫይረስ ምክንያት ሁለተኛ ሞት ዛሬ አስተናግዳለች። የሀገሪቱ የጤና ሚኒስቴር ይፋ ባደረገው መሰረት በ24 ሰአት ውስጥ ተጨማሪ 37 ኬዞች የተመዘገቡ ሲሆን በአጠቃላይ የተያዙት ቁጥር 187 እንደደረሰ ሆርን ዲፕሎማት ዘግቧል።
@YeneTube @FikerAssefa
@YeneTube @FikerAssefa
በሱማሌ ክልል ጅግጅጋ ከተማ የኮሮና ቫይረስን መመርመር የሚያስችል ላብራቶሪ በክልሉ ፕሬዝደንት ተመርቆ ተከፈተ።
Via Ethiopia Live Updates
@YeneTube @FikerAssefa
Via Ethiopia Live Updates
@YeneTube @FikerAssefa
የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ማወስፈፀሚያ ደንብ ይፋ ሆነ።
የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ማስፈፀሚያ ደንቡን የፌዴራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ ይፋ አደረገ።
የኮቪድ 19 ወረርሽኝ ስርጭትን ለመከላከል፣ለመቆጣጠርና የሚያስከትለውን ጉዳት ለመቀነስ በሚኒስተሮች ምክር ቤት የወጣው ረቂቅ አዋጅ ትናንት በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መፅጽደቁ ይታወቃል።
የፌዴራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ ወይዘሮ አዳነች አቤቤ የአዋጁን ማስፈፀሚያ ደንብ አጠቃላይ ይዘት በሚመለከት ዛሬ ማብራሪያ ሰጥተዋል።
ምንጭ:ኢ.ፕ.ድ
@YeneTube @FikerAssefa
የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ማስፈፀሚያ ደንቡን የፌዴራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ ይፋ አደረገ።
የኮቪድ 19 ወረርሽኝ ስርጭትን ለመከላከል፣ለመቆጣጠርና የሚያስከትለውን ጉዳት ለመቀነስ በሚኒስተሮች ምክር ቤት የወጣው ረቂቅ አዋጅ ትናንት በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መፅጽደቁ ይታወቃል።
የፌዴራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ ወይዘሮ አዳነች አቤቤ የአዋጁን ማስፈፀሚያ ደንብ አጠቃላይ ይዘት በሚመለከት ዛሬ ማብራሪያ ሰጥተዋል።
ምንጭ:ኢ.ፕ.ድ
@YeneTube @FikerAssefa
ማስፈፀሚያ ደንቡ አጠቃላይ አራት ዋና ዋና ከፍሎች ያሉት ሲሆን ይሄውም ክልከላን የሚያስቀምጥ፣ ግደታዎችን የሚጥል፣ የአስፈፃሚ አካላትን ክንውን እንዲሁም ልዩ ለዩ ድንጋጌዎችን የያዘ ነው።
ክልከላን በሚመለከት:
➡️ማንኛውም ሃይማኖታዊ ይሁን ፖለቲካዊ ስብሰባዎች፣ እድር፣ ደቦ፣ እቁብና ሌሎችም ከ4 ሰው በላይ ስብሰባዎች ክልክል ናቸው።
➡️ከአራት ሰዎችም ቢሆኑ ሁለት የአዋቂ ሰው እርምጃ የጠበቀ መሆን እንዳለበት አቃቤ ህጓ አብራርተዋል።
➡️ቀብርና ሌሎች አስፈላጊ ጉዳዮች ሲኖሩ ግን እየታዩ ሊፈቀዱ የሚችሉበት አሰራር መኖሩን ጠቁመዋል።
➡️ታራሚዎች ከጠበቆቻቸው ጋር አስፈላጊው ጥንቃቄ ተደርጎ እንዲገናኙ የሚፈቀድ ቢሆንም ጥየቃ ለሚሄዱ ሰዎች የማይፈቀድ መሆኑ ተገልጿል።
➡️በፖሊስ የተያዙ እስረኞችንም ስንቅ ከማቀበል በስተቀር መገናኘት የተከለከለ መሆኑን አስረድትዋል።
➡️በድንበር አካባቢ ከካርጎ፣ የደረቅና ፈሳሽ ጭነት አገልግሎቶች በስተቀር ሌሎች እንቅስቃሴዎች ዝግ ተደርገዋል።
➡️የቤት ተከራዮች በራሳቸው ፍላጎት ካልወጡ በስተቀር ማስውጣትና ኪራይም መጨመር በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ተከልክሏል።
➡️ሰራተኞችን መቀነስና የስራ ቅጥር ውል ማቋረጥም መከልከሉን ወይዘሮ አዳነች አብራርትዋል።
➡️በዚህ ደንብ መሰረት ተማሪዎችና መምህራን በኦን ላይን ካልሆነ በአካል እንዲገናኙ አይፈቀድም።
➡️ስፖርታዊ ጨዋታዎች፣ የህፃናትም ይሁን የሌሎች መጫወቻ ስፍራዎች እንዲሁም የእጅ መጨባበጥ ሰላምታ የተከለከለ መሆኑን ከኢዜአ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
➡️በትራንስፖርት ዘርፍም አገር አቋራጭ ካለው ወንበር ከ50 በመቶ በላይ ተሳፋሪ መጫን የተከለከለ ነው፡፡
Via FBC
@YeneTube @FikerAssefa
ክልከላን በሚመለከት:
➡️ማንኛውም ሃይማኖታዊ ይሁን ፖለቲካዊ ስብሰባዎች፣ እድር፣ ደቦ፣ እቁብና ሌሎችም ከ4 ሰው በላይ ስብሰባዎች ክልክል ናቸው።
➡️ከአራት ሰዎችም ቢሆኑ ሁለት የአዋቂ ሰው እርምጃ የጠበቀ መሆን እንዳለበት አቃቤ ህጓ አብራርተዋል።
➡️ቀብርና ሌሎች አስፈላጊ ጉዳዮች ሲኖሩ ግን እየታዩ ሊፈቀዱ የሚችሉበት አሰራር መኖሩን ጠቁመዋል።
➡️ታራሚዎች ከጠበቆቻቸው ጋር አስፈላጊው ጥንቃቄ ተደርጎ እንዲገናኙ የሚፈቀድ ቢሆንም ጥየቃ ለሚሄዱ ሰዎች የማይፈቀድ መሆኑ ተገልጿል።
➡️በፖሊስ የተያዙ እስረኞችንም ስንቅ ከማቀበል በስተቀር መገናኘት የተከለከለ መሆኑን አስረድትዋል።
➡️በድንበር አካባቢ ከካርጎ፣ የደረቅና ፈሳሽ ጭነት አገልግሎቶች በስተቀር ሌሎች እንቅስቃሴዎች ዝግ ተደርገዋል።
➡️የቤት ተከራዮች በራሳቸው ፍላጎት ካልወጡ በስተቀር ማስውጣትና ኪራይም መጨመር በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ተከልክሏል።
➡️ሰራተኞችን መቀነስና የስራ ቅጥር ውል ማቋረጥም መከልከሉን ወይዘሮ አዳነች አብራርትዋል።
➡️በዚህ ደንብ መሰረት ተማሪዎችና መምህራን በኦን ላይን ካልሆነ በአካል እንዲገናኙ አይፈቀድም።
➡️ስፖርታዊ ጨዋታዎች፣ የህፃናትም ይሁን የሌሎች መጫወቻ ስፍራዎች እንዲሁም የእጅ መጨባበጥ ሰላምታ የተከለከለ መሆኑን ከኢዜአ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
➡️በትራንስፖርት ዘርፍም አገር አቋራጭ ካለው ወንበር ከ50 በመቶ በላይ ተሳፋሪ መጫን የተከለከለ ነው፡፡
Via FBC
@YeneTube @FikerAssefa
አዲስ አበባ ጎተራ ወደ ወሎ ሰፈር የሚወስደዉ መንገድ ላይ የሚገኘዉ ባለ 9 ወለል ፎቅ ህንጻ ወንጌላዊት ታደሰ ህንጻ ባለቤት ወ/ሮ ገነት ታደሰ ለህንፃዉ ተከራዮች በሙሉ የአንድ ወር የቢሮ ክራይ ነፃ ማድረጋቸዉን አስታውቀዋል ፡፡
Via:- መንግስቱ ሀ/ማሪያም // Yenetube
@Yenetube @Fikerassefa
Via:- መንግስቱ ሀ/ማሪያም // Yenetube
@Yenetube @Fikerassefa
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድና ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸዉ የምግብ አቅርቦቶችን ለአዲስ አበባ መስተዳድር ለገሱ።
ባለፈው ሳምንት እያንዳንዱ ቤተሰብ ከሌላቸው ጋር “ማዕድ እንዲጋራ” ባቀረቡት ጥሪ መሠረት፣ በራሳቸው በኩል ለመስተዳድር የምግብ አቅርቦቶችን አስረክበዋል፡፡
ያስረከቡት የደረቅ ምግብ ዓይነት የከተማ መስተዳድሩ ‘እጅግ ተጋላጭ እና ድጋፍ የሚያስፈልጋቸው የከተማይቱ ነዋሪዎች’ ብሎ ለለያቸው፣ ብዙ የቤተሰብ አባል ላሏቸው 1‚000 ቤተሰቦች የሚበቃ ነው፡፡
#PMOEthiopia
@YeneTube @FikerAssefa
ባለፈው ሳምንት እያንዳንዱ ቤተሰብ ከሌላቸው ጋር “ማዕድ እንዲጋራ” ባቀረቡት ጥሪ መሠረት፣ በራሳቸው በኩል ለመስተዳድር የምግብ አቅርቦቶችን አስረክበዋል፡፡
ያስረከቡት የደረቅ ምግብ ዓይነት የከተማ መስተዳድሩ ‘እጅግ ተጋላጭ እና ድጋፍ የሚያስፈልጋቸው የከተማይቱ ነዋሪዎች’ ብሎ ለለያቸው፣ ብዙ የቤተሰብ አባል ላሏቸው 1‚000 ቤተሰቦች የሚበቃ ነው፡፡
#PMOEthiopia
@YeneTube @FikerAssefa
ሀዋሳ ከተማ የሚገኙ ባለሀብቶች ድጋፋቸውን ቀጥለዋል !!
አቶ ጋሜ ጋቲሶ የተባሉ ባለሀብት ሀዋሳ ከተማ እምብርት ላይ የሚገኘው ህንፃቸውን ( ዳሽን ህንፃ ፊት ለፊት ላይ ) የንግድ ሱቃቸውን ተከራይተው ለሚሰሩ ድርጅቶች ከመጋቢት እስከ ግንቦት ወር ድረስ ከኪራይ ነፃ አድርገዋል።
በተጨማሪ በለሀብቱ : -
-200 ሺ ብር ለሲዳማ ዞን አስተዳደር አስረክበዋል።
-100 ሺ ብር ሀዋሳ ከተማ በአስተዳደር አስረክበዋል።
- 20 ሺ ብር አዳሬ ክፍለ ከተማ በስጦታ ሰተዋል።
@Yenetube @FikerAssefa
አቶ ጋሜ ጋቲሶ የተባሉ ባለሀብት ሀዋሳ ከተማ እምብርት ላይ የሚገኘው ህንፃቸውን ( ዳሽን ህንፃ ፊት ለፊት ላይ ) የንግድ ሱቃቸውን ተከራይተው ለሚሰሩ ድርጅቶች ከመጋቢት እስከ ግንቦት ወር ድረስ ከኪራይ ነፃ አድርገዋል።
በተጨማሪ በለሀብቱ : -
-200 ሺ ብር ለሲዳማ ዞን አስተዳደር አስረክበዋል።
-100 ሺ ብር ሀዋሳ ከተማ በአስተዳደር አስረክበዋል።
- 20 ሺ ብር አዳሬ ክፍለ ከተማ በስጦታ ሰተዋል።
@Yenetube @FikerAssefa
ዋና ካምፓሱን ሀዋሳ ያደረገው ዩኒክ ስታር ኮሌጅ ኮሮና ቫይረስ ለመከላከል የሚረዱ ቁሳቁሶችን እንዲሁም 400 ሺ ብር በስጦታ አበርክቷል።
#ዩኒክ_ስታር ኮሌጅ 4 ካንፓሶቹን ለለይቶ ማቆያ እንዲውል አድርገዋል።
ካንፓሶቹ :-
- ሱሙዳ ካምፓስ ( ሀዋሳ )
- አለታጩኮ ካምፓስ ( ጩኮ )
-በንሳ ዳዬ ካምፓስ ( በንሳ )
-ሀርቤጎና ካምፓስ ( ሀርቤጎና )
ለለይቶ ማቆያ እንዲውል ለሲዳማ ህዝብ አስተዳደርና ለሀዋሳ ከተማ አስተዳደር አስረክቧል።
በተጨማሪም ለሲዳማ ህዝብ አስተዳደርና ለሀዋሳ ከተማ አስተዳደር እንዲሁም በተለያዩ ወረዳዎች ከ100 በላይ ታንከሮችን እና 5000 በላይ ጓንቶች ጨምሮ ህብረተሰብ ግንዛቤ ማስጨበጫ የሚረዱ
50,000 ፍላየሮች :
10,000 ባነሮችን እና
5,000 ስቲከሮችን አሳትመው አስረክበዋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ ተማሪዎች ባሉበት ሆነ ትምህርታቸውን የሚከታተሉበትን የትምህርት ስርዐት መዘርጋታቸውን ለየኔቲዩብ ተናግረዋል።
@Yenetube @Fikerassefa
#ዩኒክ_ስታር ኮሌጅ 4 ካንፓሶቹን ለለይቶ ማቆያ እንዲውል አድርገዋል።
ካንፓሶቹ :-
- ሱሙዳ ካምፓስ ( ሀዋሳ )
- አለታጩኮ ካምፓስ ( ጩኮ )
-በንሳ ዳዬ ካምፓስ ( በንሳ )
-ሀርቤጎና ካምፓስ ( ሀርቤጎና )
ለለይቶ ማቆያ እንዲውል ለሲዳማ ህዝብ አስተዳደርና ለሀዋሳ ከተማ አስተዳደር አስረክቧል።
በተጨማሪም ለሲዳማ ህዝብ አስተዳደርና ለሀዋሳ ከተማ አስተዳደር እንዲሁም በተለያዩ ወረዳዎች ከ100 በላይ ታንከሮችን እና 5000 በላይ ጓንቶች ጨምሮ ህብረተሰብ ግንዛቤ ማስጨበጫ የሚረዱ
50,000 ፍላየሮች :
10,000 ባነሮችን እና
5,000 ስቲከሮችን አሳትመው አስረክበዋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ ተማሪዎች ባሉበት ሆነ ትምህርታቸውን የሚከታተሉበትን የትምህርት ስርዐት መዘርጋታቸውን ለየኔቲዩብ ተናግረዋል።
@Yenetube @Fikerassefa