ማስታረቅ
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።
49፥10 ምእመናን ወንድማማቾች ናቸው፡፡ በሁለት ወንድሞቻችሁም መካከል አስታርቁ! ይታዘንላችሁም ዘንድ አላህን ፍሩ፡፡ إِنَّمَا الْمُؤْمِنُونَ إِخْوَةٌ فَأَصْلِحُوا بَيْنَ أَخَوَيْكُمْ ۚ وَاتَّقُوا اللَّهَ لَعَلَّكُمْ تُرْحَمُونَ
"ኢስላሕ" إِصْلَاح የሚለው ቃል "አስለሐ" أَصْلَحَ ማለትም "አስታረቀ" "አስማማ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "ማስታረቅ" "ማስማማት" ማለት ነው፦
4፥114 ከውይይታቸው በምጽዋት ወይም በበጎ ሥራ ወይም በሰዎች መካከል በማስታረቅ ከሚያዙ ሰዎች ውይይት በስተቀር በብዙው ውስጥ ደግ ነገር የለበትም፡፡ የአላህን ውዴታ ለመፈለግ ይህንን የሚሠራ ሰው ታላቅ ምንዳን እንሰጠዋለን፡፡ لَّا خَيْرَ فِي كَثِيرٍ مِّن نَّجْوَاهُمْ إِلَّا مَنْ أَمَرَ بِصَدَقَةٍ أَوْ مَعْرُوفٍ أَوْ إِصْلَاحٍ بَيْنَ النَّاسِ ۚ وَمَن يَفْعَلْ ذَٰلِكَ ابْتِغَاءَ مَرْضَاتِ اللَّهِ فَسَوْفَ نُؤْتِيهِ أَجْرًا عَظِيمًا
እዚህ አንቀጽ ላይ "ማስታረቅ" ለሚለው የገባው ቃል "ኢሥላሕ" إِصْلَاح ሲሆን የአሏህ ውዴታ ለመፈለግ የሚያስታርቅ ሰው ታላቅ ምንዳ አለው። የማስታረቅ ምንዳ ከሶላት፣ ከሲያም እና ከሶደቃህ በላጭ ነው፦
ሡነን አቢ ዳውድ መጽሐፍ 43, ሐዲስ 147
አቢ አድ-ደርዳህ እንደተረከው፦ "የአሏህ መልእክተኛ"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "ከሶላት፣ ከሲያም እና ከሶደቃህ ደረጃ በላጭ ነገር አልነግራችሁምን? ሶሓባዎችም፦ "እንዴታ" አሉ። እርሳቸውም፦ "በሰዎች መካካል ማስታረቅ ነው፥ በሰዎች መካከል የሚያበላሹ(የሚያጣሉ) ግን አጥፊዎች ናቸው" አሉ"። عَنْ أَبِي الدَّرْدَاءِ، قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم " أَلاَ أُخْبِرُكُمْ بِأَفْضَلَ مِنْ دَرَجَةِ الصِّيَامِ وَالصَّلاَةِ وَالصَّدَقَةِ " . قَالُوا بَلَى . قَالَ " إِصْلاَحُ ذَاتِ الْبَيْنِ وَفَسَادُ ذَاتِ الْبَيْنِ الْحَالِقَةُ " .
ቂም ይዞ ጸሎት ሳል ይዞ ስርቆት የማይሆን ነው፥ ማስታረቅ ብዙዎች የዘነጋነው ኸይር ሥራ ነው። ሙእሚን የሆኑ ሁለት ወንድሞቻችን ቢቀያየሙ ማስታረቅ ፈርድ ነው፦
49፥10 ምእመናን ወንድማማቾች ናቸው፡፡ በሁለት ወንድሞቻችሁም መካከል አስታርቁ! ይታዘንላችሁም ዘንድ አላህን ፍሩ፡፡ إِنَّمَا الْمُؤْمِنُونَ إِخْوَةٌ فَأَصْلِحُوا بَيْنَ أَخَوَيْكُمْ ۚ وَاتَّقُوا اللَّهَ لَعَلَّكُمْ تُرْحَمُونَ
እዚህ አንቀጽ ላይ "አስታርቁ" ለሚለው ትእዛዛዊ ግሥ የገባው ቃል "አስሊሑ" أَصْلِحُوا መሆኑ በራሱ ማስታረቅ ፈርድ ነው። ከወንድማማችነት በላይ ሁለት ጭፍሮች ቢጋደሉ በመካከላቸው ማስታረቅ ፈርድ ነው፦
49፥9 ከምእምናን የኾኑ ሁለት ጭፍሮች ቢጋደሉ በመካከላቸው አስታርቁ፡፡ ከሁለቱ አንደኛይቱም በሌላይቱ ላይ ወሰን ብታልፍ ያችን ወሰን የምታልፈውን ወደ አላህ ትዕዛዝ እስከምትመለስ ድረስ ተጋደሉ፡፡ وَإِن طَائِفَتَانِ مِنَ الْمُؤْمِنِينَ اقْتَتَلُوا فَأَصْلِحُوا بَيْنَهُمَا ۖ فَإِن بَغَتْ إِحْدَاهُمَا عَلَى الْأُخْرَىٰ فَقَاتِلُوا الَّتِي تَبْغِي حَتَّىٰ تَفِيءَ إِلَىٰ أَمْرِ اللَّهِ
"ወሰን አትለፉ" ወደሚለው ወደ አሏህ ትእዛዝ ከተመለሱ ስናስታርቅ ሳናዳላ በፍትሕ ማስታረቅ አለብን፦
49፥9 ብትመለስም በመካከላቸው በትክክል አስታርቁ፡፡ በነገሩ ሁሉ አስተካክሉም፡፡ አላህ አስተካካዮችን ይወዳልና፡፡ فَإِن فَاءَتْ فَأَصْلِحُوا بَيْنَهُمَا بِالْعَدْلِ وَأَقْسِطُوا ۖ إِنَّ اللَّهَ يُحِبُّ الْمُقْسِطِينَ
እዚህ አንቀጽ ላይ "ትክክል" ለሚለው የገባው ቃል "ዐድል" عَدْل ሲሆን በነገሩ ሁሉ በፍትሕ ማስተካከል ግዴታ ነው፥ አሏህ አስተካካዮችን ይወዳልና። ያስታረቀ ሰው አሏህ ዘንድ ምንዳው ያለ ግምት ነው፦
42፥40 ይቅርም ያለ እና ያስታረቀ ሰው ምንዳው በአላህ ላይ ነው፡፡ فَمَنْ عَفَا وَأَصْلَحَ فَأَجْرُهُ عَلَى اللَّهِ
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።
49፥10 ምእመናን ወንድማማቾች ናቸው፡፡ በሁለት ወንድሞቻችሁም መካከል አስታርቁ! ይታዘንላችሁም ዘንድ አላህን ፍሩ፡፡ إِنَّمَا الْمُؤْمِنُونَ إِخْوَةٌ فَأَصْلِحُوا بَيْنَ أَخَوَيْكُمْ ۚ وَاتَّقُوا اللَّهَ لَعَلَّكُمْ تُرْحَمُونَ
"ኢስላሕ" إِصْلَاح የሚለው ቃል "አስለሐ" أَصْلَحَ ማለትም "አስታረቀ" "አስማማ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "ማስታረቅ" "ማስማማት" ማለት ነው፦
4፥114 ከውይይታቸው በምጽዋት ወይም በበጎ ሥራ ወይም በሰዎች መካከል በማስታረቅ ከሚያዙ ሰዎች ውይይት በስተቀር በብዙው ውስጥ ደግ ነገር የለበትም፡፡ የአላህን ውዴታ ለመፈለግ ይህንን የሚሠራ ሰው ታላቅ ምንዳን እንሰጠዋለን፡፡ لَّا خَيْرَ فِي كَثِيرٍ مِّن نَّجْوَاهُمْ إِلَّا مَنْ أَمَرَ بِصَدَقَةٍ أَوْ مَعْرُوفٍ أَوْ إِصْلَاحٍ بَيْنَ النَّاسِ ۚ وَمَن يَفْعَلْ ذَٰلِكَ ابْتِغَاءَ مَرْضَاتِ اللَّهِ فَسَوْفَ نُؤْتِيهِ أَجْرًا عَظِيمًا
እዚህ አንቀጽ ላይ "ማስታረቅ" ለሚለው የገባው ቃል "ኢሥላሕ" إِصْلَاح ሲሆን የአሏህ ውዴታ ለመፈለግ የሚያስታርቅ ሰው ታላቅ ምንዳ አለው። የማስታረቅ ምንዳ ከሶላት፣ ከሲያም እና ከሶደቃህ በላጭ ነው፦
ሡነን አቢ ዳውድ መጽሐፍ 43, ሐዲስ 147
አቢ አድ-ደርዳህ እንደተረከው፦ "የአሏህ መልእክተኛ"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "ከሶላት፣ ከሲያም እና ከሶደቃህ ደረጃ በላጭ ነገር አልነግራችሁምን? ሶሓባዎችም፦ "እንዴታ" አሉ። እርሳቸውም፦ "በሰዎች መካካል ማስታረቅ ነው፥ በሰዎች መካከል የሚያበላሹ(የሚያጣሉ) ግን አጥፊዎች ናቸው" አሉ"። عَنْ أَبِي الدَّرْدَاءِ، قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم " أَلاَ أُخْبِرُكُمْ بِأَفْضَلَ مِنْ دَرَجَةِ الصِّيَامِ وَالصَّلاَةِ وَالصَّدَقَةِ " . قَالُوا بَلَى . قَالَ " إِصْلاَحُ ذَاتِ الْبَيْنِ وَفَسَادُ ذَاتِ الْبَيْنِ الْحَالِقَةُ " .
ቂም ይዞ ጸሎት ሳል ይዞ ስርቆት የማይሆን ነው፥ ማስታረቅ ብዙዎች የዘነጋነው ኸይር ሥራ ነው። ሙእሚን የሆኑ ሁለት ወንድሞቻችን ቢቀያየሙ ማስታረቅ ፈርድ ነው፦
49፥10 ምእመናን ወንድማማቾች ናቸው፡፡ በሁለት ወንድሞቻችሁም መካከል አስታርቁ! ይታዘንላችሁም ዘንድ አላህን ፍሩ፡፡ إِنَّمَا الْمُؤْمِنُونَ إِخْوَةٌ فَأَصْلِحُوا بَيْنَ أَخَوَيْكُمْ ۚ وَاتَّقُوا اللَّهَ لَعَلَّكُمْ تُرْحَمُونَ
እዚህ አንቀጽ ላይ "አስታርቁ" ለሚለው ትእዛዛዊ ግሥ የገባው ቃል "አስሊሑ" أَصْلِحُوا መሆኑ በራሱ ማስታረቅ ፈርድ ነው። ከወንድማማችነት በላይ ሁለት ጭፍሮች ቢጋደሉ በመካከላቸው ማስታረቅ ፈርድ ነው፦
49፥9 ከምእምናን የኾኑ ሁለት ጭፍሮች ቢጋደሉ በመካከላቸው አስታርቁ፡፡ ከሁለቱ አንደኛይቱም በሌላይቱ ላይ ወሰን ብታልፍ ያችን ወሰን የምታልፈውን ወደ አላህ ትዕዛዝ እስከምትመለስ ድረስ ተጋደሉ፡፡ وَإِن طَائِفَتَانِ مِنَ الْمُؤْمِنِينَ اقْتَتَلُوا فَأَصْلِحُوا بَيْنَهُمَا ۖ فَإِن بَغَتْ إِحْدَاهُمَا عَلَى الْأُخْرَىٰ فَقَاتِلُوا الَّتِي تَبْغِي حَتَّىٰ تَفِيءَ إِلَىٰ أَمْرِ اللَّهِ
"ወሰን አትለፉ" ወደሚለው ወደ አሏህ ትእዛዝ ከተመለሱ ስናስታርቅ ሳናዳላ በፍትሕ ማስታረቅ አለብን፦
49፥9 ብትመለስም በመካከላቸው በትክክል አስታርቁ፡፡ በነገሩ ሁሉ አስተካክሉም፡፡ አላህ አስተካካዮችን ይወዳልና፡፡ فَإِن فَاءَتْ فَأَصْلِحُوا بَيْنَهُمَا بِالْعَدْلِ وَأَقْسِطُوا ۖ إِنَّ اللَّهَ يُحِبُّ الْمُقْسِطِينَ
እዚህ አንቀጽ ላይ "ትክክል" ለሚለው የገባው ቃል "ዐድል" عَدْل ሲሆን በነገሩ ሁሉ በፍትሕ ማስተካከል ግዴታ ነው፥ አሏህ አስተካካዮችን ይወዳልና። ያስታረቀ ሰው አሏህ ዘንድ ምንዳው ያለ ግምት ነው፦
42፥40 ይቅርም ያለ እና ያስታረቀ ሰው ምንዳው በአላህ ላይ ነው፡፡ فَمَنْ عَفَا وَأَصْلَحَ فَأَجْرُهُ عَلَى اللَّهِ
ምንዳው ያለ ግምት የሆነው አስታራቂ ብቻ ሳይሆን ተበድሎ ይቅር ያለ ሰውም ጭምር ነው። ጀነት ከሰዎችም ይቅርባዮች ለኾኑት ተደግሳለች፦
3፥134 ለእነዚያ በድሎትም ኾነ በችግር ለሚለግሱት፣ ቁጭትንም ገቺዎች ከሰዎችም ይቅርታ አድራጊዎች ለኾኑት ተደግሳለች፡፡ ٱلَّذِينَ يُنفِقُونَ فِى ٱلسَّرَّآءِ وَٱلضَّرَّآءِ وَٱلْكَٰظِمِينَ ٱلْغَيْظَ وَٱلْعَافِينَ عَنِ ٱلنَّاسِ
42፥37 ለእነዚያም የኀጢኣትን ታላላቆች እና ጠያፎችን የሚርቁ በተቆጡም ጊዜ እነርሱ ይቅር የሚሉ ለኾኑት፡፡ وَٱلَّذِينَ يَجْتَنِبُونَ كَبَٰٓئِرَ ٱلْإِثْمِ وَٱلْفَوَٰحِشَ وَإِذَا مَا غَضِبُوا۟ هُمْ يَغْفِرُونَ
የተጣላ ሰውም አስታራቂ መጥቶ "ታረቁ" ሲል መታረቅ አለብን፥ መታረቅ መልካም ነው። የበደለንን ይቅርታ ሲጠይቅ ይቅር ማለት አሏህ ወንጀላችንን ይቅር ይለናል፦
4፥128 መታረቅ መልካም ነው፡፡ وَالصُّلْحُ خَيْرٌ
4፥149 ደግ ነገርን ብትገልጹ ወይም ብትደብቁት ወይም "ከበደል ይቅርታ ብታደርጉ" አላህ ይቅር ባይ ኃያል ነው፡፡ إِن تُبْدُوا۟ خَيْرًا أَوْ تُخْفُوهُ أَوْ تَعْفُوا۟ عَن سُوٓءٍۢ فَإِنَّ ٱللَّهَ كَانَ عَفُوًّۭا قَدِيرًا
2፥263 መልካም ንግግር እና ይቅርባይነት ማስከፋት ከሚከተላት ምጽዋት በላጭ ነው፡፡ አላህም ተብቃቂ ታጋሽ ነው፡፡ قَوْلٌۭ مَّعْرُوفٌۭ وَمَغْفِرَةٌ خَيْرٌۭ مِّن صَدَقَةٍۢ يَتْبَعُهَآ أَذًۭى ۗ وَٱللَّهُ غَنِىٌّ حَلِيمٌۭ
ይቅርባይነት ማስከፋት ከሚከተላት ሶደቃህ በላጭ ነው። ቂም፣ ቁርሾ እና በቀል ልብ ውስጥ ሲቀመጥ ግን የሚጎዳው በቂም ያቄምንበትን፣ በቁርሾ ያቀረሸንበት፣ በበቀል የምንበቀለውን ሰው ብቻ ሳይሆን እራሳችንንም ጭምር ነው። ቂም፣ ቁርሾ እና በቀል በልብ ውስጥ ማስቀመጥ ኪሳራ እና ጉዳት እንጂ ትርፍ እና ጥቅም የለውም፦
35፥10 እነዚያም መጥፎ ሥራዎችን የሚዶልቱ ለእነርሱ ብርቱ ቅጣት አላቸው፡፡ የእነዚያም ተንኮል እርሱ ይጠፋል፡፡ وَٱلَّذِينَ يَمْكُرُونَ ٱلسَّيِّـَٔاتِ لَهُمْ عَذَابٌۭ شَدِيدٌۭ ۖ وَمَكْرُ أُو۟لَٰٓئِكَ هُوَ يَبُورُ
ነገርን በማብረድ ከማስታረቅ ይልቅ በማንደድ ሰዎችን የሚያነካክሱ እና የሚያባሉ አጥፊዎች ናቸው። እነዚህ ወሬ የሚያዋስዱ ሰዎች ወንጀሉ ከፍተኛ ስለሆነ ጀነት አይገቡም፦
ኢማም ሙሥሊም መጽሐፍ 1 ሐዲስ 196
ሑዘይፋህ የአሏህ መልእክተኛ"ﷺ" እንዲህ ሲሉ ሰምቶ አስተላልፏል፦ "ነገር አዋሳጅ ጀነት አይገባም"። فَقَالَ حُذَيْفَةُ سَمِعْتُ رَسُولَ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم يَقُولُ " لاَ يَدْخُلُ الْجَنَّةَ نَمَّامٌ "
አምላካችን አሏህ ወሬ አዋሳጆች ከመሆን ይጠብቀን! አታራቂዎች እና ይቅርባዮች ከሚላቸው ባሮቹ ያድርገን! አሚን።
✍ከዐቃቤ ኢሥላም ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
3፥134 ለእነዚያ በድሎትም ኾነ በችግር ለሚለግሱት፣ ቁጭትንም ገቺዎች ከሰዎችም ይቅርታ አድራጊዎች ለኾኑት ተደግሳለች፡፡ ٱلَّذِينَ يُنفِقُونَ فِى ٱلسَّرَّآءِ وَٱلضَّرَّآءِ وَٱلْكَٰظِمِينَ ٱلْغَيْظَ وَٱلْعَافِينَ عَنِ ٱلنَّاسِ
42፥37 ለእነዚያም የኀጢኣትን ታላላቆች እና ጠያፎችን የሚርቁ በተቆጡም ጊዜ እነርሱ ይቅር የሚሉ ለኾኑት፡፡ وَٱلَّذِينَ يَجْتَنِبُونَ كَبَٰٓئِرَ ٱلْإِثْمِ وَٱلْفَوَٰحِشَ وَإِذَا مَا غَضِبُوا۟ هُمْ يَغْفِرُونَ
የተጣላ ሰውም አስታራቂ መጥቶ "ታረቁ" ሲል መታረቅ አለብን፥ መታረቅ መልካም ነው። የበደለንን ይቅርታ ሲጠይቅ ይቅር ማለት አሏህ ወንጀላችንን ይቅር ይለናል፦
4፥128 መታረቅ መልካም ነው፡፡ وَالصُّلْحُ خَيْرٌ
4፥149 ደግ ነገርን ብትገልጹ ወይም ብትደብቁት ወይም "ከበደል ይቅርታ ብታደርጉ" አላህ ይቅር ባይ ኃያል ነው፡፡ إِن تُبْدُوا۟ خَيْرًا أَوْ تُخْفُوهُ أَوْ تَعْفُوا۟ عَن سُوٓءٍۢ فَإِنَّ ٱللَّهَ كَانَ عَفُوًّۭا قَدِيرًا
2፥263 መልካም ንግግር እና ይቅርባይነት ማስከፋት ከሚከተላት ምጽዋት በላጭ ነው፡፡ አላህም ተብቃቂ ታጋሽ ነው፡፡ قَوْلٌۭ مَّعْرُوفٌۭ وَمَغْفِرَةٌ خَيْرٌۭ مِّن صَدَقَةٍۢ يَتْبَعُهَآ أَذًۭى ۗ وَٱللَّهُ غَنِىٌّ حَلِيمٌۭ
ይቅርባይነት ማስከፋት ከሚከተላት ሶደቃህ በላጭ ነው። ቂም፣ ቁርሾ እና በቀል ልብ ውስጥ ሲቀመጥ ግን የሚጎዳው በቂም ያቄምንበትን፣ በቁርሾ ያቀረሸንበት፣ በበቀል የምንበቀለውን ሰው ብቻ ሳይሆን እራሳችንንም ጭምር ነው። ቂም፣ ቁርሾ እና በቀል በልብ ውስጥ ማስቀመጥ ኪሳራ እና ጉዳት እንጂ ትርፍ እና ጥቅም የለውም፦
35፥10 እነዚያም መጥፎ ሥራዎችን የሚዶልቱ ለእነርሱ ብርቱ ቅጣት አላቸው፡፡ የእነዚያም ተንኮል እርሱ ይጠፋል፡፡ وَٱلَّذِينَ يَمْكُرُونَ ٱلسَّيِّـَٔاتِ لَهُمْ عَذَابٌۭ شَدِيدٌۭ ۖ وَمَكْرُ أُو۟لَٰٓئِكَ هُوَ يَبُورُ
ነገርን በማብረድ ከማስታረቅ ይልቅ በማንደድ ሰዎችን የሚያነካክሱ እና የሚያባሉ አጥፊዎች ናቸው። እነዚህ ወሬ የሚያዋስዱ ሰዎች ወንጀሉ ከፍተኛ ስለሆነ ጀነት አይገቡም፦
ኢማም ሙሥሊም መጽሐፍ 1 ሐዲስ 196
ሑዘይፋህ የአሏህ መልእክተኛ"ﷺ" እንዲህ ሲሉ ሰምቶ አስተላልፏል፦ "ነገር አዋሳጅ ጀነት አይገባም"። فَقَالَ حُذَيْفَةُ سَمِعْتُ رَسُولَ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم يَقُولُ " لاَ يَدْخُلُ الْجَنَّةَ نَمَّامٌ "
አምላካችን አሏህ ወሬ አዋሳጆች ከመሆን ይጠብቀን! አታራቂዎች እና ይቅርባዮች ከሚላቸው ባሮቹ ያድርገን! አሚን።
✍ከዐቃቤ ኢሥላም ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
አጅር ፈላጊ
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።
5፥2 በበጎ ነገር እና አላህን በመፍራትም ተረዳዱ፡፡ وَتَعَاوَنُوا عَلَى الْبِرِّ وَالتَّقْوَىٰ
አሠላሙ ዐለይኩም ያ ሙሥሊሙን ወሙሥሊማት!
እንደሚታወቀው ከቤት የሚባረሩ ሠለምቴዎችን ለስድስት ወር ያክል ጊዜያዊ መቆያ ለቤት ክራይ፣ ለቀለብ እና ለትራንስፓርት የሚሆን ወጪ ወሒድ ዕቅበተ ኢሥላም ማኅበር እና አሜሪካ መቀመጫ ያደረገው የጥሪያችን ጀመዓህ በአጋርነት ሆነው በአሳብ፣ በጉልበት እና በንዋይ እየሠሩ ይገኛል።
ያ ከመሆኑ ጋር እነዚህ ከቤት የሚባረሩት ሠለምቴዎች እራሳቸውን እንዲችሉ ለመቋቋሚያ አንዳንድ ሰዎች እነርሱን(ሠለምቴዎች) መርዳት ጀምረዋል፥ ሙሥሊም ወንድሞች እና እኅቶች ሆይ! እነዚህን ሠለምቴዎች መደበኛ ሥራ ለድርጅት ወይም ለተቋም መቅጠር እና ማስቀጠር የምትችሉ እና በቀጥታ ሠለምቴዎችን አግኝታችሁ እራሳቸውን እንዲችሉ የዘካህ ገንዘብ መስጠት የምትፈልጉ አዲስ አበባ መሬት"ground" ላይ ያሉትን ወንድሞች በቴሌ ግራም አናግሩ፦
1. ወንድም ዐብዱ ራሕማን https://tttttt.me/Abi_Abik
2. ወንድም አቡ ኑዓይም https://tttttt.me/arhmanu
3. ወንድም ልጅ ነጃ https://tttttt.me/hubi1aqsua2
በተቻለ አቅም በየግሩፑ፣ በየፔጁ፣ በቤታችሁ እና በየኮሜንት መስጫ ሥር ሼር አድርጉት!
አሏህ ኸይር ሥራችሁ በኢኽላስ ይቀበላችሁ።
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።
5፥2 በበጎ ነገር እና አላህን በመፍራትም ተረዳዱ፡፡ وَتَعَاوَنُوا عَلَى الْبِرِّ وَالتَّقْوَىٰ
አሠላሙ ዐለይኩም ያ ሙሥሊሙን ወሙሥሊማት!
እንደሚታወቀው ከቤት የሚባረሩ ሠለምቴዎችን ለስድስት ወር ያክል ጊዜያዊ መቆያ ለቤት ክራይ፣ ለቀለብ እና ለትራንስፓርት የሚሆን ወጪ ወሒድ ዕቅበተ ኢሥላም ማኅበር እና አሜሪካ መቀመጫ ያደረገው የጥሪያችን ጀመዓህ በአጋርነት ሆነው በአሳብ፣ በጉልበት እና በንዋይ እየሠሩ ይገኛል።
ያ ከመሆኑ ጋር እነዚህ ከቤት የሚባረሩት ሠለምቴዎች እራሳቸውን እንዲችሉ ለመቋቋሚያ አንዳንድ ሰዎች እነርሱን(ሠለምቴዎች) መርዳት ጀምረዋል፥ ሙሥሊም ወንድሞች እና እኅቶች ሆይ! እነዚህን ሠለምቴዎች መደበኛ ሥራ ለድርጅት ወይም ለተቋም መቅጠር እና ማስቀጠር የምትችሉ እና በቀጥታ ሠለምቴዎችን አግኝታችሁ እራሳቸውን እንዲችሉ የዘካህ ገንዘብ መስጠት የምትፈልጉ አዲስ አበባ መሬት"ground" ላይ ያሉትን ወንድሞች በቴሌ ግራም አናግሩ፦
1. ወንድም ዐብዱ ራሕማን https://tttttt.me/Abi_Abik
2. ወንድም አቡ ኑዓይም https://tttttt.me/arhmanu
3. ወንድም ልጅ ነጃ https://tttttt.me/hubi1aqsua2
በተቻለ አቅም በየግሩፑ፣ በየፔጁ፣ በቤታችሁ እና በየኮሜንት መስጫ ሥር ሼር አድርጉት!
አሏህ ኸይር ሥራችሁ በኢኽላስ ይቀበላችሁ።
ማሞት እና መሞት
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
25፥58 በዚያም በማይሞተው ሕያው አምላክ ላይ ተመካ፡፡ وَتَوَكَّلْ عَلَى الْحَيِّ الَّذِي لَا يَمُوتُ
"የሺህ ፍልጥ ማሰሪያው አንድ ልጥ" በሚል ብሒል ተነስተን ዐላዋቂ ሳሚዎች፦ "አሏህ እንሞታለን" ብሏል" ብለው የማያውቁትን ሲለቀልቁ ምናልባት ምንተ አፍታቸውን እንዲያውቁ እና ሌላው ትምህርት እንዲያገኝበት ብለን መልስ ሰተንበታል። አሏህ ሕያው የሚያደርግ እና የሚያሞት ነው፦
15፥23 እኛም ሕያው የምናደርግ እና የምናሞት እኛው ብቻ ነን፡፡ وَإِنَّا لَنَحْنُ نُحْيِي وَنُمِيتُ
50፥43 በእርግጥ እኛው ሕያው እናደርጋለን፡፡ እናሞታለንም፡፡ መመለሻም ወደ እኛ ብቻ ነው፡፡ إِنَّا نَحْنُ نُحْيِي وَنُمِيتُ وَإِلَيْنَا الْمَصِيرُ
ሁለቱም አናቅጽ ላይ "ሕያው እናደርጋለን" ለሚለው የግሥ መደብ የገባው ቃል "ኑሕዪ" نُحْيِي ሲሆን ፋዒል ነው። "ፋዒል" فَاعِل ማለት "አድራጊ"active" ማለት ነው፥ በተመሳሳይ "እናሞታለን" ለሚለው የግሥ መደብ የገባው ቃል "ኑሚቱ" نُمِيتُ ሲሆን "ፋዒል ነው።
"መፍዑል" مَفْعول ማለት "ተደራጊ"passive" ማለት ሲሆን "ሕያው የምንሆን" ለሚለው የግሥ መደብ የሚገባው "ነሕያ" نَحْيَا ነው፥ "የምንሞት" ለሚለው የግሥ መደብ ደግሞ "ነሙቱ" نَمُوتُ ነው፦
45፥24 አሉ፦ "እርሷም ሕይወት የቅርቢቱ ሕይወታችን እንጅ ሌላ አይደለችም፡፡ "እንሞታለን"፤ ሕያውም እንኾናለን"፡፡ وَقَالُوا مَا هِيَ إِلَّا حَيَاتُنَا الدُّنْيَا نَمُوتُ وَنَحْيَا
አሏህ፦ "ኑሚቱ" نُمِيتُ የሚለውን "ነሙቱ" نَمُوتُ አድርጎ በማጣመም ሙግት ማደራጀት እጅግ ሲበዛ ነውር ነው። ኑን ዶማህ "ኑ" نُ እና "ኑ ፈትሓህ "ነ" نَ ለይቶ ከማያውቅ እና ከማይረዳ ሰው የመጣ ጥያቄ ነው፥ ከመነሻው ጥያቄው ጥራዝ ነጠቅ ጥያቄ እንጂ ጥራዝ ጠለቅ ጥያቄ አይደለም። በባለቤት ቦታ ተሳቢ እያረጉ ማንበብ ኢብራሂም፦ "የሚያሞተኝ" የሚለውን "የማሞተው" እንዲሁ "ሕያው የሚያደርገኝ" የሚለውን "ሕያው የየማደርገው" ብሎ እንደመረዳት ነው፦
26፥81 ያም የሚያሞተኝ ከዚያም ሕያው የሚያደርገኝ ነው፡፡ وَالَّذِي يُمِيتُنِي ثُمَّ يُحْيِينِ
"ዩሕዪ" يُحْيِي እና "ዩሚቱ" يُمِيتُ በሦስተኛ መደብ ባለቤት አድራጊ ነው፥ በመጀመሪያ መደብ ባለቤት አድራጊ ደግሞ "ኑሕዪ" نُحْيِي እና "ኑሚቱ" نُمِيتُ ነው፦
36፥12 በእርግጥ እኛ ሙታንን ሕያው እናደርጋለን፡፡ إِنَّا نَحْنُ نُحْيِي الْمَوْتَىٰ
"ሙታንን" ሕያው የሚያደርግ እና "ሕያዋንን" የሚያሞት አሏህ ነው፥ እርሱ አሟች ሲሆን ፍጡራን ሟች ናቸው፦
30፥40 አላህ ያ የፈጠራችሁ፣ ከዚያም ሲሳይን የሰጣችሁ፣ ከዚያም የሚያሞታችሁ ከዚያም ሕያው የሚያደርጋችሁ ነው፡፡ اللَّهُ الَّذِي خَلَقَكُمْ ثُمَّ رَزَقَكُمْ ثُمَّ يُمِيتُكُمْ ثُمَّ يُحْيِيكُمْ
45፥26 «አላህ ሕያው ያደርጋችኋል፤ ከዚያም ያሞታችኋል፣ ከዚያም ወደ ትንሣኤ ቀን ይሰበስባችኋል፡፡ በእርሱ ጥርጥር የለበትም፡፡ ግን አብዛኛዎቹ ሰዎች አያውቁም» በላቸው፡፡ قُلِ اللَّهُ يُحْيِيكُمْ ثُمَّ يُمِيتُكُمْ ثُمَّ يَجْمَعُكُمْ إِلَىٰ يَوْمِ الْقِيَامَةِ لَا رَيْبَ فِيهِ وَلَـٰكِنَّ أَكْثَرَ النَّاسِ لَا يَعْلَمُونَ
"ኩም" كُمْ የሚለው ተሳቢ ፍጡራንን የሚያመለክት ሲሆን እነርሱ የሚሞቱ እና ሕያው የሚሆኑ ናቸው፥ አሏህ ግን የሚያሞትም እና ሕያው የሚያደርግ ባለቤት እንደሆነ ከላይ ያቀረብነው የሙግት አሰላለፍ እና አሰነዛዘር ከበቂ በላይ ጉልኅ ማሳያ ነው። አሏህ በሕያውነቱ ሞት የሌለበት አምላክ ነው፦
25፥58 በዚያም በማይሞተው ሕያው አምላክ ላይ ተመካ፡፡ وَتَوَكَّلْ عَلَى الْحَيِّ الَّذِي لَا يَمُوتُ
አፈሙዝ ከመያዝ ይልቅ አፍን ከፍቶ፦ "ያዙኝ ልቀቁኝ፥ ደግፉኝ ጣሉኝ" ለሚል በአንድ መጣጥፍ ማስተንፈስ እንዲህ ይቻላል፥ ሕሊናችሁን በመቅጠፍ እያቆሸሻችሁ መኖር ግን እንዴት አስቻላችሁ? የማይለውን እንደሚል አድርጎ ሙግት ማዋቀር እኮ ቁልመማዊ ሕፀፅ"strawman fallacy" ነው። አምላካችን አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይስጠን! አሚን።
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
25፥58 በዚያም በማይሞተው ሕያው አምላክ ላይ ተመካ፡፡ وَتَوَكَّلْ عَلَى الْحَيِّ الَّذِي لَا يَمُوتُ
"የሺህ ፍልጥ ማሰሪያው አንድ ልጥ" በሚል ብሒል ተነስተን ዐላዋቂ ሳሚዎች፦ "አሏህ እንሞታለን" ብሏል" ብለው የማያውቁትን ሲለቀልቁ ምናልባት ምንተ አፍታቸውን እንዲያውቁ እና ሌላው ትምህርት እንዲያገኝበት ብለን መልስ ሰተንበታል። አሏህ ሕያው የሚያደርግ እና የሚያሞት ነው፦
15፥23 እኛም ሕያው የምናደርግ እና የምናሞት እኛው ብቻ ነን፡፡ وَإِنَّا لَنَحْنُ نُحْيِي وَنُمِيتُ
50፥43 በእርግጥ እኛው ሕያው እናደርጋለን፡፡ እናሞታለንም፡፡ መመለሻም ወደ እኛ ብቻ ነው፡፡ إِنَّا نَحْنُ نُحْيِي وَنُمِيتُ وَإِلَيْنَا الْمَصِيرُ
ሁለቱም አናቅጽ ላይ "ሕያው እናደርጋለን" ለሚለው የግሥ መደብ የገባው ቃል "ኑሕዪ" نُحْيِي ሲሆን ፋዒል ነው። "ፋዒል" فَاعِل ማለት "አድራጊ"active" ማለት ነው፥ በተመሳሳይ "እናሞታለን" ለሚለው የግሥ መደብ የገባው ቃል "ኑሚቱ" نُمِيتُ ሲሆን "ፋዒል ነው።
"መፍዑል" مَفْعول ማለት "ተደራጊ"passive" ማለት ሲሆን "ሕያው የምንሆን" ለሚለው የግሥ መደብ የሚገባው "ነሕያ" نَحْيَا ነው፥ "የምንሞት" ለሚለው የግሥ መደብ ደግሞ "ነሙቱ" نَمُوتُ ነው፦
45፥24 አሉ፦ "እርሷም ሕይወት የቅርቢቱ ሕይወታችን እንጅ ሌላ አይደለችም፡፡ "እንሞታለን"፤ ሕያውም እንኾናለን"፡፡ وَقَالُوا مَا هِيَ إِلَّا حَيَاتُنَا الدُّنْيَا نَمُوتُ وَنَحْيَا
አሏህ፦ "ኑሚቱ" نُمِيتُ የሚለውን "ነሙቱ" نَمُوتُ አድርጎ በማጣመም ሙግት ማደራጀት እጅግ ሲበዛ ነውር ነው። ኑን ዶማህ "ኑ" نُ እና "ኑ ፈትሓህ "ነ" نَ ለይቶ ከማያውቅ እና ከማይረዳ ሰው የመጣ ጥያቄ ነው፥ ከመነሻው ጥያቄው ጥራዝ ነጠቅ ጥያቄ እንጂ ጥራዝ ጠለቅ ጥያቄ አይደለም። በባለቤት ቦታ ተሳቢ እያረጉ ማንበብ ኢብራሂም፦ "የሚያሞተኝ" የሚለውን "የማሞተው" እንዲሁ "ሕያው የሚያደርገኝ" የሚለውን "ሕያው የየማደርገው" ብሎ እንደመረዳት ነው፦
26፥81 ያም የሚያሞተኝ ከዚያም ሕያው የሚያደርገኝ ነው፡፡ وَالَّذِي يُمِيتُنِي ثُمَّ يُحْيِينِ
"ዩሕዪ" يُحْيِي እና "ዩሚቱ" يُمِيتُ በሦስተኛ መደብ ባለቤት አድራጊ ነው፥ በመጀመሪያ መደብ ባለቤት አድራጊ ደግሞ "ኑሕዪ" نُحْيِي እና "ኑሚቱ" نُمِيتُ ነው፦
36፥12 በእርግጥ እኛ ሙታንን ሕያው እናደርጋለን፡፡ إِنَّا نَحْنُ نُحْيِي الْمَوْتَىٰ
"ሙታንን" ሕያው የሚያደርግ እና "ሕያዋንን" የሚያሞት አሏህ ነው፥ እርሱ አሟች ሲሆን ፍጡራን ሟች ናቸው፦
30፥40 አላህ ያ የፈጠራችሁ፣ ከዚያም ሲሳይን የሰጣችሁ፣ ከዚያም የሚያሞታችሁ ከዚያም ሕያው የሚያደርጋችሁ ነው፡፡ اللَّهُ الَّذِي خَلَقَكُمْ ثُمَّ رَزَقَكُمْ ثُمَّ يُمِيتُكُمْ ثُمَّ يُحْيِيكُمْ
45፥26 «አላህ ሕያው ያደርጋችኋል፤ ከዚያም ያሞታችኋል፣ ከዚያም ወደ ትንሣኤ ቀን ይሰበስባችኋል፡፡ በእርሱ ጥርጥር የለበትም፡፡ ግን አብዛኛዎቹ ሰዎች አያውቁም» በላቸው፡፡ قُلِ اللَّهُ يُحْيِيكُمْ ثُمَّ يُمِيتُكُمْ ثُمَّ يَجْمَعُكُمْ إِلَىٰ يَوْمِ الْقِيَامَةِ لَا رَيْبَ فِيهِ وَلَـٰكِنَّ أَكْثَرَ النَّاسِ لَا يَعْلَمُونَ
"ኩም" كُمْ የሚለው ተሳቢ ፍጡራንን የሚያመለክት ሲሆን እነርሱ የሚሞቱ እና ሕያው የሚሆኑ ናቸው፥ አሏህ ግን የሚያሞትም እና ሕያው የሚያደርግ ባለቤት እንደሆነ ከላይ ያቀረብነው የሙግት አሰላለፍ እና አሰነዛዘር ከበቂ በላይ ጉልኅ ማሳያ ነው። አሏህ በሕያውነቱ ሞት የሌለበት አምላክ ነው፦
25፥58 በዚያም በማይሞተው ሕያው አምላክ ላይ ተመካ፡፡ وَتَوَكَّلْ عَلَى الْحَيِّ الَّذِي لَا يَمُوتُ
አፈሙዝ ከመያዝ ይልቅ አፍን ከፍቶ፦ "ያዙኝ ልቀቁኝ፥ ደግፉኝ ጣሉኝ" ለሚል በአንድ መጣጥፍ ማስተንፈስ እንዲህ ይቻላል፥ ሕሊናችሁን በመቅጠፍ እያቆሸሻችሁ መኖር ግን እንዴት አስቻላችሁ? የማይለውን እንደሚል አድርጎ ሙግት ማዋቀር እኮ ቁልመማዊ ሕፀፅ"strawman fallacy" ነው። አምላካችን አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይስጠን! አሚን።
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
አሏህ አንድ ነው!
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።
112፥1 በል «እርሱ አላህ አንድ ነው»። قُلْ هُوَ اللَّهُ أَحَدٌ
"አሏህ አንድ ነው" ስንል ሚሽነሪዎች፦ "በምንድን ነው አንድ? በማንነት ወይስ በምንነት? ብለው ይጠይቃሉ፥ ምክንያቱም በእነርሱ እምነት "አምላክ በማንነት ሥስት በምንነት አንድ ነው" ተብሎ ስለሚታመን "አሏህ አንድ ምንነት እንጂ ስንት ማንነት እንዳለው አይታወቅም" የሚል ባቦሰጥ ንግግር ይናገራሉ።
"ማንነት" ማለት "ማን ነው" ብለን የምንጠይቅበት የምንነት መገለጫ"identity" ሲሆን "ምንነት" ማለት ደግሞ "ምንድን ነው" ብለን የምንጠይቅበት የማንነት መሠረት"being" ነው። እኔ በምንነቴ ሰው ነኝ፥ የፈጠረኝ አሏህ ግን በምንነቱ አምላክ ነው። እርሱም ምንነቱን የማያጋራ አንድ አምላክ ነው፦
2፥163 አምላካችሁም አንድ አምላክ ብቻ ነው፥ ከእርሱ በቀር ሌላ አምላክ የለም፡፡ እርሱ እጅግ በጣም ርኅሩህ አዛኝ ነው፡፡ وَإِلَـٰهُكُمْ إِلَـٰهٌ وَاحِدٌ ۖ لَّا إِلَـٰهَ إِلَّا هُوَ الرَّحْمَـٰنُ الرَّحِيمُ
እዚህ አንቀጽ ላይ "አንድ" ለሚለው የገባው ቃል "ዋሒድ" وَاحِد ሲሆን አምላካች አሏህ አንድ አምላክ እንደሆነ አስረግጦ ያሳያል። እኔ በማንነቴ አንድ ስሆን እራሴን የምገልጽበት "እከሌ" ለምሳሌ፦ "ወሒድ" እባላለው፥ ሁሉን የፈጠረ አንድ አምላክ በማንነቱ አንድ ሲሆን "አሏህ" ይባላል፦
20፥14 እኔ አላህ እኔ ነኝ፥ ከእኔ በቀር አምላክ የለምና አምልከኝ፡፡ ሶላትንም እኔን ለማውሳት ስገድ፡፡ إِنَّنِي أَنَا اللَّهُ لَا إِلَـٰهَ إِلَّا أَنَا فَاعْبُدْنِي وَأَقِمِ الصَّلَاةَ لِذِكْرِي
"አና" أَنَا ማለት "እኔ" ማለት ሲሆን "አና" أَنَا የሚለው ደሚሩ አሽ-ሸኽስ ማንነትን ያሳያል፥ "እኔ" አንድ ነጠላ ማንነትን"one singular person" ታሳቢ እና ዋቢ ያደረገ ነው። ስለዚህ "እኔ" የሚለውን መደብ ተውላጠ ስም"personal pronoun" አሏህ አንድ ማንነት እንደሆነ ቁልጭ አርጎ ያሳያል፥ ይህ አንድ ማንነት ምንነቱ አምላክ ስለሆነ "ከእኔ በቀር አምላክ የለም" በማለት ይናገራል። "አምልኩን" እያሉ የሚናገር አንድ "እኔነት" ነው፦
21፥92 "እኔም" ጌታችሁ ነኝና "አምልኩኝ"፡፡ وَأَنَا رَبُّكُمْ فَاعْبُدُونِ
"ሸኽስ" شَخْص ማለት "ማንነት"person" ማለት ሲሆን በነሕው ሕግ "ሸኽሱል ሙፍረድ" الشَخْص المُفْرَد ማለትም "ነጠላ ማንነት"singular person" ለመጠቀም በሙተከለም "አና" أَنَا ነው፥ ስለዚህ አሏህ "አና" ስላለ በማንነት አንድ ነው። "ሁወ" هُوَ በጋኢብ ለአንድ ነጠላ ማንነት የሚውል ደሚሩ አሽ ሸኽስ ከሆነ አሏህ ስለ ራሱ "ቁል" قُلْ በሚል ትእዛዛዊ ግሥ "ሁወ" هُوَ ብሏል፦
112፥1 በል «እርሱ አላህ አንድ ነው»። قُلْ هُوَ اللَّهُ أَحَدٌ
እዚህ አንቀጽ ላይ "አንድ" ለሚለው የገባው ቃል "አሐድ" أَحَدٌ ሲሆን ምንም መፈናፈኛ እንዳይኖር አርጎ ከርችሞታል፥ ምክንያቱም "አሐድ" አንድ ማንነትን ለማሳየት ብዙ ቦታ መጥቷል፦
72፥22 «እኔ ከአላህ ቅጣት አንድም አያድነኝም፡፡ ከእርሱም ሌላ መጠጊያን አላገኝም» በላቸው፡፡ قُلْ إِنِّي لَن يُجِيرَنِي مِنَ اللَّهِ أَحَدٌ وَلَنْ أَجِدَ مِن دُونِهِ مُلْتَحَدًا
72፥20 «እኔ የማመልከው ጌታዬን ብቻ ነው፡፡ በእርሱም አንድንም አላጋራም» በል፡፡ قُلْ إِنَّمَا أَدْعُو رَبِّي وَلَا أُشْرِكُ بِهِ أَحَدًا
"ከአላህ ቅጣት አንድም አያድነኝም" ሲል ከአሏህ ጋር የሚያድን አንድ ማንነት እንደሌለ የሚያሳይ ሲሆን "በእርሱም አንድንም አላጋራም" ሲል ከአሏህ ጋር አምልኮትን የሚጋራ አንድ ማንነት እንደሌለ ያሳያል። አሏህን በማንነት የሚመስል ማንም ማንነት የለም፦
112፥4 ለእርሱም አንድም ብጤ የለውም፡፡ وَلَمْ يَكُن لَّهُ كُفُوًا أَحَدٌ
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።
112፥1 በል «እርሱ አላህ አንድ ነው»። قُلْ هُوَ اللَّهُ أَحَدٌ
"አሏህ አንድ ነው" ስንል ሚሽነሪዎች፦ "በምንድን ነው አንድ? በማንነት ወይስ በምንነት? ብለው ይጠይቃሉ፥ ምክንያቱም በእነርሱ እምነት "አምላክ በማንነት ሥስት በምንነት አንድ ነው" ተብሎ ስለሚታመን "አሏህ አንድ ምንነት እንጂ ስንት ማንነት እንዳለው አይታወቅም" የሚል ባቦሰጥ ንግግር ይናገራሉ።
"ማንነት" ማለት "ማን ነው" ብለን የምንጠይቅበት የምንነት መገለጫ"identity" ሲሆን "ምንነት" ማለት ደግሞ "ምንድን ነው" ብለን የምንጠይቅበት የማንነት መሠረት"being" ነው። እኔ በምንነቴ ሰው ነኝ፥ የፈጠረኝ አሏህ ግን በምንነቱ አምላክ ነው። እርሱም ምንነቱን የማያጋራ አንድ አምላክ ነው፦
2፥163 አምላካችሁም አንድ አምላክ ብቻ ነው፥ ከእርሱ በቀር ሌላ አምላክ የለም፡፡ እርሱ እጅግ በጣም ርኅሩህ አዛኝ ነው፡፡ وَإِلَـٰهُكُمْ إِلَـٰهٌ وَاحِدٌ ۖ لَّا إِلَـٰهَ إِلَّا هُوَ الرَّحْمَـٰنُ الرَّحِيمُ
እዚህ አንቀጽ ላይ "አንድ" ለሚለው የገባው ቃል "ዋሒድ" وَاحِد ሲሆን አምላካች አሏህ አንድ አምላክ እንደሆነ አስረግጦ ያሳያል። እኔ በማንነቴ አንድ ስሆን እራሴን የምገልጽበት "እከሌ" ለምሳሌ፦ "ወሒድ" እባላለው፥ ሁሉን የፈጠረ አንድ አምላክ በማንነቱ አንድ ሲሆን "አሏህ" ይባላል፦
20፥14 እኔ አላህ እኔ ነኝ፥ ከእኔ በቀር አምላክ የለምና አምልከኝ፡፡ ሶላትንም እኔን ለማውሳት ስገድ፡፡ إِنَّنِي أَنَا اللَّهُ لَا إِلَـٰهَ إِلَّا أَنَا فَاعْبُدْنِي وَأَقِمِ الصَّلَاةَ لِذِكْرِي
"አና" أَنَا ማለት "እኔ" ማለት ሲሆን "አና" أَنَا የሚለው ደሚሩ አሽ-ሸኽስ ማንነትን ያሳያል፥ "እኔ" አንድ ነጠላ ማንነትን"one singular person" ታሳቢ እና ዋቢ ያደረገ ነው። ስለዚህ "እኔ" የሚለውን መደብ ተውላጠ ስም"personal pronoun" አሏህ አንድ ማንነት እንደሆነ ቁልጭ አርጎ ያሳያል፥ ይህ አንድ ማንነት ምንነቱ አምላክ ስለሆነ "ከእኔ በቀር አምላክ የለም" በማለት ይናገራል። "አምልኩን" እያሉ የሚናገር አንድ "እኔነት" ነው፦
21፥92 "እኔም" ጌታችሁ ነኝና "አምልኩኝ"፡፡ وَأَنَا رَبُّكُمْ فَاعْبُدُونِ
"ሸኽስ" شَخْص ማለት "ማንነት"person" ማለት ሲሆን በነሕው ሕግ "ሸኽሱል ሙፍረድ" الشَخْص المُفْرَد ማለትም "ነጠላ ማንነት"singular person" ለመጠቀም በሙተከለም "አና" أَنَا ነው፥ ስለዚህ አሏህ "አና" ስላለ በማንነት አንድ ነው። "ሁወ" هُوَ በጋኢብ ለአንድ ነጠላ ማንነት የሚውል ደሚሩ አሽ ሸኽስ ከሆነ አሏህ ስለ ራሱ "ቁል" قُلْ በሚል ትእዛዛዊ ግሥ "ሁወ" هُوَ ብሏል፦
112፥1 በል «እርሱ አላህ አንድ ነው»። قُلْ هُوَ اللَّهُ أَحَدٌ
እዚህ አንቀጽ ላይ "አንድ" ለሚለው የገባው ቃል "አሐድ" أَحَدٌ ሲሆን ምንም መፈናፈኛ እንዳይኖር አርጎ ከርችሞታል፥ ምክንያቱም "አሐድ" አንድ ማንነትን ለማሳየት ብዙ ቦታ መጥቷል፦
72፥22 «እኔ ከአላህ ቅጣት አንድም አያድነኝም፡፡ ከእርሱም ሌላ መጠጊያን አላገኝም» በላቸው፡፡ قُلْ إِنِّي لَن يُجِيرَنِي مِنَ اللَّهِ أَحَدٌ وَلَنْ أَجِدَ مِن دُونِهِ مُلْتَحَدًا
72፥20 «እኔ የማመልከው ጌታዬን ብቻ ነው፡፡ በእርሱም አንድንም አላጋራም» በል፡፡ قُلْ إِنَّمَا أَدْعُو رَبِّي وَلَا أُشْرِكُ بِهِ أَحَدًا
"ከአላህ ቅጣት አንድም አያድነኝም" ሲል ከአሏህ ጋር የሚያድን አንድ ማንነት እንደሌለ የሚያሳይ ሲሆን "በእርሱም አንድንም አላጋራም" ሲል ከአሏህ ጋር አምልኮትን የሚጋራ አንድ ማንነት እንደሌለ ያሳያል። አሏህን በማንነት የሚመስል ማንም ማንነት የለም፦
112፥4 ለእርሱም አንድም ብጤ የለውም፡፡ وَلَمْ يَكُن لَّهُ كُفُوًا أَحَدٌ
"ብጤ" ለሚለው የገባው ቃል "ኩፉው" كُفُو ሲሆን "አቻ" "እኩያ" "ወደር" ማለት ነው፥ ለአሏህ አንድም "አቻ" "እኩያ" "ወደር" የለውም። "አንድም" ለሚለው ለሚለው የገባው ቃል "አሐድ" أَحَدٌ ሲሆን "ሸኽስ" شَخْص በሚል የመጣ ነው፦
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 67, ሐዲስ 153
ዐብደሏህ እንደተረከው፦ "ነቢዩም"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ " "ከአላህ የበለጠ የሚቀና "አንድም" የለም"። عَنْ عَبْدِ اللَّهِ، عَنِ النَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم قَالَ " مَا مِنْ أَحَدٍ أَغْيَرُ مِنَ اللَّهِ،
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 97, ሐዲስ 44
ዐብዱል ማሊክ እንደተናገረው፦ "ከአላህ የበለጠ የሚቀና "ማንነት" የለም። عَنْ عَبْدِ الْمَلِكِ " لاَ شَخْصَ أَغْيَرُ مِنَ اللَّهِ ".
"አንድ" ለሚለው የገባው ቃል "አሐድ" أَحَدٌ ሲሆን "ማንነት" ለሚለው የገባው ቃል "ሸኽስ" شَخْص ነው፥ ስለዚህ አሏህ በማንነቱ አንድ ነው። ባል በሚስቱ እንዲሁ ንጉሥ በመንግሥቱ እንደሚቀና የፈጠረን አንድ አምላክ በአምልኮቱ ይቀናል፦
ዘጸአት 20፥6 እኔ ያህዌህ አምላክህ ቀናተኛ አምላክ ነኝና።
ገለቴ ከመንጨርጨር እና ከመንተክተክ ይልቅ መቅናት አውታዊ እንደሆነ ከራስህ መጽሐፍ ተረዳ! ስለዚህ አሏህ በአምልኮቱ መቅናቱ ላይ እርር እና ምርር አትበል። አሏህ፦ "ቁል" قُلْ በሚል ትእዛዛዊ ግሥ በአምልኮው አንድንም ማንነት እንዳናጋራ በአጽንዖት እና በአንክሮት ነግሮናል፦
18፥110 "በጌታውም አምልኮ አንድንም አያጋራ"። وَلَا يُشْرِكْ بِعِبَادَةِ رَبِّهِ أَحَدًا
"አንድንም" ሲል በአሏህ አምልኮ "አንድንም ማንነት" ማጋራት እንደሌለብን ያሳያል፥ አምልኮ የአሏህ ሐቅ እና ገንዘብ ብቻ ነው።
ተወዳጁ ነቢያች"ﷺ" አንድ ማንነት ስለነበሩ በቁርኣን "አሐድ" በሐዲስ "ሸኽስ" شَخْص ተብለዋል፦
54፥24 «ከእኛ የኾነን "አንድን" ሰው እንከተለዋለን? እኛ ያን ጊዜ በስህተትና በዕብደት ውስጥ ነን» አሉ፡፡ فَقَالُوا أَبَشَرًا مِّنَّا وَاحِدًا نَّتَّبِعُهُ إِنَّا إِذًا لَّفِي ضَلَالٍ وَسُعُرٍ
ጃምዒ አት-ቲርሚዚይ መጽሐፍ 43, ሐዲስ 24
አነሥ እንደተረከው፦ "በእነርሱ ዘንድ ከአሏህ መልእክተኛ"ﷺ" የበለጠ ተወዳጅ "ማንነት" አልነበረም"። عَنْ أَنَسٍ، قَالَ لَمْ يَكُنْ شَخْصٌ أَحَبَّ إِلَيْهِمْ مِنْ رَسُولِ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم
መቼም ነቢያች"ﷺ" አንድ ማንነት ብቻ ነበሩ እንጂ ሥላሴ አልነበሩም። ሌላው ተሰምሮ ሊጤንበት የሚገባው ነጥብ "አለዚ" اَلَّذِي ኢሥሙል መውሱል ሲሆን ሙፍረድ ለሆነ ማንነት የምንጠቀምበት ነው፥ ከአንድ በላይ ለሆኑ ማንነቶች የምንጠቀምበት በሙሰና "አለዘይኒ" اَللَّذَيْنِ በጀምዕ "አለዚነ" اَلَّذِينَ ነው። አሏህ አንድ ማንነት ስለሆነ "አለዚ" اَلَّذِي ብቻ ተብሏል፦
7፥54 ጌታችሁ "ያ" ሰማያትን እና ምድርን በስድስት ቀኖች ውስጥ የፈጠረ አላህ ነው፡፡ إِنَّ رَبَّكُمُ اللَّهُ الَّذِي خَلَقَ السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضَ فِي سِتَّةِ أَيَّامٍ
"ያ" ለሚለው አንጻራዊ ተውላጠ ስም የገባው "አለዚ" اَلَّذِي እንደሆነ አስምርበት! ይህንን የሰዋስው ሙግት አፍጦና አፋጦ፤ አግጦና አንጋጦ ስታነቡ ቆሌ ተገፎ እና ቆሽት አሮ፦ "ሰማይ ተንዶ ሊናጫነኝ ነው፥ ምድር ተከፍቶ ሊውጠኝ ነው" ከምትሉ አውንታዊ መረዳት ይዛችሁ ልባችሁን ብትከፍቱ መልካም ነው። አምላካችን አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይስጠን! አሚን።
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 67, ሐዲስ 153
ዐብደሏህ እንደተረከው፦ "ነቢዩም"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ " "ከአላህ የበለጠ የሚቀና "አንድም" የለም"። عَنْ عَبْدِ اللَّهِ، عَنِ النَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم قَالَ " مَا مِنْ أَحَدٍ أَغْيَرُ مِنَ اللَّهِ،
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 97, ሐዲስ 44
ዐብዱል ማሊክ እንደተናገረው፦ "ከአላህ የበለጠ የሚቀና "ማንነት" የለም። عَنْ عَبْدِ الْمَلِكِ " لاَ شَخْصَ أَغْيَرُ مِنَ اللَّهِ ".
"አንድ" ለሚለው የገባው ቃል "አሐድ" أَحَدٌ ሲሆን "ማንነት" ለሚለው የገባው ቃል "ሸኽስ" شَخْص ነው፥ ስለዚህ አሏህ በማንነቱ አንድ ነው። ባል በሚስቱ እንዲሁ ንጉሥ በመንግሥቱ እንደሚቀና የፈጠረን አንድ አምላክ በአምልኮቱ ይቀናል፦
ዘጸአት 20፥6 እኔ ያህዌህ አምላክህ ቀናተኛ አምላክ ነኝና።
ገለቴ ከመንጨርጨር እና ከመንተክተክ ይልቅ መቅናት አውታዊ እንደሆነ ከራስህ መጽሐፍ ተረዳ! ስለዚህ አሏህ በአምልኮቱ መቅናቱ ላይ እርር እና ምርር አትበል። አሏህ፦ "ቁል" قُلْ በሚል ትእዛዛዊ ግሥ በአምልኮው አንድንም ማንነት እንዳናጋራ በአጽንዖት እና በአንክሮት ነግሮናል፦
18፥110 "በጌታውም አምልኮ አንድንም አያጋራ"። وَلَا يُشْرِكْ بِعِبَادَةِ رَبِّهِ أَحَدًا
"አንድንም" ሲል በአሏህ አምልኮ "አንድንም ማንነት" ማጋራት እንደሌለብን ያሳያል፥ አምልኮ የአሏህ ሐቅ እና ገንዘብ ብቻ ነው።
ተወዳጁ ነቢያች"ﷺ" አንድ ማንነት ስለነበሩ በቁርኣን "አሐድ" በሐዲስ "ሸኽስ" شَخْص ተብለዋል፦
54፥24 «ከእኛ የኾነን "አንድን" ሰው እንከተለዋለን? እኛ ያን ጊዜ በስህተትና በዕብደት ውስጥ ነን» አሉ፡፡ فَقَالُوا أَبَشَرًا مِّنَّا وَاحِدًا نَّتَّبِعُهُ إِنَّا إِذًا لَّفِي ضَلَالٍ وَسُعُرٍ
ጃምዒ አት-ቲርሚዚይ መጽሐፍ 43, ሐዲስ 24
አነሥ እንደተረከው፦ "በእነርሱ ዘንድ ከአሏህ መልእክተኛ"ﷺ" የበለጠ ተወዳጅ "ማንነት" አልነበረም"። عَنْ أَنَسٍ، قَالَ لَمْ يَكُنْ شَخْصٌ أَحَبَّ إِلَيْهِمْ مِنْ رَسُولِ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم
መቼም ነቢያች"ﷺ" አንድ ማንነት ብቻ ነበሩ እንጂ ሥላሴ አልነበሩም። ሌላው ተሰምሮ ሊጤንበት የሚገባው ነጥብ "አለዚ" اَلَّذِي ኢሥሙል መውሱል ሲሆን ሙፍረድ ለሆነ ማንነት የምንጠቀምበት ነው፥ ከአንድ በላይ ለሆኑ ማንነቶች የምንጠቀምበት በሙሰና "አለዘይኒ" اَللَّذَيْنِ በጀምዕ "አለዚነ" اَلَّذِينَ ነው። አሏህ አንድ ማንነት ስለሆነ "አለዚ" اَلَّذِي ብቻ ተብሏል፦
7፥54 ጌታችሁ "ያ" ሰማያትን እና ምድርን በስድስት ቀኖች ውስጥ የፈጠረ አላህ ነው፡፡ إِنَّ رَبَّكُمُ اللَّهُ الَّذِي خَلَقَ السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضَ فِي سِتَّةِ أَيَّامٍ
"ያ" ለሚለው አንጻራዊ ተውላጠ ስም የገባው "አለዚ" اَلَّذِي እንደሆነ አስምርበት! ይህንን የሰዋስው ሙግት አፍጦና አፋጦ፤ አግጦና አንጋጦ ስታነቡ ቆሌ ተገፎ እና ቆሽት አሮ፦ "ሰማይ ተንዶ ሊናጫነኝ ነው፥ ምድር ተከፍቶ ሊውጠኝ ነው" ከምትሉ አውንታዊ መረዳት ይዛችሁ ልባችሁን ብትከፍቱ መልካም ነው። አምላካችን አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይስጠን! አሚን።
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
ኢፍጣር
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ፥ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
33፥35 "ጦመኛ ወንዶች እና ጦመኛ ሴቶችም፣ ብልቶቻቸውን ጠባቂዎች ወንዶች እና ጠባቂ ሴቶችም፣ አላህን በብዙ አውሺዎች ወንዶች እና አውሺዎች ሴቶችም አላህ ለእነርሱ ምሕረትን እና ታላቅን ምንዳ አዘጋጅቶላቸዋል"፡፡ وَالصَّائِمِينَ وَالصَّائِمَاتِ وَالْحَافِظِينَ فُرُوجَهُمْ وَالْحَافِظَاتِ وَالذَّاكِرِينَ اللَّهَ كَثِيرًا وَالذَّاكِرَاتِ أَعَدَّ اللَّهُ لَهُم مَّغْفِرَةً وَأَجْرًا عَظِيمًا
“ፊጥር” فِطْر የሚለው ቃል "ፈጦረ" فَطَرَ ማለትም "ገደፈ" ከሚል ሥርወ ቃል የመጣ ሲሆን “ጦም መግደፊያ" ማለት ነው፥ የፊጥር ብዙ ቁጥር ደግሞ “ፉጡር” فُطُور ነው። ለምሳሌ፦ የረመዷን ጦም ማብቂያ በዓል እራሱ "ዒዱል ፊጥር" عِيدُ ٱلْفِطْر ይባላል፥ "ዘካቱል ፊጥር" زَكَاة الفِطْر ደግሞ ለመሣኪን በዒዱል ፊጥር ቀን ለማስፈጠሪያነት የሚውል ገንዘብ ነው። በተመሳሳይ “ኢፍጣር” إِفْطَار የሚለው ቃል "አፍጦረ" أَفْطَرَ ማለትም "አፈጠረ" ከሚል ሥርወ ቃል የመጣ ሲሆን “ጦም መግደፍ" ማለት ነው፥ ጦመኛን ያስፈጠረ ጦመኛው ከሚያገኘውን ምንዳ ምንም ሳይቀነስ ጦመኛው ሊያገኘው የሚችለውን ምንዳ ያገኛል፦
ሡነን ኢብኑ ማጃህ መጽሐፍ 7, ሐዲስ 109
ዘይድ ኢብኑ ኻሊድ አል ጁሀኒይ እንደተረከው፦ የአሏህ መልእክተኛ"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "ጦመኛን ያስፈጠረ ጦመኛው ከሚያገኘውን ምንዳ ምንም ሳይቀነስ ጦመኛው ሊያገኘው የሚችለውን ምንዳ ያገኛል"። عَنْ زَيْدِ بْنِ خَالِدٍ الْجُهَنِيِّ، قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ ـ صلى الله عليه وسلم ـ " مَنْ فَطَّرَ صَائِمًا كَانَ لَهُ مِثْلُ أَجْرِهِمْ مِنْ غَيْرِ أَنْ يَنْقُصَ مِنْ أُجُورِهِمْ شَيْئًا " .
አደባባይ ላይ እዩልኝ እና ስሙልኝ በማለት ከመበሻሸቅ፣ ከመነታረክ፣ እልህ ከመገባባት፣ ከመፎካከር ይልቅ ከወለጋ ተፈናቅለው ደብረ ብርሃን በካምፕ ውስጥ ያሉትን የወሎ ሙሥሊሞችን ማስፈጠር አንርሳ! እነዚህ ተፈናቃዮች ዱንያህ ላይ ተስፋ ቆርጠው አኺራቸውን በመጠባበቅ ላይ በሞት እና በሕይወት መካከል ያሉ የሊላሂ ወንድሞቻችን እና እኅቶቻችን ናቸው። እውነት ለአሏህ ከተባለ እነዚህን ስደተኞች ባለን አቅም መጎብኘቱ እውነተኛ አጅር አለው። አሏህ ይቀበላችሁ!
አምላካችን አሏህ ጦመኛ ወንድ ባሪያውን "ሷኢም" صَّائِم ሲለው ጦመኛ ሴት ባሪያውን ደግሞ "ሷኢማህ" صَّائِمَة ይላታል፥ ለእነርሱ ምሕረትን እና ታላቅን ምንዳ አዘጋጅቶላቸዋል፦
33፥35 "ጦመኛ ወንዶች እና ጦመኛ ሴቶችም፣ ብልቶቻቸውን ጠባቂዎች ወንዶች እና ጠባቂ ሴቶችም፣ አላህን በብዙ አውሺዎች ወንዶች እና አውሺዎች ሴቶችም አላህ ለእነርሱ ምሕረትን እና ታላቅን ምንዳ አዘጋጅቶላቸዋል"፡፡ وَالصَّائِمِينَ وَالصَّائِمَاتِ وَالْحَافِظِينَ فُرُوجَهُمْ وَالْحَافِظَاتِ وَالذَّاكِرِينَ اللَّهَ كَثِيرًا وَالذَّاكِرَاتِ أَعَدَّ اللَّهُ لَهُم مَّغْفِرَةً وَأَجْرًا عَظِيمًا
አሏህ "ሷኢሚን" صَّآئِمِين እና "ሷኢማት" صَّآئِمَٰت ከሚላቸው ባሮቹ ያድርገን! አሚን።
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ፥ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
33፥35 "ጦመኛ ወንዶች እና ጦመኛ ሴቶችም፣ ብልቶቻቸውን ጠባቂዎች ወንዶች እና ጠባቂ ሴቶችም፣ አላህን በብዙ አውሺዎች ወንዶች እና አውሺዎች ሴቶችም አላህ ለእነርሱ ምሕረትን እና ታላቅን ምንዳ አዘጋጅቶላቸዋል"፡፡ وَالصَّائِمِينَ وَالصَّائِمَاتِ وَالْحَافِظِينَ فُرُوجَهُمْ وَالْحَافِظَاتِ وَالذَّاكِرِينَ اللَّهَ كَثِيرًا وَالذَّاكِرَاتِ أَعَدَّ اللَّهُ لَهُم مَّغْفِرَةً وَأَجْرًا عَظِيمًا
“ፊጥር” فِطْر የሚለው ቃል "ፈጦረ" فَطَرَ ማለትም "ገደፈ" ከሚል ሥርወ ቃል የመጣ ሲሆን “ጦም መግደፊያ" ማለት ነው፥ የፊጥር ብዙ ቁጥር ደግሞ “ፉጡር” فُطُور ነው። ለምሳሌ፦ የረመዷን ጦም ማብቂያ በዓል እራሱ "ዒዱል ፊጥር" عِيدُ ٱلْفِطْر ይባላል፥ "ዘካቱል ፊጥር" زَكَاة الفِطْر ደግሞ ለመሣኪን በዒዱል ፊጥር ቀን ለማስፈጠሪያነት የሚውል ገንዘብ ነው። በተመሳሳይ “ኢፍጣር” إِفْطَار የሚለው ቃል "አፍጦረ" أَفْطَرَ ማለትም "አፈጠረ" ከሚል ሥርወ ቃል የመጣ ሲሆን “ጦም መግደፍ" ማለት ነው፥ ጦመኛን ያስፈጠረ ጦመኛው ከሚያገኘውን ምንዳ ምንም ሳይቀነስ ጦመኛው ሊያገኘው የሚችለውን ምንዳ ያገኛል፦
ሡነን ኢብኑ ማጃህ መጽሐፍ 7, ሐዲስ 109
ዘይድ ኢብኑ ኻሊድ አል ጁሀኒይ እንደተረከው፦ የአሏህ መልእክተኛ"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "ጦመኛን ያስፈጠረ ጦመኛው ከሚያገኘውን ምንዳ ምንም ሳይቀነስ ጦመኛው ሊያገኘው የሚችለውን ምንዳ ያገኛል"። عَنْ زَيْدِ بْنِ خَالِدٍ الْجُهَنِيِّ، قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ ـ صلى الله عليه وسلم ـ " مَنْ فَطَّرَ صَائِمًا كَانَ لَهُ مِثْلُ أَجْرِهِمْ مِنْ غَيْرِ أَنْ يَنْقُصَ مِنْ أُجُورِهِمْ شَيْئًا " .
አደባባይ ላይ እዩልኝ እና ስሙልኝ በማለት ከመበሻሸቅ፣ ከመነታረክ፣ እልህ ከመገባባት፣ ከመፎካከር ይልቅ ከወለጋ ተፈናቅለው ደብረ ብርሃን በካምፕ ውስጥ ያሉትን የወሎ ሙሥሊሞችን ማስፈጠር አንርሳ! እነዚህ ተፈናቃዮች ዱንያህ ላይ ተስፋ ቆርጠው አኺራቸውን በመጠባበቅ ላይ በሞት እና በሕይወት መካከል ያሉ የሊላሂ ወንድሞቻችን እና እኅቶቻችን ናቸው። እውነት ለአሏህ ከተባለ እነዚህን ስደተኞች ባለን አቅም መጎብኘቱ እውነተኛ አጅር አለው። አሏህ ይቀበላችሁ!
አምላካችን አሏህ ጦመኛ ወንድ ባሪያውን "ሷኢም" صَّائِم ሲለው ጦመኛ ሴት ባሪያውን ደግሞ "ሷኢማህ" صَّائِمَة ይላታል፥ ለእነርሱ ምሕረትን እና ታላቅን ምንዳ አዘጋጅቶላቸዋል፦
33፥35 "ጦመኛ ወንዶች እና ጦመኛ ሴቶችም፣ ብልቶቻቸውን ጠባቂዎች ወንዶች እና ጠባቂ ሴቶችም፣ አላህን በብዙ አውሺዎች ወንዶች እና አውሺዎች ሴቶችም አላህ ለእነርሱ ምሕረትን እና ታላቅን ምንዳ አዘጋጅቶላቸዋል"፡፡ وَالصَّائِمِينَ وَالصَّائِمَاتِ وَالْحَافِظِينَ فُرُوجَهُمْ وَالْحَافِظَاتِ وَالذَّاكِرِينَ اللَّهَ كَثِيرًا وَالذَّاكِرَاتِ أَعَدَّ اللَّهُ لَهُم مَّغْفِرَةً وَأَجْرًا عَظِيمًا
አሏህ "ሷኢሚን" صَّآئِمِين እና "ሷኢማት" صَّآئِمَٰت ከሚላቸው ባሮቹ ያድርገን! አሚን።
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
የዘካህ አወጣጥ
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ፥ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።
2፥110 ሶላትንም አስተካክላችሁ ስገዱ፡፡ ዘካንም ስጡ፡፡ وَأَقِيمُوا الصَّلَاةَ وَآتُوا الزَّكَاةَ
የዘካ ገንዘብ ከተቀማጭ ላይ ከመቶ 2.5 % የሚሰጥ ነው፥ ነቢያችን”ﷺ” ከሁለት መቶ ዲርሀም 5 ዘካህ እንደሚወጣ ተናግረዋል። ያ ማለት የዘካህ ሒሳብ በመቶ ዲርሀም 2.5 ይሆናል፥ ስሌቱ 5፥2=2.5 ነው፦
ሡነን አቢ ዳውድ መጽሐፍ 9, ሐዲስ 18 ዐሊይ”ረ.ዐ” እንደተረከው፦ “ነቢዩም”ﷺ” እንዲህ አሉ፦ ”ሁለት መቶ ዲርሀም ለአንተ በሆነች ጊዜና ዓመት ከሞላች አምስት ደራሂም ይወጣል፥ በአንተ ምንም ነገር አይሆንም ሃያ ዲናር እስኪሆን ድረስ”። عَنْ عَلِيٍّ، – رضى الله عنه – عَنِ النَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم بِبَعْضِ أَوَّلِ هَذَا الْحَدِيثِ قَالَ ” فَإِذَا كَانَتْ لَكَ مِائَتَا دِرْهَمٍ وَحَالَ عَلَيْهَا الْحَوْلُ فَفِيهَا خَمْسَةُ دَرَاهِمَ وَلَيْسَ عَلَيْكَ شَىْءٌ – يَعْنِي فِي الذَّهَبِ – حَتَّى يَكُونَ لَكَ عِشْرُونَ دِينَارًا
በዚህ ሐዲስ መሠረት የአንድ ሰው ካፒታል 20 ዲናር ወይም 200 ዲርሀም ሲሆን ዘካህ ይወጅበታል። በሸሪዓህ የዘካህ አነስተኛ የክፍያ መጠን “ኒሷብ” نِصاب ይባላል፥ ይህም ኒሷብ የሚለካው 20 ዲናር ወይም 200 ዲርሀም ሲሆን ነው። “ዲናር” دِينَار ማለት “የወርቅ ሳንቲም”gold coin” ማለት ሲሆን “ዲርሀም” دِرْهَم ማለት ደግሞ “የብር ሳንቲም”silver coin” ማለት ነው። ይህ በጥንት ጊዜ የሸቀጥ ገንዘብ”commodity money” ነው። “ዲናር” እና “ዲርሀም” የሚለኩት በሚስቃል ነው፥ “ሚስቃል” مِثْقَال የሚለው ቃል “ሰቀለ” ثَقَلَ ማለትም “ከበደ” ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን “ክብደት” ማለት ነው።
1 ሚስቃል ወርቅ 4.25 ግራም ነው፥ 20 ሚስቃል ወርቅ ደግሞ 4,25x 20 = 85 ግራም ወርቅ ይሆናል ማለት ነው።
1 ሚስቃል ብር 2.975 ግራም ነው፥ 200 ሚስቃል ብር ደግሞ 2.975x 200= 595 ግራም ብር ይሆናል ማለት ነው።
በዘካህ ላይ የሚወጅበው ኒሷብ 85 ግራም ወርቅ ወይም 595 ግራም ብር ነው።
አንድ ሙሥሊም ያስቀመጠው ካፒታል ዓመት ከሞላው እና ያም ካፒታል 85 ግራም ወርቅ ወይም 595 ግራም ብር ያክል ከሆነ ዘካህ ማውጣት ግዴታው ነው።
ዘካቱል ማል የሚወጣበት አነስተኛ ዋጋ የብር ኒሷብ ስለሆነ አብላጫው ምሁራን የብር ኒሷብን መሠረት ባደረገ መልኩ ከዚያ እንዲወጣ ፈትዋ ሰተዋል፥ ስለዚህ አንድ ሰው ዓመት የተቀመጠ 89,250 ብር(ገንዘብ) እና ከዛ በላይ ካለው ዘካህ ማውጣት ግዴታ አለበት።
እንዴት? ካላችሁ የብር ኒሷብ ወደ ወረቀት ገንዘብ”Fiat money” ለመቀየር ብርን ዛሬ ባለው የወቅቱ ግብይት ለናሙና ያክል መሥራት ይቻላል። በኢትዮጵያ አንድ ግራም ብር"silver" አሁን ባለኝ መረጃ 150 ብር"ገንዘብ" ነው፥ ስናሰላው 150×595= 89,250 ብር(ገንዘብ) ይሆናል።
ለምሳሌ፦ እኔ 100 ሺህ ብር ቢኖረኝ ከ 100 ሺህ ብር ላይ 2.5 % ዘካህ ሲሰላ 2,500 ይወጅብብኛል፥ ስናሰላው 100,000×2.5፥100= 2,500 ይሆናል።
ዘካህን መስጠት አንርሳ፦
2፥110 ሶላትንም አስተካክላችሁ ስገዱ፡፡ ዘካንም ስጡ፡፡ وَأَقِيمُوا الصَّلَاةَ وَآتُوا الزَّكَاةَ
አምላካችን አሏህ ዘካን ከሚሰጡ ባሮቹ ያድርገን! አሚን።
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ፥ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።
2፥110 ሶላትንም አስተካክላችሁ ስገዱ፡፡ ዘካንም ስጡ፡፡ وَأَقِيمُوا الصَّلَاةَ وَآتُوا الزَّكَاةَ
የዘካ ገንዘብ ከተቀማጭ ላይ ከመቶ 2.5 % የሚሰጥ ነው፥ ነቢያችን”ﷺ” ከሁለት መቶ ዲርሀም 5 ዘካህ እንደሚወጣ ተናግረዋል። ያ ማለት የዘካህ ሒሳብ በመቶ ዲርሀም 2.5 ይሆናል፥ ስሌቱ 5፥2=2.5 ነው፦
ሡነን አቢ ዳውድ መጽሐፍ 9, ሐዲስ 18 ዐሊይ”ረ.ዐ” እንደተረከው፦ “ነቢዩም”ﷺ” እንዲህ አሉ፦ ”ሁለት መቶ ዲርሀም ለአንተ በሆነች ጊዜና ዓመት ከሞላች አምስት ደራሂም ይወጣል፥ በአንተ ምንም ነገር አይሆንም ሃያ ዲናር እስኪሆን ድረስ”። عَنْ عَلِيٍّ، – رضى الله عنه – عَنِ النَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم بِبَعْضِ أَوَّلِ هَذَا الْحَدِيثِ قَالَ ” فَإِذَا كَانَتْ لَكَ مِائَتَا دِرْهَمٍ وَحَالَ عَلَيْهَا الْحَوْلُ فَفِيهَا خَمْسَةُ دَرَاهِمَ وَلَيْسَ عَلَيْكَ شَىْءٌ – يَعْنِي فِي الذَّهَبِ – حَتَّى يَكُونَ لَكَ عِشْرُونَ دِينَارًا
በዚህ ሐዲስ መሠረት የአንድ ሰው ካፒታል 20 ዲናር ወይም 200 ዲርሀም ሲሆን ዘካህ ይወጅበታል። በሸሪዓህ የዘካህ አነስተኛ የክፍያ መጠን “ኒሷብ” نِصاب ይባላል፥ ይህም ኒሷብ የሚለካው 20 ዲናር ወይም 200 ዲርሀም ሲሆን ነው። “ዲናር” دِينَار ማለት “የወርቅ ሳንቲም”gold coin” ማለት ሲሆን “ዲርሀም” دِرْهَم ማለት ደግሞ “የብር ሳንቲም”silver coin” ማለት ነው። ይህ በጥንት ጊዜ የሸቀጥ ገንዘብ”commodity money” ነው። “ዲናር” እና “ዲርሀም” የሚለኩት በሚስቃል ነው፥ “ሚስቃል” مِثْقَال የሚለው ቃል “ሰቀለ” ثَقَلَ ማለትም “ከበደ” ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን “ክብደት” ማለት ነው።
1 ሚስቃል ወርቅ 4.25 ግራም ነው፥ 20 ሚስቃል ወርቅ ደግሞ 4,25x 20 = 85 ግራም ወርቅ ይሆናል ማለት ነው።
1 ሚስቃል ብር 2.975 ግራም ነው፥ 200 ሚስቃል ብር ደግሞ 2.975x 200= 595 ግራም ብር ይሆናል ማለት ነው።
በዘካህ ላይ የሚወጅበው ኒሷብ 85 ግራም ወርቅ ወይም 595 ግራም ብር ነው።
አንድ ሙሥሊም ያስቀመጠው ካፒታል ዓመት ከሞላው እና ያም ካፒታል 85 ግራም ወርቅ ወይም 595 ግራም ብር ያክል ከሆነ ዘካህ ማውጣት ግዴታው ነው።
ዘካቱል ማል የሚወጣበት አነስተኛ ዋጋ የብር ኒሷብ ስለሆነ አብላጫው ምሁራን የብር ኒሷብን መሠረት ባደረገ መልኩ ከዚያ እንዲወጣ ፈትዋ ሰተዋል፥ ስለዚህ አንድ ሰው ዓመት የተቀመጠ 89,250 ብር(ገንዘብ) እና ከዛ በላይ ካለው ዘካህ ማውጣት ግዴታ አለበት።
እንዴት? ካላችሁ የብር ኒሷብ ወደ ወረቀት ገንዘብ”Fiat money” ለመቀየር ብርን ዛሬ ባለው የወቅቱ ግብይት ለናሙና ያክል መሥራት ይቻላል። በኢትዮጵያ አንድ ግራም ብር"silver" አሁን ባለኝ መረጃ 150 ብር"ገንዘብ" ነው፥ ስናሰላው 150×595= 89,250 ብር(ገንዘብ) ይሆናል።
ለምሳሌ፦ እኔ 100 ሺህ ብር ቢኖረኝ ከ 100 ሺህ ብር ላይ 2.5 % ዘካህ ሲሰላ 2,500 ይወጅብብኛል፥ ስናሰላው 100,000×2.5፥100= 2,500 ይሆናል።
ዘካህን መስጠት አንርሳ፦
2፥110 ሶላትንም አስተካክላችሁ ስገዱ፡፡ ዘካንም ስጡ፡፡ وَأَقِيمُوا الصَّلَاةَ وَآتُوا الزَّكَاةَ
አምላካችን አሏህ ዘካን ከሚሰጡ ባሮቹ ያድርገን! አሚን።
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
የሰው ሸይጧን
በነገራችን ላይ በረመዷን ኩፋሩል ጂን የሆኑ ሸይጧናት ይታሰራሉ።
ቅሉ ግን የማይታሰሩ የሰው ሸይጧናት አሉ፥ "ሸይጧን" شَّيْطَان የሚለው ቃል “ሸጠነ” شَّطَنَ ማለትም “ራቀ” ወይም “ተገለለ” ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን ከአሏህ ራሕመት “የተገለለ” ወይም “የራቀ” ማለት ነው፥ ሸያጢን ከአሏህ ራሕመት የራቁ ከጂንም ከሰውም ሊሆኑ ይችላል፦
6፥112 እንደዚሁም ለነቢያት ሁሉ ከሰው እና ከጂን የኾኑን ሰይጣናት ጠላት አደረግን፡፡ وَكَذَٰلِكَ جَعَلْنَا لِكُلِّ نَبِيٍّ عَدُوًّا شَيَاطِينَ الْإِنسِ وَالْجِن
114፥6 «ከጂኒዎችም ከሰዎችም ሰይጣናት እጠበቃለሁ» በል። مِنَ الْجِنَّةِ وَالنَّاسِ
23፥97 በልም «ጌታዬ ሆ! ከሰይጣናት ጉትተጎታዎች በአንተ እጠበቃለሁ» ፡፡ وَقُل رَّبِّ أَعُوذُ بِكَ مِنْ هَمَزَاتِ الشَّيَاطِينِ
እነርሱ ስላልታሠሩ ኢሥቲዓዛህ ማድረግ ግድ ይላል። በረመዷኑ በተለይ በዚህ አሥር ቀናት ውስጥ ሥራዬ ብለው ሰው እና ሰውን በማሰዳደብ እና በማጋጨት የሚያዞላልሙ በሥራቸው ኢብሊሥ የሚቀናባቸው ይመስለኛል። ላይክ እና ኮሜንት ለመሰብሰብ የግድ ሰውን ማጋጨት እኩይ ተግባር ነውና እንታቀብ!
አሏህ ሁላችንንም ያስተካክለን! አሚን።
በነገራችን ላይ በረመዷን ኩፋሩል ጂን የሆኑ ሸይጧናት ይታሰራሉ።
ቅሉ ግን የማይታሰሩ የሰው ሸይጧናት አሉ፥ "ሸይጧን" شَّيْطَان የሚለው ቃል “ሸጠነ” شَّطَنَ ማለትም “ራቀ” ወይም “ተገለለ” ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን ከአሏህ ራሕመት “የተገለለ” ወይም “የራቀ” ማለት ነው፥ ሸያጢን ከአሏህ ራሕመት የራቁ ከጂንም ከሰውም ሊሆኑ ይችላል፦
6፥112 እንደዚሁም ለነቢያት ሁሉ ከሰው እና ከጂን የኾኑን ሰይጣናት ጠላት አደረግን፡፡ وَكَذَٰلِكَ جَعَلْنَا لِكُلِّ نَبِيٍّ عَدُوًّا شَيَاطِينَ الْإِنسِ وَالْجِن
114፥6 «ከጂኒዎችም ከሰዎችም ሰይጣናት እጠበቃለሁ» በል። مِنَ الْجِنَّةِ وَالنَّاسِ
23፥97 በልም «ጌታዬ ሆ! ከሰይጣናት ጉትተጎታዎች በአንተ እጠበቃለሁ» ፡፡ وَقُل رَّبِّ أَعُوذُ بِكَ مِنْ هَمَزَاتِ الشَّيَاطِينِ
እነርሱ ስላልታሠሩ ኢሥቲዓዛህ ማድረግ ግድ ይላል። በረመዷኑ በተለይ በዚህ አሥር ቀናት ውስጥ ሥራዬ ብለው ሰው እና ሰውን በማሰዳደብ እና በማጋጨት የሚያዞላልሙ በሥራቸው ኢብሊሥ የሚቀናባቸው ይመስለኛል። ላይክ እና ኮሜንት ለመሰብሰብ የግድ ሰውን ማጋጨት እኩይ ተግባር ነውና እንታቀብ!
አሏህ ሁላችንንም ያስተካክለን! አሚን።
በነገራችን ላይ እኛ ኢትዮጵያውያን አሳባችንን በቅንነት ከማንሸራሸር እና የሌላውን አሳብ በነጻነት ከመስማት ይልቅ ስድብ ይቀናናል። ቀጣይ ትውልድ ከእኛ ምን እንደሚማር አሏህ ይሁነን። በዚሁ ከቀጠልን መጠፋፋታችን ነው።
በተሳዳቢዎች ጦስ ሙሥሊሙን አንዱ የጽንፍ ክንፍ በዘሩ ይገለዋል፥ ሌላው የጽንፍ ክንፍ በሃይማኖቱ ይገለዋል።
አሏህ ይድረስልን! በዳዮችን የእጃቸው ይስጣቸው።
በተሳዳቢዎች ጦስ ሙሥሊሙን አንዱ የጽንፍ ክንፍ በዘሩ ይገለዋል፥ ሌላው የጽንፍ ክንፍ በሃይማኖቱ ይገለዋል።
አሏህ ይድረስልን! በዳዮችን የእጃቸው ይስጣቸው።
ይጋጫልን?
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
4፥82 ቁርኣንን አያስተነትኑምን? ከአላህ ሌላ ዘንድ በነበረ ኖሮ በእርሱ ውስጥ ብዙን መለያየት ባገኙ ነበር፡፡ أَفَلَا يَتَدَبَّرُونَ الْقُرْآنَ ۚ وَلَوْ كَانَ مِنْ عِندِ غَيْرِ اللَّهِ لَوَجَدُوا فِيهِ اخْتِلَافًا كَثِيرًا
ጥያቄ፦
"አሏህ መልእክተኞች እኩል አድርጓል ወይስ አላደረገም?
A. እኩል አድርጓል፦
2፥285 "ከመልእክተኞቹ በአንድም መካከል አንለይም" لَا نُفَرِّقُ بَيْنَ أَحَدٍ مِّن رُّسُلِهِ
B. እኩል አላደረገም፦
2፥253 "እነዚህን መልእክተኞች ከፊላቸውን በከፊሉ ላይ አበለጥን"፡፡ تِلْكَ الرُّسُلُ فَضَّلْنَا بَعْضَهُمْ عَلَىٰ بَعْضٍ
መልስ፦
ለአይሁዳውያን፦ «አላህም ባወረደው ሁሉ እመኑ» በተባሉ ጊዜ «በእኛ ላይ በተወረደው ብቻ እናምናለን» ይላሉ፥ "በእኛ ላይ በተወረደው" ለሚሉት ለነቢያት ወሕይ አረጋጋጭ የሆነው ቁርኣን በመካድ በከፊሉ በማመን እና በከፊሉ በመካድ አስተባብለዋል፦
2፥91 ለእነርሱ «አላህም ባወረደው ሁሉ እመኑ» በተባሉ ጊዜ «በእኛ ላይ በተወረደው ብቻ እናምናለን» ይላሉ፥ ከእርሱ በኋላ ያለው እርሱ ከእነርሱ ጋር ላለው አረጋጋጭ እውተኛ ሲኾን ይክዳሉ፡፡ وَإِذَا قِيلَ لَهُمْ آمِنُوا بِمَا أَنزَلَ اللَّهُ قَالُوا نُؤْمِنُ بِمَا أُنزِلَ عَلَيْنَا وَيَكْفُرُونَ بِمَا وَرَاءَهُ وَهُوَ الْحَقُّ مُصَدِّقًا لِّمَا مَعَهُمْ
አምላካችን አሏህ ተወዳጁ ነቢያችንን "ቁል" قُلْ በሚል ትእዛዛዊ ግሥ በእርሳቸው ላይ በተወረደው ቁርኣን እና ከእርሳቸው በፊት በነበሩት ነቢያት ላይ በተወረደው ወሕይ "አመንን" እንዲሉ አዟል፦
3፥84 በል፦ "በአላህ እና በእኛ ላይ በተወረደው አመንን" قُلْ آمَنَّا بِاللَّهِ وَمَا أُنزِلَ عَلَيْنَا
3፥84 "በኢብራሂም፣ በኢስማዒል፣ በኢስሓቅ፣ በያዕቆብ፣ በነገዶችም ላይ በተወረደው፣ ለሙሳሣ እና ለዒሣ በተሰጡት፣ በዚያም ለነቢያት ሁሉ ከጌታቸው በተሰጠው አመንን"። وَمَا أُنزِلَ عَلَىٰ إِبْرَاهِيمَ وَإِسْمَاعِيلَ وَإِسْحَاقَ وَيَعْقُوبَ وَالْأَسْبَاطِ وَمَا أُوتِيَ مُوسَىٰ وَعِيسَىٰ وَالنَّبِيُّونَ مِن رَّبِّهِمْ
አምላካችን አሏህ ለዚያ ነው፦ "መልእክተኛው ከጌታው ወደ እርሱ በተወረደው አመነ" በማለት የነገረን፦
2፥285 መልእክተኛው ከጌታው ወደ እርሱ በተወረደው አመነ፡፡ آمَنَ الرَّسُولُ بِمَا أُنزِلَ إِلَيْهِ مِن رَّبِّهِ
ሌላ አንቀጽ ላይ ደግሞ አምላካችን አሏህ የተወዳጁ ነቢያችን ተከታዮች ምእመናን "ቁሉ" قُولُوا በሚል ትእዛዛዊ ግሥ በእነርሱ ላይ በተወረደው ቁርኣን እና ከእርሳቸው በፊት በነበሩት ነቢያት ላይ በተወረደው ወሕይ "አመንን" እንዲሉ አዟል፦
2፥136 በሉ፦ "በአላህ እና ወደ እኛ በተወረደው አመንን" قُولُوا آمَنَّا بِاللَّهِ وَمَا أُنزِلَ إِلَيْنَا
2፥136 ወደ ኢብራሂም፣ ወደ ኢስማዒል፣ ወደ ኢስሐቅ፣ ወደ ያዕቁብ እና ወደ ነገዶቹም በተወረደው፣ በዚያም ለሙሣ እና ለዒሣ በተሰጡት፣ በዚያም ለነቢያት ሁሉ ከጌታቸው በተሰጡት አመንን"። وَمَا أُنزِلَ إِلَىٰ إِبْرَاهِيمَ وَإِسْمَاعِيلَ وَإِسْحَاقَ وَيَعْقُوبَ وَالْأَسْبَاطِ وَمَا أُوتِيَ مُوسَىٰ وَعِيسَىٰ وَمَا أُوتِيَ النَّبِيُّونَ مِن رَّبِّهِمْ
አምላካችን አሏህ ለዚያ ነው፦ "ምእመናን እንደዚሁ አመኑ" በማለት የነገረን፦
2፥285 ምእመናን እንደዚሁ አመኑ፡፡ وَالْمُؤْمِنُونَ
"ሁሉም" ማለትም ተወዳጁ ነቢያችን እና ምእመናን «ከመልእክተኞቹ በአንድም መካከል አንለይም» የሚሉ ሲኾኑ አመኑ፦
2፥285 ሁሉም በአላህ፣ በመላዕክቱም፣ በመጻሕፍቱም፣ በመልእክተኞቹም «ከመልእክተኞቹ በአንድም መካከል አንለይም» የሚሉ ሲኾኑ አመኑ፡፡ كُلٌّ آمَنَ بِاللَّهِ وَمَلَائِكَتِهِ وَكُتُبِهِ وَرُسُلِهِ لَا نُفَرِّقُ بَيْنَ أَحَدٍ مِّن رُّسُلِهِ
3፥84 "ከእነርሱ መካከል አንድንም አንለይም" نُفَرِّقُ بَيْنَ أَحَدٍ مِّنْهُمْ
2፥136 "ከእነርሱ መካከል አንድንም አንለይም" نُفَرِّقُ بَيْنَ أَحَدٍ مِّنْهُمْ
በሁሉም ነቢያት ላይ የተወረደው የመልእክቱ ጭብጥ ተውሒድ ስለሆነ ከእነርሱ መካከል አንድንም ሳንለይ እናምናለን፥ "ላ ኢላሀ ኢላ አና" لَا إِلَـٰهَ إِلَّا أَنَا የሚለው መገሰጫ ለነቢያችን እና ከእርሳቸው በፊት በነበሩት ነቢያት ላይ የወረደ መገሰጫ ነው፦
21፥24 «አስረጃችሁን አምጡ፡፡ ይህ መገሰጫ እኔ ዘንድ ያለው ከእኔ በፊትም የነበረ መገሰጫ ነው» በላቸው፡፡ قُلْ هَاتُوا بُرْهَانَكُمْ ۖ هَـٰذَا ذِكْرُ مَن مَّعِيَ وَذِكْرُ مَن قَبْلِي
21፥25 ከአንተ በፊትም፦ "እነሆ ከእኔ ሌላ አምላክ የለምና አምልኩኝ" በማለት ወደ እርሱ የምናወርድለት ቢኾን እንጂ ከመልእክተኛ አንድንም አላክንም፡፡ وَمَا أَرْسَلْنَا مِن قَبْلِكَ مِن رَّسُولٍ إِلَّا نُوحِي إِلَيْهِ أَنَّهُ لَا إِلَـٰهَ إِلَّا أَنَا فَاعْبُدُونِ
"ዚክር" ذِكْر ማለት "መገሰጫ" ማለት ሲሆን ለሁሉም መልእክተኞች የወረደውን መልእክት ተህሊል ስለሆነ አይሁዳውያን በመልእክተኞቹ መካከል ሳይለዩ ማመን ሲገባቸው በተቃራኒው በመካድ «በከፊሉም እናምናለን በከፊሉም እንክዳለን» የሚሉ እነዚያ በእውነት ከሓዲዎቹ እነርሱ ናቸው። ለእነርሱ አዋራጅን ቅጣት አሏህ አዘጋጅቷል፦
4፥150 እነዚያ በአላህ እና በመልእክተኞቹ የሚክዱ፣ በአላህ እና በመልእክተኞቹም መካከል መለየትን የሚፈልጉ፣ «በከፊሉም እናምናለን በከፊሉም እንክዳለን» የሚሉ፣ በዚህም መካከል መንገድን ሊይዙ የሚፈልጉ እነዚያ በእውነት ከሓዲዎቹ እነርሱ ናቸው፡፡ ለከሓዲዎችም አዋራጅን ቅጣት አዘጋጅተናል፡፡ إِنَّ الَّذِينَ يَكْفُرُونَ بِاللَّهِ وَرُسُلِهِ وَيُرِيدُونَ أَن يُفَرِّقُوا بَيْنَ اللَّهِ وَرُسُلِهِ وَيَقُولُونَ نُؤْمِنُ بِبَعْضٍ وَنَكْفُرُ بِبَعْضٍ وَيُرِيدُونَ أَن يَتَّخِذُوا بَيْنَ ذَٰلِكَ سَبِيلًا أُولَـٰئِكَ هُمُ الْكَافِرُونَ حَقًّا ۚ وَأَعْتَدْنَا لِلْكَافِرِينَ عَذَابًا مُّهِينًا
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
4፥82 ቁርኣንን አያስተነትኑምን? ከአላህ ሌላ ዘንድ በነበረ ኖሮ በእርሱ ውስጥ ብዙን መለያየት ባገኙ ነበር፡፡ أَفَلَا يَتَدَبَّرُونَ الْقُرْآنَ ۚ وَلَوْ كَانَ مِنْ عِندِ غَيْرِ اللَّهِ لَوَجَدُوا فِيهِ اخْتِلَافًا كَثِيرًا
ጥያቄ፦
"አሏህ መልእክተኞች እኩል አድርጓል ወይስ አላደረገም?
A. እኩል አድርጓል፦
2፥285 "ከመልእክተኞቹ በአንድም መካከል አንለይም" لَا نُفَرِّقُ بَيْنَ أَحَدٍ مِّن رُّسُلِهِ
B. እኩል አላደረገም፦
2፥253 "እነዚህን መልእክተኞች ከፊላቸውን በከፊሉ ላይ አበለጥን"፡፡ تِلْكَ الرُّسُلُ فَضَّلْنَا بَعْضَهُمْ عَلَىٰ بَعْضٍ
መልስ፦
ለአይሁዳውያን፦ «አላህም ባወረደው ሁሉ እመኑ» በተባሉ ጊዜ «በእኛ ላይ በተወረደው ብቻ እናምናለን» ይላሉ፥ "በእኛ ላይ በተወረደው" ለሚሉት ለነቢያት ወሕይ አረጋጋጭ የሆነው ቁርኣን በመካድ በከፊሉ በማመን እና በከፊሉ በመካድ አስተባብለዋል፦
2፥91 ለእነርሱ «አላህም ባወረደው ሁሉ እመኑ» በተባሉ ጊዜ «በእኛ ላይ በተወረደው ብቻ እናምናለን» ይላሉ፥ ከእርሱ በኋላ ያለው እርሱ ከእነርሱ ጋር ላለው አረጋጋጭ እውተኛ ሲኾን ይክዳሉ፡፡ وَإِذَا قِيلَ لَهُمْ آمِنُوا بِمَا أَنزَلَ اللَّهُ قَالُوا نُؤْمِنُ بِمَا أُنزِلَ عَلَيْنَا وَيَكْفُرُونَ بِمَا وَرَاءَهُ وَهُوَ الْحَقُّ مُصَدِّقًا لِّمَا مَعَهُمْ
አምላካችን አሏህ ተወዳጁ ነቢያችንን "ቁል" قُلْ በሚል ትእዛዛዊ ግሥ በእርሳቸው ላይ በተወረደው ቁርኣን እና ከእርሳቸው በፊት በነበሩት ነቢያት ላይ በተወረደው ወሕይ "አመንን" እንዲሉ አዟል፦
3፥84 በል፦ "በአላህ እና በእኛ ላይ በተወረደው አመንን" قُلْ آمَنَّا بِاللَّهِ وَمَا أُنزِلَ عَلَيْنَا
3፥84 "በኢብራሂም፣ በኢስማዒል፣ በኢስሓቅ፣ በያዕቆብ፣ በነገዶችም ላይ በተወረደው፣ ለሙሳሣ እና ለዒሣ በተሰጡት፣ በዚያም ለነቢያት ሁሉ ከጌታቸው በተሰጠው አመንን"። وَمَا أُنزِلَ عَلَىٰ إِبْرَاهِيمَ وَإِسْمَاعِيلَ وَإِسْحَاقَ وَيَعْقُوبَ وَالْأَسْبَاطِ وَمَا أُوتِيَ مُوسَىٰ وَعِيسَىٰ وَالنَّبِيُّونَ مِن رَّبِّهِمْ
አምላካችን አሏህ ለዚያ ነው፦ "መልእክተኛው ከጌታው ወደ እርሱ በተወረደው አመነ" በማለት የነገረን፦
2፥285 መልእክተኛው ከጌታው ወደ እርሱ በተወረደው አመነ፡፡ آمَنَ الرَّسُولُ بِمَا أُنزِلَ إِلَيْهِ مِن رَّبِّهِ
ሌላ አንቀጽ ላይ ደግሞ አምላካችን አሏህ የተወዳጁ ነቢያችን ተከታዮች ምእመናን "ቁሉ" قُولُوا በሚል ትእዛዛዊ ግሥ በእነርሱ ላይ በተወረደው ቁርኣን እና ከእርሳቸው በፊት በነበሩት ነቢያት ላይ በተወረደው ወሕይ "አመንን" እንዲሉ አዟል፦
2፥136 በሉ፦ "በአላህ እና ወደ እኛ በተወረደው አመንን" قُولُوا آمَنَّا بِاللَّهِ وَمَا أُنزِلَ إِلَيْنَا
2፥136 ወደ ኢብራሂም፣ ወደ ኢስማዒል፣ ወደ ኢስሐቅ፣ ወደ ያዕቁብ እና ወደ ነገዶቹም በተወረደው፣ በዚያም ለሙሣ እና ለዒሣ በተሰጡት፣ በዚያም ለነቢያት ሁሉ ከጌታቸው በተሰጡት አመንን"። وَمَا أُنزِلَ إِلَىٰ إِبْرَاهِيمَ وَإِسْمَاعِيلَ وَإِسْحَاقَ وَيَعْقُوبَ وَالْأَسْبَاطِ وَمَا أُوتِيَ مُوسَىٰ وَعِيسَىٰ وَمَا أُوتِيَ النَّبِيُّونَ مِن رَّبِّهِمْ
አምላካችን አሏህ ለዚያ ነው፦ "ምእመናን እንደዚሁ አመኑ" በማለት የነገረን፦
2፥285 ምእመናን እንደዚሁ አመኑ፡፡ وَالْمُؤْمِنُونَ
"ሁሉም" ማለትም ተወዳጁ ነቢያችን እና ምእመናን «ከመልእክተኞቹ በአንድም መካከል አንለይም» የሚሉ ሲኾኑ አመኑ፦
2፥285 ሁሉም በአላህ፣ በመላዕክቱም፣ በመጻሕፍቱም፣ በመልእክተኞቹም «ከመልእክተኞቹ በአንድም መካከል አንለይም» የሚሉ ሲኾኑ አመኑ፡፡ كُلٌّ آمَنَ بِاللَّهِ وَمَلَائِكَتِهِ وَكُتُبِهِ وَرُسُلِهِ لَا نُفَرِّقُ بَيْنَ أَحَدٍ مِّن رُّسُلِهِ
3፥84 "ከእነርሱ መካከል አንድንም አንለይም" نُفَرِّقُ بَيْنَ أَحَدٍ مِّنْهُمْ
2፥136 "ከእነርሱ መካከል አንድንም አንለይም" نُفَرِّقُ بَيْنَ أَحَدٍ مِّنْهُمْ
በሁሉም ነቢያት ላይ የተወረደው የመልእክቱ ጭብጥ ተውሒድ ስለሆነ ከእነርሱ መካከል አንድንም ሳንለይ እናምናለን፥ "ላ ኢላሀ ኢላ አና" لَا إِلَـٰهَ إِلَّا أَنَا የሚለው መገሰጫ ለነቢያችን እና ከእርሳቸው በፊት በነበሩት ነቢያት ላይ የወረደ መገሰጫ ነው፦
21፥24 «አስረጃችሁን አምጡ፡፡ ይህ መገሰጫ እኔ ዘንድ ያለው ከእኔ በፊትም የነበረ መገሰጫ ነው» በላቸው፡፡ قُلْ هَاتُوا بُرْهَانَكُمْ ۖ هَـٰذَا ذِكْرُ مَن مَّعِيَ وَذِكْرُ مَن قَبْلِي
21፥25 ከአንተ በፊትም፦ "እነሆ ከእኔ ሌላ አምላክ የለምና አምልኩኝ" በማለት ወደ እርሱ የምናወርድለት ቢኾን እንጂ ከመልእክተኛ አንድንም አላክንም፡፡ وَمَا أَرْسَلْنَا مِن قَبْلِكَ مِن رَّسُولٍ إِلَّا نُوحِي إِلَيْهِ أَنَّهُ لَا إِلَـٰهَ إِلَّا أَنَا فَاعْبُدُونِ
"ዚክር" ذِكْر ማለት "መገሰጫ" ማለት ሲሆን ለሁሉም መልእክተኞች የወረደውን መልእክት ተህሊል ስለሆነ አይሁዳውያን በመልእክተኞቹ መካከል ሳይለዩ ማመን ሲገባቸው በተቃራኒው በመካድ «በከፊሉም እናምናለን በከፊሉም እንክዳለን» የሚሉ እነዚያ በእውነት ከሓዲዎቹ እነርሱ ናቸው። ለእነርሱ አዋራጅን ቅጣት አሏህ አዘጋጅቷል፦
4፥150 እነዚያ በአላህ እና በመልእክተኞቹ የሚክዱ፣ በአላህ እና በመልእክተኞቹም መካከል መለየትን የሚፈልጉ፣ «በከፊሉም እናምናለን በከፊሉም እንክዳለን» የሚሉ፣ በዚህም መካከል መንገድን ሊይዙ የሚፈልጉ እነዚያ በእውነት ከሓዲዎቹ እነርሱ ናቸው፡፡ ለከሓዲዎችም አዋራጅን ቅጣት አዘጋጅተናል፡፡ إِنَّ الَّذِينَ يَكْفُرُونَ بِاللَّهِ وَرُسُلِهِ وَيُرِيدُونَ أَن يُفَرِّقُوا بَيْنَ اللَّهِ وَرُسُلِهِ وَيَقُولُونَ نُؤْمِنُ بِبَعْضٍ وَنَكْفُرُ بِبَعْضٍ وَيُرِيدُونَ أَن يَتَّخِذُوا بَيْنَ ذَٰلِكَ سَبِيلًا أُولَـٰئِكَ هُمُ الْكَافِرُونَ حَقًّا ۚ وَأَعْتَدْنَا لِلْكَافِرِينَ عَذَابًا مُّهِينًا
ስለዚህ ከመነሻው "ከመልእክተኞቹ በአንድም መካከል አንለይም" ያለው አሏህ ሳይሆን አሏህ ተወዳጁ ነቢያችን እና ምእመናን እንዲሉ ያዘዘው ትእዛዝ ነው፥ "ከመልእክተኞቹ በአንድም መካከል አንለይም" ብለው የሚያምኑት ምእመናን ሆነው ሳለ አሏህ "ከመልእክተኞቹ በአንድም መካከል አንለይም" ብሎ እንደተናገረ አርጎ መረዳት ዓረፍተነገሩን ከዐውዱ ማፋታት ነው። "አመነ" آمَنَ እና "አመና" آمَنَّا የሚል ኃይለ ቃል ከአንቀጹ በማውጣት እና የራስን አሳብ መክተት በሥነ አፈታት ጥናት"hermeneutics" ፈቲሆት"exegesis" ሳይሆን ሰጊዎት"eisegesis" ነው።
አሏህ እኛን፦ "ከመልእክተኞቹ በአንድም መካከል አንለይም" "በሉ" ያለበት ምክንያት አይሁዳውያን አላህ ከባሮቹ በሚሻው ሰው ላይ ከችሮታው ማውረዱን በምቀኝነት በመካዳቸው ነው፦
2፥90 ነፍሶቻቸውን በእርሱ የሸጡበት ነገር ከፋ! እርሱም አላህ ከባሮቹ በሚሻው ሰው ላይ ከችሮታው ማውረዱን በመመቅኘት አላህ ባወረደው ነገር መካዳቸው ነው፡፡ بِئْسَمَا اشْتَرَوْا بِهِ أَنفُسَهُمْ أَن يَكْفُرُوا بِمَا أَنزَلَ اللَّهُ بَغْيًا أَن يُنَزِّلَ اللَّهُ مِن فَضْلِهِ عَلَىٰ مَن يَشَاءُ مِنْ عِبَادِهِ
እዚህ አንቀጽ ላይ "ችሮታ" ለሚለው የገባ ቃል "ፈድል" فَضْل ሲሆን ሲሆን "ስጦታ" "ችሮታ" "ጸጋ"Bounty” ማለት ነው፥ ሥርወ-ቃሉ "ፈዶለ" فَضَّلَ ማለትም" ሰጠ" "ቸረ" ነው። አምላካችን አሏህ በሚያወርደው ፈድል መልእክተኞች ከፊላቸውን በከፊሉ ላይ አብልጧል፦
2፥253 እነዚህን መልእክተኞች ከፊላቸውን በከፊሉ ላይ አበለጥን፡፡ تِلْكَ الرُّسُلُ فَضَّلْنَا بَعْضَهُمْ عَلَىٰ بَعْضٍ
17፥55 ከፊሉንም ነቢያት በከፊሉ ላይ በእርግጥ አበለጥን፡፡ وَلَقَدْ فَضَّلْنَا بَعْضَ النَّبِيِّينَ عَلَىٰ بَعْضٍ
እነዚህ አናቅጽ ላይ "አበለጥን" ለሚለው የገባ ቃል "ፈዶልና" فَضَّلْنَا መሆኑን ልብ ብለካልን? አንደ መልእክተኛ ጋር የተወረደለት ፈድል ሌላው ጋር ሰለሌለ ከፍሉ በከፊሉ ላይ ይበላለጣሉ፥ ለምሳሌ፦ አሏህ ሙሣን በቀጥታ ሲያናግር ሌላውን በመልአክ ወይም በራእይ በማናገር ከፊላቸውን በከፊሉ ላይ አብልጧል፦
2፥253 ከእነርሱ ውስጥ አላህ ያነጋገረው አለ፡፡ مِّنْهُم مَّن كَلَّمَ اللَّهُ
4፥164 አላህ ሙሣን ማነጋገርን አነጋገረው፡፡ وَكَلَّمَ اللَّهُ مُوسَىٰ تَكْلِيمًا
ይህ የደረጃ ልዩነት እንጂ የኑባሬ ልዩነት አይደለም። ለምሳሌ፦ አሏህ ለመርየምን ልጅ ለዒሣ ግልጽ ተአምራትን በመስጠት እና በቅዱሱ መንፈስ በማበረታታት አብልጧል፦
2፥253 ከፊሎቻቸውንም በደረጃዎች ከፍ አደረገ፡፡ የመርየምን ልጅ ዒሣን ግልጽ ተአምራትን ሰጠነው፥ በቅዱሱ መንፈስም አበረታነው፡፡ وَرَفَعَ بَعْضَهُمْ دَرَجَاتٍ ۚ وَآتَيْنَا عِيسَى ابْنَ مَرْيَمَ الْبَيِّنَاتِ وَأَيَّدْنَاهُ بِرُوحِ الْقُدُسِ
2፥87 የመርየምን ልጅ ዒሣን ግልጽ ተአምራትን ሰጠነው፡፡ በቅዱሱ መንፈስም አበረታነው፡፡ وَآتَيْنَا عِيسَى ابْنَ مَرْيَمَ الْبَيِّنَاتِ وَأَيَّدْنَاهُ بِرُوحِ الْقُدُسِ
ግጭት ማለት አሏህ እኛን፦ "እኩል አርጋችሁ እመኑ" ብሎን በተቃራኒው "አንዱን መልእክተኛ ከሌላው አስብልጡ" ቢለን ወይም አሏህ፦ "መልእክተኞች ከፊላቸውን በከፊሉ ላይ አበለጥን" ብሎ "ከመልእክተኞቹ በአንድም መካከል ስንለይ እኩል አርገናል" ቢል ኖሮ ግጭት ነበር። ነገር ግን ቁርኣን የፈጣሪያችን የአሏህ ንግግር ስለሆነ እና የሰው ንግግር ስላልገባበት የእርስ በእርስ ግጭት የለውም፦
4፥82 ቁርኣንን አያስተነትኑምን? ከአላህ ሌላ ዘንድ በነበረ ኖሮ በእርሱ ውስጥ ብዙን መለያየት ባገኙ ነበር፡፡ أَفَلَا يَتَدَبَّرُونَ الْقُرْآنَ ۚ وَلَوْ كَانَ مِنْ عِندِ غَيْرِ اللَّهِ لَوَجَدُوا فِيهِ اخْتِلَافًا كَثِيرًا
"ኢኽቲላፍ" اخْتِلَاف ማለት "ግጭት" ማለት ሲሆን ቁርኣን ከአሏህ ዘንድ በግልጠተ መለኮት የመጣ የአሏህ ንግግር ስለሆነ እርስ በእርስ አይጋጭም። አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛን ጽናቱን ይስጠን! አሚን።
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
አሏህ እኛን፦ "ከመልእክተኞቹ በአንድም መካከል አንለይም" "በሉ" ያለበት ምክንያት አይሁዳውያን አላህ ከባሮቹ በሚሻው ሰው ላይ ከችሮታው ማውረዱን በምቀኝነት በመካዳቸው ነው፦
2፥90 ነፍሶቻቸውን በእርሱ የሸጡበት ነገር ከፋ! እርሱም አላህ ከባሮቹ በሚሻው ሰው ላይ ከችሮታው ማውረዱን በመመቅኘት አላህ ባወረደው ነገር መካዳቸው ነው፡፡ بِئْسَمَا اشْتَرَوْا بِهِ أَنفُسَهُمْ أَن يَكْفُرُوا بِمَا أَنزَلَ اللَّهُ بَغْيًا أَن يُنَزِّلَ اللَّهُ مِن فَضْلِهِ عَلَىٰ مَن يَشَاءُ مِنْ عِبَادِهِ
እዚህ አንቀጽ ላይ "ችሮታ" ለሚለው የገባ ቃል "ፈድል" فَضْل ሲሆን ሲሆን "ስጦታ" "ችሮታ" "ጸጋ"Bounty” ማለት ነው፥ ሥርወ-ቃሉ "ፈዶለ" فَضَّلَ ማለትም" ሰጠ" "ቸረ" ነው። አምላካችን አሏህ በሚያወርደው ፈድል መልእክተኞች ከፊላቸውን በከፊሉ ላይ አብልጧል፦
2፥253 እነዚህን መልእክተኞች ከፊላቸውን በከፊሉ ላይ አበለጥን፡፡ تِلْكَ الرُّسُلُ فَضَّلْنَا بَعْضَهُمْ عَلَىٰ بَعْضٍ
17፥55 ከፊሉንም ነቢያት በከፊሉ ላይ በእርግጥ አበለጥን፡፡ وَلَقَدْ فَضَّلْنَا بَعْضَ النَّبِيِّينَ عَلَىٰ بَعْضٍ
እነዚህ አናቅጽ ላይ "አበለጥን" ለሚለው የገባ ቃል "ፈዶልና" فَضَّلْنَا መሆኑን ልብ ብለካልን? አንደ መልእክተኛ ጋር የተወረደለት ፈድል ሌላው ጋር ሰለሌለ ከፍሉ በከፊሉ ላይ ይበላለጣሉ፥ ለምሳሌ፦ አሏህ ሙሣን በቀጥታ ሲያናግር ሌላውን በመልአክ ወይም በራእይ በማናገር ከፊላቸውን በከፊሉ ላይ አብልጧል፦
2፥253 ከእነርሱ ውስጥ አላህ ያነጋገረው አለ፡፡ مِّنْهُم مَّن كَلَّمَ اللَّهُ
4፥164 አላህ ሙሣን ማነጋገርን አነጋገረው፡፡ وَكَلَّمَ اللَّهُ مُوسَىٰ تَكْلِيمًا
ይህ የደረጃ ልዩነት እንጂ የኑባሬ ልዩነት አይደለም። ለምሳሌ፦ አሏህ ለመርየምን ልጅ ለዒሣ ግልጽ ተአምራትን በመስጠት እና በቅዱሱ መንፈስ በማበረታታት አብልጧል፦
2፥253 ከፊሎቻቸውንም በደረጃዎች ከፍ አደረገ፡፡ የመርየምን ልጅ ዒሣን ግልጽ ተአምራትን ሰጠነው፥ በቅዱሱ መንፈስም አበረታነው፡፡ وَرَفَعَ بَعْضَهُمْ دَرَجَاتٍ ۚ وَآتَيْنَا عِيسَى ابْنَ مَرْيَمَ الْبَيِّنَاتِ وَأَيَّدْنَاهُ بِرُوحِ الْقُدُسِ
2፥87 የመርየምን ልጅ ዒሣን ግልጽ ተአምራትን ሰጠነው፡፡ በቅዱሱ መንፈስም አበረታነው፡፡ وَآتَيْنَا عِيسَى ابْنَ مَرْيَمَ الْبَيِّنَاتِ وَأَيَّدْنَاهُ بِرُوحِ الْقُدُسِ
ግጭት ማለት አሏህ እኛን፦ "እኩል አርጋችሁ እመኑ" ብሎን በተቃራኒው "አንዱን መልእክተኛ ከሌላው አስብልጡ" ቢለን ወይም አሏህ፦ "መልእክተኞች ከፊላቸውን በከፊሉ ላይ አበለጥን" ብሎ "ከመልእክተኞቹ በአንድም መካከል ስንለይ እኩል አርገናል" ቢል ኖሮ ግጭት ነበር። ነገር ግን ቁርኣን የፈጣሪያችን የአሏህ ንግግር ስለሆነ እና የሰው ንግግር ስላልገባበት የእርስ በእርስ ግጭት የለውም፦
4፥82 ቁርኣንን አያስተነትኑምን? ከአላህ ሌላ ዘንድ በነበረ ኖሮ በእርሱ ውስጥ ብዙን መለያየት ባገኙ ነበር፡፡ أَفَلَا يَتَدَبَّرُونَ الْقُرْآنَ ۚ وَلَوْ كَانَ مِنْ عِندِ غَيْرِ اللَّهِ لَوَجَدُوا فِيهِ اخْتِلَافًا كَثِيرًا
"ኢኽቲላፍ" اخْتِلَاف ማለት "ግጭት" ማለት ሲሆን ቁርኣን ከአሏህ ዘንድ በግልጠተ መለኮት የመጣ የአሏህ ንግግር ስለሆነ እርስ በእርስ አይጋጭም። አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛን ጽናቱን ይስጠን! አሚን።
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
ከዕባህ
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
105፥1 በዝሆኑ ባለቤቶች ጌታህ እንዴት እንደሠራ አላወቅህምን? أَلَمْ تَرَ كَيْفَ فَعَلَ رَبُّكَ بِأَصْحَابِ الْفِيلِ
"ከዕባህ" كَعْبَة ማለት "አንኳር“cube" ማለት ሲሆን አንኳር "ምልዓት" ነው፥ ምልአት ባለ ሦስት ቅጥ ነው። ይህም ቁመት፣ ርዝምት እና ስፋት ነው፥ አምላካችን አሏህ ከዕባን የተቀደሰ ወይም የተከበረ ቤት አደረገው፦
5፥97 "ከዕባን የተከበረውን ቤት፣ ክልክል የኾነውንም ወር፣ መስዋዕቱንና ባለ ምልክቶቹንም መንጋዎች አላህ ለሰዎች መቋቋሚያ አደረገ፡፡ جَعَلَ ٱللَّهُ ٱلْكَعْبَةَ ٱلْبَيْتَ ٱلْحَرَامَ قِيَٰمًۭا لِّلنَّاسِ وَٱلشَّهْرَ ٱلْحَرَامَ وَٱلْهَدْىَ وَٱلْقَلَٰٓئِدَ
3፥96 ለሰዎች መጀመሪያ የተኖረዉ ቤት ቡሩክ እና ለዓለማት ሁሉ መመሪያ ሲኾን ያ በበካህ ያለው ነው። إِنَّ أَوَّلَ بَيْتٍۢ وُضِعَ لِلنَّاسِ لَلَّذِى بِبَكَّةَ مُبَارَكًۭا وَهُدًۭى لِّلْعَٰلَمِينَ
ከዕባህ ለሰዎች መጀመሪያ የተኖረዉ ቤት ቡሩክ እና ለዓለማት ሁሉ መመሪያ ሆኖ ሳለ የአክሱም መንግሥት ንጉሥ ካሌብ እስከ የመን ድረስ ይገዛ ነበር። በጃሂሊያህ ጊዜ የካሌብ ጦር መሪ አብረሃህ አል አሽረም በ 527 ድኅረ ልደት በየመን ውስጥ ከአሏህ ቤት ጋር በማፎካከር ቤተክርስቲያን አሠርቷል፦
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 63, ሐዲስ 49
ጀሪር ኢብኑ ዐብደሏህ እንደተረከው፦ “በዘመነ-ጃሂሊያ ዙል-ኸለሷህ የሚባል ቤት ነበረ፥ የቀኝ ከዕባህ ወይም የግራ ከዕባህ ተብሎ ይጠራ ነበር”። عَنْ جَرِيرِ بْنِ عَبْدِ اللَّهِ، قَالَ كَانَ فِي الْجَاهِلِيَّةِ بَيْتٌ يُقَالَ لَهُ ذُو الْخَلَصَةِ، وَكَانَ يُقَالُ لَهُ الْكَعْبَةُ الْيَمَانِيَةُ، أَوِ الْكَعْبَةُ الشَّأْمِيَّةُ
“ኸለሷህ” خَلَصَة ማለት “ቀሊሥ” قَلِسْ ማለት ነው፥ “ቀሊሥ” ከግሪኩ ኮይኔ “ኤክሌሲያ” εκκλεσια የመጣ ሲሆን በተለምዶ “ቤተ ክርስቲያን” ይባል እንጂ “ጉባኤ” “ማኅበር” “ተጠርተው የወጡ” ማለት ነው። ይህንን ቤት ከከዕባ ጋር ለማመሳሰል “አል ከዕበቱል የማኒያህ” الْكَعْبَةُ الْيَمَانِيَة ወይም “አል ከዕበቱሽ ሸእሚያህ” الْكَعْبَةُ الشَّأْمِيَّة ብሎታል። በ 570 ድኅረ ልደት "አብረሃህ አል አሽረም" أَبْرَهَة ٱلْأَشْرَم እና ጭፍሮቹ የአሏህ ቤት ለማፍረስ በዝሆን ጋልበው ወደ መካ መጡ፥ አሏህም እነዚህን የዝሆን ባለቤቶችን ተንኮል በጥፋት ውስጥ ከንቱ አደረገ፦
105፥1 በዝሆኑ ባለቤቶች ጌታህ እንዴት እንደሠራ አላወቅህምን? أَلَمْ تَرَ كَيْفَ فَعَلَ رَبُّكَ بِأَصْحَابِ الْفِيلِ
105፥2 ተንኮላቸውን በጥፋት ውስጥ ከንቱ አላደረገምን? أَلَمْ يَجْعَلْ كَيْدَهُمْ فِي تَضْلِيلٍ
አምላካችን አሏህ በእነርሱም ላይ ከተጠበሰ ጭቃ በኾነ ድንጋይ ማለትም በሸክላ”brick” የሚወረውሩባቸው መንጎች የኾኑን አዕዋፍን በመላክ ቅጠሉ እንደ ተበላ አዝመራም አደረጋቸው፦
105፥3 “በእነርሱም ላይ መንጎች የኾኑን አዕዋፍን ላከ”፡፡ وَأَرْسَلَ عَلَيْهِمْ طَيْرًا أَبَابِيلَ
105፥4 “ከተጠበሰ ጭቃ በኾነ ድንጋይ የምትወረውርባቸው የኾነችን አዕዋፍ”፡፡ تَرْمِيهِم بِحِجَارَةٍ مِّن سِجِّيلٍ
105፥5 “ቅጠሉ እንደ ተበላ አዝመራም አደረጋቸው”፡፡ فَجَعَلَهُمْ كَعَصْفٍ مَّأْكُولٍ
ከዚያ ጊዜ ጀምሮ ቁረይሾች ጊዜ ሲቆጥሩ እራሱ “ዓሙል ፊል” عامُ الْفِيلِ ማለትም “የዝሆን ዓመት” እያሉ ነበር።
የአብረሃህ አል አሽረም አድራጎት ይህን ያህል ከተወገዘ ዘንዳ ከዕባን አስመስሎ ሠርቶ "ከዕባህ ነው" ማለት ከላይ እንዳየነው ዋጋ ያስከፍላል፥ የአላባ ሙሥሊሞች በቅንነት ኢሥላምን ለማስተዋወቅ ብለው የከዕባህ ቅርጽ በጊዜአዊነት መሥራታቸው ለማስተማሪያነት እንጂ በቋሚነት መሥጂድ ለማድረግ አልነበረም። ስህተታቸውን በትህትና ከማረም ይልቅ በስድብ ማጥረግረግ ጉዳዩን እንዲጦዝ እና እልክ መግባባት አርጎታል፥ ይህ ደግሞ አሏህ አደራ እንድንባባል ካዘዘን ጋር ይጋጫል፦
90፥17 ከዚያም ከነዚያ ከአመኑትና በመታገስ አደራ ከተባባሉት፣ በማዘንም አደራ ከተባባሉት ሰዎች አልኾነም፡፡ ثُمَّ كَانَ مِنَ الَّذِينَ آمَنُوا وَتَوَاصَوْا بِالصَّبْرِ وَتَوَاصَوْا بِالْمَرْحَمَةِ
103፥3 እነዚያ ያመኑትና መልካሞችን የሠሩት፣ በእውነትም አደራ የተባባሉት፣ በመታገስም አደራ የተባባሉት ብቻ ሲቀሩ፡፡ إِلَّا الَّذِينَ آمَنُوا وَعَمِلُوا الصَّالِحَاتِ وَتَوَاصَوْا بِالْحَقِّ وَتَوَاصَوْا بِالصَّبْرِ
አንድ ሰው ሐቅ ስለያዘ ብቻ ሐቁን ለማስተላለፍ ስድብ መፍትሄ አይሆንም፥ ከዚያ ይልቅ አደራ መባባል በሐቅ ብቻ ሳይሆን በትግስት እና በማዘንም ጭምር ቢሆን የተሳሳተው ሰው ከስህተቱ ሊመለስ ዝግጁ ይሆናል። ኢሻሏህ ጠርዝ ይዘው የሚጠዛጠዙ እነዚህ ሁለቱም ጽንፎች ከዚህ ድርጊታቸው እንደሚታረሙ ተስፋ አለኝ!
አምላካችን አሏህ ለሁላችንም ሂዳያህ ይስጠን! አሚን።
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
105፥1 በዝሆኑ ባለቤቶች ጌታህ እንዴት እንደሠራ አላወቅህምን? أَلَمْ تَرَ كَيْفَ فَعَلَ رَبُّكَ بِأَصْحَابِ الْفِيلِ
"ከዕባህ" كَعْبَة ማለት "አንኳር“cube" ማለት ሲሆን አንኳር "ምልዓት" ነው፥ ምልአት ባለ ሦስት ቅጥ ነው። ይህም ቁመት፣ ርዝምት እና ስፋት ነው፥ አምላካችን አሏህ ከዕባን የተቀደሰ ወይም የተከበረ ቤት አደረገው፦
5፥97 "ከዕባን የተከበረውን ቤት፣ ክልክል የኾነውንም ወር፣ መስዋዕቱንና ባለ ምልክቶቹንም መንጋዎች አላህ ለሰዎች መቋቋሚያ አደረገ፡፡ جَعَلَ ٱللَّهُ ٱلْكَعْبَةَ ٱلْبَيْتَ ٱلْحَرَامَ قِيَٰمًۭا لِّلنَّاسِ وَٱلشَّهْرَ ٱلْحَرَامَ وَٱلْهَدْىَ وَٱلْقَلَٰٓئِدَ
3፥96 ለሰዎች መጀመሪያ የተኖረዉ ቤት ቡሩክ እና ለዓለማት ሁሉ መመሪያ ሲኾን ያ በበካህ ያለው ነው። إِنَّ أَوَّلَ بَيْتٍۢ وُضِعَ لِلنَّاسِ لَلَّذِى بِبَكَّةَ مُبَارَكًۭا وَهُدًۭى لِّلْعَٰلَمِينَ
ከዕባህ ለሰዎች መጀመሪያ የተኖረዉ ቤት ቡሩክ እና ለዓለማት ሁሉ መመሪያ ሆኖ ሳለ የአክሱም መንግሥት ንጉሥ ካሌብ እስከ የመን ድረስ ይገዛ ነበር። በጃሂሊያህ ጊዜ የካሌብ ጦር መሪ አብረሃህ አል አሽረም በ 527 ድኅረ ልደት በየመን ውስጥ ከአሏህ ቤት ጋር በማፎካከር ቤተክርስቲያን አሠርቷል፦
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 63, ሐዲስ 49
ጀሪር ኢብኑ ዐብደሏህ እንደተረከው፦ “በዘመነ-ጃሂሊያ ዙል-ኸለሷህ የሚባል ቤት ነበረ፥ የቀኝ ከዕባህ ወይም የግራ ከዕባህ ተብሎ ይጠራ ነበር”። عَنْ جَرِيرِ بْنِ عَبْدِ اللَّهِ، قَالَ كَانَ فِي الْجَاهِلِيَّةِ بَيْتٌ يُقَالَ لَهُ ذُو الْخَلَصَةِ، وَكَانَ يُقَالُ لَهُ الْكَعْبَةُ الْيَمَانِيَةُ، أَوِ الْكَعْبَةُ الشَّأْمِيَّةُ
“ኸለሷህ” خَلَصَة ማለት “ቀሊሥ” قَلِسْ ማለት ነው፥ “ቀሊሥ” ከግሪኩ ኮይኔ “ኤክሌሲያ” εκκλεσια የመጣ ሲሆን በተለምዶ “ቤተ ክርስቲያን” ይባል እንጂ “ጉባኤ” “ማኅበር” “ተጠርተው የወጡ” ማለት ነው። ይህንን ቤት ከከዕባ ጋር ለማመሳሰል “አል ከዕበቱል የማኒያህ” الْكَعْبَةُ الْيَمَانِيَة ወይም “አል ከዕበቱሽ ሸእሚያህ” الْكَعْبَةُ الشَّأْمِيَّة ብሎታል። በ 570 ድኅረ ልደት "አብረሃህ አል አሽረም" أَبْرَهَة ٱلْأَشْرَم እና ጭፍሮቹ የአሏህ ቤት ለማፍረስ በዝሆን ጋልበው ወደ መካ መጡ፥ አሏህም እነዚህን የዝሆን ባለቤቶችን ተንኮል በጥፋት ውስጥ ከንቱ አደረገ፦
105፥1 በዝሆኑ ባለቤቶች ጌታህ እንዴት እንደሠራ አላወቅህምን? أَلَمْ تَرَ كَيْفَ فَعَلَ رَبُّكَ بِأَصْحَابِ الْفِيلِ
105፥2 ተንኮላቸውን በጥፋት ውስጥ ከንቱ አላደረገምን? أَلَمْ يَجْعَلْ كَيْدَهُمْ فِي تَضْلِيلٍ
አምላካችን አሏህ በእነርሱም ላይ ከተጠበሰ ጭቃ በኾነ ድንጋይ ማለትም በሸክላ”brick” የሚወረውሩባቸው መንጎች የኾኑን አዕዋፍን በመላክ ቅጠሉ እንደ ተበላ አዝመራም አደረጋቸው፦
105፥3 “በእነርሱም ላይ መንጎች የኾኑን አዕዋፍን ላከ”፡፡ وَأَرْسَلَ عَلَيْهِمْ طَيْرًا أَبَابِيلَ
105፥4 “ከተጠበሰ ጭቃ በኾነ ድንጋይ የምትወረውርባቸው የኾነችን አዕዋፍ”፡፡ تَرْمِيهِم بِحِجَارَةٍ مِّن سِجِّيلٍ
105፥5 “ቅጠሉ እንደ ተበላ አዝመራም አደረጋቸው”፡፡ فَجَعَلَهُمْ كَعَصْفٍ مَّأْكُولٍ
ከዚያ ጊዜ ጀምሮ ቁረይሾች ጊዜ ሲቆጥሩ እራሱ “ዓሙል ፊል” عامُ الْفِيلِ ማለትም “የዝሆን ዓመት” እያሉ ነበር።
የአብረሃህ አል አሽረም አድራጎት ይህን ያህል ከተወገዘ ዘንዳ ከዕባን አስመስሎ ሠርቶ "ከዕባህ ነው" ማለት ከላይ እንዳየነው ዋጋ ያስከፍላል፥ የአላባ ሙሥሊሞች በቅንነት ኢሥላምን ለማስተዋወቅ ብለው የከዕባህ ቅርጽ በጊዜአዊነት መሥራታቸው ለማስተማሪያነት እንጂ በቋሚነት መሥጂድ ለማድረግ አልነበረም። ስህተታቸውን በትህትና ከማረም ይልቅ በስድብ ማጥረግረግ ጉዳዩን እንዲጦዝ እና እልክ መግባባት አርጎታል፥ ይህ ደግሞ አሏህ አደራ እንድንባባል ካዘዘን ጋር ይጋጫል፦
90፥17 ከዚያም ከነዚያ ከአመኑትና በመታገስ አደራ ከተባባሉት፣ በማዘንም አደራ ከተባባሉት ሰዎች አልኾነም፡፡ ثُمَّ كَانَ مِنَ الَّذِينَ آمَنُوا وَتَوَاصَوْا بِالصَّبْرِ وَتَوَاصَوْا بِالْمَرْحَمَةِ
103፥3 እነዚያ ያመኑትና መልካሞችን የሠሩት፣ በእውነትም አደራ የተባባሉት፣ በመታገስም አደራ የተባባሉት ብቻ ሲቀሩ፡፡ إِلَّا الَّذِينَ آمَنُوا وَعَمِلُوا الصَّالِحَاتِ وَتَوَاصَوْا بِالْحَقِّ وَتَوَاصَوْا بِالصَّبْرِ
አንድ ሰው ሐቅ ስለያዘ ብቻ ሐቁን ለማስተላለፍ ስድብ መፍትሄ አይሆንም፥ ከዚያ ይልቅ አደራ መባባል በሐቅ ብቻ ሳይሆን በትግስት እና በማዘንም ጭምር ቢሆን የተሳሳተው ሰው ከስህተቱ ሊመለስ ዝግጁ ይሆናል። ኢሻሏህ ጠርዝ ይዘው የሚጠዛጠዙ እነዚህ ሁለቱም ጽንፎች ከዚህ ድርጊታቸው እንደሚታረሙ ተስፋ አለኝ!
አምላካችን አሏህ ለሁላችንም ሂዳያህ ይስጠን! አሚን።
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
ስለ ሸዋል ይህንን ያንብቡ እና ለሌሎች ወንድሞች እና እኅቶች ሼር ያርጉ፦ https://tttttt.me/Wahidcom/2757
ተሥሊስ
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
4፥171 «ሦስት ነው» አትበሉ! ተከልከሉ! ለእናንተ የተሻለ ይኾናልና፡፡ አላህ አንድ አምላክ ብቻ ነው፡፡ وَلَا تَقُولُوا ثَلَاثَةٌ ۚ انتَهُوا خَيْرًا لَّكُمْ ۚ إِنَّمَا اللَّهُ إِلَـٰهٌ وَاحِدٌ
"መለኮት" ማለት "አምላክነት" ማለት ነው፥ "እግዚአብሔር" የሚለው ቃል ደግሞ በግሪክ "ቴዎስ" θεός ሲሆን "አምላክ"God" ማለት ነው። በጥቅሉ "መለኮት" "እግዚአብሔር" "አምላክ" ተመሳሳይ ነገር ለማሳየት የመጣ ሲሆን በሥላሴ እሳቤ፦
1. ወላዲ ማንነት አምላክ፣
2. ተወላዲ ማንነት አምላክ፣
3. ሰራጺ ማንነት አምላክ
ከሆነ ወላዲ አምላክ፣ ተወላዲ አምላክ፣ ሰራጺ አምላክ አለ ማለት ነው፦
ሰይፈ ሥላሴ ዘሰኞ ምዕራፍ 2 ቁጥር 42
"በጽርሐ አርያም ለሚኖር ልዩ ሦስት ለሚሆን አምላክ ሰላምታ ይገባል"
"ልዩ ሦስት ለሚሆን አምላክ" የሚለው ይሰመርበት! "ሦስት ለሚሆን አምላክ" በግዕዙ "ሥሉስ አምላክ" ነው። ወላዲ አምላክ "አብ" ተወላዲ አምላክ እና ሰራጺ አምላክ ካልሆነ፣ ተወላዲ አምላክ "ወልድ" ወላዲ አምላክ እና ሰራጺ አምላክ ካልሆነ፣ ሰራጺ አምላክ "መንፈስ ቅዱስ" ወላዲ አምላክ እና ተወላዲ አምላክ ካልሆነ ስንት አምላክ አለ? መልሱ ሦስት አምላክ ይሆናል። ምክንያቱም ወላዲ አምላክ፣ ተወላዲ አምላክ፣ ሰራጺ አምላክ ሦስት ነው፥ እነርሱም፦ በግዕዙ "ሦሉስ አምላክ" ሲሉ ትርጉሙ "ሦስት አምላክ" ማለት ነው፦
ሰይፈ ሥላሴ ዘረቡዕ ምዕራፍ 4 ቁጥር 31
“መለኮት በአካል ሦስት ሲሆን በባሕርይ አንድ ነው”።
"መለኮት በአካል ሦስት ሲሆን" የሚለው ይሰመርበት! "መለኮት በአካል ሦስት ነው" ማለት የጤንነት ነውን? አምላክ አባት(እግዚአብሔር አብ)፣ አምላክ ልጅ(እግዚአብሔር ወልድ)፣ አምላክ መንፈስ ቅዱስ(እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ) የሚባሉ በአካል ሦስት አምላክ"tritheism" ናቸው። አምላክነት ሦስቱ አካላት የሚጋሩት ባሕርይ እንጂ "ማንነት ነው" ብለው አያምኑም፦
ሰይፈ ሥላሴ ዘሐሙስ ምዕራፍ 5 ቁጥር 17
"ሦስት የእሳት ባሕርይ ነገር ግን አንድ ብርሃን ነው"።
"ሦስት የእሳት ባሕርይ" የሚለው ይሰመርበት! "ሦስት የእሳት ባሕርይ" ካለ አንድ ብርሃን ሳይሆን ሦስት ብርሃናት ናቸው፦
ሃይማኖተ አበው ምዕራፍ 10 ቁጥር 6
"ዕውቀትን የሚገልጹ ብርሃናት ናቸው"።
"ብርሃናት" የብርሃን ብዙ ቁጥር ነው፥ አንዱ ብርሃን አብ ሁለቱ ብርሃናትን ወልድ እና መንፈስ ቅዱስን አስገኘ ማለት የጤንነት አይደለም፦
ሃይማኖተ አበው ምዕራፍ 10 ቁጥር 12
"አብ ብርሃን ነው፣ ከአብ የተወለደ ቃሉ ወልድ ከብርሃን የተገኘ ብርሃን ነው፣ እንዲሁ ከአብ የሠረፀ መንፈስ ቅዱስም ከብርሃን የተገኘ ብርሃን ነው"።
ከአንዱ ብርሃን ከአብ ወልድ የሚባል ብርሃን በመወለድ ተገኘ እና ከአንዱ ብርሃን ከአብ መንፈስ ቅዱስ የሚባል ብርሃን በመሥረፅ ተገኘ የሚል ትምህርት በግልጽ "ሦስት ፀሐይ" ብለው አስቀምጠዋል፦
ሰይፈ ሥላሴ ዘረቡዕ ምዕራፍ 4 ቁጥር 21
"ሦስት ፀሐይ አንድ ብርሃን.. ነው"።
ሰይፈ ሥላሴ ዘሐሙስ ምዕራፍ 5 ቁጥር 21
"ሦስት የብርሃን አዕማድ በመጠን ግን..አንድ ነው"።
ዶክተር ዛኪር፣ ዶክተር ቢላል እና ዶክተር ፊሊፕ ሦስት ዶክተር እንጂ አንድ ዶክተር አይደሉም፥ ግን አንድ ዶክትሬት ይጋራሉ። በተመሳዳይ እግዚአብሔር አብ፣ እግዚአብሔር ወልድ እና እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ሦስት እግዚአብሔር እንጂ አንድ እግዚአብሔር አይደሉም፥ ግን አንድ እግዚአብሔርነትን ይጋራሉ፦
ሰይፈ ሥላሴ ዘማክሰኞ ምዕራፍ 3 ቁጥር 21
"ቅዱስ፣ ቅዱስ፣ ቅዱስ እግዚአብሔር ሦስት ሲሆን አንድ፥ አንድ ሲሆን ሦስት የሚሆን እርሱ አንድ ቅዱስ ነው"።
"እግዚአብሔር ሦስት ሲሆን" የሚለው ይሰመርበት! "አንድ ቅዱስ ነው" ካላችሁ በኃላ "ሥሉስ ቅዱስ" ማለትም "ሦስት ቅዱስ" ማለታችሁ የጤና ነውን? "ቅድስት ሥላሴ" ማለትም "ቅዱሶች ሦስነት" ለምን ትላላችሁ? በነገራችን ላይ "ቅድስት" የሚለው ቃል "ቅዱሳን" "ቅዱሶች" የሚለውን ለመተካት የሚጠቀሙበት ነው፦
ሃይማኖተ አበው ምዕራፍ 82 ቁጥር 14
"ሥሉስ ቅዱስ ያልተፈጠሩ ናቸው"
"ሦስት ቅዱስ" "አንድ ቅዱስ" እርስ በእርሱ ይጋጫል። እንደ እናንተ ትምህርት አምላክ ከማርያም ሲወለድ የተወለደው አንዱ አምላክ ነው ወይስ ሁለተኛው ልጅ የሆነ አምላክ? አንዱ አምላክ ከሆነ አብ እና መንፈስ ቅዱስ አብረው ተወልደዋል? ምክንያቱም ማርያም የመለኮት እናት ናት ስለሚል፦
ሰይፈ ሥላሴ ዘእሑድ ምዕራፍ 8 ቁጥር 73
"በመለኮት እናት በድንግል ማርያም"።
ሁለተኛው ልጅ የሆነው አምላክ ከሆነ ያልተወለዱ ሁለት አባት እና መንፈስ ቅዱስ የሆኑ አምላክ አሉን? ከማርያም የተነሳው ሥጋ መለኮትን ገንዘብ ሲያደርግ ሙሉ መለኮትን ነው ወይስ የአብ ተወላዲ መለኮትን?
ያለው አማራጭ ሦስት አምላክ ስለሆነ በግልጽ "አምላካችን ያለ መለየት ሦስት ነው" ብለው አርፈውታል፦
ሃይማኖተ አበው ምዕራፍ 99 ቁጥር 11
“አምላካችን ያለ መለየት ሦስት ነው”።
"ኡሲያ" οὐσία የሚለው ቃል "ሃልዎት" "ኑባሬ" "ህላዌ"essence" የሚል ትርጉም አለው፥ "በአካል ሦስት ህላዌ" ማለት የጤንነት አይደለም፦
ሃይማኖተ አበው ምዕራፍ 34 ቁጥር 22
“በአካል ሦስት "ህላዌ" በመለኮት አንድ ህላዌ ነው”።
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
4፥171 «ሦስት ነው» አትበሉ! ተከልከሉ! ለእናንተ የተሻለ ይኾናልና፡፡ አላህ አንድ አምላክ ብቻ ነው፡፡ وَلَا تَقُولُوا ثَلَاثَةٌ ۚ انتَهُوا خَيْرًا لَّكُمْ ۚ إِنَّمَا اللَّهُ إِلَـٰهٌ وَاحِدٌ
"መለኮት" ማለት "አምላክነት" ማለት ነው፥ "እግዚአብሔር" የሚለው ቃል ደግሞ በግሪክ "ቴዎስ" θεός ሲሆን "አምላክ"God" ማለት ነው። በጥቅሉ "መለኮት" "እግዚአብሔር" "አምላክ" ተመሳሳይ ነገር ለማሳየት የመጣ ሲሆን በሥላሴ እሳቤ፦
1. ወላዲ ማንነት አምላክ፣
2. ተወላዲ ማንነት አምላክ፣
3. ሰራጺ ማንነት አምላክ
ከሆነ ወላዲ አምላክ፣ ተወላዲ አምላክ፣ ሰራጺ አምላክ አለ ማለት ነው፦
ሰይፈ ሥላሴ ዘሰኞ ምዕራፍ 2 ቁጥር 42
"በጽርሐ አርያም ለሚኖር ልዩ ሦስት ለሚሆን አምላክ ሰላምታ ይገባል"
"ልዩ ሦስት ለሚሆን አምላክ" የሚለው ይሰመርበት! "ሦስት ለሚሆን አምላክ" በግዕዙ "ሥሉስ አምላክ" ነው። ወላዲ አምላክ "አብ" ተወላዲ አምላክ እና ሰራጺ አምላክ ካልሆነ፣ ተወላዲ አምላክ "ወልድ" ወላዲ አምላክ እና ሰራጺ አምላክ ካልሆነ፣ ሰራጺ አምላክ "መንፈስ ቅዱስ" ወላዲ አምላክ እና ተወላዲ አምላክ ካልሆነ ስንት አምላክ አለ? መልሱ ሦስት አምላክ ይሆናል። ምክንያቱም ወላዲ አምላክ፣ ተወላዲ አምላክ፣ ሰራጺ አምላክ ሦስት ነው፥ እነርሱም፦ በግዕዙ "ሦሉስ አምላክ" ሲሉ ትርጉሙ "ሦስት አምላክ" ማለት ነው፦
ሰይፈ ሥላሴ ዘረቡዕ ምዕራፍ 4 ቁጥር 31
“መለኮት በአካል ሦስት ሲሆን በባሕርይ አንድ ነው”።
"መለኮት በአካል ሦስት ሲሆን" የሚለው ይሰመርበት! "መለኮት በአካል ሦስት ነው" ማለት የጤንነት ነውን? አምላክ አባት(እግዚአብሔር አብ)፣ አምላክ ልጅ(እግዚአብሔር ወልድ)፣ አምላክ መንፈስ ቅዱስ(እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ) የሚባሉ በአካል ሦስት አምላክ"tritheism" ናቸው። አምላክነት ሦስቱ አካላት የሚጋሩት ባሕርይ እንጂ "ማንነት ነው" ብለው አያምኑም፦
ሰይፈ ሥላሴ ዘሐሙስ ምዕራፍ 5 ቁጥር 17
"ሦስት የእሳት ባሕርይ ነገር ግን አንድ ብርሃን ነው"።
"ሦስት የእሳት ባሕርይ" የሚለው ይሰመርበት! "ሦስት የእሳት ባሕርይ" ካለ አንድ ብርሃን ሳይሆን ሦስት ብርሃናት ናቸው፦
ሃይማኖተ አበው ምዕራፍ 10 ቁጥር 6
"ዕውቀትን የሚገልጹ ብርሃናት ናቸው"።
"ብርሃናት" የብርሃን ብዙ ቁጥር ነው፥ አንዱ ብርሃን አብ ሁለቱ ብርሃናትን ወልድ እና መንፈስ ቅዱስን አስገኘ ማለት የጤንነት አይደለም፦
ሃይማኖተ አበው ምዕራፍ 10 ቁጥር 12
"አብ ብርሃን ነው፣ ከአብ የተወለደ ቃሉ ወልድ ከብርሃን የተገኘ ብርሃን ነው፣ እንዲሁ ከአብ የሠረፀ መንፈስ ቅዱስም ከብርሃን የተገኘ ብርሃን ነው"።
ከአንዱ ብርሃን ከአብ ወልድ የሚባል ብርሃን በመወለድ ተገኘ እና ከአንዱ ብርሃን ከአብ መንፈስ ቅዱስ የሚባል ብርሃን በመሥረፅ ተገኘ የሚል ትምህርት በግልጽ "ሦስት ፀሐይ" ብለው አስቀምጠዋል፦
ሰይፈ ሥላሴ ዘረቡዕ ምዕራፍ 4 ቁጥር 21
"ሦስት ፀሐይ አንድ ብርሃን.. ነው"።
ሰይፈ ሥላሴ ዘሐሙስ ምዕራፍ 5 ቁጥር 21
"ሦስት የብርሃን አዕማድ በመጠን ግን..አንድ ነው"።
ዶክተር ዛኪር፣ ዶክተር ቢላል እና ዶክተር ፊሊፕ ሦስት ዶክተር እንጂ አንድ ዶክተር አይደሉም፥ ግን አንድ ዶክትሬት ይጋራሉ። በተመሳዳይ እግዚአብሔር አብ፣ እግዚአብሔር ወልድ እና እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ሦስት እግዚአብሔር እንጂ አንድ እግዚአብሔር አይደሉም፥ ግን አንድ እግዚአብሔርነትን ይጋራሉ፦
ሰይፈ ሥላሴ ዘማክሰኞ ምዕራፍ 3 ቁጥር 21
"ቅዱስ፣ ቅዱስ፣ ቅዱስ እግዚአብሔር ሦስት ሲሆን አንድ፥ አንድ ሲሆን ሦስት የሚሆን እርሱ አንድ ቅዱስ ነው"።
"እግዚአብሔር ሦስት ሲሆን" የሚለው ይሰመርበት! "አንድ ቅዱስ ነው" ካላችሁ በኃላ "ሥሉስ ቅዱስ" ማለትም "ሦስት ቅዱስ" ማለታችሁ የጤና ነውን? "ቅድስት ሥላሴ" ማለትም "ቅዱሶች ሦስነት" ለምን ትላላችሁ? በነገራችን ላይ "ቅድስት" የሚለው ቃል "ቅዱሳን" "ቅዱሶች" የሚለውን ለመተካት የሚጠቀሙበት ነው፦
ሃይማኖተ አበው ምዕራፍ 82 ቁጥር 14
"ሥሉስ ቅዱስ ያልተፈጠሩ ናቸው"
"ሦስት ቅዱስ" "አንድ ቅዱስ" እርስ በእርሱ ይጋጫል። እንደ እናንተ ትምህርት አምላክ ከማርያም ሲወለድ የተወለደው አንዱ አምላክ ነው ወይስ ሁለተኛው ልጅ የሆነ አምላክ? አንዱ አምላክ ከሆነ አብ እና መንፈስ ቅዱስ አብረው ተወልደዋል? ምክንያቱም ማርያም የመለኮት እናት ናት ስለሚል፦
ሰይፈ ሥላሴ ዘእሑድ ምዕራፍ 8 ቁጥር 73
"በመለኮት እናት በድንግል ማርያም"።
ሁለተኛው ልጅ የሆነው አምላክ ከሆነ ያልተወለዱ ሁለት አባት እና መንፈስ ቅዱስ የሆኑ አምላክ አሉን? ከማርያም የተነሳው ሥጋ መለኮትን ገንዘብ ሲያደርግ ሙሉ መለኮትን ነው ወይስ የአብ ተወላዲ መለኮትን?
ያለው አማራጭ ሦስት አምላክ ስለሆነ በግልጽ "አምላካችን ያለ መለየት ሦስት ነው" ብለው አርፈውታል፦
ሃይማኖተ አበው ምዕራፍ 99 ቁጥር 11
“አምላካችን ያለ መለየት ሦስት ነው”።
"ኡሲያ" οὐσία የሚለው ቃል "ሃልዎት" "ኑባሬ" "ህላዌ"essence" የሚል ትርጉም አለው፥ "በአካል ሦስት ህላዌ" ማለት የጤንነት አይደለም፦
ሃይማኖተ አበው ምዕራፍ 34 ቁጥር 22
“በአካል ሦስት "ህላዌ" በመለኮት አንድ ህላዌ ነው”።
በእርግጥም "ሦስት ለሚሆን አምላክ፣ ሦስት ቅዱስ፣ ሦስት ልዑላን፣ ሦስት ጌቶች፣ ሦስት ነገሥታት፣ ሦስት ገዢዎች" ብላችሁ ካስተማራችሁ በግልጽ መድብለ አማልክታውያን ናችሁ፦
፨ሰይፈ ሥላሴ ዘሐሙስ ምዕራፍ 5 ቁጥር 22-23
“ሦስት ልዑላን ገዢዎች፥ ሦስት ጌቶች ናቸው”።
፨ ሰይፈ ሥላሴ ዘሐሙስ ምዕራፍ 5 ቁጥር 26
“ሦስት ነገሥታት አንድ አገዛዝ ናቸው”።
፨ ሰይፈ ሥላሴ ዘረቡዕ ምዕራፍ 4 ቁጥር 54
“እነዚህ ገዢዎች በገጽ ሦስት በፈቃድ አንድ ናቸው”።
"ገጽ" ማለት "ፊት" ማለት ነው፥ ባለ ሦስት ፊት አምላክ የዐረማውያን እንጂ የአብርሃም አምላክ በፍጹም አይደለም፦
ሰይፈ ሥላሴ ዘሐሙስ ምዕራፍ 5 ቁጥር 24
"ሦስት ገጽ አንድ አመለካከት ናቸው"።
ሥላሴ አካላቸው የተለያዩ ከሆኑ አካላቸው አንድ ዓይነት ወይስ የተለያየ? አንድ ዓይነት ከሆነ ምን ዓይነት አንድ ዓይነት? ከተለየስ ምን ዓይነት የተለየ አካል ነው? ገጽታቸውን ሦስት አርጎ ያለያየ ምን ዓይነት ገጽታ ይሆን? "መለኮት ሦስትም አንድም ነው" ማለት የጤና አይደለም፦
ሰይፈ ሥላሴ ዘቀዳሚት ምዕራፍ 7 ቁጥር 68
"ለመለኮት ሦስትነት ምስጋና ይገባል"።
ሰይፈ ሥላሴ ዘቀዳሚት ምዕራፍ 7 ቁጥር 69
"ለመለኮት አንድነት ምስጋና ይገባል"።
ገድለ ተክለ ሃይማኖት 60(61)፥12
"የመለኮት ሦስትነት መቆፈሪያ ልቡን በኮሰተረው እና በቆፈረው ጊዜ"።
በምድር ላይ ያለው እያንዳንዱ ሰው የራሱ ገጽ ያለው ሲሆን በስም፣ በአካል፣ በግብር ስምንት ቢልዮን ነው፥ ግን የሁሉም ምንነት አንድ ምንነት ስለሆነ ስምንት ቢልዮን ሰው አንድ ሰው አይባልም። ስምንት ቢልዮን ሰዎች ያሰኘው በማንነት እከሌ እየተባለ ስለሚለያይ ነው፥ አምላክ በማንነት እከሌ እየተባለ በስም፣ በአካል፣ በግብር ከተለያየ አንድ ሳይሆን ብዙ ነው። በሦስት ፊቶች የተለያየ መለኮት፣ ጌታ፣ ንጉሥ፣ አምላክ እና ፈጣሪ መድብለ አማልክት እንጂ ሌላ አይደለም፦
ሰይፈ ሥላሴ ዘእሑድ ምዕራፍ 8 ቁጥር 41
"ሥስት የምትሆን ጌታዬ፣ ንጉሤ፣ አምላኬ፣ ፈጣሪዬ ሆይ! ለአዳራሽህ መብራት ለመመላለሻህም ፀሐይ አትፈልግም"።
መልክአ ሥላሴ ቁጥር 39
“ሥሉስ ቅዱስ ሆይ! የአደም እና የሔዋን "ፈጣሪዎቻቸው" እንደመሆናችሁ የምርኮኞች ነጻ አውጪ የሆነ ኃይላችሁ የጣዖታትን ሐሰተኝነት አጋለጠ"።
ሥላሴ "ፈጣሪዎች" ከተባሉ ስንት ፈጣሪ ሊኖር ነው? እነርሱም በድፍረት፦ "ኤሎሂም" ማለት "አማልክት" ማለት ነውና "አማልክት" የተባለው ሥላሴን አምልካች ነው" በማለታቸው ሥላሴ "አማልክት" መሆናቸው በግልጽ ነግረውናል። ሳያቅማሙም "ሦስት በአንድ የሆነ አምላክ"Triune God" ይሉታል፣ በአገራችን "ሥላሴ" ማለት "ሦስትነት" ማለት ነው፣ በዐረብ ክርስቲያኖች ዘንድ "ተሥሊስ" تَسْلِيث ይሉታል። በፕሮቴስታንት ዘንድ ደግሞ፦ "አብ እራሱን የቻለ አእምሮ፣ ፈቃድ እና ስሜት አለው፣ ወልድ እራሱን የቻለ አእምሮ፣ ፈቃድ እና ስሜት አለው፣ መንፈስ ቅዱስ እራሱን የቻለ አእምሮ፣ ፈቃድ እና ስሜት አለው" ይላሉ፥ ይህ በኦርቶዶክስ ሦስት አማልክት ነው፦
መጽሐፈ ሜላድ 6፥38 ሦስት ልብ፣ ሦስት ቃል፣ ሦስት እስትንፋስ የሚል ግን ሦስት አማልክት አመለከ"።
"ለበወ" ማለት "አወቀ" ማለት ከሆነ ሦስቱ ማንንነቶች የየራሳቸው ዕውቀት ካላቸው እና እርስ በእርስ የሚነጋገሩ ከሆነ ሦስት ልብ ይሆናል፥ በፕሮቴስታንት ልክ እንደ አርጌናሳውያን አብ ወልድን እና መንፈስ ቅዱስን የሚገዛቸው አስተዳዳሪያቸው ነው፦
1ኛ ቆሮንቶስ 15፥28 አዲሱ መደበኛ ትርጉም ማብራሪያ፦ "ወልድ ለአብ የሚገዛው በአስተዳደር ረገድ ሲሆን..በሥላሴ አካላት መካከል አብ የበላይ አስተዳዳሪ ነው"
እንግዲህ ሥላሴ ሰው በማመኑ የሚድንበት እና በመካዱ የሚጠፋበት አንቀጸ እምነት ቢሆን ኖሮ ነቢያት እና ሐዋርያት በግልጽ ልክ እንደ ተውሒድ ያስቀምጡልን ነበር። ነገር ግን በግልጠተ መለኮት ውስጥ የሥላሴ አሳቡ ስለሌለ «ሦስት ነው» አትበሉ! ተከልከሉ! ለእናንተ የተሻለ ይኾናልና፡፡ አሏህ አንድ አምላክ ብቻ ነው፦
4፥171 «ሦስት ነው» አትበሉ! ተከልከሉ! ለእናንተ የተሻለ ይኾናልና፡፡ አላህ አንድ አምላክ ብቻ ነው፡፡ وَلَا تَقُولُوا ثَلَاثَةٌ ۚ انتَهُوا خَيْرًا لَّكُمْ ۚ إِنَّمَا اللَّهُ إِلَـٰهٌ وَاحِدٌ
አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛን ጽናቱን ይስጠን! አሚን።
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
፨ሰይፈ ሥላሴ ዘሐሙስ ምዕራፍ 5 ቁጥር 22-23
“ሦስት ልዑላን ገዢዎች፥ ሦስት ጌቶች ናቸው”።
፨ ሰይፈ ሥላሴ ዘሐሙስ ምዕራፍ 5 ቁጥር 26
“ሦስት ነገሥታት አንድ አገዛዝ ናቸው”።
፨ ሰይፈ ሥላሴ ዘረቡዕ ምዕራፍ 4 ቁጥር 54
“እነዚህ ገዢዎች በገጽ ሦስት በፈቃድ አንድ ናቸው”።
"ገጽ" ማለት "ፊት" ማለት ነው፥ ባለ ሦስት ፊት አምላክ የዐረማውያን እንጂ የአብርሃም አምላክ በፍጹም አይደለም፦
ሰይፈ ሥላሴ ዘሐሙስ ምዕራፍ 5 ቁጥር 24
"ሦስት ገጽ አንድ አመለካከት ናቸው"።
ሥላሴ አካላቸው የተለያዩ ከሆኑ አካላቸው አንድ ዓይነት ወይስ የተለያየ? አንድ ዓይነት ከሆነ ምን ዓይነት አንድ ዓይነት? ከተለየስ ምን ዓይነት የተለየ አካል ነው? ገጽታቸውን ሦስት አርጎ ያለያየ ምን ዓይነት ገጽታ ይሆን? "መለኮት ሦስትም አንድም ነው" ማለት የጤና አይደለም፦
ሰይፈ ሥላሴ ዘቀዳሚት ምዕራፍ 7 ቁጥር 68
"ለመለኮት ሦስትነት ምስጋና ይገባል"።
ሰይፈ ሥላሴ ዘቀዳሚት ምዕራፍ 7 ቁጥር 69
"ለመለኮት አንድነት ምስጋና ይገባል"።
ገድለ ተክለ ሃይማኖት 60(61)፥12
"የመለኮት ሦስትነት መቆፈሪያ ልቡን በኮሰተረው እና በቆፈረው ጊዜ"።
በምድር ላይ ያለው እያንዳንዱ ሰው የራሱ ገጽ ያለው ሲሆን በስም፣ በአካል፣ በግብር ስምንት ቢልዮን ነው፥ ግን የሁሉም ምንነት አንድ ምንነት ስለሆነ ስምንት ቢልዮን ሰው አንድ ሰው አይባልም። ስምንት ቢልዮን ሰዎች ያሰኘው በማንነት እከሌ እየተባለ ስለሚለያይ ነው፥ አምላክ በማንነት እከሌ እየተባለ በስም፣ በአካል፣ በግብር ከተለያየ አንድ ሳይሆን ብዙ ነው። በሦስት ፊቶች የተለያየ መለኮት፣ ጌታ፣ ንጉሥ፣ አምላክ እና ፈጣሪ መድብለ አማልክት እንጂ ሌላ አይደለም፦
ሰይፈ ሥላሴ ዘእሑድ ምዕራፍ 8 ቁጥር 41
"ሥስት የምትሆን ጌታዬ፣ ንጉሤ፣ አምላኬ፣ ፈጣሪዬ ሆይ! ለአዳራሽህ መብራት ለመመላለሻህም ፀሐይ አትፈልግም"።
መልክአ ሥላሴ ቁጥር 39
“ሥሉስ ቅዱስ ሆይ! የአደም እና የሔዋን "ፈጣሪዎቻቸው" እንደመሆናችሁ የምርኮኞች ነጻ አውጪ የሆነ ኃይላችሁ የጣዖታትን ሐሰተኝነት አጋለጠ"።
ሥላሴ "ፈጣሪዎች" ከተባሉ ስንት ፈጣሪ ሊኖር ነው? እነርሱም በድፍረት፦ "ኤሎሂም" ማለት "አማልክት" ማለት ነውና "አማልክት" የተባለው ሥላሴን አምልካች ነው" በማለታቸው ሥላሴ "አማልክት" መሆናቸው በግልጽ ነግረውናል። ሳያቅማሙም "ሦስት በአንድ የሆነ አምላክ"Triune God" ይሉታል፣ በአገራችን "ሥላሴ" ማለት "ሦስትነት" ማለት ነው፣ በዐረብ ክርስቲያኖች ዘንድ "ተሥሊስ" تَسْلِيث ይሉታል። በፕሮቴስታንት ዘንድ ደግሞ፦ "አብ እራሱን የቻለ አእምሮ፣ ፈቃድ እና ስሜት አለው፣ ወልድ እራሱን የቻለ አእምሮ፣ ፈቃድ እና ስሜት አለው፣ መንፈስ ቅዱስ እራሱን የቻለ አእምሮ፣ ፈቃድ እና ስሜት አለው" ይላሉ፥ ይህ በኦርቶዶክስ ሦስት አማልክት ነው፦
መጽሐፈ ሜላድ 6፥38 ሦስት ልብ፣ ሦስት ቃል፣ ሦስት እስትንፋስ የሚል ግን ሦስት አማልክት አመለከ"።
"ለበወ" ማለት "አወቀ" ማለት ከሆነ ሦስቱ ማንንነቶች የየራሳቸው ዕውቀት ካላቸው እና እርስ በእርስ የሚነጋገሩ ከሆነ ሦስት ልብ ይሆናል፥ በፕሮቴስታንት ልክ እንደ አርጌናሳውያን አብ ወልድን እና መንፈስ ቅዱስን የሚገዛቸው አስተዳዳሪያቸው ነው፦
1ኛ ቆሮንቶስ 15፥28 አዲሱ መደበኛ ትርጉም ማብራሪያ፦ "ወልድ ለአብ የሚገዛው በአስተዳደር ረገድ ሲሆን..በሥላሴ አካላት መካከል አብ የበላይ አስተዳዳሪ ነው"
እንግዲህ ሥላሴ ሰው በማመኑ የሚድንበት እና በመካዱ የሚጠፋበት አንቀጸ እምነት ቢሆን ኖሮ ነቢያት እና ሐዋርያት በግልጽ ልክ እንደ ተውሒድ ያስቀምጡልን ነበር። ነገር ግን በግልጠተ መለኮት ውስጥ የሥላሴ አሳቡ ስለሌለ «ሦስት ነው» አትበሉ! ተከልከሉ! ለእናንተ የተሻለ ይኾናልና፡፡ አሏህ አንድ አምላክ ብቻ ነው፦
4፥171 «ሦስት ነው» አትበሉ! ተከልከሉ! ለእናንተ የተሻለ ይኾናልና፡፡ አላህ አንድ አምላክ ብቻ ነው፡፡ وَلَا تَقُولُوا ثَلَاثَةٌ ۚ انتَهُوا خَيْرًا لَّكُمْ ۚ إِنَّمَا اللَّهُ إِلَـٰهٌ وَاحِدٌ
አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛን ጽናቱን ይስጠን! አሚን።
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
የባሕርይ እናት
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
3፥36 «እኔም እርስዋን እና ዝርያዋን ከተረገመው ሰይጣን በአንተ እጠብቃቸዋለሁ» وَإِنِّي أُعِيذُهَا بِكَ وَذُرِّيَّتَهَا مِنَ الشَّيْطَانِ الرَّجِيمِ
የመርየም እናት፦ "እርስዋን እና ዝርያዋን" በማለቷ ዒሣ የመርየም ዘር እንደሆነ ቁርኣን አስረግጦ እና ረግጦ ያሳያል፦
3፥36 «እኔም እርስዋን እና ዝርያዋን ከተረገመው ሰይጣን በአንተ እጠብቃቸዋለሁ» وَإِنِّي أُعِيذُهَا بِكَ وَذُرِّيَّتَهَا مِنَ الشَّيْطَانِ الرَّجِيمِ
"ዙሪያህ" ذُرِّيَّة ማለት "ዘር"offspring" ማለት ሲሆን "ዙሪያህ" ذُرِّيَّة በሚለው መድረሻ ቅጥያ ላይ "ሃ" هَا የሚለው አንስታይ አገናዛቢ ተውላጠ ስም መርየምን አመላካች ስለሆነ ዒሣ የመርየም ዘር መሆኑን ቁልጭ እና ፍንትው አርጎ ያሳያል። "ባሕርይ" ማለት "ምንነት" ማለት ሲሆን ለምሳሌ፦ የእኔ እናት ለእኔ የባሕርይ እናት ናት፥ ምክንያቱም የእኔ መገኛ እናቴ ስለሆነች እና እርሷን አህዬ እና መስዬ ከማንነቷ ማንነት ከምንነቷ ምንነት ወስጃለው፥ በተመሳሳይ የኢየሱስ መገኛው እናቱ ማርያም ስለሆነች ከእርሷ ምንነት ምንነት ወስዶ እና ከእርሷ ማንነት ማንነት ወስዶ ሰው ሆኗል።
ይህ ሆኖ ሳለ በዐበይት ክርስትና ኢየሱስ "ከአብ ባሕርይ ባሕርይን እንዲሁ ከአካሉ አካልን ወስዶ የተገኘ አምላክ" ተብሎ ይታመናል፦
ሃይማኖተ አበው 74፥8 "ከባሕርይ አምላክ የተገኘ የባሕርይ አምላክ"።
ሃይማኖተ አበው 70፥17 "ከአብ ባሕርይ የተገኘ አምላክ"።
ሃይማኖተ አበው 78፥8 "አካል ዘእምአካል ባሕርይ ዘእምባሕርይ የተወለደው ልደት የማይመረመር ነው"።
ሃይማኖተ አበው 121፥10 "ከአብ አካል ዘእምአካል ባሕርይ ዘእምባሕርይ ተወልዶ የመጣ አምላክ"።
ኢየሱስ ከአብ ተገኘ ሲባል ምን ማለት ነው? የሚለውን ጥያቄ ርዕስ እንዳያስቀይስ ሙግቱን አጥበበነው እውን ማርያም ለመለኮት የባሕርይ እናቱ ናትን? መለኮት ከማርያም ለሁለተኛ ጊዜ ተገኝቷልን? ይህንን ነጥብ እስቲ እንመልከት፦
ሃይማኖተ አበው 74፥13 "የመለኮት መገኘት ከድንግል አይደለም፥ ከአብ ከተወለደ በኃላ ለመለኮት ሁለተኛ ልደት አይሻምና"።
ስለዚህ ከማርያም ተፀንሶ የተወለደው ሰው ብቻ እና ብቻ ነው፥ ማርያም መለኮትን ከወለደች ሁለተኛ ልደት አይሆንምን? መለኮትን ካልወለደች እና መለኮት ከእርሷ ካልተገኘ የአምላክ እናት አይደለችም ማለት ነው። ወይም ማርያም ለመለኮት የጸጋ እናት እንጂ የባሕርይ እናቱ አይደለች ይሆን? ውስብስብ ትምህርት ነው፦
ሰይፈ ሥላሴ ዘእሑድ ምዕራፍ 8 ቁጥር 73
"በመለኮት እናት በድንግል ማርያም"።
ማርያም ለመለኮት የባሕርይ እናቱ ናትን? መለኮትስ ለማርያም የባሕርይ ልጇ ነውን? "አዎ" ካላችሁን መለኮትነቱን አስገኝታለችን? እርሱስ መለኮትነቱ ከእርሷ ተገኝቷልን?
እሺ ይሁን እንበልና መለኮት አንድ ከሆነ ማርያም የሥላሴን መለኮት ወልዳለችን? ወይስ የወለደችው የወልድን መለኮት ብቻ ነው? የአብ እና የመንፈስ ቅዱስ መለኮትነት ካልወለደች ስንት መለኮት ሊኖር ነው? ማርያም "ቴዎቶኮስ" ናትን? "ቴዎቶኮስ" Θεοτόκος የሚለው ቃል "ቴዎስ" Θεός እና "ቶኮስ" τόκος ከሚል ሁለት ቃላት የተዋቀረ ሲሆን "ወላዲተ መለኮት" "የመለኮት ወላጅ" ማለት ነው፥ መለኮት ከእሷ ሳይገኝ እንዴት ወልዳ እናቱ ትሆናለች? በነገራችን ላይ "መለኮት" ማለት በቀላሉ "አምላክ" ማለት ነው።
የቁስጥንጥንያው ኤጲስ ቆጶስ ንስጥሮስ "ማርያም የወለደች ሰው ብቻ ነው" ብሎ ኢየሱስን ምንታዌ ከማድረግ ባሻገር ከማርያም ተፀንሶ የተወለደውን ሰው የሥላሴ አራተኛ አባል አርጎ ሲያርፈው ይህንን የሥላሴን ርባቤ "እንፈታለን" ብሎ የእስክንድርያው ኤጲስ ቆጶስ ቄርሎስ ሁለት አካላት የአብ ልጅ መለኮታዊ አካል እና የማርያም ልጅ ሰዋዊ አካል አንድ አካል ሆኑ በማለት ማርያምን "ቴዎቶኮስ" ብሏታል፦
ሃይማኖተ አበው 49፥15 "ቅድስት ሥላሴን እንዴት አራተኛ አካል ያደርጋሉ? እንዲህ ያለ የተነቀፈ ነገር ሊነገር አይገባውም"።
ንስጥሮስ እና ፕሮቴስታንት፣ የይሆዋ ምስክር፣ ሰባተኛው ቀን የመገለጣውያን ቤተክርስቲያን"The Seventh-day Adventist Church" የሚባሉ አንጃዎች "ማርያም "ኽሪስቶቶኮስ" ብቻ ናት" ብለው ያምናሉ፥ "ኽሪስቶቶኮስ" Χριστοτόκος የሚለው ቃል "ኽሪስቶስ" χρῑστός እና "ቶኮስ" τόκος ከሚል ሁለት ቃላት የተዋቀረ ሲሆን "ወላዲተ ክርስቶስ" "የክርስቶስ ወላጅ" ማለት ነው። ክርስቶስ ደግሞ የአምላክ እንጂ አምላክ አይደለም፦
1ኛ ቆሮንቶስ 3፥23 ክርስቶስ የአምላክ ነው። Χριστὸς δὲ Θεοῦ.
ሉቃስ 9፥20 እናንተስ እኔ ማን እንደ ሆንሁ ትላላችሁ? አላቸው። ጴጥሮስም መልሶ፦ "የአምላክ ክርስቶስ ነህ" አለ። εἶπεν δὲ αὐτοῖς Ὑμεῖς δὲ τίνα με λέγετε εἶναι; Πέτρος δὲ ἀποκριθεὶς εἶπεν Τὸν Χριστὸν τοῦ Θεοῦ.
በእርግጥም ማርያም የክርስቶስ ኢየሱስ የባሕርይ እናቱ ናት። መለኮት ግን አስገኝ እንጂ ከፍጡር ሆነ ከመለኮት የሚገኝ አይደለም፥ መለኮት መነሻ፣ ምንጭ እና መገኛ ካለው መለኮት እንዴት ይባላል? መነሻ እና ጅማሮ ያለው እኮ ፍጡር ብቻ ነው።
አምላካችን ሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይስጠን! አሚን።
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
3፥36 «እኔም እርስዋን እና ዝርያዋን ከተረገመው ሰይጣን በአንተ እጠብቃቸዋለሁ» وَإِنِّي أُعِيذُهَا بِكَ وَذُرِّيَّتَهَا مِنَ الشَّيْطَانِ الرَّجِيمِ
የመርየም እናት፦ "እርስዋን እና ዝርያዋን" በማለቷ ዒሣ የመርየም ዘር እንደሆነ ቁርኣን አስረግጦ እና ረግጦ ያሳያል፦
3፥36 «እኔም እርስዋን እና ዝርያዋን ከተረገመው ሰይጣን በአንተ እጠብቃቸዋለሁ» وَإِنِّي أُعِيذُهَا بِكَ وَذُرِّيَّتَهَا مِنَ الشَّيْطَانِ الرَّجِيمِ
"ዙሪያህ" ذُرِّيَّة ማለት "ዘር"offspring" ማለት ሲሆን "ዙሪያህ" ذُرِّيَّة በሚለው መድረሻ ቅጥያ ላይ "ሃ" هَا የሚለው አንስታይ አገናዛቢ ተውላጠ ስም መርየምን አመላካች ስለሆነ ዒሣ የመርየም ዘር መሆኑን ቁልጭ እና ፍንትው አርጎ ያሳያል። "ባሕርይ" ማለት "ምንነት" ማለት ሲሆን ለምሳሌ፦ የእኔ እናት ለእኔ የባሕርይ እናት ናት፥ ምክንያቱም የእኔ መገኛ እናቴ ስለሆነች እና እርሷን አህዬ እና መስዬ ከማንነቷ ማንነት ከምንነቷ ምንነት ወስጃለው፥ በተመሳሳይ የኢየሱስ መገኛው እናቱ ማርያም ስለሆነች ከእርሷ ምንነት ምንነት ወስዶ እና ከእርሷ ማንነት ማንነት ወስዶ ሰው ሆኗል።
ይህ ሆኖ ሳለ በዐበይት ክርስትና ኢየሱስ "ከአብ ባሕርይ ባሕርይን እንዲሁ ከአካሉ አካልን ወስዶ የተገኘ አምላክ" ተብሎ ይታመናል፦
ሃይማኖተ አበው 74፥8 "ከባሕርይ አምላክ የተገኘ የባሕርይ አምላክ"።
ሃይማኖተ አበው 70፥17 "ከአብ ባሕርይ የተገኘ አምላክ"።
ሃይማኖተ አበው 78፥8 "አካል ዘእምአካል ባሕርይ ዘእምባሕርይ የተወለደው ልደት የማይመረመር ነው"።
ሃይማኖተ አበው 121፥10 "ከአብ አካል ዘእምአካል ባሕርይ ዘእምባሕርይ ተወልዶ የመጣ አምላክ"።
ኢየሱስ ከአብ ተገኘ ሲባል ምን ማለት ነው? የሚለውን ጥያቄ ርዕስ እንዳያስቀይስ ሙግቱን አጥበበነው እውን ማርያም ለመለኮት የባሕርይ እናቱ ናትን? መለኮት ከማርያም ለሁለተኛ ጊዜ ተገኝቷልን? ይህንን ነጥብ እስቲ እንመልከት፦
ሃይማኖተ አበው 74፥13 "የመለኮት መገኘት ከድንግል አይደለም፥ ከአብ ከተወለደ በኃላ ለመለኮት ሁለተኛ ልደት አይሻምና"።
ስለዚህ ከማርያም ተፀንሶ የተወለደው ሰው ብቻ እና ብቻ ነው፥ ማርያም መለኮትን ከወለደች ሁለተኛ ልደት አይሆንምን? መለኮትን ካልወለደች እና መለኮት ከእርሷ ካልተገኘ የአምላክ እናት አይደለችም ማለት ነው። ወይም ማርያም ለመለኮት የጸጋ እናት እንጂ የባሕርይ እናቱ አይደለች ይሆን? ውስብስብ ትምህርት ነው፦
ሰይፈ ሥላሴ ዘእሑድ ምዕራፍ 8 ቁጥር 73
"በመለኮት እናት በድንግል ማርያም"።
ማርያም ለመለኮት የባሕርይ እናቱ ናትን? መለኮትስ ለማርያም የባሕርይ ልጇ ነውን? "አዎ" ካላችሁን መለኮትነቱን አስገኝታለችን? እርሱስ መለኮትነቱ ከእርሷ ተገኝቷልን?
እሺ ይሁን እንበልና መለኮት አንድ ከሆነ ማርያም የሥላሴን መለኮት ወልዳለችን? ወይስ የወለደችው የወልድን መለኮት ብቻ ነው? የአብ እና የመንፈስ ቅዱስ መለኮትነት ካልወለደች ስንት መለኮት ሊኖር ነው? ማርያም "ቴዎቶኮስ" ናትን? "ቴዎቶኮስ" Θεοτόκος የሚለው ቃል "ቴዎስ" Θεός እና "ቶኮስ" τόκος ከሚል ሁለት ቃላት የተዋቀረ ሲሆን "ወላዲተ መለኮት" "የመለኮት ወላጅ" ማለት ነው፥ መለኮት ከእሷ ሳይገኝ እንዴት ወልዳ እናቱ ትሆናለች? በነገራችን ላይ "መለኮት" ማለት በቀላሉ "አምላክ" ማለት ነው።
የቁስጥንጥንያው ኤጲስ ቆጶስ ንስጥሮስ "ማርያም የወለደች ሰው ብቻ ነው" ብሎ ኢየሱስን ምንታዌ ከማድረግ ባሻገር ከማርያም ተፀንሶ የተወለደውን ሰው የሥላሴ አራተኛ አባል አርጎ ሲያርፈው ይህንን የሥላሴን ርባቤ "እንፈታለን" ብሎ የእስክንድርያው ኤጲስ ቆጶስ ቄርሎስ ሁለት አካላት የአብ ልጅ መለኮታዊ አካል እና የማርያም ልጅ ሰዋዊ አካል አንድ አካል ሆኑ በማለት ማርያምን "ቴዎቶኮስ" ብሏታል፦
ሃይማኖተ አበው 49፥15 "ቅድስት ሥላሴን እንዴት አራተኛ አካል ያደርጋሉ? እንዲህ ያለ የተነቀፈ ነገር ሊነገር አይገባውም"።
ንስጥሮስ እና ፕሮቴስታንት፣ የይሆዋ ምስክር፣ ሰባተኛው ቀን የመገለጣውያን ቤተክርስቲያን"The Seventh-day Adventist Church" የሚባሉ አንጃዎች "ማርያም "ኽሪስቶቶኮስ" ብቻ ናት" ብለው ያምናሉ፥ "ኽሪስቶቶኮስ" Χριστοτόκος የሚለው ቃል "ኽሪስቶስ" χρῑστός እና "ቶኮስ" τόκος ከሚል ሁለት ቃላት የተዋቀረ ሲሆን "ወላዲተ ክርስቶስ" "የክርስቶስ ወላጅ" ማለት ነው። ክርስቶስ ደግሞ የአምላክ እንጂ አምላክ አይደለም፦
1ኛ ቆሮንቶስ 3፥23 ክርስቶስ የአምላክ ነው። Χριστὸς δὲ Θεοῦ.
ሉቃስ 9፥20 እናንተስ እኔ ማን እንደ ሆንሁ ትላላችሁ? አላቸው። ጴጥሮስም መልሶ፦ "የአምላክ ክርስቶስ ነህ" አለ። εἶπεν δὲ αὐτοῖς Ὑμεῖς δὲ τίνα με λέγετε εἶναι; Πέτρος δὲ ἀποκριθεὶς εἶπεν Τὸν Χριστὸν τοῦ Θεοῦ.
በእርግጥም ማርያም የክርስቶስ ኢየሱስ የባሕርይ እናቱ ናት። መለኮት ግን አስገኝ እንጂ ከፍጡር ሆነ ከመለኮት የሚገኝ አይደለም፥ መለኮት መነሻ፣ ምንጭ እና መገኛ ካለው መለኮት እንዴት ይባላል? መነሻ እና ጅማሮ ያለው እኮ ፍጡር ብቻ ነው።
አምላካችን ሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይስጠን! አሚን።
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
አሥ ሠላሙ ዐለይኩም ሙሥሊም ወንድሞቼ እና እኅቶቼ እንዲሁ ክርስቲያን ወገኖች ሰላም ብያለው!
እውን ኢየሱስ የባሕርይ አምላክ ነውን? የሚለው ይህ መጽሐፌ አዲስ አበባ በለገሃር እና በሜክሲኮ መካከል ኮሜርስ ወይም ከጃፋር መጽሐፍ መደብር በስተቀኝ "ኮሜርስ የመጽሐፍ መደብር" በሚባለው ውስጥ ይገኛል። ለበለጠ መረጃ 0920781016 ዐብዱ ብለው ይደውሉ!
ሌሎቻችሁ ተደራሽነት እንዲኖረው በየታይም ላይናችሁ፣ በየጉሩፑ፣ በየፔጁ፣ በየቻናሉ፣ በየኮሜንቱ ሼር እና ፓስት በማድረግ የአጅሩ ተካፋይ ይሁኑ!
እውን ኢየሱስ የባሕርይ አምላክ ነውን? የሚለው ይህ መጽሐፌ አዲስ አበባ በለገሃር እና በሜክሲኮ መካከል ኮሜርስ ወይም ከጃፋር መጽሐፍ መደብር በስተቀኝ "ኮሜርስ የመጽሐፍ መደብር" በሚባለው ውስጥ ይገኛል። ለበለጠ መረጃ 0920781016 ዐብዱ ብለው ይደውሉ!
ሌሎቻችሁ ተደራሽነት እንዲኖረው በየታይም ላይናችሁ፣ በየጉሩፑ፣ በየፔጁ፣ በየቻናሉ፣ በየኮሜንቱ ሼር እና ፓስት በማድረግ የአጅሩ ተካፋይ ይሁኑ!
የእግዚአብሔር አካል
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።
42፥11 የሚመስለው ምንም "ነገር" የለም፡፡ እርሱም ሰሚው ተመልካቹ ነው፡፡ لَيْسَ كَمِثْلِهِ شَيْءٌ ۖ وَهُوَ السَّمِيعُ الْبَصِيرُ
አምላካችን አሏህ ከፍጡራኑ ጋር የማይመሳሰል የራሱ ባሕርያት አሉት፥ እርሱን የሚመስል ምንም ነገር የለም፦
42፥11 የሚመስለው ምንም "ነገር" የለም፡፡ እርሱም ሰሚው ተመልካቹ ነው፡፡ لَيْسَ كَمِثْلِهِ شَيْءٌ ۖ وَهُوَ السَّمِيعُ الْبَصِيرُ
እዚህ አንቀጽ ላይ "ሚስል" مِثْل በሚለው ቃል ላይ መነሻ ቅጥያ ሆኖ የገባው "ከ" كَ የሚል መስተዋድድ "በጭራሽ" ማለት ነው፥ "ነገር" በሚለው ቃል ውስጥ ሁሉም ፍጡራን የሚካተቱ ሲሆኑ ከፍጡራን መካከል እርሱን የሚመስል ብጤ በጭራሽ የለም። እዚሁ አንቀጽ ላይ አሏህ "ሰሚ እና ተመልካች" እንደሆነ ተገልጿል፥ ሰውም "ሰሚ እና ተመልካች" እንደሆነ ሌላ አንቀጽ ላይ ተገልጿል፦
76፥2 እኛ ሰውን በሕግ ግዳጅ የምንፈትነው ስንኾን ቅልቅሎች ከኾኑ የፍትወት ጠብታ ፈጠርነው፡፡ ሰሚ ተመልካችም አደረግነው*፡፡ إِنَّا خَلَقْنَا الْإِنسَانَ مِن نُّطْفَةٍ أَمْشَاجٍ نَّبْتَلِيهِ فَجَعَلْنَاهُ سَمِيعًا بَصِيرًا
የአሏህ መስማት እና ማየት ከፍጡራን ጋር እንደማይመሳሰል እና እንደማይነጻጸር ሁሉ የፈጣሪ ባሕርዮት ከፍጡራን ባሕርዮት ጋር አይመሳሰለም አይነጻጸርም።
በኢሥላም ያለውን የአሏህ ሲፋት በመጠኑ እዚህ ድረስ ካየን ዘንዳ በባይብል እግዚአብሔር የአካል ክፍል የሆኑት ከንፈር እና ምላስ አለው፦
ኢሳይያስ 30፥27 "ከንፈሮቹም" ቍጣን የሞሉ ናቸው፥ "ምላሱም" እንደምትበላ እሳት ናት።
"ከንፈሮች" የሚለው "ከንፈር" ለሚል ብዙ ቁጥር ሲሆን የላይኛው ከንፈር እና የታችኛው ከንፈር ያመለክታል፥ ምላስ ግን በነጠላ ስለሆነ አንድ ብቻ ይመስላል። "ባት" ሲባል ደንግጠህ "የግድ ሥጋ መሆን አለበት" ካልክ ከንፈር እና ምላስ የግድ ሥጋ መሆን አለበት ብዬ እሞግትካለው፥ በሰፈሩት ቁና መሰፈር ግድ ነውና። እግዚአብሔር የአካል ክፍሎች የሆኑት ዓይኖች፣ ቅንድቦች እና ጆሮዎች አሉት፦
መዝሙር 11፥4 "ዓይኖቹ" ወደ ድሃ ይመለከታሉ፥ "ቅንድቦቹም" የሰው ልጆችን ይመረምራሉ።
1 ጴጥሮስ 3፥12 የጌታ ዓይኖች ወደ ጻድቃን ናቸውና፥ "ጆሮዎቹም" ለጸሎታቸው ተከፍተዋል።
"ዓይኖች" "ቅንድቦች" እና "ጆሮዎች" የተባሉት "ዓይን" "ቅንድብ" "ጆሮ" ለሚሉት ብዙ ቁጥር ስለሆነ ቢያንስ ከአንድ በላይ ዓይኖች፣ ቅንድቦች እና ጆሮዎች አሉት፥ ሰው ላይ ያየሁት ዓይኖች፣ ቅንድቦች እና ጆሮዎች ሥጋ ስለሆኑ "የእግዚአብሔር ዓይኖች፣ ቅንድቦች እና ጆሮዎች ሥጋ ናቸው" ብዬ ደረቅ ንትርክ መነታረክ አላቃተኝም። እግዚአብሔር የአካል ክፍሎች የሆኑት አፍንጫ እና አፍ አሉት፦
ዘጸአት 15፥8 "በአፍንጫህ" እስትንፋስ ውኆች ተከመሩ።
መዝሙር 33፥6 ሠራዊታቸውም ሁሉ "በአፉ" እስትንፋስ።
ሰው የሚተነፍስበት አፍንጫ እና አፍ ሥጋ ስለሆነ "እግዚአብሔር የሚተነፍስበት አፍንጫ እና አፍ ሥጋ ነው" ብዬ ጉንጭ አልፋ ንትርክ መነታረክ አላቃተኝም። እግዚአብሔር የአካል ክፍሎች የሆኑት ክንድ፣ ብብት፣ እግሮች፣ እጆች፣ ጣቶች አሉት፦
ኢሳይያስ 40፥11 ጠቦቶቹን "በክንዱ" ሰብስቦ "በብብቱ" ይሸከማል።
መዝሙር 132፥7 "እግሮቹ" በሚቆሙበት ስፍራ እንሰግዳለን።
መዝሙር 119፥73 "እጆችህ" ሠሩኝ አበጃጁኝም።
መዝሙር 8፥3 "የጣቶችህን" ሥራ ሰማዮችን ባየሁ ጊዜ፥
ባሻዬ እኔ የማውቀው ክንድ፣ ብብት፣ እግሮች፣ እጆች፣ ጣቶች ሥጋ ናቸው፥ እና እግዚአብሔር ልክ እንደ ሰው ክንድ፣ ብብት፣ እግሮች፣ እጆች፣ ጣቶች አሉትን? "አይ ክንድ፣ ብብት፣ እግሮች፣ እጆች፣ ጣቶች፣ አፍንጫ፣ አፍ፣ ዓይኖች፣ ቅንድቦች፣ ጆሮዎች፣ ምላስ፣ ከንፈሮች ትርጉም አላቸው" ካላችሁ በጥቅስ መሞገት እንጂ ከኪስ እየመዘዙ እንቶ ፈንቶ ማውራት ውኃ የማያነሳ እና የማይቋጥር ሙግት ነው። ምክንያቱም እነዚህ የአካል ክፍሎች ትርጉም መስጠት ሠለስቱ ምዕት ከልክለዋል፦
ሃይማኖተ አበው ምዕራፍ 19 ቁጥር 33
“ለእግዚአብሔር ዓይኖች እና ጆሮዎች እንዳሉት መጽሐፍት የተናገሩት እና የቀሩት እንዳሉት ስለ እግዚአብሔር የተነገረው ሁሉ የታመነ እውነተኛ እንደሆነ እናምናለን፥ ነገር ግን አይመረመርም አይታሰብም”።
"ሠለስቱ ምዕት" ማለት በ 325 ድኅረ ልደት በኒቂያ ጉባኤ የተሰበሰቡት 318 ሊቃውንት ናቸው፥ እነርሱ፦ "የቀሩት" ያሉት ከዓይኖች እና ከጆሮዎች ሌላ የተገለጹትን የአካል ክፍሎች ነው፦
ሃይማኖተ አበው ምዕራፍ 28 ቁጥር 30
“ለእግዚአብሔር ዓይን፣ ጆሮ፣ እጅ፣ እግር እንዳለው የተነገረው ሁሉ ስለ እግዚአብሔር በከበሩ መጻሕፍት የተጻፈ ሁሉ የታመነ የተረዳ ነው፥ የተናገርነው ሁሉ አለው። ነገር ግን አይመረመርም አይታወቅም”።
እርማችሁን አውጡ! ጆሮ፣ እጅ፣ እግር እንዳለ እንቅጩን ፍርጥ አርገው ተናግረዋል። ለእግዚአብሔር እጅ፣ ጥፍር፣ እግር እንዳለው አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ በመጽሐፈ ምሥጢር ተናግሯል፦
መጽሐፈ ምሥጢር ምዕራፍ 1 ቁጥር 62
“እግዚአብሔር እጆች እና ክንድ፣ ጥፍር እንዳለው ዕወቁ”።
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።
42፥11 የሚመስለው ምንም "ነገር" የለም፡፡ እርሱም ሰሚው ተመልካቹ ነው፡፡ لَيْسَ كَمِثْلِهِ شَيْءٌ ۖ وَهُوَ السَّمِيعُ الْبَصِيرُ
አምላካችን አሏህ ከፍጡራኑ ጋር የማይመሳሰል የራሱ ባሕርያት አሉት፥ እርሱን የሚመስል ምንም ነገር የለም፦
42፥11 የሚመስለው ምንም "ነገር" የለም፡፡ እርሱም ሰሚው ተመልካቹ ነው፡፡ لَيْسَ كَمِثْلِهِ شَيْءٌ ۖ وَهُوَ السَّمِيعُ الْبَصِيرُ
እዚህ አንቀጽ ላይ "ሚስል" مِثْل በሚለው ቃል ላይ መነሻ ቅጥያ ሆኖ የገባው "ከ" كَ የሚል መስተዋድድ "በጭራሽ" ማለት ነው፥ "ነገር" በሚለው ቃል ውስጥ ሁሉም ፍጡራን የሚካተቱ ሲሆኑ ከፍጡራን መካከል እርሱን የሚመስል ብጤ በጭራሽ የለም። እዚሁ አንቀጽ ላይ አሏህ "ሰሚ እና ተመልካች" እንደሆነ ተገልጿል፥ ሰውም "ሰሚ እና ተመልካች" እንደሆነ ሌላ አንቀጽ ላይ ተገልጿል፦
76፥2 እኛ ሰውን በሕግ ግዳጅ የምንፈትነው ስንኾን ቅልቅሎች ከኾኑ የፍትወት ጠብታ ፈጠርነው፡፡ ሰሚ ተመልካችም አደረግነው*፡፡ إِنَّا خَلَقْنَا الْإِنسَانَ مِن نُّطْفَةٍ أَمْشَاجٍ نَّبْتَلِيهِ فَجَعَلْنَاهُ سَمِيعًا بَصِيرًا
የአሏህ መስማት እና ማየት ከፍጡራን ጋር እንደማይመሳሰል እና እንደማይነጻጸር ሁሉ የፈጣሪ ባሕርዮት ከፍጡራን ባሕርዮት ጋር አይመሳሰለም አይነጻጸርም።
በኢሥላም ያለውን የአሏህ ሲፋት በመጠኑ እዚህ ድረስ ካየን ዘንዳ በባይብል እግዚአብሔር የአካል ክፍል የሆኑት ከንፈር እና ምላስ አለው፦
ኢሳይያስ 30፥27 "ከንፈሮቹም" ቍጣን የሞሉ ናቸው፥ "ምላሱም" እንደምትበላ እሳት ናት።
"ከንፈሮች" የሚለው "ከንፈር" ለሚል ብዙ ቁጥር ሲሆን የላይኛው ከንፈር እና የታችኛው ከንፈር ያመለክታል፥ ምላስ ግን በነጠላ ስለሆነ አንድ ብቻ ይመስላል። "ባት" ሲባል ደንግጠህ "የግድ ሥጋ መሆን አለበት" ካልክ ከንፈር እና ምላስ የግድ ሥጋ መሆን አለበት ብዬ እሞግትካለው፥ በሰፈሩት ቁና መሰፈር ግድ ነውና። እግዚአብሔር የአካል ክፍሎች የሆኑት ዓይኖች፣ ቅንድቦች እና ጆሮዎች አሉት፦
መዝሙር 11፥4 "ዓይኖቹ" ወደ ድሃ ይመለከታሉ፥ "ቅንድቦቹም" የሰው ልጆችን ይመረምራሉ።
1 ጴጥሮስ 3፥12 የጌታ ዓይኖች ወደ ጻድቃን ናቸውና፥ "ጆሮዎቹም" ለጸሎታቸው ተከፍተዋል።
"ዓይኖች" "ቅንድቦች" እና "ጆሮዎች" የተባሉት "ዓይን" "ቅንድብ" "ጆሮ" ለሚሉት ብዙ ቁጥር ስለሆነ ቢያንስ ከአንድ በላይ ዓይኖች፣ ቅንድቦች እና ጆሮዎች አሉት፥ ሰው ላይ ያየሁት ዓይኖች፣ ቅንድቦች እና ጆሮዎች ሥጋ ስለሆኑ "የእግዚአብሔር ዓይኖች፣ ቅንድቦች እና ጆሮዎች ሥጋ ናቸው" ብዬ ደረቅ ንትርክ መነታረክ አላቃተኝም። እግዚአብሔር የአካል ክፍሎች የሆኑት አፍንጫ እና አፍ አሉት፦
ዘጸአት 15፥8 "በአፍንጫህ" እስትንፋስ ውኆች ተከመሩ።
መዝሙር 33፥6 ሠራዊታቸውም ሁሉ "በአፉ" እስትንፋስ።
ሰው የሚተነፍስበት አፍንጫ እና አፍ ሥጋ ስለሆነ "እግዚአብሔር የሚተነፍስበት አፍንጫ እና አፍ ሥጋ ነው" ብዬ ጉንጭ አልፋ ንትርክ መነታረክ አላቃተኝም። እግዚአብሔር የአካል ክፍሎች የሆኑት ክንድ፣ ብብት፣ እግሮች፣ እጆች፣ ጣቶች አሉት፦
ኢሳይያስ 40፥11 ጠቦቶቹን "በክንዱ" ሰብስቦ "በብብቱ" ይሸከማል።
መዝሙር 132፥7 "እግሮቹ" በሚቆሙበት ስፍራ እንሰግዳለን።
መዝሙር 119፥73 "እጆችህ" ሠሩኝ አበጃጁኝም።
መዝሙር 8፥3 "የጣቶችህን" ሥራ ሰማዮችን ባየሁ ጊዜ፥
ባሻዬ እኔ የማውቀው ክንድ፣ ብብት፣ እግሮች፣ እጆች፣ ጣቶች ሥጋ ናቸው፥ እና እግዚአብሔር ልክ እንደ ሰው ክንድ፣ ብብት፣ እግሮች፣ እጆች፣ ጣቶች አሉትን? "አይ ክንድ፣ ብብት፣ እግሮች፣ እጆች፣ ጣቶች፣ አፍንጫ፣ አፍ፣ ዓይኖች፣ ቅንድቦች፣ ጆሮዎች፣ ምላስ፣ ከንፈሮች ትርጉም አላቸው" ካላችሁ በጥቅስ መሞገት እንጂ ከኪስ እየመዘዙ እንቶ ፈንቶ ማውራት ውኃ የማያነሳ እና የማይቋጥር ሙግት ነው። ምክንያቱም እነዚህ የአካል ክፍሎች ትርጉም መስጠት ሠለስቱ ምዕት ከልክለዋል፦
ሃይማኖተ አበው ምዕራፍ 19 ቁጥር 33
“ለእግዚአብሔር ዓይኖች እና ጆሮዎች እንዳሉት መጽሐፍት የተናገሩት እና የቀሩት እንዳሉት ስለ እግዚአብሔር የተነገረው ሁሉ የታመነ እውነተኛ እንደሆነ እናምናለን፥ ነገር ግን አይመረመርም አይታሰብም”።
"ሠለስቱ ምዕት" ማለት በ 325 ድኅረ ልደት በኒቂያ ጉባኤ የተሰበሰቡት 318 ሊቃውንት ናቸው፥ እነርሱ፦ "የቀሩት" ያሉት ከዓይኖች እና ከጆሮዎች ሌላ የተገለጹትን የአካል ክፍሎች ነው፦
ሃይማኖተ አበው ምዕራፍ 28 ቁጥር 30
“ለእግዚአብሔር ዓይን፣ ጆሮ፣ እጅ፣ እግር እንዳለው የተነገረው ሁሉ ስለ እግዚአብሔር በከበሩ መጻሕፍት የተጻፈ ሁሉ የታመነ የተረዳ ነው፥ የተናገርነው ሁሉ አለው። ነገር ግን አይመረመርም አይታወቅም”።
እርማችሁን አውጡ! ጆሮ፣ እጅ፣ እግር እንዳለ እንቅጩን ፍርጥ አርገው ተናግረዋል። ለእግዚአብሔር እጅ፣ ጥፍር፣ እግር እንዳለው አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ በመጽሐፈ ምሥጢር ተናግሯል፦
መጽሐፈ ምሥጢር ምዕራፍ 1 ቁጥር 62
“እግዚአብሔር እጆች እና ክንድ፣ ጥፍር እንዳለው ዕወቁ”።