ኢሬቻ
በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
29፥56 እናንተ ያመናችሁ ባሮቼ ሆይ! ምድሬ በእርግጥ ሰፊ ናት፤ ብትቸገሩ ተሰደዱ፡፡ "እኔንም ብቻ አምልኩኝ"፡፡ يَٰعِبَادِىَ ٱلَّذِينَ ءَامَنُوٓا۟ إِنَّ أَرْضِى وَٰسِعَةٌۭ فَإِيَّٰىَ فَٱعْبُدُونِ
አምላካችን አሏህ መለኮት ነው፥ “መለኮት” ማለት "ሁሉን ነገር የሚሰማ፣ ሁሉን ነገር የሚመለከት፣ ሁሉን ነገር የሚያውቅ፣ ሁሉን ነገር የፈጠረ፣ በሁሉን ነገር ላይ ቻይ" ማለት ነው። እርሱ በእኔነት የሚናገር ነባቢ እና ሕያው መለኮት ነው፥ አምላካችን አሏህ ብዙ አናቅጽ ላይ “አምልኩኝ” እያለ በመጀመሪያ መደብ ይናገራል፦
21፥92 ይህች አንዲት መንገድ ስትሆን በእርግጥ ሃይማኖታችሁ ናት፤ "እኔም ጌታችሁ ነኝና አምልኩኝ"፡፡ إِنَّ هَٰذِهِۦٓ أُمَّتُكُمْ أُمَّةًۭ وَٰحِدَةًۭ وَأَنَا۠ رَبُّكُمْ فَٱعْبُدُونِ
29፥56 እናንተ ያመናችሁ ባሮቼ ሆይ! ምድሬ በእርግጥ ሰፊ ናት፤ ብትቸገሩ ተሰደዱ፡፡ "እኔንም ብቻ አምልኩኝ”፡፡ يَٰعِبَادِىَ ٱلَّذِينَ ءَامَنُوٓا۟ إِنَّ أَرْضِى وَٰسِعَةٌۭ فَإِيَّٰىَ فَٱعْبُدُونِ
"እኔንም ብቻ አምልኩኝ" የሚለው ይሰመርበት! "አምልኩኝ" ለሚለው የገባው ቃል "አዕቡዱኒ" ٱعْبُدُونِ ሲሆን አምላካችን አሏህ ጥንት ለነበሩ ነቢያትም "ከእኔ ሌላ አምላክ የለምና አምልኩኝ" በማለት የሚናገር አምላክ ነው፦
21፥25 ከአንተ በፊትም እነሆ "ከእኔ ሌላ አምላክ የለምና አምልኩኝ" በማለት ወደ እርሱ ”የምናወርድለት” ቢኾን እንጅ ከመልእክተኛ አንድንም አልላክንም፡፡ وَمَآ أَرْسَلْنَا مِن قَبْلِكَ مِن رَّسُولٍ إِلَّا نُوحِىٓ إِلَيْهِ أَنَّهُۥ لَآ إِلَٰهَ إِلَّآ أَنَا۠ فَٱعْبُدُونِ
ሰው የተፈጠረበት ዓላማ እና ዒላማ የአምልኮ ሐቅ የሚገባውን አሏህን ብቻ ለማምለክ ነው፥ አንድ ሙሥሊም በጌታው አምልኮን ማንንም ሆነ ምንንም ማጋራት የለበትም፦
51፥56 ጂኒን እና ሰውንም ሊያመልኩኝ እንጅ ለሌላ አልፈጠርኳቸውም፡፡ وَمَا خَلَقْتُ الْجِنَّ وَالْإِنسَ إِلَّا لِيَعْبُدُونِ
18፥110 «በጌታውም አምልኮ አንድንም አያጋራ» በላቸው፡፡ وَلَا يُشْرِكْ بِعِبَادَةِ رَبِّهِ أَحَدًا
"ዒባዳህ" عِبَادَة ማለት እራሱ "አምልኮ" ማለት ነው። ይህንን ከተረዳን ዘንዳ ስለ ኢሬቻ ትንሽ እንበል? “ኢሬቻ” ማለት “አምልኮ” ማለት ሲሆን “ገልማ” ማለት “ቤተ አምልኮ” ማለት ነው፥ ኢሬቻ ገልማ ውስጥ በጭፈራዎቹ እና በፌሽታዎች የሚከበር በዓል ነው። ኢሬቻን የምትለዋ ቃል የምትወክለው እርጥብ ሣር ወይም አበባ በማቅረብ “መሬሆ” ማለትም “መዝሙር” መዘመሩን ነው፥ "ኢሬቻ ባህል እንጂ ሃይማኖት አይደለም" ለምትሉ ስመ ሙሥሊም ይህንን ስትረዱ ምን ይውጣችሁ ይሆን?
“ዋቃ” ማለት እኮ “አምላክ” ማለት ነው፥ "ዋቃ ጉራቻ" ማለት "ጥቁር አምላክ" ማለት ሲሆን "ዋቃ ጉራቻ" እያሉ ለወንዙ፣ ለተራራው፣ ለሐይቁ የሚደረገው የሁሉ አምላክነት”Pantheism” እሳቤ ባዕድ አምልኮ ነው። በዚህ አምልኮ ውስጥ ልመና፣ ምስጋና፣ ስለት፣ ስግደ፣ የእድርድ መሥዋዕት የመሳሰሉት ይካሄዳሉ፥ ዛፍ ቅቤ በመቀባት መለማመን፣ ማመስገን፣ መሳል፣ መስገድ ባዕድ አምልኮ ካልሆነ ምንድን ይሆን?
እንደውም “ቃሊቻ” የሚለው ቃል የተገኘው “ቃሉ” ከሚለው እንደሆነም ይነገራል፥ “ቃሉ” የተባሉት መሪዎች ከአጋንንት ጋር እየተነጋገሩ ሺርክ እንደሚያደርጉ የዚህ ባዕድ አምልኮ ነጻ የወጡ ሰዎች ይናገራሉ።
ይህንን አምልኮ የሚፈጽሙ ምዕመናኑ “ሚሤንሣ” ሲባሉ እምነቱን የሚመሩት ካህናቱ “ቃሉ” ይባላሉ፥ ፓለቲካውን “ሲርነ ገዳ” ሲባል ፓለቲካውን የሚመሩት መሪዎች ደግሞ “አባ ገዳ” ይባላሉ።
የዚህ ባዕድ አምልኮ ስም "ዋቄፈና" ሲባል ይህንን እምነት የሚከተል ሰው ደግሞ “ዋቄፈታ” ይባላል፥ ይህ እምነት አምልኮውን የሚፈጽመው በተራራ እና በሃይቅ ወዘተ ነው። “ቱሉ” ማለት “ተራራ” ማለት ሲሆን “ቱሉ ጩቋላ(የዝቋላ ተራራ) “ቱሉ ፊሪ” “ቱሉ ኤረር” እየተባለ ወደ ስምንት ተራሮች ላይ አምልኮ ይፈጸማል፥ “ሆረ” ማለት “ሃይቅ” ማለት ሲሆን “ሆረ አርሰዴ” “ሆረ ፊንፊኔ” “ሆረ ኪሎሌ” እየተባሉ ሰባቱ የዋቃ ሃይቆች ላይ አምልኮ ይፈጸማል።
ይህንን የባዕድ አምልኮ በዓል በዓመት ሁለት ጊዜ ይከበራል፥ ቅሉ እና ጥቅሉ ግን ሙሥሊም የሚያከብረው በዓል ዒዱል ፊጥር እና ዒዱል አድሓ ብቻ እና ብቻ ናቸው፦
ጃሚዕ አት ቲርሚዚይ መጽሐፍ 8, ሐዲስ 121
ዓኢሻህ”ረ.ዐ.” እንደተረከችው የአሏህ መልእክተኛም”ﷺ” እንዲህ አሉ፦ “ዒዱል ፈጥር ሰዎች ጾም የሚፈቱበት ነው፤ ዒዱል አደሐ ደግሞ መስዋዕት የሚያቀርቡበት ቀን ነው"። عَنْ عَائِشَةَ، قَالَتْ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم “ الْفِطْرُ يَوْمَ يُفْطِرُ النَّاسُ وَالأَضْحَى يَوْمَ يُضَحِّي النَّاسُ ”
ይህ እምነት ታሪካዊ ዳራው ከክርስቶስ ልደት በፊት በ3000 ቅድመ ልደት እንደተጀመረ እና ጅምሩ የአንድ አምላክ አስተምህሮት እንደነበር ይገመታል ይነገራል፥ እንደ ጎርጎሮሳውያን አቆጣጠር በ 2007 ድህረ ልደት በተደረገው የሕዝብ እና ቤቶች ቆጠራ ከኦሮሞ ሕዝብ ወደ 3.3 በመቶ የሚደርሰው ሕዝብ የዚህ እምነት ተከታይ ነበር። በአሁኑ ጊዜ ይሄ ቁጥር ወደ 3 በመቶ ዝቅ እንዳለ ይነገራል፥ አንዳንዶች ደግሞ፦ “አብዛኛው ዋቄፈናን ከእሥልምና ጋር ወይንም ከክርስትና ጋር ቀይጦ ነው የሚያመልከው” ይላሉ። ይህ ስህተት ነው፥ ምክንያቱም የሚያመልኩት ዋቃ አንድም ቀን እንዴት መመለክ እንዳለበት አልነገራቸውም። ደግሞም “አይናገርምም” ይላሉ፥ እነርሱም ባወጡት ሰው ሠራሽ አምልኮ ያመልኩታል።
"የመውሊድ በዓል ቢድዓህ ነው፥ የገና እና የፋሲካ በዓል ሐራም" ብለህ እየተቃወምክ ኢሬቻ ላይ መሳተፍ እና በዓሉን ማክበር በምን ሞራልህ እና ስሌትህ ነው "ሐላል ነው፥ ባህል ነው" የምትለው? ስለዚህ እዚህ እምነት ውስጥ ያላችሁ ዋቄፈታዎች የነቢያት አምላክ የሆነውን አንዱን አምላክ አሏህን በብቸኝነት እንድታመልኩ ጥሪያችን ነው። ሙሥሊሞች ሆናችሁ ይህንን በዓል ባለማወቅ የምታከብሩም እና የምታመልኩ ካላችሁ በንስሓ ወደ አሏህ ተመለሱ! አሏህ ወደ እርሱ በመጸጸት ለሚመለሱት ይቅር ባይና አዛኝ ነው፦
2፥160 እነዚያ ከመደበቅ የተጸጸቱና ሥራቸውን ያሳመሩም የደበቁትን የገለጹም ብቻ ሲቀሩ፡፡ እነዚህም በእነርሱ ላይ ጸጸታቸውን እቀበላለሁ፤ እኔም ጸጸትን በጣም ተቀባይ አዛኙ ነኝ፡፡ إِلَّا الَّذِينَ تَابُوا وَأَصْلَحُوا وَبَيَّنُوا فَأُولَـٰئِكَ أَتُوبُ عَلَيْهِمْ ۚ وَأَنَا التَّوَّابُ الرَّحِيمُ
"እኔም ጸጸትን በጣም ተቀባይ አዛኙ ነኝ" ብሎ የተናገረን አምላክ በብቸኝነት ማምለክ ምንኛ መታደል ነው? አምላካችን አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይወፍቀን! አሚን።
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
29፥56 እናንተ ያመናችሁ ባሮቼ ሆይ! ምድሬ በእርግጥ ሰፊ ናት፤ ብትቸገሩ ተሰደዱ፡፡ "እኔንም ብቻ አምልኩኝ"፡፡ يَٰعِبَادِىَ ٱلَّذِينَ ءَامَنُوٓا۟ إِنَّ أَرْضِى وَٰسِعَةٌۭ فَإِيَّٰىَ فَٱعْبُدُونِ
አምላካችን አሏህ መለኮት ነው፥ “መለኮት” ማለት "ሁሉን ነገር የሚሰማ፣ ሁሉን ነገር የሚመለከት፣ ሁሉን ነገር የሚያውቅ፣ ሁሉን ነገር የፈጠረ፣ በሁሉን ነገር ላይ ቻይ" ማለት ነው። እርሱ በእኔነት የሚናገር ነባቢ እና ሕያው መለኮት ነው፥ አምላካችን አሏህ ብዙ አናቅጽ ላይ “አምልኩኝ” እያለ በመጀመሪያ መደብ ይናገራል፦
21፥92 ይህች አንዲት መንገድ ስትሆን በእርግጥ ሃይማኖታችሁ ናት፤ "እኔም ጌታችሁ ነኝና አምልኩኝ"፡፡ إِنَّ هَٰذِهِۦٓ أُمَّتُكُمْ أُمَّةًۭ وَٰحِدَةًۭ وَأَنَا۠ رَبُّكُمْ فَٱعْبُدُونِ
29፥56 እናንተ ያመናችሁ ባሮቼ ሆይ! ምድሬ በእርግጥ ሰፊ ናት፤ ብትቸገሩ ተሰደዱ፡፡ "እኔንም ብቻ አምልኩኝ”፡፡ يَٰعِبَادِىَ ٱلَّذِينَ ءَامَنُوٓا۟ إِنَّ أَرْضِى وَٰسِعَةٌۭ فَإِيَّٰىَ فَٱعْبُدُونِ
"እኔንም ብቻ አምልኩኝ" የሚለው ይሰመርበት! "አምልኩኝ" ለሚለው የገባው ቃል "አዕቡዱኒ" ٱعْبُدُونِ ሲሆን አምላካችን አሏህ ጥንት ለነበሩ ነቢያትም "ከእኔ ሌላ አምላክ የለምና አምልኩኝ" በማለት የሚናገር አምላክ ነው፦
21፥25 ከአንተ በፊትም እነሆ "ከእኔ ሌላ አምላክ የለምና አምልኩኝ" በማለት ወደ እርሱ ”የምናወርድለት” ቢኾን እንጅ ከመልእክተኛ አንድንም አልላክንም፡፡ وَمَآ أَرْسَلْنَا مِن قَبْلِكَ مِن رَّسُولٍ إِلَّا نُوحِىٓ إِلَيْهِ أَنَّهُۥ لَآ إِلَٰهَ إِلَّآ أَنَا۠ فَٱعْبُدُونِ
ሰው የተፈጠረበት ዓላማ እና ዒላማ የአምልኮ ሐቅ የሚገባውን አሏህን ብቻ ለማምለክ ነው፥ አንድ ሙሥሊም በጌታው አምልኮን ማንንም ሆነ ምንንም ማጋራት የለበትም፦
51፥56 ጂኒን እና ሰውንም ሊያመልኩኝ እንጅ ለሌላ አልፈጠርኳቸውም፡፡ وَمَا خَلَقْتُ الْجِنَّ وَالْإِنسَ إِلَّا لِيَعْبُدُونِ
18፥110 «በጌታውም አምልኮ አንድንም አያጋራ» በላቸው፡፡ وَلَا يُشْرِكْ بِعِبَادَةِ رَبِّهِ أَحَدًا
"ዒባዳህ" عِبَادَة ማለት እራሱ "አምልኮ" ማለት ነው። ይህንን ከተረዳን ዘንዳ ስለ ኢሬቻ ትንሽ እንበል? “ኢሬቻ” ማለት “አምልኮ” ማለት ሲሆን “ገልማ” ማለት “ቤተ አምልኮ” ማለት ነው፥ ኢሬቻ ገልማ ውስጥ በጭፈራዎቹ እና በፌሽታዎች የሚከበር በዓል ነው። ኢሬቻን የምትለዋ ቃል የምትወክለው እርጥብ ሣር ወይም አበባ በማቅረብ “መሬሆ” ማለትም “መዝሙር” መዘመሩን ነው፥ "ኢሬቻ ባህል እንጂ ሃይማኖት አይደለም" ለምትሉ ስመ ሙሥሊም ይህንን ስትረዱ ምን ይውጣችሁ ይሆን?
“ዋቃ” ማለት እኮ “አምላክ” ማለት ነው፥ "ዋቃ ጉራቻ" ማለት "ጥቁር አምላክ" ማለት ሲሆን "ዋቃ ጉራቻ" እያሉ ለወንዙ፣ ለተራራው፣ ለሐይቁ የሚደረገው የሁሉ አምላክነት”Pantheism” እሳቤ ባዕድ አምልኮ ነው። በዚህ አምልኮ ውስጥ ልመና፣ ምስጋና፣ ስለት፣ ስግደ፣ የእድርድ መሥዋዕት የመሳሰሉት ይካሄዳሉ፥ ዛፍ ቅቤ በመቀባት መለማመን፣ ማመስገን፣ መሳል፣ መስገድ ባዕድ አምልኮ ካልሆነ ምንድን ይሆን?
እንደውም “ቃሊቻ” የሚለው ቃል የተገኘው “ቃሉ” ከሚለው እንደሆነም ይነገራል፥ “ቃሉ” የተባሉት መሪዎች ከአጋንንት ጋር እየተነጋገሩ ሺርክ እንደሚያደርጉ የዚህ ባዕድ አምልኮ ነጻ የወጡ ሰዎች ይናገራሉ።
ይህንን አምልኮ የሚፈጽሙ ምዕመናኑ “ሚሤንሣ” ሲባሉ እምነቱን የሚመሩት ካህናቱ “ቃሉ” ይባላሉ፥ ፓለቲካውን “ሲርነ ገዳ” ሲባል ፓለቲካውን የሚመሩት መሪዎች ደግሞ “አባ ገዳ” ይባላሉ።
የዚህ ባዕድ አምልኮ ስም "ዋቄፈና" ሲባል ይህንን እምነት የሚከተል ሰው ደግሞ “ዋቄፈታ” ይባላል፥ ይህ እምነት አምልኮውን የሚፈጽመው በተራራ እና በሃይቅ ወዘተ ነው። “ቱሉ” ማለት “ተራራ” ማለት ሲሆን “ቱሉ ጩቋላ(የዝቋላ ተራራ) “ቱሉ ፊሪ” “ቱሉ ኤረር” እየተባለ ወደ ስምንት ተራሮች ላይ አምልኮ ይፈጸማል፥ “ሆረ” ማለት “ሃይቅ” ማለት ሲሆን “ሆረ አርሰዴ” “ሆረ ፊንፊኔ” “ሆረ ኪሎሌ” እየተባሉ ሰባቱ የዋቃ ሃይቆች ላይ አምልኮ ይፈጸማል።
ይህንን የባዕድ አምልኮ በዓል በዓመት ሁለት ጊዜ ይከበራል፥ ቅሉ እና ጥቅሉ ግን ሙሥሊም የሚያከብረው በዓል ዒዱል ፊጥር እና ዒዱል አድሓ ብቻ እና ብቻ ናቸው፦
ጃሚዕ አት ቲርሚዚይ መጽሐፍ 8, ሐዲስ 121
ዓኢሻህ”ረ.ዐ.” እንደተረከችው የአሏህ መልእክተኛም”ﷺ” እንዲህ አሉ፦ “ዒዱል ፈጥር ሰዎች ጾም የሚፈቱበት ነው፤ ዒዱል አደሐ ደግሞ መስዋዕት የሚያቀርቡበት ቀን ነው"። عَنْ عَائِشَةَ، قَالَتْ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم “ الْفِطْرُ يَوْمَ يُفْطِرُ النَّاسُ وَالأَضْحَى يَوْمَ يُضَحِّي النَّاسُ ”
ይህ እምነት ታሪካዊ ዳራው ከክርስቶስ ልደት በፊት በ3000 ቅድመ ልደት እንደተጀመረ እና ጅምሩ የአንድ አምላክ አስተምህሮት እንደነበር ይገመታል ይነገራል፥ እንደ ጎርጎሮሳውያን አቆጣጠር በ 2007 ድህረ ልደት በተደረገው የሕዝብ እና ቤቶች ቆጠራ ከኦሮሞ ሕዝብ ወደ 3.3 በመቶ የሚደርሰው ሕዝብ የዚህ እምነት ተከታይ ነበር። በአሁኑ ጊዜ ይሄ ቁጥር ወደ 3 በመቶ ዝቅ እንዳለ ይነገራል፥ አንዳንዶች ደግሞ፦ “አብዛኛው ዋቄፈናን ከእሥልምና ጋር ወይንም ከክርስትና ጋር ቀይጦ ነው የሚያመልከው” ይላሉ። ይህ ስህተት ነው፥ ምክንያቱም የሚያመልኩት ዋቃ አንድም ቀን እንዴት መመለክ እንዳለበት አልነገራቸውም። ደግሞም “አይናገርምም” ይላሉ፥ እነርሱም ባወጡት ሰው ሠራሽ አምልኮ ያመልኩታል።
"የመውሊድ በዓል ቢድዓህ ነው፥ የገና እና የፋሲካ በዓል ሐራም" ብለህ እየተቃወምክ ኢሬቻ ላይ መሳተፍ እና በዓሉን ማክበር በምን ሞራልህ እና ስሌትህ ነው "ሐላል ነው፥ ባህል ነው" የምትለው? ስለዚህ እዚህ እምነት ውስጥ ያላችሁ ዋቄፈታዎች የነቢያት አምላክ የሆነውን አንዱን አምላክ አሏህን በብቸኝነት እንድታመልኩ ጥሪያችን ነው። ሙሥሊሞች ሆናችሁ ይህንን በዓል ባለማወቅ የምታከብሩም እና የምታመልኩ ካላችሁ በንስሓ ወደ አሏህ ተመለሱ! አሏህ ወደ እርሱ በመጸጸት ለሚመለሱት ይቅር ባይና አዛኝ ነው፦
2፥160 እነዚያ ከመደበቅ የተጸጸቱና ሥራቸውን ያሳመሩም የደበቁትን የገለጹም ብቻ ሲቀሩ፡፡ እነዚህም በእነርሱ ላይ ጸጸታቸውን እቀበላለሁ፤ እኔም ጸጸትን በጣም ተቀባይ አዛኙ ነኝ፡፡ إِلَّا الَّذِينَ تَابُوا وَأَصْلَحُوا وَبَيَّنُوا فَأُولَـٰئِكَ أَتُوبُ عَلَيْهِمْ ۚ وَأَنَا التَّوَّابُ الرَّحِيمُ
"እኔም ጸጸትን በጣም ተቀባይ አዛኙ ነኝ" ብሎ የተናገረን አምላክ በብቸኝነት ማምለክ ምንኛ መታደል ነው? አምላካችን አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይወፍቀን! አሚን።
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
አሥ ሠላሙ ዐለይኩም ያ ጀመዓህ!
ወሒድ የዕቅበተ ኢሥላም ቤተ መጣጥፍ ብዙ ሰዎች እያነበቡ እየተለወጡበት ይገኛል። ሠበቡል ሂዳያህ ለመሆን ይህንን ቤተ መጣጥፍ ከ 37 ሺህ ወደ 100 ሺህ ለማስገባት የእናንተ ሼር ማድረግ እና እርብርብ ይጠይቃል። ሊንኩ ይህ ነው፦
https://tttttt.me/Wahidcom
ይህንን ቻናል በተሻለ ረብጣ አሳብ ለማረቅ እና ለማሳለጥ የምትፈልጉ በኮሜንት ክፍል ውስጥ አስተያየታችሁን ማስፈር ትችላላችሁ።
ጥሪአችን ሰዎች አንዱን አምላክ በብቸኝነት እንዲያመልኩ ነው፦
24፥55 በእኔ ምንን ነገር የማያጋሩ ሆነው ያመልኩኛል፡፡ ከዚያም በኋላ የካደ ሰው እነዚያ እነርሱ አመጸኞች ናቸው፡፡ يَعْبُدُونَنِي لَا يُشْرِكُونَ بِي شَيْئًا ۚ وَمَن كَفَرَ بَعْدَ ذَٰلِكَ فَأُولَـٰئِكَ هُمُ الْفَاسِقُونَ
ወሒድ የዕቅበተ ኢሥላም ቤተ መጣጥፍ ብዙ ሰዎች እያነበቡ እየተለወጡበት ይገኛል። ሠበቡል ሂዳያህ ለመሆን ይህንን ቤተ መጣጥፍ ከ 37 ሺህ ወደ 100 ሺህ ለማስገባት የእናንተ ሼር ማድረግ እና እርብርብ ይጠይቃል። ሊንኩ ይህ ነው፦
https://tttttt.me/Wahidcom
ይህንን ቻናል በተሻለ ረብጣ አሳብ ለማረቅ እና ለማሳለጥ የምትፈልጉ በኮሜንት ክፍል ውስጥ አስተያየታችሁን ማስፈር ትችላላችሁ።
ጥሪአችን ሰዎች አንዱን አምላክ በብቸኝነት እንዲያመልኩ ነው፦
24፥55 በእኔ ምንን ነገር የማያጋሩ ሆነው ያመልኩኛል፡፡ ከዚያም በኋላ የካደ ሰው እነዚያ እነርሱ አመጸኞች ናቸው፡፡ يَعْبُدُونَنِي لَا يُشْرِكُونَ بِي شَيْئًا ۚ وَمَن كَفَرَ بَعْدَ ذَٰلِكَ فَأُولَـٰئِكَ هُمُ الْفَاسِقُونَ
ዐቂዳህ
በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
3፥103 የአሏህን ገመድ ሁላችሁም ያዙ። وَاعْتَصِمُوا بِحَبْلِ اللَّهِ جَمِيعًا
"ዐቂዳህ" عَقِيدَة የሚለው ቃል "ዐቀደ" عَقَدَ ማለትም "ቋጠረ" "ያዘ" ከሚል ሥርወ ቃል የመጣ ሲሆን "መቋጠር" "መያዝ" ማለት ነው፥ "ዐቃኢድ" عَقَائِد ደግሞ "ዐቂዳህ" عَقِيدَة ለሚለው ብዙ ቁጥር ነው፦
113፥4 “በየተቋጠሩ” ክሮች ላይ ተፊዎች ከኾኑት ደጋሚ ሴቶችም ክፋት፡፡ وَمِن شَرِّ ٱلنَّفَّٰثَٰتِ فِى ٱلْعُقَدِ
እዚህ አንቀጽ ላይ "የተቋጠሩ" ለሚለው የገባው ቃል "ዑቀድ" عُقَد እንደሆነ ልብ አድርግ! ለምሳሌ፦ የጋብቻ ቃል ኪዳን "ዑቅደቱን ኒካህ" عُقْدَةُ النِّكَاح ተብሎ ይጠራል፦
2፥237 ለእነርሱም መወሰንን በእርግጥ የወሰናችሁላቸው ስትኾኑ ሳትነኳቸው በፊት ብተፈቷቸው ካልማሩዋችሁ ወይም ያ "የጋብቻው ውል" በእጁ የኾነው ባልየው ካልማረ በስተቀር የወሰናችሁት ግማሹ አላቸው፡፡ وَإِن طَلَّقْتُمُوهُنَّ مِن قَبْلِ أَن تَمَسُّوهُنَّ وَقَدْ فَرَضْتُمْ لَهُنَّ فَرِيضَةً فَنِصْفُ مَا فَرَضْتُمْ إِلَّا أَن يَعْفُونَ أَوْ يَعْفُوَ الَّذِي بِيَدِهِ عُقْدَةُ النِّكَاحِ
እዚህ አንቀጽ ላይ "የጋብቻው ውል" ለሚለው የገባው ቃል "ዑቅደቱን ኒካህ" عُقْدَةُ النِّكَاحعُقَد ነው፥ ስለዚህ አንድ ሰው እኔን፡- "ዐቂዳህ" ምንድነው? ብሎ ቢጠይቀኝ ጥያቄው፡- በልብህ አምነህ የያዝከው እና የቋጠርከው ምንድነው? ማለቱ ነው።
ይህ ቋንቋዊ ፍቺው ሲሆን "ዐቂዳህ" عَقِيدَة ሸሪዓዊ ፍቺው ደግሞ "አንቀጸ እምነት" "ዶግማ" ማለት ነው፥ "ዶግማ" δόγμα የሚለው ቃል የግሪክ ቃል ሲሆን "መሠረት" "መርሕ" "አንቀጸ እምነት"creed" ማለት ነው፦
ሡነን አድ ዳርሚይ መጽሐፍ 1 ሐዲስ 231
ዐብዱር ረሕማን ኢብኑ አባን እንደተረከው፦ "የአሏህ መልእክተኛ"ﷺ":እንዲህ አሉ፦ "የሙሥሊም ልብ በሦስት ጉዳይ "አያምንም" ጀነት የሚገባበት ቢሆን እንጂ፥ እኔም፦ "ምንድን ናቸው? አልኩኝ። እርሳቸው፦ "ለአሏህ ብሎ በኢኽላስ መሥራት፣ ለአሚር ቅን ምክር መስጠት እና ጀመዓን አጥብቆ መያዝ"። عَنْ عَبْدِ الرَّحْمَنِ بْنِ أَبَانَ رَسُولِ اللَّهِ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ قَالَ :" لَا يَعْتَقِدُ قَلْبُ مُسْلِمٍ عَلَى ثَلَاثِ خِصَالٍ إِلَّا دَخَلَ الْجَنَّةَ "، قَالَ : قُلْتُ : مَا هُنَّ؟، قَالَ : إِخْلَاصُ الْعَمَلِ لِلَّهِ، وَالنَّصِيحَةُ لِوُلَاةِ الْأَمْرِ، وَلُزُومُ الْجَمَاعَةِ،
እዚህ ሐዲስ ላይ "የዕተቂዱ" يَعْتَقِدُ የሚለው "ዩእሚኑ" يُؤْمِنُو በሚል የመጣ ነው፥ ቁርኣን ላይ "ኢማን" إِيمَان የሚለው "ኢዕቲቃድ" اِعْتِقَاد ማለት ነው፦
5፥89 አሏህ በመሐላዎቻችሁ በውድቁ አይዛችሁም፥ ግን መሐላዎችን "ባሰባችሁት" ይይዛችኋል፡፡ لَا يُؤَاخِذُكُمُ اللَّهُ بِاللَّغْوِ فِي أَيْمَانِكُمْ وَلَـٰكِن يُؤَاخِذُكُم بِمَا عَقَّدتُّمُ الْأَيْمَانَ
እዚህ አንቀጽ ላይ "ባሰባችሁት" ለሚለው የገባው ቃል "ዐቀድቱም" عَقَّدتُّم ሲሆን "በወጠናችሁት" ማለት ነው፥ "ዐቅድ" عَقْد ማለት በልብ ውስጥ ያለ "ውጥን" ማለት ሲሆን በልብ ውስጥ የሚቀመጥ ውጥን ደግሞ እምነት ነው።
በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
3፥103 የአሏህን ገመድ ሁላችሁም ያዙ። وَاعْتَصِمُوا بِحَبْلِ اللَّهِ جَمِيعًا
"ዐቂዳህ" عَقِيدَة የሚለው ቃል "ዐቀደ" عَقَدَ ማለትም "ቋጠረ" "ያዘ" ከሚል ሥርወ ቃል የመጣ ሲሆን "መቋጠር" "መያዝ" ማለት ነው፥ "ዐቃኢድ" عَقَائِد ደግሞ "ዐቂዳህ" عَقِيدَة ለሚለው ብዙ ቁጥር ነው፦
113፥4 “በየተቋጠሩ” ክሮች ላይ ተፊዎች ከኾኑት ደጋሚ ሴቶችም ክፋት፡፡ وَمِن شَرِّ ٱلنَّفَّٰثَٰتِ فِى ٱلْعُقَدِ
እዚህ አንቀጽ ላይ "የተቋጠሩ" ለሚለው የገባው ቃል "ዑቀድ" عُقَد እንደሆነ ልብ አድርግ! ለምሳሌ፦ የጋብቻ ቃል ኪዳን "ዑቅደቱን ኒካህ" عُقْدَةُ النِّكَاح ተብሎ ይጠራል፦
2፥237 ለእነርሱም መወሰንን በእርግጥ የወሰናችሁላቸው ስትኾኑ ሳትነኳቸው በፊት ብተፈቷቸው ካልማሩዋችሁ ወይም ያ "የጋብቻው ውል" በእጁ የኾነው ባልየው ካልማረ በስተቀር የወሰናችሁት ግማሹ አላቸው፡፡ وَإِن طَلَّقْتُمُوهُنَّ مِن قَبْلِ أَن تَمَسُّوهُنَّ وَقَدْ فَرَضْتُمْ لَهُنَّ فَرِيضَةً فَنِصْفُ مَا فَرَضْتُمْ إِلَّا أَن يَعْفُونَ أَوْ يَعْفُوَ الَّذِي بِيَدِهِ عُقْدَةُ النِّكَاحِ
እዚህ አንቀጽ ላይ "የጋብቻው ውል" ለሚለው የገባው ቃል "ዑቅደቱን ኒካህ" عُقْدَةُ النِّكَاحعُقَد ነው፥ ስለዚህ አንድ ሰው እኔን፡- "ዐቂዳህ" ምንድነው? ብሎ ቢጠይቀኝ ጥያቄው፡- በልብህ አምነህ የያዝከው እና የቋጠርከው ምንድነው? ማለቱ ነው።
ይህ ቋንቋዊ ፍቺው ሲሆን "ዐቂዳህ" عَقِيدَة ሸሪዓዊ ፍቺው ደግሞ "አንቀጸ እምነት" "ዶግማ" ማለት ነው፥ "ዶግማ" δόγμα የሚለው ቃል የግሪክ ቃል ሲሆን "መሠረት" "መርሕ" "አንቀጸ እምነት"creed" ማለት ነው፦
ሡነን አድ ዳርሚይ መጽሐፍ 1 ሐዲስ 231
ዐብዱር ረሕማን ኢብኑ አባን እንደተረከው፦ "የአሏህ መልእክተኛ"ﷺ":እንዲህ አሉ፦ "የሙሥሊም ልብ በሦስት ጉዳይ "አያምንም" ጀነት የሚገባበት ቢሆን እንጂ፥ እኔም፦ "ምንድን ናቸው? አልኩኝ። እርሳቸው፦ "ለአሏህ ብሎ በኢኽላስ መሥራት፣ ለአሚር ቅን ምክር መስጠት እና ጀመዓን አጥብቆ መያዝ"። عَنْ عَبْدِ الرَّحْمَنِ بْنِ أَبَانَ رَسُولِ اللَّهِ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ قَالَ :" لَا يَعْتَقِدُ قَلْبُ مُسْلِمٍ عَلَى ثَلَاثِ خِصَالٍ إِلَّا دَخَلَ الْجَنَّةَ "، قَالَ : قُلْتُ : مَا هُنَّ؟، قَالَ : إِخْلَاصُ الْعَمَلِ لِلَّهِ، وَالنَّصِيحَةُ لِوُلَاةِ الْأَمْرِ، وَلُزُومُ الْجَمَاعَةِ،
እዚህ ሐዲስ ላይ "የዕተቂዱ" يَعْتَقِدُ የሚለው "ዩእሚኑ" يُؤْمِنُو በሚል የመጣ ነው፥ ቁርኣን ላይ "ኢማን" إِيمَان የሚለው "ኢዕቲቃድ" اِعْتِقَاد ማለት ነው፦
5፥89 አሏህ በመሐላዎቻችሁ በውድቁ አይዛችሁም፥ ግን መሐላዎችን "ባሰባችሁት" ይይዛችኋል፡፡ لَا يُؤَاخِذُكُمُ اللَّهُ بِاللَّغْوِ فِي أَيْمَانِكُمْ وَلَـٰكِن يُؤَاخِذُكُم بِمَا عَقَّدتُّمُ الْأَيْمَانَ
እዚህ አንቀጽ ላይ "ባሰባችሁት" ለሚለው የገባው ቃል "ዐቀድቱም" عَقَّدتُّم ሲሆን "በወጠናችሁት" ማለት ነው፥ "ዐቅድ" عَقْد ማለት በልብ ውስጥ ያለ "ውጥን" ማለት ሲሆን በልብ ውስጥ የሚቀመጥ ውጥን ደግሞ እምነት ነው።
አርካኑል ኢማን "ዐቀዲይ" عَقَدِيّ ወይም "ዐቃኢዲይ" عَقَائِدِيّ ናቸው፥ "ዐቀዲይ" عَقَدِيّ ወይም "ዐቃኢዲይ" عَقَائِدِيّ ማለት "ዶግማዊ"dogmatic" ማለት ነው። "ላ ኢላሀ ኢለል ሏህ" لَا إِلَـٰهَ إِلَّا اللَّه ማለት "ከአሏህ በስተቀር በሐቅ የሚመለክ አምላክ የለም" ማለት ነው፥ "ኢማን" إِيمَٰن ማለት "እምነት" ማለት ሲሆን የኢማን ትልቁ ቅርንጫፍ "ላ ኢላሀ ኢለል ሏህ" ማለት ነው፦
ኢማም ሙሥሊም መጽሐፍ 1, ሐዲስ 60
አቢ ሁረይራህ እንደተረከው፦ “የአሏህ መልእክተኛም”ﷺ” እንዲህ አሉ፦ "ኢማን ከሰባ ወይም ከስልሳ በላይ ቅርንጫፎች አሉት፥ ትልቁ ቅርንጫፍ "ላ ኢላሀ ኢለል ሏህ" ማለት ነው"። عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ، قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم “ الإِيمَانُ بِضْعٌ وَسَبْعُونَ أَوْ بِضْعٌ وَسِتُّونَ شُعْبَةً فَأَفْضَلُهَا قَوْلُ لاَ إِلَهَ إِلاَّ اللَّهُ
"ነፍይ" نَفْي ማለት “ማፍረስ” ማለት ሲሆን ነፍይ “ላ ኢላሀ” لَا إِلَـٰهَ ነው፥ “ኢስባት” إِثْبَات ማለት “ማጽደቅ” ማለት ሲሆን ኢስባት "ኢለል ሏህ” إِلَّا اللّٰه ነው፦
2፥256 “በጣዖት የሚክድ እና በአሏህ የሚያምን ሰው ለእርሷ መበጠስ የሌላትን ጠንካራ ገመድ በእርግጥ ያዘ”፡፡ فَمَن يَكْفُرْ بِالطَّاغُوتِ وَيُؤْمِن بِاللَّهِ فَقَدِ اسْتَمْسَكَ بِالْعُرْوَةِ الْوُثْقَىٰ لَا انفِصَامَ لَهَا
“ላ ኢላሀ” لَا إِلَـٰهَ በጣዖት መካድ ሲሆን “ኢለል ሏህ” إِلَّا اللّٰه በአሏህ ማመን ነው፥ ከአርካኑል ኢማን አንዱ የሆነው የመጀመሪያው እና ዋናው "አመንቱ ቢላህ" آمَنْتُ بِاللَّه ነው። "ላ ኢላሀ ኢለል ሏህ" لَا إِلَـٰهَ إِلَّا اللَّه የሚለውን ጠንካራ የአሏህን ገመድ መያዝ "ዐቂዳህ" عَقِيدَة ይባላል፦
3፥103 የአሏህን ገመድ ሁላችሁም ያዙ። وَاعْتَصِمُوا بِحَبْلِ اللَّهِ جَمِيعًا
"ያዙ" የሚለው ይሰመርበት! ይህ ገመድ ሰዎች ከጀሀነም እሳት ጉድጋድ አፋፍ ላይ እያሉ ተንጠንጥለው የሚድኑበት ገመድ ነው፦
3፥103 በእሳት ጉድጓድ አፋፍም ላይ ነበራችሁ፥ ከእርስዋም አዳናችሁ፡፡ وَكُنتُمْ عَلَىٰ شَفَا حُفْرَةٍ مِّنَ النَّارِ فَأَنقَذَكُم مِّنْهَا
አርካኑል ኢሥላም "ዐቂዲያህ" عَقِيدِيَّة ወይም "ዐቃዒዲያህ" عَقَائِدِيَّة ናቸው፥ "ዐቂዲያህ" عَقِيدِيَّة ወይም "ዐቃዒዲያህ" عَقَائِدِيَّة ማለት "ዶግማውያን"dogmatism" ማለት ነው። ከአርካኑል ኢሥላም አንዱ የሆነው የመጀመሪያው እና ዋናው "ላ ኢላሀ ኢለል ሏህ" لَا إِلَـٰهَ إِلَّا اللَّه ነው፥ ሙሉ ሁለንተናውን ለአሏህ የሰጠ ሙሥሊም ጠንካራ ገመድን በእርግጥ ያዘ፦
31፥22 እርሱ መልካም ሠሪ ሆኖ ፊቱን ወደ አሏህ የሚሰጥም ሰው ጠንካራ ገመድን በእርግጥ ያዘ፡፡ وَمَن يُسْلِمْ وَجْهَهُ إِلَى اللَّهِ وَهُوَ مُحْسِنٌ فَقَدِ اسْتَمْسَكَ بِالْعُرْوَةِ الْوُثْقَىٰ
እዚህ አንቀጽ "የሚሰጥ" ለሚለው የገባው ቃል "ዩሥሊም" يُسْلِمْ እንደሆነ ልብ አድርግ! ስለዚህ "ዐቂዳህ" عَقِيدَة ማለት "ሁለተኛ ወይም ንዑስ የዲን ቅርንጫፍ" ሳይሆን የመጀመሪያ እና ዐቢይ የዲን ቅርንጫፍ ነው፥ "ዐቂዳህ ምንድን ነው? ሲባል "እርሱ ሁለተኛ እና ንዑስ የዲን ቅርንጫፍ ነው" ብሎ ከመናገር በላይ የሚያሳፍር ነገር የለም። አምላካችን አሏህ ፈሣድን ከሚያስፋፉ ኢሕዋኑል ሙፍሢዱን ይጠብቀን! አሚን።
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
ኢማም ሙሥሊም መጽሐፍ 1, ሐዲስ 60
አቢ ሁረይራህ እንደተረከው፦ “የአሏህ መልእክተኛም”ﷺ” እንዲህ አሉ፦ "ኢማን ከሰባ ወይም ከስልሳ በላይ ቅርንጫፎች አሉት፥ ትልቁ ቅርንጫፍ "ላ ኢላሀ ኢለል ሏህ" ማለት ነው"። عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ، قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم “ الإِيمَانُ بِضْعٌ وَسَبْعُونَ أَوْ بِضْعٌ وَسِتُّونَ شُعْبَةً فَأَفْضَلُهَا قَوْلُ لاَ إِلَهَ إِلاَّ اللَّهُ
"ነፍይ" نَفْي ማለት “ማፍረስ” ማለት ሲሆን ነፍይ “ላ ኢላሀ” لَا إِلَـٰهَ ነው፥ “ኢስባት” إِثْبَات ማለት “ማጽደቅ” ማለት ሲሆን ኢስባት "ኢለል ሏህ” إِلَّا اللّٰه ነው፦
2፥256 “በጣዖት የሚክድ እና በአሏህ የሚያምን ሰው ለእርሷ መበጠስ የሌላትን ጠንካራ ገመድ በእርግጥ ያዘ”፡፡ فَمَن يَكْفُرْ بِالطَّاغُوتِ وَيُؤْمِن بِاللَّهِ فَقَدِ اسْتَمْسَكَ بِالْعُرْوَةِ الْوُثْقَىٰ لَا انفِصَامَ لَهَا
“ላ ኢላሀ” لَا إِلَـٰهَ በጣዖት መካድ ሲሆን “ኢለል ሏህ” إِلَّا اللّٰه በአሏህ ማመን ነው፥ ከአርካኑል ኢማን አንዱ የሆነው የመጀመሪያው እና ዋናው "አመንቱ ቢላህ" آمَنْتُ بِاللَّه ነው። "ላ ኢላሀ ኢለል ሏህ" لَا إِلَـٰهَ إِلَّا اللَّه የሚለውን ጠንካራ የአሏህን ገመድ መያዝ "ዐቂዳህ" عَقِيدَة ይባላል፦
3፥103 የአሏህን ገመድ ሁላችሁም ያዙ። وَاعْتَصِمُوا بِحَبْلِ اللَّهِ جَمِيعًا
"ያዙ" የሚለው ይሰመርበት! ይህ ገመድ ሰዎች ከጀሀነም እሳት ጉድጋድ አፋፍ ላይ እያሉ ተንጠንጥለው የሚድኑበት ገመድ ነው፦
3፥103 በእሳት ጉድጓድ አፋፍም ላይ ነበራችሁ፥ ከእርስዋም አዳናችሁ፡፡ وَكُنتُمْ عَلَىٰ شَفَا حُفْرَةٍ مِّنَ النَّارِ فَأَنقَذَكُم مِّنْهَا
አርካኑል ኢሥላም "ዐቂዲያህ" عَقِيدِيَّة ወይም "ዐቃዒዲያህ" عَقَائِدِيَّة ናቸው፥ "ዐቂዲያህ" عَقِيدِيَّة ወይም "ዐቃዒዲያህ" عَقَائِدِيَّة ማለት "ዶግማውያን"dogmatism" ማለት ነው። ከአርካኑል ኢሥላም አንዱ የሆነው የመጀመሪያው እና ዋናው "ላ ኢላሀ ኢለል ሏህ" لَا إِلَـٰهَ إِلَّا اللَّه ነው፥ ሙሉ ሁለንተናውን ለአሏህ የሰጠ ሙሥሊም ጠንካራ ገመድን በእርግጥ ያዘ፦
31፥22 እርሱ መልካም ሠሪ ሆኖ ፊቱን ወደ አሏህ የሚሰጥም ሰው ጠንካራ ገመድን በእርግጥ ያዘ፡፡ وَمَن يُسْلِمْ وَجْهَهُ إِلَى اللَّهِ وَهُوَ مُحْسِنٌ فَقَدِ اسْتَمْسَكَ بِالْعُرْوَةِ الْوُثْقَىٰ
እዚህ አንቀጽ "የሚሰጥ" ለሚለው የገባው ቃል "ዩሥሊም" يُسْلِمْ እንደሆነ ልብ አድርግ! ስለዚህ "ዐቂዳህ" عَقِيدَة ማለት "ሁለተኛ ወይም ንዑስ የዲን ቅርንጫፍ" ሳይሆን የመጀመሪያ እና ዐቢይ የዲን ቅርንጫፍ ነው፥ "ዐቂዳህ ምንድን ነው? ሲባል "እርሱ ሁለተኛ እና ንዑስ የዲን ቅርንጫፍ ነው" ብሎ ከመናገር በላይ የሚያሳፍር ነገር የለም። አምላካችን አሏህ ፈሣድን ከሚያስፋፉ ኢሕዋኑል ሙፍሢዱን ይጠብቀን! አሚን።
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
ወሒድ የዕቅበተ ኢሥላም መጣጥፍት"Wahid Articles of Islamic Apologetics"
Video
ቴሊቲስሞስ
በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
19፥34 ይህ የመርየም ልጅ ዒሣ ነው፡፡ ያ “በ”እርሱ የሚከራከሩበት እውነተኛ ቃል ነው፡፡ ذَٰلِكَ عِيسَى ٱبْنُ مَرْيَمَ ۚ قَوْلَ ٱلْحَقِّ ٱلَّذِى فِيهِ يَمْتَرُونَ
"ቴሎ" θέλω ማለት "ፈቃድ"will" ማለት ሲሆን ስለ "ፈቃድ" ያለው እሳቤ "ቴሊቲስሞስ" θελητισμός ይባላል፥ "ፈቃድ" ምንነትን"essence" ብቻ ሳይሆን ማንነትን"person" ታሳቢ እና ዋቢ ያደረገ ነው። ለምሳሌ፦ እያንዳንዱ ሰው ከሌላው ሰው የሚለየው በምንነቱ ሳይሆን በማንነቱ ነው፥ እያንዳንዱ ሰው ከሌላው ሰው የሚለየው በማንነቱ ስለሆነ እያንዳንዱ ሰው የራሱ "ፈቃድ" አለው። ፈጣሪ የራሱ ማንነት ስላለው የራሱ መለኮታዊ ፈቃድ አለው፦
ሉቃስ 22፥42 ነገር ግን የእኔ ፈቃድ አይሁን የአንተ ፈቃድ እንጂ። πλὴν μὴ τὸ θέλημά μου ἀλλὰ τὸ σὸν γινέσθω.
እዚህ አንቀጽ ላይ "ፈቃድ" ለሚለው የገባው ቃል "ቴሌማ" θέλημά ነው፥ ኢየሱስ አብን "አንተ" ሲል ማንነትን ታሳቢ ያደረገ ስለሆነ "ፈቃድ" የሚለው "አንተ" በሚል መነሻ ቅጥያ ላይ "የ" በሚል አጋናዛቢ ዘርፍ ስለመጣ ማንነትን ዋቢ ያደረገ ነው። ይሁን እና አይሁን ሁለት ፈቃድ እንጂ አንድ ፈቃድ በፍጹም አይደለም፥ ኢየሱስ ሰው ስለሆነ የሰው ማንነት እስካለው ድረስ "የእኔ ፈቃድ" ሲል "እኔ" ሲል ማንነትን ታሳቢ ያደረገ ስለሆነ "ፈቃድ" የሚለው "እኔ" በሚል መነሻ ቅጥያ ላይ "የ" በሚል አጋናዛቢ ዘርፍ ስለመጣ ማንነትን ዋቢ ያደረገ ነው። ስለዚህ ኢየሱስ እና አብ ሁለት የተለያየ ፈቃድ ያላቸው ማንነቶች ናቸው፦
ዮሐንስ 5፥30 የላከኝን ፈቃድ እንጂ የእኔን ፈቃድ አልሻምና። ὅτι οὐ ζητῶ τὸ θέλημα τὸ ἐμὸν ἀλλὰ τὸ θέλημα τοῦ πέμψαντός με.
እዚህ አንቀጽ ላይ ላይ ሁለት ጊዜ "ፈቃድ" ለሚለው የገባው ቃል "ቴሌማ" θέλημά ሲሆን አብ እና ወልድ ሁለት የተለያየ"distinct" ፈቃዶች ያላቸው ናቸው። "ፈቃድ" ምንነትን ታሳቢ ቢያደርግ ኖሮ በምድር ላይ ያለው ሰው ሁሉ በምንነት አንድ ስለሆነ አንድ ፈቃድ ብቻ ይኖረን ነበር፥ ነገር ግን እውነታው እያንዳንዱ ማንነት ከሌላው ማንነት የሚለይበት እራሱን የቻለ የራሱ ፈቃድ አለው።
፨ በአገራችን የፕሮቴስታንት ዐቃቢ እምነት ዶክተር ተስፋዬ ሮበሌ በአንድ ትምህርታቸው ላይ ዮሐንስ 5፥30 ሲያብራሩ፦ "ሁለት ፈቃድ አለ፥ ፈቃድ የሚባለው ነገር ማንነትን ሲገልጽ ዕውቀት፣ ስሜት እና ፈቃድ ነውና እዚህ ጋር "የላከኝን ፈቃድ እንጂ ፈቃዴን አልሻምና" በማለት ሁለት ፈቃድን ያሳያል" ብለዋል፥ በተጨማሪ ዶክተሩ ከዚህ ቀደም "የአሥተምህሮተ ሥላሴ መጽሐፍ ቅዱሳዊ መሠረት" በሚል መጻፋቸው፦ "ሦስት አካል ናቸው" ስንል ደግሞ አብ፣ ወልድ እና መንፈስ ቅዱስ የራሳቸው ስሜት፣ ፈቃድ እና ዕውቀት አላቸው" ማለታችን ነው" በማለት እያንዳንዱ አካል የየራሱ ፈቃድ እንዳለው ጽፏል።
፨ አሜሪካዊ የክርስትና ዐቃቢ እምነት እና የሥነ መለኮት ምሁር ዊልያም ሌን ክሬግ"William Lane Craig" የተባሉት "Reasonable Faith" በሚል ድረ ገጻቸው ሦስቱ አካላት ሦስት ፈቃድ እንዳላቸው አስቀምጠዋል፦
"አንድ የማንነት ጠንካራ እሳቤ የራስ ንቃተ ሕሊና፣ ውጥን እና ፈቃድ ማዕከል እንዳለው ካረጋገጥን ያንን ተከትለን የሥላሴ አካላት ሦስት ፈቃዳት እንዳላቸው አስባለው"።
784 Monothelitism and the Trinity May 22, 2022
https://www.reasonablefaith.org/question-answer/P50/monothelitism-and-the-trinity
"ፈቃድ ማንነትን ታሳቢ ያደረገ ነው" የሚለው ዘመናዊ የፕሮቴስታንት እሳቤ እኔ የምቀበለው እሳቤ ሲሆን ምናልባት ቀደማይ እና ታሪካዊ ፕሮቴስታንት ይህንን እሳቤ የሚቀበል አይመስለኝም።
"አብ እና ወልድ በውጫዊ ግብር ይለያያሉ፣ ሁለት የተለያየ ፈቃድ ስላላቸው አብ ላኪ ወልድ ተላኪ በመሆን የተለያየ የሥራ ድርሻ አላቸው" የሚለው የሎዶቂያው ኤጲስ ቆጶስ አቡሊናርዮስ ነው፥ ይህም እሳቤ በ381 ድኅረ ልደት በቆስጠንጢኒያ ጉባኤ ተወግዟል። የእስክንድርያው ኤጲስ ቆጶስ ፊላታዎስ እና የአንጾኪያ ኤጲስ ቆጶስ ዲዮናስዮስ ሦስቱ አካላት አንድ ፈቃድ እንዳላቸው ተናግረዋል፦
ሃይማኖተ አበው 105፥1 "ሦስቱ አካላት በመለኮት አንድ ናቸው፥ አንድ ባሕርይ፣ አንድ መንግሥት፣ አንድ አሳብ፣ ፈቃድ ናቸው"።
ሃይማኖተ አበው 111፥4 "እኛ መለኮትን እና መንግሥትን ወደ መክፈል አንገባም፥ አንድ መለኮት፣ አንድ ባሕርይ፣ አንድ ፈቃድ፣ አንዲት ውድ፣ ሦስት አካላት እና ሦስት ገጻት ብለን በጎላ በተረዳ እናስተምራለን እንጂ"።
ሌላው በ 680 ድኅረ ልደት በ 3ኛው የቁስጥንጥንያ ጉባኤ ግብጽ እና ሶሪያ እንደ ሰደድ እሳት ተዛምቶ የነበረውን የልሙጥ ፈቃድ ሙግት ለማውገዝ የተሰበሰቡበት ነው፥ "ሞኖ ቴሊቲስሞስ" μόνο θελητισμός ማለት "ልሙጥ ፈቃድ" ወይም "ሞኖ ቴሌቲዝም"Mono thelitism" ሲሆን "ዲያ ቴሊቲስሞስ" δυο θελητισμός ማለት "ሁለት ፈቃድ" ወይም "ዲያ ቴሌቲዝም"Dyo thelitism" ማለት ነው። 3ኛው የቁስጥንጥንያ ጉባኤው "ኢየሱስ ልሙጥ ፈቃድ ብቻ አለው" የሚለው ትምህርት አውግዞ በተቃራኒው "ኢየሱስ ሁለት ፈቃድ አለው" የሚለው እሳቤ አጽድቋል፥ "አንድ ነጠላ ማንነት"person" አንድ ፈቃድ አለው" በሚል መርሕ ከሄደን ኢየሱስን ሁለት ማንነት ያረገዋል። ካቶሊካውያን፣ የምሥራቅ ኦርቶዶክስ እና ፕሮቴስታንት የሚያራምዱ "ዲያ ቴሊቲስሞስ" δυο θελητισμός ሲሆኑ የጽብሓውያን ኦርቶዶክስ"Oriental Orthodox" የሚያራምዱት ደግሞ "ሚያ ቴሊቲስሞስ" μία θελητισμός ነው፥ "ሚያ ቴሊቲስሞስ" μία θελητισμός ማለት "አንድ ፈቃድ" ወይም "ሚያ ቴሌቲዝም"Mia thelitism" ማለት ሲሆን "ከሁለት ፈቃድ አንድ ፈቃድ ሆነ" የሚል ነው።
እንደ ዲኑል ኢሥላም አስተምህሮት ኢየሱስ አንድ ልሙጥ የሰው ባሕርይ"human nature" ያለው ሰዋዊ ማንነት"human person" ሲሆን ያለው ፈቃድ ደግሞ ሰዋዊ ፈቃድ"human will" ነው። እንግዲህ አምላካችን አሏህ ስለ ዒሣ ምንነት እና ማንነት በቁርኣን የነገረን ቃል እውነተኛ ቃል ነው፦
19፥34 ይህ የመርየም ልጅ ዒሣ ነው፡፡ ያ “በ”እርሱ የሚከራከሩበት እውነተኛ ቃል ነው፡፡ ذَٰلِكَ عِيسَى ٱبْنُ مَرْيَمَ ۚ قَوْلَ ٱلْحَقِّ ٱلَّذِى فِيهِ يَمْتَرُونَ
“የምተሩነ” يَمْتَرُونَ ማለት “የሚከራከሩበት” ማለት ሲሆን ብዙ ሰዎች በዒሣ ምንነት እና ማንነት ቢከራከሩበትም አሏህ ስለ ዒሣ የነገረን ግን እውነተኛ ንግግር ነው፥ “ሂ” هِ ማለትም “እርሱ” የተባለው ዒሣ ሲሆን “እርሱ” በሚለው መነሻ ቅጥያ ላይ “ፊ” فِي የሚል መስተዋድድ ሲኖር “ስለ”about” በሚል የመጣ ነው፦
"That is Jesus, son of Mary. And this is a word of truth, “about” which they dispute".
አምላካችን አሏህ በዒሣ ዙሪያ የሚወዛገቡትን ሂዳያህ ይስጣቸው! ለእኛም ጽናቱን ይስጠን! አሚን።
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
19፥34 ይህ የመርየም ልጅ ዒሣ ነው፡፡ ያ “በ”እርሱ የሚከራከሩበት እውነተኛ ቃል ነው፡፡ ذَٰلِكَ عِيسَى ٱبْنُ مَرْيَمَ ۚ قَوْلَ ٱلْحَقِّ ٱلَّذِى فِيهِ يَمْتَرُونَ
"ቴሎ" θέλω ማለት "ፈቃድ"will" ማለት ሲሆን ስለ "ፈቃድ" ያለው እሳቤ "ቴሊቲስሞስ" θελητισμός ይባላል፥ "ፈቃድ" ምንነትን"essence" ብቻ ሳይሆን ማንነትን"person" ታሳቢ እና ዋቢ ያደረገ ነው። ለምሳሌ፦ እያንዳንዱ ሰው ከሌላው ሰው የሚለየው በምንነቱ ሳይሆን በማንነቱ ነው፥ እያንዳንዱ ሰው ከሌላው ሰው የሚለየው በማንነቱ ስለሆነ እያንዳንዱ ሰው የራሱ "ፈቃድ" አለው። ፈጣሪ የራሱ ማንነት ስላለው የራሱ መለኮታዊ ፈቃድ አለው፦
ሉቃስ 22፥42 ነገር ግን የእኔ ፈቃድ አይሁን የአንተ ፈቃድ እንጂ። πλὴν μὴ τὸ θέλημά μου ἀλλὰ τὸ σὸν γινέσθω.
እዚህ አንቀጽ ላይ "ፈቃድ" ለሚለው የገባው ቃል "ቴሌማ" θέλημά ነው፥ ኢየሱስ አብን "አንተ" ሲል ማንነትን ታሳቢ ያደረገ ስለሆነ "ፈቃድ" የሚለው "አንተ" በሚል መነሻ ቅጥያ ላይ "የ" በሚል አጋናዛቢ ዘርፍ ስለመጣ ማንነትን ዋቢ ያደረገ ነው። ይሁን እና አይሁን ሁለት ፈቃድ እንጂ አንድ ፈቃድ በፍጹም አይደለም፥ ኢየሱስ ሰው ስለሆነ የሰው ማንነት እስካለው ድረስ "የእኔ ፈቃድ" ሲል "እኔ" ሲል ማንነትን ታሳቢ ያደረገ ስለሆነ "ፈቃድ" የሚለው "እኔ" በሚል መነሻ ቅጥያ ላይ "የ" በሚል አጋናዛቢ ዘርፍ ስለመጣ ማንነትን ዋቢ ያደረገ ነው። ስለዚህ ኢየሱስ እና አብ ሁለት የተለያየ ፈቃድ ያላቸው ማንነቶች ናቸው፦
ዮሐንስ 5፥30 የላከኝን ፈቃድ እንጂ የእኔን ፈቃድ አልሻምና። ὅτι οὐ ζητῶ τὸ θέλημα τὸ ἐμὸν ἀλλὰ τὸ θέλημα τοῦ πέμψαντός με.
እዚህ አንቀጽ ላይ ላይ ሁለት ጊዜ "ፈቃድ" ለሚለው የገባው ቃል "ቴሌማ" θέλημά ሲሆን አብ እና ወልድ ሁለት የተለያየ"distinct" ፈቃዶች ያላቸው ናቸው። "ፈቃድ" ምንነትን ታሳቢ ቢያደርግ ኖሮ በምድር ላይ ያለው ሰው ሁሉ በምንነት አንድ ስለሆነ አንድ ፈቃድ ብቻ ይኖረን ነበር፥ ነገር ግን እውነታው እያንዳንዱ ማንነት ከሌላው ማንነት የሚለይበት እራሱን የቻለ የራሱ ፈቃድ አለው።
፨ በአገራችን የፕሮቴስታንት ዐቃቢ እምነት ዶክተር ተስፋዬ ሮበሌ በአንድ ትምህርታቸው ላይ ዮሐንስ 5፥30 ሲያብራሩ፦ "ሁለት ፈቃድ አለ፥ ፈቃድ የሚባለው ነገር ማንነትን ሲገልጽ ዕውቀት፣ ስሜት እና ፈቃድ ነውና እዚህ ጋር "የላከኝን ፈቃድ እንጂ ፈቃዴን አልሻምና" በማለት ሁለት ፈቃድን ያሳያል" ብለዋል፥ በተጨማሪ ዶክተሩ ከዚህ ቀደም "የአሥተምህሮተ ሥላሴ መጽሐፍ ቅዱሳዊ መሠረት" በሚል መጻፋቸው፦ "ሦስት አካል ናቸው" ስንል ደግሞ አብ፣ ወልድ እና መንፈስ ቅዱስ የራሳቸው ስሜት፣ ፈቃድ እና ዕውቀት አላቸው" ማለታችን ነው" በማለት እያንዳንዱ አካል የየራሱ ፈቃድ እንዳለው ጽፏል።
፨ አሜሪካዊ የክርስትና ዐቃቢ እምነት እና የሥነ መለኮት ምሁር ዊልያም ሌን ክሬግ"William Lane Craig" የተባሉት "Reasonable Faith" በሚል ድረ ገጻቸው ሦስቱ አካላት ሦስት ፈቃድ እንዳላቸው አስቀምጠዋል፦
"አንድ የማንነት ጠንካራ እሳቤ የራስ ንቃተ ሕሊና፣ ውጥን እና ፈቃድ ማዕከል እንዳለው ካረጋገጥን ያንን ተከትለን የሥላሴ አካላት ሦስት ፈቃዳት እንዳላቸው አስባለው"።
784 Monothelitism and the Trinity May 22, 2022
https://www.reasonablefaith.org/question-answer/P50/monothelitism-and-the-trinity
"ፈቃድ ማንነትን ታሳቢ ያደረገ ነው" የሚለው ዘመናዊ የፕሮቴስታንት እሳቤ እኔ የምቀበለው እሳቤ ሲሆን ምናልባት ቀደማይ እና ታሪካዊ ፕሮቴስታንት ይህንን እሳቤ የሚቀበል አይመስለኝም።
"አብ እና ወልድ በውጫዊ ግብር ይለያያሉ፣ ሁለት የተለያየ ፈቃድ ስላላቸው አብ ላኪ ወልድ ተላኪ በመሆን የተለያየ የሥራ ድርሻ አላቸው" የሚለው የሎዶቂያው ኤጲስ ቆጶስ አቡሊናርዮስ ነው፥ ይህም እሳቤ በ381 ድኅረ ልደት በቆስጠንጢኒያ ጉባኤ ተወግዟል። የእስክንድርያው ኤጲስ ቆጶስ ፊላታዎስ እና የአንጾኪያ ኤጲስ ቆጶስ ዲዮናስዮስ ሦስቱ አካላት አንድ ፈቃድ እንዳላቸው ተናግረዋል፦
ሃይማኖተ አበው 105፥1 "ሦስቱ አካላት በመለኮት አንድ ናቸው፥ አንድ ባሕርይ፣ አንድ መንግሥት፣ አንድ አሳብ፣ ፈቃድ ናቸው"።
ሃይማኖተ አበው 111፥4 "እኛ መለኮትን እና መንግሥትን ወደ መክፈል አንገባም፥ አንድ መለኮት፣ አንድ ባሕርይ፣ አንድ ፈቃድ፣ አንዲት ውድ፣ ሦስት አካላት እና ሦስት ገጻት ብለን በጎላ በተረዳ እናስተምራለን እንጂ"።
ሌላው በ 680 ድኅረ ልደት በ 3ኛው የቁስጥንጥንያ ጉባኤ ግብጽ እና ሶሪያ እንደ ሰደድ እሳት ተዛምቶ የነበረውን የልሙጥ ፈቃድ ሙግት ለማውገዝ የተሰበሰቡበት ነው፥ "ሞኖ ቴሊቲስሞስ" μόνο θελητισμός ማለት "ልሙጥ ፈቃድ" ወይም "ሞኖ ቴሌቲዝም"Mono thelitism" ሲሆን "ዲያ ቴሊቲስሞስ" δυο θελητισμός ማለት "ሁለት ፈቃድ" ወይም "ዲያ ቴሌቲዝም"Dyo thelitism" ማለት ነው። 3ኛው የቁስጥንጥንያ ጉባኤው "ኢየሱስ ልሙጥ ፈቃድ ብቻ አለው" የሚለው ትምህርት አውግዞ በተቃራኒው "ኢየሱስ ሁለት ፈቃድ አለው" የሚለው እሳቤ አጽድቋል፥ "አንድ ነጠላ ማንነት"person" አንድ ፈቃድ አለው" በሚል መርሕ ከሄደን ኢየሱስን ሁለት ማንነት ያረገዋል። ካቶሊካውያን፣ የምሥራቅ ኦርቶዶክስ እና ፕሮቴስታንት የሚያራምዱ "ዲያ ቴሊቲስሞስ" δυο θελητισμός ሲሆኑ የጽብሓውያን ኦርቶዶክስ"Oriental Orthodox" የሚያራምዱት ደግሞ "ሚያ ቴሊቲስሞስ" μία θελητισμός ነው፥ "ሚያ ቴሊቲስሞስ" μία θελητισμός ማለት "አንድ ፈቃድ" ወይም "ሚያ ቴሌቲዝም"Mia thelitism" ማለት ሲሆን "ከሁለት ፈቃድ አንድ ፈቃድ ሆነ" የሚል ነው።
እንደ ዲኑል ኢሥላም አስተምህሮት ኢየሱስ አንድ ልሙጥ የሰው ባሕርይ"human nature" ያለው ሰዋዊ ማንነት"human person" ሲሆን ያለው ፈቃድ ደግሞ ሰዋዊ ፈቃድ"human will" ነው። እንግዲህ አምላካችን አሏህ ስለ ዒሣ ምንነት እና ማንነት በቁርኣን የነገረን ቃል እውነተኛ ቃል ነው፦
19፥34 ይህ የመርየም ልጅ ዒሣ ነው፡፡ ያ “በ”እርሱ የሚከራከሩበት እውነተኛ ቃል ነው፡፡ ذَٰلِكَ عِيسَى ٱبْنُ مَرْيَمَ ۚ قَوْلَ ٱلْحَقِّ ٱلَّذِى فِيهِ يَمْتَرُونَ
“የምተሩነ” يَمْتَرُونَ ማለት “የሚከራከሩበት” ማለት ሲሆን ብዙ ሰዎች በዒሣ ምንነት እና ማንነት ቢከራከሩበትም አሏህ ስለ ዒሣ የነገረን ግን እውነተኛ ንግግር ነው፥ “ሂ” هِ ማለትም “እርሱ” የተባለው ዒሣ ሲሆን “እርሱ” በሚለው መነሻ ቅጥያ ላይ “ፊ” فِي የሚል መስተዋድድ ሲኖር “ስለ”about” በሚል የመጣ ነው፦
"That is Jesus, son of Mary. And this is a word of truth, “about” which they dispute".
አምላካችን አሏህ በዒሣ ዙሪያ የሚወዛገቡትን ሂዳያህ ይስጣቸው! ለእኛም ጽናቱን ይስጠን! አሚን።
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
"ከአንድ በላይ አምላክ ቢኖርም ችግር የለውም" ዶክተር ተስፋዬ ሮበሌ
የመድብለ አማልክት አባዜ ሲጸናወት እንዲህ ነው።
የመድብለ አማልክት አባዜ ሲጸናወት እንዲህ ነው።
የጀነት ወጣቶች
በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
52፥24 ለእነርሱም የኾኑ ወጣቶች ልክ የተሸፈነ ሉል መስለው በእነርሱ ላይ ለማሳለፍ ይዘዋወራሉ፡፡ وَيَطُوفُ عَلَيْهِمْ غِلْمَانٌ لَّهُمْ كَأَنَّهُمْ لُؤْلُؤٌ مَّكْنُونٌ
"ወሊድ" وَلِيد ማለት "ወጣት ልጅ" ማለት ሲሆን "ዊልዳን" وِلْدَان ማለት ደግሞ "ወጣቶች ልጆች" ማለት ነው፥ በተመሳሳይ "ጉላም" غُلَام ማለት "ወጣት ልጅ" ማለት ሲሆን "ጊልማን" غِلْمَان ማለት ደግሞ "ወጣቶች ልጆች" ማለት ነው። አምላካች አሏህ ሙተቂን ለሆኑት ባሮቹ በጀነት የሚያስተናግዷቸውን አስተናጋጆች "ዊልዳን" وِلْدَان ወይም "ጊልማን" غِلْمَان በማለት ይጠራቸዋል፦
56፥17 በእነርሱ ላይ ሁል ጊዜ የማያረጁ ወጣቶች ልጆች ይዘዋወራሉ፡፡ يَطُوفُ عَلَيْهِمْ وِلْدَانٌ مُّخَلَّدُونَ
52፥24 ለእነርሱም የኾኑ ወጣቶች ልክ የተሸፈነ ሉል መስለው በእነርሱ ላይ ለማሳለፍ ይዘዋወራሉ፡፡ وَيَطُوفُ عَلَيْهِمْ غِلْمَانٌ لَّهُمْ كَأَنَّهُمْ لُؤْلُؤٌ مَّكْنُونٌ
እነዚህ አናቅጽ ላይ "ይዘዋወራሉ" ለሚለው የገባው ቃል "የጡፉ" يَطُوفُ ሲሆን "ያስተናግዳሉ" ማለት ነው። ይህ ሆኖ ሳለ "የጡፉ" يَطُوفُ የሚለውን ወልመካ እና ወሰክ የሆኑ ሚሽነሪዎች "ይዳራሉ" በማለት ይቀጥፋሉ፥ ቅሉ ግን "የጡፉ" يَطُوفُ የሚለውን "ይዳራሉ" ተብሎ የተረጎመ አንድ የቁርኣን ትርጉም የለም። ሰዎች የአሏህን ቤት ሲጎበኙ በመዘዋወር ዙሪያውን ይዞራሉ፦
22፥29 በጥንታዊውም ቤት "ይዙሩ"፡፡ وَلْيَطَّوَّفُوا بِالْبَيْتِ الْعَتِيقِ
እዚህ አንቀጽ ላይ "ይዙሩ" ለሚል የገባው የግሥ መደብ "የጦወፉ" يَطَّوَّفُوا ሲሆን "ይዳሩ" ማለት ነው? "ጦዋፍ" طَواف የሚለው ቃል "ጧፈ" طَافَ ማለትም "ዞረ" ከሚለው ሥርወ ቃል የመጣ ሲሆን "ዙረት" ማለት ነው፥ "ጧኢፊን" طَّائِفِين ደግሞ የሚዞሩት አማኞች ናቸው። ስለዚህ አንድ ቃል ብዙ ትርጉም ካለው ዐውደ ንባቡ ያላማከለ ትርጉም ለማሰጠት መሞከር እጅግ ሲበዛ ቂልነት ነው። የጀነት ወጣቶች የሚያስተናግዱት ወይን ጠጅ የሚያሰክር አይደለም፦
37፥45 ከሚመነጭ ወይን ጠጅ በያዘ ብርጭቆ በእነርሱ ላይ ይዞርባቸዋል፡፡ يُطَافُ عَلَيْهِم بِكَأْسٍ مِّن مَّعِينٍ
56፥18 ከወይን ጠጅ ምንጭ በብርጭቆዎች፣ በኩስኩስቶች እና በጽዋም በእነርሱ ላይ ይዝዞራሉ፡፡ بِأَكْوَابٍ وَأَبَارِيقَ وَكَأْسٍ مِّن مَّعِينٍ
56፥19 ከእርሷ የራስ ምታት አያገኛቸውም፤ አይሰክሩምም፡፡ لَّا يُصَدَّعُونَ عَنْهَا وَلَا يُنزِفُونَ
"ሃ" هَا ማለት "እርሷ" ማለት ሲሆን "ሃ" هَا የሚለው ተውላጠ ስም "የወይን ጠጅ ምንጭ" የሚለውን ተክቶ የመጣ ቃል ነው፥ ይህ ሆኖ ሳለ "አይሰክሩም" ለሚለው የገባው ቃል "ዩንዚፉን" يُنزِفُون ሲሆን ሚሽነሪዎች "አይደሙም" ማለት ነው" በማለት የጀነት ወጣቶች ከአማኞች ጋር የግብረ ሰዶም ተራክቦ ሲያደርጉ እንደማይደሙ ለማስመሰል ይዳዳሉ።
በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
52፥24 ለእነርሱም የኾኑ ወጣቶች ልክ የተሸፈነ ሉል መስለው በእነርሱ ላይ ለማሳለፍ ይዘዋወራሉ፡፡ وَيَطُوفُ عَلَيْهِمْ غِلْمَانٌ لَّهُمْ كَأَنَّهُمْ لُؤْلُؤٌ مَّكْنُونٌ
"ወሊድ" وَلِيد ማለት "ወጣት ልጅ" ማለት ሲሆን "ዊልዳን" وِلْدَان ማለት ደግሞ "ወጣቶች ልጆች" ማለት ነው፥ በተመሳሳይ "ጉላም" غُلَام ማለት "ወጣት ልጅ" ማለት ሲሆን "ጊልማን" غِلْمَان ማለት ደግሞ "ወጣቶች ልጆች" ማለት ነው። አምላካች አሏህ ሙተቂን ለሆኑት ባሮቹ በጀነት የሚያስተናግዷቸውን አስተናጋጆች "ዊልዳን" وِلْدَان ወይም "ጊልማን" غِلْمَان በማለት ይጠራቸዋል፦
56፥17 በእነርሱ ላይ ሁል ጊዜ የማያረጁ ወጣቶች ልጆች ይዘዋወራሉ፡፡ يَطُوفُ عَلَيْهِمْ وِلْدَانٌ مُّخَلَّدُونَ
52፥24 ለእነርሱም የኾኑ ወጣቶች ልክ የተሸፈነ ሉል መስለው በእነርሱ ላይ ለማሳለፍ ይዘዋወራሉ፡፡ وَيَطُوفُ عَلَيْهِمْ غِلْمَانٌ لَّهُمْ كَأَنَّهُمْ لُؤْلُؤٌ مَّكْنُونٌ
እነዚህ አናቅጽ ላይ "ይዘዋወራሉ" ለሚለው የገባው ቃል "የጡፉ" يَطُوفُ ሲሆን "ያስተናግዳሉ" ማለት ነው። ይህ ሆኖ ሳለ "የጡፉ" يَطُوفُ የሚለውን ወልመካ እና ወሰክ የሆኑ ሚሽነሪዎች "ይዳራሉ" በማለት ይቀጥፋሉ፥ ቅሉ ግን "የጡፉ" يَطُوفُ የሚለውን "ይዳራሉ" ተብሎ የተረጎመ አንድ የቁርኣን ትርጉም የለም። ሰዎች የአሏህን ቤት ሲጎበኙ በመዘዋወር ዙሪያውን ይዞራሉ፦
22፥29 በጥንታዊውም ቤት "ይዙሩ"፡፡ وَلْيَطَّوَّفُوا بِالْبَيْتِ الْعَتِيقِ
እዚህ አንቀጽ ላይ "ይዙሩ" ለሚል የገባው የግሥ መደብ "የጦወፉ" يَطَّوَّفُوا ሲሆን "ይዳሩ" ማለት ነው? "ጦዋፍ" طَواف የሚለው ቃል "ጧፈ" طَافَ ማለትም "ዞረ" ከሚለው ሥርወ ቃል የመጣ ሲሆን "ዙረት" ማለት ነው፥ "ጧኢፊን" طَّائِفِين ደግሞ የሚዞሩት አማኞች ናቸው። ስለዚህ አንድ ቃል ብዙ ትርጉም ካለው ዐውደ ንባቡ ያላማከለ ትርጉም ለማሰጠት መሞከር እጅግ ሲበዛ ቂልነት ነው። የጀነት ወጣቶች የሚያስተናግዱት ወይን ጠጅ የሚያሰክር አይደለም፦
37፥45 ከሚመነጭ ወይን ጠጅ በያዘ ብርጭቆ በእነርሱ ላይ ይዞርባቸዋል፡፡ يُطَافُ عَلَيْهِم بِكَأْسٍ مِّن مَّعِينٍ
56፥18 ከወይን ጠጅ ምንጭ በብርጭቆዎች፣ በኩስኩስቶች እና በጽዋም በእነርሱ ላይ ይዝዞራሉ፡፡ بِأَكْوَابٍ وَأَبَارِيقَ وَكَأْسٍ مِّن مَّعِينٍ
56፥19 ከእርሷ የራስ ምታት አያገኛቸውም፤ አይሰክሩምም፡፡ لَّا يُصَدَّعُونَ عَنْهَا وَلَا يُنزِفُونَ
"ሃ" هَا ማለት "እርሷ" ማለት ሲሆን "ሃ" هَا የሚለው ተውላጠ ስም "የወይን ጠጅ ምንጭ" የሚለውን ተክቶ የመጣ ቃል ነው፥ ይህ ሆኖ ሳለ "አይሰክሩም" ለሚለው የገባው ቃል "ዩንዚፉን" يُنزِفُون ሲሆን ሚሽነሪዎች "አይደሙም" ማለት ነው" በማለት የጀነት ወጣቶች ከአማኞች ጋር የግብረ ሰዶም ተራክቦ ሲያደርጉ እንደማይደሙ ለማስመሰል ይዳዳሉ።
፨ሲጀመር "ከእርሷ" ማለትም "ከወይን ጠጇ አይደሙም" በሰዋሰዋዊ አወቃቀር ትርጉም አይሰጥም።
፨ ሲቀጥል ግብረ ሰዶም በኢሥላም እጅግ አጸያፊ ኃጢአት ነው።
፨ሢሰልስ "ነዘፈ" نَزَفَ ማለት "ሰከረ" "ደማ" በሚል ይመጣል፥ ነገር ግን እዚህ ዐውድ ላይ "ላ ዩንዚፉን" لَا يُنزِفُون የሚለው "አይሰክሩም" እንጂ "አይደሙም" ለማለት እንደማያስኬድ የምናውቀው "የራስ ምታት አያገኛቸውም" የሚለው ኃይለ ቃል መቀመጡም ነው፦
37፥47 በእርሷ ውስጥም የራስ ምታት የለባትም፡፡ እነርሱም ከእርሷ የሚሰክሩ አይደሉም፡፡ لَا فِيهَا غَوْلٌ وَلَا هُمْ عَنْهَا يُنزَفُونَ
56፥19 ከእርሷ የራስ ምታት አያገኛቸውም፤ አይሰክሩምም፡፡ لَّا يُصَدَّعُونَ عَنْهَا وَلَا يُنزِفُونَ
"ፊ ሃ" فِيهَا ማለት "በእርሷ ውስጥ" ማለት ሲሆን "እርሷ" የተባለችው "ጀናህ" ናት፥ "ዐን ሃ" عَنْهَا ማለት ደግሞ "ከእርሷ" ማለት ሲሆን "እርሷ" የተባለችው "የወይን ጠጅ ምንጭ" ናት። ዱንያህ ላይ ያለው የወይን ጠጅ የራስ ምታት እና ስካር አለው፥ በጀናህ ውስጥ ያለችው ግን የራስ ምታት እና ስካር የላትም።
፨ ሲያረብብ "ኢሥሙል ሙሽተሪክ" اِسْم المُشْتَرِك ማለት "ተመሳሳይ ቃል ግን የተለያየ ትርጉም ያለው አሳብ"Homonym" ነው፥ ዐረቢኛ ላይ ተመሳሳይ ቃል ቢኖረው እንኳን ተመሳሳይ አሳብ እና ትርጉም አለው ማለት አይደለም። የአንድን ቃል አማራጭ ትርጉም የሚወስነው ቃሉ የሚገኝበት አረፍተ ነገር ወይም ዐውድ እንደ ሆነ ቅቡል ነው፥ መታየት ያለበት ቃሉ ብቻ ሳይሆን ቃሉ የወከለው አሳብም ጭምር ነው። ለምሳሌ፦ "በዐሰ" بَعَثَ ማለት "ላከ" ማለት ነው፦
25፥41 ባዩህም ጊዜ ያ አሏህ መልእክተኛ አድርጎ የላከው ይህ ነውን እያሉ መሳለቂያ እንጂ ሌላ አያደርጉህም፡፡ وَإِذَا رَأَوْكَ إِن يَتَّخِذُونَكَ إِلَّا هُزُوًا أَهَـٰذَا الَّذِي بَعَثَ اللَّهُ رَسُولًا
እዚህ አንቀጽ ላይ "ላከ" ለሚለው የገባው ቃል "በዐሰ" بَعَثَ ሲሆን "አርሠለ" أَرْسَلَ ማለት ነው፥ ነገር ግን "በዐሰ" بَعَثَ ማለት "ቀሰቀሰ" ወይም "አስነሳ" ማለት ነው፦
36፥52 «ወይ ጥፋታችን! ከመኝታችን ማን ቀሰቀሰን? ይህ ያ አዛኙ ጌታ በእርሱ የቀጠረን መልክተኞቹም እውነትን የነገሩን ነው» ይላሉ፡፡ قَالُوا يَا وَيْلَنَا مَن بَعَثَنَا مِن مَّرْقَدِنَا ۜ ۗ هَـٰذَا مَا وَعَدَ الرَّحْمَـٰنُ وَصَدَقَ الْمُرْسَلُونَ
እዚህ አንቀጽ ላይ "ቀሰቀሰ" ለሚለው የገባው ቃል "በዐሰ" بَعَثَ ሲሆን "አቃመ" أقَامَ ማለት ነው፥ ስለዚህ "አሏህ መልእክተኛ አድርጎ የቀሰቀሰው ይህ ነው" ወይም "ወይ ጥፋታችን! ከመኝታችን ማን ላከን" ብለን ብናስቀምጠው ትርጉም አልባ ነው። ሌላ ምሳሌ ከባይብል "ኤል" אֵל ማለት "አምላክ" ማለት ነው፦
ሚክያስ 7፥18 እንደ አንተ ያለ "አምላክ" ማን ነው? מִי־אֵ֣ל כָּמֹ֗וךָ
እዚህ አንቀጽ ላይ "አምላክ" ለሚለው የገባው ቃል "ኤል" אֵל ሲሆን "ኤሎሃ" אֱלוֹהַּ ለሚል ምጻረ ቃል ነው፥ ነገር ግን "ኤል" אֵל ማለት "ኃይል" ማለትም ነው፦
ሚክያስ 2፥1 በመኝታቸው ላይ በደልን ለሚያስቡ ክፋትንም ለሚያደርጉ ወዮላቸው! "ኃይል" በእጃቸው ነውና ሲነጋ ይፈጽሙታል። הֹ֧וי חֹֽשְׁבֵי־אָ֛וֶן וּפֹ֥עֲלֵי רָ֖ע עַל־מִשְׁכְּבֹותָ֑ם בְּאֹ֤ור הַבֹּ֙קֶר֙ יַעֲשׂ֔וּהָ כִּ֥י יֶשׁ־לְאֵ֖ל יָדָֽם׃
እዚህ አንቀጽ ላይ "ኃይል" ለሚለው የገባው ቃል "ኤል" אֵל ሲሆን "አምላክ" በሚል ፍቺ ብቻ ይዤ "አምላክ በእጃቸው ነውና ሲነጋ ይፈጽሙታል" ትርጉም ይሰጣል? ግግም ብዬ "በመኝታ ላይ ስለ ተራክቦ የሚያስብ ሲነጋ አምላክ በእጁ ነውና አምላክን ተራክቦ ያደርገዋል" ብል እችል ይሆናል፥ ቅሉ እና ጥቅሉ ግን አንደኛ ትርጉም አይሰጥም፣ ሁለተኛ አምላክ በሰው እጅ አይደለም፣ ሦስተኛ ዐውዱን ያላማከለ ሰጊዎታዊ ሥነ አፈታት ነው።
ይህንን ከተረዳን ዘንዳ ከላይ ያለውንም የቁርኣን አንቀጽ በዚህ መልክ እና ልክ ቆፍጠን ብላችሁ ተረዱት ለሰዎችን አስረዱት እንጂ "እኛ ያልወጠወጥነው ወጥ አይጣፍጥም" ብሎ መጀባነን አዋጪ አይደለም፥ በዘርፉ የተሰማሩ የቋንቋው መስክ ምሁራን እያሉ "እኔ ዐውቃለው" ብሎ ማንቃረር ከዘፋኙ በላይ መወዝወዝ ነው። አምላካችን አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይወፍቀን! አሚን።
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
፨ ሲቀጥል ግብረ ሰዶም በኢሥላም እጅግ አጸያፊ ኃጢአት ነው።
፨ሢሰልስ "ነዘፈ" نَزَفَ ማለት "ሰከረ" "ደማ" በሚል ይመጣል፥ ነገር ግን እዚህ ዐውድ ላይ "ላ ዩንዚፉን" لَا يُنزِفُون የሚለው "አይሰክሩም" እንጂ "አይደሙም" ለማለት እንደማያስኬድ የምናውቀው "የራስ ምታት አያገኛቸውም" የሚለው ኃይለ ቃል መቀመጡም ነው፦
37፥47 በእርሷ ውስጥም የራስ ምታት የለባትም፡፡ እነርሱም ከእርሷ የሚሰክሩ አይደሉም፡፡ لَا فِيهَا غَوْلٌ وَلَا هُمْ عَنْهَا يُنزَفُونَ
56፥19 ከእርሷ የራስ ምታት አያገኛቸውም፤ አይሰክሩምም፡፡ لَّا يُصَدَّعُونَ عَنْهَا وَلَا يُنزِفُونَ
"ፊ ሃ" فِيهَا ማለት "በእርሷ ውስጥ" ማለት ሲሆን "እርሷ" የተባለችው "ጀናህ" ናት፥ "ዐን ሃ" عَنْهَا ማለት ደግሞ "ከእርሷ" ማለት ሲሆን "እርሷ" የተባለችው "የወይን ጠጅ ምንጭ" ናት። ዱንያህ ላይ ያለው የወይን ጠጅ የራስ ምታት እና ስካር አለው፥ በጀናህ ውስጥ ያለችው ግን የራስ ምታት እና ስካር የላትም።
፨ ሲያረብብ "ኢሥሙል ሙሽተሪክ" اِسْم المُشْتَرِك ማለት "ተመሳሳይ ቃል ግን የተለያየ ትርጉም ያለው አሳብ"Homonym" ነው፥ ዐረቢኛ ላይ ተመሳሳይ ቃል ቢኖረው እንኳን ተመሳሳይ አሳብ እና ትርጉም አለው ማለት አይደለም። የአንድን ቃል አማራጭ ትርጉም የሚወስነው ቃሉ የሚገኝበት አረፍተ ነገር ወይም ዐውድ እንደ ሆነ ቅቡል ነው፥ መታየት ያለበት ቃሉ ብቻ ሳይሆን ቃሉ የወከለው አሳብም ጭምር ነው። ለምሳሌ፦ "በዐሰ" بَعَثَ ማለት "ላከ" ማለት ነው፦
25፥41 ባዩህም ጊዜ ያ አሏህ መልእክተኛ አድርጎ የላከው ይህ ነውን እያሉ መሳለቂያ እንጂ ሌላ አያደርጉህም፡፡ وَإِذَا رَأَوْكَ إِن يَتَّخِذُونَكَ إِلَّا هُزُوًا أَهَـٰذَا الَّذِي بَعَثَ اللَّهُ رَسُولًا
እዚህ አንቀጽ ላይ "ላከ" ለሚለው የገባው ቃል "በዐሰ" بَعَثَ ሲሆን "አርሠለ" أَرْسَلَ ማለት ነው፥ ነገር ግን "በዐሰ" بَعَثَ ማለት "ቀሰቀሰ" ወይም "አስነሳ" ማለት ነው፦
36፥52 «ወይ ጥፋታችን! ከመኝታችን ማን ቀሰቀሰን? ይህ ያ አዛኙ ጌታ በእርሱ የቀጠረን መልክተኞቹም እውነትን የነገሩን ነው» ይላሉ፡፡ قَالُوا يَا وَيْلَنَا مَن بَعَثَنَا مِن مَّرْقَدِنَا ۜ ۗ هَـٰذَا مَا وَعَدَ الرَّحْمَـٰنُ وَصَدَقَ الْمُرْسَلُونَ
እዚህ አንቀጽ ላይ "ቀሰቀሰ" ለሚለው የገባው ቃል "በዐሰ" بَعَثَ ሲሆን "አቃመ" أقَامَ ማለት ነው፥ ስለዚህ "አሏህ መልእክተኛ አድርጎ የቀሰቀሰው ይህ ነው" ወይም "ወይ ጥፋታችን! ከመኝታችን ማን ላከን" ብለን ብናስቀምጠው ትርጉም አልባ ነው። ሌላ ምሳሌ ከባይብል "ኤል" אֵל ማለት "አምላክ" ማለት ነው፦
ሚክያስ 7፥18 እንደ አንተ ያለ "አምላክ" ማን ነው? מִי־אֵ֣ל כָּמֹ֗וךָ
እዚህ አንቀጽ ላይ "አምላክ" ለሚለው የገባው ቃል "ኤል" אֵל ሲሆን "ኤሎሃ" אֱלוֹהַּ ለሚል ምጻረ ቃል ነው፥ ነገር ግን "ኤል" אֵל ማለት "ኃይል" ማለትም ነው፦
ሚክያስ 2፥1 በመኝታቸው ላይ በደልን ለሚያስቡ ክፋትንም ለሚያደርጉ ወዮላቸው! "ኃይል" በእጃቸው ነውና ሲነጋ ይፈጽሙታል። הֹ֧וי חֹֽשְׁבֵי־אָ֛וֶן וּפֹ֥עֲלֵי רָ֖ע עַל־מִשְׁכְּבֹותָ֑ם בְּאֹ֤ור הַבֹּ֙קֶר֙ יַעֲשׂ֔וּהָ כִּ֥י יֶשׁ־לְאֵ֖ל יָדָֽם׃
እዚህ አንቀጽ ላይ "ኃይል" ለሚለው የገባው ቃል "ኤል" אֵל ሲሆን "አምላክ" በሚል ፍቺ ብቻ ይዤ "አምላክ በእጃቸው ነውና ሲነጋ ይፈጽሙታል" ትርጉም ይሰጣል? ግግም ብዬ "በመኝታ ላይ ስለ ተራክቦ የሚያስብ ሲነጋ አምላክ በእጁ ነውና አምላክን ተራክቦ ያደርገዋል" ብል እችል ይሆናል፥ ቅሉ እና ጥቅሉ ግን አንደኛ ትርጉም አይሰጥም፣ ሁለተኛ አምላክ በሰው እጅ አይደለም፣ ሦስተኛ ዐውዱን ያላማከለ ሰጊዎታዊ ሥነ አፈታት ነው።
ይህንን ከተረዳን ዘንዳ ከላይ ያለውንም የቁርኣን አንቀጽ በዚህ መልክ እና ልክ ቆፍጠን ብላችሁ ተረዱት ለሰዎችን አስረዱት እንጂ "እኛ ያልወጠወጥነው ወጥ አይጣፍጥም" ብሎ መጀባነን አዋጪ አይደለም፥ በዘርፉ የተሰማሩ የቋንቋው መስክ ምሁራን እያሉ "እኔ ዐውቃለው" ብሎ ማንቃረር ከዘፋኙ በላይ መወዝወዝ ነው። አምላካችን አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይወፍቀን! አሚን።
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
የሂንዱ ሥላሴ
ክፍል አንድ
በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
4፥171 «ሦስት ነው» አትበሉ! ተከልከሉ! ለእናንተ የተሻለ ይኾናልና፡፡ አሏህ አንድ አምላክ ብቻ ነው፡፡ وَلَا تَقُولُوا ثَلَاثَةٌ ۚ انتَهُوا خَيْرًا لَّكُمْ ۚ إِنَّمَا اللَّهُ إِلَـٰهٌ وَاحِدٌ
አምላካችን አሏህ ከነቢያችን”ﷺ” በፊት መልእክተኞች ልኳል፥ ከእነርሱ ውስጥ በነቢያችን”ﷺ” ላይ ስማቸው የተተረኩ እና ከእነርሱም ውስጥ ስማቸው ያልተተረኩ አሉ፦
40፥78 ከአንተ በፊትም መልእክተኞችን በእርግጥ ልከናል፡፡ ከእነርሱ በአንተ ላይ የተረክንልህ አለ፥ ከእነርሱም በአንተ ላይ ያልተረክነው አለ፡፡ وَلَقَدْ أَرْسَلْنَا رُسُلًا مِّن قَبْلِكَ مِنْهُم مَّن قَصَصْنَا عَلَيْكَ وَمِنْهُم مَّن لَّمْ نَقْصُصْ عَلَيْكَ
ስማቸው የተተረኩ ነቢያት በቁርኣን በግልጽ ተቀምጠዋል፥ ነገር ግን ስማቸው ያልተጠቀሱ ግን አሏህ በቁርኣን ያልተረካቸው ነቢያት አሉ። ክሪሺና እና የቬዳህ ነቢያት በቁርኣን ስላልተጠቀሱ "የአሏህ ነቢያት ናቸው" ብለን መናገር ባንችልም "ሐሰተኛ ነቢያት ናቸው" ለማለት ግን የሚያስደፍር አይደለም፥ ምክንያቱም ቅዱሳን መጻሕፍቶቻቸው ስለ ተበረዙ እና በመጻሕፍቶቻቸው የተውሒድ ትምህርት እና ትንቢት ስላቀፉ ጭምር ነው። "ነቢያት ናቸው" "ነቢያት አይደሉም" ከማለት ይልቅ ዝምታን መምረጡ ብልህነት ነው፥ ምክንያቱም በግልጽ በቁርኣን የተቀመጠ ነገር የለም።
"ሳንስክሪት"Sanskrit" የሚለው ቃል "ሳምስክርታ" संस्कृत ከሚል ቃል የመጣ ሲሆን የሁለት ቃላት ውቅር ነው፥ "ሳም" कृत ማለት "ጥምረት" ማለት ሲሆን "ስክርታ" संस् ማለት "ሥራ" ማለት ነው። የኢንዶ እና የአርያን ሥራ ጥምረት ያመጣው ቋንቋ "ሳምስክርታ" संस्कृत ይባላል፥የሂንዱ ቅዱሳን መጽሐፍት የተዘጋጁት በሳንስክሪት ቋንቋ ነው።
፨ በድራቪድ ህንድ ዘመን በ 3102 ቅድመ ልደት ክሪሽና ለንጉሥ አርጁ የሰጠበት ምክር ቅዱስ መጽሐፍ "ባቫጋድ ጊታ" भगवद्गीता ይባላል።
፨ በ 1500 ቅድመ ልደት አርአያን ወደ ህንድ ሲገቡ ከተነሱት ነቢያት የተገለጠላቸው መጽሐፍ "ቬዳህ" वेदः ሲባል ቬዳህ አራት ክፍል ሲኖሩት የምሥጋና ቬዳህ "ሪግ ቬዳህ" ऋग्वेद ሲባል፣ የመሥዋዕት ቬዳህ "ያጁር ቬዳህ" यजुर्वेद ሲባል፣ የመዝሙር ቬዳህ "ሳም ቬዳህ" सामवेद ሲባል፣ የክህነት ቬዳህ "አዛርቫ ቬዳህ" अथर्ववेद ይባላል።
፨ በ 1500 ቅድመ ልደት "ፑራና" पुराण የሚባለው ትውፊት ሲሆን ይህ ትውፊት መጻፍ የተጀመረው በ 250 ድኅረ ልደት ነው፥ ስለ ብራህማን የሚናገረው ፑራና "ብርሃማ ፑራና" ब्रह्मपुराण ሲባል፣ ስለ ቪሽኑ የሚናገረው ፑራና "ቪሽኑ ፑራና" विष्णुपुराण ሲባል፣ ስለ ሺቫ የሚናገረው ፑራና "ሺቫ ፑራና" शिवपुराण ሲባል ብዙ ፑራናዎች አሉ።
፨ "ኡፓኒሻድ" उपनिषद् ከ 600 እስከ 300 ቅድመ ልደት በቬዳህ ላይ የተሰጠ ሰፊ ማብራሪያ"Commentary" ነው፥ ይህም ማብራሪያ "ብሪሃዳራንያካ ኦፓኒሻድ" बृहदारण्यकोपनिषद् "ቻንዶግያ ኡፓኒሻድ" छान्दोग्योपनिषद् "ስቬታስቫታራ ኡፓኒሻድ" श्वेताश्वतरोपनिषद् "ካዛ ኡፓኒሻድ" कठोपनिषद् እየተባሉ ይጠራሉ።
ይህንን ከተረዳን ዘንዳ በሂንዱ ጥንታዊ አስተምህሮት አምልኮ የሚገባው አንዱ አምላክ "ብሃጋባን" ነው፥ "ብሃጋቫን" भगवान् የሚለው ቃል "ብሃጋ" भज् ማለትም "ተመለከ" "ተባረከ" ከሚል ሥርወ ቃል የመጣ ሲሆን "የሚመለክ" "የሚባረክ" ማለት ነው። የእርሱ አምላክነት አምላክ ዘባሕርይ"Ontological term" ነው፥ እርሱ የአማልክት አምላክ ሲሆን መላእክት በእርሱ ሥር ያሉ አማልክት ናቸው። አምልኮን የሚቀበል ይህ አንድ አምላክ ብቻ እደሆን የሂንዱ ጉሪጂዎች አበክረው እና አዘክረው ይራገራሉ፦
ቻንዶግያ ኡፓኒሻድ ቅጽ 6 ምዕራፍ 2 ቁጥር 1
"ያለ ሁለተኛ አንድ ብቻ ነው"። आसीदेकमेवाद्वितीयं तस्मादसतः
ስቬታስቫታራ ኡፓኒሻድ ምዕራፍ 6 ቁጥር 11
"እርሱ አንድ አምላክ ነው፥ እርሱ በፍጥረታት ሁሉ ውስጥ የተደበቀ እና ሁሉን የሚሠራ ነው"። वह एक ईश्वर है, वह सभी रचनाओं में छिपा हुआ है और वह सब कुछ करता है
አምልኮ ለእርሱ ብቻ እንደሆነ እና ይህ አንድ አምላክ ባሕርያቱን የሚገልጹ ብዙ ስሞች እንዳሉት ተነግሯል፦
ሪግ ቬዳ መጽሐፍ 1 ምዕራፍ 1 ቁጥር 1
"ወዳጆች ሆይ! እርሱን እንጂ ሌላን አታምልኩ። ብቻውን አመስግኑት"። मा चि॑द॒न्यद्वि शं॑सत॒ सखा॑यो॒ मा रि॑षण्यत । इन्द्र॒मित्स्तो॑ता॒ वृष॑णं॒ सचा॑ सु॒ते
ሪግ ቬዳ መጽሐፍ 1 ምዕረፍ 164 ቁጥር 46
እርሱ አንድ ነው፥ ብዙ ስሞች አሉት"። सुपर्णो गरुत्मान् । एकं सद्विप्रा बहुधा वदन्त्यग्निं यमं मातरिश्वानमाहुः
ታዲያ ይህ የአንድ አምላክ አስተምህሮት ወደ አንድም ሦስትም ትምህርት እንዴት ሊሄድ ቻለ? "ትሪ" त्रि ማለት "ሦስት" ማለት ሲሆን "ሙርቲ" मूर्ति ማለት "ገጽ" "ፊት" "መልክ" ማለት ነው፥ በጥቅሉ "ትሪሙርቲ" त्रिमूर्ति ማለት "ሦስት ፊት" ማለት ሲሆን የሂዱ የሥላሴ አስተምህሮት "ትሪሙርቲ" ይባላል። በግሪክ "ፕሮሶፓን" πρόσωπον ማለት "ፊት" "ገጽ" "መልክ" ማለት ሲሆን እነዚህ የተለያየ የብሃጋቫን ፊቶች ብራህማን፣ ቪሽኑ እና ሺቫ ናቸው፦
ቪሽኑ ፑራና መጽሐፍ 1 ምዕረፍ 2 ቁጥር 66
"አንድ ልዑል ኑባሬ ራሱን በሦስት አካላት ይለያል፥ እነርሱም ብራህማን፣ ቪሽኑ እና ሺቫ ሲሆኑ እርሱ የተለያዩ ገጽታዎችን ይይዛል። እርሱ በተለያዩ ጊዜያት አጽናፈ ዓለም ይፈጥራል፣ ይጠብቃል፣ ያጠፋል"። एक राजकुमार नुबारे खुद को तीन रूपों में पहचानता है, जो ब्राह्मण, विष्णु और शिव हैं, और वह विभिन्न पहलुओं को अपनाता है। वह अलग-अलग समय पर ब्रह्मांड की रचना, संरक्षण और विनाश करता है।"
"ፓርማ" परम् ማለት "ልዑል" ማለት ነው፥ ብርሃማን አጽናፈ ዓለምን ፈጣሪ ነው፣ ቪሽኑ አጽናፈ ዓለምን ጠባቂ ነው፣ ሺቫ ደግሞ አጽናፈ ዓለምን አጥፊ ነው። እርሱ አንድ የማይከፈል መለኮት ሲሆን በሦስት አካላት ማለትም በፈጣሪው"The Creator" በብርሃማን፣ በጠባቂው"The Sustainer" በቪሽኑ እና በአጥፊው"The Annihilator" በሺቫ ይገለጣል ተብሎ ይታመናል፦
ባቫጋድ ጊታ ምዕራፍ 13 ቁጥር 17
"እርሱ የማይከፋፈል ነው፥ ነገር ግን በሕያዋን ፍጥረታት መካከል የተከፋፈለ ይመስላል። እርሱ የበላይ "ጠባቂ"፣ "አጥፊ" እና የፍጥረታት ሁሉ "ፈጣሪ" መሆኑን እወቅ። अविभक्तं च भूतेषु विभक्तमिव च स्थितम् | भूतभर्तृ च तज्ज्ञेयं ग्रसिष्णु प्रभविष्णु च ||
በቀጣይ ክፍል ኢንሻላህ አንድ መለኮትን ስለሚጋሩት ስለ ሦስቱ አካላት ስለ ፈጣሪው ብራህማን፣ ስለ ጠባቂው ቪሽኑ እና ስለ አጥፊው ሺቫ እንዳስሳለን!
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
ክፍል አንድ
በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
4፥171 «ሦስት ነው» አትበሉ! ተከልከሉ! ለእናንተ የተሻለ ይኾናልና፡፡ አሏህ አንድ አምላክ ብቻ ነው፡፡ وَلَا تَقُولُوا ثَلَاثَةٌ ۚ انتَهُوا خَيْرًا لَّكُمْ ۚ إِنَّمَا اللَّهُ إِلَـٰهٌ وَاحِدٌ
አምላካችን አሏህ ከነቢያችን”ﷺ” በፊት መልእክተኞች ልኳል፥ ከእነርሱ ውስጥ በነቢያችን”ﷺ” ላይ ስማቸው የተተረኩ እና ከእነርሱም ውስጥ ስማቸው ያልተተረኩ አሉ፦
40፥78 ከአንተ በፊትም መልእክተኞችን በእርግጥ ልከናል፡፡ ከእነርሱ በአንተ ላይ የተረክንልህ አለ፥ ከእነርሱም በአንተ ላይ ያልተረክነው አለ፡፡ وَلَقَدْ أَرْسَلْنَا رُسُلًا مِّن قَبْلِكَ مِنْهُم مَّن قَصَصْنَا عَلَيْكَ وَمِنْهُم مَّن لَّمْ نَقْصُصْ عَلَيْكَ
ስማቸው የተተረኩ ነቢያት በቁርኣን በግልጽ ተቀምጠዋል፥ ነገር ግን ስማቸው ያልተጠቀሱ ግን አሏህ በቁርኣን ያልተረካቸው ነቢያት አሉ። ክሪሺና እና የቬዳህ ነቢያት በቁርኣን ስላልተጠቀሱ "የአሏህ ነቢያት ናቸው" ብለን መናገር ባንችልም "ሐሰተኛ ነቢያት ናቸው" ለማለት ግን የሚያስደፍር አይደለም፥ ምክንያቱም ቅዱሳን መጻሕፍቶቻቸው ስለ ተበረዙ እና በመጻሕፍቶቻቸው የተውሒድ ትምህርት እና ትንቢት ስላቀፉ ጭምር ነው። "ነቢያት ናቸው" "ነቢያት አይደሉም" ከማለት ይልቅ ዝምታን መምረጡ ብልህነት ነው፥ ምክንያቱም በግልጽ በቁርኣን የተቀመጠ ነገር የለም።
"ሳንስክሪት"Sanskrit" የሚለው ቃል "ሳምስክርታ" संस्कृत ከሚል ቃል የመጣ ሲሆን የሁለት ቃላት ውቅር ነው፥ "ሳም" कृत ማለት "ጥምረት" ማለት ሲሆን "ስክርታ" संस् ማለት "ሥራ" ማለት ነው። የኢንዶ እና የአርያን ሥራ ጥምረት ያመጣው ቋንቋ "ሳምስክርታ" संस्कृत ይባላል፥የሂንዱ ቅዱሳን መጽሐፍት የተዘጋጁት በሳንስክሪት ቋንቋ ነው።
፨ በድራቪድ ህንድ ዘመን በ 3102 ቅድመ ልደት ክሪሽና ለንጉሥ አርጁ የሰጠበት ምክር ቅዱስ መጽሐፍ "ባቫጋድ ጊታ" भगवद्गीता ይባላል።
፨ በ 1500 ቅድመ ልደት አርአያን ወደ ህንድ ሲገቡ ከተነሱት ነቢያት የተገለጠላቸው መጽሐፍ "ቬዳህ" वेदः ሲባል ቬዳህ አራት ክፍል ሲኖሩት የምሥጋና ቬዳህ "ሪግ ቬዳህ" ऋग्वेद ሲባል፣ የመሥዋዕት ቬዳህ "ያጁር ቬዳህ" यजुर्वेद ሲባል፣ የመዝሙር ቬዳህ "ሳም ቬዳህ" सामवेद ሲባል፣ የክህነት ቬዳህ "አዛርቫ ቬዳህ" अथर्ववेद ይባላል።
፨ በ 1500 ቅድመ ልደት "ፑራና" पुराण የሚባለው ትውፊት ሲሆን ይህ ትውፊት መጻፍ የተጀመረው በ 250 ድኅረ ልደት ነው፥ ስለ ብራህማን የሚናገረው ፑራና "ብርሃማ ፑራና" ब्रह्मपुराण ሲባል፣ ስለ ቪሽኑ የሚናገረው ፑራና "ቪሽኑ ፑራና" विष्णुपुराण ሲባል፣ ስለ ሺቫ የሚናገረው ፑራና "ሺቫ ፑራና" शिवपुराण ሲባል ብዙ ፑራናዎች አሉ።
፨ "ኡፓኒሻድ" उपनिषद् ከ 600 እስከ 300 ቅድመ ልደት በቬዳህ ላይ የተሰጠ ሰፊ ማብራሪያ"Commentary" ነው፥ ይህም ማብራሪያ "ብሪሃዳራንያካ ኦፓኒሻድ" बृहदारण्यकोपनिषद् "ቻንዶግያ ኡፓኒሻድ" छान्दोग्योपनिषद् "ስቬታስቫታራ ኡፓኒሻድ" श्वेताश्वतरोपनिषद् "ካዛ ኡፓኒሻድ" कठोपनिषद् እየተባሉ ይጠራሉ።
ይህንን ከተረዳን ዘንዳ በሂንዱ ጥንታዊ አስተምህሮት አምልኮ የሚገባው አንዱ አምላክ "ብሃጋባን" ነው፥ "ብሃጋቫን" भगवान् የሚለው ቃል "ብሃጋ" भज् ማለትም "ተመለከ" "ተባረከ" ከሚል ሥርወ ቃል የመጣ ሲሆን "የሚመለክ" "የሚባረክ" ማለት ነው። የእርሱ አምላክነት አምላክ ዘባሕርይ"Ontological term" ነው፥ እርሱ የአማልክት አምላክ ሲሆን መላእክት በእርሱ ሥር ያሉ አማልክት ናቸው። አምልኮን የሚቀበል ይህ አንድ አምላክ ብቻ እደሆን የሂንዱ ጉሪጂዎች አበክረው እና አዘክረው ይራገራሉ፦
ቻንዶግያ ኡፓኒሻድ ቅጽ 6 ምዕራፍ 2 ቁጥር 1
"ያለ ሁለተኛ አንድ ብቻ ነው"። आसीदेकमेवाद्वितीयं तस्मादसतः
ስቬታስቫታራ ኡፓኒሻድ ምዕራፍ 6 ቁጥር 11
"እርሱ አንድ አምላክ ነው፥ እርሱ በፍጥረታት ሁሉ ውስጥ የተደበቀ እና ሁሉን የሚሠራ ነው"። वह एक ईश्वर है, वह सभी रचनाओं में छिपा हुआ है और वह सब कुछ करता है
አምልኮ ለእርሱ ብቻ እንደሆነ እና ይህ አንድ አምላክ ባሕርያቱን የሚገልጹ ብዙ ስሞች እንዳሉት ተነግሯል፦
ሪግ ቬዳ መጽሐፍ 1 ምዕራፍ 1 ቁጥር 1
"ወዳጆች ሆይ! እርሱን እንጂ ሌላን አታምልኩ። ብቻውን አመስግኑት"። मा चि॑द॒न्यद्वि शं॑सत॒ सखा॑यो॒ मा रि॑षण्यत । इन्द्र॒मित्स्तो॑ता॒ वृष॑णं॒ सचा॑ सु॒ते
ሪግ ቬዳ መጽሐፍ 1 ምዕረፍ 164 ቁጥር 46
እርሱ አንድ ነው፥ ብዙ ስሞች አሉት"። सुपर्णो गरुत्मान् । एकं सद्विप्रा बहुधा वदन्त्यग्निं यमं मातरिश्वानमाहुः
ታዲያ ይህ የአንድ አምላክ አስተምህሮት ወደ አንድም ሦስትም ትምህርት እንዴት ሊሄድ ቻለ? "ትሪ" त्रि ማለት "ሦስት" ማለት ሲሆን "ሙርቲ" मूर्ति ማለት "ገጽ" "ፊት" "መልክ" ማለት ነው፥ በጥቅሉ "ትሪሙርቲ" त्रिमूर्ति ማለት "ሦስት ፊት" ማለት ሲሆን የሂዱ የሥላሴ አስተምህሮት "ትሪሙርቲ" ይባላል። በግሪክ "ፕሮሶፓን" πρόσωπον ማለት "ፊት" "ገጽ" "መልክ" ማለት ሲሆን እነዚህ የተለያየ የብሃጋቫን ፊቶች ብራህማን፣ ቪሽኑ እና ሺቫ ናቸው፦
ቪሽኑ ፑራና መጽሐፍ 1 ምዕረፍ 2 ቁጥር 66
"አንድ ልዑል ኑባሬ ራሱን በሦስት አካላት ይለያል፥ እነርሱም ብራህማን፣ ቪሽኑ እና ሺቫ ሲሆኑ እርሱ የተለያዩ ገጽታዎችን ይይዛል። እርሱ በተለያዩ ጊዜያት አጽናፈ ዓለም ይፈጥራል፣ ይጠብቃል፣ ያጠፋል"። एक राजकुमार नुबारे खुद को तीन रूपों में पहचानता है, जो ब्राह्मण, विष्णु और शिव हैं, और वह विभिन्न पहलुओं को अपनाता है। वह अलग-अलग समय पर ब्रह्मांड की रचना, संरक्षण और विनाश करता है।"
"ፓርማ" परम् ማለት "ልዑል" ማለት ነው፥ ብርሃማን አጽናፈ ዓለምን ፈጣሪ ነው፣ ቪሽኑ አጽናፈ ዓለምን ጠባቂ ነው፣ ሺቫ ደግሞ አጽናፈ ዓለምን አጥፊ ነው። እርሱ አንድ የማይከፈል መለኮት ሲሆን በሦስት አካላት ማለትም በፈጣሪው"The Creator" በብርሃማን፣ በጠባቂው"The Sustainer" በቪሽኑ እና በአጥፊው"The Annihilator" በሺቫ ይገለጣል ተብሎ ይታመናል፦
ባቫጋድ ጊታ ምዕራፍ 13 ቁጥር 17
"እርሱ የማይከፋፈል ነው፥ ነገር ግን በሕያዋን ፍጥረታት መካከል የተከፋፈለ ይመስላል። እርሱ የበላይ "ጠባቂ"፣ "አጥፊ" እና የፍጥረታት ሁሉ "ፈጣሪ" መሆኑን እወቅ። अविभक्तं च भूतेषु विभक्तमिव च स्थितम् | भूतभर्तृ च तज्ज्ञेयं ग्रसिष्णु प्रभविष्णु च ||
በቀጣይ ክፍል ኢንሻላህ አንድ መለኮትን ስለሚጋሩት ስለ ሦስቱ አካላት ስለ ፈጣሪው ብራህማን፣ ስለ ጠባቂው ቪሽኑ እና ስለ አጥፊው ሺቫ እንዳስሳለን!
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
የሂንዱ ሥላሴ
ክፍል ሁለት
በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
4፥171 «ሦስት ነው» አትበሉ! ተከልከሉ! ለእናንተ የተሻለ ይኾናልና፡፡ አሏህ አንድ አምላክ ብቻ ነው፡፡ وَلَا تَقُولُوا ثَلَاثَةٌ ۚ انتَهُوا خَيْرًا لَّكُمْ ۚ إِنَّمَا اللَّهُ إِلَـٰهٌ وَاحِدٌ
የሂንዱ አምላክ አንድም ሥስትም አምላክ"Triune God" ነው፥ ብርሃማን አምላክ ነው፣ ቪሽኑ አምላክ ነው፣ ሺቫ አምላክ ነው። ሦስቱ አካላት ምንነታቸው አምላክ ስለሆነ አንድ አምላክ ናቸው፥ በአካል ሦስት ሲሆኑ ብርሃማን አባት፣ ቪሽኑ ልጅ፣ ሺቫ ቅዱስ መንፈስ ናቸው። በስም ሦስት ሲሆኑ ስማቸው ብርሃማን፣ ቪሽኑ፣ ሺቫ ናቸው፥ በግብር ሦስት ሲሆኑ ብርሃማን ጽንፈ ዓለምን "ፈጣሪ"፣ ቪሽኑ ጽንፈ ዓለምን "ጠባቂ"፣ ሺቫ ጽንፈ ዓለምን "አጥፊ" ናቸው።
በጥቅሉ ትሪሙርቲ፦
1. አምላክ አንድ ነው፣
2. ብርሃማን አምላክ ነው፣
3. ቪሽኑ አምላክ ነው፣
4. ሺቫ አምላክ ነው፣
5. ብርሃማን፣ ቪሽኑ እና ሺቫ ሦስት የተለያዩ አካላት ናቸው" የሚል ነው።
ስለ እነዚህ ሦስት መለኮታዊ አካላት እንመልከት!
ነጥብ አንድ
"ብርሃማን"
"ብርሃማን" ब्रह्मन् የሚለው ቃል "ብርሃማ" ब्रह्म ማለትም "ሠራ" "ፈጠረ" "አደረገ" ከሚል ሥርወ ቃል የመጣ ሲሆን "ሠሪ" "ፈጣሪ" "አድራጊ" ማለት ነው፥ ብርሃማን "እኔ ብርሃማን ነኝ" ብሎ የሚናገር ቅዋሜ ማንነት ነው፦
ብሪሃዳራንያካ ኦፓኒሻድ ቅጽ 1 ምዕራፍ 4 ቁጥር 10
"እኔ ብርሃማን ነኝ"። अहं ब्रह्म अस्मि
"አትማን" आत्मन् ማለት "በራሱ የሚኖር" ማለት ሲሆን ጅማሮ እና ፍጻሜ የሌለው ነው፥ ይህ መጀመሪያ የሌለው ፊተኛ መጨረሻ የሌለው ኃለኛ ብርሃማን ነው፦
ብሪሃዳራንያካ ኦፓኒሻድ ቅጽ 4 ምዕራፍ 4 ቁጥር 5
"አትማን ብርሃማህ ነው"። स वा अयमात्मा ब्रह्म
ይህ አትማን ብርሃማ የማይታይ፣ የማይታሰብ እና የማይለወጥ ነው፥ ብርሃማ አይወለድም፣ አይሞትም፣ አንድ ጊዜ ህልውናው አያበቃም፥ አትማን ልደት አልባ፣ የቀናት ቀደምት፣ የማይሞት እና የማያረጅ ነው፥ ፍጡር በሚጠፋ ጊዜ የማይጠፋ ነው፦
ባቫጋድ ጊታ ምዕራፍ 2 ቁጥር 25
"አትማን የማይታይ፣ የማይታሰብ እና የማይለወጥ" ተብሎ ተነግሯል። अव्यक्तोऽयमचिन्त्योऽयमविकार्योऽयमुच्यते | तस्मादेवं विदित्वैनं नानुशोचितुमर्हसि
ባቫጋድ ጊታ ምዕራፍ 2 ቁጥር 20
"አትማን አይወለድም፣ አይሞትም፣ አንድ ጊዜ ህልውናው አያበቃም፥ አትማን ልደት አልባ፣ የቀናት ቀደምት፣ የማይሞት እና የማያረጅ ነው፥ ፍጡር በሚጠፋ ጊዜ የማይጠፋ ነው"። न जायते म्रियते वा कदाचि नायं भूत्वा भविता वा न भूय: | अजो नित्य: शाश्वतोऽयं पुराणो
न हन्यते हन्यमाने शरीरे
ብርሃማን "እኔ" ባይ ነባቢ መለኮት ነው፥ "እኔ ያልተወለድኩኝ፣ ጅማሮ የለሽ እና የአጽናፈ ዓለሙ ሁሉ ታላቅ ጌታ ነኝ" በማለት የሚናገር ነው፦
ባቫጋድ ጊታ ምዕራፍ 10 ቁጥር 3
"እኔ ያልተወለድኩኝ፣ ጅማሮ የለሽ እና የአጽናፈ ዓለሙ ሁሉ ታላቅ ጌታ መሆኔን የሚያውቁኝ እነርሱ በሟቾች መካከል ከቅዠት የፀዱ እና ከክፋት ሁሉ የተላቀቁ ናቸው። यो मामजमनादिं च वेत्ति लोकमहेश्वरम् | असम्मूढ: स मर्त्येषु सर्वपापै: प्रमुच्यते
ባቫጋድ ጊታ ምዕራፍ 4 ቁጥር 6
"ምንም እንኳን እኔ ያልወለድኩኝ፣ የሕያዋን ፍጥረታት ሁሉ ጌታ እና የማይጠፋ ተፈጥሮ ቢኖረኝም እኔ ግን በዚህ ዓለም በመለኮታዊ ኃይሌ እና በባሕርያቴ እታወቃለው"። अजोऽपि सन्नव्ययात्मा भूतानामीश्वरोऽपि सन् | प्रकृतिं स्वामधिष्ठाय सम्भवाम्यात्ममायया
ብርሃማን በዚህ ዓለም በመለኮታዊ ኃይሉ እና ባሕርያቱ ይታወቃል እንጂ በምንነቱ ከፍጥረት ውጪ እና በላይ ሆኖ የሚኖር ነው፥ "አብ" ማለት "አባት"The Father" ማለት ሲሆን "ፒታ" पिता ማለት "አባት" ማለት ነው። ብርሃማህ "አባት" ተብሎአል፦
ባቫጋድ ጊታ ምዕራፍ 14 ቁጥር 4
"እኔ ሕይወት ሰጪ አባት ነኝ"። तासां ब्रह्म महद्योनिरहं बीजप्रद: पिता
ስቬታስቫታራ ኡፓኒሻድ ምዕራፍ 6 ቁጥር 9
"ለእርሱ ወላጆችም ጌታም የሉትም"። उसके न तो माता-पिता हैं और न ही गुरु
ይህ ወላጅ የሌለው ግን "አባት" የተባለው የእርሱ መልክ አይታይም፥ ማንም በዓይኑ አያየውም፦
ስቬታስቫታራ ኡፓኒሻድ ምዕራፍ 4 ቁጥር 20
"የእርሱ መልክ አይታይም፥ ማንም በዓይኑ አያየውም"። उसका रूप नहीं देखा जाता, कोई उसे आँखों से नहीं देखता
"ኦም" मो ማለት "ቃል" ማለት ሲሆን ብርሃማን ንግግር ባሕርይው የሆነ ተናጋሪ ማንነት ስለሆነ ቃል ነው፥ እርሱም "እኔ ቅዱስ ቃል ነኝ" ብሎአል፦
ባቫጋድ ጊታ ምዕራፍ 9 ቁጥር 17
"እኔ አንጺ፣ የዕውቀት ግብ እና ቅዱስ ቃል ነኝ"። वेद्यं पवित्र मो ङ्कार
ካዛ ኡፓኒሻድ ቅጽ 1 ምዕራፍ 2 ቁጥር 16
"ቃልን በህላዌው ተረዱት! አዎ ይህ ቃል ብራህማ ነው፥ ይህም ቃል ልዑል ነው"። एतद्ध्येवाक्शरं ब्रह्म एतद्ध्येवाक्शरं परम्
በእርግጥ በሂንዱ መጻሕፍት ፈርጅ እና ደርዝ ባለው መልኩ ቢጠና አንድ አምላክ ብርሃማን ነው። ታዲያ ቪሽኑ ማን ነው?
ክፍል ሁለት
በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
4፥171 «ሦስት ነው» አትበሉ! ተከልከሉ! ለእናንተ የተሻለ ይኾናልና፡፡ አሏህ አንድ አምላክ ብቻ ነው፡፡ وَلَا تَقُولُوا ثَلَاثَةٌ ۚ انتَهُوا خَيْرًا لَّكُمْ ۚ إِنَّمَا اللَّهُ إِلَـٰهٌ وَاحِدٌ
የሂንዱ አምላክ አንድም ሥስትም አምላክ"Triune God" ነው፥ ብርሃማን አምላክ ነው፣ ቪሽኑ አምላክ ነው፣ ሺቫ አምላክ ነው። ሦስቱ አካላት ምንነታቸው አምላክ ስለሆነ አንድ አምላክ ናቸው፥ በአካል ሦስት ሲሆኑ ብርሃማን አባት፣ ቪሽኑ ልጅ፣ ሺቫ ቅዱስ መንፈስ ናቸው። በስም ሦስት ሲሆኑ ስማቸው ብርሃማን፣ ቪሽኑ፣ ሺቫ ናቸው፥ በግብር ሦስት ሲሆኑ ብርሃማን ጽንፈ ዓለምን "ፈጣሪ"፣ ቪሽኑ ጽንፈ ዓለምን "ጠባቂ"፣ ሺቫ ጽንፈ ዓለምን "አጥፊ" ናቸው።
በጥቅሉ ትሪሙርቲ፦
1. አምላክ አንድ ነው፣
2. ብርሃማን አምላክ ነው፣
3. ቪሽኑ አምላክ ነው፣
4. ሺቫ አምላክ ነው፣
5. ብርሃማን፣ ቪሽኑ እና ሺቫ ሦስት የተለያዩ አካላት ናቸው" የሚል ነው።
ስለ እነዚህ ሦስት መለኮታዊ አካላት እንመልከት!
ነጥብ አንድ
"ብርሃማን"
"ብርሃማን" ब्रह्मन् የሚለው ቃል "ብርሃማ" ब्रह्म ማለትም "ሠራ" "ፈጠረ" "አደረገ" ከሚል ሥርወ ቃል የመጣ ሲሆን "ሠሪ" "ፈጣሪ" "አድራጊ" ማለት ነው፥ ብርሃማን "እኔ ብርሃማን ነኝ" ብሎ የሚናገር ቅዋሜ ማንነት ነው፦
ብሪሃዳራንያካ ኦፓኒሻድ ቅጽ 1 ምዕራፍ 4 ቁጥር 10
"እኔ ብርሃማን ነኝ"። अहं ब्रह्म अस्मि
"አትማን" आत्मन् ማለት "በራሱ የሚኖር" ማለት ሲሆን ጅማሮ እና ፍጻሜ የሌለው ነው፥ ይህ መጀመሪያ የሌለው ፊተኛ መጨረሻ የሌለው ኃለኛ ብርሃማን ነው፦
ብሪሃዳራንያካ ኦፓኒሻድ ቅጽ 4 ምዕራፍ 4 ቁጥር 5
"አትማን ብርሃማህ ነው"። स वा अयमात्मा ब्रह्म
ይህ አትማን ብርሃማ የማይታይ፣ የማይታሰብ እና የማይለወጥ ነው፥ ብርሃማ አይወለድም፣ አይሞትም፣ አንድ ጊዜ ህልውናው አያበቃም፥ አትማን ልደት አልባ፣ የቀናት ቀደምት፣ የማይሞት እና የማያረጅ ነው፥ ፍጡር በሚጠፋ ጊዜ የማይጠፋ ነው፦
ባቫጋድ ጊታ ምዕራፍ 2 ቁጥር 25
"አትማን የማይታይ፣ የማይታሰብ እና የማይለወጥ" ተብሎ ተነግሯል። अव्यक्तोऽयमचिन्त्योऽयमविकार्योऽयमुच्यते | तस्मादेवं विदित्वैनं नानुशोचितुमर्हसि
ባቫጋድ ጊታ ምዕራፍ 2 ቁጥር 20
"አትማን አይወለድም፣ አይሞትም፣ አንድ ጊዜ ህልውናው አያበቃም፥ አትማን ልደት አልባ፣ የቀናት ቀደምት፣ የማይሞት እና የማያረጅ ነው፥ ፍጡር በሚጠፋ ጊዜ የማይጠፋ ነው"። न जायते म्रियते वा कदाचि नायं भूत्वा भविता वा न भूय: | अजो नित्य: शाश्वतोऽयं पुराणो
न हन्यते हन्यमाने शरीरे
ብርሃማን "እኔ" ባይ ነባቢ መለኮት ነው፥ "እኔ ያልተወለድኩኝ፣ ጅማሮ የለሽ እና የአጽናፈ ዓለሙ ሁሉ ታላቅ ጌታ ነኝ" በማለት የሚናገር ነው፦
ባቫጋድ ጊታ ምዕራፍ 10 ቁጥር 3
"እኔ ያልተወለድኩኝ፣ ጅማሮ የለሽ እና የአጽናፈ ዓለሙ ሁሉ ታላቅ ጌታ መሆኔን የሚያውቁኝ እነርሱ በሟቾች መካከል ከቅዠት የፀዱ እና ከክፋት ሁሉ የተላቀቁ ናቸው። यो मामजमनादिं च वेत्ति लोकमहेश्वरम् | असम्मूढ: स मर्त्येषु सर्वपापै: प्रमुच्यते
ባቫጋድ ጊታ ምዕራፍ 4 ቁጥር 6
"ምንም እንኳን እኔ ያልወለድኩኝ፣ የሕያዋን ፍጥረታት ሁሉ ጌታ እና የማይጠፋ ተፈጥሮ ቢኖረኝም እኔ ግን በዚህ ዓለም በመለኮታዊ ኃይሌ እና በባሕርያቴ እታወቃለው"። अजोऽपि सन्नव्ययात्मा भूतानामीश्वरोऽपि सन् | प्रकृतिं स्वामधिष्ठाय सम्भवाम्यात्ममायया
ብርሃማን በዚህ ዓለም በመለኮታዊ ኃይሉ እና ባሕርያቱ ይታወቃል እንጂ በምንነቱ ከፍጥረት ውጪ እና በላይ ሆኖ የሚኖር ነው፥ "አብ" ማለት "አባት"The Father" ማለት ሲሆን "ፒታ" पिता ማለት "አባት" ማለት ነው። ብርሃማህ "አባት" ተብሎአል፦
ባቫጋድ ጊታ ምዕራፍ 14 ቁጥር 4
"እኔ ሕይወት ሰጪ አባት ነኝ"። तासां ब्रह्म महद्योनिरहं बीजप्रद: पिता
ስቬታስቫታራ ኡፓኒሻድ ምዕራፍ 6 ቁጥር 9
"ለእርሱ ወላጆችም ጌታም የሉትም"። उसके न तो माता-पिता हैं और न ही गुरु
ይህ ወላጅ የሌለው ግን "አባት" የተባለው የእርሱ መልክ አይታይም፥ ማንም በዓይኑ አያየውም፦
ስቬታስቫታራ ኡፓኒሻድ ምዕራፍ 4 ቁጥር 20
"የእርሱ መልክ አይታይም፥ ማንም በዓይኑ አያየውም"። उसका रूप नहीं देखा जाता, कोई उसे आँखों से नहीं देखता
"ኦም" मो ማለት "ቃል" ማለት ሲሆን ብርሃማን ንግግር ባሕርይው የሆነ ተናጋሪ ማንነት ስለሆነ ቃል ነው፥ እርሱም "እኔ ቅዱስ ቃል ነኝ" ብሎአል፦
ባቫጋድ ጊታ ምዕራፍ 9 ቁጥር 17
"እኔ አንጺ፣ የዕውቀት ግብ እና ቅዱስ ቃል ነኝ"። वेद्यं पवित्र मो ङ्कार
ካዛ ኡፓኒሻድ ቅጽ 1 ምዕራፍ 2 ቁጥር 16
"ቃልን በህላዌው ተረዱት! አዎ ይህ ቃል ብራህማ ነው፥ ይህም ቃል ልዑል ነው"። एतद्ध्येवाक्शरं ब्रह्म एतद्ध्येवाक्शरं परम्
በእርግጥ በሂንዱ መጻሕፍት ፈርጅ እና ደርዝ ባለው መልኩ ቢጠና አንድ አምላክ ብርሃማን ነው። ታዲያ ቪሽኑ ማን ነው?
ነጥብ ሁለት
"ቪሽኑ"
"ቪሽኑ" विष्णु የሚለው ቃል "ቪሽነ" विष्ण ማለትም "ጠበቀ" ከሚል ሥርወ ቃል የመጣ ሲሆን "ጠባቂ" ማለት ነው፥ ቪሽኑ በተለያየ ጊዜ ሥጋ እየለበሰ ስለሚመጣ "አቫታር" ይባላል። "አቫታር" अवतार የሚለው ቃል "አቫ" अव ማለትም "ወለደ" ከሚል ሥርወ ቃል የመጣ ሲሆን "ተወላጅ" "ወልድ"The Son" ማለት ነው፥ ከሦስቱ አካላት አንዱ ቪሽኑ በተለየ አካሉ እስከ ዛሬ ዘጠኝ ጊዜ ሥጋ ለብሶ ተወልዷል፦
ባቫጋድ ጊታ ምዕራፍ 4 ቁጥር 7
"መቼም ቢሆን ጽድቅ ባነሰ እና አመጻ በጨመረ ጊዜ አርጁን ሆይ! በዚያን ጊዜ ራሴን በምድር ላይ ተወልጄ እገልጣለሁ"። यदा यदा हि धर्मस्य ग्लानिर्भवति भारत | अभ्युत्थानमधर्मस्य तदात्मानं सृजाम्यहम्
ቪሽኑ ዘጠኝ ጊዜ ሲወለድ ማትስያ፣ ኩርማ፣ ቫራሃ፤ ናራሲማ፣ ቫማና፣ ፓራሹራማ፣ ራማ፣ ክሪሽና፣ ቡድሃ ሲሆን "ለአሥረኛ ጊዜ ወደፊት ይወለዳል" ብለው የሚጠብቁት "ካልኪ" ነው። ቪሽኑ ከዘመን ዘመን ተወልዶ በሥጋ የሚገለጥ ነው፦
ባቫጋድ ጊታ ምዕራፍ 4 ቁጥር 8
"ጻድቁን ለመጠበቅ፣ ኃጥኣንን ለማጥፋት እና የሥነ-ምግባር ሕግጋትን ድጋሚ ለመመሥረት በምድር ላይ ከዘመን ዘመን ተወልጄ እገለጣለው"። परित्राणाय साधूनां विनाशाय च दुष्कृताम् | धर्मसंस्थापनार्थाय सम्भवामि युगे युगे
ቪሽኑ የሰው ሥጋ እየለበሰ የሚመጣ ሥግው አምላክ ነው፥ እርሱ ሥጋ እየለበሰ የሚመጣ "ትሥጉት" ነው። "ሥግው" የሚለው ቃል "ተሠገወ" ማለት "ሥጋ ለበሰ" ከሚል ሥርወ ቃል የመጣ ሲሆን "ሥጋ መልበስ" ማለት ነው፥ የቪሽኑ በተደጋጋሚ ጊዜ ሥጋ እየተበሰ መምጣት እሳቤው "ተሠግዎት"Incarnation" ይባላል፦
ባቫጋድ ጊታ ምዕራፍ 9 ቁጥር 11
"በሰው መልክ ስወርድ የተታለሉ ሰዎች ሊያውቁኝ አልቻሉም፥ የፍጥረታት ሁሉ የበላይ ጌታ እንደመሆኔ የእኔን ማንነታዊ አምላክነት አያውቁም። अवजानन्ति मां मूढा मानुषीं तनुमाश्रितम् | परं भावमजानन्तो मम भूतमहेश्वरम्
በእርግጥ በሂንዱ መጻሕፍት በእማኝነት እና በአስረጅነት ቢጠና ቪሽኑ የአንዱ አምላክ መልእክተኛ ነቢይ ነው። ታዲያ ሺቫ ማን ነው?
ነጥብ ሦስት
"ሺቫ"
"ስፋጋ" स्वर्गः ማለት "ብርሃናዊ ኑባሬ" ማለት ሲሆን መላእክት ናቸው፥ ስፋጋ ልክ እንደ ባይብሉ አማልክት ዘበጸጋ"Functional term" ናቸው። "ዴቫ" देव ማለት "ሰማያዊ ኑባሬ" ማለት ሲሆን "አምላክ" ማለት ነው፥ "ዴቫታ" देवता ማለት ደግሞ "ዴቫ" देव ለሚለው ብዙ ቁጥር ሲሆን "አማልክት" ማለት ነው። ከእነዚህ የአምላክ መላእክት በተልእኮ ውኃውን የሚቆጣጠረው መልአክ "ቫሩና" वरुण ሲባል፣ ነፋስን የሚቆጣጠረው መልአክ "ቫዩ" वायु ሲባል፣ ብርሃንን የሚቆጣጠረው መልአክ "ሱርያ" सूर्य ሲባል እነዚህ መልእክተኞች እልፍ አእላፋት ናቸው። እነዚህ መላእክት መናፍስት ናቸው፥ የእነርሱ ንጉሥ እና አለቃ "ኢንድራ" "ሩንዳ" ይባላል፥ "ኢንድራ" इन्द्र ማለት "መንፈስ" ማለት ሲሆን "ሩንዳ" रुद्र ማለትም በተመሳሳይ "መንፈስ" ማለት ነው። "ሺቫ" शिव የሚለው ቃል "ሺቨ" शि ማለትም "ወደደ" ከሚል ሥርወ ቃል የመጣ ሲሆን "ተወዳጅ" ማለት ነው፥ ሺቫ ቅዱስ የሆነ መንፈስ ነው፦
ሪግ ቬዳ መጽሐፍ 2 ምዕረፍ 20 ቁጥር 3
"በታላቅ ጥሪ የተጠራ "መንፈስ" ለግላጋ፣ ወዳጅ፣ የሰዎች ተወዳጅ ቅዱስ ነው"። स नो॒ युवेन्द्रो॑ जो॒हूत्र॒: सखा॑ शि॒वो न॒राम॑स्तु पा॒ता । यः शंस॑न्तं॒ यः श॑शमा॒नमू॒ती पच॑न्तं च स्तु॒वन्तं॑ च पवित्र ॥
እዚህ አንቀጽ ላይ "ፓቪትራ" पवित्र ማለት "ቅዱስ" ማለት ሲሆን "መንፈስ" ለሚለው የገባው ቃል "ኢንድራ" इन्द्र ነው፥ "ተወዳጅ" ለሚለው የገባው ቃል ደግሞ "ሺቫ" शि॒वो ነው፦
ሪግ ቬዳ መጽሐፍ 8 ምዕረፍ 93 ቁጥር 3
"መንፈስ "ተወዳጁ" ጓደኛችን ነው"።स न॒ इन्द्र॑: शि॒वः सखाश
አሁንም "መንፈስ" ለሚለው የገባው ቃል "ኢንድራ" इन्द्र ሲሆን "ተወዳጁ" ለሚለው የገባው ቃል ደግሞ "ሺቫ" शि॒वो እንደሆነ ልብ አድርግ! ስለዚህ ሺቫ ቅዱስ መንፈስ"The Holy Spirit" ነው፥ በእርግጥ በሂንዱ መጻሕፍት በአጽንዖት እና በአንክሮት ቢጠና ሺቫ የአንዱ አምላክ መልአክ እና የመላእክት አለቃ ነው።
ክርስቲያኖች አባት"The Father፣ ልጅ"The son" እና ቅዱስ መንፈስ"The Holy Spirit" የሚሏቸው ሦስት አካላት ክርስትና ከመመሥረቱ በፊት የሂንዱ ሥላሴ ትምህርት ውስጥ ነበረ፥ ማን ከማን ኮረጀ? "ገጽ" ማለት በግዕዝ "ፊት" ማለት ሲሆን ሥላሴ ሦስት ፍፐት ያላቸው ሦስት ጌቶች ናቸው፦
ሰይፈ ሥላሴ ዘሐሙስ ምዕራፍ 5 ቁጥር 24
"ሦስት ገጽ አንድ አመለካከት ናቸው"።
ሰይፈ ሥላሴ ዘሐሙስ ምዕራፍ 5 ቁጥር 22-23
“ሦስት ጌቶች ናቸው”።
ክርስቲያኖች ሆይ! «ሦስት ነው» አትበሉ! ተከልከሉ! ለእናንተ የተሻለ ይኾናልና፡፡ አሏህ አንድ አምላክ ብቻ ነው፦
4፥171 «ሦስት ነው» አትበሉ! ተከልከሉ! ለእናንተ የተሻለ ይኾናልና፡፡ አሏህ አንድ አምላክ ብቻ ነው፡፡ وَلَا تَقُولُوا ثَلَاثَةٌ ۚ انتَهُوا خَيْرًا لَّكُمْ ۚ إِنَّمَا اللَّهُ إِلَـٰهٌ وَاحِدٌ
፨ ተፍሢሩል በገዊይ 4፥171 "ሦስት ነው አትበሉ" ያ "ሦስት ናቸው አትበሉ" ነው፥ ክርስቲያኖች፦ "አባት፣ ልጅ እና መንፈስ ቅዱስ" ይላሉ"።
(ولا تقولوا ثلاثة ) أي : ولا تقولوا هم ثلاثة ، وكانت النصارى تقول : أب وابن وروح قدس
፨ ተፍሢሩ አት ተንዊር 4፥171 "ሦስቱ አካላትን የሆኑ ክፍሎችን " "አባት፣ ልጅ እና መንፈስ ቅዱስ" በሚል ሐረግ ይገልጻሉ"። وعبّروا عن مجموع الأقانيم الثلاثة بعبارة ( آبَا ابنَا رُوحا قُدُسا )
፨ ተፍሢሩል ቁርጡቢይ 4፥171 "ክርስቲያኖቹ ከቡድኖቻቸው ጋር በሥላሴ አንድ ሆነው እንዲህ ይላሉ፦ "አሏህ አንድ ኑባሬ ነው፥ ሦስት አካላት አሉት። እያንዳንዱ አካል አምላክ ነው፥ እነርሱ በሕይወት ይኖራሉ። "አባት፣ ልጅ እና መንፈስ ቅዱስ" በሚል ይገለጻሉ"። والنصارى مع فرقهم مجمعون على التثليث ويقولون : إن الله جوهر واحد وله ثلاثة أقانيم ؛ فيجعلون كل أقنوم إلها ويعنون بالأقانيم الوجود والحياة والعلم ، وربما يعبرون عن الأقانيم بالأب والابن وروح القدس
፨ ተፍሢሩል ወሢጥ 4፥171 "ሦስት ነው አትበሉ" በተባለው ከተባለው ይልቅ ለምሳሌ፦ "በሦስት አትመኑ" ማለት ነው፥ ምክንያቱም የሦስቱ ጉዳይ የሚሉት አባባል ነው። ትርጉሙም ብትጠይቃቸው "አንዳንድ ጊዜ፦ " "አባት፣ ልጅ እና መንፈስ ቅዱስ" ይላሉ"። بقوله : ( وَلاَ تَقُولُواْ ثَلاَثَةٌ ) بدل قوله - مثلا - : ولا تؤمنن بثلاثة؛ لأن أمر الثلاثة قول يقولونه ، فإن سألتهم عن معناه قالوا تارة معناه : الآب والإِبن والروح والقدس
አምላካችን አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይወፍቀን! አሚን።
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
"ቪሽኑ"
"ቪሽኑ" विष्णु የሚለው ቃል "ቪሽነ" विष्ण ማለትም "ጠበቀ" ከሚል ሥርወ ቃል የመጣ ሲሆን "ጠባቂ" ማለት ነው፥ ቪሽኑ በተለያየ ጊዜ ሥጋ እየለበሰ ስለሚመጣ "አቫታር" ይባላል። "አቫታር" अवतार የሚለው ቃል "አቫ" अव ማለትም "ወለደ" ከሚል ሥርወ ቃል የመጣ ሲሆን "ተወላጅ" "ወልድ"The Son" ማለት ነው፥ ከሦስቱ አካላት አንዱ ቪሽኑ በተለየ አካሉ እስከ ዛሬ ዘጠኝ ጊዜ ሥጋ ለብሶ ተወልዷል፦
ባቫጋድ ጊታ ምዕራፍ 4 ቁጥር 7
"መቼም ቢሆን ጽድቅ ባነሰ እና አመጻ በጨመረ ጊዜ አርጁን ሆይ! በዚያን ጊዜ ራሴን በምድር ላይ ተወልጄ እገልጣለሁ"። यदा यदा हि धर्मस्य ग्लानिर्भवति भारत | अभ्युत्थानमधर्मस्य तदात्मानं सृजाम्यहम्
ቪሽኑ ዘጠኝ ጊዜ ሲወለድ ማትስያ፣ ኩርማ፣ ቫራሃ፤ ናራሲማ፣ ቫማና፣ ፓራሹራማ፣ ራማ፣ ክሪሽና፣ ቡድሃ ሲሆን "ለአሥረኛ ጊዜ ወደፊት ይወለዳል" ብለው የሚጠብቁት "ካልኪ" ነው። ቪሽኑ ከዘመን ዘመን ተወልዶ በሥጋ የሚገለጥ ነው፦
ባቫጋድ ጊታ ምዕራፍ 4 ቁጥር 8
"ጻድቁን ለመጠበቅ፣ ኃጥኣንን ለማጥፋት እና የሥነ-ምግባር ሕግጋትን ድጋሚ ለመመሥረት በምድር ላይ ከዘመን ዘመን ተወልጄ እገለጣለው"። परित्राणाय साधूनां विनाशाय च दुष्कृताम् | धर्मसंस्थापनार्थाय सम्भवामि युगे युगे
ቪሽኑ የሰው ሥጋ እየለበሰ የሚመጣ ሥግው አምላክ ነው፥ እርሱ ሥጋ እየለበሰ የሚመጣ "ትሥጉት" ነው። "ሥግው" የሚለው ቃል "ተሠገወ" ማለት "ሥጋ ለበሰ" ከሚል ሥርወ ቃል የመጣ ሲሆን "ሥጋ መልበስ" ማለት ነው፥ የቪሽኑ በተደጋጋሚ ጊዜ ሥጋ እየተበሰ መምጣት እሳቤው "ተሠግዎት"Incarnation" ይባላል፦
ባቫጋድ ጊታ ምዕራፍ 9 ቁጥር 11
"በሰው መልክ ስወርድ የተታለሉ ሰዎች ሊያውቁኝ አልቻሉም፥ የፍጥረታት ሁሉ የበላይ ጌታ እንደመሆኔ የእኔን ማንነታዊ አምላክነት አያውቁም። अवजानन्ति मां मूढा मानुषीं तनुमाश्रितम् | परं भावमजानन्तो मम भूतमहेश्वरम्
በእርግጥ በሂንዱ መጻሕፍት በእማኝነት እና በአስረጅነት ቢጠና ቪሽኑ የአንዱ አምላክ መልእክተኛ ነቢይ ነው። ታዲያ ሺቫ ማን ነው?
ነጥብ ሦስት
"ሺቫ"
"ስፋጋ" स्वर्गः ማለት "ብርሃናዊ ኑባሬ" ማለት ሲሆን መላእክት ናቸው፥ ስፋጋ ልክ እንደ ባይብሉ አማልክት ዘበጸጋ"Functional term" ናቸው። "ዴቫ" देव ማለት "ሰማያዊ ኑባሬ" ማለት ሲሆን "አምላክ" ማለት ነው፥ "ዴቫታ" देवता ማለት ደግሞ "ዴቫ" देव ለሚለው ብዙ ቁጥር ሲሆን "አማልክት" ማለት ነው። ከእነዚህ የአምላክ መላእክት በተልእኮ ውኃውን የሚቆጣጠረው መልአክ "ቫሩና" वरुण ሲባል፣ ነፋስን የሚቆጣጠረው መልአክ "ቫዩ" वायु ሲባል፣ ብርሃንን የሚቆጣጠረው መልአክ "ሱርያ" सूर्य ሲባል እነዚህ መልእክተኞች እልፍ አእላፋት ናቸው። እነዚህ መላእክት መናፍስት ናቸው፥ የእነርሱ ንጉሥ እና አለቃ "ኢንድራ" "ሩንዳ" ይባላል፥ "ኢንድራ" इन्द्र ማለት "መንፈስ" ማለት ሲሆን "ሩንዳ" रुद्र ማለትም በተመሳሳይ "መንፈስ" ማለት ነው። "ሺቫ" शिव የሚለው ቃል "ሺቨ" शि ማለትም "ወደደ" ከሚል ሥርወ ቃል የመጣ ሲሆን "ተወዳጅ" ማለት ነው፥ ሺቫ ቅዱስ የሆነ መንፈስ ነው፦
ሪግ ቬዳ መጽሐፍ 2 ምዕረፍ 20 ቁጥር 3
"በታላቅ ጥሪ የተጠራ "መንፈስ" ለግላጋ፣ ወዳጅ፣ የሰዎች ተወዳጅ ቅዱስ ነው"። स नो॒ युवेन्द्रो॑ जो॒हूत्र॒: सखा॑ शि॒वो न॒राम॑स्तु पा॒ता । यः शंस॑न्तं॒ यः श॑शमा॒नमू॒ती पच॑न्तं च स्तु॒वन्तं॑ च पवित्र ॥
እዚህ አንቀጽ ላይ "ፓቪትራ" पवित्र ማለት "ቅዱስ" ማለት ሲሆን "መንፈስ" ለሚለው የገባው ቃል "ኢንድራ" इन्द्र ነው፥ "ተወዳጅ" ለሚለው የገባው ቃል ደግሞ "ሺቫ" शि॒वो ነው፦
ሪግ ቬዳ መጽሐፍ 8 ምዕረፍ 93 ቁጥር 3
"መንፈስ "ተወዳጁ" ጓደኛችን ነው"።स न॒ इन्द्र॑: शि॒वः सखाश
አሁንም "መንፈስ" ለሚለው የገባው ቃል "ኢንድራ" इन्द्र ሲሆን "ተወዳጁ" ለሚለው የገባው ቃል ደግሞ "ሺቫ" शि॒वो እንደሆነ ልብ አድርግ! ስለዚህ ሺቫ ቅዱስ መንፈስ"The Holy Spirit" ነው፥ በእርግጥ በሂንዱ መጻሕፍት በአጽንዖት እና በአንክሮት ቢጠና ሺቫ የአንዱ አምላክ መልአክ እና የመላእክት አለቃ ነው።
ክርስቲያኖች አባት"The Father፣ ልጅ"The son" እና ቅዱስ መንፈስ"The Holy Spirit" የሚሏቸው ሦስት አካላት ክርስትና ከመመሥረቱ በፊት የሂንዱ ሥላሴ ትምህርት ውስጥ ነበረ፥ ማን ከማን ኮረጀ? "ገጽ" ማለት በግዕዝ "ፊት" ማለት ሲሆን ሥላሴ ሦስት ፍፐት ያላቸው ሦስት ጌቶች ናቸው፦
ሰይፈ ሥላሴ ዘሐሙስ ምዕራፍ 5 ቁጥር 24
"ሦስት ገጽ አንድ አመለካከት ናቸው"።
ሰይፈ ሥላሴ ዘሐሙስ ምዕራፍ 5 ቁጥር 22-23
“ሦስት ጌቶች ናቸው”።
ክርስቲያኖች ሆይ! «ሦስት ነው» አትበሉ! ተከልከሉ! ለእናንተ የተሻለ ይኾናልና፡፡ አሏህ አንድ አምላክ ብቻ ነው፦
4፥171 «ሦስት ነው» አትበሉ! ተከልከሉ! ለእናንተ የተሻለ ይኾናልና፡፡ አሏህ አንድ አምላክ ብቻ ነው፡፡ وَلَا تَقُولُوا ثَلَاثَةٌ ۚ انتَهُوا خَيْرًا لَّكُمْ ۚ إِنَّمَا اللَّهُ إِلَـٰهٌ وَاحِدٌ
፨ ተፍሢሩል በገዊይ 4፥171 "ሦስት ነው አትበሉ" ያ "ሦስት ናቸው አትበሉ" ነው፥ ክርስቲያኖች፦ "አባት፣ ልጅ እና መንፈስ ቅዱስ" ይላሉ"።
(ولا تقولوا ثلاثة ) أي : ولا تقولوا هم ثلاثة ، وكانت النصارى تقول : أب وابن وروح قدس
፨ ተፍሢሩ አት ተንዊር 4፥171 "ሦስቱ አካላትን የሆኑ ክፍሎችን " "አባት፣ ልጅ እና መንፈስ ቅዱስ" በሚል ሐረግ ይገልጻሉ"። وعبّروا عن مجموع الأقانيم الثلاثة بعبارة ( آبَا ابنَا رُوحا قُدُسا )
፨ ተፍሢሩል ቁርጡቢይ 4፥171 "ክርስቲያኖቹ ከቡድኖቻቸው ጋር በሥላሴ አንድ ሆነው እንዲህ ይላሉ፦ "አሏህ አንድ ኑባሬ ነው፥ ሦስት አካላት አሉት። እያንዳንዱ አካል አምላክ ነው፥ እነርሱ በሕይወት ይኖራሉ። "አባት፣ ልጅ እና መንፈስ ቅዱስ" በሚል ይገለጻሉ"። والنصارى مع فرقهم مجمعون على التثليث ويقولون : إن الله جوهر واحد وله ثلاثة أقانيم ؛ فيجعلون كل أقنوم إلها ويعنون بالأقانيم الوجود والحياة والعلم ، وربما يعبرون عن الأقانيم بالأب والابن وروح القدس
፨ ተፍሢሩል ወሢጥ 4፥171 "ሦስት ነው አትበሉ" በተባለው ከተባለው ይልቅ ለምሳሌ፦ "በሦስት አትመኑ" ማለት ነው፥ ምክንያቱም የሦስቱ ጉዳይ የሚሉት አባባል ነው። ትርጉሙም ብትጠይቃቸው "አንዳንድ ጊዜ፦ " "አባት፣ ልጅ እና መንፈስ ቅዱስ" ይላሉ"። بقوله : ( وَلاَ تَقُولُواْ ثَلاَثَةٌ ) بدل قوله - مثلا - : ولا تؤمنن بثلاثة؛ لأن أمر الثلاثة قول يقولونه ، فإن سألتهم عن معناه قالوا تارة معناه : الآب والإِبن والروح والقدس
አምላካችን አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይወፍቀን! አሚን።
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
ማበረታታት
አንድ ሰው በሚሠራው መልካም ሥራ ስናበረታታው በውስጥ ደስታ እና ፈገግታ የሚያመነጩ ሆርሞኖች አሉ፥ እነዚህ ሆርሞኖች ለውበት፣ ለጤና፣ ህመም ለማስታገስ እና እርጅና ለማደስ የሚረዱ ፍቱን መድኃኒት ናቸው። ሰውን ማበረታታት አንርሳ!
አሏህ መልካም ሥራችሁን በኢኽላስ ይቀበላችሁ! አሚን።
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom
አንድ ሰው በሚሠራው መልካም ሥራ ስናበረታታው በውስጥ ደስታ እና ፈገግታ የሚያመነጩ ሆርሞኖች አሉ፥ እነዚህ ሆርሞኖች ለውበት፣ ለጤና፣ ህመም ለማስታገስ እና እርጅና ለማደስ የሚረዱ ፍቱን መድኃኒት ናቸው። ሰውን ማበረታታት አንርሳ!
አሏህ መልካም ሥራችሁን በኢኽላስ ይቀበላችሁ! አሚን።
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom
የግብፅ ሥላሴ
በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
4፥171 «ሦስት ነው» አትበሉ! ተከልከሉ! ለእናንተ የተሻለ ይኾናልና፡፡ አሏህ አንድ አምላክ ብቻ ነው፡፡ وَلَا تَقُولُوا ثَلَاثَةٌ ۚ انتَهُوا خَيْرًا لَّكُمْ ۚ إِنَّمَا اللَّهُ إِلَـٰهٌ وَاحِدٌ
በሥነ ሥላሴ ጥናት"Triadology" ከክርስትናው ሥላሴ በፊት ሦስት የተለያየ ፊት ያላቸው "ሥሉስ አምላክ"Triple Deity" በተለያየ የዓለም ክፍሎች ይታምባቸው ነበር፥ ከእነዚያ አንዱ የግብፅ ሥላሴ ነበር። ግብፅ "እስክንድሪያ" ተብላ የተቆረቆረችው 331 ቅድመ ልደት በግሪክ ንጉሥ በታላቁ እስክንድር ሲሆን የግሪክ ቋንቋ በእስክንድሪያ ተጽዕኖ ስሳደረ አብዛኛውን የግብፅ ባህል በግሪክ ቋንቋ የተዘጋጁ ናቸው።
ይህንን ከተረዳን ዘንዳ በኮይኔ ግሪክ "ትሪ" τρῐ ማለት "ሦስት" ማለት ሲሆን "ትሪያስ" τρῐᾰς ደግሞ "ሦስትነት" ማለት ነው፥ በግዕዝ "ሥሉስ" ማለት "ሦስት" ማለት ሲሆን "ሥላሴ" ደግሞ "ሦስትነት" ማለት ነው።
"ፕሮሶፓን" πρόσωπον ማለት "ፊት" "ገጽ" "መልክ" ማለት ሲሆን በግብፅ ከጥንት ጀምሮ ሦስት ፊቶች ያላቸው ነገር ግን አምላክነትን የሚጋሩ "ኦሲሪስ" Όσιρις አባት አምላክ፣ "አይሲስ" Ἶσῐς እናት አምላክ እና "ሆረስ" Ὧρος ልጅ አምላክ ይመለኩ ነበር።
፨ "ሆ ቴዎስ ሆ ፓትሮስ" Ο Θεός ο πατρὸς ማለት "አባት አምላክ"God the Father" ማለት ሲሆን እርሱም ኦሲሪስ ነው፣
፨ "ቴስ ቴያ ቴስ ሜትሮስ" τῆς θεά τῆς μητρὸς ማለት "እናት አምላክ"Goddess the Mother" ማለት ሲሆን አይሲስ ናት፣
፨ "ሆ ቴዎስ ሆ ሁዮስ" Ο Θεός ο υἱός ማለትም "ልጅ አምላክ"God the Son" ማለት ሲሆን ሆረስ ነው።
Strudwick, Helen (2006). The Encyclopedia of Ancient Egypt. New York: Page 118.
ኤጵፋኒዮስ ዘሳልሚስ"Epiphanius of Salamis" ከ 320 እስከ 403 ድኅረ ልደት ይኖር የነበረ የቆጵሮስ ኤጲስ ቆጶስ ሲሆን "The Panarion of Epiphanius of Salamis" የተባለ ዕውቅ የታሪክ መጽሐፉ ገጽ 637 ላይ "ኮሊሪዲያን"Collyridian" ብሎ የሚጠራቸው የክርስትና ጎጥ በዐረብ ዙሪያ ይኖሩ የነበሩ "ማርያማውያን"Mariamites" ናቸው፦
"ኮሊሪዲያን ድንግል ማርያምን እንደ አምላክ ያመልኩ ነበር፥ እነዚህ ጎጥ ድንግልን በማላቅ በግጻዌ መለኮት ውስጥ ስለሚያካትቱ ማርያማውያን ይባሉ ነበር"።
Readings in Biography: A Selection of the Lives of Eminent Men of All Nations <by William Cooke Taylor> Page 192.
የማርያማውያን ሥላሴ ከግብፅ ሥላሴ የተኮረጀ ሲሆን አባት፣ እናት ማርያም እና ልጅ ኢየሱስ የተባሉ ሦስት አካላት ናቸው። ፕሮፌሰር ጆን ሆልመስ"John Holmes" ማርያማውያን ማርያምን ከሥላሴ ሦስት አካላት አንዷ እንደሆነች አድርገው ያምኑ እንደነበር አበክረው ተናግረዋል፦
"ማርያማውያን በዚህ ስያሜ የተጠሩት ማርያም ስለሚያምልኩ እና ከአባት እና ከልጅ ጋር ከመለኮታዊ የሥላሴ አካላት አንዷ አርገው ስለሚያምኑ ነው"።
The Eclectic Magazine: Foreign Literature science and Art. By John Holmes Agnew, Walter Hilliard Bidwell, volume 21, page 40.
ሚሽነሪው የሥነ መለኮት ምሁር ጊልበርት ሪድ"Gilbert Reid" የማርያማውያን ሥሉስ አምላክ"Tritheism" አባትን፣ እናትን እና ልጅን እንደሚያቅፍ ተናግረዋል፦
"ክርስትናን በተመለከተ በዐረብ አገር የተወከለው ሥሉስ አምላክ እንጂ ግልጽ ያልተበከለ አምላካዊነት አልነበረም፥ ሰማያዊ አባት፣ የአምላክ እናት ማርያም እና ልጃቸው ኢየሱስ ሥሉስ አምላክ ሆነው ይመለኩ ነበር"።
Gilbert Reid – The Biblical World: Volume 48, Number 1, Page 12.
"ትራይቴይዝም"Tritheism" የሚለው የእንግሊዝኛ ቃል "ትሪ" τρῐ እና "ቴዎስ" θεός ከሚሉ ሁለት ቃላት የተዋቀረ ነው፥ "ትሪ" τρῐ ማለት "ሦስት" ማለት ሲሆን "ቴዎስ" θεός ደግሞ "አምላክ" ማለት ነው። በላቲን "ትሪኒ" trīni ማለት "ሦስት" ማለት ሲሆን "ትሪኒታስ" trīnitās ማለት ደግሞ "ሦስትነት" ማለት ነው፥ "ትሪኒቲይ"Trinity" የሚለው የእንግሊዝኛው ቃል እራሱ "ሦስትነት"threeness" ማለት ነው።
የማርያማውያን ሥላሴ ልክ እንደ ዮሐንስ ተዐቃቢ"John Philoponus" ሦስቱ አካላት የየራሳቸው ፈቃድ፣ ዕውቀት፣ ቃል፣ ሕይወት አላቸው ስለሚሉ በዐበይት የክርስትና ሥሉሳውያን ዘንድ "ሦሉስ አምላካውያን ወይም የሦስት ባሕርያት አማንያን" የሚል ነቀፌታ ይደርስባቸዋል፥ ዮሐንስ ተዐቃቢ ከ 490 እስከ 570 ድኅረ ልደት በእስክንድርያ ይኖር የነበረ ሲሆን "ሥላሴ በከዊን አይገናዘቡም" በማለቱ እና ፈቃድን ለባሕርይ ሳይሆን ለአካል ስለሚሰጥ "ሦስት ባሕርያት" ይላል በሚል የሐሰት ክስ በ 680 ድኅረ ልደት በ3ኛው የቆስጠንጢኒያ ጉባኤ ተወግዟል፦
ሃይማኖተ አበው ምዕራፍ 85 ቁጥር 23
"ሐሰትን የያዙ ሌሎችም "ሥላሴ በባሕርይ እንደሆኑ ይናገራሉ"።
ሃይማኖተ አበው ምዕራፍ 91 ቁጥር 11
"ሦስት አማልክት እና ሦስት ባሕርያት ከሚሉት መናፍቃን ጋር አንድ በሚሆን ድንቁርናው የሚመካ ተዐቃቢ የሚባል ዮሐንስ እንደ ተናገረ ይህ የቅድስት ቤተ ክርስቲያን አነጋገር አይደለም"።
በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
4፥171 «ሦስት ነው» አትበሉ! ተከልከሉ! ለእናንተ የተሻለ ይኾናልና፡፡ አሏህ አንድ አምላክ ብቻ ነው፡፡ وَلَا تَقُولُوا ثَلَاثَةٌ ۚ انتَهُوا خَيْرًا لَّكُمْ ۚ إِنَّمَا اللَّهُ إِلَـٰهٌ وَاحِدٌ
በሥነ ሥላሴ ጥናት"Triadology" ከክርስትናው ሥላሴ በፊት ሦስት የተለያየ ፊት ያላቸው "ሥሉስ አምላክ"Triple Deity" በተለያየ የዓለም ክፍሎች ይታምባቸው ነበር፥ ከእነዚያ አንዱ የግብፅ ሥላሴ ነበር። ግብፅ "እስክንድሪያ" ተብላ የተቆረቆረችው 331 ቅድመ ልደት በግሪክ ንጉሥ በታላቁ እስክንድር ሲሆን የግሪክ ቋንቋ በእስክንድሪያ ተጽዕኖ ስሳደረ አብዛኛውን የግብፅ ባህል በግሪክ ቋንቋ የተዘጋጁ ናቸው።
ይህንን ከተረዳን ዘንዳ በኮይኔ ግሪክ "ትሪ" τρῐ ማለት "ሦስት" ማለት ሲሆን "ትሪያስ" τρῐᾰς ደግሞ "ሦስትነት" ማለት ነው፥ በግዕዝ "ሥሉስ" ማለት "ሦስት" ማለት ሲሆን "ሥላሴ" ደግሞ "ሦስትነት" ማለት ነው።
"ፕሮሶፓን" πρόσωπον ማለት "ፊት" "ገጽ" "መልክ" ማለት ሲሆን በግብፅ ከጥንት ጀምሮ ሦስት ፊቶች ያላቸው ነገር ግን አምላክነትን የሚጋሩ "ኦሲሪስ" Όσιρις አባት አምላክ፣ "አይሲስ" Ἶσῐς እናት አምላክ እና "ሆረስ" Ὧρος ልጅ አምላክ ይመለኩ ነበር።
፨ "ሆ ቴዎስ ሆ ፓትሮስ" Ο Θεός ο πατρὸς ማለት "አባት አምላክ"God the Father" ማለት ሲሆን እርሱም ኦሲሪስ ነው፣
፨ "ቴስ ቴያ ቴስ ሜትሮስ" τῆς θεά τῆς μητρὸς ማለት "እናት አምላክ"Goddess the Mother" ማለት ሲሆን አይሲስ ናት፣
፨ "ሆ ቴዎስ ሆ ሁዮስ" Ο Θεός ο υἱός ማለትም "ልጅ አምላክ"God the Son" ማለት ሲሆን ሆረስ ነው።
Strudwick, Helen (2006). The Encyclopedia of Ancient Egypt. New York: Page 118.
ኤጵፋኒዮስ ዘሳልሚስ"Epiphanius of Salamis" ከ 320 እስከ 403 ድኅረ ልደት ይኖር የነበረ የቆጵሮስ ኤጲስ ቆጶስ ሲሆን "The Panarion of Epiphanius of Salamis" የተባለ ዕውቅ የታሪክ መጽሐፉ ገጽ 637 ላይ "ኮሊሪዲያን"Collyridian" ብሎ የሚጠራቸው የክርስትና ጎጥ በዐረብ ዙሪያ ይኖሩ የነበሩ "ማርያማውያን"Mariamites" ናቸው፦
"ኮሊሪዲያን ድንግል ማርያምን እንደ አምላክ ያመልኩ ነበር፥ እነዚህ ጎጥ ድንግልን በማላቅ በግጻዌ መለኮት ውስጥ ስለሚያካትቱ ማርያማውያን ይባሉ ነበር"።
Readings in Biography: A Selection of the Lives of Eminent Men of All Nations <by William Cooke Taylor> Page 192.
የማርያማውያን ሥላሴ ከግብፅ ሥላሴ የተኮረጀ ሲሆን አባት፣ እናት ማርያም እና ልጅ ኢየሱስ የተባሉ ሦስት አካላት ናቸው። ፕሮፌሰር ጆን ሆልመስ"John Holmes" ማርያማውያን ማርያምን ከሥላሴ ሦስት አካላት አንዷ እንደሆነች አድርገው ያምኑ እንደነበር አበክረው ተናግረዋል፦
"ማርያማውያን በዚህ ስያሜ የተጠሩት ማርያም ስለሚያምልኩ እና ከአባት እና ከልጅ ጋር ከመለኮታዊ የሥላሴ አካላት አንዷ አርገው ስለሚያምኑ ነው"።
The Eclectic Magazine: Foreign Literature science and Art. By John Holmes Agnew, Walter Hilliard Bidwell, volume 21, page 40.
ሚሽነሪው የሥነ መለኮት ምሁር ጊልበርት ሪድ"Gilbert Reid" የማርያማውያን ሥሉስ አምላክ"Tritheism" አባትን፣ እናትን እና ልጅን እንደሚያቅፍ ተናግረዋል፦
"ክርስትናን በተመለከተ በዐረብ አገር የተወከለው ሥሉስ አምላክ እንጂ ግልጽ ያልተበከለ አምላካዊነት አልነበረም፥ ሰማያዊ አባት፣ የአምላክ እናት ማርያም እና ልጃቸው ኢየሱስ ሥሉስ አምላክ ሆነው ይመለኩ ነበር"።
Gilbert Reid – The Biblical World: Volume 48, Number 1, Page 12.
"ትራይቴይዝም"Tritheism" የሚለው የእንግሊዝኛ ቃል "ትሪ" τρῐ እና "ቴዎስ" θεός ከሚሉ ሁለት ቃላት የተዋቀረ ነው፥ "ትሪ" τρῐ ማለት "ሦስት" ማለት ሲሆን "ቴዎስ" θεός ደግሞ "አምላክ" ማለት ነው። በላቲን "ትሪኒ" trīni ማለት "ሦስት" ማለት ሲሆን "ትሪኒታስ" trīnitās ማለት ደግሞ "ሦስትነት" ማለት ነው፥ "ትሪኒቲይ"Trinity" የሚለው የእንግሊዝኛው ቃል እራሱ "ሦስትነት"threeness" ማለት ነው።
የማርያማውያን ሥላሴ ልክ እንደ ዮሐንስ ተዐቃቢ"John Philoponus" ሦስቱ አካላት የየራሳቸው ፈቃድ፣ ዕውቀት፣ ቃል፣ ሕይወት አላቸው ስለሚሉ በዐበይት የክርስትና ሥሉሳውያን ዘንድ "ሦሉስ አምላካውያን ወይም የሦስት ባሕርያት አማንያን" የሚል ነቀፌታ ይደርስባቸዋል፥ ዮሐንስ ተዐቃቢ ከ 490 እስከ 570 ድኅረ ልደት በእስክንድርያ ይኖር የነበረ ሲሆን "ሥላሴ በከዊን አይገናዘቡም" በማለቱ እና ፈቃድን ለባሕርይ ሳይሆን ለአካል ስለሚሰጥ "ሦስት ባሕርያት" ይላል በሚል የሐሰት ክስ በ 680 ድኅረ ልደት በ3ኛው የቆስጠንጢኒያ ጉባኤ ተወግዟል፦
ሃይማኖተ አበው ምዕራፍ 85 ቁጥር 23
"ሐሰትን የያዙ ሌሎችም "ሥላሴ በባሕርይ እንደሆኑ ይናገራሉ"።
ሃይማኖተ አበው ምዕራፍ 91 ቁጥር 11
"ሦስት አማልክት እና ሦስት ባሕርያት ከሚሉት መናፍቃን ጋር አንድ በሚሆን ድንቁርናው የሚመካ ተዐቃቢ የሚባል ዮሐንስ እንደ ተናገረ ይህ የቅድስት ቤተ ክርስቲያን አነጋገር አይደለም"።
የዘመናችን የፕሮቴስታንት ሥላሴ ሦስቱ አካላት የየራሳቸው ዕውቀት፣ ስሜት እና ፈቃድ አላቸው በሚል "ማኅበራዊ ሥላሴን"Social Trinity" እሳቤ የሚታወቁ ሲሆኑ ዕውቀት፣ ስሜት እና ፈቃድ አካልን እንጂ ባሕርይን ታሳቢ ስለማያረጉ ከዮሐንስ ተዐቃቢ ጋር ያመሳስላቸዋል። እሩቅ ሳንሄድ ዶክተር ተስፋዬ ሮበሌ ከዚህ ቀደም "የአስተምህሮተ ሥላሴ መጽሐፍ ቅዱሳዊ መሠረት" በሚል መጣጥፋቸው ላይ፦ "ሦስት አካል ናቸው" ስንል ደግሞ አብ፣ ወልድ እና መንፈስ ቅዱስ የራሳቸው ስሜት፣ ፈቃድ እና ዕውቀት አላቸው" ማለታችን ነው፥ አካል የሚለውን ቃል የምንጠቀመው እግዚአብሔር የራሱ የሆነ ስሜት፣ ፈቃድ እና ዕውቀት እንዳለው ለማሳየት ብቻ ነው" በማለት እያንዳንዱ አካል የየራሱ ዕውቀት፣ ስሜት እና ፈቃድ እንዳለው ጦምረዋል።
ወደ ነጥባችን ስንመለስ በዐረብ ዙሪያ ይኖሩ የነበሩ ማርያማውያን የክርስትና ጎጥ "ሦስት ነው" የሚሉትን ሆነ ዐበይት ክርስትና "ሦስት ነው" የሚሉትን አምላካችን አሏህ «ሦስት ነው» አትበሉ" በማለት ሁለቱንም ድንበር አላፊያን ይገስጻቸዋል፦
4፥171 «ሦስት ነው» አትበሉ! ተከልከሉ! ለእናንተ የተሻለ ይኾናልና፡፡ አሏህ አንድ አምላክ ብቻ ነው፡፡ وَلَا تَقُولُوا ثَلَاثَةٌ ۚ انتَهُوا خَيْرًا لَّكُمْ ۚ إِنَّمَا اللَّهُ إِلَـٰهٌ وَاحِدٌ
በአንድ ድንጋይ ሁለት ወፍ ይሉካል እንደዚህ ነው፥ ሦስቱን አካላት እነማን እነደሆኑ ቁርኣን ቢጠቅስ ኖሮ እያንዳንዱ አንጃ "የእኛን ሥላሴ በቅጡ አልተረዳውም፥ ቁልመማዊ ሕፀፅ አፅፆአል" ተብሎ ከሁለቱ ወገን በአንዱ ክስ ይቀርብ ነበር። ኢየሱስን የላከ አንድ አምላክ አሏህ ሆኖ ሳለ ያንን አንድ አምላክ ከሦስቱ ማንነቶች አንዱ ማንነት ነው" ማለት በእርግጥ ክህደት ነው፦
5፥73 እነዚያ «አላህ ከሦስቱ አንዱ ነው» ያሉ በእርግጥ ካዱ፡፡ لَّقَدْ كَفَرَ الَّذِينَ قَالُوا إِنَّ اللَّهَ ثَالِثُ ثَلَاثَةٍ
"Certainly they are unbelievers who say: "Allah is one of three". (Farook Malik Translation)
ተፍሢሩል ቁርጡቢይ 5፥73
የላቀው አሏህ ንግግር፦ "እነዚያ «አላህ የሦስት ሦስተኛ ነው» ያሉ በእርግጥ ካዱ" ማለት "ከሦስቱ አንዱ ነው" ማለታቸው ነው። قوله تعالى: { لَّقَدْ كَفَرَ ٱلَّذِينَ قَالُوۤاْ إِنَّ ٱللَّهَ ثَالِثُ ثَلاَثَةٍ }. أي أحد ثلاثة.
ኢብኑ ዐባሥ ዐበይት የሥላሴ አማንያን የሚሉትን ታሳቢ በማድረግ «ሦስት» ያሉት "አባትን፣ ልጅን፣ መንፈስ ቅዱስ" እንደሆኑ ሲያስቀምጥልን ጀላለይን ደግሞ ማርያማውያንን የሚሉትን ዋቢ በማድረግ «ሦስት» ያሉት "አባትን፣ ልጅን፣ እናትን" እንደሆኑ አስቀምጦልናል፦
ተፍሢር ኢብኑ ዐባሥ 5፥73 "እነዚያ «አሏህ ከሦስቱ አንዱ ነው» ያሉ በእርግጥ ካዱ፥ መርቁሢያህ፦ "አባትን፣ ልጅን፣ መንፈስ ቅዱስ" አሉ"። { لَّقَدْ كَفَرَ ٱلَّذِينَ قَالُوۤاْ إِنَّ ٱللَّهَ ثَالِثُ ثَلاَثَةٍ } وهي مقالة المرقوسية يقول أب وابن وروح قدس
ተፍሢር ጀላለይን 5፥73 «እነዚያ "አሏህ ሦስተኛ" ያሉ በእርግጥ ካዱ» አማልክት «ሦስት» አሉ፥ እርሱ(አሏህ) ከእነርሱ አንዱ ነው፥ ሁለቱ ኢየሱስ እና እናቱ ናቸው" ይህንን የሚሉት ከነሷሪይ ፊርቃህ ናቸው"።
{ لَّقَدْ كَفَرَ ٱلَّذِينَ قَالُواْ إِنَّ ٱللَّهَ ثَالِثُ } آلهة { ثَلَٰثَةً } أي أحدها والآخران عيسى وأُمّه وهم فرقة من النصارى
"ፊርቃህ" فِرْقَة ማለት "ጎጥ" "አንጃ" ማለት ነው፥ ኮሊሪዲያን በአንድ ወቅት የነበረ አሁን ላይ የጠፋ የክርስትና ጎጥ"sect" ነው። ዐበይት የክርስትና ሥሉሳውያን ሥላሴያቸው ከሂንዱ ሥላሴ የተቀዳ ሲሆን የኮሊሪዲያን ሥላሴያቸው ደግሞ ከግብፅ ሥላሴ የተቀዳ ነው፥ "ክርስቲያን ነን" የሚሉት ሁለቱም የየራሳቸውን ሥላሴ በጥቅሉ ቁርኣን በአንድ ድንጋይ "ሦስት ነው አትበሉ" በማለት ሁለቱንም አእዋፍ መቷቸዋል። ደግ አረገ! "ክርስትና የበቀለው ከዐረማዊነት ነው" የምንለው በምክንያት ነው። የክርስትና ታሪክ ምሁር ኤድዋርድ ጊቦን "History of christianity" በተባለው መጽሐፋቸው ላይ ስለ ክርስትና ዐረማዊነት"paganism" እንዲህ ሲሉ ተናግረዋል፦
"አረማዊነት በክርስትና ድል ቢነሳም ክርስትናም በዚያው መጠን በአረማዊነት ተበክሏል"።
History of christianity (Edward Gibbon) page XVI(16)
የሥላሴ አማንያን ክርስቲያኖች ሆይ! ነቢያት እና ሐዋርያት የማያውቁት እና ውስብስብ ከሆነው የክርስትና ሥላሴ ወጥታችሁ በተውሒድ እንድታምኑ ጥሪያችን ነው። አምላካችን አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይወፍቀን! አሚን።
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
ወደ ነጥባችን ስንመለስ በዐረብ ዙሪያ ይኖሩ የነበሩ ማርያማውያን የክርስትና ጎጥ "ሦስት ነው" የሚሉትን ሆነ ዐበይት ክርስትና "ሦስት ነው" የሚሉትን አምላካችን አሏህ «ሦስት ነው» አትበሉ" በማለት ሁለቱንም ድንበር አላፊያን ይገስጻቸዋል፦
4፥171 «ሦስት ነው» አትበሉ! ተከልከሉ! ለእናንተ የተሻለ ይኾናልና፡፡ አሏህ አንድ አምላክ ብቻ ነው፡፡ وَلَا تَقُولُوا ثَلَاثَةٌ ۚ انتَهُوا خَيْرًا لَّكُمْ ۚ إِنَّمَا اللَّهُ إِلَـٰهٌ وَاحِدٌ
በአንድ ድንጋይ ሁለት ወፍ ይሉካል እንደዚህ ነው፥ ሦስቱን አካላት እነማን እነደሆኑ ቁርኣን ቢጠቅስ ኖሮ እያንዳንዱ አንጃ "የእኛን ሥላሴ በቅጡ አልተረዳውም፥ ቁልመማዊ ሕፀፅ አፅፆአል" ተብሎ ከሁለቱ ወገን በአንዱ ክስ ይቀርብ ነበር። ኢየሱስን የላከ አንድ አምላክ አሏህ ሆኖ ሳለ ያንን አንድ አምላክ ከሦስቱ ማንነቶች አንዱ ማንነት ነው" ማለት በእርግጥ ክህደት ነው፦
5፥73 እነዚያ «አላህ ከሦስቱ አንዱ ነው» ያሉ በእርግጥ ካዱ፡፡ لَّقَدْ كَفَرَ الَّذِينَ قَالُوا إِنَّ اللَّهَ ثَالِثُ ثَلَاثَةٍ
"Certainly they are unbelievers who say: "Allah is one of three". (Farook Malik Translation)
ተፍሢሩል ቁርጡቢይ 5፥73
የላቀው አሏህ ንግግር፦ "እነዚያ «አላህ የሦስት ሦስተኛ ነው» ያሉ በእርግጥ ካዱ" ማለት "ከሦስቱ አንዱ ነው" ማለታቸው ነው። قوله تعالى: { لَّقَدْ كَفَرَ ٱلَّذِينَ قَالُوۤاْ إِنَّ ٱللَّهَ ثَالِثُ ثَلاَثَةٍ }. أي أحد ثلاثة.
ኢብኑ ዐባሥ ዐበይት የሥላሴ አማንያን የሚሉትን ታሳቢ በማድረግ «ሦስት» ያሉት "አባትን፣ ልጅን፣ መንፈስ ቅዱስ" እንደሆኑ ሲያስቀምጥልን ጀላለይን ደግሞ ማርያማውያንን የሚሉትን ዋቢ በማድረግ «ሦስት» ያሉት "አባትን፣ ልጅን፣ እናትን" እንደሆኑ አስቀምጦልናል፦
ተፍሢር ኢብኑ ዐባሥ 5፥73 "እነዚያ «አሏህ ከሦስቱ አንዱ ነው» ያሉ በእርግጥ ካዱ፥ መርቁሢያህ፦ "አባትን፣ ልጅን፣ መንፈስ ቅዱስ" አሉ"። { لَّقَدْ كَفَرَ ٱلَّذِينَ قَالُوۤاْ إِنَّ ٱللَّهَ ثَالِثُ ثَلاَثَةٍ } وهي مقالة المرقوسية يقول أب وابن وروح قدس
ተፍሢር ጀላለይን 5፥73 «እነዚያ "አሏህ ሦስተኛ" ያሉ በእርግጥ ካዱ» አማልክት «ሦስት» አሉ፥ እርሱ(አሏህ) ከእነርሱ አንዱ ነው፥ ሁለቱ ኢየሱስ እና እናቱ ናቸው" ይህንን የሚሉት ከነሷሪይ ፊርቃህ ናቸው"።
{ لَّقَدْ كَفَرَ ٱلَّذِينَ قَالُواْ إِنَّ ٱللَّهَ ثَالِثُ } آلهة { ثَلَٰثَةً } أي أحدها والآخران عيسى وأُمّه وهم فرقة من النصارى
"ፊርቃህ" فِرْقَة ማለት "ጎጥ" "አንጃ" ማለት ነው፥ ኮሊሪዲያን በአንድ ወቅት የነበረ አሁን ላይ የጠፋ የክርስትና ጎጥ"sect" ነው። ዐበይት የክርስትና ሥሉሳውያን ሥላሴያቸው ከሂንዱ ሥላሴ የተቀዳ ሲሆን የኮሊሪዲያን ሥላሴያቸው ደግሞ ከግብፅ ሥላሴ የተቀዳ ነው፥ "ክርስቲያን ነን" የሚሉት ሁለቱም የየራሳቸውን ሥላሴ በጥቅሉ ቁርኣን በአንድ ድንጋይ "ሦስት ነው አትበሉ" በማለት ሁለቱንም አእዋፍ መቷቸዋል። ደግ አረገ! "ክርስትና የበቀለው ከዐረማዊነት ነው" የምንለው በምክንያት ነው። የክርስትና ታሪክ ምሁር ኤድዋርድ ጊቦን "History of christianity" በተባለው መጽሐፋቸው ላይ ስለ ክርስትና ዐረማዊነት"paganism" እንዲህ ሲሉ ተናግረዋል፦
"አረማዊነት በክርስትና ድል ቢነሳም ክርስትናም በዚያው መጠን በአረማዊነት ተበክሏል"።
History of christianity (Edward Gibbon) page XVI(16)
የሥላሴ አማንያን ክርስቲያኖች ሆይ! ነቢያት እና ሐዋርያት የማያውቁት እና ውስብስብ ከሆነው የክርስትና ሥላሴ ወጥታችሁ በተውሒድ እንድታምኑ ጥሪያችን ነው። አምላካችን አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይወፍቀን! አሚን።
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
ማኅበራዊ ሥላሴ
በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
21፥22 በሁለቱ በሰማያት እና በምድር ውስጥ ከአሏህ ሌላ አማልክት በነበሩ ኖሮ በተበላሹ ነበር፡፡ የዐርሹ ጌታ አሏህ ከሚሉት ሁሉ ጠራ፡፡ لَوْ كَانَ فِيهِمَا آلِهَةٌ إِلَّا اللَّهُ لَفَسَدَتَا ۚ فَسُبْحَانَ اللَّهِ رَبِّ الْعَرْشِ عَمَّا يَصِفُونَ
"ማኅበር" ማለት የእርስ በእርስ ግኑኝነት ሲሆን በሥነ እውነት ጥናት"Metaphysics" እያንዳንዱ ማንነት ከሌላው ማንነት ጋር ያለው ዕውቀት፣ ስሜት እና ፈቃድ ነው፥ በነገረ ሥላሴ ጥናት ውስጥ ማኅበራዊ ሥላሴ"Social Trinity" ማለት አብ፣ ወልድ እና መንፈስ ቅዱስ አንዱ ከሌላው ጋር ያላቸው ግንኙነት እና በዕውቀት፣ በስሜት እና በፈቃድ ያላቸው የእርሱ በእርስ መስተጋብር ነው። ለምሳሌ፦ ኢየሱስ ከተከታዮቹ ጋር የእርስ በእርስ ትውውቅ ማኅበራዊ ግኑኝነት እና መስተጋብር ነበር፦
ዮሐንስ 10፥14 መልካም እረኛ እኔ ነኝ፥ የራሴን በጎች አውቃለሁ የራሴም በጎች ያውቁኛል። ἐγώ εἰμι ὁ ποιμὴν ὁ καλός, καὶ γινώσκω τὰ ἐμὰ καὶ γινώσκουσί με τὰ ἐμά,
ኢየሱስ እና ተከታዮቹ በእርሱ የሚተዋወቁበት የየራሳቸው ዕውቀት አላቸው፥ "ግኖሲስ" γνῶσῐς ማለት "ዕውቀት" ማለት ሲሆን ልክ እንደ ኢየሱስ ከተከታዮቹ ጋር የእርስ በእርስ ትውውቅ አብ እና ወልድ እርስ በእርስ ይተዋወቃሉ፦
ዮሐንስ 10፥15 እንዲሁ አብ እንደሚያውቀኝ እኔም አብን አውቀዋለው። καθὼς γινώσκει με ὁ Πατὴρ κἀγὼ γινώσκω τὸν Πατέρα,
አብ ወልድን የሚያውቅበት የራሱ መለኮታዊ ዕውቀት እንዳለው ሁሉ ወልድም አብን የሚያውቅበት የራሱ ሰዋዊ ዕውቀት አለው፥ እርስ በእርስ ትውውቅ ሁለት የተለያዩ ማንነት እንደሆኑ ማሳያ ከሆነ "አብ የወልድ እና የመንፈስ ቅዱስ ልብ(ዕውቀት) ነው" የሚለው የኩነት"mode of existence" ትምህርት ውኃ በላው።
"ስሜት" ማለት "ፍቅር እና ጥላቻ" "ደስታ እና ሀዘን" ነው፥ "አጋፔ" ᾰγᾰπη ማለት "ፍቅር" ማለት ሲሆን አብ ወልድ ሲወድ ወልድም አብን ይወዳል፦
ዮሐንስ 3፥35 አባት ልጁን ይወዳል። ὁ Πατὴρ ἀγαπᾷ τὸν Υἱόν,
ዮሐንስ 14፥31 ነገር ግን እኔ አብን እንደምወድ ዓለም ይወቅልኝ። ἀλλ’ ἵνα γνῷ ὁ κόσμος ὅτι ἀγαπῶ τὸν Πατέρα,
አብ እና ወልድ እርስ በእርስ ከተዋደዱ የየራሳቸው ስሜት እንዳላቸው አመላካች ነው፥ አብ ወልድን የሚወድበት የራሱ መለኮታዊ ፍቅር እንዳለው ሁሉ ወልድም አብን የሚወድበት የራሱ ሰዋዊ ፍቅር አለው።
"ቴሎ" θέλω ማለት "ፈቃድ"will" ማለት ሲሆን እያንዳንዱ ማንነት ከሌላው ማንነት የሚለየው የራሱ "ፈቃድ" አለው፥ አብ የራሱ ማንነት ስላለው የራሱ መለኮታዊ ፈቃድ እንዳለው ሁሉ ወልድም የራሱ ማንነት ስላለው የራሱ ሰዋዊ ፈቃድ አለው፦
ሉቃስ 22፥42 ነገር ግን የእኔ ፈቃድ አይሁን የአንተ ፈቃድ እንጂ። πλὴν μὴ τὸ θέλημά μου ἀλλὰ τὸ σὸν γινέσθω.
እዚህ አንቀጽ ላይ "ፈቃድ" ለሚለው የገባው ቃል "ቴሌማ" θέλημά ነው፥ ኢየሱስ አብን "አንተ" ሲል ማንነትን ታሳቢ ያደረገ ስለሆነ "ፈቃድ" የሚለው "አንተ" በሚል መነሻ ቅጥያ ላይ "የ" በሚል አጋናዛቢ ዘርፍ ስለመጣ ማንነትን ዋቢ ያደረገ ነው። "ፈቃድ ምንነትን ታሳቢ ያደረገ ነው" የሚለው ፍልስፍና አርስጣጣሊሳዊ ትንተና"Aristotelian Analysis" ነው፥ የቀጰዶቅያ አበው"The Cappadocian Fathers" የሚባሉት ታላቁ ባስልዮስ ዘቂሳሪያ፣ የባስልዮስ ታናሽ ወንድሙ ጎርጎርዮስ ዘኑሲስ፣ የጎርጎርዮስ ዘኑሲስ ቅርብ ጓደኛ ጎርጎርዮስ ዘእንዚናዙ "ፈቃድ ምንነትን ታሳቢ ያደረገ ነው" የሚለው እሳቤ የቀዱት ከአርስጣጣሊስ ነው።
"አካል" የሚለው የግዕዙ ቃል "አከለ" ማለትም "በቃ" ከሚል ሥርወ ቃል የመጣ ሲሆን "ብቃት" ማለት ነው፥ አካል "የግብር እና የፈቃድ ባለቤት" ነው። ዐዋቂ እና ታዋቂ እንዲሁ አፍቃሪ እና ተፈቃሪ ትርጉም የሚኖረው በሁለት አካላት ነው፥ አብ እና ወልድ የተለያየ ማንነት ስላላቸው እርስ በእርሳቸው ያወራሉ። አብ እራሱን "እኔ" እያለ ወልድን "አንተ" እያለ ሲያናግር በተመሳሳይ ወልድም እራሱን "እኔ" እያለ አብን "አንተ" እያለ ያናግር ነበር፦
ዮሐንስ 17፥11 "እኔም" ወደ "አንተ" እመጣለሁ። κἀγὼ πρὸς σὲ ἔρχομαι.
ማርቆስ 1፥11 "እኔ" የምወድህ ልጄ "አንተ" ነህ፥ በአንተ ደስ ይለኛል። Σὺ εἶ ὁ Υἱός μου ὁ ἀγαπητός, ἐν σοὶ εὐδόκησα.
የፕሮቴስታንት የሥላሴ አማንያን"Trinitarians"፦ "ሦስት የሥላሴ አካላት የየራሳቸው ዕውቀት፣ ስሜት እና ፈቃድ አላቸው" ብለው ስለሚያምኑ የእነርሱ ሥላሴ "ማኅበራዊ ሥላሴ" ነው፥ አንዱ አምላክ በዕብራይስጥ "ኤሎሂም" אלהים ስለተባለ "ኤሎሂም ሥላሴ ነው" የሚል እምነት አላቸው። "ኤሎሃ" אלוהּ ማለት "አምላክ" ማለት ሲሆን "ኤሎሂም" אלהים ማለት "አማልክት" ማለት ነው፥ ሥላሴ የሚባሉ አማልክት በጽንፈ ዓለማት ውስጥ በነበሩ ኖሮ በተበላሹ ነበር፡፡ የዐርሹ ጌታ አሏህ ከሚሉት ሁሉ ጠራ፦
21፥22 በሁለቱ በሰማያት እና በምድር ውስጥ ከአሏህ ሌላ አማልክት በነበሩ ኖሮ በተበላሹ ነበር፡፡ የዐርሹ ጌታ አሏህ ከሚሉት ሁሉ ጠራ፡፡ لَوْ كَانَ فِيهِمَا آلِهَةٌ إِلَّا اللَّهُ لَفَسَدَتَا ۚ فَسُبْحَانَ اللَّهِ رَبِّ الْعَرْشِ عَمَّا يَصِفُونَ
"ከሚሉት" ለሚለው ቃል የገባው "የሲፉን" يَصِفُون ሲሆን "ባሕርይ ካደረጉለት"They attribute” ማለት ነው፥ ፍጡራን እራሱን ባልገለጸበት ሲፋህ መወሰፋቸው ሺርክ ነው። አሏህ ከሚያጋሩት ሁሉ የጠራ ነው፦
53፥43 አሏህ "ከሚያጋሩት" ሁሉ ጠራ፡፡ سُبْحَانَ اللَّهِ عَمَّا يُشْرِكُونَ
አምላካችን አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይወፍቀን! አሚን።
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
21፥22 በሁለቱ በሰማያት እና በምድር ውስጥ ከአሏህ ሌላ አማልክት በነበሩ ኖሮ በተበላሹ ነበር፡፡ የዐርሹ ጌታ አሏህ ከሚሉት ሁሉ ጠራ፡፡ لَوْ كَانَ فِيهِمَا آلِهَةٌ إِلَّا اللَّهُ لَفَسَدَتَا ۚ فَسُبْحَانَ اللَّهِ رَبِّ الْعَرْشِ عَمَّا يَصِفُونَ
"ማኅበር" ማለት የእርስ በእርስ ግኑኝነት ሲሆን በሥነ እውነት ጥናት"Metaphysics" እያንዳንዱ ማንነት ከሌላው ማንነት ጋር ያለው ዕውቀት፣ ስሜት እና ፈቃድ ነው፥ በነገረ ሥላሴ ጥናት ውስጥ ማኅበራዊ ሥላሴ"Social Trinity" ማለት አብ፣ ወልድ እና መንፈስ ቅዱስ አንዱ ከሌላው ጋር ያላቸው ግንኙነት እና በዕውቀት፣ በስሜት እና በፈቃድ ያላቸው የእርሱ በእርስ መስተጋብር ነው። ለምሳሌ፦ ኢየሱስ ከተከታዮቹ ጋር የእርስ በእርስ ትውውቅ ማኅበራዊ ግኑኝነት እና መስተጋብር ነበር፦
ዮሐንስ 10፥14 መልካም እረኛ እኔ ነኝ፥ የራሴን በጎች አውቃለሁ የራሴም በጎች ያውቁኛል። ἐγώ εἰμι ὁ ποιμὴν ὁ καλός, καὶ γινώσκω τὰ ἐμὰ καὶ γινώσκουσί με τὰ ἐμά,
ኢየሱስ እና ተከታዮቹ በእርሱ የሚተዋወቁበት የየራሳቸው ዕውቀት አላቸው፥ "ግኖሲስ" γνῶσῐς ማለት "ዕውቀት" ማለት ሲሆን ልክ እንደ ኢየሱስ ከተከታዮቹ ጋር የእርስ በእርስ ትውውቅ አብ እና ወልድ እርስ በእርስ ይተዋወቃሉ፦
ዮሐንስ 10፥15 እንዲሁ አብ እንደሚያውቀኝ እኔም አብን አውቀዋለው። καθὼς γινώσκει με ὁ Πατὴρ κἀγὼ γινώσκω τὸν Πατέρα,
አብ ወልድን የሚያውቅበት የራሱ መለኮታዊ ዕውቀት እንዳለው ሁሉ ወልድም አብን የሚያውቅበት የራሱ ሰዋዊ ዕውቀት አለው፥ እርስ በእርስ ትውውቅ ሁለት የተለያዩ ማንነት እንደሆኑ ማሳያ ከሆነ "አብ የወልድ እና የመንፈስ ቅዱስ ልብ(ዕውቀት) ነው" የሚለው የኩነት"mode of existence" ትምህርት ውኃ በላው።
"ስሜት" ማለት "ፍቅር እና ጥላቻ" "ደስታ እና ሀዘን" ነው፥ "አጋፔ" ᾰγᾰπη ማለት "ፍቅር" ማለት ሲሆን አብ ወልድ ሲወድ ወልድም አብን ይወዳል፦
ዮሐንስ 3፥35 አባት ልጁን ይወዳል። ὁ Πατὴρ ἀγαπᾷ τὸν Υἱόν,
ዮሐንስ 14፥31 ነገር ግን እኔ አብን እንደምወድ ዓለም ይወቅልኝ። ἀλλ’ ἵνα γνῷ ὁ κόσμος ὅτι ἀγαπῶ τὸν Πατέρα,
አብ እና ወልድ እርስ በእርስ ከተዋደዱ የየራሳቸው ስሜት እንዳላቸው አመላካች ነው፥ አብ ወልድን የሚወድበት የራሱ መለኮታዊ ፍቅር እንዳለው ሁሉ ወልድም አብን የሚወድበት የራሱ ሰዋዊ ፍቅር አለው።
"ቴሎ" θέλω ማለት "ፈቃድ"will" ማለት ሲሆን እያንዳንዱ ማንነት ከሌላው ማንነት የሚለየው የራሱ "ፈቃድ" አለው፥ አብ የራሱ ማንነት ስላለው የራሱ መለኮታዊ ፈቃድ እንዳለው ሁሉ ወልድም የራሱ ማንነት ስላለው የራሱ ሰዋዊ ፈቃድ አለው፦
ሉቃስ 22፥42 ነገር ግን የእኔ ፈቃድ አይሁን የአንተ ፈቃድ እንጂ። πλὴν μὴ τὸ θέλημά μου ἀλλὰ τὸ σὸν γινέσθω.
እዚህ አንቀጽ ላይ "ፈቃድ" ለሚለው የገባው ቃል "ቴሌማ" θέλημά ነው፥ ኢየሱስ አብን "አንተ" ሲል ማንነትን ታሳቢ ያደረገ ስለሆነ "ፈቃድ" የሚለው "አንተ" በሚል መነሻ ቅጥያ ላይ "የ" በሚል አጋናዛቢ ዘርፍ ስለመጣ ማንነትን ዋቢ ያደረገ ነው። "ፈቃድ ምንነትን ታሳቢ ያደረገ ነው" የሚለው ፍልስፍና አርስጣጣሊሳዊ ትንተና"Aristotelian Analysis" ነው፥ የቀጰዶቅያ አበው"The Cappadocian Fathers" የሚባሉት ታላቁ ባስልዮስ ዘቂሳሪያ፣ የባስልዮስ ታናሽ ወንድሙ ጎርጎርዮስ ዘኑሲስ፣ የጎርጎርዮስ ዘኑሲስ ቅርብ ጓደኛ ጎርጎርዮስ ዘእንዚናዙ "ፈቃድ ምንነትን ታሳቢ ያደረገ ነው" የሚለው እሳቤ የቀዱት ከአርስጣጣሊስ ነው።
"አካል" የሚለው የግዕዙ ቃል "አከለ" ማለትም "በቃ" ከሚል ሥርወ ቃል የመጣ ሲሆን "ብቃት" ማለት ነው፥ አካል "የግብር እና የፈቃድ ባለቤት" ነው። ዐዋቂ እና ታዋቂ እንዲሁ አፍቃሪ እና ተፈቃሪ ትርጉም የሚኖረው በሁለት አካላት ነው፥ አብ እና ወልድ የተለያየ ማንነት ስላላቸው እርስ በእርሳቸው ያወራሉ። አብ እራሱን "እኔ" እያለ ወልድን "አንተ" እያለ ሲያናግር በተመሳሳይ ወልድም እራሱን "እኔ" እያለ አብን "አንተ" እያለ ያናግር ነበር፦
ዮሐንስ 17፥11 "እኔም" ወደ "አንተ" እመጣለሁ። κἀγὼ πρὸς σὲ ἔρχομαι.
ማርቆስ 1፥11 "እኔ" የምወድህ ልጄ "አንተ" ነህ፥ በአንተ ደስ ይለኛል። Σὺ εἶ ὁ Υἱός μου ὁ ἀγαπητός, ἐν σοὶ εὐδόκησα.
የፕሮቴስታንት የሥላሴ አማንያን"Trinitarians"፦ "ሦስት የሥላሴ አካላት የየራሳቸው ዕውቀት፣ ስሜት እና ፈቃድ አላቸው" ብለው ስለሚያምኑ የእነርሱ ሥላሴ "ማኅበራዊ ሥላሴ" ነው፥ አንዱ አምላክ በዕብራይስጥ "ኤሎሂም" אלהים ስለተባለ "ኤሎሂም ሥላሴ ነው" የሚል እምነት አላቸው። "ኤሎሃ" אלוהּ ማለት "አምላክ" ማለት ሲሆን "ኤሎሂም" אלהים ማለት "አማልክት" ማለት ነው፥ ሥላሴ የሚባሉ አማልክት በጽንፈ ዓለማት ውስጥ በነበሩ ኖሮ በተበላሹ ነበር፡፡ የዐርሹ ጌታ አሏህ ከሚሉት ሁሉ ጠራ፦
21፥22 በሁለቱ በሰማያት እና በምድር ውስጥ ከአሏህ ሌላ አማልክት በነበሩ ኖሮ በተበላሹ ነበር፡፡ የዐርሹ ጌታ አሏህ ከሚሉት ሁሉ ጠራ፡፡ لَوْ كَانَ فِيهِمَا آلِهَةٌ إِلَّا اللَّهُ لَفَسَدَتَا ۚ فَسُبْحَانَ اللَّهِ رَبِّ الْعَرْشِ عَمَّا يَصِفُونَ
"ከሚሉት" ለሚለው ቃል የገባው "የሲፉን" يَصِفُون ሲሆን "ባሕርይ ካደረጉለት"They attribute” ማለት ነው፥ ፍጡራን እራሱን ባልገለጸበት ሲፋህ መወሰፋቸው ሺርክ ነው። አሏህ ከሚያጋሩት ሁሉ የጠራ ነው፦
53፥43 አሏህ "ከሚያጋሩት" ሁሉ ጠራ፡፡ سُبْحَانَ اللَّهِ عَمَّا يُشْرِكُونَ
አምላካችን አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይወፍቀን! አሚን።
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
ሒጃብ
በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።
24፥31 ለምእምናትም ንገራቸው፡- ዓይኖቻቸውን ይከልክሉ፡፡ ብልቶቻቸውንም ይጠብቁ፡፡ ጌጣቸውንም ከእርሷ ግልጽ ከኾነው በስተቀር አይግለጡ፡፡ ጉፍታዎቻቸውንም በአንገትጌዎቻቸው ላይ ያጣፉ፡፡ وَقُل لِّلْمُؤْمِنَاتِ يَغْضُضْنَ مِنْ أَبْصَارِهِنَّ وَيَحْفَظْنَ فُرُوجَهُنَّ وَلَا يُبْدِينَ زِينَتَهُنَّ إِلَّا مَا ظَهَرَ مِنْهَا ۖ وَلْيَضْرِبْنَ بِخُمُرِهِنَّ عَلَىٰ جُيُوبِهِنَّ
"ሒጃብ" حِجَاب የሚለው ቃል "ሐጀበ" حَجَبَ ማለትም "ጋረደ" "ሸፈነ" ከሚል ሥርወ ቃል የመጣ ሲሆን "መሸፈኛ" "መሸፋፈኛ" "መጋረጃ" "ግርዶ" ማለት ነው፦
19፥17 ከእነርሱም መጋረጃን አደረገች፡፡ فَاتَّخَذَتْ مِن دُونِهِمْ حِجَابًا
እዚህ አንቀጽ ላይ መርየም እንዳያዩአት ያደረገችው መጋረጃ "ሒጃብ" حِجَاب ተብሎ ተቀምጧል። ሒጃብ ሙሥሊም ሴት የምትሰተርበት ኺማር እና ጂልባብ ነው፦
24፥31 ለምእምናትም ንገራቸው፡- ዓይኖቻቸውን ይከልክሉ፡፡ ብልቶቻቸውንም ይጠብቁ፡፡ ጌጣቸውንም ከእርሷ ግልጽ ከኾነው በስተቀር አይግለጡ፡፡ ጉፍታዎቻቸውንም በአንገትጌዎቻቸው ላይ ያጣፉ፡፡ وَقُل لِّلْمُؤْمِنَاتِ يَغْضُضْنَ مِنْ أَبْصَارِهِنَّ وَيَحْفَظْنَ فُرُوجَهُنَّ وَلَا يُبْدِينَ زِينَتَهُنَّ إِلَّا مَا ظَهَرَ مِنْهَا ۖ وَلْيَضْرِبْنَ بِخُمُرِهِنَّ عَلَىٰ جُيُوبِهِنَّ
"ጉፍታዎች" ለሚለው በብዜት የገባው ቃል "ኹሙር" خُمُر ሲሆን በነጠላ ደግሞ "ኺማር" خِمَار ነው። ይህ አንቀጽ ሲወርድ ሴቶች በኒቃብ ተሰትረዋል፦
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 65, ሐዲስ 4759
ሶፊያህ ቢንት ሸይባህ እንደተረከችው፦ "ዓኢሻህ"ረ.ዐ." እንዲህ ትል ነበር፦ "ጉፍታዎቻቸውንም በአንገትጌዎቻቸው ላይ ያጣፉ" የሚለው አንቀጽ በወረደች ጊዜ ሴቶቹ ከወገቦቻቸውን ጨርቆች በኩል ይቆርጡና ጭንቅላታቸውን እና ፊታቸውን በተቆረጡት የጨርቅ ቁርጥራጮች ይሸፍኑ ነበር"። عَنْ صَفِيَّةَ بِنْتِ شَيْبَةَ، أَنَّ عَائِشَةَ ـ رضى الله عنها ـ كَانَتْ تَقُولُ لَمَّا نَزَلَتْ هَذِهِ الآيَةُ {وَلْيَضْرِبْنَ بِخُمُرِهِنَّ عَلَى جُيُوبِهِنَّ} أَخَذْنَ أُزْرَهُنَّ فَشَقَّقْنَهَا مِنْ قِبَلِ الْحَوَاشِي فَاخْتَمَرْنَ بِهَا.
"ኒቃብ" نِقَاب ማለት "መሸፈኛ" ማለት ሲሆን "ጉፍታዎች" በሌላ አንቀጽ "መከናነቢያዎች" በሚል ተለዋዋጭ ቃል መጥቷል፦
33፥59 አንተ ነቢዩ ሆይ! ለሚስቶቸህ፣ ለሴቶች ልጆችህም፣ ለምእምናን ሚስቶችም ከመከናነቢያዎቻቸው በላያቸው ላይ እንዲለቁ ንገራቸው፡፡ ይህ እንዲታወቁ እና በባለጌዎች እንዳይደፈሩ ለመኾን በጣም የቀረበ ነው፡፡ አላህም መሓሪ አዛኝ ነው፡፡ يَا أَيُّهَا النَّبِيُّ قُل لِّأَزْوَاجِكَ وَبَنَاتِكَ وَنِسَاءِ الْمُؤْمِنِينَ يُدْنِينَ عَلَيْهِنَّ مِن جَلَابِيبِهِنَّ ۚ ذَٰلِكَ أَدْنَىٰ أَن يُعْرَفْنَ فَلَا يُؤْذَيْنَ ۗ وَكَانَ اللَّهُ غَفُورًا رَّحِيمًا
እዚህ አንቀጽ ላይ "መከናነቢያዎች" ለሚለው በብዜት የገባው ቃል "ጀላቢብ" جَلَٰبِيب ሲሆን በነጠላ ደግሞ "ጂልባብ" جِلْبَاب ነው።
በባይብል ውስጥ ይስሐቅም ርብቃን ከማግባቱ በፊት አጅነቢይ ስለነበረ እንዳያያት ኺማር ወስዳ ተከናነበች፦
ዘፍጥረት 24፥65 "እርስዋም መሸፈኛ ወስዳ ተከናነበች"። فَأخَذَتْ رِفقَةُ الخِمارَ وَغَطَّتْ وَجهَها
እዚህ አንቀጽ ላይ "መሸፈኛ" ለሚለው ቃል የገባው "ኺማር" خِمارَ ሲሆን "ፊቷን" ለሚለው የገባው ቃል "ወጀሀሃ" وَجهَها ነው፥ ርብቃ በሒጃብ የተሰተረችው ፊቷን ነው። በእስራኤል ሴቶቹ ዓይናቸውን በኒቃብ ይሸፈኑ ነበር፥ ንጉሥ ሰለሞን የሱላማጢስ ልጃገረድን በዓይነ ርግብ መሸፈኛሽ ውስጥ ዓይኖች እና ጕንጭና ጕንጯ እንዳሉ መናገሩ በኒቃብ ፊታቸው እና ዓይናቸው ይሰተሩ እንደነበር አመላካች ነው፦
መኃልይ 4፥1 በዓይነ ርግብ መሸፈኛሽ ውስጥ ዓይኖችሽ እንደ ርግቦች ናቸው። عَيْنَاكِ حَمَامَتَانِ مِنْ تَحْتِ نَقَابِكِ
አንቀጹ ላይ "መሸፈኛሽ" ለሚለው ቃል የገባው "ነቃቢኪ" نَقَابِكِ ሲሆን "ኒቃብ" نِقَاب በጥንትም ፊትን መሸፈኛ ነው፥ እዚሁ ዐውድ ላይ "መሸፈኛሽ" ለሚለው ቃል የገባው "ሒማሪኪ" خِمارِكِ ነው፦
መኃልይ 4፥3 በዓይነ ርግብ መሸፈኛሽ ውስጥ ጕንጭና ጕንጭሽ እንደ ተከፈለ ሮማን ናቸው። كَفَلَقَةِ رُمّانَةٍ هُوَ خَدُّكِ تَحتَ خِمارِكِ
የሱላማጢስ ልጃገረድን ሒጃቧትን ልክ እንደ ኢትዮጵያዊያን ሴት ሙሥሊሞች ቅጥር ጠባቂዎች እንደወሰዱባት መናገሯ በራሱ ሒጃብ ታደርግ እንደነበር ማሳያ ነው፦
መኃልይ 5፥7 ቅጥር ጠባቂዎችም የዓይነ ርግብ መሸፈኛዬን ወሰዱት። وَنَزَعَ حُرّاسُ الأسوارِ خِمارِي عَنِّي
እዚህ አንቀጽ ላይ "መሸፈኛ" ለሚለው የገባው ቃል "ኺማር" خِمَار እንደሆነ ልብ አድርግ! ሴት ራስዋን በኺማር ሳትሸፍን ወደ ፈጣሪ ልትጸልይ አይገባትም፥ ሴት አማኝ ሁሉም ቦታ እንድትከናነብ ወፍራም ትእዛዝ አለ፦
1ኛ ቆሮንቶስ 11፥13 በእናንተ በራሳችሁ መካከል ፍረዱ፤ ሴት "ራስዋን ሳትሸፍን" ወደ አምላክ ልትጸልይ ይገባታልን?
ዲድስቅልያ 3፥32 ነገር ግን ላመኑ ሴቶች ራሳቸውን በንጽህና “ሊከናነቡ” ይገባል። እነርሱ “ተከናንበው” በጎዳና ራሳቸውን ዝቅ አድርገው ይሂዱ!።
በግዕዝ "ዲድስቅሊያ" በውጪው ዓለም "ዲዳኬ"Didache" ከ 60-85 ድኅረ ልደት የተዘጋጀ የሐዋርያት ትምህርት ነው፥ ይህ መጽሐፍ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ የአዲስ ኪዳን 35 ከምትላቸው የቀኖና መጻሕፍት አንዱ ነው። "እነርሱ “ተከናንበው” በጎዳና ራሳቸውን ዝቅ አድርገው ይሂዱ" የሚለው ይሰመርበት! ታዲያ ለምን ይሆን ክርስቲያን ሴት ተገላልጣ በጎዳና ላይ የምትሄደው? መልሱ መጽሐፉን ለትራስነት እንጂ አያነቡትም፥ ያነበቡትም የሚከተሉት መጽሐፉን ሳይሆን የምዕራቡን ርዕዮት እና እሳቦት ነው። መራቆትን እንደ መሰልጠን መሰተርን እንደ ኃላ ቀርነት ለሚቆጥሩት አሏህ ቀልብ ይስጣቸው! ለእኛም ጽናቱን ይወፍቀን! አሚን።
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።
24፥31 ለምእምናትም ንገራቸው፡- ዓይኖቻቸውን ይከልክሉ፡፡ ብልቶቻቸውንም ይጠብቁ፡፡ ጌጣቸውንም ከእርሷ ግልጽ ከኾነው በስተቀር አይግለጡ፡፡ ጉፍታዎቻቸውንም በአንገትጌዎቻቸው ላይ ያጣፉ፡፡ وَقُل لِّلْمُؤْمِنَاتِ يَغْضُضْنَ مِنْ أَبْصَارِهِنَّ وَيَحْفَظْنَ فُرُوجَهُنَّ وَلَا يُبْدِينَ زِينَتَهُنَّ إِلَّا مَا ظَهَرَ مِنْهَا ۖ وَلْيَضْرِبْنَ بِخُمُرِهِنَّ عَلَىٰ جُيُوبِهِنَّ
"ሒጃብ" حِجَاب የሚለው ቃል "ሐጀበ" حَجَبَ ማለትም "ጋረደ" "ሸፈነ" ከሚል ሥርወ ቃል የመጣ ሲሆን "መሸፈኛ" "መሸፋፈኛ" "መጋረጃ" "ግርዶ" ማለት ነው፦
19፥17 ከእነርሱም መጋረጃን አደረገች፡፡ فَاتَّخَذَتْ مِن دُونِهِمْ حِجَابًا
እዚህ አንቀጽ ላይ መርየም እንዳያዩአት ያደረገችው መጋረጃ "ሒጃብ" حِجَاب ተብሎ ተቀምጧል። ሒጃብ ሙሥሊም ሴት የምትሰተርበት ኺማር እና ጂልባብ ነው፦
24፥31 ለምእምናትም ንገራቸው፡- ዓይኖቻቸውን ይከልክሉ፡፡ ብልቶቻቸውንም ይጠብቁ፡፡ ጌጣቸውንም ከእርሷ ግልጽ ከኾነው በስተቀር አይግለጡ፡፡ ጉፍታዎቻቸውንም በአንገትጌዎቻቸው ላይ ያጣፉ፡፡ وَقُل لِّلْمُؤْمِنَاتِ يَغْضُضْنَ مِنْ أَبْصَارِهِنَّ وَيَحْفَظْنَ فُرُوجَهُنَّ وَلَا يُبْدِينَ زِينَتَهُنَّ إِلَّا مَا ظَهَرَ مِنْهَا ۖ وَلْيَضْرِبْنَ بِخُمُرِهِنَّ عَلَىٰ جُيُوبِهِنَّ
"ጉፍታዎች" ለሚለው በብዜት የገባው ቃል "ኹሙር" خُمُر ሲሆን በነጠላ ደግሞ "ኺማር" خِمَار ነው። ይህ አንቀጽ ሲወርድ ሴቶች በኒቃብ ተሰትረዋል፦
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 65, ሐዲስ 4759
ሶፊያህ ቢንት ሸይባህ እንደተረከችው፦ "ዓኢሻህ"ረ.ዐ." እንዲህ ትል ነበር፦ "ጉፍታዎቻቸውንም በአንገትጌዎቻቸው ላይ ያጣፉ" የሚለው አንቀጽ በወረደች ጊዜ ሴቶቹ ከወገቦቻቸውን ጨርቆች በኩል ይቆርጡና ጭንቅላታቸውን እና ፊታቸውን በተቆረጡት የጨርቅ ቁርጥራጮች ይሸፍኑ ነበር"። عَنْ صَفِيَّةَ بِنْتِ شَيْبَةَ، أَنَّ عَائِشَةَ ـ رضى الله عنها ـ كَانَتْ تَقُولُ لَمَّا نَزَلَتْ هَذِهِ الآيَةُ {وَلْيَضْرِبْنَ بِخُمُرِهِنَّ عَلَى جُيُوبِهِنَّ} أَخَذْنَ أُزْرَهُنَّ فَشَقَّقْنَهَا مِنْ قِبَلِ الْحَوَاشِي فَاخْتَمَرْنَ بِهَا.
"ኒቃብ" نِقَاب ማለት "መሸፈኛ" ማለት ሲሆን "ጉፍታዎች" በሌላ አንቀጽ "መከናነቢያዎች" በሚል ተለዋዋጭ ቃል መጥቷል፦
33፥59 አንተ ነቢዩ ሆይ! ለሚስቶቸህ፣ ለሴቶች ልጆችህም፣ ለምእምናን ሚስቶችም ከመከናነቢያዎቻቸው በላያቸው ላይ እንዲለቁ ንገራቸው፡፡ ይህ እንዲታወቁ እና በባለጌዎች እንዳይደፈሩ ለመኾን በጣም የቀረበ ነው፡፡ አላህም መሓሪ አዛኝ ነው፡፡ يَا أَيُّهَا النَّبِيُّ قُل لِّأَزْوَاجِكَ وَبَنَاتِكَ وَنِسَاءِ الْمُؤْمِنِينَ يُدْنِينَ عَلَيْهِنَّ مِن جَلَابِيبِهِنَّ ۚ ذَٰلِكَ أَدْنَىٰ أَن يُعْرَفْنَ فَلَا يُؤْذَيْنَ ۗ وَكَانَ اللَّهُ غَفُورًا رَّحِيمًا
እዚህ አንቀጽ ላይ "መከናነቢያዎች" ለሚለው በብዜት የገባው ቃል "ጀላቢብ" جَلَٰبِيب ሲሆን በነጠላ ደግሞ "ጂልባብ" جِلْبَاب ነው።
በባይብል ውስጥ ይስሐቅም ርብቃን ከማግባቱ በፊት አጅነቢይ ስለነበረ እንዳያያት ኺማር ወስዳ ተከናነበች፦
ዘፍጥረት 24፥65 "እርስዋም መሸፈኛ ወስዳ ተከናነበች"። فَأخَذَتْ رِفقَةُ الخِمارَ وَغَطَّتْ وَجهَها
እዚህ አንቀጽ ላይ "መሸፈኛ" ለሚለው ቃል የገባው "ኺማር" خِمارَ ሲሆን "ፊቷን" ለሚለው የገባው ቃል "ወጀሀሃ" وَجهَها ነው፥ ርብቃ በሒጃብ የተሰተረችው ፊቷን ነው። በእስራኤል ሴቶቹ ዓይናቸውን በኒቃብ ይሸፈኑ ነበር፥ ንጉሥ ሰለሞን የሱላማጢስ ልጃገረድን በዓይነ ርግብ መሸፈኛሽ ውስጥ ዓይኖች እና ጕንጭና ጕንጯ እንዳሉ መናገሩ በኒቃብ ፊታቸው እና ዓይናቸው ይሰተሩ እንደነበር አመላካች ነው፦
መኃልይ 4፥1 በዓይነ ርግብ መሸፈኛሽ ውስጥ ዓይኖችሽ እንደ ርግቦች ናቸው። عَيْنَاكِ حَمَامَتَانِ مِنْ تَحْتِ نَقَابِكِ
አንቀጹ ላይ "መሸፈኛሽ" ለሚለው ቃል የገባው "ነቃቢኪ" نَقَابِكِ ሲሆን "ኒቃብ" نِقَاب በጥንትም ፊትን መሸፈኛ ነው፥ እዚሁ ዐውድ ላይ "መሸፈኛሽ" ለሚለው ቃል የገባው "ሒማሪኪ" خِمارِكِ ነው፦
መኃልይ 4፥3 በዓይነ ርግብ መሸፈኛሽ ውስጥ ጕንጭና ጕንጭሽ እንደ ተከፈለ ሮማን ናቸው። كَفَلَقَةِ رُمّانَةٍ هُوَ خَدُّكِ تَحتَ خِمارِكِ
የሱላማጢስ ልጃገረድን ሒጃቧትን ልክ እንደ ኢትዮጵያዊያን ሴት ሙሥሊሞች ቅጥር ጠባቂዎች እንደወሰዱባት መናገሯ በራሱ ሒጃብ ታደርግ እንደነበር ማሳያ ነው፦
መኃልይ 5፥7 ቅጥር ጠባቂዎችም የዓይነ ርግብ መሸፈኛዬን ወሰዱት። وَنَزَعَ حُرّاسُ الأسوارِ خِمارِي عَنِّي
እዚህ አንቀጽ ላይ "መሸፈኛ" ለሚለው የገባው ቃል "ኺማር" خِمَار እንደሆነ ልብ አድርግ! ሴት ራስዋን በኺማር ሳትሸፍን ወደ ፈጣሪ ልትጸልይ አይገባትም፥ ሴት አማኝ ሁሉም ቦታ እንድትከናነብ ወፍራም ትእዛዝ አለ፦
1ኛ ቆሮንቶስ 11፥13 በእናንተ በራሳችሁ መካከል ፍረዱ፤ ሴት "ራስዋን ሳትሸፍን" ወደ አምላክ ልትጸልይ ይገባታልን?
ዲድስቅልያ 3፥32 ነገር ግን ላመኑ ሴቶች ራሳቸውን በንጽህና “ሊከናነቡ” ይገባል። እነርሱ “ተከናንበው” በጎዳና ራሳቸውን ዝቅ አድርገው ይሂዱ!።
በግዕዝ "ዲድስቅሊያ" በውጪው ዓለም "ዲዳኬ"Didache" ከ 60-85 ድኅረ ልደት የተዘጋጀ የሐዋርያት ትምህርት ነው፥ ይህ መጽሐፍ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ የአዲስ ኪዳን 35 ከምትላቸው የቀኖና መጻሕፍት አንዱ ነው። "እነርሱ “ተከናንበው” በጎዳና ራሳቸውን ዝቅ አድርገው ይሂዱ" የሚለው ይሰመርበት! ታዲያ ለምን ይሆን ክርስቲያን ሴት ተገላልጣ በጎዳና ላይ የምትሄደው? መልሱ መጽሐፉን ለትራስነት እንጂ አያነቡትም፥ ያነበቡትም የሚከተሉት መጽሐፉን ሳይሆን የምዕራቡን ርዕዮት እና እሳቦት ነው። መራቆትን እንደ መሰልጠን መሰተርን እንደ ኃላ ቀርነት ለሚቆጥሩት አሏህ ቀልብ ይስጣቸው! ለእኛም ጽናቱን ይወፍቀን! አሚን።
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
የግብር መገዛዛት
በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
23፥91 ከእርሱም ጋር አንድም አምላክ የለም፡፡ ያን ጊዜ ሌላ አምላክ በነበረ አምላክ ሁሉ በፈጠረው ነገር በተለየ ነበር፡፡ ከፊላቸውም በከፊሉ ላይ በላቀ ነበር፡፡ وَمَا كَانَ مَعَهُ مِنْ إِلَـٰهٍ ۚ إِذًا لَّذَهَبَ كُلُّ إِلَـٰهٍ بِمَا خَلَقَ وَلَعَلَا بَعْضُهُمْ عَلَىٰ بَعْضٍ
ላዕላይ ነገረ ክርስቶስ ጥናት"Higher Christology" ማለት ከአምላክነት ወደ ሰውነት የሚደረግ አፍላጦናዊ መሠረት ያረገ ጥናት ነው፥ በላዕላይ ነገረ ክርስቶስ ጥናት ውስጥ "የግብር መገዛዛት"Functional subordination" የሚባል እሳቤ አለ። "የግብር መገዛዛት" ማለት በባሕርይ ተመሳሳይ ሆነው ነገር ግን በደረጃ አንዱ ከሌላው ስለሚበልጥ በመካከላቸው ገዥ እና ተገዥ አለ፥ ለምሳሌ፦ ባል እና ሚስት በምንነት ተመሳሳይ "ሰው" የሚባል ባሕርይ"Essence" ሲኖራቸው ቅሉ ግን በደረጃ ልዩነት ወንድ ገዥ ሴት ተገዥ ናት፦
ኤፌሶን 5፥24 ዳሩ ግን ቤተ ክርስቲያን ለክርስቶስ እንደምትገዛ እንዲሁ ሚስቶች ደግሞ በሁሉ ለባሎቻቸው ይገዙ። ἀλλὰ ὡς ἡ ἐκκλησία ὑποτάσσεται τῷ Χριστῷ, οὕτως καὶ αἱ γυναῖκες τοῖς ἀνδράσιν ἐν παντί.
እዚህ አንቀጽ ላይ ለመገዛት የገባው ሥርወ ቃል "ሃይፖታሶ" ὑποτάσσω ሲሆን ኢየሱስ ለአብ የሚገዛበትን ለማሳየት የገባው ቃል በተመሳሳይ ይህ ነው፦
1ኛ ቆሮንቶስ 15፥28 ሁሉ ከተገዛለት በኋላ ግን እግዚአብሔር ሁሉ በሁሉ ይሆን ዘንድ በዚያን ጊዜ ልጁ ራሱ ደግሞ ሁሉን ላስገዛለት "ይገዛል"። ὅταν δὲ ὑποταγῇ αὐτῷ τὰ πάντα, τότε καὶ αὐτὸς ὁ Υἱὸς ὑποταγήσεται τῷ ὑποτάξαντι αὐτῷ τὰ πάντα, ἵνα ᾖ ὁ Θεὸς πάντα ἐν πᾶσιν.
እዚህ አንቀጽ ላይ ለመገዛት የገባው ሥርወ ቃል "ሃይፖታሶ" ὑποτάσσω ነው። ይህንን ታሳቢ አድርገው የቤተክርስቲያን አበው ወልድ ለአብ የሚገዛ ሁለተኛ ደረጃ ያለው ሁለተኛ አምላክ እና ሁለተኛ ጌታ እንደሆነ በስፋት ተናግረዋል። እስቲ እንመልከት፦
፨ አውሳብዮስ ዘቂሳሪያ"Eusebius of Caesarea" ኢየሱስን "ሁለተኛ ጌታ" ይለዋል፦
"ሙሴ ከአብ ቀጥሎ ሁለተኛ ጌታ መሆኑን በግልፅ ያውጃል"።
Church History (Eusebius) > Book I(1) Chapter 2 Number 9
፨ ቀለሜንጦስ ዘእስክንድርያ"Clement of Alexandria" ኢየሱስን "ወልድ ሁለተኛ ነው" በማለት ደረጃውን ተናግሯል፦
"በአብ ፈቃድ ሁሉ ነገር በእርሱ የሆነው ወልድ ሁለተኛ ነው"።
The Stromata (Clement of Alexandria) Chapter 14
፨ ጠርጡሊያኖስ ዘካርቴጅ"Tertullian of Carthage" ኢየሱስን "በህልውና መንገድ በደረጃ ሁለተኛ ነው" ብሎታል፦
"በባሕርይ ሳይሆን በህልውና መንገድ በደረጃ ሁለተኛ ነው"።
Apology (Tertullian) Chapter 21
፨ አርጌንስ ዘእስክንድርያ"Origen of Alexandria" ኢየሱስን "ሁለተኛ አምላክ" ብሎ ያስተምር ነበር፦
"ቢሆንም እኛ "ሁለተኛ አምላክ" ብለን ልንጠራው እንችላለን"።
Origen Against(Contra) Celsum, Book 5 chapter 39
፨ ዮስጦስ ሰማዕቱ"Justin Martyr" ኢየሱስ በደረጃ ሁለተኛ እንደሆነ እና ሌላ አምላክ እና ጌታ ሆኖ ለሁሉን ነገር ፈጣሪ ለሆነው ለአብ እንደሚገዛ ተናግሯል፦
"በምክንያት የራሱ የእውነተኛ አምላክ ልጅ መሆኑን ተምረን እና በሁለተኛ ደረጃ ይዘን እንሰግድለታለን"።
The First Apology (St. Justin Martyr) Chapter 13 Number 6
"ሌላ አምላክ" እና ጌታ ለሁሉን ነገር ፈጣሪ ይገዛል"።
Justin Martyr, Dialogue with Trypho, chapter 56
ይህ የግብር መገዛዛት ትልቅ ችግር አለበት፥ ምክንያቱም በሥላሴ እሳቤ "ውሳጣዊ ግብር"inward function" ማለት ወላዲ፣ ተወላዲ እና ሠራጺ የሚባለው አካላዊ ግብር እና ልባዊ፣ ቃላዊ እና እስትንፋሳዊ የሚባለው ኩነታዊ ግብር ሲሆን "ኑባሬአዊ ሥላሴ"Immanent Trinity" ነው። ወልድ ለአብ የሚገዛው በውሳጣዊ ግብር ነውን? አይ "በውጫዊ ግብር ነው" ይሉናል፥ "ውጫዊ ግብር"outward function" ማለት ደግሞ ሦስቱ አካላት በጋራ የሚያደርጉት ግብር ሲሆን "ምጣኔያዊ"Economic Trinity" ነው። "በውጫዊ ግብር ሥላሴ አንድ ናቸው" ስለሚሉ አንዱ ሌላውን ከገዛ በውጫዊ ግብር ሥላሴ አንድ አይደሉም ማለት ነው።
፨ 2ኛው ዓለም ዓቀፍ ጉባኤ በ381 ድኅረ ልደት 1ኛ የቁስጥንጥንያ ጉባኤ "አብ እና ወልድ በውጫዊ ግብር አብ ላኪ ወልድ ተላኪ በመሆን የተለያየ የሥራ ድርሻ አላቸው" የሚለውን የሎዶቂያው ኤጲስ ቆጶስ አቡሊናርዮስ አውግዟል።
፨ 5ኛው ዓለም ዓቀፍ ጉባኤ በ 553 ድኅረ ልደት 2ኛው የቁስጥንጥንያ ጉባኤ "ወልድ ለአብ የግብር መገዛዛት ይገዛል" የሚሉትን የአርጌንስን ተከታይ የሆኑትን አርጌንሳውያን አውግዟል።
"ወልድ ለአብ በድኅረ ተሰግዎት ብቻ ሳይሆን በቅድመ ተሰግዎትም ይገዛል" የሚል እምነት ያላቸው የፕሮቴስታንት እና የአድቬንቲስት ክርስቲያኖች ናቸው፥ በተቃራኒው ከቤተክርስቲያን አበው መካከል አትናቴዎስ ዘእስክንድርያ፣ አውግስጢኖስ ዘሂፓ፣ ጎርጎርዮስ ዘኑሲስ፣ ኤጲፋኒዮስ ዘሳልሚስ እንዲሁ የኦርቶዶክስ እና የካቶሊክ ክርስቲያኖች የግብር መገዛዛትን በምንም መልኩ አይቀበሉም።
ላኪ እና ተላኪ ውጫዊ ግብር ነው፥ በውጫዊ ግብር አብ እና ወልድ አንድ ከሆኑ ወልድ ሲላክ አብም ተልኳልን? ወልድ ሰው ሆኖ ከሴት ሲወለድ አብም ሰው ሆኖ ከሴት ተወልዷልን? "አይ" ከተባለ እንግዲያውስ በውጫዊ ግብር አብ እና ወልድ አንድ አይደሉም።
በዲኑል ኢሥላም አሏህ በማንነት ሆነ በምንነት አንድ ነው፥ ከእርሱ ጋር አንድም አምላክ የለም። ከእርሱ ጋር ምንነትን የሚጋራ ልጅ ቢኖር ኖሮ በሥራ ክፍልፍል በፈጠረው ነገር በተለየ እና ከፊላቸውም በከፊሉ ላይ የበላይ በሆነ ነበር፦
23፥91 አሏህ ምንም ልጅን አልወለደም፥ ከእርሱም ጋር አንድም አምላክ የለም፡፡ ያን ጊዜ ሌላ አምላክ በነበረ አምላክ ሁሉ በፈጠረው ነገር በተለየ ነበር፡፡ ከፊላቸውም በከፊሉ ላይ በላቀ ነበር፡፡ አሏህ ከሚሉት ሁሉ ጠራ፡፡ مَا اتَّخَذَ اللَّهُ مِن وَلَدٍ وَمَا كَانَ مَعَهُ مِنْ إِلَـٰهٍ ۚ إِذًا لَّذَهَبَ كُلُّ إِلَـٰهٍ بِمَا خَلَقَ وَلَعَلَا بَعْضُهُمْ عَلَىٰ بَعْضٍ ۚ سُبْحَانَ اللَّهِ عَمَّا يَصِفُونَ
"ከሚሉት" ለሚለው ቃል የገባው "የሲፉን" يَصِفُون ሲሆን "ባሕርይ ካደረጉለት"They attribute” ማለት ነው፥ "አንደኛው አምላካዊ ቀዋሚ ማንነት በሌላው አምላካዊ ቀዋሚ ማንነት ላይ የበላይ ነው" ብለው መወሰፋቸው ሺርክ ነው። አሏህ ከሚያጋሩት ሁሉ የጠራ ነው፦
53፥43 አሏህ "ከሚያጋሩት" ሁሉ ጠራ፡፡ سُبْحَانَ اللَّهِ عَمَّا يُشْرِكُونَ
አምላካችን አሏህ አባጣ እና ጎርባጣ ከሆነ የሺርክ ሕይወት አውጥቶ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይወፍቀን! አሚን።
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
23፥91 ከእርሱም ጋር አንድም አምላክ የለም፡፡ ያን ጊዜ ሌላ አምላክ በነበረ አምላክ ሁሉ በፈጠረው ነገር በተለየ ነበር፡፡ ከፊላቸውም በከፊሉ ላይ በላቀ ነበር፡፡ وَمَا كَانَ مَعَهُ مِنْ إِلَـٰهٍ ۚ إِذًا لَّذَهَبَ كُلُّ إِلَـٰهٍ بِمَا خَلَقَ وَلَعَلَا بَعْضُهُمْ عَلَىٰ بَعْضٍ
ላዕላይ ነገረ ክርስቶስ ጥናት"Higher Christology" ማለት ከአምላክነት ወደ ሰውነት የሚደረግ አፍላጦናዊ መሠረት ያረገ ጥናት ነው፥ በላዕላይ ነገረ ክርስቶስ ጥናት ውስጥ "የግብር መገዛዛት"Functional subordination" የሚባል እሳቤ አለ። "የግብር መገዛዛት" ማለት በባሕርይ ተመሳሳይ ሆነው ነገር ግን በደረጃ አንዱ ከሌላው ስለሚበልጥ በመካከላቸው ገዥ እና ተገዥ አለ፥ ለምሳሌ፦ ባል እና ሚስት በምንነት ተመሳሳይ "ሰው" የሚባል ባሕርይ"Essence" ሲኖራቸው ቅሉ ግን በደረጃ ልዩነት ወንድ ገዥ ሴት ተገዥ ናት፦
ኤፌሶን 5፥24 ዳሩ ግን ቤተ ክርስቲያን ለክርስቶስ እንደምትገዛ እንዲሁ ሚስቶች ደግሞ በሁሉ ለባሎቻቸው ይገዙ። ἀλλὰ ὡς ἡ ἐκκλησία ὑποτάσσεται τῷ Χριστῷ, οὕτως καὶ αἱ γυναῖκες τοῖς ἀνδράσιν ἐν παντί.
እዚህ አንቀጽ ላይ ለመገዛት የገባው ሥርወ ቃል "ሃይፖታሶ" ὑποτάσσω ሲሆን ኢየሱስ ለአብ የሚገዛበትን ለማሳየት የገባው ቃል በተመሳሳይ ይህ ነው፦
1ኛ ቆሮንቶስ 15፥28 ሁሉ ከተገዛለት በኋላ ግን እግዚአብሔር ሁሉ በሁሉ ይሆን ዘንድ በዚያን ጊዜ ልጁ ራሱ ደግሞ ሁሉን ላስገዛለት "ይገዛል"። ὅταν δὲ ὑποταγῇ αὐτῷ τὰ πάντα, τότε καὶ αὐτὸς ὁ Υἱὸς ὑποταγήσεται τῷ ὑποτάξαντι αὐτῷ τὰ πάντα, ἵνα ᾖ ὁ Θεὸς πάντα ἐν πᾶσιν.
እዚህ አንቀጽ ላይ ለመገዛት የገባው ሥርወ ቃል "ሃይፖታሶ" ὑποτάσσω ነው። ይህንን ታሳቢ አድርገው የቤተክርስቲያን አበው ወልድ ለአብ የሚገዛ ሁለተኛ ደረጃ ያለው ሁለተኛ አምላክ እና ሁለተኛ ጌታ እንደሆነ በስፋት ተናግረዋል። እስቲ እንመልከት፦
፨ አውሳብዮስ ዘቂሳሪያ"Eusebius of Caesarea" ኢየሱስን "ሁለተኛ ጌታ" ይለዋል፦
"ሙሴ ከአብ ቀጥሎ ሁለተኛ ጌታ መሆኑን በግልፅ ያውጃል"።
Church History (Eusebius) > Book I(1) Chapter 2 Number 9
፨ ቀለሜንጦስ ዘእስክንድርያ"Clement of Alexandria" ኢየሱስን "ወልድ ሁለተኛ ነው" በማለት ደረጃውን ተናግሯል፦
"በአብ ፈቃድ ሁሉ ነገር በእርሱ የሆነው ወልድ ሁለተኛ ነው"።
The Stromata (Clement of Alexandria) Chapter 14
፨ ጠርጡሊያኖስ ዘካርቴጅ"Tertullian of Carthage" ኢየሱስን "በህልውና መንገድ በደረጃ ሁለተኛ ነው" ብሎታል፦
"በባሕርይ ሳይሆን በህልውና መንገድ በደረጃ ሁለተኛ ነው"።
Apology (Tertullian) Chapter 21
፨ አርጌንስ ዘእስክንድርያ"Origen of Alexandria" ኢየሱስን "ሁለተኛ አምላክ" ብሎ ያስተምር ነበር፦
"ቢሆንም እኛ "ሁለተኛ አምላክ" ብለን ልንጠራው እንችላለን"።
Origen Against(Contra) Celsum, Book 5 chapter 39
፨ ዮስጦስ ሰማዕቱ"Justin Martyr" ኢየሱስ በደረጃ ሁለተኛ እንደሆነ እና ሌላ አምላክ እና ጌታ ሆኖ ለሁሉን ነገር ፈጣሪ ለሆነው ለአብ እንደሚገዛ ተናግሯል፦
"በምክንያት የራሱ የእውነተኛ አምላክ ልጅ መሆኑን ተምረን እና በሁለተኛ ደረጃ ይዘን እንሰግድለታለን"።
The First Apology (St. Justin Martyr) Chapter 13 Number 6
"ሌላ አምላክ" እና ጌታ ለሁሉን ነገር ፈጣሪ ይገዛል"።
Justin Martyr, Dialogue with Trypho, chapter 56
ይህ የግብር መገዛዛት ትልቅ ችግር አለበት፥ ምክንያቱም በሥላሴ እሳቤ "ውሳጣዊ ግብር"inward function" ማለት ወላዲ፣ ተወላዲ እና ሠራጺ የሚባለው አካላዊ ግብር እና ልባዊ፣ ቃላዊ እና እስትንፋሳዊ የሚባለው ኩነታዊ ግብር ሲሆን "ኑባሬአዊ ሥላሴ"Immanent Trinity" ነው። ወልድ ለአብ የሚገዛው በውሳጣዊ ግብር ነውን? አይ "በውጫዊ ግብር ነው" ይሉናል፥ "ውጫዊ ግብር"outward function" ማለት ደግሞ ሦስቱ አካላት በጋራ የሚያደርጉት ግብር ሲሆን "ምጣኔያዊ"Economic Trinity" ነው። "በውጫዊ ግብር ሥላሴ አንድ ናቸው" ስለሚሉ አንዱ ሌላውን ከገዛ በውጫዊ ግብር ሥላሴ አንድ አይደሉም ማለት ነው።
፨ 2ኛው ዓለም ዓቀፍ ጉባኤ በ381 ድኅረ ልደት 1ኛ የቁስጥንጥንያ ጉባኤ "አብ እና ወልድ በውጫዊ ግብር አብ ላኪ ወልድ ተላኪ በመሆን የተለያየ የሥራ ድርሻ አላቸው" የሚለውን የሎዶቂያው ኤጲስ ቆጶስ አቡሊናርዮስ አውግዟል።
፨ 5ኛው ዓለም ዓቀፍ ጉባኤ በ 553 ድኅረ ልደት 2ኛው የቁስጥንጥንያ ጉባኤ "ወልድ ለአብ የግብር መገዛዛት ይገዛል" የሚሉትን የአርጌንስን ተከታይ የሆኑትን አርጌንሳውያን አውግዟል።
"ወልድ ለአብ በድኅረ ተሰግዎት ብቻ ሳይሆን በቅድመ ተሰግዎትም ይገዛል" የሚል እምነት ያላቸው የፕሮቴስታንት እና የአድቬንቲስት ክርስቲያኖች ናቸው፥ በተቃራኒው ከቤተክርስቲያን አበው መካከል አትናቴዎስ ዘእስክንድርያ፣ አውግስጢኖስ ዘሂፓ፣ ጎርጎርዮስ ዘኑሲስ፣ ኤጲፋኒዮስ ዘሳልሚስ እንዲሁ የኦርቶዶክስ እና የካቶሊክ ክርስቲያኖች የግብር መገዛዛትን በምንም መልኩ አይቀበሉም።
ላኪ እና ተላኪ ውጫዊ ግብር ነው፥ በውጫዊ ግብር አብ እና ወልድ አንድ ከሆኑ ወልድ ሲላክ አብም ተልኳልን? ወልድ ሰው ሆኖ ከሴት ሲወለድ አብም ሰው ሆኖ ከሴት ተወልዷልን? "አይ" ከተባለ እንግዲያውስ በውጫዊ ግብር አብ እና ወልድ አንድ አይደሉም።
በዲኑል ኢሥላም አሏህ በማንነት ሆነ በምንነት አንድ ነው፥ ከእርሱ ጋር አንድም አምላክ የለም። ከእርሱ ጋር ምንነትን የሚጋራ ልጅ ቢኖር ኖሮ በሥራ ክፍልፍል በፈጠረው ነገር በተለየ እና ከፊላቸውም በከፊሉ ላይ የበላይ በሆነ ነበር፦
23፥91 አሏህ ምንም ልጅን አልወለደም፥ ከእርሱም ጋር አንድም አምላክ የለም፡፡ ያን ጊዜ ሌላ አምላክ በነበረ አምላክ ሁሉ በፈጠረው ነገር በተለየ ነበር፡፡ ከፊላቸውም በከፊሉ ላይ በላቀ ነበር፡፡ አሏህ ከሚሉት ሁሉ ጠራ፡፡ مَا اتَّخَذَ اللَّهُ مِن وَلَدٍ وَمَا كَانَ مَعَهُ مِنْ إِلَـٰهٍ ۚ إِذًا لَّذَهَبَ كُلُّ إِلَـٰهٍ بِمَا خَلَقَ وَلَعَلَا بَعْضُهُمْ عَلَىٰ بَعْضٍ ۚ سُبْحَانَ اللَّهِ عَمَّا يَصِفُونَ
"ከሚሉት" ለሚለው ቃል የገባው "የሲፉን" يَصِفُون ሲሆን "ባሕርይ ካደረጉለት"They attribute” ማለት ነው፥ "አንደኛው አምላካዊ ቀዋሚ ማንነት በሌላው አምላካዊ ቀዋሚ ማንነት ላይ የበላይ ነው" ብለው መወሰፋቸው ሺርክ ነው። አሏህ ከሚያጋሩት ሁሉ የጠራ ነው፦
53፥43 አሏህ "ከሚያጋሩት" ሁሉ ጠራ፡፡ سُبْحَانَ اللَّهِ عَمَّا يُشْرِكُونَ
አምላካችን አሏህ አባጣ እና ጎርባጣ ከሆነ የሺርክ ሕይወት አውጥቶ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይወፍቀን! አሚን።
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
የባሕርይ መገዛዛት
በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
4፥172 መሢሑ ለአሏህ ባሪያ ከመኾን ፈጽሞ አይጠየፍም፥ ቀራቢዎች የኾኑት መላእክትም አይጠየፉም፡፡ እርሱን ከመገዛት የሚጠየፍ እና የሚኮራም ሰው አሏህ ሁሉንም ወደ እርሱ በእርግጥ ይሰበስባቸዋል፡፡ لَّن يَسْتَنكِفَ الْمَسِيحُ أَن يَكُونَ عَبْدًا لِّلَّهِ وَلَا الْمَلَائِكَةُ الْمُقَرَّبُونَ ۚ وَمَن يَسْتَنكِفْ عَنْ عِبَادَتِهِ وَيَسْتَكْبِرْ فَسَيَحْشُرُهُمْ إِلَيْهِ جَمِيعًا
ታሕታይ ነገረ ክርስቶስ ጥናት"Lower Christology" ማለት ከሰውነት ወደ አምላክነት የሚደረግ አሪስጣጣሊሳዊ መሠረት ያረገ ጥናት ነው፥ በታሕታይ ነገረ ክርስቶስ ጥናት ውስጥ "የባሕርይ መገዛዛት"Ontological subordination" የሚባል እሳቤ አለ። "የባሕርይ መገዛዛት" ማለት በባሕርይ የማይመሳሰሉ ሆነው ነገር ግን በባሕርይ አንዱ ከሌላው ስለሚበልጥ በመካከላቸው ገዥ እና ተገዥ አለ። ለምሳሌ፦ ሰው እና እንስሳ በምንነት የተለያዩ "ባሕርይ"Essence" ስላላቸው ሰው ገዥ እንስሳ ተገዥ ነው፦
መዝሙር 8፥6 ሁሉን ከእግሮቹ በታች አስገዛህለት። πάντα ὑπέταξας ὑποκάτω τῶν ποδῶν αὐτοῦ,
እዚህ አንቀጽ ላይ ለመገዛት የገባው ሥርወ ቃል "ሃይፖታሶ" ὑποτάσσω ሲሆን ገዥው ሰው ተገዥው በጎችን፣ ላሞችን፣ ሁሉ ደግሞም የምድረ በዳውን እንስሶች፣ የሰማይንም ወፎች፣ የባሕርን ዓሦች፣ በባሕር መንገድ የሚሄደውንም ሁሉ ነው፦
ዘፍጥረት 1፥28 የባሕርን ዓሦችና የሰማይን ወፎች በምድር ላይ የሚንቀሳቀሱትንም ሁሉ "ግዙአቸው"።
መዝሙር 8፥8 በጎችን፣ ላሞችን፣ ሁሉ ደግሞም የምድረ በዳውን እንስሶች፣ የሰማይንም ወፎች፣ የባሕርን ዓሦች፣ በባሕር መንገድ የሚሄደውንም ሁሉ።
በተመሳሳይ ኢየሱስ ፍጡር ስለሆነ እና አብ የኢየሱስ ፈጣሪ ስለሆነ ኢየሱስ ለአብ የሚገዛበትን ለማሳየት የገባው ሥርወ ቃል "ሃይፖታሶ" ὑποτάσσω ነው፦
1ኛ ቆሮንቶስ 15፥28 ሁሉ ከተገዛለት በኋላ ግን እግዚአብሔር ሁሉ በሁሉ ይሆን ዘንድ በዚያን ጊዜ ልጁ ራሱ ደግሞ ሁሉን ላስገዛለት "ይገዛል"። ὅταν δὲ ὑποταγῇ αὐτῷ τὰ πάντα, τότε καὶ αὐτὸς ὁ Υἱὸς ὑποταγήσεται τῷ ὑποτάξαντι αὐτῷ τὰ πάντα, ἵνα ᾖ ὁ Θεὸς πάντα ἐν πᾶσιν.
አንዱን አምላክነቱ ለሰዎች የባሕርይ ሲሆን ኢየሱስ እራሱን ከሰዎች ጋር አካቶ "አምላካችን" ማለቱ በራሱ ኢየሱስ ለአንዱ አምላክ የሚገዛው የባሕርይ መገዛዛት ነው፦
ኢሳይያስ 61፥2 የተወደደችውን የያህዌን ዓመት "አምላካችን" የሚበቀልበትን ቀን እናገር ዘንድ እና የሚያለቅሱትን ሁሉ አጽናና ዘንድ ልኮኛል። לִקְרֹ֤א שְׁנַת־רָצֹון֙ לַֽיהוָ֔ה וְיֹ֥ום נָקָ֖ם לֵאלֹהֵ֑ינוּ לְנַחֵ֖ם כָּל־אֲבֵלִֽים׃
ራእይ 19፥5 ድምፅም እንዲህ ሲል ከዙፋኑ ወጣ፦ “ባሪያዎቹ ሁሉ እርሱንም የምትፈሩት ታናናሾችና ታላላቆች ሆይ! "አምላካችንን" አመስግኑ”። καὶ φωνὴ ἀπὸ τοῦ θρόνου ἐξῆλθεν λέγουσα Αἰνεῖτε τῷ Θεῷ ἡμῶν, πάντες οἱ δοῦλοι αὐτοῦ, οἱ φοβούμενοι αὐτόν, οἱ μικροὶ καὶ οἱ μεγάλοι.
"አምላካችን" የሚለው ቃል ይሰመርበት! ከዙፋኑ የወጣው "አምላካችን" የሚል ድምፅ በዙፋኑ መካከል ካለው ከኢየሱስ የወጣ ድምፅ ነው። የሥነ መለኮት ምሁር እና ተንታኝ ዮሐንስ ጊል "አምላካችን" የሚለው ኢየሱስ ስለመሆኑ ባብራሩበት የትርጓሜ መጽሐፍ እንዲህ ብለዋል፦
ራእይ 7፥17 "በዙፋኑ መካከል ያለው" በጉ እረኛቸው ይሆናልና። ὅτι τὸ Ἀρνίον τὸ ἀνὰ μέσον τοῦ θρόνου ποιμανεῖ αὐτούς
"ድምፅም እንዲህ ሲል ከዙፋኑ ወጣ" የሚለው በዙፋኑ ላይ ከተቀመጠው ከእግዚአብሔር አብ አይደለም፥ "አምላካችንን አመስግኑ" የሚለው ሐረግ በትክክለኛነት እና በአግባብነት በአብ ሊነገር አይችልም። ይልቁንም መካከለኛ ሆኖ ስለ አብ ለሕዝቡ፦ "አምላኬ እና አምላካችሁ፥ እና አባቴ እና አባታችሁ" ያለው በዙፋኑ መካከል ካለው በግ ከክርስቶስ ነው። Gill's Exposition of the Whole Bible Commentary, Revelation 19:5
ኢየሱስ ወደ አንዱ አምላክ ከሰገደ፣ ከጦመ፣ ከጸለየ እንዲሁ እርሱ ከፈራው እና ካመለከው ለአንድ አምላክ የሚገዛው መገዛት የባሕርይ መገዛዛት ነው። አንዱ አምላክ ከሁሉ ይበልጣል፥ "ሁሉ" በሚል ቃል ውስጥ ኢየሱስ ስለሚካተት ከእርሱ አብ በባሕርይ የሚበልጠው የበላይ ነው፦
ዮሐንስ 10፥29 የሰጠኝ አባቴ ከሁሉ ይበልጣል። ὁ Πατήρ μου ὃ δέδωκέν μοι πάντων μεῖζόν ἐστιν
ዮሐንስ 14፥28 "ከ"እኔ" አብ ይበልጣልና። ὁ Πατὴρ μείζων μού ἐστιν.
1ኛ ቆሮንቶስ 11፥3 የክርስቶስም ራስ አምላክ ነው። κεφαλὴ δὲ τοῦ Χριστοῦ ὁ Θεός.
"አባቴ ከሁሉ ይበልጣል" ሲል አብ ሁሉንም የሚበልጠው በባሕርይ ከሆነ ከኢየሱስም የሚበልጠው በባሕርይ ነው፥ "ከእኔ አብ ይበልጣል" ሲል በሰውነቱ ከሆነ አምላክ ሰውን የሚበልጠው በባሕርይ እንጂ በግብር አይደለም። "ክርስቶስ" ማለት "የተቀባ" ማለት ሲሆን የተቀባውን ሰው የቀባው አምላክ በባሕርይ ስለሚበልጠው "የክርስቶስም ራስ አምላክ ነው" ተብሏል።
በእርግጥ መሢሑ ለአሏህ ባሪያ ከመኾን ፈጽሞ አይጠየፍም፥ ቀራቢዎች የኾኑት መላእክትም አይጠየፉም፡፡ እርሱን ከመገዛት የሚጠየፍ እና የሚኮራም ሰው አሏህ ሁሉንም ወደ እርሱ በእርግጥ ይሰበስባቸዋል፦
፥172 መሢሑ ለአሏህ ባሪያ ከመኾን ፈጽሞ አይጠየፍም፥ ቀራቢዎች የኾኑት መላእክትም አይጠየፉም፡፡ እርሱን ከመገዛት የሚጠየፍ እና የሚኮራም ሰው አሏህ ሁሉንም ወደ እርሱ በእርግጥ ይሰበስባቸዋል፡፡ لَّن يَسْتَنكِفَ الْمَسِيحُ أَن يَكُونَ عَبْدًا لِّلَّهِ وَلَا الْمَلَائِكَةُ الْمُقَرَّبُونَ ۚ وَمَن يَسْتَنكِفْ عَنْ عِبَادَتِهِ وَيَسْتَكْبِرْ فَسَيَحْشُرُهُمْ إِلَيْهِ جَمِيعًا
ሳታመቻምቹ እና ሳታመናፍሱ አንዱን አምላክ አሏህን በብቸኝነት እንድታመልኩ ጥሪያችን ነው። አምላካችን አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይስጠን! አሚን።
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
4፥172 መሢሑ ለአሏህ ባሪያ ከመኾን ፈጽሞ አይጠየፍም፥ ቀራቢዎች የኾኑት መላእክትም አይጠየፉም፡፡ እርሱን ከመገዛት የሚጠየፍ እና የሚኮራም ሰው አሏህ ሁሉንም ወደ እርሱ በእርግጥ ይሰበስባቸዋል፡፡ لَّن يَسْتَنكِفَ الْمَسِيحُ أَن يَكُونَ عَبْدًا لِّلَّهِ وَلَا الْمَلَائِكَةُ الْمُقَرَّبُونَ ۚ وَمَن يَسْتَنكِفْ عَنْ عِبَادَتِهِ وَيَسْتَكْبِرْ فَسَيَحْشُرُهُمْ إِلَيْهِ جَمِيعًا
ታሕታይ ነገረ ክርስቶስ ጥናት"Lower Christology" ማለት ከሰውነት ወደ አምላክነት የሚደረግ አሪስጣጣሊሳዊ መሠረት ያረገ ጥናት ነው፥ በታሕታይ ነገረ ክርስቶስ ጥናት ውስጥ "የባሕርይ መገዛዛት"Ontological subordination" የሚባል እሳቤ አለ። "የባሕርይ መገዛዛት" ማለት በባሕርይ የማይመሳሰሉ ሆነው ነገር ግን በባሕርይ አንዱ ከሌላው ስለሚበልጥ በመካከላቸው ገዥ እና ተገዥ አለ። ለምሳሌ፦ ሰው እና እንስሳ በምንነት የተለያዩ "ባሕርይ"Essence" ስላላቸው ሰው ገዥ እንስሳ ተገዥ ነው፦
መዝሙር 8፥6 ሁሉን ከእግሮቹ በታች አስገዛህለት። πάντα ὑπέταξας ὑποκάτω τῶν ποδῶν αὐτοῦ,
እዚህ አንቀጽ ላይ ለመገዛት የገባው ሥርወ ቃል "ሃይፖታሶ" ὑποτάσσω ሲሆን ገዥው ሰው ተገዥው በጎችን፣ ላሞችን፣ ሁሉ ደግሞም የምድረ በዳውን እንስሶች፣ የሰማይንም ወፎች፣ የባሕርን ዓሦች፣ በባሕር መንገድ የሚሄደውንም ሁሉ ነው፦
ዘፍጥረት 1፥28 የባሕርን ዓሦችና የሰማይን ወፎች በምድር ላይ የሚንቀሳቀሱትንም ሁሉ "ግዙአቸው"።
መዝሙር 8፥8 በጎችን፣ ላሞችን፣ ሁሉ ደግሞም የምድረ በዳውን እንስሶች፣ የሰማይንም ወፎች፣ የባሕርን ዓሦች፣ በባሕር መንገድ የሚሄደውንም ሁሉ።
በተመሳሳይ ኢየሱስ ፍጡር ስለሆነ እና አብ የኢየሱስ ፈጣሪ ስለሆነ ኢየሱስ ለአብ የሚገዛበትን ለማሳየት የገባው ሥርወ ቃል "ሃይፖታሶ" ὑποτάσσω ነው፦
1ኛ ቆሮንቶስ 15፥28 ሁሉ ከተገዛለት በኋላ ግን እግዚአብሔር ሁሉ በሁሉ ይሆን ዘንድ በዚያን ጊዜ ልጁ ራሱ ደግሞ ሁሉን ላስገዛለት "ይገዛል"። ὅταν δὲ ὑποταγῇ αὐτῷ τὰ πάντα, τότε καὶ αὐτὸς ὁ Υἱὸς ὑποταγήσεται τῷ ὑποτάξαντι αὐτῷ τὰ πάντα, ἵνα ᾖ ὁ Θεὸς πάντα ἐν πᾶσιν.
አንዱን አምላክነቱ ለሰዎች የባሕርይ ሲሆን ኢየሱስ እራሱን ከሰዎች ጋር አካቶ "አምላካችን" ማለቱ በራሱ ኢየሱስ ለአንዱ አምላክ የሚገዛው የባሕርይ መገዛዛት ነው፦
ኢሳይያስ 61፥2 የተወደደችውን የያህዌን ዓመት "አምላካችን" የሚበቀልበትን ቀን እናገር ዘንድ እና የሚያለቅሱትን ሁሉ አጽናና ዘንድ ልኮኛል። לִקְרֹ֤א שְׁנַת־רָצֹון֙ לַֽיהוָ֔ה וְיֹ֥ום נָקָ֖ם לֵאלֹהֵ֑ינוּ לְנַחֵ֖ם כָּל־אֲבֵלִֽים׃
ራእይ 19፥5 ድምፅም እንዲህ ሲል ከዙፋኑ ወጣ፦ “ባሪያዎቹ ሁሉ እርሱንም የምትፈሩት ታናናሾችና ታላላቆች ሆይ! "አምላካችንን" አመስግኑ”። καὶ φωνὴ ἀπὸ τοῦ θρόνου ἐξῆλθεν λέγουσα Αἰνεῖτε τῷ Θεῷ ἡμῶν, πάντες οἱ δοῦλοι αὐτοῦ, οἱ φοβούμενοι αὐτόν, οἱ μικροὶ καὶ οἱ μεγάλοι.
"አምላካችን" የሚለው ቃል ይሰመርበት! ከዙፋኑ የወጣው "አምላካችን" የሚል ድምፅ በዙፋኑ መካከል ካለው ከኢየሱስ የወጣ ድምፅ ነው። የሥነ መለኮት ምሁር እና ተንታኝ ዮሐንስ ጊል "አምላካችን" የሚለው ኢየሱስ ስለመሆኑ ባብራሩበት የትርጓሜ መጽሐፍ እንዲህ ብለዋል፦
ራእይ 7፥17 "በዙፋኑ መካከል ያለው" በጉ እረኛቸው ይሆናልና። ὅτι τὸ Ἀρνίον τὸ ἀνὰ μέσον τοῦ θρόνου ποιμανεῖ αὐτούς
"ድምፅም እንዲህ ሲል ከዙፋኑ ወጣ" የሚለው በዙፋኑ ላይ ከተቀመጠው ከእግዚአብሔር አብ አይደለም፥ "አምላካችንን አመስግኑ" የሚለው ሐረግ በትክክለኛነት እና በአግባብነት በአብ ሊነገር አይችልም። ይልቁንም መካከለኛ ሆኖ ስለ አብ ለሕዝቡ፦ "አምላኬ እና አምላካችሁ፥ እና አባቴ እና አባታችሁ" ያለው በዙፋኑ መካከል ካለው በግ ከክርስቶስ ነው። Gill's Exposition of the Whole Bible Commentary, Revelation 19:5
ኢየሱስ ወደ አንዱ አምላክ ከሰገደ፣ ከጦመ፣ ከጸለየ እንዲሁ እርሱ ከፈራው እና ካመለከው ለአንድ አምላክ የሚገዛው መገዛት የባሕርይ መገዛዛት ነው። አንዱ አምላክ ከሁሉ ይበልጣል፥ "ሁሉ" በሚል ቃል ውስጥ ኢየሱስ ስለሚካተት ከእርሱ አብ በባሕርይ የሚበልጠው የበላይ ነው፦
ዮሐንስ 10፥29 የሰጠኝ አባቴ ከሁሉ ይበልጣል። ὁ Πατήρ μου ὃ δέδωκέν μοι πάντων μεῖζόν ἐστιν
ዮሐንስ 14፥28 "ከ"እኔ" አብ ይበልጣልና። ὁ Πατὴρ μείζων μού ἐστιν.
1ኛ ቆሮንቶስ 11፥3 የክርስቶስም ራስ አምላክ ነው። κεφαλὴ δὲ τοῦ Χριστοῦ ὁ Θεός.
"አባቴ ከሁሉ ይበልጣል" ሲል አብ ሁሉንም የሚበልጠው በባሕርይ ከሆነ ከኢየሱስም የሚበልጠው በባሕርይ ነው፥ "ከእኔ አብ ይበልጣል" ሲል በሰውነቱ ከሆነ አምላክ ሰውን የሚበልጠው በባሕርይ እንጂ በግብር አይደለም። "ክርስቶስ" ማለት "የተቀባ" ማለት ሲሆን የተቀባውን ሰው የቀባው አምላክ በባሕርይ ስለሚበልጠው "የክርስቶስም ራስ አምላክ ነው" ተብሏል።
በእርግጥ መሢሑ ለአሏህ ባሪያ ከመኾን ፈጽሞ አይጠየፍም፥ ቀራቢዎች የኾኑት መላእክትም አይጠየፉም፡፡ እርሱን ከመገዛት የሚጠየፍ እና የሚኮራም ሰው አሏህ ሁሉንም ወደ እርሱ በእርግጥ ይሰበስባቸዋል፦
፥172 መሢሑ ለአሏህ ባሪያ ከመኾን ፈጽሞ አይጠየፍም፥ ቀራቢዎች የኾኑት መላእክትም አይጠየፉም፡፡ እርሱን ከመገዛት የሚጠየፍ እና የሚኮራም ሰው አሏህ ሁሉንም ወደ እርሱ በእርግጥ ይሰበስባቸዋል፡፡ لَّن يَسْتَنكِفَ الْمَسِيحُ أَن يَكُونَ عَبْدًا لِّلَّهِ وَلَا الْمَلَائِكَةُ الْمُقَرَّبُونَ ۚ وَمَن يَسْتَنكِفْ عَنْ عِبَادَتِهِ وَيَسْتَكْبِرْ فَسَيَحْشُرُهُمْ إِلَيْهِ جَمِيعًا
ሳታመቻምቹ እና ሳታመናፍሱ አንዱን አምላክ አሏህን በብቸኝነት እንድታመልኩ ጥሪያችን ነው። አምላካችን አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይስጠን! አሚን።
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም