በአርባ ምንጭ ከተማ በኮሮና ቫይረስ ጋር የተጠረጠረ የ36 ዓመት ግለሰብ በለይቶ ማቆያ ክትትል እየተደረገለት እንደሚገኝ የዞኑ ጤና መምሪያ ገለጸ
የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊና የዞኑ ምክትል አስተዳዳሪ አቶ ተሻለ ማናዬ ዛሬ በሰጡት መግለጫ የ36 ዓመት ግለሰብ ጉንፋን መሰል ምልክቶች ታይቶበት አርባምንጭ ሆስፒታል ለህክምና በመጣበት ተጠርጥሮ ለጥንቃቄ ሲባል ለይቶ ማቆያ መዕከል ላይ እንዲቆይና የባለሙያ ክትትል እየተደረገለት ይገኛል፡፡
ግለሰቡም በቀን 07/07/2012 ዓ.ም. ለአንድ ቀን በኬንያ ለንግድ የተንቀሳቀሰ በመሆኑና ኬንያ ደግሞ የኮሮና ቫይረስ የተገኘበት አገር በመሆኑ ምክንያት ግለሰቡ ሊጠረጠር ችሏል፡፡ በአሁኑ ሰዓት ግለሰቡ በመልካም የጤንነት ሁኔታ ላይ ይገኛል ያሉት አቶ ተሻለ ከግለሰቡ ጋር ንኪኪ ያላቸዉን ሰዎች የመለየት ስራም እየተሰራ ይገኛል፡፡ ከተጠርጣሪዉ ግለሰብ በዛሬዉ ዕለት ናሙና ተወስዶ በምርመራ እንዲረጋገጥ ከክልል ጤና ቢሮ ጋር በጥምረት እየተሰራን ይገኛል ፡፡
ህብረተሰቡ በምርመራ ባልተረጋገጠ መረጃ መረበሽና መደናገር እንደሌለበት አቶ ተሻለ አሳስበዋል፡፡
@Yenetube @FikerAssefa
የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊና የዞኑ ምክትል አስተዳዳሪ አቶ ተሻለ ማናዬ ዛሬ በሰጡት መግለጫ የ36 ዓመት ግለሰብ ጉንፋን መሰል ምልክቶች ታይቶበት አርባምንጭ ሆስፒታል ለህክምና በመጣበት ተጠርጥሮ ለጥንቃቄ ሲባል ለይቶ ማቆያ መዕከል ላይ እንዲቆይና የባለሙያ ክትትል እየተደረገለት ይገኛል፡፡
ግለሰቡም በቀን 07/07/2012 ዓ.ም. ለአንድ ቀን በኬንያ ለንግድ የተንቀሳቀሰ በመሆኑና ኬንያ ደግሞ የኮሮና ቫይረስ የተገኘበት አገር በመሆኑ ምክንያት ግለሰቡ ሊጠረጠር ችሏል፡፡ በአሁኑ ሰዓት ግለሰቡ በመልካም የጤንነት ሁኔታ ላይ ይገኛል ያሉት አቶ ተሻለ ከግለሰቡ ጋር ንኪኪ ያላቸዉን ሰዎች የመለየት ስራም እየተሰራ ይገኛል፡፡ ከተጠርጣሪዉ ግለሰብ በዛሬዉ ዕለት ናሙና ተወስዶ በምርመራ እንዲረጋገጥ ከክልል ጤና ቢሮ ጋር በጥምረት እየተሰራን ይገኛል ፡፡
ህብረተሰቡ በምርመራ ባልተረጋገጠ መረጃ መረበሽና መደናገር እንደሌለበት አቶ ተሻለ አሳስበዋል፡፡
@Yenetube @FikerAssefa
ኤምሬትስ ከኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ጋር በተያያዘ ሁሉንም የመንገደኛ በረራዎቹን፣ ከመጪው ረቡዕ ጀምሮ እንደሚሰርዝ አስታውቋል።
@Yenetube @FikerAssefa
@Yenetube @FikerAssefa
የፀረ ኤች አይ ቪ መድሃኒት ያልጀመሩና ያቋረጡ ሰዎች ለኮቪድ19 ከፍተኛ ተጋላጭ ናቸው ተባለ!
የዓለም አቀፍ ወረርሺኙ ኮቪድ19 በሽታ የመከላከል አቅማቸው ዝቅተኛ የሆኑ ሰዎች ላይ ጫናው የበረታ እንደሆነ የዓለም የጤና ድርጅት በተደጋጋሚ አስታውቋል። በኢትዮጵያ ከ 600 ሺህ በላይ ከቫይረሱ ጋር የሚኖሩ ዜጎች አሉ ተብሎ ሲገመት ከዚህ ውስጥ ከ 110 ሺህ በላዩ ቫይረሱ እንዳለባቸው ተመርምረው ያላወቁ፣ አውቀው መድሃኒት መውሰድ ያልጀመሩና ጀምረው ያቋረጡ እንደሆኑ ሪፖርቶች ያሳያሉ።ኤች አይ ቪ ኤድስን ጨምሮ በተለያዩ የጤና ጉዳዮች ላይ አተኩሮ የሚሰራው የፖፑሌሽን ኢትዮጵያ ባልደረባ የሆኑት ቤዛዊት አድማሱ እንደሚሉት መድሃኒታቸውን ባግባቡ እየወሰዱ ያሉ እና በሽታ የመከላከል አቅማቸው በመደበኛ ሁኔታ ላይ ያሉ ሰዎች የተለየ ስጋት የለባቸውም። ነገር ግን አምስቱን የኮቪድ19 የመከላከያ እርምጃዎች ለራሳቸውም ሆነ ለሌሎች ዝቅተኛ የበሽታ መከላከል አቅም ላላቸው ሰዎች ሲባል ባግባቡ መተግበር ይገባቸዋል ይላሉ።
‹‹ ቫይረሱ ይኖርብኛል ብለው ለመጠርጠር በቂ ምክንያት ቢኖራቸውም ሄደው ለመመርመር ያልደፈሩ፣ ሃኪም የኤች አይ ቪ ቫይረስ እንዳለባቸው ቢያረጋግጥላቸውም መድሃኒቱን ያልጀመሩ ወይም ጀምረው ያቋረጡ ሰዎች ግን ቢቻል ዛሬ ወይም ነገ መድሃኒቱን መጀመር አለባቸው›› ሲሉ ያስጠነቅቃሉ።‹‹ ከዚህ ባሻገር የአመጋገብ ስርአታቸውን እና የበሽታ መከላከል አቅምን የሚቀንሱ እንደ ሱስ ያሉ ልምዶችን በፍጥነት ማቆም እና የኮሮና ቫይረስን ለመከላከል የሚመከሩ እርምጃዎችን ሳያወላውሉ መፈፀም አለባቸው›› እንደ ቤዛዊት ገለጻ።
Via Addis Maleda
@YeneTube @FikerAssefa
የዓለም አቀፍ ወረርሺኙ ኮቪድ19 በሽታ የመከላከል አቅማቸው ዝቅተኛ የሆኑ ሰዎች ላይ ጫናው የበረታ እንደሆነ የዓለም የጤና ድርጅት በተደጋጋሚ አስታውቋል። በኢትዮጵያ ከ 600 ሺህ በላይ ከቫይረሱ ጋር የሚኖሩ ዜጎች አሉ ተብሎ ሲገመት ከዚህ ውስጥ ከ 110 ሺህ በላዩ ቫይረሱ እንዳለባቸው ተመርምረው ያላወቁ፣ አውቀው መድሃኒት መውሰድ ያልጀመሩና ጀምረው ያቋረጡ እንደሆኑ ሪፖርቶች ያሳያሉ።ኤች አይ ቪ ኤድስን ጨምሮ በተለያዩ የጤና ጉዳዮች ላይ አተኩሮ የሚሰራው የፖፑሌሽን ኢትዮጵያ ባልደረባ የሆኑት ቤዛዊት አድማሱ እንደሚሉት መድሃኒታቸውን ባግባቡ እየወሰዱ ያሉ እና በሽታ የመከላከል አቅማቸው በመደበኛ ሁኔታ ላይ ያሉ ሰዎች የተለየ ስጋት የለባቸውም። ነገር ግን አምስቱን የኮቪድ19 የመከላከያ እርምጃዎች ለራሳቸውም ሆነ ለሌሎች ዝቅተኛ የበሽታ መከላከል አቅም ላላቸው ሰዎች ሲባል ባግባቡ መተግበር ይገባቸዋል ይላሉ።
‹‹ ቫይረሱ ይኖርብኛል ብለው ለመጠርጠር በቂ ምክንያት ቢኖራቸውም ሄደው ለመመርመር ያልደፈሩ፣ ሃኪም የኤች አይ ቪ ቫይረስ እንዳለባቸው ቢያረጋግጥላቸውም መድሃኒቱን ያልጀመሩ ወይም ጀምረው ያቋረጡ ሰዎች ግን ቢቻል ዛሬ ወይም ነገ መድሃኒቱን መጀመር አለባቸው›› ሲሉ ያስጠነቅቃሉ።‹‹ ከዚህ ባሻገር የአመጋገብ ስርአታቸውን እና የበሽታ መከላከል አቅምን የሚቀንሱ እንደ ሱስ ያሉ ልምዶችን በፍጥነት ማቆም እና የኮሮና ቫይረስን ለመከላከል የሚመከሩ እርምጃዎችን ሳያወላውሉ መፈፀም አለባቸው›› እንደ ቤዛዊት ገለጻ።
Via Addis Maleda
@YeneTube @FikerAssefa
ኬንያ ከካርጎ ውጭ ያሉትን ሁሉንም አለምአቀፍ በረራዎች አቋርጣለች። በዛሬው እለት በሀገሪቱ 8 አዲስ ተጠቂዎች የተመዘገቡ ሲሆን ከ20- 57 እድሜ ክልል ውስጥ ያሉ ናቸው። ከሰው ጋር በተያያዘ ባሮች ላልተወሰነ ጊዜ እንዲዘጉ የተወሰነ ሲሆን የቀብር ስነ ስርዓቶች የቅርብ ዘመዶች ብቻ በተገኙበት እንዲፈጸም ተወስኗል።
@YeneTube @FikerAssefa
@YeneTube @FikerAssefa
በምዕራብ አርሲ ዞን ከወትሮ የተለየ በረዶ ጣለ!
በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ አርሲ ዞን ወቅቱን ያልጠበቀ እና ከወትሮ የተለየ በረዶ ጣለ።ከወትሮ የተለየ በረዶው ምዕራብ አርሲ ዞን ኮፈሌ ወረዳ አሾካ ቀበሌ መጣሉን የዞኑ የመንግስት ኮሙዪኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት አስታውቋል።በረዶው በአካባቢው ያለውን መንገድ እና መኖሪያ ቤቶች መሸፈኑም ነው የተገለፀው።በአካባቢው የጣለው በረዶም የትራፊክ እንቅስቃሴውን እያስተጓጎለ መሆኑን የገለፀው ጽህፈት ቤቱ፤ አሽከርካሪዎች በስፍራው ላይ በጥንቃቄ እንዲያሽከረክሩም አሳስቧል።
Via FBC
@YeneTube @FikerAssefa
በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ አርሲ ዞን ወቅቱን ያልጠበቀ እና ከወትሮ የተለየ በረዶ ጣለ።ከወትሮ የተለየ በረዶው ምዕራብ አርሲ ዞን ኮፈሌ ወረዳ አሾካ ቀበሌ መጣሉን የዞኑ የመንግስት ኮሙዪኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት አስታውቋል።በረዶው በአካባቢው ያለውን መንገድ እና መኖሪያ ቤቶች መሸፈኑም ነው የተገለፀው።በአካባቢው የጣለው በረዶም የትራፊክ እንቅስቃሴውን እያስተጓጎለ መሆኑን የገለፀው ጽህፈት ቤቱ፤ አሽከርካሪዎች በስፍራው ላይ በጥንቃቄ እንዲያሽከረክሩም አሳስቧል።
Via FBC
@YeneTube @FikerAssefa
በጣሊያን ዛሬ 5,560 ሰዎች በቫይረሱ የተጠቁ ሲሆን 651 ሰዎች በቫይረሱ ምክንያት ሞተዋል። በአጠቃላይ ጣሊያን 59,138 በቫይረሱ የተጠቁ ሰዎች ሲኖሩ በኮሮና ቫይረስ ምክንያት እስከ ዛሬ በጣሊያን 5,476 ሰው ሞቷል።
@Yenetube @Fikerassefa
@Yenetube @Fikerassefa
በባህርዳር ከተማ የኮሮና ቫይረስ ለመከላከል የተቋቋመው ግብረ ሀይል በከተማው ስብሰባ ማካሄድን ከልክሏል። በመጠጥ ቤቶች፣ ምሸት ቤቶች፣አዝማሪ ቤቶች፣ ውስኪ ቤቶች ውሰጥ በጋራ ተሠብስቦ መጠጣት ሆነ ከፍቶ አገልግሎት መስጠትንም ከልክሏል።
ምሽት ላይ መንገድ ዳር ቁሞ መገኘትን ከልክሏል። ስፖርት ቤቶች እና መዋኛ ቦታዎች አገልግሎት እንዳይሰጡም ከልክሏል። መንገድ ላይ መጫዎትንም ከልክሏል።
#ElU
@Yenetube @Fikerassefa
ምሽት ላይ መንገድ ዳር ቁሞ መገኘትን ከልክሏል። ስፖርት ቤቶች እና መዋኛ ቦታዎች አገልግሎት እንዳይሰጡም ከልክሏል። መንገድ ላይ መጫዎትንም ከልክሏል።
#ElU
@Yenetube @Fikerassefa
#Update
ሁሉም የአበባ እርሻ ድርጅቾት ወደ አውሮፓ (በተለይም ሆላንድ)የሚላኩ አበባዎች በመቆማቸው ምክንያት 50,000 የሚጠጉ ሰራተኞች ስራ ሊያቆሙ እንደሚችሉ ተነግሯል ይህ የሆነው ኮሮና ቫይረስ በአውሮፓ በከፍተኛ መጠን በመስፋፋቱ ነው።
@Yenetube @Fikerassefa
ሁሉም የአበባ እርሻ ድርጅቾት ወደ አውሮፓ (በተለይም ሆላንድ)የሚላኩ አበባዎች በመቆማቸው ምክንያት 50,000 የሚጠጉ ሰራተኞች ስራ ሊያቆሙ እንደሚችሉ ተነግሯል ይህ የሆነው ኮሮና ቫይረስ በአውሮፓ በከፍተኛ መጠን በመስፋፋቱ ነው።
@Yenetube @Fikerassefa
የጀርመኗ መራሂተ መንግሥት አንጌላ ሜርክል በቫይረሱ ከተያዘ ዶክተር ጋር መገናኘታቸውን ተከትሎ ወደ ለይቶ ማቆያ ክፍል ገብተዋል።
@YeneTube @FikerAssefa
@YeneTube @FikerAssefa
Forwarded from HEY Online Market
iPhone 11 (New)
Condition : Packed
Storage: 64GB
Color: Grey
💵Price 32,000
Contact us
0953964175 @Heymobile
0925927457
091069510
Condition : Packed
Storage: 64GB
Color: Grey
💵Price 32,000
Contact us
0953964175 @Heymobile
0925927457
091069510
Forwarded from SCHOOL OF AMERICAN ENGLISH(DEUTSCH)
Join our channel and keep learning American English Beginners- Advanced
Communicative English
General English
English for Specific Purpose
Social English
Business English
TOEFL IELTS SAT GMAT GRE KET
Morning Sessions
Afternoon Sessions
Night Sessions
Weekend Sessions
Flexible Sessions
Group Classes/ Mini Group/Private/ VIP/
Report Writing
Thesis Writing
Academic Writing
Research Writing
Project Writing
Proposal Writing
Scholarship Consultation
USA Canada England China Europe
+251 921 309530
☑️ቻናላችንን ይቀላቀሉ።
👉https://tttttt.me/SCHOOLOFAMERICAN
Communicative English
General English
English for Specific Purpose
Social English
Business English
TOEFL IELTS SAT GMAT GRE KET
Morning Sessions
Afternoon Sessions
Night Sessions
Weekend Sessions
Flexible Sessions
Group Classes/ Mini Group/Private/ VIP/
Report Writing
Thesis Writing
Academic Writing
Research Writing
Project Writing
Proposal Writing
Scholarship Consultation
USA Canada England China Europe
+251 921 309530
☑️ቻናላችንን ይቀላቀሉ።
👉https://tttttt.me/SCHOOLOFAMERICAN
የኮሮና ቫይረስ ስርጭትን ለመከላከል የባቡር ትራንዚት አገልግሎት የተሳፋሪውን ቁጥር 50 በመቶ እንደሚቀንስ የትራንስፖርት ሚኒስቴር ገለጸ!
የኮሮና ቫይረስ ስርጭትን ለመከላከል የአዲስ አበባ ባቡር ትራንዚት አገልግሎት ከዛሬ ጀምሮ የተሳፋሪውን ቁጥር 50 በመቶ በመቀነስ አገልግሎት እንደሚሰጥ የትራንስፖርት ሚኒስትር ወ/ሮ ዳግማዊት ሞገስ ገልጸዋል፡፡ህዝቡ በሚሳፈርበበት ጊዜ ርቀት ጠብቆ በመቆም የበኩሉን አስተዋፆ እንዲያበረክትም ሚኒስትሯ ጥሪ አቅርበዋል፡፡
Via ETV
@YeneTube @FikerAssefa
የኮሮና ቫይረስ ስርጭትን ለመከላከል የአዲስ አበባ ባቡር ትራንዚት አገልግሎት ከዛሬ ጀምሮ የተሳፋሪውን ቁጥር 50 በመቶ በመቀነስ አገልግሎት እንደሚሰጥ የትራንስፖርት ሚኒስትር ወ/ሮ ዳግማዊት ሞገስ ገልጸዋል፡፡ህዝቡ በሚሳፈርበበት ጊዜ ርቀት ጠብቆ በመቆም የበኩሉን አስተዋፆ እንዲያበረክትም ሚኒስትሯ ጥሪ አቅርበዋል፡፡
Via ETV
@YeneTube @FikerAssefa
"ከዛሬ ጀምሮ በተወሰነው መሰረት
በተለያየ መንገድ፣ ለተለያየ ጉዳይ ከኢትዮጵያ ውጭ የነበሩ ወገኖቻችን ወደ ኅብረተሰቡ ከመቀላቀላቸው በፊት ሁለት ሳምንታት ለየት ብለው የሚቆዩባቸውን ስፍራዎች አሰናድተናል።በተለይም ለቆይታ ጊዜው ወጪያቸውን ለመሸፈን ለማይችሉ ዜጎቻችን ሙሉ ወጪያቸውን እኛ እንሸፍናለን።"
-ም/ል ከንቲባ ታከለ ኡማ
@YeneTube @FikerAssefa
በተለያየ መንገድ፣ ለተለያየ ጉዳይ ከኢትዮጵያ ውጭ የነበሩ ወገኖቻችን ወደ ኅብረተሰቡ ከመቀላቀላቸው በፊት ሁለት ሳምንታት ለየት ብለው የሚቆዩባቸውን ስፍራዎች አሰናድተናል።በተለይም ለቆይታ ጊዜው ወጪያቸውን ለመሸፈን ለማይችሉ ዜጎቻችን ሙሉ ወጪያቸውን እኛ እንሸፍናለን።"
-ም/ል ከንቲባ ታከለ ኡማ
@YeneTube @FikerAssefa
ለእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችና ሠራተኞች በሙሉ
የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የCOVID-19 ወረርሽኝ የመከላከል ግብረ-ሃይል ዛሬ ባካሄደው አስቸኳይ ስብሰባ ያለፉ ቀናት ስራውን ገምግሞ፤ ክፍተቶችን ለመሙላትና የመከላከል ስራውን ውጤታማ ለማድረግ የሚከተሉትን ውሳኔዎች አሳልፏል፡፡
1ኛ. ከሰኞ መጋቢት 14/2012 ዓ.ም ጀምሮ ተማሪዎች በማንኛውም ጉዳይ ከዩኒቨርሲቲው ግቢ መውጣት አይችሉም፡፡ ውጭ ለሚመገቡ (non-cafe) ተማሪዎች ዩኒቨርሲቲው የምግብ አገልግሎት ይሰጣል፡፡
2ኛ. ከግቢ ውጭ የምትኖሩ ተማሪዎች እስከ ነገ መጋቢት 14/2012 ዓ.ም ከቀኑ 12፡00 ሰዐት ድረስ እንድትገቡ፤ ከተቀመጠው ቀንና ሰዐት ውጪ የሚመጡ ተማሪዎችን ዩኒቨርስቲው አያስተናግድም።
3ኛ. ከወረርሽኙ ስራ ጋር የተያያዘ ካልሆነ ከዩኒቨርሲቲው ሠራተኞች ውጪ ማንኛውም ባለጉዳይ ላልተወሰነ ጊዜ ወደ ዩኒቨርሲቲው ቅጥር ግቢ መግባት ተከልክሏል፡፡ አስቸኳይ ለሆኑ ጉዳዮች የሚመለከተውን አካል በተለያዩ መገናኛ ዘዴዎች ማግኘት እንደምትችሉ እንገልጻለን፡፡
4ኛ. ሁሉም የዩኒቨርሲቲው ሰራተኛ ለውሳኔው ተፈጻሚነት የሚጠበቅበትን አስተዋፅኦ እንዲያደርግ እንዲሁም በግብረ-ሃይሉ የሚሰጡ የመከላከል የጥንቃቄ መልእክቶችን በመተግበር ራሱንና ማህበረሰቡን ከወረርሽኙ እንዲከላከል ጥሪ እናቀርባለን፡፡
-የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የCOVID-19 ወረርሽኝ የመከላከል ግብረ-ሃይል
@YeneTube @FikerAssefa
የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የCOVID-19 ወረርሽኝ የመከላከል ግብረ-ሃይል ዛሬ ባካሄደው አስቸኳይ ስብሰባ ያለፉ ቀናት ስራውን ገምግሞ፤ ክፍተቶችን ለመሙላትና የመከላከል ስራውን ውጤታማ ለማድረግ የሚከተሉትን ውሳኔዎች አሳልፏል፡፡
1ኛ. ከሰኞ መጋቢት 14/2012 ዓ.ም ጀምሮ ተማሪዎች በማንኛውም ጉዳይ ከዩኒቨርሲቲው ግቢ መውጣት አይችሉም፡፡ ውጭ ለሚመገቡ (non-cafe) ተማሪዎች ዩኒቨርሲቲው የምግብ አገልግሎት ይሰጣል፡፡
2ኛ. ከግቢ ውጭ የምትኖሩ ተማሪዎች እስከ ነገ መጋቢት 14/2012 ዓ.ም ከቀኑ 12፡00 ሰዐት ድረስ እንድትገቡ፤ ከተቀመጠው ቀንና ሰዐት ውጪ የሚመጡ ተማሪዎችን ዩኒቨርስቲው አያስተናግድም።
3ኛ. ከወረርሽኙ ስራ ጋር የተያያዘ ካልሆነ ከዩኒቨርሲቲው ሠራተኞች ውጪ ማንኛውም ባለጉዳይ ላልተወሰነ ጊዜ ወደ ዩኒቨርሲቲው ቅጥር ግቢ መግባት ተከልክሏል፡፡ አስቸኳይ ለሆኑ ጉዳዮች የሚመለከተውን አካል በተለያዩ መገናኛ ዘዴዎች ማግኘት እንደምትችሉ እንገልጻለን፡፡
4ኛ. ሁሉም የዩኒቨርሲቲው ሰራተኛ ለውሳኔው ተፈጻሚነት የሚጠበቅበትን አስተዋፅኦ እንዲያደርግ እንዲሁም በግብረ-ሃይሉ የሚሰጡ የመከላከል የጥንቃቄ መልእክቶችን በመተግበር ራሱንና ማህበረሰቡን ከወረርሽኙ እንዲከላከል ጥሪ እናቀርባለን፡፡
-የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የCOVID-19 ወረርሽኝ የመከላከል ግብረ-ሃይል
@YeneTube @FikerAssefa
ባህር ዳር ዩንቨርስቲ በተደጋጋሚ የተላኩ መረጃዎች #ጥንቃቄ ይደረግ:-
ባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ውስጥ ምንም እንኳን ለማንኛውም ተማሪ ከግቢ መውጣትም ሆነ መግባት ፈፅሞ የተከለከለ ቢሆንም አሁንም ድረስ ተማሪዎች ከግቢ በአጥር እየዘለሉ እየወጡ እና ተመልሰው እየገቡ እንደሚገኙ ተነግሮናል።
ከግቢ እንዳይወጡ ተከልክለው የተቀመጡ ተማሪዎች ላይ በአንዳንድ ተማሪዎች ምክንያት በሽታ ከውጭ ይዘው ዩኒቨርሲቲውን በሙሉ ሊበክሉ ስለሚችል የግቢ አስተዳደር በግቢው ቅጥር ዙርያ ከፍተኛ ቁጥጥር ጥበቃ ከዚህም በተጨማሪ አስተማሪ እርምጃ ሊወስድ ይገባዋል።
ከዚህም ሌላ የግቢው አስተዳደር አሁንም ቢሆን በሩን ዘግቶት በግቢው ውስጥ ያለው ጥንቃቄ ግን በጣም አሳዛኝ ነው።
ለዚህም ዋነኛው ምክንያት በግቢው ውስጥ ያለው የምግብ ቤት እጥረት ሲሆን ተማሪዎች አሁንም ምግብ ለመግዛት ተፋፍገው እየተገፋፉ የሚህገኙበት ሁኔታ መኖሩ ነው።
ተጨማሪ የምግብ ቤት ሊከፈት እንዲሁም ያለው ላውንጅ በስነ ስርዓት አገግሎት ሊሰጥ እንደሚገባ ተማሪዎች ጠቁመዋል።
@Yenetube @FikerAssefa
ባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ውስጥ ምንም እንኳን ለማንኛውም ተማሪ ከግቢ መውጣትም ሆነ መግባት ፈፅሞ የተከለከለ ቢሆንም አሁንም ድረስ ተማሪዎች ከግቢ በአጥር እየዘለሉ እየወጡ እና ተመልሰው እየገቡ እንደሚገኙ ተነግሮናል።
ከግቢ እንዳይወጡ ተከልክለው የተቀመጡ ተማሪዎች ላይ በአንዳንድ ተማሪዎች ምክንያት በሽታ ከውጭ ይዘው ዩኒቨርሲቲውን በሙሉ ሊበክሉ ስለሚችል የግቢ አስተዳደር በግቢው ቅጥር ዙርያ ከፍተኛ ቁጥጥር ጥበቃ ከዚህም በተጨማሪ አስተማሪ እርምጃ ሊወስድ ይገባዋል።
ከዚህም ሌላ የግቢው አስተዳደር አሁንም ቢሆን በሩን ዘግቶት በግቢው ውስጥ ያለው ጥንቃቄ ግን በጣም አሳዛኝ ነው።
ለዚህም ዋነኛው ምክንያት በግቢው ውስጥ ያለው የምግብ ቤት እጥረት ሲሆን ተማሪዎች አሁንም ምግብ ለመግዛት ተፋፍገው እየተገፋፉ የሚህገኙበት ሁኔታ መኖሩ ነው።
ተጨማሪ የምግብ ቤት ሊከፈት እንዲሁም ያለው ላውንጅ በስነ ስርዓት አገግሎት ሊሰጥ እንደሚገባ ተማሪዎች ጠቁመዋል።
@Yenetube @FikerAssefa
ወደ ኢትዮጵያ የሚገቡ መንገደኞች የ14 ቀናት የለይቶ ማቆያ ግዴታ ዛሬ ይጀመራል
ወደ ኢትዮጵያ በሚመጡ ሁሉም መንገደኞች ላይ ተፈፃሚ የሚሆነው የ14 ቀናት በልዩ ማቆያ ማዕከል የመቆየት ግዴታ ዛሬ እንደሚጀመር የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ።
ሚኒስቴሩ ወደ ኢትዮጵያ የሚገቡ መንገደኞች በስካይ ላይት እና ጊዮን ሆቴሎች ለ14 ቀናት ተለይተው ይቆያሉ ብሏል።
ቆይታቸውም በራሳቸው ወጪ የሚሸፈን ይሆናል።
ዲፕሎማቶች ደግሞ በኤምባሲዎቻቸው ተለይተው እንደሚቆዩ የጤና ሚኒስቴር ገልጿል።
የትራንዚት ተጓዦችም እስከ ቀጣዩ ጉዟቸው ድረስ በስካይ ላይት ሆቴል ተለይተው ይቆያሉም ነው የተባለው።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ 30 ሀገራት የሚያደርገውን በረራ በጊዜያዊነት ማቆሙ መግለፁ ይታወሳል።
- FBC
@Yenetube @FikerAssefa
ወደ ኢትዮጵያ በሚመጡ ሁሉም መንገደኞች ላይ ተፈፃሚ የሚሆነው የ14 ቀናት በልዩ ማቆያ ማዕከል የመቆየት ግዴታ ዛሬ እንደሚጀመር የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ።
ሚኒስቴሩ ወደ ኢትዮጵያ የሚገቡ መንገደኞች በስካይ ላይት እና ጊዮን ሆቴሎች ለ14 ቀናት ተለይተው ይቆያሉ ብሏል።
ቆይታቸውም በራሳቸው ወጪ የሚሸፈን ይሆናል።
ዲፕሎማቶች ደግሞ በኤምባሲዎቻቸው ተለይተው እንደሚቆዩ የጤና ሚኒስቴር ገልጿል።
የትራንዚት ተጓዦችም እስከ ቀጣዩ ጉዟቸው ድረስ በስካይ ላይት ሆቴል ተለይተው ይቆያሉም ነው የተባለው።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ 30 ሀገራት የሚያደርገውን በረራ በጊዜያዊነት ማቆሙ መግለፁ ይታወሳል።
- FBC
@Yenetube @FikerAssefa
በኮሎምቢያ ማረሚያ ቤት ከኮሮና ቫይረስ ወረርሺኝ ጋር በተያያዘ በተቀሰቀሰ አመፅ ከ23 ሰዎች በላይ ሰዎች ለህልፈት መዳረጋቸው ተሰማ። አመፁ በመዲናዋ ቦጎታ በሚገኝ ትልቅ ማረሚያ ቤት ውስጥ የተነሳ ሲሆን፥ ከሞቱት በተጨማሪ 83 እስረኞች መቁሰላቸውን የሃገሪቱ ፍትህ ሚኒስትር አስታውቀዋል።
-FBC
@Yenetube @Fikerassefa
-FBC
@Yenetube @Fikerassefa
ዳሽን ባንክ የኮሮና ስርጭት የሚያስከትለውን ጫና ለመቀነስ የክፍያ ማሻሻያዎችን አደረገ!
ዳሽን ባንክ በአሁኑ ወቅት የዓለም ስጋት የሆነው የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ በአገሪቷ ኢኮኖሚ ላይ የሚያስከትለውን ጫና ለመቀነስ ከዛሬ ጀምሮ የተለያዩ የክፍያ ማሻሻያዎችን እንደሚያደርግ አስታወቀ። የዳሽን ባንክ ማርኬቲንግ እና የደንበኞች አገልግሎት ዳይሬክተር አቶ አስቻለው ታምሩ እንደገለፁት ባንኩ ቀድሞ ደንበኞች በኤቲኤም ያወጡ የነበረውን የገንዘብ መጠን ከአራት ሺህ ወደ አስር ሺህ ብር ያሳደገ መሆኑን ገልጸዋል።ደንበኞች ማንኛውንም ገንዘብ በሚያወጡበት ጊዜም የነበረው የአገልግሎት ክፍያ ሙሉ በሙሉ ነፃ መደረጉንም ተናግረዋል።
Via EPA
@YeneTube @FikerAssefa
ዳሽን ባንክ በአሁኑ ወቅት የዓለም ስጋት የሆነው የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ በአገሪቷ ኢኮኖሚ ላይ የሚያስከትለውን ጫና ለመቀነስ ከዛሬ ጀምሮ የተለያዩ የክፍያ ማሻሻያዎችን እንደሚያደርግ አስታወቀ። የዳሽን ባንክ ማርኬቲንግ እና የደንበኞች አገልግሎት ዳይሬክተር አቶ አስቻለው ታምሩ እንደገለፁት ባንኩ ቀድሞ ደንበኞች በኤቲኤም ያወጡ የነበረውን የገንዘብ መጠን ከአራት ሺህ ወደ አስር ሺህ ብር ያሳደገ መሆኑን ገልጸዋል።ደንበኞች ማንኛውንም ገንዘብ በሚያወጡበት ጊዜም የነበረው የአገልግሎት ክፍያ ሙሉ በሙሉ ነፃ መደረጉንም ተናግረዋል።
Via EPA
@YeneTube @FikerAssefa
በኮሮና ቫይረስ መከሰት ምክንያት በሸቀጦች ላይ ዋጋ የሚጨምሩ ነጋዴዎችን ንብረት እንደምትወርስ ኤርትራ አስጠነቀቀች፡፡
በኤርትራ ከኮሮና ቫይረስ ጋር በተያያዘ የፍጆታ ዕቃዎች ላይ ‘ምክንያታዊ ያልሆነ’ የዋጋ ጭማሪ መታየቱን የሀገሪቱ የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር አስታውቋል።በተለይም በአሥመራ ከተማ በእህል፣ ዘይት፣ ስኳርና የጽዳት ዕቃዎች ላይ የዋጋ ጭማሪ መስተዋሉን የገለጸው ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ድርጊቱ የሕዝቡን ኑሮ የሚጎዳ በመሆኑ ከባድ ርምጃ እንደሚወስድ አስጠንቅቋል።ተገቢ ያልሆነ የዋጋ ጭማሪ በሚያደርጉና ዕቃዎችን በሚደብቁ ነጋዴዎች ላይ የንግድ ፍቃድን ከመንጠቅ አንስቶ እስከ ንብረት መውረስ የሚደርስ ርምጃን እንደሚወስድም እንዳስታወቀ ቢቢሲ ዘግቧል።በኤርትራ አንድ ሰው በኮሮና ቫይረስ መያዙ ከሰሞኑ ተረጋግጧል፤ ግለሰቡ ከውጭ የገባ መሆኑም ታውቋል፡፡
Via AMMA
@YeneTube @FikerAssefa
በኤርትራ ከኮሮና ቫይረስ ጋር በተያያዘ የፍጆታ ዕቃዎች ላይ ‘ምክንያታዊ ያልሆነ’ የዋጋ ጭማሪ መታየቱን የሀገሪቱ የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር አስታውቋል።በተለይም በአሥመራ ከተማ በእህል፣ ዘይት፣ ስኳርና የጽዳት ዕቃዎች ላይ የዋጋ ጭማሪ መስተዋሉን የገለጸው ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ድርጊቱ የሕዝቡን ኑሮ የሚጎዳ በመሆኑ ከባድ ርምጃ እንደሚወስድ አስጠንቅቋል።ተገቢ ያልሆነ የዋጋ ጭማሪ በሚያደርጉና ዕቃዎችን በሚደብቁ ነጋዴዎች ላይ የንግድ ፍቃድን ከመንጠቅ አንስቶ እስከ ንብረት መውረስ የሚደርስ ርምጃን እንደሚወስድም እንዳስታወቀ ቢቢሲ ዘግቧል።በኤርትራ አንድ ሰው በኮሮና ቫይረስ መያዙ ከሰሞኑ ተረጋግጧል፤ ግለሰቡ ከውጭ የገባ መሆኑም ታውቋል፡፡
Via AMMA
@YeneTube @FikerAssefa
የዶ/ር ካትሪን ሐምሊን የቀብር ሥነ-ሥርዓት ዛሬ ይፈጸማል!
የኢትዮጵያ የፌስቱላ ሆስፒታል መሥራች የዶ/ር ካትሪን ሐምሊን የቀብር ሥነ-ሥርዓት በዛሬው ዕለት በጴጥሮስ ወጳውሎስ ቤተክርስቲያን ይፈጸማል። የዶክተር ካትሪን ሐምሊን ቤተሰቦች እና ወዳጅ ዘመዶች በተገኙበት በመኖሪያ ቤታቸው የአስከሬን ሽኝት እየተደረገ ነው።ዶክተር ካትሪን ሐምሊን በ96 ዓመታቸው መጋቢት 9 ቀን 2012 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸው ይታወሳል።
Via EBC
@YeneTube @FikerAssefa
የኢትዮጵያ የፌስቱላ ሆስፒታል መሥራች የዶ/ር ካትሪን ሐምሊን የቀብር ሥነ-ሥርዓት በዛሬው ዕለት በጴጥሮስ ወጳውሎስ ቤተክርስቲያን ይፈጸማል። የዶክተር ካትሪን ሐምሊን ቤተሰቦች እና ወዳጅ ዘመዶች በተገኙበት በመኖሪያ ቤታቸው የአስከሬን ሽኝት እየተደረገ ነው።ዶክተር ካትሪን ሐምሊን በ96 ዓመታቸው መጋቢት 9 ቀን 2012 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸው ይታወሳል።
Via EBC
@YeneTube @FikerAssefa