ወሒድ የዕቅበተ ኢሥላም መጣጥፍት"Wahid Articles of Islamic Apologetics"
58.3K subscribers
68 photos
69 videos
19 files
1.72K links
ዳዒ ወሒድ በኢሥላም እና በክርስትና መካከል ያለውን ልዩነት እና አንድነት በንጽጽር የሚያስቀምጥ ወንድም ነው። ለዚህም የቋንቋ፣ የሰዋስው፣ የዐውድ፣ የተዛማች እና የሥነ አመክንዮ ሙግት በማቅረብ የሚታወቅ ተሟጋች እና ጦማሪ ነው። ለሙግቱ ነጥብ በዋነኝነት የሚጠቀምባቸው ቋንቋ ዐማርኛ፣ ግዕዝ፣ እንግሊዝኛ፣ ዐረቢኛ፣ ዕብራይስጥ እና ግሪክ ናቸው። መልካም የንባብ፣ የጥናት፣ የማነጻጸር ጊዜ ይሁንልዎ!
Download Telegram
ጣዖት እና አምልኮ

ክፍል ሁለት

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡

ነጥብ አንድ
“ጣዖት”
በዕብራይስጥ “ኤሊል” אֱלִיל ማለት “ምስል”፣ “ቅርፅ”፣ “ጣዖት” ማለት ሲሆን በግሪክ ደግሞ “ኤዶሎን” εἴδωλον ነው፤ ትርጉሙ ተመሳሳይ የሙሴ አምላክ ለሙሴ “”ለእናንተ ጣዖት አታድርጉ፥ የተቀረጸም ምስል ወይም ሐውልት አታቁሙ፤ ትሰግዱለትም ዘንድ በምድራችሁ ላይ የተቀረጸ ድንጋይ አታኑሩ፣ የማናቸውንም ምሳሌ፥ የተቀረጸውንም ምስል ለአንተ አታድርግ፣ አትስገድላቸው፥ አታምልካቸውምም”” ብሎ ተናግሯል፦
ዘሌዋውያን 26፥1 እኔ ያህዌህ አምላካችሁ ነኝና ለእናንተ #ጣዖት አታድርጉ፥ የተቀረጸም ምስል ወይም ሐውልት አታቁሙ፤ ትሰግዱለትም ዘንድ በምድራችሁ ላይ የተቀረጸ ድንጋይ አታኑሩ።
ዘጸአት 20፥4 በላይ በሰማይ ካለው፥ በታችም በምድር ካለው፥ ከምድርም በታች በውኃ ካለው ነገር #የማናቸውንም #ምሳሌ#የተቀረጸውንም #ምስል ለአንተ አታድርግ፤ አትስገድላቸው፥ አታምልካቸውምም፤

የሙሴ አምላክ ይናገራል እንጂ መልኩን ይህንን ይመስላል ብሎ በወንድ ሽማሌዎች ቅርፅና ምስል ማቅረብ እጅግ ወንጀል ነው፦
ዘዳግም 4፥15-18 ያህዌህ በኮሬብ በእሳት ውስጥ ሆኖ በተናገራችሁ ጊዜ #መልክ ከቶ #አላያችሁምና እጅግ ተጠንቀቁ፤ እንዳትረክሱ፥ #የተቀረጸውን #ምስል #የማናቸውንም ነገር #ምሳሌ#በወንድ ወይም #በሴት #መልክ የተሠራውን፥ በምድር ላይ ያለውን የእንስሳን ሁሉ ምሳሌ፥ በሰማይም በታች የሚበርረውን የወፍን ሁሉ ምሳሌ፥ በምድርም ላይ የሚሽከረከረውን ሁሉ ምሳሌ፥ ከምድርም በታች በውኃ ውስጥ የሚኖረውን የዓሣን ሁሉ #ምሳሌ #እንዳታደርጉ

በተለይ የሥላሴ ሁለቱ አባላት ካልታዩ በሽማግሌ ሰዎች መመሰሉ ምን አይነት ጣራ የነካ ወንጀል ነው? ከእስራኤል ልጆች ዙርያ ያሉት ህዝቦች ጣዖታቶቻቸው የወርቅና የብር፥ የሰው እጅ ሥራ ናቸው። አፍ አላቸው አይናገሩምም፤ ዓይን አላቸው አያዩምም፤ ጆሮ አላቸው አይሰሙምም፤ አፍንጫ አላቸው አያሸትቱምም፤ እጅ አላቸው አይዳሰሱምም፤ እግር አላቸው አይሄዱምም፤ በጕሮሮአቸውም አይናገሩም ነበር፤ ይህ ለተቀረጸ ምስል የሚሰግዱ ሁሉና የሚመኩ የሚያሳፍ ነበር፦
መዝሙር 115፥4-7 የአሕዛብ ጣዖታቶች የወርቅና የብር፥ የሰው እጅ ሥራ ናቸው። አፍ አላቸው አይናገሩምም፤ ዓይን አላቸው አያዩምም፤ ጆሮ አላቸው አይሰሙምም፤ አፍንጫ አላቸው አያሸትቱምም፤ እጅ አላቸው አይዳሰሱምም፤ እግር አላቸው አይሄዱምም፤ በጕሮሮአቸውም አይናገሩም።
መዝሙር 97፥7 #ለተቀረጸ #ምስል የሚሰግዱ ሁሉ፥ #በጣዖቶቻቸውም የሚመኩ ይፈሩ፤

የጣኦት አምልኮ በምስል እና በሃውልት ሲሆን ይህንን ድርጊት ሲደረግ ያየ ሰው አቀጣጡ ማንኮታኮትና ማቃጠል ነው፦
ዘዳግም 12፥3 መሠዊያቸውንም አፍርሱ፥ ሐውልቶቻቸውንም ሰባብሩ፥ የማምለኪያ ዐፀዶቻቸውንም በእሳት አቃጥሉ፥ የአማልክቶቻቸውንም #የተቀረጹ #ምስሎች #አንከታክቱ
ዘዳግም 7፣25 #የተቀረጸውንም የአምላኮቻቸውን #ምስል #በእሳት #ታቃጥላለህ፤ የተሠራባቸውን ብርና ወርቅ አትመኝ፤ በአምላክህም በእግዚአብሔር ዘንድ ርኩስ ነውና እንዳትጠመድበት ከእርሱ ምንም አትውሰድ።

በትንሳኤ ቀንም ቅጣቱ ጀሃነም ነው፦
ራዕይ 21፥8 ዳሩ ግን የሚፈሩና የማያምኑ የርኵሳንም የነፍሰ ገዳዮችም የሴሰኛዎችም የአስማተኛዎችም #ጣዖትንም #የሚያመልኩ የሐሰተኛዎችም ሁሉ ዕድላቸው በዲንና በእሳት በሚቃጠል ባሕር ነው፤ ይኸውም ሁለተኛው ሞት ነው።

ራዕይ ላይ “ጣዖትን ማምለክ” ተብሎ የተቀመጠው የግሪኩ ቃል “ኤዶልላትሬአ” εἰδωλολατρεία ሲሆን የሁለት ቃላት ውቅር ነው፤ እርሱም፦ “ኤዶሎን” εἴδωλον “ምስል” እና
“ላትሬኦ” λατρεύω “አምልኮ” ነው፤ ይህም ቃል አዲስ ኪዳን ላይ 7 ጊዜ ተጠቅሟል። ይህንን በሚቀጥለው ነጥብ ስለ አምልኮ እንቀጥል፦
የአላህ ባህርይ

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።

ኢማም ሙስሊም መጽሐፍ 53, ሐዲስ 32
አቢ ሁረይራህ"ረ.አ." እንደተረከው የአላህ መልእክተኛ"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ አላህ አዝዘ ወጀል አደምን ስልሳ ኩብ ቁመት አድርጎ በራሱ "መልክ" ፈጠረው። خَلَقَ اللَّهُ عَزَّ وَجَلَّ آدَمَ عَلَى صُورَتِهِ طُولُهُ سِتُّونَ ذِرَاعًا.
ኢማም ቡኻሪይ መጽሐፍ 79, ሐዲስ 1
አቢ ሁረይራህ"ረ.አ." እንደተረከው የአላህ መልእክተኛ"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ አላህ አደምን ስልሳ ኩብ ቁመት አድርጎ በራሱ "መልክ" ፈጠረው። خَلَقَ اللَّهُ آدَمَ عَلَى صُورَتِهِ، طُولُهُ سِتُّونَ ذِرَاعًا،

የቋንቋው ሊሂቃን "ሱራ" صورة ማለት "መልክ" image" ብለው ያስቀመጡት ሲሆን ይህም "መልክ" ባህርይ ለማመልከት እንደሚመጣ ይናገራሉ፦
ኢማም ቡኻሪይ መጽሐፍ 60 ሐዲስ 2
አቢ ሁረይራህ"ረ.አ." እንደተረከው የአላህ መልእክተኛ"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ የመጀመሪያው ግሩፕ በሌሊት ሙሉ እንደሆነች በጨረቃ "#መልክ" صُورَةِ ሆኖ ወደ ጀነት ይገባሉ። إِنَّ أَوَّلَ زُمْرَةٍ يَدْخُلُونَ الْجَنَّةَ عَلَى صُورَةِ الْقَمَرِ لَيْلَةَ الْبَدْرِ،

በዚህ ሐዲስ ላይ መቼም የጨረቃ መልክ የጨረቃን ቅርፅና ክብደት ለማመልከት ነው ከተባለ የጨረቃ ቅርጷ 1958×1010 km3 እንዲሁ ክብደቷ 7.342×1022 kg ነው፤ ያ ማለት ሰው ጀነት የሚገባው በጨረቃ ቅርፅና ክብደት ነው ማለት ሳይሆን የጨረቃ ባህርይ የሆኑን ንፅህናዋን፣ ድምቀቷ እና ውበቷን ማለቱ ነው፤ እንግዲህ "ሱራ" صورة "መልክ" የአንድን ህላዌ ባህርይ ለማመልከት ከመጣ ይህም "መልክ" ማየት፣ መስማት፣ ማወቅ የሚባሉትን ባህርያት ያቅፋል፤ አላህ ሁሉን ነገር ተመልካች፣ ሁሉን ነገር ሰሚ እና ሁሉን ነገር አዋቂ ነው፤ አላህ አደምን ሲፈጥረው በባህርያቱ የሚያይበት አይን፣ የሚሰማበት ጆሮ እና የሚያውቅበት ልብ"አንጎል" ሰቶታል ማለት ነው፦
67:23 እርሱ ያ የፈጠራችሁ ለእናንተም "#መስሚያ" እና "#ማያዎችን" "#ልቦችንም" ያደረገላችሁ ነው፤ ጥቂትንም አታመሰግኑም በላቸው።
23፥78 እርሱም ያ "#መስሚያዎችንና" "#ማያዎችን" "#ልቦችንም" ለእናንተ የፈጠረላችሁ ነው፤ ጥቂትን እንጅ አታመሰግኑም፡፡

አላህ "የሚመስለው ምንም ነገር የለም" አላህ ሰሚው" "ተመልካቹ" ነው፦
42:11"የሚመስለው" ምንም ነገር የለም፤ እርሱም "ሰሚው" "ተመልካቹ" ነው።

አላህ ሰሚ" እና "ተመልካች" ነው እንደተባለ ሁሉ ሰውም ሰሚ" እና "ተመልካች" ነው ተብሏል፦
76:2 እኛ ሰዉን፥ በሕግ ግዳጅ የምንሞክረዉ ስንሆን፥ ቅልቅሎች ከሆኑ የፍትወት ጠብታ ፈጠርነዉ፤ "ሰሚ" "ተመልካችም" አደረግነዉ።

ነገር ግን አላህ ሰሚ" እና "ተመልካች" ነው የተባለው ሰው ሰሚ" እና "ተመልካች" በተባለበት ሂሳብ አይደለም፤ ምክንያቱም አላህ ሁሉን ነገር ይሰማል ያያል፤ ይህ ባህርይ ጊዜና ቦታ አይገድበውም፤ ሰው ግን ያለ ብርሃን ማየት እና ያለ ድምፅ መስማት አይችልም፤ በተመሳሳይ አላህ ሁሉን አዋቂን ነው እውቀቱ በጊዜና በቦታ አይገደብም፤ ሰው ግን እውቀቱ ጊዜ እና ቦታ ይገድበዋል፦
58:6 አላህም በነገሩ ሁሉ ላይ አዋቂ ነው።
67:19 እርሱ በነገር ሁሉ ተመልካች ነው።
4:86 አላህ በነገሩ ሁሉ ላይ ተቆጣጣሪ ነውና።
39:62 እርሱም በነገሩ ሁሉ ላይ አስተናባሪ ነው።
33:27 አላህም በነገሩ ሁሉ ላይ ቻይ ነው።

የሰው መስሚያ፣ ማያም፣ ልብም ከአላህ የሆኑ ፀጋ ሲሆኑ ከእንስሳ በተለየ መልኩ ይሰሩት በነበሩት ሁሉ ተጠያቂ ናቸው፦
17:36 ለአንተም በእርሱ ዕውቀት የሌለህን ነገር አትከተል፤ #መስሚያ#ማያም#ልብም፣ እነዚህ ሁሉ ባለቤታቸው ከእነርሱ #ተጠያቂ ነውና إِنَّ السَّمْعَ وَالْبَصَرَ وَالْفُؤَادَ كُلُّ أُولَٰئِكَ كَانَ عَنْهُ مَسْئُولًا ።
102:8 ከዚያም #ከጸጋዎቻችሁ النَّعِيمِ ሁሉ በዚያ ቀን #ትጠየቃላችሁ ثُمَّ لَتُسْأَلُنَّ يَوْمَئِذٍ عَنِ النَّعِيمِ ።
16:93 ትሠሩት ከነበራችሁትም ሁሉ በእርግጥ #ትጠየቃላችሁ" وَلَتُسْأَلُنَّ عَمَّا كُنْتُمْ تَعْمَلُونَ ።

የአላህ ዛት የራሱ ሲፋ አለው ማየት፣ መስማት፣ መናገር፣ ማወቅ እና እጅ ግን ከፍጡራን ማየት፣ መስማት፣ ማወቅ፣ መናገር እና እጅ ጋር አይመሳሰልም። ለምሳሌ የሰው እጅ ቀኝና ግራ ነው የአላህ እጆች ግን ቀኝ ናቸው፦
ኢማም ሙስሊም 33, ሐዲስ 21 ፍትኸኞች አላህ ዘንድ በብርሃን መንበሮች ላይ ከአር-ረህማን በስ-ተቀኝ በኩል ይሆናሉ፤ ሁለቱም እጆቹ #ቀኝ ናቸው። " ﺇِﻥَّ ﺍﻟْﻤُﻘْﺴِﻄِﻴﻦَ ﻋِﻨْﺪَ ﺍﻟﻠَّﻪِ ﻋَﻠَﻰ ﻣَﻨَﺎﺑِﺮَ ﻣِﻦْ ﻧُﻮﺭٍ ﻋَﻦْ ﻳَﻤِﻴﻦِ ﺍﻟﺮَّﺣْﻤَﻦِ ﻋَﺰَّ ﻭَﺟَﻞَّ ﻭَﻛِﻠْﺘَﺎ ﻳَﺪَﻳْﻪِ ﻳَﻤِﻴﻦٌ ﺍﻟَّﺬِﻳﻦَ ﻳَﻌْﺪِﻟُﻮﻥَ ﻓِﻲ ﺣُﻜْﻤِﻬِﻢْ ﻭَﺃَﻫْﻠِﻴﻬِﻢْ ﻭَﻣَﺎ ﻭَﻟُﻮﺍ "

አላህ በራሱ ባህርይ ፈጠረው ማለት ለምሳሌ አላህ አደምን በእጁ ፈጥሮታል፦
38፥75 አላህም «ኢብሊስ ሆይ! *"በሁለት እጆቼ"* "ለፈጠርኩት" ከመስገድ ምን ከለከለህ? አሁን ኮራህን? ወይስ ከትዕቢተኞቹ ነበርክ?» አለው፡፡ قَالَ يَٰٓإِبْلِيسُ مَا مَنَعَكَ أَن تَسْجُدَ لِمَا خَلَقْتُ بِيَدَىَّ ۖ أَسْتَكْبَرْتَ أَمْ كُنتَ مِنَ ٱلْعَالِينَ
36፥71 እኛ *"እጆቻችን ከሠሩት"* ለእነርሱ እንስሳዎችን መፍጠራችንን አያውቁምን? እነርሱም ለእርሷ ባለ መብቶች ናቸው፡፡ أَوَلَمْ يَرَوْا۟ أَنَّا خَلَقْنَا لَهُم مِّمَّا عَمِلَتْ أَيْدِينَآ أَنْعَٰمًۭا فَهُمْ لَهَا مَٰلِكُونَ

እጅ የአላህ ባህርይ ነው፤ ኹን የሚለው ንግግሩ የራሱ ባህርይ ነው፤ በባህርይው አደምን ፈጥሮታል።

ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሰላሙ አለይኩም
የአላህ ባህርይ

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።

ኢማም ሙስሊም መጽሐፍ 53, ሐዲስ 32
አቢ ሁረይራህ"ረ.አ." እንደተረከው የአላህ መልእክተኛ"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ አላህ አዝዘ ወጀል አደምን ስልሳ ኩብ ቁመት አድርጎ በራሱ "መልክ" ፈጠረው። خَلَقَ اللَّهُ عَزَّ وَجَلَّ آدَمَ عَلَى صُورَتِهِ طُولُهُ سِتُّونَ ذِرَاعًا.
ኢማም ቡኻሪይ መጽሐፍ 79, ሐዲስ 1
አቢ ሁረይራህ"ረ.አ." እንደተረከው የአላህ መልእክተኛ"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ አላህ አደምን ስልሳ ኩብ ቁመት አድርጎ በራሱ "መልክ" ፈጠረው። خَلَقَ اللَّهُ آدَمَ عَلَى صُورَتِهِ، طُولُهُ سِتُّونَ ذِرَاعًا،

የቋንቋው ሊሂቃን "ሱራ" صورة ማለት "መልክ" image" ብለው ያስቀመጡት ሲሆን ይህም "መልክ" ባህርይ ለማመልከት እንደሚመጣ ይናገራሉ፦
ኢማም ቡኻሪይ መጽሐፍ 60 ሐዲስ 2
አቢ ሁረይራህ"ረ.አ." እንደተረከው የአላህ መልእክተኛ"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ የመጀመሪያው ግሩፕ በሌሊት ሙሉ እንደሆነች በጨረቃ "#መልክ" صُورَةِ ሆኖ ወደ ጀነት ይገባሉ። إِنَّ أَوَّلَ زُمْرَةٍ يَدْخُلُونَ الْجَنَّةَ عَلَى صُورَةِ الْقَمَرِ لَيْلَةَ الْبَدْرِ،

በዚህ ሐዲስ ላይ መቼም የጨረቃ መልክ የጨረቃን ቅርፅና ክብደት ለማመልከት ነው ከተባለ የጨረቃ ቅርጷ 1958×1010 km3 እንዲሁ ክብደቷ 7.342×1022 kg ነው፤ ያ ማለት ሰው ጀነት የሚገባው በጨረቃ ቅርፅና ክብደት ነው ማለት ሳይሆን የጨረቃ ባህርይ የሆኑን ንፅህናዋን፣ ድምቀቷ እና ውበቷን ማለቱ ነው፤ እንግዲህ "ሱራ" صورة "መልክ" የአንድን ህላዌ ባህርይ ለማመልከት ከመጣ ይህም "መልክ" ማየት፣ መስማት፣ ማወቅ የሚባሉትን ባህርያት ያቅፋል፤ አላህ ሁሉን ነገር ተመልካች፣ ሁሉን ነገር ሰሚ እና ሁሉን ነገር አዋቂ ነው፤ አላህ አደምን ሲፈጥረው በባህርያቱ የሚያይበት አይን፣ የሚሰማበት ጆሮ እና የሚያውቅበት ልብ"አንጎል" ሰቶታል ማለት ነው፦
67:23 እርሱ ያ የፈጠራችሁ ለእናንተም "#መስሚያ" እና "#ማያዎችን" "#ልቦችንም" ያደረገላችሁ ነው፤ ጥቂትንም አታመሰግኑም በላቸው።
23፥78 እርሱም ያ "#መስሚያዎችንና" "#ማያዎችን" "#ልቦችንም" ለእናንተ የፈጠረላችሁ ነው፤ ጥቂትን እንጅ አታመሰግኑም፡፡

አላህ "የሚመስለው ምንም ነገር የለም" አላህ ሰሚው" "ተመልካቹ" ነው፦
42:11"የሚመስለው" ምንም ነገር የለም፤ እርሱም "ሰሚው" "ተመልካቹ" ነው።

አላህ ሰሚ" እና "ተመልካች" ነው እንደተባለ ሁሉ ሰውም ሰሚ" እና "ተመልካች" ነው ተብሏል፦
76:2 እኛ ሰዉን፥ በሕግ ግዳጅ የምንሞክረዉ ስንሆን፥ ቅልቅሎች ከሆኑ የፍትወት ጠብታ ፈጠርነዉ፤ "ሰሚ" "ተመልካችም" አደረግነዉ።

ነገር ግን አላህ ሰሚ" እና "ተመልካች" ነው የተባለው ሰው ሰሚ" እና "ተመልካች" በተባለበት ሂሳብ አይደለም፤ ምክንያቱም አላህ ሁሉን ነገር ይሰማል ያያል፤ ይህ ባህርይ ጊዜና ቦታ አይገድበውም፤ ሰው ግን ያለ ብርሃን ማየት እና ያለ ድምፅ መስማት አይችልም፤ በተመሳሳይ አላህ ሁሉን አዋቂን ነው እውቀቱ በጊዜና በቦታ አይገደብም፤ ሰው ግን እውቀቱ ጊዜ እና ቦታ ይገድበዋል፦
58:6 አላህም በነገሩ ሁሉ ላይ አዋቂ ነው።
67:19 እርሱ በነገር ሁሉ ተመልካች ነው።
4:86 አላህ በነገሩ ሁሉ ላይ ተቆጣጣሪ ነውና።
39:62 እርሱም በነገሩ ሁሉ ላይ አስተናባሪ ነው።
33:27 አላህም በነገሩ ሁሉ ላይ ቻይ ነው።

የሰው መስሚያ፣ ማያም፣ ልብም ከአላህ የሆኑ ፀጋ ሲሆኑ ከእንስሳ በተለየ መልኩ ይሰሩት በነበሩት ሁሉ ተጠያቂ ናቸው፦
17:36 ለአንተም በእርሱ ዕውቀት የሌለህን ነገር አትከተል፤ #መስሚያ#ማያም#ልብም፣ እነዚህ ሁሉ ባለቤታቸው ከእነርሱ #ተጠያቂ ነውና إِنَّ السَّمْعَ وَالْبَصَرَ وَالْفُؤَادَ كُلُّ أُولَٰئِكَ كَانَ عَنْهُ مَسْئُولًا ።
102:8 ከዚያም #ከጸጋዎቻችሁ النَّعِيمِ ሁሉ በዚያ ቀን #ትጠየቃላችሁ ثُمَّ لَتُسْأَلُنَّ يَوْمَئِذٍ عَنِ النَّعِيمِ ።
16:93 ትሠሩት ከነበራችሁትም ሁሉ በእርግጥ #ትጠየቃላችሁ" وَلَتُسْأَلُنَّ عَمَّا كُنْتُمْ تَعْمَلُونَ ።

የአላህ ዛት የራሱ ሲፋ አለው ማየት፣ መስማት፣ መናገር፣ ማወቅ እና እጅ ግን ከፍጡራን ማየት፣ መስማት፣ ማወቅ፣ መናገር እና እጅ ጋር አይመሳሰልም። ለምሳሌ የሰው እጅ ቀኝና ግራ ነው የአላህ እጆች ግን ቀኝ ናቸው፦
ኢማም ሙስሊም 33, ሐዲስ 21 ፍትኸኞች አላህ ዘንድ በብርሃን መንበሮች ላይ ከአር-ረህማን በስ-ተቀኝ በኩል ይሆናሉ፤ ሁለቱም እጆቹ #ቀኝ ናቸው። " ﺇِﻥَّ ﺍﻟْﻤُﻘْﺴِﻄِﻴﻦَ ﻋِﻨْﺪَ ﺍﻟﻠَّﻪِ ﻋَﻠَﻰ ﻣَﻨَﺎﺑِﺮَ ﻣِﻦْ ﻧُﻮﺭٍ ﻋَﻦْ ﻳَﻤِﻴﻦِ ﺍﻟﺮَّﺣْﻤَﻦِ ﻋَﺰَّ ﻭَﺟَﻞَّ ﻭَﻛِﻠْﺘَﺎ ﻳَﺪَﻳْﻪِ ﻳَﻤِﻴﻦٌ ﺍﻟَّﺬِﻳﻦَ ﻳَﻌْﺪِﻟُﻮﻥَ ﻓِﻲ ﺣُﻜْﻤِﻬِﻢْ ﻭَﺃَﻫْﻠِﻴﻬِﻢْ ﻭَﻣَﺎ ﻭَﻟُﻮﺍ "

አላህ በራሱ ባህርይ ፈጠረው ማለት ለምሳሌ አላህ አደምን በእጁ ፈጥሮታል፦
38፥75 አላህም «ኢብሊስ ሆይ! *"በሁለት እጆቼ"* "ለፈጠርኩት" ከመስገድ ምን ከለከለህ? አሁን ኮራህን? ወይስ ከትዕቢተኞቹ ነበርክ?» አለው፡፡ قَالَ يَٰٓإِبْلِيسُ مَا مَنَعَكَ أَن تَسْجُدَ لِمَا خَلَقْتُ بِيَدَىَّ ۖ أَسْتَكْبَرْتَ أَمْ كُنتَ مِنَ ٱلْعَالِينَ
36፥71 እኛ *"እጆቻችን ከሠሩት"* ለእነርሱ እንስሳዎችን መፍጠራችንን አያውቁምን? እነርሱም ለእርሷ ባለ መብቶች ናቸው፡፡ أَوَلَمْ يَرَوْا۟ أَنَّا خَلَقْنَا لَهُم مِّمَّا عَمِلَتْ أَيْدِينَآ أَنْعَٰمًۭا فَهُمْ لَهَا مَٰلِكُونَ

እጅ የአላህ ባህርይ ነው፤ ኹን የሚለው ንግግሩ የራሱ ባህርይ ነው፤ በባህርይው አደምን ፈጥሮታል።

ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሰላሙ አለይኩም