ወሒድ የዕቅበተ ኢሥላም መጣጥፍት"Wahid Articles of Islamic Apologetics"
58.4K subscribers
68 photos
69 videos
19 files
1.72K links
ዳዒ ወሒድ በኢሥላም እና በክርስትና መካከል ያለውን ልዩነት እና አንድነት በንጽጽር የሚያስቀምጥ ወንድም ነው። ለዚህም የቋንቋ፣ የሰዋስው፣ የዐውድ፣ የተዛማች እና የሥነ አመክንዮ ሙግት በማቅረብ የሚታወቅ ተሟጋች እና ጦማሪ ነው። ለሙግቱ ነጥብ በዋነኝነት የሚጠቀምባቸው ቋንቋ ዐማርኛ፣ ግዕዝ፣ እንግሊዝኛ፣ ዐረቢኛ፣ ዕብራይስጥ እና ግሪክ ናቸው። መልካም የንባብ፣ የጥናት፣ የማነጻጸር ጊዜ ይሁንልዎ!
Download Telegram
2. የተዛማች ሙግት
ጋብቻን ጋብቻ ከሚያሰኘው አንዱ በህጋዊ እና እውቅና ተሰጦት መህርን ሰጥቶ ማግባት ነው፤ ከዚያ ውጪ እውቅና እና ህጋዊ ያልሆነ የሚስጢር ወዳጅ ወይም የስርቆሽ ወዳጅ ማለትም የከንፈር ወዳጅ ሆነ ዘማዊነት ማለትም አንሶላ መጋፈፍ ሃራም ነው፦
5፥5 ከምእምናት ጥብቆቹም ከነዚያ ከናንተ በፊት መጽሐፍን ክተሰጡት ሴቶች ጥብቆቹም ዘማዊዎች እና የሚስጢር ወዳጅ ያዢዎች ሳትሆኑ ጥብቆች ሆናችሁ “”መህሮቻቸውን በሰጠችኋቸው ጊዜ”” ልታገቡዋቸው የተፈቀዱ ናቸው፤
4:25 ከእናንተም ውስጥ ጥብቆች ምእምናት የሆኑትን ለማግባት ሀብትን ያልቻለ ሰው እጆቻችሁ ንብረት ካደረጓቸው ከምእመናት፣ ወጣቶቻችሁ ባሪያን ያግባ፤ አላህም እምነታችሁን ዐዋቂ ነው፤ ከፊላችሁ ከከፊሉ የተራባ ነው። ባሮችን በጌቶቻቸውም ፈቃድ አግቡዋቸው። “መህሮቻቸውንም” በመልካም መንገድ ስጧቸው፤ ጥብቆች ሆነው ዝሙተኞች ያልሆኑ የስርቆሽ ወዳጆችንም ያልያዙ ሲኮኑ አግቧቸው፤

“በገንዘቦቻችሁ ልትፈልጉ ተፈቀደ” የተባለው ገንዘብ መህር መሆኑ ሌሎች አንፆች ያስረዳሉ፦
60፥10 ያወጡትንም “ገንዘብ” ስጧቸው፤ “መህራቸውንም” በሰጣችኋቸው ጊዜ ብታገቡዋቸው በእናንተ ላይ ኃጢያት የለባችሁም።
4፥4 ሴቶችንም መህሮቻቸውን በደስታ ስጡ፡፡ ለእናንተም ከእርሱ አንዳችን ነገር ነፍሶቻቸው ቢለግሱ መልካም ምስጉን ሲኾን ብሉት፡፡
4፥19 እናንተ ያመናችሁ ሰዎች ሆይ! ሴቶችን ያስገደዳችሁ ኾናችሁ ልትወርሱና ግልጽን መጥፎ ሥራ ካልሠሩ በስተቀር ከሰጣችኋቸው ከፊሉን ልትወስዱ ልታጉላሏቸውም ለእናንተ አይፈቀድም፤ በመልካምም ተኗኗሩዋቸው፤ ብትጠሉዋቸውም ታገሱ፡፡ አንዳችን ነገር ብትጠሉ አላህም በእርሱ ብዙ ደግ ነገርን ሊያደርግ ይቻላልና፡፡

መደምደሚያ
ለመሆኑ ባይብል ስለ ጥሎሽ ምን ይላል? በባይብል ላይ ጥሎሽ የተባለው ቃል “ማጫ” ይባላል፤ ይህም ለትዳት የሚሰጥ ንብረት ነው፤ አንድ ወንድ ከጋብቻ በፊት ሴትን ቢደፍራት ማጫዋን ሰጥቶ ሚስት ያደርጋታል፤ ይህም መህር አምሳ የብር ሰቅል ነው፦
ዘፍጥረት 34፥12 ብዙ “ማጫ” እና እጅ መንሻ አምጣ በሉኝ፥ በነገራችሁኝም መጠን እሰጣለሁ፤ ይህችን ብላቴና ግን “አጋቡኝ”።
ዘጸአት 22፥16 ሰው ያልታጨችውን ድንግል ቢያስታት፥ ከእርስዋም ጋር ቢተኛ፥ “ማጫዋን” ሰጥቶ ሚስት ያድርጋት።
ዘዳግም 22፥29 ያ የደረሰባት ሰው አምሳ የብር ሰቅል ለብላቴናይቱ አባት ይስጥ፤ አስነውሮአታልና ሚስት ትሁነው፤ በዕድሜውም ዘመን ሁሉ ሊፈታት አይገባውም።

ዳዊት ሜልኮልን ለማግባት የሰጠው መህር የመቶ ወንድ ብልት ቆርጦ ነው፦
1ኛ ሳሙኤል 18፥25-27 ሳኦልም ዳዊትን በፍልስጥኤማውያን እጅ ይጥለው ዘንድ አስቦ፦ የንጉሥን ጠላቶች ይበቀል ዘንድ #ከመቶ ፍልስጥኤማውያን #ሸለፈት በቀር ንጉሥ ማጫ አይሻም ብላችሁ ለዳዊት ንገሩት አላቸው። የሳኦልም ባሪያዎች ይህን ቃል ለዳዊት ነገሩት፥ ለንጉሥም አማች ይሆን ዘንድ ዳዊትን ደስ አሰኘው። ዳዊትና ሰዎቹም ተነሥተው ሄዱ፥ ከፍልስጥኤማውያንም #መቶ ሰዎች ገደሉ፤ ዳዊትም ለንጉሥ አማች ይሆን ዘንድ ሰለባቸውን አምጥቶ በቍጥራቸው ልክ ለንጉሡ ሰጠ። ሳኦልም ልጁን ሜልኮልን ዳረለት።

የወንድ ብልት መህር? ይህ ነው እንግዲህ መህር።

ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሰላሙ አለይኩም
መደምደሚያ
ለመሆኑ ባይብል ስለ ጥሎሽ ምን ይላል? በባይብል ላይ ጥሎሽ የተባለው ቃል “ማጫ” ይባላል፤ ይህም ለትዳት የሚሰጥ ንብረት ነው፤ አንድ ወንድ ከጋብቻ በፊት ሴትን ቢደፍራት ማጫዋን ሰጥቶ ሚስት ያደርጋታል፤ ይህም መህር አምሳ የብር ሰቅል ነው፦
ዘፍጥረት 34፥12 ብዙ “ማጫ” እና እጅ መንሻ አምጣ በሉኝ፥ በነገራችሁኝም መጠን እሰጣለሁ፤ ይህችን ብላቴና ግን “አጋቡኝ”።
ዘጸአት 22፥16 ሰው ያልታጨችውን ድንግል ቢያስታት፥ ከእርስዋም ጋር ቢተኛ፥ “ማጫዋን” ሰጥቶ ሚስት ያድርጋት።
ዘዳግም 22፥29 ያ የደረሰባት ሰው አምሳ የብር ሰቅል ለብላቴናይቱ አባት ይስጥ፤ አስነውሮአታልና ሚስት ትሁነው፤ በዕድሜውም ዘመን ሁሉ ሊፈታት አይገባውም።

ዳዊት ሜልኮልን ለማግባት የሰጠው መህር የመቶ ወንድ ብልት ቆርጦ ነው፦
1ኛ ሳሙኤል 18፥25-27 ሳኦልም ዳዊትን በፍልስጥኤማውያን እጅ ይጥለው ዘንድ አስቦ፦ የንጉሥን ጠላቶች ይበቀል ዘንድ #ከመቶ ፍልስጥኤማውያን #ሸለፈት በቀር ንጉሥ ማጫ አይሻም ብላችሁ ለዳዊት ንገሩት አላቸው። የሳኦልም ባሪያዎች ይህን ቃል ለዳዊት ነገሩት፥ ለንጉሥም አማች ይሆን ዘንድ ዳዊትን ደስ አሰኘው። ዳዊትና ሰዎቹም ተነሥተው ሄዱ፥ ከፍልስጥኤማውያንም #መቶ ሰዎች ገደሉ፤ ዳዊትም ለንጉሥ አማች ይሆን ዘንድ ሰለባቸውን አምጥቶ በቍጥራቸው ልክ ለንጉሡ ሰጠ። ሳኦልም ልጁን ሜልኮልን ዳረለት።

የወንድ ብልት መህር? ይህ ነው እንግዲህ መህር።

ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሰላሙ አለይኩም