ዶክተር አሚር አማን በሥጦታ ያገኙትን 1 ሚሊዮን ብር ለሥራ ዕድል ፈጠራ ኮሚሽን አበረከቱ፡፡
የቀድሞው የጤና ሚኒስትር አሚር አማን (ዶክተር) ከኢትዮጵያ ጤና ክብካቤ 1 ሚሊዮን ብር ተበርክቶላቸዋል፡፡ለዶክተር አሚር ዕውቅናው የተሰጣቸው መንግስት ከግሉ ዘርፍ ጋር በቅርበትና በትብብር እንዲሠራና በዘርፉ መሻሻሎች እንዲመዘገቡ ላደረጉት አስተዋጽኦ እንደሆነ በምስጋናና ዕውቅና መርሀ ግብሩ ላይ ተገልጧል፡፡ለኢትዮጵያ የሥራ ዕድል ፈጠራ ኮሚሽን ያደረጉት የ 1 ሚሊዮን ብር ድጋፍም ሌሎች ባለሀብቶች እና ድርጅቶች ከሥራ ፈላጊዎች ጎን እንዲቆሙ ለማበረታታት እንደሚያስችል ታምኖበታል፡፡ ብዙዎቹ ዘርፉን ከደገፉ ደግሞ የመነሻ መሥሪያ ገንዘብ የሌላቸው ብዙ የጤና ሙያ ተመራቂዎች ሥራ እንዲፈጥሩና ማኅበረሰባቸውን እንዲያገለግሉ ያግዛል፡፡
በመርሃ ግብሩ ላይ መልዕክት ያስተላለፉት አሚር አማን (ዶክተር) የዕውቅና ሽልማቱ ለአንድ ሰው ሳይሆን በግሉ ዘርፍና በጤና ሚኒስቴር በኩል ለተጀመረው መልካም ግንኙነት የተሰጠ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ መንግሥት ባለበት የበጀት ውስንነት የተነሳ ሳይቀጥራቸው የሚቀሩ ባለሙያዎችን በመቅጠር የግሉ ዘርፍ እየፈጠረ ላለው የሥራ ዕድልም ምሥጋና አቅርበዋል፡፡የኢትዮጵያ የሥራ ዕድል ፈጠራ ኮሚሽን እስከ 2012 በጀት ዓመት ማገባደጃ ለ 3 ሚሊዮን ዜጎች የሥራ ዕድል ለመፍጠር ማቀዱ ይታወሳል፡፡
Via AMMA
@YeneTube @FikerAssefa
የቀድሞው የጤና ሚኒስትር አሚር አማን (ዶክተር) ከኢትዮጵያ ጤና ክብካቤ 1 ሚሊዮን ብር ተበርክቶላቸዋል፡፡ለዶክተር አሚር ዕውቅናው የተሰጣቸው መንግስት ከግሉ ዘርፍ ጋር በቅርበትና በትብብር እንዲሠራና በዘርፉ መሻሻሎች እንዲመዘገቡ ላደረጉት አስተዋጽኦ እንደሆነ በምስጋናና ዕውቅና መርሀ ግብሩ ላይ ተገልጧል፡፡ለኢትዮጵያ የሥራ ዕድል ፈጠራ ኮሚሽን ያደረጉት የ 1 ሚሊዮን ብር ድጋፍም ሌሎች ባለሀብቶች እና ድርጅቶች ከሥራ ፈላጊዎች ጎን እንዲቆሙ ለማበረታታት እንደሚያስችል ታምኖበታል፡፡ ብዙዎቹ ዘርፉን ከደገፉ ደግሞ የመነሻ መሥሪያ ገንዘብ የሌላቸው ብዙ የጤና ሙያ ተመራቂዎች ሥራ እንዲፈጥሩና ማኅበረሰባቸውን እንዲያገለግሉ ያግዛል፡፡
በመርሃ ግብሩ ላይ መልዕክት ያስተላለፉት አሚር አማን (ዶክተር) የዕውቅና ሽልማቱ ለአንድ ሰው ሳይሆን በግሉ ዘርፍና በጤና ሚኒስቴር በኩል ለተጀመረው መልካም ግንኙነት የተሰጠ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ መንግሥት ባለበት የበጀት ውስንነት የተነሳ ሳይቀጥራቸው የሚቀሩ ባለሙያዎችን በመቅጠር የግሉ ዘርፍ እየፈጠረ ላለው የሥራ ዕድልም ምሥጋና አቅርበዋል፡፡የኢትዮጵያ የሥራ ዕድል ፈጠራ ኮሚሽን እስከ 2012 በጀት ዓመት ማገባደጃ ለ 3 ሚሊዮን ዜጎች የሥራ ዕድል ለመፍጠር ማቀዱ ይታወሳል፡፡
Via AMMA
@YeneTube @FikerAssefa
የአብን ሥራ አስፈፃሚ አመራሮች፦
1. አቶ በለጠ ሞላ - ሊቀመንበር
2. አቶ የሱፍ ኢብራሂም - ም/ሊቀመንበር
3. አቶ አዲስ ኃረገወይን - የፖሊሲ ስትራቴጂ ኃላፊ
4. አቶ ጣሂር ሞሐመድ - የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ
5. ዶ/ር ቴዎድሮስ ኃ/ማርያም - የውጭ ጉዳይና ዓለማቀፍ ግንኙነት
6. አቶ ጋሻው መርሻ - የአደረጃጀት ጉዳይ ኃላፊ
7. አቶ መልካሙ ፀጋዬ - የፅሕፈት ቤት ኃላፊ
8. አቶ ጥበበ ሰይፈ - የሕግና ስነምግባር ኃላፊ
9. አቶ ክርስቲያን ታደለ - የፓለቲካ ጉዳዮች ኃላፊ ናቸው።
Via፦ አብን
@YeneTube @Fikerassefa
1. አቶ በለጠ ሞላ - ሊቀመንበር
2. አቶ የሱፍ ኢብራሂም - ም/ሊቀመንበር
3. አቶ አዲስ ኃረገወይን - የፖሊሲ ስትራቴጂ ኃላፊ
4. አቶ ጣሂር ሞሐመድ - የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ
5. ዶ/ር ቴዎድሮስ ኃ/ማርያም - የውጭ ጉዳይና ዓለማቀፍ ግንኙነት
6. አቶ ጋሻው መርሻ - የአደረጃጀት ጉዳይ ኃላፊ
7. አቶ መልካሙ ፀጋዬ - የፅሕፈት ቤት ኃላፊ
8. አቶ ጥበበ ሰይፈ - የሕግና ስነምግባር ኃላፊ
9. አቶ ክርስቲያን ታደለ - የፓለቲካ ጉዳዮች ኃላፊ ናቸው።
Via፦ አብን
@YeneTube @Fikerassefa
ዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ ከአብን ሊቀመንበርነት በአቶ በለጠ ሞላ ስለመተካታቸው ከነገሩኝ:
"በቅርቡ ሪፎርም እያረግን ነበር፣ አንዱ ዋናው የሪፎርሙ አካል ደግሞ ተቋማዊ ለውጥ ማድረግ ነበር። ሁለተኛው ደግሞ አዲስ የስራ አስፈፃሚ አባላትን መምረጥ ነበር። እኔ በሊቀመንበርነት ያገለገልኩበት ሁለት አመት በቂ ነው ብዬ አስባለሁ። በአዲስ መንፈስ ስራ ሊሰራ የሚችል አዲስ አመራር እንዲመረጥ አድርገናል። ይህ በግል ፈቃዴ የተደረገ ነው። ፓርቲው ውስጥ አሁንም የማእከላዊ ኮሚቴ አባል ነኝ፣ በአባልነቴም እቀጥላለሁ።"
Via:- eliasmeseret
@YeneTube @Fikerassefa
"በቅርቡ ሪፎርም እያረግን ነበር፣ አንዱ ዋናው የሪፎርሙ አካል ደግሞ ተቋማዊ ለውጥ ማድረግ ነበር። ሁለተኛው ደግሞ አዲስ የስራ አስፈፃሚ አባላትን መምረጥ ነበር። እኔ በሊቀመንበርነት ያገለገልኩበት ሁለት አመት በቂ ነው ብዬ አስባለሁ። በአዲስ መንፈስ ስራ ሊሰራ የሚችል አዲስ አመራር እንዲመረጥ አድርገናል። ይህ በግል ፈቃዴ የተደረገ ነው። ፓርቲው ውስጥ አሁንም የማእከላዊ ኮሚቴ አባል ነኝ፣ በአባልነቴም እቀጥላለሁ።"
Via:- eliasmeseret
@YeneTube @Fikerassefa
በአማራ ክልል አዊ ዞን ጃዊ ወረዳ ሰዋታምፕ ቀበሌ 2ሕጻናትን ይዘው ለማስለቀቂያ 400 ሺህ ብር የተጠየቁ ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር ማዋሉን የወረዳው ፓሊስ አስታወቀ። ሕጻናቱም በሰላም ተለቀዋል።
@YeneTube @Fikerassefa
@YeneTube @Fikerassefa
የትግራይ ክልል መንግስት የቀድሞ ጠቅላይ ሚንስትሮች መለስ ዜናዊ እና ሀይለማሪያም ደሳለኝ የምጣኔ ሀብት አማካሪ በነበሩት አቶ ነዋይ ገብረዓብ ሞት የተሰማውን ሀዘን ገለጸ። አቶ ነዋይ በህክምና ሲረዱ ቆይተው ዛሬ ማለዳ አርፈዋል።
#ELU
@YeneTube @Fikerassefa
#ELU
@YeneTube @Fikerassefa
ምርጫ ቦርድ የፓለቲካ ፓርቲዎች ማሟላት የሚገባቸውን ዝርዝር ጉዳዮች እስከ መጋቢት 3 እንዲያሟሉ አሳሰበ!
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የፖለቲካ ፓርቲዎች ሟሟላት የሚገባቸውን ዝርዝር ጉዳዮች እስከ መጋቢት 3 ቀን 2012 ዓ.ም እንዲያሟሉ አሳሰበ።በፓለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና ምርጫ አዋጅ ቁጥር 1162/2011 መሰረት በቦርዱ ሀገር አቀፍ እና የክልል ፓርቲዎች ማሟሟላት ያለባቸው ግዴታ ለማስፈጸም የወጣው መመሪያ ቁጥር 3/2012 መሰረት የፓለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባ ማሟላት የሚገባቸውን ዝርዝር ሁኔታ የሚያስረዱ ሰነዶች ማዘጋጀቱ እና ለፓርቲዎች እንዲደርሳቸው ማድረጉ አስታውሷል፡፡ለእያንዳንዱ ፓርቲም በደብዳቤ ሟሟላት የሚገባቸውን ሁኔታዎች ሁሉ እስከ መጋቢት 03 ቀን 2012 ዓ.ም ድረስ አሟልተው እንዲያቀርቡ ቦርዱ እንዳስታወቀ ተጠቁሟል።ሆኖም እስከአሁን ሰነዶቻቸውን ያስገቡ ፓርቲዎች ቁጥር ዝቅተኛ መሆኑን ቦርዱ በዛሬው ዕለት ገልጿል።በመሆኑም ሟሟላት የሚጠበቅባቸው ዝርዝር ሁኔታዎችን የሚያስረዱ ሰነዶች የደረሳቸው የፓለቲካ ፓርቲዎች በሙሉ መጋቢት 3 ቀን 2012 ከመድረሱ በፊት ሟሟላት የሚገባቸውን በሙሉ አሟልተው የምዝገባ ስርአቱን እንዲጀምሩ አሳስቧል።
Via FBC
@YeneTube @FikerAssefa
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የፖለቲካ ፓርቲዎች ሟሟላት የሚገባቸውን ዝርዝር ጉዳዮች እስከ መጋቢት 3 ቀን 2012 ዓ.ም እንዲያሟሉ አሳሰበ።በፓለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና ምርጫ አዋጅ ቁጥር 1162/2011 መሰረት በቦርዱ ሀገር አቀፍ እና የክልል ፓርቲዎች ማሟሟላት ያለባቸው ግዴታ ለማስፈጸም የወጣው መመሪያ ቁጥር 3/2012 መሰረት የፓለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባ ማሟላት የሚገባቸውን ዝርዝር ሁኔታ የሚያስረዱ ሰነዶች ማዘጋጀቱ እና ለፓርቲዎች እንዲደርሳቸው ማድረጉ አስታውሷል፡፡ለእያንዳንዱ ፓርቲም በደብዳቤ ሟሟላት የሚገባቸውን ሁኔታዎች ሁሉ እስከ መጋቢት 03 ቀን 2012 ዓ.ም ድረስ አሟልተው እንዲያቀርቡ ቦርዱ እንዳስታወቀ ተጠቁሟል።ሆኖም እስከአሁን ሰነዶቻቸውን ያስገቡ ፓርቲዎች ቁጥር ዝቅተኛ መሆኑን ቦርዱ በዛሬው ዕለት ገልጿል።በመሆኑም ሟሟላት የሚጠበቅባቸው ዝርዝር ሁኔታዎችን የሚያስረዱ ሰነዶች የደረሳቸው የፓለቲካ ፓርቲዎች በሙሉ መጋቢት 3 ቀን 2012 ከመድረሱ በፊት ሟሟላት የሚገባቸውን በሙሉ አሟልተው የምዝገባ ስርአቱን እንዲጀምሩ አሳስቧል።
Via FBC
@YeneTube @FikerAssefa
የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ምርጫው እንዲራዘም ጠየቀ!
የኢትዮጽያ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ምርጫ 2012ትን በተመለከተ በሰጠዉ መግለጫ ምርጫዉ እንዲራዘም መወሰኑን አስታወቀ።ምክር ቤቱ “ከምርጫ የአገር ህልዉና ይቅደም” በሚል ርዕስ አርብ የካቲት 13/2012 በሰጠዉ ጋዜጣዊ መግለጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች በጋራ ባደረጉት ዉይይት ምርጫዉ መራዘም አለበት ሲሉ በአብላጫ ድምፅ መወሰናቸዉን አስታውቋል።ምክር ቤቱ የካቲት 7/2012 75 የፖለቲካ ፓርቲዎች በተገኙበት ባደረገው ውይይት ከአገር ህልዉና የምርጫ ሊቀድም ስለማይገባ፣ ፓርቲዎቹ ምርጫዉ ይራዘም የሚል ሐሳብ ማንፀባረቃቸውን ገልጿል።
Via Addis Maleda
@YeneTube @FikerAssefa
የኢትዮጽያ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ምርጫ 2012ትን በተመለከተ በሰጠዉ መግለጫ ምርጫዉ እንዲራዘም መወሰኑን አስታወቀ።ምክር ቤቱ “ከምርጫ የአገር ህልዉና ይቅደም” በሚል ርዕስ አርብ የካቲት 13/2012 በሰጠዉ ጋዜጣዊ መግለጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች በጋራ ባደረጉት ዉይይት ምርጫዉ መራዘም አለበት ሲሉ በአብላጫ ድምፅ መወሰናቸዉን አስታውቋል።ምክር ቤቱ የካቲት 7/2012 75 የፖለቲካ ፓርቲዎች በተገኙበት ባደረገው ውይይት ከአገር ህልዉና የምርጫ ሊቀድም ስለማይገባ፣ ፓርቲዎቹ ምርጫዉ ይራዘም የሚል ሐሳብ ማንፀባረቃቸውን ገልጿል።
Via Addis Maleda
@YeneTube @FikerAssefa
የከፍተኛ የኤሌክትሪክ መስመር ማሻሻያ ሥራ ለማከናወን የኃይል አቅርቦት በተወሰኑ አካባቢዎች ይቋረጣል።
በአዲስ አበባ ከተማ በአንዳንድ አካባቢዎች ለማሻሻያ ሥራ ሲባል የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት እንደሚቋረጥ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አስታወቋል ።
በዚሁ መሰረት
ነገ ማክሰኞ የካቲት 17 ቀን 2012 ዓ.ም ከጠዋቱ 2:00 እስከ ቀኑ 8:00 ሰዓት ድረስ፣
• በሳሪስ አቦ ቤ/ክ፣ በቦሌ ቡልቡላ ኮንዶሚኒየም፣ በቡልቡላ ማርያም ማዞርያ፣ በክሬሸር፣ በባሌስቴራ ፋብሪካ፣ በGW2 ውሃ፣ በአደይ አበባ፣ በሳሪስ አዲስ ሰፈር፣ በአዋሽ ቆዳ ፋብሪካ እና አካባቢዎቻቸው፣
እንዲሁም በተመሳሳይ ቀን ከጠዋቱ 1፡00 እስከ ቀኑ 10፡00 ስዓት ድረስ፣
• በጎላጎል ወደ መገናኛ፣ በገቢዎች፣ በቅዱስ ገብርኤል ሆስፒታል፣ በሻላ መናፈሻ፣ በቦሌ ጤና ጣቢያ፣ በመገናኛ በከፊል፣ በኢትዮፕላስቲክ፣ በየነገው ሰው ት/ቤት፣ በ17/24 ታክሲ ማዞርያ፣ በአዲሱ የወጣቶች ማዕከል ስታዲየም እና አካባቢዎቻቸው፣
ረቡዕ የካቲት 18 ቀን 2012 ዓ.ም ከጠዋቱ 2:00 እስከ ቀኑ 6:00 ሰዓት ድረስ፣
• በፈጥኖ ደራሽ፣ በኮልፌ ኮፕሪሄንሲፍ ት/ቤት፣ በደጉ ሆቴል፣ በታይዋን ገበያ፣ በኢትዮ ጠቢብ ሆስፒታል እና አካባቢዎቻቸው፣
በዚሁ ቀን በተመሳሳይ ከጠዋቱ 1፡00 እስከ ቀኑ 10፡00 ስዓት ድረስ፣
• በቦሌ መድሃኒያለም ቤ/ክ፣ በአያት ሆስፒታል፣ በብራስ ሆስፒታል፣ በሚሊኒየም አዳራሽ፣ በቦሌ ሚኒ፣ በኢትዮፕላስቲክ፣ በየነገው ሰው ት/ቤት፣ በ17/24 ታክሲ ማዞርያ፣ በአዲሱ የወጣቶች ማዕከል ስታዲየም እና አካባቢዎቻቸው፣
በከፍተኛ የኤሌክትሪክ መስመር ላይ የማሻሻያ ሥራ ለማከናወን ሲባል የኃይል አቅርቦት የሚቋረጥ በመሆኑ ነዋሪዎች እና ደንበኞች ከወዲሁ አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት እንዲያደርጉ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አሳስቧል ፡፡
Via:- Addis Ababa City administration
@Yenetube @Fikerassefa
በአዲስ አበባ ከተማ በአንዳንድ አካባቢዎች ለማሻሻያ ሥራ ሲባል የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት እንደሚቋረጥ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አስታወቋል ።
በዚሁ መሰረት
ነገ ማክሰኞ የካቲት 17 ቀን 2012 ዓ.ም ከጠዋቱ 2:00 እስከ ቀኑ 8:00 ሰዓት ድረስ፣
• በሳሪስ አቦ ቤ/ክ፣ በቦሌ ቡልቡላ ኮንዶሚኒየም፣ በቡልቡላ ማርያም ማዞርያ፣ በክሬሸር፣ በባሌስቴራ ፋብሪካ፣ በGW2 ውሃ፣ በአደይ አበባ፣ በሳሪስ አዲስ ሰፈር፣ በአዋሽ ቆዳ ፋብሪካ እና አካባቢዎቻቸው፣
እንዲሁም በተመሳሳይ ቀን ከጠዋቱ 1፡00 እስከ ቀኑ 10፡00 ስዓት ድረስ፣
• በጎላጎል ወደ መገናኛ፣ በገቢዎች፣ በቅዱስ ገብርኤል ሆስፒታል፣ በሻላ መናፈሻ፣ በቦሌ ጤና ጣቢያ፣ በመገናኛ በከፊል፣ በኢትዮፕላስቲክ፣ በየነገው ሰው ት/ቤት፣ በ17/24 ታክሲ ማዞርያ፣ በአዲሱ የወጣቶች ማዕከል ስታዲየም እና አካባቢዎቻቸው፣
ረቡዕ የካቲት 18 ቀን 2012 ዓ.ም ከጠዋቱ 2:00 እስከ ቀኑ 6:00 ሰዓት ድረስ፣
• በፈጥኖ ደራሽ፣ በኮልፌ ኮፕሪሄንሲፍ ት/ቤት፣ በደጉ ሆቴል፣ በታይዋን ገበያ፣ በኢትዮ ጠቢብ ሆስፒታል እና አካባቢዎቻቸው፣
በዚሁ ቀን በተመሳሳይ ከጠዋቱ 1፡00 እስከ ቀኑ 10፡00 ስዓት ድረስ፣
• በቦሌ መድሃኒያለም ቤ/ክ፣ በአያት ሆስፒታል፣ በብራስ ሆስፒታል፣ በሚሊኒየም አዳራሽ፣ በቦሌ ሚኒ፣ በኢትዮፕላስቲክ፣ በየነገው ሰው ት/ቤት፣ በ17/24 ታክሲ ማዞርያ፣ በአዲሱ የወጣቶች ማዕከል ስታዲየም እና አካባቢዎቻቸው፣
በከፍተኛ የኤሌክትሪክ መስመር ላይ የማሻሻያ ሥራ ለማከናወን ሲባል የኃይል አቅርቦት የሚቋረጥ በመሆኑ ነዋሪዎች እና ደንበኞች ከወዲሁ አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት እንዲያደርጉ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አሳስቧል ፡፡
Via:- Addis Ababa City administration
@Yenetube @Fikerassefa
የዙምባብዌ ቢሊየነር ከኢትዮ ቴሎኮም ፈቃድ ለማግኘት እየተንቀሳቀሱ ነው
በዙምባብዌው ቢሊየነር ስትራይቭ ማሲያዋ ባለቤትነት የሚተዳደረው ኢኮኔት ግሎባል የተባለው ኩባንያ በኢትዮጵያ የቴሌኮም አገልግሎት ለመስጠት ከኢትዮ ቴሎኮም ፈቃድ ለማግኝት እየተንቀሳቀሰ መሆኑን ብሉምበርግ ዘገበ፡፡
#addisMaleda
@YeneTube @Fikerassefa
በዙምባብዌው ቢሊየነር ስትራይቭ ማሲያዋ ባለቤትነት የሚተዳደረው ኢኮኔት ግሎባል የተባለው ኩባንያ በኢትዮጵያ የቴሌኮም አገልግሎት ለመስጠት ከኢትዮ ቴሎኮም ፈቃድ ለማግኝት እየተንቀሳቀሰ መሆኑን ብሉምበርግ ዘገበ፡፡
#addisMaleda
@YeneTube @Fikerassefa
በተለያዩ ምክንያቶች በእሥር ላይ የሚገኙ ግለሰቦች ክስ እንዲቋረጥ መንግሥት ወሰነ።
በተለያዩ ምክንያቶች በእሥር ላይ የሚገኙ ግለሰቦች ክስ እንዲቋረጥ መንግሥት መወሰኑን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ፕረስ ሴክሬታሪ ኃላፊ ንጉሱ ጥላሁን አስታውቀዋል። በሀገሪቱ የሰው ህይወት መጥፋት፣ ግጭት፣ መፈናቀል እና የሀይማኖት ተቋማት ላይ ጥቃት መከሰቱን ያወሱት የጽህፈት ቤት ኃላፊው በእነዚህ ሁኔታዎች መረጃ የተገኘባቸው 1 ሺህ 682 ሰዎች በቁጥጥር ሥር ሆነው ጉዳያቸው እየታየ መሆኑን አስታውቀዋል።
ከሙስናና በህገ ወጥ መንገድ ከማዘዋወር ጋር በተያያዘ ደግሞ 470 ሚሊዮን 6 መቶ ሺህ ብር ታግዶ ጉዳዩ እየታየ እንደሆነም ነው የገለጹት። ይሁን እንጂ በታጋሽነት እና የፖለቲካ ምኅዳሩን ለማስፋት ሲል የተወሰኑት ክስ እንዲቋረጥ መንግሥት መወሰኑን ነው አቶ ንጉሱ የተናገሩት። በዚህም መሠረት የ60 ሰዎች ክስ ማቋረጡን ገልጸዋል። ክሳቸው የተቋረጠላቸው በየትኛው አግባብ፣ በምን ሁኔታ፣ እነማን እንደሆኑ እና ሌሎች ዝርዝር ጉዳዮችን በተመለከተ ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ ነገ ማብራሪያ እንደሚሰጥም አስታውቀዋል።በለውጡ ሂደት ብቻ 43 ሺህ 531 ዜጎች ምሕረት እንደተደረገላቸውም አቶ ንጉሱ አስታውሰዋል።
Via AMMA
@YeneTube @FikerAssefa
በተለያዩ ምክንያቶች በእሥር ላይ የሚገኙ ግለሰቦች ክስ እንዲቋረጥ መንግሥት መወሰኑን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ፕረስ ሴክሬታሪ ኃላፊ ንጉሱ ጥላሁን አስታውቀዋል። በሀገሪቱ የሰው ህይወት መጥፋት፣ ግጭት፣ መፈናቀል እና የሀይማኖት ተቋማት ላይ ጥቃት መከሰቱን ያወሱት የጽህፈት ቤት ኃላፊው በእነዚህ ሁኔታዎች መረጃ የተገኘባቸው 1 ሺህ 682 ሰዎች በቁጥጥር ሥር ሆነው ጉዳያቸው እየታየ መሆኑን አስታውቀዋል።
ከሙስናና በህገ ወጥ መንገድ ከማዘዋወር ጋር በተያያዘ ደግሞ 470 ሚሊዮን 6 መቶ ሺህ ብር ታግዶ ጉዳዩ እየታየ እንደሆነም ነው የገለጹት። ይሁን እንጂ በታጋሽነት እና የፖለቲካ ምኅዳሩን ለማስፋት ሲል የተወሰኑት ክስ እንዲቋረጥ መንግሥት መወሰኑን ነው አቶ ንጉሱ የተናገሩት። በዚህም መሠረት የ60 ሰዎች ክስ ማቋረጡን ገልጸዋል። ክሳቸው የተቋረጠላቸው በየትኛው አግባብ፣ በምን ሁኔታ፣ እነማን እንደሆኑ እና ሌሎች ዝርዝር ጉዳዮችን በተመለከተ ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ ነገ ማብራሪያ እንደሚሰጥም አስታውቀዋል።በለውጡ ሂደት ብቻ 43 ሺህ 531 ዜጎች ምሕረት እንደተደረገላቸውም አቶ ንጉሱ አስታውሰዋል።
Via AMMA
@YeneTube @FikerAssefa
ሊደመጥ የሚገባው!!! ሕውሓት ከብልፅግና ጋር ሊመክር እንደሆነ ተሰምቷል። ለዚው ጉዳይ ኮሚቴም መቋቋሙ ታውቋል ⬇️
https://youtu.be/wUI0T0oRfDM
https://youtu.be/wUI0T0oRfDM
YouTube
Ethiopia : ሰበር መረጃ ፡ ህውሃት እና ብልጽግና ፓርቲ እርቅ ለመፍጠር ኮሚቴ አቋቋሙ
We are YeneTube official subscribe us for more videos and to enjoy!
ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በዘንድሮው ጠቅላላ #ምርጫ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤትና ለክልል ምክር ቤቶች የሚያቀርባቸውን ዕጩዎች ለመለየት የቅድመ ዕጩ ምዝገባ መጀመሩን አስታወቀ፡፡ ፓርቲው የተወዳዳሪዎች ምልመላ መመሪያውንም ይፋ አድርጓል።
Via Ethiopia Election
@YeneTube @FikerAssefa
Via Ethiopia Election
@YeneTube @FikerAssefa
በምዕራብና ደቡብ ኦሮሚያ አካባቢዎች አንጻራዊ ሰላም እየታየ መምጣቱን የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ!
በምዕራብና ደቡብ ኦሮሚያ አካባቢዎች ተከስቶ የነበረው የጸጥታ ችግር በፀጥታ ሃይሉ በተወሰዱ እርምጃዎች አንጻራዊ ሰላም እየታየበት መምጣቱን የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ።በደቡብና በምዕራብ ኦሮሚያ በሚገኙ የተለያዩ አካባቢዎች ግጭቶችና የጸጥታ ችግሮች መታየት ከጀመሩ ሰነባብቷል።
የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጀነራል አራርሳ መርዳሳ እንዳሉት፥ በአካባቢው የለውጥ እንቅስቃሴውን ለማደናቀፍ ላለፈው አንድ ዓመት የታጠቁ ሃይሎች ችግር ሲፈጥሩ ቆይተዋል።
እነዚህ ሀይሎች በአካባቢው የመንግስት የሥራ ኃላፊዎችና የጸጥታ አካላትን እስከ በመግደል መድረስ በአካባቢው ማህበረሰብ ስጋት ፈጥሮ ቆይቷል።ታጣቂ ኃይሉ ባለሀብቶችን፣ ግለሰቦችን፣ የመንግስት አመራሮችና የጸጥታ ኃይል አባላትን ሳይቀር በመግደል በከተሞችና ገጠር አካባቢም በርካታ ጥፋቶችን አድርሷል።ሆኖም መንግስት ችግሮችን በውይይት ለመፍታት ጥረት ሲያደርግ ቢቆይም ሊሳካ ሳይችል መቅረቱን ያነሱ ሲሆን፥ መንግስትም የህግ የበላይነትን ለማስከበር ወደ እርምጃ መግባቱን ኮሚሽሩ ገልጸዋል።
በምዕራብ ወለጋ እና ቄለም ወለጋ ዞኖች፤ በደቡብ ኦሮሚያ ጉጂ እና ምዕራብ ጉጂ ዞኖች ታጣቂ ኃይሉ የሚንቀሳቀስባቸው ቦታዎች መሆናቸውንም ኮሚሽነሩ አመልክተዋል።በመሆኑም የመንግስት የጸጥታ አካላት ከህዝቡ ጋር በመተባበር በታጣቂ ቡድኑ ላይ በተወሰደው እርምጃ አሁን ላይ አንፃራዊ ሰላም እየታየ መሆኑን ገልጸዋል።ህብረተሰቡ ለጸጥታ አካላት እያደረገ ያለውን ትብብርም አጠናክሮ እንዲቀጥልም ኮሚሽነር ጀነራል አራርሳ ጥሪ አቅርበዋል።
ምንጭ፦ ኢዜአ
@YeneTube @FikerAssefa
በምዕራብና ደቡብ ኦሮሚያ አካባቢዎች ተከስቶ የነበረው የጸጥታ ችግር በፀጥታ ሃይሉ በተወሰዱ እርምጃዎች አንጻራዊ ሰላም እየታየበት መምጣቱን የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ።በደቡብና በምዕራብ ኦሮሚያ በሚገኙ የተለያዩ አካባቢዎች ግጭቶችና የጸጥታ ችግሮች መታየት ከጀመሩ ሰነባብቷል።
የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጀነራል አራርሳ መርዳሳ እንዳሉት፥ በአካባቢው የለውጥ እንቅስቃሴውን ለማደናቀፍ ላለፈው አንድ ዓመት የታጠቁ ሃይሎች ችግር ሲፈጥሩ ቆይተዋል።
እነዚህ ሀይሎች በአካባቢው የመንግስት የሥራ ኃላፊዎችና የጸጥታ አካላትን እስከ በመግደል መድረስ በአካባቢው ማህበረሰብ ስጋት ፈጥሮ ቆይቷል።ታጣቂ ኃይሉ ባለሀብቶችን፣ ግለሰቦችን፣ የመንግስት አመራሮችና የጸጥታ ኃይል አባላትን ሳይቀር በመግደል በከተሞችና ገጠር አካባቢም በርካታ ጥፋቶችን አድርሷል።ሆኖም መንግስት ችግሮችን በውይይት ለመፍታት ጥረት ሲያደርግ ቢቆይም ሊሳካ ሳይችል መቅረቱን ያነሱ ሲሆን፥ መንግስትም የህግ የበላይነትን ለማስከበር ወደ እርምጃ መግባቱን ኮሚሽሩ ገልጸዋል።
በምዕራብ ወለጋ እና ቄለም ወለጋ ዞኖች፤ በደቡብ ኦሮሚያ ጉጂ እና ምዕራብ ጉጂ ዞኖች ታጣቂ ኃይሉ የሚንቀሳቀስባቸው ቦታዎች መሆናቸውንም ኮሚሽነሩ አመልክተዋል።በመሆኑም የመንግስት የጸጥታ አካላት ከህዝቡ ጋር በመተባበር በታጣቂ ቡድኑ ላይ በተወሰደው እርምጃ አሁን ላይ አንፃራዊ ሰላም እየታየ መሆኑን ገልጸዋል።ህብረተሰቡ ለጸጥታ አካላት እያደረገ ያለውን ትብብርም አጠናክሮ እንዲቀጥልም ኮሚሽነር ጀነራል አራርሳ ጥሪ አቅርበዋል።
ምንጭ፦ ኢዜአ
@YeneTube @FikerAssefa
መንግሥት ማዳበርያ አስኪያስገባ አስመጪዎች የወደብ እንዲከፍሉ ተገደዱ!
ማዳበሪያውን ማስገባት ለሚቀጥሉት ኹለት ወራት ይቀጥላል የኢትዮጵያ መንግሥት 1.5 ሚሊዮን ቶን ማዳበሪያ እያስገባ መሆኑን ተከትሎ በጅቡቲ ወደብ በኩል ወደ ኢትዮጵያ ሊገቡ የነበሩ ኮንቴይነሮች የወደብ ኪራይ እየከፈሉ በጅቡቲ ወደብ እንዲቆዩ ተደርገዋል። ማንነታቸው እንዲገለፅ ያልፈለጉ በአስመጪ እና ላኪነት ሥራ ላይ የተሰማሩ ነጋዴዎች ለአዲስ ማለዳ እንደተናገሩት፣ ጅቡቲ ወደብ የደረሱት እቃዎች ወደ አገር ውስጥ እንዳይገቡ መደረግ ከተጀመረ ሦስት ሳምንት ሆኖታል። ይህም በመሆኑ ምክንያት ለከፍተኛ ወጪ እና ኪሳራ መዳረጋቸውን ገልጸዋል፡፡
Via Addis Maleda
@YeneTube @FikerAssefa
ማዳበሪያውን ማስገባት ለሚቀጥሉት ኹለት ወራት ይቀጥላል የኢትዮጵያ መንግሥት 1.5 ሚሊዮን ቶን ማዳበሪያ እያስገባ መሆኑን ተከትሎ በጅቡቲ ወደብ በኩል ወደ ኢትዮጵያ ሊገቡ የነበሩ ኮንቴይነሮች የወደብ ኪራይ እየከፈሉ በጅቡቲ ወደብ እንዲቆዩ ተደርገዋል። ማንነታቸው እንዲገለፅ ያልፈለጉ በአስመጪ እና ላኪነት ሥራ ላይ የተሰማሩ ነጋዴዎች ለአዲስ ማለዳ እንደተናገሩት፣ ጅቡቲ ወደብ የደረሱት እቃዎች ወደ አገር ውስጥ እንዳይገቡ መደረግ ከተጀመረ ሦስት ሳምንት ሆኖታል። ይህም በመሆኑ ምክንያት ለከፍተኛ ወጪ እና ኪሳራ መዳረጋቸውን ገልጸዋል፡፡
Via Addis Maleda
@YeneTube @FikerAssefa
በመጀመሪያው ግማሽ ዓመት በ1328 የትምህርት መስኮች የዕውቅና ፈቃድ እና የዕውቅና ፈቃድ ዕድሳት የተሰጣቸው 763 የትምህርት መስኮች ሲሆኑ ያልተሰጣቸው ደግሞ ለ565 መሆናቸውን ኤጀንሲው ገለጸ፤
እስከ ታህሳስ 2012 ዓ.ም. የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ብዛት 246 ደርሷል።
የከፍተኛ ትምህርት አግባብነትና ጥራት ኤጀንሲ በ2012 የመጀመሪያው ግማሽ አመት 497 ካምፓሶች ላይ በ1045 የትምህርት መስኮች የእውቅና ፈቃድ እንዲሁም 132 ካምፓሶች ላይ በ283 የትምህርት መስኮች የእውቅና ፈቃድ እድሳት እንዲሰጣቸው የተለየያዩ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጥያቄ አቅርበውለታል፡፡
ባጠቃላይ 629 ካምፓሶች በ1328 የትምህርት መስኮች የእውቅና ፈቃድ እና እውቅና ፈቃድ እድሳት ጥያቄዎች ተቋማት ለኤጀንሲው አቅርበውለታል፤ የቀረቡ ጥያቄዎች መነሻ በማድረግ ባካሄደው የሰነድና የመስክ ግምገማዎች ውጤት መሰረት 365 ካምፓሶች ላይ ለ763 የትምህርት መስኮች የእውቅና ፈቃድ እና እድሳት ሰጥቷል፤ በ264 ካምፓሶች ለ565 የትምህርት መስኮች ደግሞ አለመስጠቱን ኤጀንሲው አሳውቋል፡፡የእውቅና ፈቃድ እና እውቅና ፈቃድ እድሳት የተሰጣቸው ምክንያት ለየትምህርት መስኩ የተቀመጡትን መስፈርቶች አሟልተው በመገኘታቸው ነው፤ የእውቅና ፈቃድ እና የእውቅና ፈቃድ እድሳት ያልተሰጠባቸው የትምህርት መስኮች የመመዘኛ መስፈርቶችን አሟልተው ባለመገኘታቸው ነው፡፡
እስከ ታህሳስ 2012 ዓ.ም.ድረስ ባለው ወቅታዊ መረጃ መሰረት የእውቅና ፈቃድ አግኝተው ተማሪ ማስተማር የሚችሉ ተቋማት ብዛት 247 ደርሷል፡፡ የተቋማት ዝርዝር መረጃ ወቅታዊ ተደርጎ እስከ የካቲት 20 2012 ዓ.ም ድረስ በድረ-ገጽ እና በፌስ ቡክ ገጹ ለህዝብ ይፋ መደረጉን ኤጀንሲው ገልጿል፡፡
ማንኛውም የከፍተኛ ትምህርት ተቋም ተማሪዎችን መዝግቦ ማስተማር የሚችለው ለኤጀንሲው ጥያቄ አቅርቦ ከተገመገመ በኋላ በተገኘው ውጤት መሰረት ፈቃድ ማግኘቱ ሲገለጽለት ብቻ መሆኑ ታውቆ መላው ህብረተሰብ የተለመደውን ጥንቃቄ እንዲያደርግ ኤጀንሲው ጥብቅ መልዕክቱን አስተላልፏል፡፡
ምንጭ:HERQA
@YeneTube @FikerAssefa
እስከ ታህሳስ 2012 ዓ.ም. የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ብዛት 246 ደርሷል።
የከፍተኛ ትምህርት አግባብነትና ጥራት ኤጀንሲ በ2012 የመጀመሪያው ግማሽ አመት 497 ካምፓሶች ላይ በ1045 የትምህርት መስኮች የእውቅና ፈቃድ እንዲሁም 132 ካምፓሶች ላይ በ283 የትምህርት መስኮች የእውቅና ፈቃድ እድሳት እንዲሰጣቸው የተለየያዩ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጥያቄ አቅርበውለታል፡፡
ባጠቃላይ 629 ካምፓሶች በ1328 የትምህርት መስኮች የእውቅና ፈቃድ እና እውቅና ፈቃድ እድሳት ጥያቄዎች ተቋማት ለኤጀንሲው አቅርበውለታል፤ የቀረቡ ጥያቄዎች መነሻ በማድረግ ባካሄደው የሰነድና የመስክ ግምገማዎች ውጤት መሰረት 365 ካምፓሶች ላይ ለ763 የትምህርት መስኮች የእውቅና ፈቃድ እና እድሳት ሰጥቷል፤ በ264 ካምፓሶች ለ565 የትምህርት መስኮች ደግሞ አለመስጠቱን ኤጀንሲው አሳውቋል፡፡የእውቅና ፈቃድ እና እውቅና ፈቃድ እድሳት የተሰጣቸው ምክንያት ለየትምህርት መስኩ የተቀመጡትን መስፈርቶች አሟልተው በመገኘታቸው ነው፤ የእውቅና ፈቃድ እና የእውቅና ፈቃድ እድሳት ያልተሰጠባቸው የትምህርት መስኮች የመመዘኛ መስፈርቶችን አሟልተው ባለመገኘታቸው ነው፡፡
እስከ ታህሳስ 2012 ዓ.ም.ድረስ ባለው ወቅታዊ መረጃ መሰረት የእውቅና ፈቃድ አግኝተው ተማሪ ማስተማር የሚችሉ ተቋማት ብዛት 247 ደርሷል፡፡ የተቋማት ዝርዝር መረጃ ወቅታዊ ተደርጎ እስከ የካቲት 20 2012 ዓ.ም ድረስ በድረ-ገጽ እና በፌስ ቡክ ገጹ ለህዝብ ይፋ መደረጉን ኤጀንሲው ገልጿል፡፡
ማንኛውም የከፍተኛ ትምህርት ተቋም ተማሪዎችን መዝግቦ ማስተማር የሚችለው ለኤጀንሲው ጥያቄ አቅርቦ ከተገመገመ በኋላ በተገኘው ውጤት መሰረት ፈቃድ ማግኘቱ ሲገለጽለት ብቻ መሆኑ ታውቆ መላው ህብረተሰብ የተለመደውን ጥንቃቄ እንዲያደርግ ኤጀንሲው ጥብቅ መልዕክቱን አስተላልፏል፡፡
ምንጭ:HERQA
@YeneTube @FikerAssefa
YeneTube
በመጀመሪያው ግማሽ ዓመት በ1328 የትምህርት መስኮች የዕውቅና ፈቃድ እና የዕውቅና ፈቃድ ዕድሳት የተሰጣቸው 763 የትምህርት መስኮች ሲሆኑ ያልተሰጣቸው ደግሞ ለ565 መሆናቸውን ኤጀንሲው ገለጸ፤ እስከ ታህሳስ 2012 ዓ.ም. የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ብዛት 246 ደርሷል። የከፍተኛ ትምህርት አግባብነትና ጥራት ኤጀንሲ በ2012 የመጀመሪያው ግማሽ አመት 497 ካምፓሶች ላይ በ1045 የትምህርት መስኮች…
ከ2011 ዓ.ም. ጀምሮ ከህሙማን ጋር ግንኙነት ያላቸውን የጤና ስልጠናዎች በማታ፣ ቅዳሜና እሁድ ማሰልጠን አይቻልም። በተደጋጋሚ የተገለጸ ስለሆነ ከውሳኔው ውጪ ገብተው የሚማሩ ካሉ ኃላፊነቱ የተቋሙ እና የተማሪው ብቻ ይሆናል።
-ኤጀንሲው
@YeneTube @FikerAssefa
-ኤጀንሲው
@YeneTube @FikerAssefa
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ በገንዘብ እጥረት የተነሳ ፕሮጀክቶች ለማቆም ጫፍ ደርሶ ነበር
ከፍተኛ የገንዘብ ቀውስ ውስጥ ወድቆ የነበረው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በ2012 የመጀመሪያ ሩብ ዓመት ያለበትን የብድር ወለድ ለመክፈል እንዲሁም ለህዳሴ ግድብ ግንባታ እና ለሌሎች ትላልቅ ፕሮጀክቶች ማስገንቢያ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሰባት ነጥብ አምስት ቢሊዮን ብር መበደሩን ይፋ አደረገ። ይህንንም ተከትሎ ድርጅቱ ከንግድ ባንክ የወሰደው ብድር ወደ 271 ቢሊዮን ብር ገደማ ሲደርስ፣ አጠቃላይ ዕዳውን ከ300 ቢሊዮን ብር በላይ እንዲሆን አድርጎታል።
Via:- Addis Maleda
@YeneTube @Fikerassefa
ከፍተኛ የገንዘብ ቀውስ ውስጥ ወድቆ የነበረው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በ2012 የመጀመሪያ ሩብ ዓመት ያለበትን የብድር ወለድ ለመክፈል እንዲሁም ለህዳሴ ግድብ ግንባታ እና ለሌሎች ትላልቅ ፕሮጀክቶች ማስገንቢያ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሰባት ነጥብ አምስት ቢሊዮን ብር መበደሩን ይፋ አደረገ። ይህንንም ተከትሎ ድርጅቱ ከንግድ ባንክ የወሰደው ብድር ወደ 271 ቢሊዮን ብር ገደማ ሲደርስ፣ አጠቃላይ ዕዳውን ከ300 ቢሊዮን ብር በላይ እንዲሆን አድርጎታል።
Via:- Addis Maleda
@YeneTube @Fikerassefa
ኦፌኮ ለኢሳት በላከው ማሳሰቢያ "የኦሮሚያ ቤተ ክህነት መግለጫ በፓርቲያችን ጽ/ቤት ዉስጥ እንደተሰጠ ተደርጎ የቀረበው መረጃ እውነት አይደለም" ብሏል።
Via:- ኦፌኮ / ኤልያስ መሰረት
@Yenetube @Fikerassefa
Via:- ኦፌኮ / ኤልያስ መሰረት
@Yenetube @Fikerassefa
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ኤምባሲው በሳኡዲ አረቢያ ደማም በአሰሪዎቿ ታግታ የነበረችውን ኢትዮጵያዊት አለቅቄያለው ብሏል።
ህይወቷን ለመቀየር የዛሬ ሰባት አመት ሳኡዲ አረቢያ ደማም ከተማ የገባችው ኢትዮጵያዊት ትዕግስት ፍስሃ አሰሪዎቿ የመብት ጥሰቶችን በተደጋጋሚ በማድረስ ከምትሰራበት ቤት እንዳትወጣና እንዳትንቀሳቀስ ያደርጓታል።ለሰባት አመታት በዚህ አይነት ጭንቅ፣ እንግልት እንዲሁም እገታ የቆየችው እህታችን፣ በቅርቡ ኤምባሲው በህይወት እንዲደርስላት፣ አሰሪዎቿ ያልከፈሏትን የአንድ አመት ከዘጠኝ ወር ደመወዝ እንዲያስከፍልላት እና ለአገሯ አፈር እንዲያበቃት ትጠይቃለች። ኤምባሲው በደማም ከተማ ካለው የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ ማህበር ጋር በመተባበር እህት ትዕግስት ፍስሃ ከታገተችበት ቤት እንድትወጣ እና ያልተከፈላትን ደመወዝ ለአሁኑ አስር ሺህ አራት መቶ የሳኡዲ ሪያል (10 400 ሳ.ሪ) እንድታገኝ(በቀጣይ ቀሪውን እንድታገኝ ጥረት የሚደረግ ይሆናል) ያደረገ ሲሆን፣ በቅርቡም ወደ አገር እንድትሸኝ የሚያደርግ ይሆናል።
ምንጭ: በሪያድ የኢትዮጵያ ኤምባሲ
@YeneTube @FikerAssefa
ህይወቷን ለመቀየር የዛሬ ሰባት አመት ሳኡዲ አረቢያ ደማም ከተማ የገባችው ኢትዮጵያዊት ትዕግስት ፍስሃ አሰሪዎቿ የመብት ጥሰቶችን በተደጋጋሚ በማድረስ ከምትሰራበት ቤት እንዳትወጣና እንዳትንቀሳቀስ ያደርጓታል።ለሰባት አመታት በዚህ አይነት ጭንቅ፣ እንግልት እንዲሁም እገታ የቆየችው እህታችን፣ በቅርቡ ኤምባሲው በህይወት እንዲደርስላት፣ አሰሪዎቿ ያልከፈሏትን የአንድ አመት ከዘጠኝ ወር ደመወዝ እንዲያስከፍልላት እና ለአገሯ አፈር እንዲያበቃት ትጠይቃለች። ኤምባሲው በደማም ከተማ ካለው የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ ማህበር ጋር በመተባበር እህት ትዕግስት ፍስሃ ከታገተችበት ቤት እንድትወጣ እና ያልተከፈላትን ደመወዝ ለአሁኑ አስር ሺህ አራት መቶ የሳኡዲ ሪያል (10 400 ሳ.ሪ) እንድታገኝ(በቀጣይ ቀሪውን እንድታገኝ ጥረት የሚደረግ ይሆናል) ያደረገ ሲሆን፣ በቅርቡም ወደ አገር እንድትሸኝ የሚያደርግ ይሆናል።
ምንጭ: በሪያድ የኢትዮጵያ ኤምባሲ
@YeneTube @FikerAssefa
መቀሌን ዋና ማእከሉ ለማድረግ ያቀደው ኖርዝ ስታር አየር መንገድ የመስች ጉባኤውን አደረገ፡፡
በርካታ ታዋቂ ሰዎችን፣ ባለሃብቶችን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያንን ያቀፈው እና በመቋቋም ላይ ያለው ድርጅት በአገሪቱ እየመጡ ያሉትን በርካታ ማሻሻያዎች መነሻ በማድረግ ወደ ስራው ለመግባት መነሳቱን አስታውቋል፡፡
በተለይ ከኤርትራ ጋር የተደረገው እርቅ፣ አዲሱ የኢንቨስትመንት አዋጅ የግል አየር መንገዶች ላይ የነበረውን የአውሮፕላን መቀመጫ ገደብ ማንሳቱ እንዲሁም መንግስት በግዙፉ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ላይ ድርሻ ለመሸጥ መነሳቱ በዘርፉ ለመሳተፍ እንዳነሳሳቸው የሃሳቡ ባለቤት አቶ መኮንን አሰፋ ተናግረዋል፡፡
በ2017 ይፋ የተደረገ ጥናት እንደሚያሳው 60 ሚሊየን እና ወደ 50 ሚሊየን ህዝብ ያለባቸው ደቡብ አፍሪካ እና ኬንያ እንደቅደም ተከተላቸው በአገራቸው ከ 5 ሺ እና 2 ሺ አውሮፕላኖች በአገራቸው ይገኛሉ፡፡ከ110 ሚሊየን ህዝብ በላይ ባላት ኢትዮጵያ ይህ ቁጥር በተጠቀሰው የፈረንጆቹ አመት 140 አውሮፕላኖች ብቻ ነበር፡፡ ከዚህም ሁሉም በሚባል ደረጃ በኢትዮጵያ አየር መንገድ የተያዘ ነው፡፡
Via Capital
@YeneTube @FikerAssefa
በርካታ ታዋቂ ሰዎችን፣ ባለሃብቶችን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያንን ያቀፈው እና በመቋቋም ላይ ያለው ድርጅት በአገሪቱ እየመጡ ያሉትን በርካታ ማሻሻያዎች መነሻ በማድረግ ወደ ስራው ለመግባት መነሳቱን አስታውቋል፡፡
በተለይ ከኤርትራ ጋር የተደረገው እርቅ፣ አዲሱ የኢንቨስትመንት አዋጅ የግል አየር መንገዶች ላይ የነበረውን የአውሮፕላን መቀመጫ ገደብ ማንሳቱ እንዲሁም መንግስት በግዙፉ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ላይ ድርሻ ለመሸጥ መነሳቱ በዘርፉ ለመሳተፍ እንዳነሳሳቸው የሃሳቡ ባለቤት አቶ መኮንን አሰፋ ተናግረዋል፡፡
በ2017 ይፋ የተደረገ ጥናት እንደሚያሳው 60 ሚሊየን እና ወደ 50 ሚሊየን ህዝብ ያለባቸው ደቡብ አፍሪካ እና ኬንያ እንደቅደም ተከተላቸው በአገራቸው ከ 5 ሺ እና 2 ሺ አውሮፕላኖች በአገራቸው ይገኛሉ፡፡ከ110 ሚሊየን ህዝብ በላይ ባላት ኢትዮጵያ ይህ ቁጥር በተጠቀሰው የፈረንጆቹ አመት 140 አውሮፕላኖች ብቻ ነበር፡፡ ከዚህም ሁሉም በሚባል ደረጃ በኢትዮጵያ አየር መንገድ የተያዘ ነው፡፡
Via Capital
@YeneTube @FikerAssefa