ባልደራስ በባሕር ዳር ከሕዝብ ጋር እየተወያየ ነው
የባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች ትናንት አመሻሽ ባሕር ዳር ገብተዋል።
ሕዝብ ለፓርቲው ያደረገውን ጥሪ ተከትሎ የባልደራስ ሊቀ መንበር ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ እና የሕዝብ ግንኙነት ሓላፊው አቶ ስንታየሁ ቸኮል ባሕር ዳር በላይ ዘለቀ አውሮፕላን ጣቢያ ሲደርሱ የአማራ ወጣቶች ማሕበር በባሕር ዳር ደማቅ አቀባበል አድርጎላቸዋል።
በጣና ግዮን ወጣቶች የበጎ አድራጎት ማህበር አስተባባሪነት የባልደራስ ከፍተኛ አመራሮች በባሕር ዳር ጣና ዳር የፅዳት ሥራ ዛሬ ጧት አከናውኗል።
ሕዝባዊ ውይይቱም በቴዎድሮስ ስታዲዮም ሊጀመር ዝግጅቱ ተጠናቋል። በመድረኩ የባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ ሊቀመንበር ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ በፓርቲው እንቅስቃሴ ዙሪያ ንግግር እንደሚያደርጉ የሕዝብ ግንኙነት ሓላፊው አቶ ስንታየሁ ቸኮል ለኢትዮጲስ ገልፀዋል።
ባልደራስ ነገ እሁድ የካቲት 8 ቀን በጎንደር ከተማ ተመሳሳይ ሕዝባዊ ውይይት እንደሚያደርግም አቶ ስንታየሁ ገልፀዋል።
Via:- ኢትዮጲስ ጋዜጣ
@Yenetube @Fikerassefa
የባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች ትናንት አመሻሽ ባሕር ዳር ገብተዋል።
ሕዝብ ለፓርቲው ያደረገውን ጥሪ ተከትሎ የባልደራስ ሊቀ መንበር ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ እና የሕዝብ ግንኙነት ሓላፊው አቶ ስንታየሁ ቸኮል ባሕር ዳር በላይ ዘለቀ አውሮፕላን ጣቢያ ሲደርሱ የአማራ ወጣቶች ማሕበር በባሕር ዳር ደማቅ አቀባበል አድርጎላቸዋል።
በጣና ግዮን ወጣቶች የበጎ አድራጎት ማህበር አስተባባሪነት የባልደራስ ከፍተኛ አመራሮች በባሕር ዳር ጣና ዳር የፅዳት ሥራ ዛሬ ጧት አከናውኗል።
ሕዝባዊ ውይይቱም በቴዎድሮስ ስታዲዮም ሊጀመር ዝግጅቱ ተጠናቋል። በመድረኩ የባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ ሊቀመንበር ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ በፓርቲው እንቅስቃሴ ዙሪያ ንግግር እንደሚያደርጉ የሕዝብ ግንኙነት ሓላፊው አቶ ስንታየሁ ቸኮል ለኢትዮጲስ ገልፀዋል።
ባልደራስ ነገ እሁድ የካቲት 8 ቀን በጎንደር ከተማ ተመሳሳይ ሕዝባዊ ውይይት እንደሚያደርግም አቶ ስንታየሁ ገልፀዋል።
Via:- ኢትዮጲስ ጋዜጣ
@Yenetube @Fikerassefa
የአማራ ብሔራዊ ክልል ምክር ቤት አስቸኳይ ጉባዔ ሊያካሂድ ነው፡፡
የአማራ ብሔራዊ ክልል ምክር ቤት የፊታችን ማክሰኞ የካቲት 10/2012 ዓ.ም አስቸኳይ ጉባዔ እንደሚያካሂድ ይጠበቃል፡፡በዕለቱም ልዩ ልዩ ውሳኔዎችን እንደሚያሳልፍ እና ሹመቶችንም እንደሚያጸድቅ ይጠበቃል፡፡
Via AMMA
@YeneTube @FikerAssefa
የአማራ ብሔራዊ ክልል ምክር ቤት የፊታችን ማክሰኞ የካቲት 10/2012 ዓ.ም አስቸኳይ ጉባዔ እንደሚያካሂድ ይጠበቃል፡፡በዕለቱም ልዩ ልዩ ውሳኔዎችን እንደሚያሳልፍ እና ሹመቶችንም እንደሚያጸድቅ ይጠበቃል፡፡
Via AMMA
@YeneTube @FikerAssefa
በአፍሪካ ውስጥ የመጀመሪያው በኮሮና ቫይረስ መያዙ የተረጋገጠ ህመምተኛ ግብጽ ውስጥ መገኘቱ ተነገረ።
ይህም ለግብጽ የመጀመሪያው በበሽታው የተጠረጠረና በሽታው የተገኘበት ሰው መሆኑ የተገለጸ ሲሆን፤ ግለሰቡም በአህጉሪቱ የተገኘ የመጀመሪያው የኮሮና ቫይረስ ተጠቂ ሆኗል።
የግብጽ የጤና ሚኒስቴር እንዳስታወቀው በሽታው የተገኘበት ግለሰብ የውጪ አገር ዜግነት ያለው መሆኑን ቢገልጽም ከየት አገር እንደመጣ ግን አላመለከተም።
ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ አክሎም ስለበሽታው ክስተት ለዓለም የጤና ድርጅት ማሳወቁንና በበሽታው የተያዘው ግለሰብም በአንድ ሆስፒታል ውስጥ ተለይቶ ክትትል እየተደረገለት መሆኑን ገልጿል።
የአፍሪካ አገራት ከቻይና ጋር ባላቸው የጠበቀ ግንኙነት ምክንያት በሽታው በአጭር ጊዜ አፍሪካ ውስጥ ሊታይ እንደሚችል የጤና ባለሙያዎች ቀደም ሲል ሲያስጠነቅቁ ነበር።
በሽታው በወረርሽኝ መልክ መከሰቱና በተለያዩ አገራት ውስጥ መታየቱ ከተነገረ በኋላ ጥቂት የማይባሉ የአፍሪካ አገራት፣ የበሽታው ምልክት የታየባቸው ሰዎችን እንዳገኙ ቢገልጹም በኋላ ላይ በተደረጉ ምርመራዎች ግለሰቦቹ ከቫይረሱ ነጻ መሆናቸው ተረጋግጧል።
ከቻይናዋ የዉሃን ከተማ ተነስቶ ወደ ተለያዩ አገራት የተዛመተው ይህ በሽታ እስካሁን ድረስ ከ1ሺህ 500 በላይ ሰዎችን ህይወት የቀጠፈ ሲሆን ከእነዚህም መካከል የሚበዙት ቻይናውያን ናቸው።
Via:- BBC
@YeneTube @FikerAssefa
ይህም ለግብጽ የመጀመሪያው በበሽታው የተጠረጠረና በሽታው የተገኘበት ሰው መሆኑ የተገለጸ ሲሆን፤ ግለሰቡም በአህጉሪቱ የተገኘ የመጀመሪያው የኮሮና ቫይረስ ተጠቂ ሆኗል።
የግብጽ የጤና ሚኒስቴር እንዳስታወቀው በሽታው የተገኘበት ግለሰብ የውጪ አገር ዜግነት ያለው መሆኑን ቢገልጽም ከየት አገር እንደመጣ ግን አላመለከተም።
ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ አክሎም ስለበሽታው ክስተት ለዓለም የጤና ድርጅት ማሳወቁንና በበሽታው የተያዘው ግለሰብም በአንድ ሆስፒታል ውስጥ ተለይቶ ክትትል እየተደረገለት መሆኑን ገልጿል።
የአፍሪካ አገራት ከቻይና ጋር ባላቸው የጠበቀ ግንኙነት ምክንያት በሽታው በአጭር ጊዜ አፍሪካ ውስጥ ሊታይ እንደሚችል የጤና ባለሙያዎች ቀደም ሲል ሲያስጠነቅቁ ነበር።
በሽታው በወረርሽኝ መልክ መከሰቱና በተለያዩ አገራት ውስጥ መታየቱ ከተነገረ በኋላ ጥቂት የማይባሉ የአፍሪካ አገራት፣ የበሽታው ምልክት የታየባቸው ሰዎችን እንዳገኙ ቢገልጹም በኋላ ላይ በተደረጉ ምርመራዎች ግለሰቦቹ ከቫይረሱ ነጻ መሆናቸው ተረጋግጧል።
ከቻይናዋ የዉሃን ከተማ ተነስቶ ወደ ተለያዩ አገራት የተዛመተው ይህ በሽታ እስካሁን ድረስ ከ1ሺህ 500 በላይ ሰዎችን ህይወት የቀጠፈ ሲሆን ከእነዚህም መካከል የሚበዙት ቻይናውያን ናቸው።
Via:- BBC
@YeneTube @FikerAssefa
ከጂንጆ ከተማ የኢትዮጵያ ተማሪዎች ተጠሪ
በጂንጆ ሁበይ ከተማ የምንኖር ኢትዮጵያውን ቁጥራችን ትንሽ ቢሆንም ሰው እያወራ እየተጨነቀ ያለው ስለ ዉሀን ብቻ ነው ጂንጆ የምንገኝ ተማሪዎች እኛም ተመሳሳይ ጭንቀት ላይ ስላለን መንግስት ትኩረቱን ለኛም እንዲሰጠን እንጠይቃለን ።
@Yenetube @Fikerassefa
በጂንጆ ሁበይ ከተማ የምንኖር ኢትዮጵያውን ቁጥራችን ትንሽ ቢሆንም ሰው እያወራ እየተጨነቀ ያለው ስለ ዉሀን ብቻ ነው ጂንጆ የምንገኝ ተማሪዎች እኛም ተመሳሳይ ጭንቀት ላይ ስላለን መንግስት ትኩረቱን ለኛም እንዲሰጠን እንጠይቃለን ።
@Yenetube @Fikerassefa
በኢትዮጵያ በትላንትናው እለት በኮርኖ ቫይረስ ተጠርጥሮ በለይቶ ማከምያ ክፍል የገባው ተጠርጣሪ ከቫይረሱ ነጻ መሆኑ ተገለጸ።
የኢትዮጵያ የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ለኢትዮ ኤፍ ኤም እንዳስታወቀው የኮሮና ቫይረስ በሽታ ምልክቶችን ያሳየ አንድ ሰው በለይቶ ማቆያ ማዕከሉ ውስጥ ከገባ በኋላ የምርመራ ናሙናው ለምርመራ ተልኮ ነበር።
ተጠርጣሪው አሁን የምርመራው ውጤት የደረሰ ሲሆን ከበሽታው ነጻ መሆኑ እንደተረጋገጠ ኢንስቲትዩቱ ገልጿል፡፡
በቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ እና 27 የተለያዩ የድምበር መግቢያ እና መውጫ ኬላዎች ላይ የሚደረገው የማጣራት ምርመራ በተጠናከረ ሁኔታ እየቀጠለ ይገኛል፡፡
እስከ ትላንት ድረስ ለ118 ሺህ 882 ተጓዦች የሙቀት መለያ ምርመራ የተደረገላቸው ሲሆን ከነዚህም ውስጥ 3 ሺህ 380ዎቹ የመጡት ቫይረሱ ሪፖርት ከተደረገባቸው ሀገራት ነው፡፡
እንዲሁም ከ455 በላይ የሚሆኑት ባሉበት ቦታ ሆነው የጤና ክትትል እየተደረገላቸው እንደሆነ ነው የተገለጸው፡፡
በኮሮና ቫይረስ እስካሁን 48 ሺህ ታካሚዎች በቫይረሱ መያዛቸው ሪፖርት የተደረገ ሲሆን 1ሺህ 500 ሰዎች ደግሞ ህይወታቸው ማለፉን የአለም ጤና ድርጅት አስታውቃል፡፡
Via:- Ethio FM
@YeneTube @Fikerassefa
የኢትዮጵያ የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ለኢትዮ ኤፍ ኤም እንዳስታወቀው የኮሮና ቫይረስ በሽታ ምልክቶችን ያሳየ አንድ ሰው በለይቶ ማቆያ ማዕከሉ ውስጥ ከገባ በኋላ የምርመራ ናሙናው ለምርመራ ተልኮ ነበር።
ተጠርጣሪው አሁን የምርመራው ውጤት የደረሰ ሲሆን ከበሽታው ነጻ መሆኑ እንደተረጋገጠ ኢንስቲትዩቱ ገልጿል፡፡
በቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ እና 27 የተለያዩ የድምበር መግቢያ እና መውጫ ኬላዎች ላይ የሚደረገው የማጣራት ምርመራ በተጠናከረ ሁኔታ እየቀጠለ ይገኛል፡፡
እስከ ትላንት ድረስ ለ118 ሺህ 882 ተጓዦች የሙቀት መለያ ምርመራ የተደረገላቸው ሲሆን ከነዚህም ውስጥ 3 ሺህ 380ዎቹ የመጡት ቫይረሱ ሪፖርት ከተደረገባቸው ሀገራት ነው፡፡
እንዲሁም ከ455 በላይ የሚሆኑት ባሉበት ቦታ ሆነው የጤና ክትትል እየተደረገላቸው እንደሆነ ነው የተገለጸው፡፡
በኮሮና ቫይረስ እስካሁን 48 ሺህ ታካሚዎች በቫይረሱ መያዛቸው ሪፖርት የተደረገ ሲሆን 1ሺህ 500 ሰዎች ደግሞ ህይወታቸው ማለፉን የአለም ጤና ድርጅት አስታውቃል፡፡
Via:- Ethio FM
@YeneTube @Fikerassefa
ጁነዲን ሳዶ ሸገር የተሰኘ አዲስ ባንክ ሊመርቱ ነው!
የቀድሞው የኦሮምያ ክልል ርዕሰ መስተዳደር ጁነዲን ሳዶ #ሸገር የተሰኘ አዲስ ባንክ ከሌሎች አጋሮቻቸው ጋር በመሆን በማቋቋም ላይ መሆናቸውን አስታወቁ።
የባንኩ መስራች ቦርድ የሆኑት ጁነዲን እንደተናገሩት ድርሻ የመሸጥ ፍቃድ ከብሔራዊ ባንክ አግኝተው ከየካቲት 7 ጀምሮ በይፋ አክሲሆን መሸጥ ይጀምራል ብሏል ።
Via:- አዲስ ማለዳ ጋዜጣ 🖊 YeneTube
@YeneTube @Fikerassefa
የቀድሞው የኦሮምያ ክልል ርዕሰ መስተዳደር ጁነዲን ሳዶ #ሸገር የተሰኘ አዲስ ባንክ ከሌሎች አጋሮቻቸው ጋር በመሆን በማቋቋም ላይ መሆናቸውን አስታወቁ።
የባንኩ መስራች ቦርድ የሆኑት ጁነዲን እንደተናገሩት ድርሻ የመሸጥ ፍቃድ ከብሔራዊ ባንክ አግኝተው ከየካቲት 7 ጀምሮ በይፋ አክሲሆን መሸጥ ይጀምራል ብሏል ።
Via:- አዲስ ማለዳ ጋዜጣ 🖊 YeneTube
@YeneTube @Fikerassefa
አውሮፓ ውስጥ በኮሮና ቫይረስ የመጀመሪያው ሞት ተመዝግቧል። የ80 አመት ቻይናዊ አዛውንት ወደ ፓሪስ ለጉብኝት በመጡበት እንደሞቱ VoA ዘግቧል።
@YeneTube @FikerAssefa
@YeneTube @FikerAssefa
የክልል ልዩ ሃይል እና ሚሊሻ በፌደራል ስር እንዲጠቃለሉ የሚመክር ጉባኤ በአዲስ አበባ በመካሄድ ላይ ነው።
ውይይቱን ጽናት ኢትዮጵያ የተሰኘው የበጎ አድራጎት ማህበር ያዘጋጀው ሲሆን የክልል ልዩ ሃይልና ሚሊሻዎች ለአገራችን ሰላም ያላቸው ሚና በሚል መሪ ሃሳብ በአዲስ አበባ በመካሄድ ላይ ይግኛል። በኢትዮጵያ የዜጎች መፈናቀል፣ የማምለኪያ ቦታዎች መቃጠል እና ሌሎች እየተፈጠሩ ያሉ ችግሮች እንዲቆሙ እና የህግ የበከላይነት እንዲረጋገጥ መፍትሔዎቹ ምን ምን ናቸው በሚል ላይ እንደሚያተኩር የውይይቱ አዘጋጆች ለኢትዮ ኤፍ ኤም ተናግረዋል።
በውይይቱ ላይ የህግ ምሁራን፣ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች፣ የሃይማኖት አባቶች፣የአገር ሽማግሌዎች፣ የጸጥታ እና የፍትህ ተቋማት አመራሮች ተገኝተዋል።የክልል ልዩ ሃይሎች እና ሚሊሻዎች አሁን ካሉበት ፉክክር ወጥተው እንዴት ለአገር ግንባታ እናውለው በሚልም የመፍትሔ ሃሳቦች እንደሚነሱበትም ይጠበቃል።
Via Ethio FM
@YeneTube @FikerAssefa
ውይይቱን ጽናት ኢትዮጵያ የተሰኘው የበጎ አድራጎት ማህበር ያዘጋጀው ሲሆን የክልል ልዩ ሃይልና ሚሊሻዎች ለአገራችን ሰላም ያላቸው ሚና በሚል መሪ ሃሳብ በአዲስ አበባ በመካሄድ ላይ ይግኛል። በኢትዮጵያ የዜጎች መፈናቀል፣ የማምለኪያ ቦታዎች መቃጠል እና ሌሎች እየተፈጠሩ ያሉ ችግሮች እንዲቆሙ እና የህግ የበከላይነት እንዲረጋገጥ መፍትሔዎቹ ምን ምን ናቸው በሚል ላይ እንደሚያተኩር የውይይቱ አዘጋጆች ለኢትዮ ኤፍ ኤም ተናግረዋል።
በውይይቱ ላይ የህግ ምሁራን፣ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች፣ የሃይማኖት አባቶች፣የአገር ሽማግሌዎች፣ የጸጥታ እና የፍትህ ተቋማት አመራሮች ተገኝተዋል።የክልል ልዩ ሃይሎች እና ሚሊሻዎች አሁን ካሉበት ፉክክር ወጥተው እንዴት ለአገር ግንባታ እናውለው በሚልም የመፍትሔ ሃሳቦች እንደሚነሱበትም ይጠበቃል።
Via Ethio FM
@YeneTube @FikerAssefa
የሴቶች ህጻናትና ወጣቶች ሚኒስቴር ያለዕድሜ ጋብቻንና የሴት ልጅ ግርዛትን ለማስቆም የተዘጋጀዉን ፍኖተ ካርታ በኦሮሚያ ክልል ማስተዋወቅ ጀመረ!
ያለዕድሜ ጋብቻንና የሴት ልጅ ግርዛትን ለማስቆም የተዘጋጀዉን ፍኖተ ካርታ በኦሮሚያ ክልል ማስተዋወቅ በዛሬዉ ዕለት በጅማ ዞን ተጀምሯል፡፡ይህንንኑ ፍኖተ ካርታ አጠር ባለ መልኩ ያስተወወቁት አቶ ሰሎሞን አሰፋ በሚኒስቴር መ/ቤቱ የሚኒስቴር ጽ/ቤት ሀላፊ ሲሆኑ በገለጻቸዉም ፍኖተ ካርታዉ ከሌሎች መሰል አስትራተጂዎች በተለየ መልኩ ለስራዉ አስፈላጊ የሆነ በጀት በዉስጡ እንዳካተተና ያለዕድሜ ጋብቻንና የሴት ልጅ ግርዛትን ለማስቆም በከፍተኛ ፍጥነት መሰራት እንዳለበት አጽንኦት የሰጠ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡
በማስተዋወቂያ መድረኩ ላይ ከጅማ ዞን የተዉጣጡ በሴቶች፣ህጻናትና ወጣቶች ላይ የሚሰሩ ሴክተር መ/ቤት ተወካዮች፣ የሀይማኖት ተቋማት ተወካዮችና ሌሎች ጉዳዮ ከሚመለከታቸዉ አካላት የተዉጣጡ ከ 250 በላይ የሚገመቱ ተሳታፊዎች ተገኝተዋል፡፡
ምንጭ: የሴቶች ህፃናትና ወጣቶች ሚኒስቴር
@YeneTube @FikerAssefa
ያለዕድሜ ጋብቻንና የሴት ልጅ ግርዛትን ለማስቆም የተዘጋጀዉን ፍኖተ ካርታ በኦሮሚያ ክልል ማስተዋወቅ በዛሬዉ ዕለት በጅማ ዞን ተጀምሯል፡፡ይህንንኑ ፍኖተ ካርታ አጠር ባለ መልኩ ያስተወወቁት አቶ ሰሎሞን አሰፋ በሚኒስቴር መ/ቤቱ የሚኒስቴር ጽ/ቤት ሀላፊ ሲሆኑ በገለጻቸዉም ፍኖተ ካርታዉ ከሌሎች መሰል አስትራተጂዎች በተለየ መልኩ ለስራዉ አስፈላጊ የሆነ በጀት በዉስጡ እንዳካተተና ያለዕድሜ ጋብቻንና የሴት ልጅ ግርዛትን ለማስቆም በከፍተኛ ፍጥነት መሰራት እንዳለበት አጽንኦት የሰጠ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡
በማስተዋወቂያ መድረኩ ላይ ከጅማ ዞን የተዉጣጡ በሴቶች፣ህጻናትና ወጣቶች ላይ የሚሰሩ ሴክተር መ/ቤት ተወካዮች፣ የሀይማኖት ተቋማት ተወካዮችና ሌሎች ጉዳዮ ከሚመለከታቸዉ አካላት የተዉጣጡ ከ 250 በላይ የሚገመቱ ተሳታፊዎች ተገኝተዋል፡፡
ምንጭ: የሴቶች ህፃናትና ወጣቶች ሚኒስቴር
@YeneTube @FikerAssefa
#COVID-2019_update
የቫይረሱ ተጠቂዎች ቁጥር ከስድሳ ስድስት ሺህ ያለፈ ሲሆን የሟቾች ቁጥር ደግሞ 1526 ደርሷል።
Via AFP
@YeneTube @FikerAssefa
የቫይረሱ ተጠቂዎች ቁጥር ከስድሳ ስድስት ሺህ ያለፈ ሲሆን የሟቾች ቁጥር ደግሞ 1526 ደርሷል።
Via AFP
@YeneTube @FikerAssefa
"ከ350 በላይ የሚሆኑ አባላቶቻችን እና ደጋፊዎቻችን ለእስር ተዳርገውብናል" ኦ.ነ.ግ
“27 አባላት እና ደጋፊዎቻችን ለእስር ተዳርገዋል” ኦ.ፌ.ኮ
"በክልላችን የፖለቲካ ፓርቲ አባል ስለሆነ ብቻ ማንም ሰው አይታሰርም መታሰርም የለበትም።” ኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት
Via Sheger Times
@YeneTube @FikerAssefa
“27 አባላት እና ደጋፊዎቻችን ለእስር ተዳርገዋል” ኦ.ፌ.ኮ
"በክልላችን የፖለቲካ ፓርቲ አባል ስለሆነ ብቻ ማንም ሰው አይታሰርም መታሰርም የለበትም።” ኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት
Via Sheger Times
@YeneTube @FikerAssefa
በጅግጅጋ ከተማ ነገ የድጋፍ ሰልፍ ይደረጋል።
በሶማሌ ክልል ዋና ከተማ ጅግጅጋ በነገው እለት ለጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ ታላቅ የድጋፍ ሰልፍ እንደሚደረግ ከአዘጋጆቹ ያገኘነው መረጃ ይጠቁማል።በነገው እለት ከማለዳው አንስቶ በሚካሄደው ታላቅ የድጋፍ ሰልፍ ላይ በጅግጅጋ እና በአከባቢው የሚገኙ በርካታ ነዋሪዎች የሚሳተፉበት ሲሆን "በህብር ወደ ብልፅግና!" እንዲሁም " ብልፅግና ለሁሉም ሁሉም ወደ ብልፅግና" በሚል መሪ ቃልም እንደሚካሄድ ታውቋል።
Via Sheger Times
@YeneTube @FikerAssefa
በሶማሌ ክልል ዋና ከተማ ጅግጅጋ በነገው እለት ለጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ ታላቅ የድጋፍ ሰልፍ እንደሚደረግ ከአዘጋጆቹ ያገኘነው መረጃ ይጠቁማል።በነገው እለት ከማለዳው አንስቶ በሚካሄደው ታላቅ የድጋፍ ሰልፍ ላይ በጅግጅጋ እና በአከባቢው የሚገኙ በርካታ ነዋሪዎች የሚሳተፉበት ሲሆን "በህብር ወደ ብልፅግና!" እንዲሁም " ብልፅግና ለሁሉም ሁሉም ወደ ብልፅግና" በሚል መሪ ቃልም እንደሚካሄድ ታውቋል።
Via Sheger Times
@YeneTube @FikerAssefa
በተቀማጭ ገንዘብ ማነስ ምክንያት ከባንኮች የሚገኘው ብድር እጅግ ቀንሷል!
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክን ጨምሮ በሀገሪቱ ያሉ የግል ባንኮች በተቀማጭነት ያስቀመጡት ገንዘብ ከሰጡት ብድር ጋር ስላልተጣጣመ ለደንበኞቻቸው የሚሰጠው ብድር ካለፈው አንድ ወር ጀምሮ እጅግ መቀነሱን የባንክ ሰራተኞች ለፊደል ፓስት ተናግረዋል።አብዛኞቹ ባንኮችም ካላቸው ተቀማጭ ገንዘብ ከ70 እሰከ 90 ከመቶ ብድር ላይ በማዋላቸው የገንዘብ እጥረት ገጥሟቸዋል።
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ለላኪዎች፣ መድሀኒትና ዘይት አቅራቢዎችእንዲሁም ሌሎች ለሀገሪቱ የግድ አስፈላጊ ከሆኑ ምርቶች በስተቀር ለሀገር ውስጥ እቃዎች ግዢም ይሁን ለሌሎች እቃዎች የሚሰጠውን ብድር እንዳቆመ ስማቸው እንዳይገለፅ ያልፈለጉ የባንኩ ሰራተኞች ለፊደል ፓስት ተናግረዋል። ንግድ ባንክ ለሰራተኞቹ የሚሰጠውን ብድር በተቀማጭ ገንዘብ ማነሱ ምክንያት እንዳቆመ ተናግረዋል።
በዳሽን ባንክ የምትሰራ አንዲት ሰራተኛም ብድሮች እንደድሮ እየተለቀቁ እንዳልሆ ተናግራለች ።እንደሰራተኞቹ ገለፃ ባንኮች የብድር አለቃቀቃቸውን ካላቸው ተቀማጭ ገንዘብ ጋር አመጣጥኖ አለመሄድ፣ የኢኮኖሚው መቀዝቀዝ ፣የዋጋ ንረት ባንኮችን ተቀማጭ ገንዘባቸው እንዲቀንስ አድርጎ የብድር አገልግሎታቸው እንዲቀነስ አድርጎታል።ይሄም ችግርን ለመፍታት ኢኮኖሚውን ማቅናትና የሰጡትን ብድር የመመለስ ረጅም ስራ ይጠብቃል በማለት የባንክ ሰራተኞቹ አስተያየታቸውን ገልፀዋል።
Via Fidelpost
@YeneTube @FikerAssefa
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክን ጨምሮ በሀገሪቱ ያሉ የግል ባንኮች በተቀማጭነት ያስቀመጡት ገንዘብ ከሰጡት ብድር ጋር ስላልተጣጣመ ለደንበኞቻቸው የሚሰጠው ብድር ካለፈው አንድ ወር ጀምሮ እጅግ መቀነሱን የባንክ ሰራተኞች ለፊደል ፓስት ተናግረዋል።አብዛኞቹ ባንኮችም ካላቸው ተቀማጭ ገንዘብ ከ70 እሰከ 90 ከመቶ ብድር ላይ በማዋላቸው የገንዘብ እጥረት ገጥሟቸዋል።
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ለላኪዎች፣ መድሀኒትና ዘይት አቅራቢዎችእንዲሁም ሌሎች ለሀገሪቱ የግድ አስፈላጊ ከሆኑ ምርቶች በስተቀር ለሀገር ውስጥ እቃዎች ግዢም ይሁን ለሌሎች እቃዎች የሚሰጠውን ብድር እንዳቆመ ስማቸው እንዳይገለፅ ያልፈለጉ የባንኩ ሰራተኞች ለፊደል ፓስት ተናግረዋል። ንግድ ባንክ ለሰራተኞቹ የሚሰጠውን ብድር በተቀማጭ ገንዘብ ማነሱ ምክንያት እንዳቆመ ተናግረዋል።
በዳሽን ባንክ የምትሰራ አንዲት ሰራተኛም ብድሮች እንደድሮ እየተለቀቁ እንዳልሆ ተናግራለች ።እንደሰራተኞቹ ገለፃ ባንኮች የብድር አለቃቀቃቸውን ካላቸው ተቀማጭ ገንዘብ ጋር አመጣጥኖ አለመሄድ፣ የኢኮኖሚው መቀዝቀዝ ፣የዋጋ ንረት ባንኮችን ተቀማጭ ገንዘባቸው እንዲቀንስ አድርጎ የብድር አገልግሎታቸው እንዲቀነስ አድርጎታል።ይሄም ችግርን ለመፍታት ኢኮኖሚውን ማቅናትና የሰጡትን ብድር የመመለስ ረጅም ስራ ይጠብቃል በማለት የባንክ ሰራተኞቹ አስተያየታቸውን ገልፀዋል።
Via Fidelpost
@YeneTube @FikerAssefa
41 የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ ባወጣው የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ እንደማይስማሙ ድምጽ ሰጡ።
ዛሬ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክርቤት ፓርቲዎች በጊዜ ሰሌዳው ላይ ድምጽ እንዲሰጡ ባሰናደው መድረክ ከተገኙ ፓርቲዎች 41ዱ በጊዜ ሰሌዳው እንደማይስማሙ የገለጹ ሲሆን፣ ብልጽግና ፓርቲን ጨምሮ 6 ፓርቲዎች የጊዜ ሰሌዳውን ደግፈዋል።
6 ፓርቲዎች በበኩላቸው ድምጽ ተሃቅቦን መርጠዋል። የጋራ ምክርቤቱ የፓርቲዎችን አቋም ለምርጫ ቦርድ እንደሚያቀርብ አስታውቋል።
Via:- ELU
@Yenetube @Fikerassefa
ዛሬ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክርቤት ፓርቲዎች በጊዜ ሰሌዳው ላይ ድምጽ እንዲሰጡ ባሰናደው መድረክ ከተገኙ ፓርቲዎች 41ዱ በጊዜ ሰሌዳው እንደማይስማሙ የገለጹ ሲሆን፣ ብልጽግና ፓርቲን ጨምሮ 6 ፓርቲዎች የጊዜ ሰሌዳውን ደግፈዋል።
6 ፓርቲዎች በበኩላቸው ድምጽ ተሃቅቦን መርጠዋል። የጋራ ምክርቤቱ የፓርቲዎችን አቋም ለምርጫ ቦርድ እንደሚያቀርብ አስታውቋል።
Via:- ELU
@Yenetube @Fikerassefa
ዩናይትድ ስቴትስ በኮሮና ቫይረስ የተነሳ አንድ ግዙፍ መርከብ ውስጥ ተገልለው የሚገኙ ዜጎቿን ወደ ሀገሯ ልትመልስ ነው።
ቶኪዮ የሚገኘው የዩ ኤስ ኤምባሲ እንዳስታወቀው አንድ አይሮፕላን ወደ ጃፓን በመላክ ዜጎቹን ወደ ካሊፎርኒያ እሁድ ዕለት ለመመለስ አቅዷል።
ዲያመንድ ፕሪንሰስ የተባለችው ትልቅ መርከብ ውስጥ ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ከተረጋገጠ አንስቶ መርከቧ ፎኮሹማ ወደብ አቅራቢያ ካለፈው ወር አንስቶ እንዳንትቀሳቀስ ታግታ ትገኛለች። በርካታ አገር ጎብኚዎች በተሳፈሩባት በዚችው መርከብ ውስጥ ዛሬ ብቻ 67 ሰዎች ቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል።
በዚህም የተነሳ የተያዙት ሰዎች ቁጥር ወደ 285 አሻቅቧል። በመርከቧ ላይ በጠቅላላው 3500 የሚሆኑ ሰዎች የሚገኙ ሲሆን ከነዚህም ውስጥ 380 የሚሆኑት አሜሪካውያን ናቸው።
Via:- DW
@YeneTube @Fikerassefa
ቶኪዮ የሚገኘው የዩ ኤስ ኤምባሲ እንዳስታወቀው አንድ አይሮፕላን ወደ ጃፓን በመላክ ዜጎቹን ወደ ካሊፎርኒያ እሁድ ዕለት ለመመለስ አቅዷል።
ዲያመንድ ፕሪንሰስ የተባለችው ትልቅ መርከብ ውስጥ ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ከተረጋገጠ አንስቶ መርከቧ ፎኮሹማ ወደብ አቅራቢያ ካለፈው ወር አንስቶ እንዳንትቀሳቀስ ታግታ ትገኛለች። በርካታ አገር ጎብኚዎች በተሳፈሩባት በዚችው መርከብ ውስጥ ዛሬ ብቻ 67 ሰዎች ቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል።
በዚህም የተነሳ የተያዙት ሰዎች ቁጥር ወደ 285 አሻቅቧል። በመርከቧ ላይ በጠቅላላው 3500 የሚሆኑ ሰዎች የሚገኙ ሲሆን ከነዚህም ውስጥ 380 የሚሆኑት አሜሪካውያን ናቸው።
Via:- DW
@YeneTube @Fikerassefa
የቴዲ አፍሮ ኢትዮጵያ ወደ ፍቅር ኮንሰርት ቀጣይ ሳምንት ቅዳሜ የካቲት 14 መስቀል አደባባይ ይካሄዳል።
ቴዲ በመድረክ ላይ የ3 ሰዓት ቆይታ የሚያደርግ ሲሆን የመግቢያ ዋጋ ቪ.አይ.ፒ 500ብር መደበኛ 200 ብር ሲሆን ትኬቶቹም ከማክሰኞ ጀምሮ በሁሉም ዳሽን ባንክ ቅርንጫፎች ይሸጣሉ ተብሏል።
Via:- ዳሰሳ አዲስ
@yeneTube @Fikerassefa
ቴዲ በመድረክ ላይ የ3 ሰዓት ቆይታ የሚያደርግ ሲሆን የመግቢያ ዋጋ ቪ.አይ.ፒ 500ብር መደበኛ 200 ብር ሲሆን ትኬቶቹም ከማክሰኞ ጀምሮ በሁሉም ዳሽን ባንክ ቅርንጫፎች ይሸጣሉ ተብሏል።
Via:- ዳሰሳ አዲስ
@yeneTube @Fikerassefa
የኦሮሞ ሚዲያ ኔትወርክ ዳይሬክተር ግርማ ጉተማ አርቲስት ልጅ ያሬድ በቡራዩ ከተማ መታሰሩን አስታውቋል።
በተጨማሪም በዜግነት ኖርዌያዊ የሆነች ሀዊ የተባለች አርቲስት ለጊዜው ባልታወቀ የፀጥታ አስከባሪ ክፉኛ ተጎድታ ሆስፒታል መግባቷን በግርማ ጉቱማ ገፅ እና ከOMN ሚዲያ የፌስቡክ ገፅ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
OMN ለብራዩ ከተማ ከንቲባ ስልክ ቢሞክርም እንዳልተሳካለት አስነብቧል።
በዚህ ጉዳይ ላይ ነገ በሰፊው የምንመለስበት ይሆናል።
@Yenetube @Fikerassefa
በተጨማሪም በዜግነት ኖርዌያዊ የሆነች ሀዊ የተባለች አርቲስት ለጊዜው ባልታወቀ የፀጥታ አስከባሪ ክፉኛ ተጎድታ ሆስፒታል መግባቷን በግርማ ጉቱማ ገፅ እና ከOMN ሚዲያ የፌስቡክ ገፅ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
OMN ለብራዩ ከተማ ከንቲባ ስልክ ቢሞክርም እንዳልተሳካለት አስነብቧል።
በዚህ ጉዳይ ላይ ነገ በሰፊው የምንመለስበት ይሆናል።
@Yenetube @Fikerassefa
ሀይቲ ውስጥ በአንድ የልጆች ማሣደጊያ ጣቢያ ውስጥ በደረሰ ቃጠሎ የ15 ልጆች ህይወት ማለፉን ባለስልጣናት አስታወቁ።
የሁለቱ ልጆች ህይወት እዛው ማሣደጊያ ጣቢያው ውስጥ ሲያልፍ የሌሎች 13 ደግሞ ሀኪም ቤት ከደረሱ በኋላ በቃጠሎው ጭስ ምክንያት ህይወታቸው ማለፉ ተዘግቧል።
በዚሁ መንግስታዊ ባልሆነው የልጆች ማሳደጊያ ጣቢያ ውስጥ 66 ህፃናት ይኖሩ ነበር። አንድ የጣቢያው ሰራተኛ ለፈረንሳይ ዜና ምንጭ እንደገለፁት እሳቱ የተነሳው ሀሙስ ዕለት በሀገሪቱ የሰዓት አቆጣጠር ከምሽቱ ሶስት ሰአት አካባቢ ሲሆን የእሳት አደጋ ሰራተኞች ስፍራው እስኪደርሱም 90 ደቂቃ ያህል ፈጅቷል።
በዚሁ ወላጆቻቸውን ያጡ ልጆች ማሳደጊያ ጣቢያ ውስጥ መብራት ስላልነበረ ሻማ ይጠቀሙ እንደነበርም ሰራተኛዋ ተናግረዋል። ከሟቾቹ መካከል አብዛኞቹ ገና ጨቅላዎች እንደነበሩ ተዘግቧል።
የካረቢክ ደሴቷ ሀገር ሀይቲ እኢአ በ 2010 ዓ ም ከደረሰባት ከፍተኛ የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋ አሁንም አላገገመችም። በዚሁ አደጋ ከ 200 ሺ በላይ ሰዎች ህይወት የጠፋ ሲሆን ከ 1,5 ሚሊዮን በላይ ህዝብ ቤት አልባ ሆኗል።
Via:- DW
@YeneTube @Fikerassefa
የሁለቱ ልጆች ህይወት እዛው ማሣደጊያ ጣቢያው ውስጥ ሲያልፍ የሌሎች 13 ደግሞ ሀኪም ቤት ከደረሱ በኋላ በቃጠሎው ጭስ ምክንያት ህይወታቸው ማለፉ ተዘግቧል።
በዚሁ መንግስታዊ ባልሆነው የልጆች ማሳደጊያ ጣቢያ ውስጥ 66 ህፃናት ይኖሩ ነበር። አንድ የጣቢያው ሰራተኛ ለፈረንሳይ ዜና ምንጭ እንደገለፁት እሳቱ የተነሳው ሀሙስ ዕለት በሀገሪቱ የሰዓት አቆጣጠር ከምሽቱ ሶስት ሰአት አካባቢ ሲሆን የእሳት አደጋ ሰራተኞች ስፍራው እስኪደርሱም 90 ደቂቃ ያህል ፈጅቷል።
በዚሁ ወላጆቻቸውን ያጡ ልጆች ማሳደጊያ ጣቢያ ውስጥ መብራት ስላልነበረ ሻማ ይጠቀሙ እንደነበርም ሰራተኛዋ ተናግረዋል። ከሟቾቹ መካከል አብዛኞቹ ገና ጨቅላዎች እንደነበሩ ተዘግቧል።
የካረቢክ ደሴቷ ሀገር ሀይቲ እኢአ በ 2010 ዓ ም ከደረሰባት ከፍተኛ የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋ አሁንም አላገገመችም። በዚሁ አደጋ ከ 200 ሺ በላይ ሰዎች ህይወት የጠፋ ሲሆን ከ 1,5 ሚሊዮን በላይ ህዝብ ቤት አልባ ሆኗል።
Via:- DW
@YeneTube @Fikerassefa
የአየር መንገድ ሰራተኞች በነፃ ትኬት ተጉዘው ለሚያመጡት እቃ ሶስት እጥፍ ቀረጥ መጣሉ ከፍተኛ ቅሬታን ፈጠረ
የገቢዎች ሚኒስቴር አየር መንገድ ለሰራተኞቹ በሚሰጠው ነፃ ትኬት የንግድ እቃዎችን በብዛት እየመጡ ሰለሆነ ማንኛውም በነፃ ትኬት ውጭ የሚሄድ የአየር መንገድ ሰራተኛ ይዞ በሚመጣው እቃ ላይ ሶስት እጥፍ ቀረጥ እጥላለው ማለቱ ከፍተኛ ቅሬታን ፈጥሯል።
ገቢዎች በዚህ አሰራሩ ለሌላውም መንገደኛ እንደሚያደርገው በቁጥር 60 በአይነት አራት ከቀረጥ ነፃ የሚፈቅደውን አልባሳት ለአየር መንገዱ ሰራተኞች ከልክሎ አንድም ልብስ ከውጭ ቢያመጡ እንደሚቀርጥ አስታውቋል።
ሚኔስቴሩ ከሳምንት በፊት ዱባይ በተጓዙ የአየር መንገዱ ሰራተኞች ላይ ተግባራዊ አርጎ ከዛም በተቃውሞ የጣለውን የሶስት እጥፍ ቀረጥ ያነሳ ቢሆንም አሰራሩ ሙሉ ለሙሉ ተግባራዊ መልሶ ተግባራዊ ይሆናል ተብሎ ይጠበቃል።
ይሄ አዲስ አሰራር በሁለት ሻንጣ ልብስ ላይ እሰከ መቶ ሺ ብር ድረስ ሊቀርጠን ይችላል በማለት የአየር መንገዱ ሰራተኞች ተቃውሞ አሰምተል።
በስልክ ለፊደል ፓስት ቅሬታዋን የገለፀቸው ሄለን የተባለች የአየር መንገዱ ሰራተኛ እንዳለችው ” እኛ ነፃ ትኬት አገኘን እንጂ ውጭ ስንሄድ ልብስ በነፃ አናመጣም ።እንድ መንገደኛ ከቀረጥ ነፃ የሚፈቀድ ነገረ ሊፈቀደልን ይገባል። ከዛ በላይ በሆነ ነገር ደግሞ እንደመንገደኛው ልንቀረጥ ይገባል። አዲሱ አሰራር አድሏዊ ነው።
የአየር መንገድ ሰራተኛ ለሀገሪቷ ትልቅ ገቢ እያስገባ ገና ለገና በነፃ ትኬት ሄደሀልና አንድም ልብስ ብታመጣ ትቀረጣለህ ማለት ለእኛ ክብር አለመስጠት ነው ” ብላለች ።
የአየር መንገዱ መሰረታዊ የሰራተኛ ማህበር ለሚኒስቴር መሰርያቤቱ በፃፈው ደብዳቤ በአመት ከሁለት ጉዞ በላይ በነፃ ትኬት ውጭ ደርሰው የሚመጡትን የአየር መንገዱን ሰራተኞች እንደ ነጋዴ ማየት ተገቢ አይደለም እንደከዚ በፊቱ መንገደኞች በሚቀረጡበት አይን ሊታዩ ይገባል በማለት አዲሱ መመርየ እንዲቀር ጠይቋል ።
Via:- FidelPost.com
@YeneTube @Fikerassefa
የገቢዎች ሚኒስቴር አየር መንገድ ለሰራተኞቹ በሚሰጠው ነፃ ትኬት የንግድ እቃዎችን በብዛት እየመጡ ሰለሆነ ማንኛውም በነፃ ትኬት ውጭ የሚሄድ የአየር መንገድ ሰራተኛ ይዞ በሚመጣው እቃ ላይ ሶስት እጥፍ ቀረጥ እጥላለው ማለቱ ከፍተኛ ቅሬታን ፈጥሯል።
ገቢዎች በዚህ አሰራሩ ለሌላውም መንገደኛ እንደሚያደርገው በቁጥር 60 በአይነት አራት ከቀረጥ ነፃ የሚፈቅደውን አልባሳት ለአየር መንገዱ ሰራተኞች ከልክሎ አንድም ልብስ ከውጭ ቢያመጡ እንደሚቀርጥ አስታውቋል።
ሚኔስቴሩ ከሳምንት በፊት ዱባይ በተጓዙ የአየር መንገዱ ሰራተኞች ላይ ተግባራዊ አርጎ ከዛም በተቃውሞ የጣለውን የሶስት እጥፍ ቀረጥ ያነሳ ቢሆንም አሰራሩ ሙሉ ለሙሉ ተግባራዊ መልሶ ተግባራዊ ይሆናል ተብሎ ይጠበቃል።
ይሄ አዲስ አሰራር በሁለት ሻንጣ ልብስ ላይ እሰከ መቶ ሺ ብር ድረስ ሊቀርጠን ይችላል በማለት የአየር መንገዱ ሰራተኞች ተቃውሞ አሰምተል።
በስልክ ለፊደል ፓስት ቅሬታዋን የገለፀቸው ሄለን የተባለች የአየር መንገዱ ሰራተኛ እንዳለችው ” እኛ ነፃ ትኬት አገኘን እንጂ ውጭ ስንሄድ ልብስ በነፃ አናመጣም ።እንድ መንገደኛ ከቀረጥ ነፃ የሚፈቀድ ነገረ ሊፈቀደልን ይገባል። ከዛ በላይ በሆነ ነገር ደግሞ እንደመንገደኛው ልንቀረጥ ይገባል። አዲሱ አሰራር አድሏዊ ነው።
የአየር መንገድ ሰራተኛ ለሀገሪቷ ትልቅ ገቢ እያስገባ ገና ለገና በነፃ ትኬት ሄደሀልና አንድም ልብስ ብታመጣ ትቀረጣለህ ማለት ለእኛ ክብር አለመስጠት ነው ” ብላለች ።
የአየር መንገዱ መሰረታዊ የሰራተኛ ማህበር ለሚኒስቴር መሰርያቤቱ በፃፈው ደብዳቤ በአመት ከሁለት ጉዞ በላይ በነፃ ትኬት ውጭ ደርሰው የሚመጡትን የአየር መንገዱን ሰራተኞች እንደ ነጋዴ ማየት ተገቢ አይደለም እንደከዚ በፊቱ መንገደኞች በሚቀረጡበት አይን ሊታዩ ይገባል በማለት አዲሱ መመርየ እንዲቀር ጠይቋል ።
Via:- FidelPost.com
@YeneTube @Fikerassefa