የአማኝ መልካም ሥራ
ክፍል አንድ
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
20፥75 በጎ ሥራዎችን በእርግጥ የሠራ ምእመን ኾኖ የመጣውም ሰው እነዚያ ለእነርሱ ከፍተኛ ደረጃዎች አላቸው፡፡ وَمَن يَأْتِهِ مُؤْمِنًا قَدْ عَمِلَ الصَّالِحَاتِ فَأُولَـٰئِكَ لَهُمُ الدَّرَجَاتُ الْعُلَىٰ
"ላ ኢላሀ ኢለል ሏህ" لَا إِلَـٰهَ إِلَّا اللَّه ማለት "ከአሏህ በስተቀር በሐቅ የሚመለክ አምላክ የለም" ማለት ነው፥ "ኢማን" إِيمَٰن ማለት "እምነት" ማለት ሲሆን የኢማን ትልቁ ቅርንጫፍ "ላ ኢላሀ ኢለል ሏህ" ማለት ነው፦
ኢማም ሙሥሊም መጽሐፍ 1, ሐዲስ 60
አቢ ሁረይራህ እንደተረከው፦ “የአላህ መልእክተኛም”ﷺ” እንዲህ አሉ፦ "ኢማን ከሰባ ወይም ከስልሳ በላይ ቅርንጫፎች አሉት፥ ትልቁ ቅርንጫፍ "ላ ኢላሀ ኢለል ሏህ" ማለት ነው"። عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ، قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم “ الإِيمَانُ بِضْعٌ وَسَبْعُونَ أَوْ بِضْعٌ وَسِتُّونَ شُعْبَةً فَأَفْضَلُهَا قَوْلُ لاَ إِلَهَ إِلاَّ اللَّهُ
"ላ ኢላሀ ኢለል ሏህ" ያለ ሙሥሊም እንጂ ጀነት ሌላው አይገባትም፥ ሙእሚን ምንም ነገር በአሏህ ላይ ሳያሻርክ አሏህን የሚገናኝ ጀነት ይገባል፦
ኢማም ሙሥሊም መጽሐፍ 1, ሐዲስ 212
አቢ ሁረይራህ"ረ.ዐ." እንደተረከው፦ "ነቢዩ"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "እነሆ ጀነት ሙሥሊም የሆነች ነፍስ እንጂ ሌላው አይገባትም"።ﻋَﻦْ ﺃَﺑِﻲ ﻫُﺮَﻳْﺮَﺓَ، ﺭﺿﻲ ﺍﻟﻠﻪ ﻋﻨﻪ ﻗَﺎﻝ ﻋﻦ ﺍﻟﻨَّﺒِﻲّ ﺻَﻠَّﻰ ﺍﻟﻠﻪُ ﻋَﻠَﻴْﻪِ ﻭَﺳَﻠَّﻢَ ﺃﻧﻪ ﻗَﺎﻝَ ﺃَﻧَّﻪُ ﻟَﺎ ﻳَﺪْﺧُﻞُ ﺍﻟْﺠَﻨَّﺔَ ﺇِﻟَّﺎ ﻧَﻔْﺲٌ ﻣُﺴْﻠِﻤَﺔٌ
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 3, ሐዲስ 71
አነሥ ሰምቶ እንደተረከው፦ "ነቢዩ"ﷺ" ለሙዓዝ እንዲህ ሲሉ ተነገረኝ፦ "ማንም ምንም ነገር በአሏህ ላይ ሳያሻርክ አሏህን የሚገናኝ ጀነት ገባ"። سَمِعْتُ أَنَسًا، قَالَ ذُكِرَ لِي أَنَّ النَّبِيَّ صلى الله عليه وسلم قَالَ لِمُعَاذٍ " مَنْ لَقِيَ اللَّهَ لاَ يُشْرِكُ بِهِ شَيْئًا دَخَلَ الْجَنَّةَ ".
አንድ ሰው "ላ ኢላሀ" لَا إِلَـٰهَ ብሎ ጣዖታትን ነፍይ በማድረግ ሲክድ እና "ኢለል ሏህ" إِلَّا اللَّه ብሎ ኢስባት በማድረግ በአሏህ ሲያምን ወደ አሏህ በንስሓ ይመለሳል፥ ወደ አሏህ በንስሓ ሲመለስ የአሏህን ይቅርታ እና ምሕረት ስለሚያገኝ በአሏህ ይቅርታ እና ምሕረት ጀነት ይገባል፦
ኢማም ሙሥሊም መጽሐፍ 52, ሐዲስ 69
አቢ ሁረይራህ"ረ.ዐ." እንደተረከው፦ "ነቢዩ"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "አቢ ሁረይራህ እንደተረከው፦ "የአሏህ መልእክተኛ"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "ከእናንተ መካከል ማንም በሥራው ብቻ ጀናህ መግባት አይችልም፥ ሶሓባዎችም፦ "የአሏህ መልእክተኛ ሆይ! እርሶም ቢሆኑ? አሉ። እርሳቸውም፦ "እኔም ብሆን፥ ነገር ግን አሏህ ከእርሱ በይቅርታው እና በምሕረቱ ሸፍኖኛል"። عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ، قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم " لَنْ يُدْخِلَ أَحَدًا مِنْكُمْ عَمَلُهُ الْجَنَّةَ " . قَالُوا وَلاَ أَنْتَ يَا رَسُولَ اللَّهِ قَالَ " وَلاَ أَنَا إِلاَّ أَنْ يَتَغَمَّدَنِيَ اللَّهُ مِنْهُ بِفَضْلٍ وَرَحْمَةٍ " .
"ላ ኢላሀ ኢለል ሏህ" ብሎ ያመነ አማኝ የሚሠራው መልካም ሥራ አሏህ በቁርኣኑ መልእክተኛው"ﷺ" በሡናህ "ሥሩ" ያሉን በጎ ሥራ ሲሆን አምልኮ ነው፥ ይህ መልካም ሥራ ለአማንያን ለሁለት ነገሮች ይጠቅማል።
ክፍል አንድ
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
20፥75 በጎ ሥራዎችን በእርግጥ የሠራ ምእመን ኾኖ የመጣውም ሰው እነዚያ ለእነርሱ ከፍተኛ ደረጃዎች አላቸው፡፡ وَمَن يَأْتِهِ مُؤْمِنًا قَدْ عَمِلَ الصَّالِحَاتِ فَأُولَـٰئِكَ لَهُمُ الدَّرَجَاتُ الْعُلَىٰ
"ላ ኢላሀ ኢለል ሏህ" لَا إِلَـٰهَ إِلَّا اللَّه ማለት "ከአሏህ በስተቀር በሐቅ የሚመለክ አምላክ የለም" ማለት ነው፥ "ኢማን" إِيمَٰن ማለት "እምነት" ማለት ሲሆን የኢማን ትልቁ ቅርንጫፍ "ላ ኢላሀ ኢለል ሏህ" ማለት ነው፦
ኢማም ሙሥሊም መጽሐፍ 1, ሐዲስ 60
አቢ ሁረይራህ እንደተረከው፦ “የአላህ መልእክተኛም”ﷺ” እንዲህ አሉ፦ "ኢማን ከሰባ ወይም ከስልሳ በላይ ቅርንጫፎች አሉት፥ ትልቁ ቅርንጫፍ "ላ ኢላሀ ኢለል ሏህ" ማለት ነው"። عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ، قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم “ الإِيمَانُ بِضْعٌ وَسَبْعُونَ أَوْ بِضْعٌ وَسِتُّونَ شُعْبَةً فَأَفْضَلُهَا قَوْلُ لاَ إِلَهَ إِلاَّ اللَّهُ
"ላ ኢላሀ ኢለል ሏህ" ያለ ሙሥሊም እንጂ ጀነት ሌላው አይገባትም፥ ሙእሚን ምንም ነገር በአሏህ ላይ ሳያሻርክ አሏህን የሚገናኝ ጀነት ይገባል፦
ኢማም ሙሥሊም መጽሐፍ 1, ሐዲስ 212
አቢ ሁረይራህ"ረ.ዐ." እንደተረከው፦ "ነቢዩ"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "እነሆ ጀነት ሙሥሊም የሆነች ነፍስ እንጂ ሌላው አይገባትም"።ﻋَﻦْ ﺃَﺑِﻲ ﻫُﺮَﻳْﺮَﺓَ، ﺭﺿﻲ ﺍﻟﻠﻪ ﻋﻨﻪ ﻗَﺎﻝ ﻋﻦ ﺍﻟﻨَّﺒِﻲّ ﺻَﻠَّﻰ ﺍﻟﻠﻪُ ﻋَﻠَﻴْﻪِ ﻭَﺳَﻠَّﻢَ ﺃﻧﻪ ﻗَﺎﻝَ ﺃَﻧَّﻪُ ﻟَﺎ ﻳَﺪْﺧُﻞُ ﺍﻟْﺠَﻨَّﺔَ ﺇِﻟَّﺎ ﻧَﻔْﺲٌ ﻣُﺴْﻠِﻤَﺔٌ
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 3, ሐዲስ 71
አነሥ ሰምቶ እንደተረከው፦ "ነቢዩ"ﷺ" ለሙዓዝ እንዲህ ሲሉ ተነገረኝ፦ "ማንም ምንም ነገር በአሏህ ላይ ሳያሻርክ አሏህን የሚገናኝ ጀነት ገባ"። سَمِعْتُ أَنَسًا، قَالَ ذُكِرَ لِي أَنَّ النَّبِيَّ صلى الله عليه وسلم قَالَ لِمُعَاذٍ " مَنْ لَقِيَ اللَّهَ لاَ يُشْرِكُ بِهِ شَيْئًا دَخَلَ الْجَنَّةَ ".
አንድ ሰው "ላ ኢላሀ" لَا إِلَـٰهَ ብሎ ጣዖታትን ነፍይ በማድረግ ሲክድ እና "ኢለል ሏህ" إِلَّا اللَّه ብሎ ኢስባት በማድረግ በአሏህ ሲያምን ወደ አሏህ በንስሓ ይመለሳል፥ ወደ አሏህ በንስሓ ሲመለስ የአሏህን ይቅርታ እና ምሕረት ስለሚያገኝ በአሏህ ይቅርታ እና ምሕረት ጀነት ይገባል፦
ኢማም ሙሥሊም መጽሐፍ 52, ሐዲስ 69
አቢ ሁረይራህ"ረ.ዐ." እንደተረከው፦ "ነቢዩ"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "አቢ ሁረይራህ እንደተረከው፦ "የአሏህ መልእክተኛ"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "ከእናንተ መካከል ማንም በሥራው ብቻ ጀናህ መግባት አይችልም፥ ሶሓባዎችም፦ "የአሏህ መልእክተኛ ሆይ! እርሶም ቢሆኑ? አሉ። እርሳቸውም፦ "እኔም ብሆን፥ ነገር ግን አሏህ ከእርሱ በይቅርታው እና በምሕረቱ ሸፍኖኛል"። عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ، قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم " لَنْ يُدْخِلَ أَحَدًا مِنْكُمْ عَمَلُهُ الْجَنَّةَ " . قَالُوا وَلاَ أَنْتَ يَا رَسُولَ اللَّهِ قَالَ " وَلاَ أَنَا إِلاَّ أَنْ يَتَغَمَّدَنِيَ اللَّهُ مِنْهُ بِفَضْلٍ وَرَحْمَةٍ " .
"ላ ኢላሀ ኢለል ሏህ" ብሎ ያመነ አማኝ የሚሠራው መልካም ሥራ አሏህ በቁርኣኑ መልእክተኛው"ﷺ" በሡናህ "ሥሩ" ያሉን በጎ ሥራ ሲሆን አምልኮ ነው፥ ይህ መልካም ሥራ ለአማንያን ለሁለት ነገሮች ይጠቅማል።
፨ አንደኛ አማኞች ይሠሩት የነበሩትን መልካም ሥራ በእርግጥ ይመነዳሉ፥ በጀነት ውስጥም የተለያየ መቶ ደረጃዎች ስላሉ በሚሠሩት መልካም ሥራ መጠን የተለያየ ደረጃዎችን ያገኙበታል፦
18፥180 ይሠሩት የነበሩትን ነገር በእርግጥ ይመነዳሉ፡፡ سَيُجْزَوْنَ مَا كَانُوا يَعْمَلُونَ
20፥75 በጎ ሥራዎችን በእርግጥ የሠራ ምእመን ኾኖ የመጣውም ሰው እነዚያ ለእነርሱ ከፍተኛ ደረጃዎች አላቸው፡፡ وَمَن يَأْتِهِ مُؤْمِنًا قَدْ عَمِلَ الصَّالِحَاتِ فَأُولَـٰئِكَ لَهُمُ الدَّرَجَاتُ الْعُلَىٰ
3፥163 እነርሱ አላህ ዘንድ ባለ ደረጃዎች ናቸው፡፡ አላህም የሚሠሩትን ነገር ተመልካች ነው፡፡ هُمْ دَرَجَاتٌ عِندَ اللَّهِ ۗ وَاللَّهُ بَصِيرٌ بِمَا يَعْمَلُونَ
6፥132 ለሁሉም ከሠሩት ሥራ ደረጃዎች አላቸው፡፡ ጌታህም ከሚሠሩት ሁሉ ዘንጊ አይደለም፡፡ وَلِكُلٍّ دَرَجَاتٌ مِّمَّا عَمِلُوا ۚ وَمَا رَبُّكَ بِغَافِلٍ عَمَّا يَعْمَلُونَ
46፥19 ለሁሉም ከሠሩት ሥራ ደረጃዎች አላቸው፡፡ ሥራዎቻቸውንም ይሞላላቸው ዘንድ ይህንን መነዳቸው፥ እነርሱም አይበደሉም፡፡ وَلِكُلٍّ دَرَجَاتٌ مِّمَّا عَمِلُوا ۖ وَلِيُوَفِّيَهُمْ أَعْمَالَهُمْ وَهُمْ لَا يُظْلَمُونَ
ሡነን ኢብኑ ማጃህ መጽሐፍ 37, ሐዲስ 4474
ሙዓዝ ኢብኑ ጀበል የአሏህ መልእክተኛ"ﷺ" እንዲህ ሲሉ ሰማው ብሎ እንደተረከው፦ "እርሳቸውም አሉ፦ "ጀናህ መቶ ጀረዎች አሏት፥ ደረጃዎቿም ያላቸው እርቀት ልክ የሰማይ እና የምድር እርቀት ያክል ነው። ከፍተኛ ደረጃዋ ፊርደውሥ ነው፥ أَنَّ مُعَاذَ بْنَ جَبَلٍ، قَالَ سَمِعْتُ رَسُولَ اللَّهِ ـ صلى الله عليه وسلم ـ يَقُولُ " الْجَنَّةُ مِائَةُ دَرَجَةٍ كُلُّ دَرَجَةٍ مِنْهَا مَا بَيْنَ السَّمَاءِ وَالأَرْضِ وَإِنَّ أَعْلاَهَا الْفِرْدَوْسُ
"ጀናህ" جَنَّة በ "ታ" ة መርቡጧህ በነጠላ ሲሆን አጠቃላይ ጀነትን ያመለክታል፥ በአጠቃላዩ ጀነት ውስጥ ለመግባት ቁልፉ "ላ ኢላሀ ኢለል ሏህ" ሲሆን በጀነት ውስጥ ያሉትን ጀረጃዎች ውስጥ ለመግባት እና ለመመንዳት መልካም ሥራ ያስፈልጋል። በጀነት ውስጥ ያሉት መቶ የተለያዩ ደረጃዎች እራሱ "ጀናት" جَنَّات ተብለዋል፥ "ጀናት" جَنَّات በ "ታ" ت መፍቱሓህ ሲሆን በብዜት "ጀነቶች" "ገነቶች" ማለት ነው። እነዚህ የተለያየ ደረጃዎች የሆኑ ጀነቶች አምነው መልካም ለሚሠሩ የሚሰጥ ምንዳ፣ ትሩፋት፣ ወሮታ፣ ስርጉት፣ ትርሲት ነው፦
31፥8 እነዚያ ያመኑ እና መልካሞችንም የሠሩ ለእነርሱ የጸጋ "ገነቶች" አላቸው፡፡ إِنَّ الَّذِينَ آمَنُوا وَعَمِلُوا الصَّالِحَاتِ لَهُمْ جَنَّاتُ النَّعِيمِ
እዚህ አንቀጽ ላይ "ገነቶች" ለሚለው የገባው በብዙ ቁጥር "ጀናት" جَنَّات እንደሆነ ልብ አድርግ! እያንዳንዱ ደረጃ "ጀነቱል ፊርደውሥ" جَنَّةُ الفِرْدَوْسُ "ጀነቱል ዐድን" جَنَّةُ العَدْن "ጀነቱ አን-ነዒም" جَنَّةُ النَّعِيمِ "ጀነቱል መእዋ" جَنَّةُ المَأْوَىٰ እየተባለ ይጠራል።
ኢንሻሏህ ይቀጥላል......
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
18፥180 ይሠሩት የነበሩትን ነገር በእርግጥ ይመነዳሉ፡፡ سَيُجْزَوْنَ مَا كَانُوا يَعْمَلُونَ
20፥75 በጎ ሥራዎችን በእርግጥ የሠራ ምእመን ኾኖ የመጣውም ሰው እነዚያ ለእነርሱ ከፍተኛ ደረጃዎች አላቸው፡፡ وَمَن يَأْتِهِ مُؤْمِنًا قَدْ عَمِلَ الصَّالِحَاتِ فَأُولَـٰئِكَ لَهُمُ الدَّرَجَاتُ الْعُلَىٰ
3፥163 እነርሱ አላህ ዘንድ ባለ ደረጃዎች ናቸው፡፡ አላህም የሚሠሩትን ነገር ተመልካች ነው፡፡ هُمْ دَرَجَاتٌ عِندَ اللَّهِ ۗ وَاللَّهُ بَصِيرٌ بِمَا يَعْمَلُونَ
6፥132 ለሁሉም ከሠሩት ሥራ ደረጃዎች አላቸው፡፡ ጌታህም ከሚሠሩት ሁሉ ዘንጊ አይደለም፡፡ وَلِكُلٍّ دَرَجَاتٌ مِّمَّا عَمِلُوا ۚ وَمَا رَبُّكَ بِغَافِلٍ عَمَّا يَعْمَلُونَ
46፥19 ለሁሉም ከሠሩት ሥራ ደረጃዎች አላቸው፡፡ ሥራዎቻቸውንም ይሞላላቸው ዘንድ ይህንን መነዳቸው፥ እነርሱም አይበደሉም፡፡ وَلِكُلٍّ دَرَجَاتٌ مِّمَّا عَمِلُوا ۖ وَلِيُوَفِّيَهُمْ أَعْمَالَهُمْ وَهُمْ لَا يُظْلَمُونَ
ሡነን ኢብኑ ማጃህ መጽሐፍ 37, ሐዲስ 4474
ሙዓዝ ኢብኑ ጀበል የአሏህ መልእክተኛ"ﷺ" እንዲህ ሲሉ ሰማው ብሎ እንደተረከው፦ "እርሳቸውም አሉ፦ "ጀናህ መቶ ጀረዎች አሏት፥ ደረጃዎቿም ያላቸው እርቀት ልክ የሰማይ እና የምድር እርቀት ያክል ነው። ከፍተኛ ደረጃዋ ፊርደውሥ ነው፥ أَنَّ مُعَاذَ بْنَ جَبَلٍ، قَالَ سَمِعْتُ رَسُولَ اللَّهِ ـ صلى الله عليه وسلم ـ يَقُولُ " الْجَنَّةُ مِائَةُ دَرَجَةٍ كُلُّ دَرَجَةٍ مِنْهَا مَا بَيْنَ السَّمَاءِ وَالأَرْضِ وَإِنَّ أَعْلاَهَا الْفِرْدَوْسُ
"ጀናህ" جَنَّة በ "ታ" ة መርቡጧህ በነጠላ ሲሆን አጠቃላይ ጀነትን ያመለክታል፥ በአጠቃላዩ ጀነት ውስጥ ለመግባት ቁልፉ "ላ ኢላሀ ኢለል ሏህ" ሲሆን በጀነት ውስጥ ያሉትን ጀረጃዎች ውስጥ ለመግባት እና ለመመንዳት መልካም ሥራ ያስፈልጋል። በጀነት ውስጥ ያሉት መቶ የተለያዩ ደረጃዎች እራሱ "ጀናት" جَنَّات ተብለዋል፥ "ጀናት" جَنَّات በ "ታ" ت መፍቱሓህ ሲሆን በብዜት "ጀነቶች" "ገነቶች" ማለት ነው። እነዚህ የተለያየ ደረጃዎች የሆኑ ጀነቶች አምነው መልካም ለሚሠሩ የሚሰጥ ምንዳ፣ ትሩፋት፣ ወሮታ፣ ስርጉት፣ ትርሲት ነው፦
31፥8 እነዚያ ያመኑ እና መልካሞችንም የሠሩ ለእነርሱ የጸጋ "ገነቶች" አላቸው፡፡ إِنَّ الَّذِينَ آمَنُوا وَعَمِلُوا الصَّالِحَاتِ لَهُمْ جَنَّاتُ النَّعِيمِ
እዚህ አንቀጽ ላይ "ገነቶች" ለሚለው የገባው በብዙ ቁጥር "ጀናት" جَنَّات እንደሆነ ልብ አድርግ! እያንዳንዱ ደረጃ "ጀነቱል ፊርደውሥ" جَنَّةُ الفِرْدَوْسُ "ጀነቱል ዐድን" جَنَّةُ العَدْن "ጀነቱ አን-ነዒም" جَنَّةُ النَّعِيمِ "ጀነቱል መእዋ" جَنَّةُ المَأْوَىٰ እየተባለ ይጠራል።
ኢንሻሏህ ይቀጥላል......
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
የአማኝ መልካም ሥራ
ክፍል ሁለት
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
22፥77 እናንተ ያመናችሁ ሰዎች ሆይ! በስግደታችሁ አጎንብሱ፣ በግንባራችሁም ተደፉ፣ ጌታችሁንም አምልኩ፣ ትድኑ ዘንድ በጎንም ነገር ሥሩ፡፡ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا ارْكَعُوا وَاسْجُدُوا وَاعْبُدُوا رَبَّكُمْ وَافْعَلُوا الْخَيْرَ لَعَلَّكُمْ تُفْلِحُونَ ۩
አንድ ሙእሚን የአሏህ ፊት በውጥን ፈልጎ "ላ ኢላሀ ኢለል ሏህ" لَا إِلَـٰهَ إِلَّا اللَّه ብሎ በትንሳኤ ቀን ከመጣ አሏህ እሳትን በእርሱ ላይ እርም አድርጓል፦
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 81, ሐዲስ 12
ከበኒ ሣሊም አንዱ የሆነው ዒትባን ኢብኑ ማሊክ አል-አንሷሪይ እንደተረከው፦ "የአሏህ መልእክተኛ”ﷺ” ወደ እኔ መጡና እንዲህ አሉ፦ "ማንም የአሏህ ፊት በውጥን ፈልጎ "ላ ኢላሀ ኢለል ሏህ" ብሎ በትንሳኤ ቀን ከመጣ አሏህ እሳትን በእርሱ ላይ እርም አድርጓል"። قَالَ سَمِعْتُ عِتْبَانَ بْنَ مَالِكٍ الأَنْصَارِيَّ، ثُمَّ أَحَدَ بَنِي سَالِمٍ قَالَ غَدَا عَلَىَّ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم فَقَالَ " لَنْ يُوَافِيَ عَبْدٌ يَوْمَ الْقِيَامَةِ يَقُولُ لاَ إِلَهَ إِلاَّ اللَّهُ. يَبْتَغِي بِهِ وَجْهَ اللَّهِ، إِلاَّ حَرَّمَ اللَّهُ عَلَيْهِ النَّارَ ".
ያ ማለት እስካላሻረከ ድረስ ለዝንተ ዓለም በጀሀነም እሳት ውስጥ አይኖርም ማለት ነው፥ ነገር ግን ከሺርክ ውጪ ለሚሠራቸው ዐበይት ኃጢአቶች ንስሓ ካልገባ እና ለሚሠራቸው ንዑሣን ኃጢአቶች መልካም ሥራ ካልሠራ ይቀጣል፦
6፥120 እነዚያ ኃጢአትን የሚሠሩ ይሠሩት በነበሩት ነገር በእርግጥ ይቀጣሉ፡፡ نَّ الَّذِينَ يَكْسِبُونَ الْإِثْمَ سَيُجْزَوْنَ بِمَا كَانُوا يَقْتَرِفُونَ
"ዘንብ" ذَنب የሚለው ቃል "ዘነበ" ذَنَبَ ማለትም "ዓመፀ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "ዓመፅ" "ኃጢአት" ማለት ነው፥ አሏህ ያዘዘውን መልካም ሥራ አለመሥራት እና የከለከለውን ክፉ ሥራ መሥራት በእርሱ ላይ ማመፅ ስለሆነ "ኃጢአት" ይባላል። ኃጢአት "ከባኢሩ አዝ-ዘንብ" كَبَائِر الْذَنب እና "ሶጋኢሩ አዝ-ዘንብ" صَغَائِر الْذَنب ተብለው ለሁለት ይከፈላሉ፦
53፥32 እነርሱ እነዚያ የኃጢአትን ታላላቆች እና አስጸያፊዎቹን የሚርቁ ናቸው፡፡ ግን ትናንሾቹ ኃጢአቶች የሚማሩ ናቸው፡፡ ጌታህ ምሕረተ ሰፊ ነውና፡፡ الَّذِينَ يَجْتَنِبُونَ كَبَائِرَ الْإِثْمِ وَالْفَوَاحِشَ إِلَّا اللَّمَمَ ۚ إِنَّ رَبَّكَ وَاسِعُ الْمَغْفِرَةِ
4፥31 ከእርሱ ከተከለከላችሁት ታላላቆቹን ኃጢአቶች ብትርቁ ትናንሾቹን ኃጢአቶቻችሁን ከእናንተ እናብሳለን፡፡ የተከበረንም ስፍራ ገነትን እናገባችኋለን፡፡ إِن تَجْتَنِبُوا كَبَائِرَ مَا تُنْهَوْنَ عَنْهُ نُكَفِّرْ عَنكُمْ سَيِّئَاتِكُمْ وَنُدْخِلْكُم مُّدْخَلًا كَرِيمًا
"ከባኢር" كَبَائِر ማለት "ዐብይ" "ታላቅ" ማለት ሲሆን "ሶጋኢር" صَغَائِر ማለት ደግሞ "ንዑስ" "ትንሽ" ማለት ነው። "ዐበይት ኃጢአቶች" የሚባሉት ሺርክ፣ መግደል፣ መተት፣ ጥንቆላ፣ ሶላትን መተው፣ ወላጆችን አለማክበር፣ ዝምድናን መቁረጥ፣ ዝሙት፣ ወለድ ወዘተ... ናቸው፦
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 83, ሐዲስ 53
ዐብደሏህ ኢብኑ ዐምሪው እንደተረከው፦ "ነቢዩም"ﷺ" አሉ፦ "ዐበይት ኃጢአቶች በአሏህ ላይ ማሻረክ፣ ወላጆችን አለማክበር፣ ነፍስን መግደል እና የውሸት መሓላ ናቸው"። عَنْ عَبْدِ اللَّهِ بْنِ عَمْرٍو، عَنِ النَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم قَالَ " الْكَبَائِرُ الإِشْرَاكُ بِاللَّهِ، وَعُقُوقُ الْوَالِدَيْنِ، وَقَتْلُ النَّفْسِ، وَالْيَمِينُ الْغَمُوسُ ".
ዐበይት ኃጢአቶች ንስሓ ከተገባባቸው አሏህ ይቅር ይለናል እንጂ አይቀጣንም፥ ዐበይት ኃጢአቶች ተሠርቶ በንስሓ ካልተመለስን የእሳት ቅጣት ስላለ ከእሳት ቅጣት ለመዳን ብቸኛ መዳኛ ንስሓ መግባት ነው፦
8፥33 አላህም እነርሱ ይቅርታ የሚጠይቁ ሲኾኑ የሚቀጣቸው አይደለም፡፡ وَمَا كَانَ اللَّهُ مُعَذِّبَهُمْ وَهُمْ يَسْتَغْفِرُونَ
24፥31 ምእመናን ሆይ! ትድኑ ዘንድ ሁላችሁም ወደ አላህ በንስሓ ተመለሱ። وَتُوبُوا إِلَى اللَّهِ جَمِيعًا أَيُّهَ الْمُؤْمِنُونَ لَعَلَّكُمْ تُفْلِحُونَ
ኢማም ሙሥሊም መጽሐፍ 52, ሐዲስ 67
አቢ ሁረይራህ እንደተረከው፦ "ነቢዩም"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "ከእናንተ መካከል ሥራው ብቻ የሚያድነው ማንም የለም፥ ሶሓባዎችም፦ "የአሏህ መልእክተኛ ሆይ! እርሶም ቢሆኑ? አሉ። እርሳቸውም፦ "እኔም ብሆን፥ ነገር ግን አሏህ ከእርሱ በይቅርታው እና በምሕረቱ ሸፍኖኛል"። عَنْ أَبِي، هُرَيْرَةَ قَالَ قَالَ النَّبِيُّ صلى الله عليه وسلم " لَيْسَ أَحَدٌ مِنْكُمْ يُنْجِيهِ عَمَلُهُ " . قَالُوا وَلاَ أَنْتَ يَا رَسُولَ اللَّهِ قَالَ " وَلاَ أَنَا إِلاَّ أَنْ يَتَغَمَّدَنِيَ اللَّهُ مِنْهُ بِمَغْفِرَةٍ وَرَحْمَةٍ "
ክፍል ሁለት
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
22፥77 እናንተ ያመናችሁ ሰዎች ሆይ! በስግደታችሁ አጎንብሱ፣ በግንባራችሁም ተደፉ፣ ጌታችሁንም አምልኩ፣ ትድኑ ዘንድ በጎንም ነገር ሥሩ፡፡ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا ارْكَعُوا وَاسْجُدُوا وَاعْبُدُوا رَبَّكُمْ وَافْعَلُوا الْخَيْرَ لَعَلَّكُمْ تُفْلِحُونَ ۩
አንድ ሙእሚን የአሏህ ፊት በውጥን ፈልጎ "ላ ኢላሀ ኢለል ሏህ" لَا إِلَـٰهَ إِلَّا اللَّه ብሎ በትንሳኤ ቀን ከመጣ አሏህ እሳትን በእርሱ ላይ እርም አድርጓል፦
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 81, ሐዲስ 12
ከበኒ ሣሊም አንዱ የሆነው ዒትባን ኢብኑ ማሊክ አል-አንሷሪይ እንደተረከው፦ "የአሏህ መልእክተኛ”ﷺ” ወደ እኔ መጡና እንዲህ አሉ፦ "ማንም የአሏህ ፊት በውጥን ፈልጎ "ላ ኢላሀ ኢለል ሏህ" ብሎ በትንሳኤ ቀን ከመጣ አሏህ እሳትን በእርሱ ላይ እርም አድርጓል"። قَالَ سَمِعْتُ عِتْبَانَ بْنَ مَالِكٍ الأَنْصَارِيَّ، ثُمَّ أَحَدَ بَنِي سَالِمٍ قَالَ غَدَا عَلَىَّ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم فَقَالَ " لَنْ يُوَافِيَ عَبْدٌ يَوْمَ الْقِيَامَةِ يَقُولُ لاَ إِلَهَ إِلاَّ اللَّهُ. يَبْتَغِي بِهِ وَجْهَ اللَّهِ، إِلاَّ حَرَّمَ اللَّهُ عَلَيْهِ النَّارَ ".
ያ ማለት እስካላሻረከ ድረስ ለዝንተ ዓለም በጀሀነም እሳት ውስጥ አይኖርም ማለት ነው፥ ነገር ግን ከሺርክ ውጪ ለሚሠራቸው ዐበይት ኃጢአቶች ንስሓ ካልገባ እና ለሚሠራቸው ንዑሣን ኃጢአቶች መልካም ሥራ ካልሠራ ይቀጣል፦
6፥120 እነዚያ ኃጢአትን የሚሠሩ ይሠሩት በነበሩት ነገር በእርግጥ ይቀጣሉ፡፡ نَّ الَّذِينَ يَكْسِبُونَ الْإِثْمَ سَيُجْزَوْنَ بِمَا كَانُوا يَقْتَرِفُونَ
"ዘንብ" ذَنب የሚለው ቃል "ዘነበ" ذَنَبَ ማለትም "ዓመፀ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "ዓመፅ" "ኃጢአት" ማለት ነው፥ አሏህ ያዘዘውን መልካም ሥራ አለመሥራት እና የከለከለውን ክፉ ሥራ መሥራት በእርሱ ላይ ማመፅ ስለሆነ "ኃጢአት" ይባላል። ኃጢአት "ከባኢሩ አዝ-ዘንብ" كَبَائِر الْذَنب እና "ሶጋኢሩ አዝ-ዘንብ" صَغَائِر الْذَنب ተብለው ለሁለት ይከፈላሉ፦
53፥32 እነርሱ እነዚያ የኃጢአትን ታላላቆች እና አስጸያፊዎቹን የሚርቁ ናቸው፡፡ ግን ትናንሾቹ ኃጢአቶች የሚማሩ ናቸው፡፡ ጌታህ ምሕረተ ሰፊ ነውና፡፡ الَّذِينَ يَجْتَنِبُونَ كَبَائِرَ الْإِثْمِ وَالْفَوَاحِشَ إِلَّا اللَّمَمَ ۚ إِنَّ رَبَّكَ وَاسِعُ الْمَغْفِرَةِ
4፥31 ከእርሱ ከተከለከላችሁት ታላላቆቹን ኃጢአቶች ብትርቁ ትናንሾቹን ኃጢአቶቻችሁን ከእናንተ እናብሳለን፡፡ የተከበረንም ስፍራ ገነትን እናገባችኋለን፡፡ إِن تَجْتَنِبُوا كَبَائِرَ مَا تُنْهَوْنَ عَنْهُ نُكَفِّرْ عَنكُمْ سَيِّئَاتِكُمْ وَنُدْخِلْكُم مُّدْخَلًا كَرِيمًا
"ከባኢር" كَبَائِر ማለት "ዐብይ" "ታላቅ" ማለት ሲሆን "ሶጋኢር" صَغَائِر ማለት ደግሞ "ንዑስ" "ትንሽ" ማለት ነው። "ዐበይት ኃጢአቶች" የሚባሉት ሺርክ፣ መግደል፣ መተት፣ ጥንቆላ፣ ሶላትን መተው፣ ወላጆችን አለማክበር፣ ዝምድናን መቁረጥ፣ ዝሙት፣ ወለድ ወዘተ... ናቸው፦
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 83, ሐዲስ 53
ዐብደሏህ ኢብኑ ዐምሪው እንደተረከው፦ "ነቢዩም"ﷺ" አሉ፦ "ዐበይት ኃጢአቶች በአሏህ ላይ ማሻረክ፣ ወላጆችን አለማክበር፣ ነፍስን መግደል እና የውሸት መሓላ ናቸው"። عَنْ عَبْدِ اللَّهِ بْنِ عَمْرٍو، عَنِ النَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم قَالَ " الْكَبَائِرُ الإِشْرَاكُ بِاللَّهِ، وَعُقُوقُ الْوَالِدَيْنِ، وَقَتْلُ النَّفْسِ، وَالْيَمِينُ الْغَمُوسُ ".
ዐበይት ኃጢአቶች ንስሓ ከተገባባቸው አሏህ ይቅር ይለናል እንጂ አይቀጣንም፥ ዐበይት ኃጢአቶች ተሠርቶ በንስሓ ካልተመለስን የእሳት ቅጣት ስላለ ከእሳት ቅጣት ለመዳን ብቸኛ መዳኛ ንስሓ መግባት ነው፦
8፥33 አላህም እነርሱ ይቅርታ የሚጠይቁ ሲኾኑ የሚቀጣቸው አይደለም፡፡ وَمَا كَانَ اللَّهُ مُعَذِّبَهُمْ وَهُمْ يَسْتَغْفِرُونَ
24፥31 ምእመናን ሆይ! ትድኑ ዘንድ ሁላችሁም ወደ አላህ በንስሓ ተመለሱ። وَتُوبُوا إِلَى اللَّهِ جَمِيعًا أَيُّهَ الْمُؤْمِنُونَ لَعَلَّكُمْ تُفْلِحُونَ
ኢማም ሙሥሊም መጽሐፍ 52, ሐዲስ 67
አቢ ሁረይራህ እንደተረከው፦ "ነቢዩም"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "ከእናንተ መካከል ሥራው ብቻ የሚያድነው ማንም የለም፥ ሶሓባዎችም፦ "የአሏህ መልእክተኛ ሆይ! እርሶም ቢሆኑ? አሉ። እርሳቸውም፦ "እኔም ብሆን፥ ነገር ግን አሏህ ከእርሱ በይቅርታው እና በምሕረቱ ሸፍኖኛል"። عَنْ أَبِي، هُرَيْرَةَ قَالَ قَالَ النَّبِيُّ صلى الله عليه وسلم " لَيْسَ أَحَدٌ مِنْكُمْ يُنْجِيهِ عَمَلُهُ " . قَالُوا وَلاَ أَنْتَ يَا رَسُولَ اللَّهِ قَالَ " وَلاَ أَنَا إِلاَّ أَنْ يَتَغَمَّدَنِيَ اللَّهُ مِنْهُ بِمَغْفِرَةٍ وَرَحْمَةٍ "
፨ሁለተኛ የምንሠራው መልካም ሥራ ለንዑሳን ኀጢአቶች ቅጣት ማስወገጃ ነው፥ "ንዑሳን ኀጢአቶች" የሚባሉት መጥፎ ጥርጣሬ፣ አማና ማጉደል፣ ግዴለሽነት፣ ብኩንነት፣ ስስት ወዘተ.. ሲሆኑ እነዚህ ንዑሳን ኀጢአቶች ይቅር የሚባሉት በንስሓ እና መልካም ሥራ በመሥራት ነው፦
11፥114 ሶላትንም በቀን ጫፎች ከሌሊትም ክፍሎች ፈጽም፡፡ "መልካም ሥራዎች ኃጢአቶችን ያስወገድዳሉና"፡፡ وَأَقِمِ الصَّلَاةَ طَرَفَيِ النَّهَارِ وَزُلَفًا مِّنَ اللَّيْلِ ۚ إِنَّ الْحَسَنَاتِ يُذْهِبْنَ السَّيِّئَاتِ
"መልካም ሥራ" አሏህ "ሥሩ" ያለን መልካም ነገር ሲሆን እራሱ አምልኮ ነው፥ "መልካም ሥራዎች" የሚባሉት ለምሳሌ፦ ሶላት፣ ዘካህ፣ ፆም፣ ሐጅ እና በእነርሱ ውስጥ ያሉ ተግባራት እንዲሁ ሥነ ምግባር እና ግብረገብ ያቀፉ ናቸው። ለምሳሌ፦
1. ለይለቱል ቀድር በኢማን እና በኢሕቲሣብ ሶላት የቆመ ያለፈው ኃጢአቶቹ ሁሉ ይቅር ይባልለታል፦ ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 2, ሐዲስ 28
2. የዓሹራእ ቀን መጾም ያለፈውን አንድ ዓመት ኃጢአት ይሠረይለታል፦ ሡነን ኢብኑ ማጃህ መጽሐፍ 7, ሐዲስ 1810
3. በመልካም ውዱእ ያረገ፣ ከዚያም ጁሙዓህ የመጣ፣ በቅጡ የሰማ እና ያዳመጠ በጁሙዓህ እና በጁሙዓህ መካከል ያለው ኃጢአቱ ይቅር ይባልለታል፦ ኢማም ሙሥሊም መጽሐፍ 7, ሐዲስ 38
"ኃጢአቶቹ ሁሉ ይቅር ይባልለታል" "ኃጢአት ይሠረይለታል" የተባለው ንዑሣን ኃጢአትን ነው። አሏህ የሙእሚንም ክፉ ሥራቸው በመልካም ሥራቸው ይለውጣል፦
25፥70 ተጸጽቶ የተመለሰና ያመነ መልካምንም ሥራ የሠራ ሰው ብቻ ሲቀር፡፡ እነዚያም አላህ መጥፎ ሥራዎቻቸውን በመልካም ሥራዎች ይለውጣል፡፡ አላህም እጅግ መሓሪ አዛኝ ነው፡፡ إِلَّا مَن تَابَ وَآمَنَ وَعَمِلَ عَمَلًا صَالِحًا فَأُولَـٰئِكَ يُبَدِّلُ اللَّهُ سَيِّئَاتِهِمْ حَسَنَاتٍ ۗ وَكَانَ اللَّهُ غَفُورًا رَّحِيمًا
29፥7 እነዚያም ያመኑ፤ መልካሞችንም የሠሩ መጥፎዎቹን ሥራዎቻቸውን ከእነሱ ላይ እናብስላቸዋለን፡፡ በዚያም ይሠሩት በነበሩት መልካም ሥራ በእርግጥ እንመነዳቸዋለን፡፡ وَالَّذِينَ آمَنُوا وَعَمِلُوا الصَّالِحَاتِ لَنُكَفِّرَنَّ عَنْهُمْ سَيِّئَاتِهِمْ وَلَنَجْزِيَنَّهُمْ أَحْسَنَ الَّذِي كَانُوا يَعْمَلُونَ
በትንሳኤ ቀን የአማኞች ሥራ በሚዛን ተመዝኖ መልካም ሥራቸው ሚዛኑ ከከበደ በመልካም ሥራቸው ክፉ ሥራቸው ይታበስላቸዋል፥ ንዑሳን ኃጢአት ሠርቶ ከመቀጣት ለመዳን በጎ ሥራ መሥራት መስፈርት ነው፦
21፥47 በትንሣኤም ቀን ትክክለኛ ሚዛኖችን እናቆማለን፥ ማንኛይቱም ነፍስ ምንንም አትበደልም፡፡ ሥራው የሰናፍጭ ቅንጣት ያክል ቢኾንም እርሷን እናመጣታለን፥ ተቆጣጣሪዎችም በኛ በቃ፡፡ وَنَضَعُ الْمَوَازِينَ الْقِسْطَ لِيَوْمِ الْقِيَامَةِ فَلَا تُظْلَمُ نَفْسٌ شَيْئًا ۖ وَإِن كَانَ مِثْقَالَ حَبَّةٍ مِّنْ خَرْدَلٍ أَتَيْنَا بِهَا ۗ وَكَفَىٰ بِنَا حَاسِبِينَ
22፥77 እናንተ ያመናችሁ ሰዎች ሆይ! በስግደታችሁ አጎንብሱ፣ በግንባራችሁም ተደፉ፣ ጌታችሁንም አምልኩ፣ ትድኑ ዘንድ በጎንም ነገር ሥሩ፡፡ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا ارْكَعُوا وَاسْجُدُوا وَاعْبُدُوا رَبَّكُمْ وَافْعَلُوا الْخَيْرَ لَعَلَّكُمْ تُفْلِحُونَ ۩
"በጎ ሥራ ሥሩ" ብሎን ካልሠራን ኃጢአት ነው፥ አማኞች በሚሠሩት መጥፎ ሥራ ስለሚቀጡ "እራሳችሁን እና ቤተሰቦቻችሁን ከእሳት ጠብቁ" በማለት ያስጠነቅቀናል፦
5፥105 እናንተ ያመናችሁ ሆይ! እራሳችሁን ከእሳት ጠብቁ፡፡ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا عَلَيْكُمْ أَنفُسَكُمْ
66፥6 እናንተ ያመናችሁ ሆይ! እራሳችሁን እና ቤተሰቦቻችሁን መቀጣጠያዋ ሰዎች እና ደንጋዮች ከኾነች እሳት ጠብቁ፡፡ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا قُوا أَنفُسَكُمْ وَأَهْلِيكُمْ نَارًا وَقُودُهَا النَّاسُ وَالْحِجَارَةُ
"እናንተ ያመናችሁ ሆይ" መባሉ አማንያንን ቁልጭ አድርጎ እንደሚያሳይ ተመልከት! ስለዚህ ጀነት ለመግባት ቁልፉ "ላ ኢላሀ ኢለል ሏህ" لَا إِلَـٰهَ إِلَّا اللَّه ሲሆን ካመኑ በኃላ የሚሠራው መልካም ሥራ ጀነት ውስጥ ላሉት የተለያየ ደረጃዎች መግቢያ ሠበብ እና ለንዑሣን ኃጢአቶች ማስተሠሪያ እንዲሁ ከማይዘወተር የእሳት ቅጣት መዳኛ ነው። አምላካችን አሏህ ሙሕሢን ከሚላቸው ባሮቹ ያድርገን! አሚን።
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
11፥114 ሶላትንም በቀን ጫፎች ከሌሊትም ክፍሎች ፈጽም፡፡ "መልካም ሥራዎች ኃጢአቶችን ያስወገድዳሉና"፡፡ وَأَقِمِ الصَّلَاةَ طَرَفَيِ النَّهَارِ وَزُلَفًا مِّنَ اللَّيْلِ ۚ إِنَّ الْحَسَنَاتِ يُذْهِبْنَ السَّيِّئَاتِ
"መልካም ሥራ" አሏህ "ሥሩ" ያለን መልካም ነገር ሲሆን እራሱ አምልኮ ነው፥ "መልካም ሥራዎች" የሚባሉት ለምሳሌ፦ ሶላት፣ ዘካህ፣ ፆም፣ ሐጅ እና በእነርሱ ውስጥ ያሉ ተግባራት እንዲሁ ሥነ ምግባር እና ግብረገብ ያቀፉ ናቸው። ለምሳሌ፦
1. ለይለቱል ቀድር በኢማን እና በኢሕቲሣብ ሶላት የቆመ ያለፈው ኃጢአቶቹ ሁሉ ይቅር ይባልለታል፦ ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 2, ሐዲስ 28
2. የዓሹራእ ቀን መጾም ያለፈውን አንድ ዓመት ኃጢአት ይሠረይለታል፦ ሡነን ኢብኑ ማጃህ መጽሐፍ 7, ሐዲስ 1810
3. በመልካም ውዱእ ያረገ፣ ከዚያም ጁሙዓህ የመጣ፣ በቅጡ የሰማ እና ያዳመጠ በጁሙዓህ እና በጁሙዓህ መካከል ያለው ኃጢአቱ ይቅር ይባልለታል፦ ኢማም ሙሥሊም መጽሐፍ 7, ሐዲስ 38
"ኃጢአቶቹ ሁሉ ይቅር ይባልለታል" "ኃጢአት ይሠረይለታል" የተባለው ንዑሣን ኃጢአትን ነው። አሏህ የሙእሚንም ክፉ ሥራቸው በመልካም ሥራቸው ይለውጣል፦
25፥70 ተጸጽቶ የተመለሰና ያመነ መልካምንም ሥራ የሠራ ሰው ብቻ ሲቀር፡፡ እነዚያም አላህ መጥፎ ሥራዎቻቸውን በመልካም ሥራዎች ይለውጣል፡፡ አላህም እጅግ መሓሪ አዛኝ ነው፡፡ إِلَّا مَن تَابَ وَآمَنَ وَعَمِلَ عَمَلًا صَالِحًا فَأُولَـٰئِكَ يُبَدِّلُ اللَّهُ سَيِّئَاتِهِمْ حَسَنَاتٍ ۗ وَكَانَ اللَّهُ غَفُورًا رَّحِيمًا
29፥7 እነዚያም ያመኑ፤ መልካሞችንም የሠሩ መጥፎዎቹን ሥራዎቻቸውን ከእነሱ ላይ እናብስላቸዋለን፡፡ በዚያም ይሠሩት በነበሩት መልካም ሥራ በእርግጥ እንመነዳቸዋለን፡፡ وَالَّذِينَ آمَنُوا وَعَمِلُوا الصَّالِحَاتِ لَنُكَفِّرَنَّ عَنْهُمْ سَيِّئَاتِهِمْ وَلَنَجْزِيَنَّهُمْ أَحْسَنَ الَّذِي كَانُوا يَعْمَلُونَ
በትንሳኤ ቀን የአማኞች ሥራ በሚዛን ተመዝኖ መልካም ሥራቸው ሚዛኑ ከከበደ በመልካም ሥራቸው ክፉ ሥራቸው ይታበስላቸዋል፥ ንዑሳን ኃጢአት ሠርቶ ከመቀጣት ለመዳን በጎ ሥራ መሥራት መስፈርት ነው፦
21፥47 በትንሣኤም ቀን ትክክለኛ ሚዛኖችን እናቆማለን፥ ማንኛይቱም ነፍስ ምንንም አትበደልም፡፡ ሥራው የሰናፍጭ ቅንጣት ያክል ቢኾንም እርሷን እናመጣታለን፥ ተቆጣጣሪዎችም በኛ በቃ፡፡ وَنَضَعُ الْمَوَازِينَ الْقِسْطَ لِيَوْمِ الْقِيَامَةِ فَلَا تُظْلَمُ نَفْسٌ شَيْئًا ۖ وَإِن كَانَ مِثْقَالَ حَبَّةٍ مِّنْ خَرْدَلٍ أَتَيْنَا بِهَا ۗ وَكَفَىٰ بِنَا حَاسِبِينَ
22፥77 እናንተ ያመናችሁ ሰዎች ሆይ! በስግደታችሁ አጎንብሱ፣ በግንባራችሁም ተደፉ፣ ጌታችሁንም አምልኩ፣ ትድኑ ዘንድ በጎንም ነገር ሥሩ፡፡ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا ارْكَعُوا وَاسْجُدُوا وَاعْبُدُوا رَبَّكُمْ وَافْعَلُوا الْخَيْرَ لَعَلَّكُمْ تُفْلِحُونَ ۩
"በጎ ሥራ ሥሩ" ብሎን ካልሠራን ኃጢአት ነው፥ አማኞች በሚሠሩት መጥፎ ሥራ ስለሚቀጡ "እራሳችሁን እና ቤተሰቦቻችሁን ከእሳት ጠብቁ" በማለት ያስጠነቅቀናል፦
5፥105 እናንተ ያመናችሁ ሆይ! እራሳችሁን ከእሳት ጠብቁ፡፡ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا عَلَيْكُمْ أَنفُسَكُمْ
66፥6 እናንተ ያመናችሁ ሆይ! እራሳችሁን እና ቤተሰቦቻችሁን መቀጣጠያዋ ሰዎች እና ደንጋዮች ከኾነች እሳት ጠብቁ፡፡ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا قُوا أَنفُسَكُمْ وَأَهْلِيكُمْ نَارًا وَقُودُهَا النَّاسُ وَالْحِجَارَةُ
"እናንተ ያመናችሁ ሆይ" መባሉ አማንያንን ቁልጭ አድርጎ እንደሚያሳይ ተመልከት! ስለዚህ ጀነት ለመግባት ቁልፉ "ላ ኢላሀ ኢለል ሏህ" لَا إِلَـٰهَ إِلَّا اللَّه ሲሆን ካመኑ በኃላ የሚሠራው መልካም ሥራ ጀነት ውስጥ ላሉት የተለያየ ደረጃዎች መግቢያ ሠበብ እና ለንዑሣን ኃጢአቶች ማስተሠሪያ እንዲሁ ከማይዘወተር የእሳት ቅጣት መዳኛ ነው። አምላካችን አሏህ ሙሕሢን ከሚላቸው ባሮቹ ያድርገን! አሚን።
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
የከሓዲ መልካም ሥራ
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
14፥18 የእነዚያ በጌታቸው የካዱት ሰዎች ምሳሌ መልካም ሥራዎቻቸው በነፋሻ ቀን ነፋስ በእርሱ እንደ በረታችበት አመድ ነው፡፡ በሠሩት ሥራ በምንም ላይ ሊጠቀሙ አይችሉም፡፡ ይህ እርሱ ሩቅ ጥፋት ነው፡፡ مَّثَلُ الَّذِينَ كَفَرُوا بِرَبِّهِمْ ۖ أَعْمَالُهُمْ كَرَمَادٍ اشْتَدَّتْ بِهِ الرِّيحُ فِي يَوْمٍ عَاصِفٍ ۖ لَّا يَقْدِرُونَ مِمَّا كَسَبُوا عَلَىٰ شَيْءٍ ۚ ذَٰلِكَ هُوَ الضَّلَالُ الْبَعِيدُ
ከሓድያንን ጀነት እርም የሚሆንባቸው እና በጀሀነም ለዝንተ ዓለም እንዲዘወትሩ የሚዳርጋቸው የሠሩት መጥፎ ሥራ ሳይሆን ማሻረካቸው እና አለማመናቸው ነው፦
5፥72 እነሆ! በአላህ የሚያጋራ ሰው አላህ በእርሱ ላይ ገነትን በእርግጥ እርም አደረገ፡፡ መኖሪያውም እሳት ናት፡፡ ለበዳዮችም ምንም ረዳቶች የሏቸውም፡፡ إِنَّهُ مَن يُشْرِكْ بِاللَّهِ فَقَدْ حَرَّمَ اللَّهُ عَلَيْهِ الْجَنَّةَ وَمَأْوَاهُ النَّارُ ۖ وَمَا لِلظَّالِمِينَ مِنْ أَنصَارٍ
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 23, ሐዲስ 2
ዐብደሏህ"ረ.ዐ." እንደተረከው፦ "የአሏህ መልእክተኛም"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "ማንም ሰው በአሏህ ላይ ምንንም እያሻረከ የሞተ እሳት ገባ"። عَنْ عَبْدِ اللَّهِ ـ رضى الله عنه ـ قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم " مَنْ مَاتَ يُشْرِكُ بِاللَّهِ شَيْئًا دَخَلَ النَّارَ "
የላ ኢላሀ ኢለል ሏህ ቁልፍ በእጁ የያዘ ሙእሚን ምንም እንኳን ንስሓ ባልገባበት ዐቢይ ኃጢአት እና በመልካም ሥራ ባላካካሰው ንዑስ ኃጢአት ምክንያት ተቀጥቶ ሲወጣ ቅሉ ግን ሙሽሪክ ጀነት እርም ስለሆነበት ከእሳት ሊወጣ ቢፈልግም ከእርስዋ ወጪ አይደለም፦
5፥37 ከእሳት ሊወጡ ይፈልጋሉ፡፡ እነርሱም ከእርስዋ ወጪዎች አይደሉም፡፡ ለእነርሱም ዘውታሪ ቅጣት አላቸው፡፡ يُرِيدُونَ أَن يَخْرُجُوا مِنَ النَّارِ وَمَا هُم بِخَارِجِينَ مِنْهَا ۖ وَلَهُمْ عَذَابٌ مُّقِيمٌ
የዲን ሦስት ደረጃዎች ኢሥላም፣ ኢማን እና ኢሕሣን ናቸው፥ "ኢሕሣን" إِحْسَٰن የሚለው ቃል "አሕሠነ" أَحْسَنَ ማለትም "አስዋበ" "አሳመረ" ከሚለው ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "ማስዋብ" "ማሳመር" "መልካም ሥራ" ማለት ነው፦
55፥60 የበጎ ሥራ ዋጋ በጎ እንጅ ሌላ ነውን? هَلْ جَزَاءُ الْإِحْسَانِ إِلَّا الْإِحْسَانُ
እዚህ አንቀጽ ላይ "በጎ ሥራ" ለሚለው የገባው ቃል "ኢሕሣን" إِحْسَان ሲሆን "መልካም ሥራ" አሏህ ዘንድ ተቀባይነት እንዲያገኝ ሸርጦቹ ሦስት ናቸው፥ እነርሱም፦ ኢማን፣ ኢኽላስ እና ኢትባዕ ናቸው። ከሓድያን በዱንያ ላይ የሚሠሩት የሰፋና የተንሰራፋ መልካም ሥራ ከመነሻው ኢማን ስለሌለው ለሚቀጥለው ዓለም ምንም አይጠቅማቸውም፦
7፥147 እነዚያም በአንቀጾቻችንና መጨረሻይቱን ዓለም በመገናኘት ያስተባበሉት ሥራዎቻቸው ተበላሹ፡፡ ይሠሩት የነበረውን እንጂ ይመነዳሉን? وَالَّذِينَ كَذَّبُوا بِآيَاتِنَا وَلِقَاءِ الْآخِرَةِ حَبِطَتْ أَعْمَالُهُمْ ۚ هَلْ يُجْزَوْنَ إِلَّا مَا كَانُوا يَعْمَلُونَ
"ይሠሩት የነበረውን እንጂ ይመነዳሉን" የሚለው ይሰመርበት! ከሓድያን በዱንያ ላይ የሚሠሩት መልካም ሥራ በዱንያ ውስጥ ይመነዳሉ፥ ዱንያህ ለከሓዲያን ደግሞ ጀናህ ናት፦
11፥15 ቅርቢቱን ሕይወት እና ጌጧን የሚሹ የሆኑትን ሰዎች ሥራዎቻቸውን በእርሷ ውስጥ ወደ እነርሱ እንሞላላቸዋለን፡፡ እነርሱም በእርሷ ውስጥ ምንም አይጎድልባቸውም። مَن كَانَ يُرِيدُ ٱلْحَيَوٰةَ ٱلدُّنْيَا وَزِينَتَهَا نُوَفِّ إِلَيْهِمْ أَعْمَٰلَهُمْ فِيهَا وَهُمْ فِيهَا لَا يُبْخَسُونَ
ኢማም ሙሥሊም መጽሐፍ 55, ሐዲስ 1
አቢ ሁረይራህ እንደተረከው የአሏህ መልእክተኛም"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "ዱንያህ ለሙእሚን እስር ቤት ናት፥ ለከሓዲ ደግሞ ጀናህ ናት"። عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ، قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم " الدُّنْيَا سِجْنُ الْمُؤْمِنِ وَجَنَّةُ الْكَافِرِ " .
ከሓድያን በዱንያ ላይ የሚሠሩት መልካም ሥራ በጀነት ውስጥ ምንም ስለማይጠቅማቸው መልካም ሥራቸው የሚመዘንበት ሚዛን የላቸውም፦
18፥105 እነዚያ እነርሱ በጌታቸው ማስረጃዎች እና በመገናኘቱ የካዱት ናቸው፡፡ ሥራዎቻቸውም ተበላሹ፡፡ ለእነሱም በትንሣኤ ቀን ሚዛንን አናቆምላቸውም፡፡ أُولَـٰئِكَ الَّذِينَ كَفَرُوا بِآيَاتِ رَبِّهِمْ وَلِقَائِهِ فَحَبِطَتْ أَعْمَالُهُمْ فَلَا نُقِيمُ لَهُمْ يَوْمَ الْقِيَامَةِ وَزْنًا
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
14፥18 የእነዚያ በጌታቸው የካዱት ሰዎች ምሳሌ መልካም ሥራዎቻቸው በነፋሻ ቀን ነፋስ በእርሱ እንደ በረታችበት አመድ ነው፡፡ በሠሩት ሥራ በምንም ላይ ሊጠቀሙ አይችሉም፡፡ ይህ እርሱ ሩቅ ጥፋት ነው፡፡ مَّثَلُ الَّذِينَ كَفَرُوا بِرَبِّهِمْ ۖ أَعْمَالُهُمْ كَرَمَادٍ اشْتَدَّتْ بِهِ الرِّيحُ فِي يَوْمٍ عَاصِفٍ ۖ لَّا يَقْدِرُونَ مِمَّا كَسَبُوا عَلَىٰ شَيْءٍ ۚ ذَٰلِكَ هُوَ الضَّلَالُ الْبَعِيدُ
ከሓድያንን ጀነት እርም የሚሆንባቸው እና በጀሀነም ለዝንተ ዓለም እንዲዘወትሩ የሚዳርጋቸው የሠሩት መጥፎ ሥራ ሳይሆን ማሻረካቸው እና አለማመናቸው ነው፦
5፥72 እነሆ! በአላህ የሚያጋራ ሰው አላህ በእርሱ ላይ ገነትን በእርግጥ እርም አደረገ፡፡ መኖሪያውም እሳት ናት፡፡ ለበዳዮችም ምንም ረዳቶች የሏቸውም፡፡ إِنَّهُ مَن يُشْرِكْ بِاللَّهِ فَقَدْ حَرَّمَ اللَّهُ عَلَيْهِ الْجَنَّةَ وَمَأْوَاهُ النَّارُ ۖ وَمَا لِلظَّالِمِينَ مِنْ أَنصَارٍ
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 23, ሐዲስ 2
ዐብደሏህ"ረ.ዐ." እንደተረከው፦ "የአሏህ መልእክተኛም"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "ማንም ሰው በአሏህ ላይ ምንንም እያሻረከ የሞተ እሳት ገባ"። عَنْ عَبْدِ اللَّهِ ـ رضى الله عنه ـ قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم " مَنْ مَاتَ يُشْرِكُ بِاللَّهِ شَيْئًا دَخَلَ النَّارَ "
የላ ኢላሀ ኢለል ሏህ ቁልፍ በእጁ የያዘ ሙእሚን ምንም እንኳን ንስሓ ባልገባበት ዐቢይ ኃጢአት እና በመልካም ሥራ ባላካካሰው ንዑስ ኃጢአት ምክንያት ተቀጥቶ ሲወጣ ቅሉ ግን ሙሽሪክ ጀነት እርም ስለሆነበት ከእሳት ሊወጣ ቢፈልግም ከእርስዋ ወጪ አይደለም፦
5፥37 ከእሳት ሊወጡ ይፈልጋሉ፡፡ እነርሱም ከእርስዋ ወጪዎች አይደሉም፡፡ ለእነርሱም ዘውታሪ ቅጣት አላቸው፡፡ يُرِيدُونَ أَن يَخْرُجُوا مِنَ النَّارِ وَمَا هُم بِخَارِجِينَ مِنْهَا ۖ وَلَهُمْ عَذَابٌ مُّقِيمٌ
የዲን ሦስት ደረጃዎች ኢሥላም፣ ኢማን እና ኢሕሣን ናቸው፥ "ኢሕሣን" إِحْسَٰن የሚለው ቃል "አሕሠነ" أَحْسَنَ ማለትም "አስዋበ" "አሳመረ" ከሚለው ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "ማስዋብ" "ማሳመር" "መልካም ሥራ" ማለት ነው፦
55፥60 የበጎ ሥራ ዋጋ በጎ እንጅ ሌላ ነውን? هَلْ جَزَاءُ الْإِحْسَانِ إِلَّا الْإِحْسَانُ
እዚህ አንቀጽ ላይ "በጎ ሥራ" ለሚለው የገባው ቃል "ኢሕሣን" إِحْسَان ሲሆን "መልካም ሥራ" አሏህ ዘንድ ተቀባይነት እንዲያገኝ ሸርጦቹ ሦስት ናቸው፥ እነርሱም፦ ኢማን፣ ኢኽላስ እና ኢትባዕ ናቸው። ከሓድያን በዱንያ ላይ የሚሠሩት የሰፋና የተንሰራፋ መልካም ሥራ ከመነሻው ኢማን ስለሌለው ለሚቀጥለው ዓለም ምንም አይጠቅማቸውም፦
7፥147 እነዚያም በአንቀጾቻችንና መጨረሻይቱን ዓለም በመገናኘት ያስተባበሉት ሥራዎቻቸው ተበላሹ፡፡ ይሠሩት የነበረውን እንጂ ይመነዳሉን? وَالَّذِينَ كَذَّبُوا بِآيَاتِنَا وَلِقَاءِ الْآخِرَةِ حَبِطَتْ أَعْمَالُهُمْ ۚ هَلْ يُجْزَوْنَ إِلَّا مَا كَانُوا يَعْمَلُونَ
"ይሠሩት የነበረውን እንጂ ይመነዳሉን" የሚለው ይሰመርበት! ከሓድያን በዱንያ ላይ የሚሠሩት መልካም ሥራ በዱንያ ውስጥ ይመነዳሉ፥ ዱንያህ ለከሓዲያን ደግሞ ጀናህ ናት፦
11፥15 ቅርቢቱን ሕይወት እና ጌጧን የሚሹ የሆኑትን ሰዎች ሥራዎቻቸውን በእርሷ ውስጥ ወደ እነርሱ እንሞላላቸዋለን፡፡ እነርሱም በእርሷ ውስጥ ምንም አይጎድልባቸውም። مَن كَانَ يُرِيدُ ٱلْحَيَوٰةَ ٱلدُّنْيَا وَزِينَتَهَا نُوَفِّ إِلَيْهِمْ أَعْمَٰلَهُمْ فِيهَا وَهُمْ فِيهَا لَا يُبْخَسُونَ
ኢማም ሙሥሊም መጽሐፍ 55, ሐዲስ 1
አቢ ሁረይራህ እንደተረከው የአሏህ መልእክተኛም"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "ዱንያህ ለሙእሚን እስር ቤት ናት፥ ለከሓዲ ደግሞ ጀናህ ናት"። عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ، قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم " الدُّنْيَا سِجْنُ الْمُؤْمِنِ وَجَنَّةُ الْكَافِرِ " .
ከሓድያን በዱንያ ላይ የሚሠሩት መልካም ሥራ በጀነት ውስጥ ምንም ስለማይጠቅማቸው መልካም ሥራቸው የሚመዘንበት ሚዛን የላቸውም፦
18፥105 እነዚያ እነርሱ በጌታቸው ማስረጃዎች እና በመገናኘቱ የካዱት ናቸው፡፡ ሥራዎቻቸውም ተበላሹ፡፡ ለእነሱም በትንሣኤ ቀን ሚዛንን አናቆምላቸውም፡፡ أُولَـٰئِكَ الَّذِينَ كَفَرُوا بِآيَاتِ رَبِّهِمْ وَلِقَائِهِ فَحَبِطَتْ أَعْمَالُهُمْ فَلَا نُقِيمُ لَهُمْ يَوْمَ الْقِيَامَةِ وَزْنًا
አሏህ ኩፋሮችን የሚቀጣቸው መልካም ሥራ ስላልሠሩ ሳይሆን መልካም ሥራቸው ያለ ኢማን ስለሆነ አይጠቅማቸው፥ በመጨረሻይቱ ዓለም ለእነርሱ ከእሳት በቀር ሌላ የሌላቸው ናቸው፦
8፥14 ለከሓዲዎችም የእሳት ቅጣት በእርግጥ አለባቸው፡፡ وَأَنَّ لِلْكَافِرِينَ عَذَابَ النَّارِ
11፥16 እነዚያ እነርሱ በመጨረሻይቱ ዓለም ለእነርሱ ከእሳት በቀር የሌላቸው ናቸው፡፡ የሠሩትም ሥራ በእርሷ ውስጥ ተበላሸ፡፡ በቅርቢቱ ዓለም ይሠሩት የነበሩትም በጎ ሥራ ብልሹ ነው፡፡ أُولَـٰئِكَ الَّذِينَ لَيْسَ لَهُمْ فِي الْآخِرَةِ إِلَّا النَّارُ ۖ وَحَبِطَ مَا صَنَعُوا فِيهَا وَبَاطِلٌ مَّا كَانُوا يَعْمَلُونَ
24፥39 እነዚያም የካዱት ሰዎች መልካም ሥራዎቻቸው በበረሃ ሜዳ እንዳለ ሲሪብዱ የጠማው ሰው "ውኃ ነው" ብሎ እንደሚያስበው በመጣውም ጊዜ ምንም ነገር ኾኖ እንደማያገኘው ነው፡፡ وَالَّذِينَ كَفَرُوا أَعْمَالُهُمْ كَسَرَابٍ بِقِيعَةٍ يَحْسَبُهُ الظَّمْآنُ مَاءً حَتَّىٰ إِذَا جَاءَهُ لَمْ يَجِدْهُ شَيْئًا وَوَجَدَ اللَّهَ عِندَهُ فَوَفَّاهُ حِسَابَهُ ۗ وَاللَّهُ سَرِيعُ الْحِسَابِ
እዚህ አንቀጽ ላይ "ሲብሪድ" ተብሎ የተቀመጠው ቃል "ሠራብ" سَرَاب ሲሆን ሲቀርቡት ልክ እንደ ጉም ባዶ ነገር ቅሉ ግን በሩቅ በበረሃ ላይ በቀትር ወቅት ሲያዩት የተንጣለለ ውኃ የሚመስል "ነጸብራቅ"mirage" ነው፥ የከሓድያን መልካም ሥራዎቻቸው በተመሳሳይ ያለ ኢማን ስለሆነ አሏህ የፍርዱ ቀን የተበተነ ትንቢያ ያደርገዋል። በሠሩት ሥራ በምንም ላይ ሊጠቀሙ አይችሉም፥ ይህ እርሱ ሩቅ ጥፋት ነው፦
25፥23 ከሥራም ወደ ሠሩት እናስባለን፡፡ የተበተነ ትቢያም እናደርገዋለን፡፡ وَقَدِمْنَا إِلَىٰ مَا عَمِلُوا مِنْ عَمَلٍ فَجَعَلْنَاهُ هَبَاءً مَّنثُورًا
14፥18 የእነዚያ በጌታቸው የካዱት ሰዎች ምሳሌ መልካም ሥራዎቻቸው በነፋሻ ቀን ነፋስ በእርሱ እንደ በረታችበት አመድ ነው፡፡ በሠሩት ሥራ በምንም ላይ ሊጠቀሙ አይችሉም፡፡ ይህ እርሱ ሩቅ ጥፋት ነው፡፡ مَّثَلُ الَّذِينَ كَفَرُوا بِرَبِّهِمْ ۖ أَعْمَالُهُمْ كَرَمَادٍ اشْتَدَّتْ بِهِ الرِّيحُ فِي يَوْمٍ عَاصِفٍ ۖ لَّا يَقْدِرُونَ مِمَّا كَسَبُوا عَلَىٰ شَيْءٍ ۚ ذَٰلِكَ هُوَ الضَّلَالُ الْبَعِيدُ
አምላካችን አሏህ ከሺርክ እና ከኩፍር ይጠብቀን! አሚን።
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
8፥14 ለከሓዲዎችም የእሳት ቅጣት በእርግጥ አለባቸው፡፡ وَأَنَّ لِلْكَافِرِينَ عَذَابَ النَّارِ
11፥16 እነዚያ እነርሱ በመጨረሻይቱ ዓለም ለእነርሱ ከእሳት በቀር የሌላቸው ናቸው፡፡ የሠሩትም ሥራ በእርሷ ውስጥ ተበላሸ፡፡ በቅርቢቱ ዓለም ይሠሩት የነበሩትም በጎ ሥራ ብልሹ ነው፡፡ أُولَـٰئِكَ الَّذِينَ لَيْسَ لَهُمْ فِي الْآخِرَةِ إِلَّا النَّارُ ۖ وَحَبِطَ مَا صَنَعُوا فِيهَا وَبَاطِلٌ مَّا كَانُوا يَعْمَلُونَ
24፥39 እነዚያም የካዱት ሰዎች መልካም ሥራዎቻቸው በበረሃ ሜዳ እንዳለ ሲሪብዱ የጠማው ሰው "ውኃ ነው" ብሎ እንደሚያስበው በመጣውም ጊዜ ምንም ነገር ኾኖ እንደማያገኘው ነው፡፡ وَالَّذِينَ كَفَرُوا أَعْمَالُهُمْ كَسَرَابٍ بِقِيعَةٍ يَحْسَبُهُ الظَّمْآنُ مَاءً حَتَّىٰ إِذَا جَاءَهُ لَمْ يَجِدْهُ شَيْئًا وَوَجَدَ اللَّهَ عِندَهُ فَوَفَّاهُ حِسَابَهُ ۗ وَاللَّهُ سَرِيعُ الْحِسَابِ
እዚህ አንቀጽ ላይ "ሲብሪድ" ተብሎ የተቀመጠው ቃል "ሠራብ" سَرَاب ሲሆን ሲቀርቡት ልክ እንደ ጉም ባዶ ነገር ቅሉ ግን በሩቅ በበረሃ ላይ በቀትር ወቅት ሲያዩት የተንጣለለ ውኃ የሚመስል "ነጸብራቅ"mirage" ነው፥ የከሓድያን መልካም ሥራዎቻቸው በተመሳሳይ ያለ ኢማን ስለሆነ አሏህ የፍርዱ ቀን የተበተነ ትንቢያ ያደርገዋል። በሠሩት ሥራ በምንም ላይ ሊጠቀሙ አይችሉም፥ ይህ እርሱ ሩቅ ጥፋት ነው፦
25፥23 ከሥራም ወደ ሠሩት እናስባለን፡፡ የተበተነ ትቢያም እናደርገዋለን፡፡ وَقَدِمْنَا إِلَىٰ مَا عَمِلُوا مِنْ عَمَلٍ فَجَعَلْنَاهُ هَبَاءً مَّنثُورًا
14፥18 የእነዚያ በጌታቸው የካዱት ሰዎች ምሳሌ መልካም ሥራዎቻቸው በነፋሻ ቀን ነፋስ በእርሱ እንደ በረታችበት አመድ ነው፡፡ በሠሩት ሥራ በምንም ላይ ሊጠቀሙ አይችሉም፡፡ ይህ እርሱ ሩቅ ጥፋት ነው፡፡ مَّثَلُ الَّذِينَ كَفَرُوا بِرَبِّهِمْ ۖ أَعْمَالُهُمْ كَرَمَادٍ اشْتَدَّتْ بِهِ الرِّيحُ فِي يَوْمٍ عَاصِفٍ ۖ لَّا يَقْدِرُونَ مِمَّا كَسَبُوا عَلَىٰ شَيْءٍ ۚ ذَٰلِكَ هُوَ الضَّلَالُ الْبَعِيدُ
አምላካችን አሏህ ከሺርክ እና ከኩፍር ይጠብቀን! አሚን።
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
የአሏህ ፍትሓዊነት
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
18፥49 ጌታህም አንድንም አይበድልም፡፡ وَلَا يَظْلِمُ رَبُّكَ أَحَدًا
አምላካችን አሏህ ፍትሓዊ አምላክ ሰለሆነ ማንንም አይበድልም፥ “ዘራህ” ذَرَّة ማለት “ቅንጣት”atom” ማለት ሲሆን አሏህ ቅንጣት ታክል ማንንም አይበድልም። ነገር ግን ሰው እራሱን የሚበድነው ማመን እና መታዘዝ ሲችል በመካድ እና በማመጽ ነው፦
18፥49 ጌታህም አንድንም አይበድልም፡፡ وَلَا يَظْلِمُ رَبُّكَ أَحَدًا
4፥40 አላህ የብናኝን ክብደት ያህል አይበድልም፡፡ إِنَّ اللَّهَ لَا يَظْلِمُ مِثْقَالَ ذَرَّةٍ
10፥44 አላህ ሰዎችን ምንም አይበድልም፡፡ ግን ሰዎች እራሳቸውን ይበድላሉ፡፡ إِنَّ اللَّهَ لَا يَظْلِمُ النَّاسَ شَيْئًا وَلَـٰكِنَّ النَّاسَ أَنفُسَهُمْ يَظْلِمُونَ
ባለማወቅ የሚሠራ መጥፎ ሥራ “ስህተት” ሲባል በመርሳት የማይሠራ መልካም ሥራ “ግድፈት” ይባላል፥ አሏህ ሰዎች ባለማወቅ በሠሩት ስህተት ሆነ በመርሳት በማይሠሩት ግድፈት አይቀጣም፦
2፥286 “ጌታችን ሆይ! ”ብንረሳ ወይም ብንስት አትቅጣን” በሉ፡፡ رَبَّنَا لَا تُؤَاخِذْنَا إِن نَّسِينَا أَوْ أَخْطَأْنَ
33፥5 በእርሱ በተሳሳታችሁበትም ነገርም በእናንተ ላይ ኃጢአት የለባችሁም፥ ግን ልቦቻችሁ ዐዉቀው በሠሩት ኃጢአት አለባችሁ”። አላህም መሃሪ አዛኝ ነው። وَلَيْسَ عَلَيْكُمْ جُنَاحٌۭ فِيمَآ أَخْطَأْتُم بِهِۦ وَلَٰكِن مَّا تَعَمَّدَتْ قُلُوبُكُمْ ۚ وَكَانَ ٱللَّهُ غَفُورًۭا رَّحِيمًا
“ብንረሳ” ማለት መሥራቱ ግዴታ የሆነ መልካም ሥራ በመርሳት መግደፍ ሲሆን “ብንስት” ማለት መሥራቱ ክልክል የሆነ መጥፎ ሥራ ባለማወቅ መሳሳት ነው። በተሳሳትንበት ነገር በእኛ ላይ ኃጢአት የለብንም፥ ቅሉ ግን ልባችን እያወቀው በሠራነው መጥፎ ሥራ ኃጢአት አለበት። ሰው ድርሻው በሌለበት እና ጣልቃ ገብ ባልሆነበት ጉዳይ ተገዶ ነውና የተገደዱበት ነገር አያስጠይቅም አያስቀጣም፦
2፥173 ሽፍታ እና ወሰን አላፊ ሳይኾን ለመብላት "የተገደደ ሰውም በእርሱ ላይ ኃጢኣት የለበትም"፥ አላህ መሓሪ አዛኝ ነውና፡፡ فَمَنِ اضْطُرَّ غَيْرَ بَاغٍ وَلَا عَادٍ فَلَا إِثْمَ عَلَيْهِ ۚ إِنَّ اللَّهَ غَفُورٌ رَّحِيمٌ
ሡነን ኢብኑ ማጃህ መጽሐፍ 10, ሐዲስ 2123
ኢብኑ ዐባሥ እንደተረከው፦ “ነቢዩም”ﷺ” አሉ፦ ”አላህ በኡማዬ ላይ ስህተት፣ መርሳት እና የገተደዱበትን ነገር አንስቷል”። عَنِ ابْنِ عَبَّاسٍ، عَنِ النَّبِيِّ ـ صلى الله عليه وسلم ـ قَالَ “ إِنَّ اللَّهَ وَضَعَ عَنْ أُمَّتِي الْخَطَأَ وَالنِّسْيَانَ وَمَا اسْتُكْرِهُوا عَلَيْهِ
“ውሥዕ” وُسْع ማለት “ችሎታ” ማለት ሲሆን ሰው አሏህ “አድርግ” ብሎ ያዘዘውን የማድረግ እና “አታድርግ” ብሎ የከለከውን ያለማድረግ ችሎታ እና ዐቅም ያሳያል፥ ጌታችን አሏህ ፍትሓዊ ስለሆነ ማንኛይቱንም ነፍስ ችሎታዋን እንጂ አያስገድድም፦
23፥62 ማንኛይቱንም ነፍስ ችሎታዋን እንጂ አናስገድዳትም፡፡ وَلَا نُكَلِّفُ نَفْسًا إِلَّا وُسْعَهَا
“ኪራመን ካቲቢን” كِرَامًا كَاتِبِين ማለት “የተከበሩ ጸሐፊዎች” ማለት ሲሆን እነዚህ ጸሐፊዎች በእያንዳንዱ ሰው ቀኝ እና ግራ ያሉ ሁለት መላእክት ናቸው፥ በቀኝ ያለው መልአክ ሠናይ ተግባራትን በብዕር ሲመዘግብ በግራ ያለው መልአክ ደግሞ እኩይ ተግባራትን በብዕር ይመዘግባል። እነዚህ መላእክት በእንቅልፍ ልብ፣ በዕብደት እና በእንጭጭነት የሚደረግ ሥራ አይመዘግቡትም፦
68፥1 “ኑን”፤ በብርዕ እምላለሁ፥ በዚያም በሚጽፉት”። نٓ ۚ وَٱلْقَلَمِ وَمَا يَسْطُرُونَ
ሡነን አቢ ዳውድ መጽሐፍ 40, ሐዲስ 48
ዓኢሻህ "ረ.ዐ." እንደተረከው፦ "የአላህ መልእክተኛ”ﷺ” እንዲህ አሉ፦ "ብዕር ከሦስት ሰዎች ተነስቷል። እነርሱም፦ የተኛ ሰው እስኪነሳ ድረስ፣ ዕብደ ወደ ዐቅሉ እስኪመለስ ድረስ፣ ልጅ እስኪጎሎብት ድረስ"። عَنْ عَائِشَةَ، رضى الله عنها أَنَّ رَسُولَ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم قَالَ " رُفِعَ الْقَلَمُ عَنْ ثَلاَثَةٍ عَنِ النَّائِمِ حَتَّى يَسْتَيْقِظَ وَعَنِ الْمُبْتَلَى حَتَّى يَبْرَأَ وَعَنِ الصَّبِيِّ حَتَّى يَكْبَرَ
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
18፥49 ጌታህም አንድንም አይበድልም፡፡ وَلَا يَظْلِمُ رَبُّكَ أَحَدًا
አምላካችን አሏህ ፍትሓዊ አምላክ ሰለሆነ ማንንም አይበድልም፥ “ዘራህ” ذَرَّة ማለት “ቅንጣት”atom” ማለት ሲሆን አሏህ ቅንጣት ታክል ማንንም አይበድልም። ነገር ግን ሰው እራሱን የሚበድነው ማመን እና መታዘዝ ሲችል በመካድ እና በማመጽ ነው፦
18፥49 ጌታህም አንድንም አይበድልም፡፡ وَلَا يَظْلِمُ رَبُّكَ أَحَدًا
4፥40 አላህ የብናኝን ክብደት ያህል አይበድልም፡፡ إِنَّ اللَّهَ لَا يَظْلِمُ مِثْقَالَ ذَرَّةٍ
10፥44 አላህ ሰዎችን ምንም አይበድልም፡፡ ግን ሰዎች እራሳቸውን ይበድላሉ፡፡ إِنَّ اللَّهَ لَا يَظْلِمُ النَّاسَ شَيْئًا وَلَـٰكِنَّ النَّاسَ أَنفُسَهُمْ يَظْلِمُونَ
ባለማወቅ የሚሠራ መጥፎ ሥራ “ስህተት” ሲባል በመርሳት የማይሠራ መልካም ሥራ “ግድፈት” ይባላል፥ አሏህ ሰዎች ባለማወቅ በሠሩት ስህተት ሆነ በመርሳት በማይሠሩት ግድፈት አይቀጣም፦
2፥286 “ጌታችን ሆይ! ”ብንረሳ ወይም ብንስት አትቅጣን” በሉ፡፡ رَبَّنَا لَا تُؤَاخِذْنَا إِن نَّسِينَا أَوْ أَخْطَأْنَ
33፥5 በእርሱ በተሳሳታችሁበትም ነገርም በእናንተ ላይ ኃጢአት የለባችሁም፥ ግን ልቦቻችሁ ዐዉቀው በሠሩት ኃጢአት አለባችሁ”። አላህም መሃሪ አዛኝ ነው። وَلَيْسَ عَلَيْكُمْ جُنَاحٌۭ فِيمَآ أَخْطَأْتُم بِهِۦ وَلَٰكِن مَّا تَعَمَّدَتْ قُلُوبُكُمْ ۚ وَكَانَ ٱللَّهُ غَفُورًۭا رَّحِيمًا
“ብንረሳ” ማለት መሥራቱ ግዴታ የሆነ መልካም ሥራ በመርሳት መግደፍ ሲሆን “ብንስት” ማለት መሥራቱ ክልክል የሆነ መጥፎ ሥራ ባለማወቅ መሳሳት ነው። በተሳሳትንበት ነገር በእኛ ላይ ኃጢአት የለብንም፥ ቅሉ ግን ልባችን እያወቀው በሠራነው መጥፎ ሥራ ኃጢአት አለበት። ሰው ድርሻው በሌለበት እና ጣልቃ ገብ ባልሆነበት ጉዳይ ተገዶ ነውና የተገደዱበት ነገር አያስጠይቅም አያስቀጣም፦
2፥173 ሽፍታ እና ወሰን አላፊ ሳይኾን ለመብላት "የተገደደ ሰውም በእርሱ ላይ ኃጢኣት የለበትም"፥ አላህ መሓሪ አዛኝ ነውና፡፡ فَمَنِ اضْطُرَّ غَيْرَ بَاغٍ وَلَا عَادٍ فَلَا إِثْمَ عَلَيْهِ ۚ إِنَّ اللَّهَ غَفُورٌ رَّحِيمٌ
ሡነን ኢብኑ ማጃህ መጽሐፍ 10, ሐዲስ 2123
ኢብኑ ዐባሥ እንደተረከው፦ “ነቢዩም”ﷺ” አሉ፦ ”አላህ በኡማዬ ላይ ስህተት፣ መርሳት እና የገተደዱበትን ነገር አንስቷል”። عَنِ ابْنِ عَبَّاسٍ، عَنِ النَّبِيِّ ـ صلى الله عليه وسلم ـ قَالَ “ إِنَّ اللَّهَ وَضَعَ عَنْ أُمَّتِي الْخَطَأَ وَالنِّسْيَانَ وَمَا اسْتُكْرِهُوا عَلَيْهِ
“ውሥዕ” وُسْع ማለት “ችሎታ” ማለት ሲሆን ሰው አሏህ “አድርግ” ብሎ ያዘዘውን የማድረግ እና “አታድርግ” ብሎ የከለከውን ያለማድረግ ችሎታ እና ዐቅም ያሳያል፥ ጌታችን አሏህ ፍትሓዊ ስለሆነ ማንኛይቱንም ነፍስ ችሎታዋን እንጂ አያስገድድም፦
23፥62 ማንኛይቱንም ነፍስ ችሎታዋን እንጂ አናስገድዳትም፡፡ وَلَا نُكَلِّفُ نَفْسًا إِلَّا وُسْعَهَا
“ኪራመን ካቲቢን” كِرَامًا كَاتِبِين ማለት “የተከበሩ ጸሐፊዎች” ማለት ሲሆን እነዚህ ጸሐፊዎች በእያንዳንዱ ሰው ቀኝ እና ግራ ያሉ ሁለት መላእክት ናቸው፥ በቀኝ ያለው መልአክ ሠናይ ተግባራትን በብዕር ሲመዘግብ በግራ ያለው መልአክ ደግሞ እኩይ ተግባራትን በብዕር ይመዘግባል። እነዚህ መላእክት በእንቅልፍ ልብ፣ በዕብደት እና በእንጭጭነት የሚደረግ ሥራ አይመዘግቡትም፦
68፥1 “ኑን”፤ በብርዕ እምላለሁ፥ በዚያም በሚጽፉት”። نٓ ۚ وَٱلْقَلَمِ وَمَا يَسْطُرُونَ
ሡነን አቢ ዳውድ መጽሐፍ 40, ሐዲስ 48
ዓኢሻህ "ረ.ዐ." እንደተረከው፦ "የአላህ መልእክተኛ”ﷺ” እንዲህ አሉ፦ "ብዕር ከሦስት ሰዎች ተነስቷል። እነርሱም፦ የተኛ ሰው እስኪነሳ ድረስ፣ ዕብደ ወደ ዐቅሉ እስኪመለስ ድረስ፣ ልጅ እስኪጎሎብት ድረስ"። عَنْ عَائِشَةَ، رضى الله عنها أَنَّ رَسُولَ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم قَالَ " رُفِعَ الْقَلَمُ عَنْ ثَلاَثَةٍ عَنِ النَّائِمِ حَتَّى يَسْتَيْقِظَ وَعَنِ الْمُبْتَلَى حَتَّى يَبْرَأَ وَعَنِ الصَّبِيِّ حَتَّى يَكْبَرَ
ይህ የአሏህ ፍትሓዊነት ምን ያህል ጥልቅ እና ምጥቅ መሆኑን የሚያሳይ ነው፥ የተመራ ሰው የሚመራው ለራሱ ብቻ ነው። የጠመመም ሰው የሚሚጠመው ጉዳቱ በእርሷ ላይ ነው፥ ተሸካሚም ነፍስ የሌላይቱን ነፍስ ኃጢኣት አትሸከምም፡፡ እንደውም አንድ የአሏህ መልእክተኛ ይዞት የመጣውን መልእክት ያልሰማ አይቀጣም፦
17፥15 የተመራ ሰው የሚመራው ለራሱ ብቻ ነው፥ የጠመመም ሰው የሚሚጠመው ጉዳቱ በእርሷ ላይ ነው፡፡ ተሸካሚም ነፍስ የሌላይቱን ነፍስ ኃጢኣት አትሸከምም፡፡ መልእክተኛንም እስከምንልክ ድረስ የምንቀጣ አይደለንም፡፡ مَّنِ اهْتَدَىٰ فَإِنَّمَا يَهْتَدِي لِنَفْسِهِ ۖ وَمَن ضَلَّ فَإِنَّمَا يَضِلُّ عَلَيْهَا ۚ وَلَا تَزِرُ وَازِرَةٌ وِزْرَ أُخْرَىٰ ۗ وَمَا كُنَّا مُعَذِّبِينَ حَتَّىٰ نَبْعَثَ رَسُولًا
"መልእክተኛንም እስከምንልክ ድረስ የምንቀጣ አይደለንም" የሚለው ይሰመርበት! "ፈህም" فَهْم የሚለው ቃል "ፈሂመ" فَهِمَ ማለትም "ተረዳ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "መረዳት"understanding" ማለት ነው፥ "መዕና" مَعْنًى የሚለው ቃል "ዐነ" عَنَى ማለትም "ተረጎመ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "ትርጉም"meaning" ማለት ነው። አንድ ሰው መልእክተኛ ይዞት የመጣውን መልእክት አመመስማት ብቻ ሳይሆን የመልእክቱን ፈህም እና መዕና ካላወቀ አይቀጣም፥ ይህ "ዑዝር ቢል-ጀህል" عُذْر بِالجَهْل ነውና።
"ኒያህ" نِيَّة የሚለው ቃል "ነዋ" نَوَى ማለትም "ወጠነ" ከሚለው ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "ውጥን"intention" ማለት ነው። ሥራ የሚለካው በኒያህ ነው፥ ማንኛውምንም ሰው የነየተውን ያገኛል። የፍርዱ ቀን ሰዎች ተቀስቅሰው ምንዳ እና ፍዳ የሚበየንባቸው በነየቱት ኒያህ ነው፦
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 2, ሐዲስ 47
ዑመር እንደተረከው፦ "የአሏህ መልክተኛ"ﷺ" እንዲህ ብለዋል፦ "ሥራ የሚለካው በኒያህ ነው፥ ማንኛውምንም ሰው የነየተውን ያገኛል። عَنْ عُمَرَ، أَنَّ رَسُولَ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم قَالَ “ الأَعْمَالُ بِالنِّيَّةِ، وَلِكُلِّ امْرِئٍ مَا نَوَى
ሡነን ኢብኑ ማጃህ መጽሐፍ 37, ሐዲስ 4370
አቢ ሁራይራህ እንደተረከው፦ "የአሏህ መልእክተኛ"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "ሰዎች ተቀስቅሰው የሚበየንባቸው በነየቱት ነው"። عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ، قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ ـ صلى الله عليه وسلم ـ : “ إِنَّمَا يُبْعَثُ النَّاسُ عَلَى نِيَّاتِهِمْ
ሰዎች የምንፈርደው በምላስ በተነገረን እና በውጫዊ አካል በሚደረገው ድርጊት እንጂ በልብ ላይ በተቀመጠው ኒያህ አይደለም፥ በፍርዱ ቀን በሁሉም ላይ በእውነት እና በትክክሉ ፈራጁ አሏህ ነው፦
34፥26 «ጌታችን በመካከላችን ይሰበስባል፡፡ ከዚያም በመካከላችን በእውነት ይፈርዳል፡፡ እርሱም በትክክል ፈራጁ ዐዋቂው ነው» በላቸው፡፡ قُلْ يَجْمَعُ بَيْنَنَا رَبُّنَا ثُمَّ يَفْتَحُ بَيْنَنَا بِالْحَقِّ وَهُوَ الْفَتَّاحُ الْعَلِيمُ
አምላካችን አሏህ የእርሱን ፍትሕ ከሚያስተነትኑት ያድርገን! አሚን።
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
17፥15 የተመራ ሰው የሚመራው ለራሱ ብቻ ነው፥ የጠመመም ሰው የሚሚጠመው ጉዳቱ በእርሷ ላይ ነው፡፡ ተሸካሚም ነፍስ የሌላይቱን ነፍስ ኃጢኣት አትሸከምም፡፡ መልእክተኛንም እስከምንልክ ድረስ የምንቀጣ አይደለንም፡፡ مَّنِ اهْتَدَىٰ فَإِنَّمَا يَهْتَدِي لِنَفْسِهِ ۖ وَمَن ضَلَّ فَإِنَّمَا يَضِلُّ عَلَيْهَا ۚ وَلَا تَزِرُ وَازِرَةٌ وِزْرَ أُخْرَىٰ ۗ وَمَا كُنَّا مُعَذِّبِينَ حَتَّىٰ نَبْعَثَ رَسُولًا
"መልእክተኛንም እስከምንልክ ድረስ የምንቀጣ አይደለንም" የሚለው ይሰመርበት! "ፈህም" فَهْم የሚለው ቃል "ፈሂመ" فَهِمَ ማለትም "ተረዳ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "መረዳት"understanding" ማለት ነው፥ "መዕና" مَعْنًى የሚለው ቃል "ዐነ" عَنَى ማለትም "ተረጎመ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "ትርጉም"meaning" ማለት ነው። አንድ ሰው መልእክተኛ ይዞት የመጣውን መልእክት አመመስማት ብቻ ሳይሆን የመልእክቱን ፈህም እና መዕና ካላወቀ አይቀጣም፥ ይህ "ዑዝር ቢል-ጀህል" عُذْر بِالجَهْل ነውና።
"ኒያህ" نِيَّة የሚለው ቃል "ነዋ" نَوَى ማለትም "ወጠነ" ከሚለው ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "ውጥን"intention" ማለት ነው። ሥራ የሚለካው በኒያህ ነው፥ ማንኛውምንም ሰው የነየተውን ያገኛል። የፍርዱ ቀን ሰዎች ተቀስቅሰው ምንዳ እና ፍዳ የሚበየንባቸው በነየቱት ኒያህ ነው፦
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 2, ሐዲስ 47
ዑመር እንደተረከው፦ "የአሏህ መልክተኛ"ﷺ" እንዲህ ብለዋል፦ "ሥራ የሚለካው በኒያህ ነው፥ ማንኛውምንም ሰው የነየተውን ያገኛል። عَنْ عُمَرَ، أَنَّ رَسُولَ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم قَالَ “ الأَعْمَالُ بِالنِّيَّةِ، وَلِكُلِّ امْرِئٍ مَا نَوَى
ሡነን ኢብኑ ማጃህ መጽሐፍ 37, ሐዲስ 4370
አቢ ሁራይራህ እንደተረከው፦ "የአሏህ መልእክተኛ"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "ሰዎች ተቀስቅሰው የሚበየንባቸው በነየቱት ነው"። عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ، قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ ـ صلى الله عليه وسلم ـ : “ إِنَّمَا يُبْعَثُ النَّاسُ عَلَى نِيَّاتِهِمْ
ሰዎች የምንፈርደው በምላስ በተነገረን እና በውጫዊ አካል በሚደረገው ድርጊት እንጂ በልብ ላይ በተቀመጠው ኒያህ አይደለም፥ በፍርዱ ቀን በሁሉም ላይ በእውነት እና በትክክሉ ፈራጁ አሏህ ነው፦
34፥26 «ጌታችን በመካከላችን ይሰበስባል፡፡ ከዚያም በመካከላችን በእውነት ይፈርዳል፡፡ እርሱም በትክክል ፈራጁ ዐዋቂው ነው» በላቸው፡፡ قُلْ يَجْمَعُ بَيْنَنَا رَبُّنَا ثُمَّ يَفْتَحُ بَيْنَنَا بِالْحَقِّ وَهُوَ الْفَتَّاحُ الْعَلِيمُ
አምላካችን አሏህ የእርሱን ፍትሕ ከሚያስተነትኑት ያድርገን! አሚን።
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
የአሏህ ህልውና
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
22፥6 ይህ አላህ እርሱ መኖሩ የተረጋገጠ፣ እርሱም ሙታንን ሕያው የሚያደርግ፣ እርሱም በነገሩ ሁሉ ላይ ቻይ በመሆኑ ነው፡፡ ذَٰلِكَ بِأَنَّ اللَّهَ هُوَ الْحَقُّ وَأَنَّهُ يُحْيِي الْمَوْتَىٰ وَأَنَّهُ عَلَىٰ كُلِّ شَيْءٍ قَدِيرٌ
በአንድ ወቅት የነገረ ልቦና ምሁር ሲይግመን ፍሮይድ፦ "ሁሉን የሚቆጣጠር እና የሚመግብ አምላክ ፍቅር፣ እንክብካቤ እና ጥበቃ በሚያስፈልገው በሰው ሥነ ልቡና የተፈጠረ ነው"The God who controls and provides everything, is created by the human psyche in response to its need for love, saftey and security" በማለት ኢ-አማኝነቱን ገልጿል። ይህ የኢልሓድ እሳቤ ነው፥ በፈጣሪ እሳቦት ውስጥ ኢማን፣ ኩፍር እና ኢልሓድ ተጠቃሽ ናቸው።
"ኢልሓድ" إِلْحَاد የሚለው ቃል "አልሐደ" أَلْحَدَ ማለትም "ኢ-አመነ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን በአምላክ መኖር "ኢ-አማኒነት"atheism" ማለት ነው፥ በነጠላ "ሙልሒድ" مُلْحِد ማለት "ኢ-አማኝ"atheist" ማለት ሲሆን "ሙልሒዱን" مُلْحِدُون ደግሞ የሙልሒድ ብዙ ቁጥር ነው። ሙልሒድ የኢልሓድ እሳቤ የሚያራምዱ ናቸው፦
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 87 ሐዲስ 21
ኢብኑ ዐባሥ እንደተረከው፦ “ነቢዩም፦ “ﷺ” እንዲህ አሉ፦ “አሏህ ዘንድ የተጠሉ ሦስት ሰዎች አሉ፦ “በሐረም ውስጥ ያለ ሙልሒድ፣ የጃሂሊያህን ሡናህ ኢሥላም ውስጥ ለማስቀረት የሚፈልግ እና ያለ ሕግ የአንድ ሰው ደም ማፍሰስ የሚፈልግ ናቸው"። عَنِ ابْنِ عَبَّاسٍ، أَنَّ النَّبِيَّ صلى الله عليه وسلم قَالَ أَبْغَضُ النَّاسِ إِلَى اللَّهِ ثَلاَثَةٌ مُلْحِدٌ فِي الْحَرَمِ، وَمُبْتَغٍ فِي الإِسْلاَمِ سُنَّةَ الْجَاهِلِيَّةِ، وَمُطَّلِبُ دَمِ امْرِئٍ بِغَيْرِ حَقٍّ لِيُهَرِيقَ دَمَهُ.
"ዉጁድ" وُجُود የሚለው ቃል "ወጀደ" وَجَدَ ማለትም "አለወ" "ኖረ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "መኖር" ሃልዎት" "ህልውና" ማለት ነው፥ "ዉጁዱል ሏህ" وُجُود الله ማለት "የአሏህ ህልውና"the existence of Allah" ማለት ነው። የአሏህ መኖር የተረጋገጠ ነው፦
22፥6 ይህ አላህ እርሱ "መኖሩ የተረጋገጠ"፣ እርሱም ሙታንን ሕያው የሚያደርግ፣ እርሱም በነገሩ ሁሉ ላይ ቻይ በመሆኑ ነው፡፡ ذَٰلِكَ بِأَنَّ اللَّهَ هُوَ الْحَقُّ وَأَنَّهُ يُحْيِي الْمَوْتَىٰ وَأَنَّهُ عَلَىٰ كُلِّ شَيْءٍ قَدِيرٌ
24፥25 በዚያ ቀን አላህ እውነተኛ ዋጋቸውን ይሞላላቸዋል፡፡ አላህም እርሱ "መኖሩ የተረጋገጠ" ሁሉን ነገር ገላጭ መኾኑን ያውቃሉ፡፡ يَوْمَئِذٍ يُوَفِّيهِمُ اللَّهُ دِينَهُمُ الْحَقَّ وَيَعْلَمُونَ أَنَّ اللَّهَ هُوَ الْحَقُّ الْمُبِينُ
"አል ሐቅ" الْحَقّ ማለት "መኖሩ ተረጋገጠ" ማለትም ሲሆን አንድ ሰው የአሏህን መኖር የሚረጋገጠው እንደ ሲይግመን ፍሮይድ ማየት፣ መስማት፣ ማሽተት፣ መቅመስ እና መዳደስ በሚባሉት አምስት የስሜት ሕዋሳት ሳይሆን በመኽሉቅ፣ በፊጥራህ፣ በዐቅል፣ በነቅል፣ በአደብ ነው። እነዚህ ማረጋገጫዎች እንመልከት፦
፨ "መኽሉቅ" مَخْلُق ማለት "ፍጥረት" ማለት ሲሆን ፍጥረት ውጤት ከሆነ ፈጣሪ መንስኤ ነው፥ አሏህ ስለመኖሩ ጉልኅ ማረጋገጫ የፍጥረት ሙግት"cosmological argument" ነው፦
56፥58 በማኅፀኖች የምታፈሱትን አያችሁን? أَفَرَأَيْتُم مَّا تُمْنُونَ
56፥59 እናንተ ትፈጥሩታላችሁን? ወይስ እኛ ፈጣሪዎቹን ነን? أَأَنتُمْ تَخْلُقُونَهُ أَمْ نَحْنُ الْخَالِقُونَ
በተራክቦ ጊዜ በሴት ብልት ውስጥ የሚፈሰውን የወንድ ሕዋስ"sperm cell" ሰው አርገን መፍጠር አለመቻላችን በራሱ የተፈረጠውን የሚፈጥር ፈጣሪ እንዳለ አመላካች ነው፥ በመንስኤ እና በውጤት ሕግ ያለ ሠሪ ተሠሪ እንደሌለ ሁሉ ያለ ፈጣሪ ተፈጣሪ የለም። የፍጥረት ሙግት በመቀጠል ሰው እራሱን እራሱ አለመፍጠሩ የፈጠረውን ፈጣሪ እንዳለ በቂ ማሳያ ነው፦
52፥35 ወይስ ያለ አንዳች "ነገር" ተፈጠሩን? ወይስ እነርሱ ፈጣሪዎች ናቸውን? أَمْ خُلِقُوا مِنْ غَيْرِ شَيْءٍ أَمْ هُمُ الْخَالِقُونَ
52፥36 ወይስ ሰማያትን እና ምድርን ፈጠሩን? አይደለም አያረጋግጡም፡፡ أَمْ خَلَقُوا السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضَ ۚ بَل لَّا يُوقِنُونَ
ፍጥረት ያለምንም ፈጣሪ እንዳልተፈጠረ እሙን እና ቅቡል ነው፥ ፍጥረትን ፍጡር አልፈጠረም። ሰማያትን እና ምድርን ሰው አለመፍጠሩ በራሱ ፈጣሪ መኖሩን ማረጋገጫ ነው። ይህንን ሙግት በምንጨታዊ፣ በስሙር፣ በርቱዕ ሙግት ስናዋቅረው፦
1. ማንኛውም ነገር መነሾ አለው፣
2. መነሾ ያለው ነገር መንስኤ"cause" አለው፣
3. ስለዚህ ፍጥረትን ያስገኘው መንስኤ ፈጣሪ ነው፦
46፥3 በሰማያት እና በምድር ውስጥ ለምእምናን ሁሉ እርግጠኛ ምልክቶች አሉ፡፡ إِنَّ فِي السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضِ لَآيَاتٍ لِّلْمُؤْمِنِينَ
7፥54 ጌታችሁ ያ ሰማያትንና ምድርን በስድስት ቀኖች ውስጥ የፈጠረ አላህ ነው፡፡ إِنَّ رَبَّكُمُ اللَّهُ الَّذِي خَلَقَ السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضَ فِي سِتَّةِ أَيَّامٍ
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
22፥6 ይህ አላህ እርሱ መኖሩ የተረጋገጠ፣ እርሱም ሙታንን ሕያው የሚያደርግ፣ እርሱም በነገሩ ሁሉ ላይ ቻይ በመሆኑ ነው፡፡ ذَٰلِكَ بِأَنَّ اللَّهَ هُوَ الْحَقُّ وَأَنَّهُ يُحْيِي الْمَوْتَىٰ وَأَنَّهُ عَلَىٰ كُلِّ شَيْءٍ قَدِيرٌ
በአንድ ወቅት የነገረ ልቦና ምሁር ሲይግመን ፍሮይድ፦ "ሁሉን የሚቆጣጠር እና የሚመግብ አምላክ ፍቅር፣ እንክብካቤ እና ጥበቃ በሚያስፈልገው በሰው ሥነ ልቡና የተፈጠረ ነው"The God who controls and provides everything, is created by the human psyche in response to its need for love, saftey and security" በማለት ኢ-አማኝነቱን ገልጿል። ይህ የኢልሓድ እሳቤ ነው፥ በፈጣሪ እሳቦት ውስጥ ኢማን፣ ኩፍር እና ኢልሓድ ተጠቃሽ ናቸው።
"ኢልሓድ" إِلْحَاد የሚለው ቃል "አልሐደ" أَلْحَدَ ማለትም "ኢ-አመነ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን በአምላክ መኖር "ኢ-አማኒነት"atheism" ማለት ነው፥ በነጠላ "ሙልሒድ" مُلْحِد ማለት "ኢ-አማኝ"atheist" ማለት ሲሆን "ሙልሒዱን" مُلْحِدُون ደግሞ የሙልሒድ ብዙ ቁጥር ነው። ሙልሒድ የኢልሓድ እሳቤ የሚያራምዱ ናቸው፦
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 87 ሐዲስ 21
ኢብኑ ዐባሥ እንደተረከው፦ “ነቢዩም፦ “ﷺ” እንዲህ አሉ፦ “አሏህ ዘንድ የተጠሉ ሦስት ሰዎች አሉ፦ “በሐረም ውስጥ ያለ ሙልሒድ፣ የጃሂሊያህን ሡናህ ኢሥላም ውስጥ ለማስቀረት የሚፈልግ እና ያለ ሕግ የአንድ ሰው ደም ማፍሰስ የሚፈልግ ናቸው"። عَنِ ابْنِ عَبَّاسٍ، أَنَّ النَّبِيَّ صلى الله عليه وسلم قَالَ أَبْغَضُ النَّاسِ إِلَى اللَّهِ ثَلاَثَةٌ مُلْحِدٌ فِي الْحَرَمِ، وَمُبْتَغٍ فِي الإِسْلاَمِ سُنَّةَ الْجَاهِلِيَّةِ، وَمُطَّلِبُ دَمِ امْرِئٍ بِغَيْرِ حَقٍّ لِيُهَرِيقَ دَمَهُ.
"ዉጁድ" وُجُود የሚለው ቃል "ወጀደ" وَجَدَ ማለትም "አለወ" "ኖረ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "መኖር" ሃልዎት" "ህልውና" ማለት ነው፥ "ዉጁዱል ሏህ" وُجُود الله ማለት "የአሏህ ህልውና"the existence of Allah" ማለት ነው። የአሏህ መኖር የተረጋገጠ ነው፦
22፥6 ይህ አላህ እርሱ "መኖሩ የተረጋገጠ"፣ እርሱም ሙታንን ሕያው የሚያደርግ፣ እርሱም በነገሩ ሁሉ ላይ ቻይ በመሆኑ ነው፡፡ ذَٰلِكَ بِأَنَّ اللَّهَ هُوَ الْحَقُّ وَأَنَّهُ يُحْيِي الْمَوْتَىٰ وَأَنَّهُ عَلَىٰ كُلِّ شَيْءٍ قَدِيرٌ
24፥25 በዚያ ቀን አላህ እውነተኛ ዋጋቸውን ይሞላላቸዋል፡፡ አላህም እርሱ "መኖሩ የተረጋገጠ" ሁሉን ነገር ገላጭ መኾኑን ያውቃሉ፡፡ يَوْمَئِذٍ يُوَفِّيهِمُ اللَّهُ دِينَهُمُ الْحَقَّ وَيَعْلَمُونَ أَنَّ اللَّهَ هُوَ الْحَقُّ الْمُبِينُ
"አል ሐቅ" الْحَقّ ማለት "መኖሩ ተረጋገጠ" ማለትም ሲሆን አንድ ሰው የአሏህን መኖር የሚረጋገጠው እንደ ሲይግመን ፍሮይድ ማየት፣ መስማት፣ ማሽተት፣ መቅመስ እና መዳደስ በሚባሉት አምስት የስሜት ሕዋሳት ሳይሆን በመኽሉቅ፣ በፊጥራህ፣ በዐቅል፣ በነቅል፣ በአደብ ነው። እነዚህ ማረጋገጫዎች እንመልከት፦
፨ "መኽሉቅ" مَخْلُق ማለት "ፍጥረት" ማለት ሲሆን ፍጥረት ውጤት ከሆነ ፈጣሪ መንስኤ ነው፥ አሏህ ስለመኖሩ ጉልኅ ማረጋገጫ የፍጥረት ሙግት"cosmological argument" ነው፦
56፥58 በማኅፀኖች የምታፈሱትን አያችሁን? أَفَرَأَيْتُم مَّا تُمْنُونَ
56፥59 እናንተ ትፈጥሩታላችሁን? ወይስ እኛ ፈጣሪዎቹን ነን? أَأَنتُمْ تَخْلُقُونَهُ أَمْ نَحْنُ الْخَالِقُونَ
በተራክቦ ጊዜ በሴት ብልት ውስጥ የሚፈሰውን የወንድ ሕዋስ"sperm cell" ሰው አርገን መፍጠር አለመቻላችን በራሱ የተፈረጠውን የሚፈጥር ፈጣሪ እንዳለ አመላካች ነው፥ በመንስኤ እና በውጤት ሕግ ያለ ሠሪ ተሠሪ እንደሌለ ሁሉ ያለ ፈጣሪ ተፈጣሪ የለም። የፍጥረት ሙግት በመቀጠል ሰው እራሱን እራሱ አለመፍጠሩ የፈጠረውን ፈጣሪ እንዳለ በቂ ማሳያ ነው፦
52፥35 ወይስ ያለ አንዳች "ነገር" ተፈጠሩን? ወይስ እነርሱ ፈጣሪዎች ናቸውን? أَمْ خُلِقُوا مِنْ غَيْرِ شَيْءٍ أَمْ هُمُ الْخَالِقُونَ
52፥36 ወይስ ሰማያትን እና ምድርን ፈጠሩን? አይደለም አያረጋግጡም፡፡ أَمْ خَلَقُوا السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضَ ۚ بَل لَّا يُوقِنُونَ
ፍጥረት ያለምንም ፈጣሪ እንዳልተፈጠረ እሙን እና ቅቡል ነው፥ ፍጥረትን ፍጡር አልፈጠረም። ሰማያትን እና ምድርን ሰው አለመፍጠሩ በራሱ ፈጣሪ መኖሩን ማረጋገጫ ነው። ይህንን ሙግት በምንጨታዊ፣ በስሙር፣ በርቱዕ ሙግት ስናዋቅረው፦
1. ማንኛውም ነገር መነሾ አለው፣
2. መነሾ ያለው ነገር መንስኤ"cause" አለው፣
3. ስለዚህ ፍጥረትን ያስገኘው መንስኤ ፈጣሪ ነው፦
46፥3 በሰማያት እና በምድር ውስጥ ለምእምናን ሁሉ እርግጠኛ ምልክቶች አሉ፡፡ إِنَّ فِي السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضِ لَآيَاتٍ لِّلْمُؤْمِنِينَ
7፥54 ጌታችሁ ያ ሰማያትንና ምድርን በስድስት ቀኖች ውስጥ የፈጠረ አላህ ነው፡፡ إِنَّ رَبَّكُمُ اللَّهُ الَّذِي خَلَقَ السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضَ فِي سِتَّةِ أَيَّامٍ
፨ "ፊጥራህ" فِطْرَة ማለት "ተፈጥሮ ማለት ሲሆን አሏህ ስለመኖሩ ማረጋገጫ የሥነ ኑባሬ ሙግት"ontological argument" ነው፦
30፥30 ወደ እውነት ተዘንባይ ኾነህም ፊትህን ለሃይማኖት ቀጥ አድርግ፡፡ የአላህን ፍጥረት ያችን አላህ ሰዎችን በእርስዋ ላይ የፈጠረባትን ሃይማኖት ያዟት፡፡ فَأَقِمْ وَجْهَكَ لِلدِّينِ حَنِيفًا ۚ فِطْرَتَ اللَّهِ الَّتِي فَطَرَ النَّاسَ عَلَيْهَا
ኢማም ሙሥሊም መጽሐፍ 46, ሐዲስ 38
አቢ ሙዓዊያህ እንደተረከው፦ ነቢዩም”ﷺ” አሉ፦ "ማንም የሚወለድ ሰው በአንደበቱ እስከሚል ድረስ በአል-ፊጥራህ ላይ ሆኖ እንጂ አይወለድም። عَنْ أَبِي مُعَاوِيَةَ قَالَ النَّبِيُّ صلى الله عليه وسلم " إِلاَّ عَلَى هَذِهِ الْمِلَّةِ حَتَّى يُبَيِّنَ عَنْهُ لِسَانُهُ " .
አሏህ በፊጥራህ ጊዜ ከአደም ልጆች ከጀርቦቻቸው ዘሮቻቸውን በማውጣት፦ "ጌታችሁ አይደለሁምን" ብሎ አስመስክሯል፦
7፥172 "ጌታህም ከአደም ልጆች ከጀርቦቻቸው ዘሮቻቸውን ባወጣና፦ «ጌታችሁ አይደለሁምን?» ሲል በራሳቸው ላይ ባስመሰከራቸው ጊዜ የኾነውን አስታውስ፡፡ «ጌታችን ነህ መሰከርን» አሉ፡፡ «በትንሣኤ ቀን ከዚህ ኪዳን ዘንጊዎች ነበርን እንዳትሉ፡፡» وَإِذْ أَخَذَ رَبُّكَ مِن بَنِي آدَمَ مِن ظُهُورِهِمْ ذُرِّيَّتَهُمْ وَأَشْهَدَهُمْ عَلَىٰ أَنفُسِهِمْ أَلَسْتُ بِرَبِّكُمْ ۖ قَالُوا بَلَىٰ ۛ شَهِدْنَا ۛ أَن تَقُولُوا يَوْمَ الْقِيَامَةِ إِنَّا كُنَّا عَنْ هَـٰذَا غَافِلِينَ
ሰው በተፈጥሮው የአምልኮ ፍላጎት እና ዝንባሌ ያለው ፍጡር የሆነው በዚህ ምክንያት ነው፥ ሰው በፊጥራህ ጊዜ "ጌታችን ነህ መሰከርን" ማለታቸው በታኅታይ ሕሊና"subconscious" የተቀመጠ ሲሆን በትንሳኤ ቀን ይህ ውስጣችን ያለው ምሥጢር ይገለጻል፦
100፥10 "በልቦች ውስጥ ያለውም ሁሉ በተገለጸ ጊዜ እንዴት እንደሚኾን፡፡ وَحُصِّلَ مَا فِي الصُّدُورِ
86፥9 "ምሥጢሮች በሚገለጡበት ቀን"፡፡ يَوْمَ تُبْلَى السَّرَائِرُ
፨ "ዐቅል" عَقْل ማለት "አእምሮ" ማለት ሲሆን አሏህ ስለመኖሩ ማረጋገጫ የሥነ አመክንዮ ሙግት"logical argument" ነው፦
51፥21 በነፍሶቻችሁም ውስጥ ምልክቶች አሉ፤ ታዲያ አትመለከቱምን? وَفِي أَنفُسِكُمْ ۚ أَفَلَا تُبْصِرُونَ
የሰው ውሳጣዊ ተፈጥሮ በሥነ አመክንዮ ፈጣሪ እንዳለ ምስክርነት ነው፥ በነፍሶቻችን ውስጥ ያሉት የአስተሳሰብ ቅኝት"mindset" ተአምራት ሲሆኑ ከተመለከትን የአሏህን መኖር ፍትንው አርገው ያረጋግጣሉ፦
91፥8 አመጽዋን እና ፍርሃትዋንም ባሳወቃት፡፡ فَأَلْهَمَهَا فُجُورَهَا وَتَقْوَاهَا
እዚህ አንቀጽ ላይ "ባሳወቀ" ለሚለው የገባው ቃል "አልሀመ" أَلْهَمَ መሆኑን ልብ በል! "ኢልሃም" إِلْهَام የሚለው ቃል እራሱ "አልሀመ" أَلْهَمَ ከሚለው ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን “ውሳጣዊ ግንዛቤ ወይም ዕውቀ-ልቦና”intuition” ማለት ነው፥ ለነፍስ በመልካም መታዘዝ እና በክፉን ማመጽ በውስጧ ያሳወቃት መኖሩ በራሱ የአሏህ መኖር የሕሊና ምስክርነት ነው።
፨ "ነቅል" نَقْل ማለት "ግልጠተ መለኮት" ማለት ሲሆን በነቢያቱ በኩል የመጣ ማረጋገጫ ነው፥ "ላ ኢላሀ ኢለል ሏህ" لَا إِلَـٰهَ إِلَّا اللَّه የሚለው መርሕ የሁሉም ነቢያት መርሕ ነው፦
21፥25 ከአንተ በፊትም እነሆ፦ "ከእኔ ሌላ አምላክ የለምና አምልኩኝ" በማለት ወደ እርሱ የምናወርድለት ቢኾን እንጅ ከመልእክተኛ አንድንም አላክንም፡፡ وَمَا أَرْسَلْنَا مِن قَبْلِكَ مِن رَّسُولٍ إِلَّا نُوحِي إِلَيْهِ أَنَّهُ لَا إِلَـٰهَ إِلَّا أَنَا فَاعْبُدُونِ
20፥14 እኔ አላህ እኔ ነኝ ያለ እኔ አምላክ የለምና አምልከኝ፡፡ ሶላትንም በእርሷ እኔን ለማውሳት ስገድ፡፡ إِنَّنِي أَنَا اللَّهُ لَا إِلَـٰهَ إِلَّا أَنَا فَاعْبُدْنِي وَأَقِمِ الصَّلَاةَ لِذِكْرِي
በነቢያቱ በኩል ወሕይ በማውረድ "ከእኔ ሌላ አምላክ የለምና አምልኩኝ" እያለ የሚናገር ነባቢ መለኮት መኖሩ፣ ሰዎች የሚመሩበትን ሙሐከማት መስጠቱ እና "ሰማያትን እና ምድርን በመካከላቸው ያለውንም ሁሉ በስድስት ቀናት ውስጥ በእርግጥ ፈጠርን" ማለቱ በራሱ የሥነ መለኮት ሙግት"theological argument" ነው፦
50፥38 ሰማያትን እና ምድርን በመካከላቸው ያለውንም ሁሉ በስድስት ቀናት ውስጥ በእርግጥ ፈጠርን፡፡ ድካምም ምንም አልነካንም፡፡ وَلَقَدْ خَلَقْنَا السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضَ وَمَا بَيْنَهُمَا فِي سِتَّةِ أَيَّامٍ وَمَا مَسَّنَا مِن لُّغُوبٍ
፨ "አደብ" اَدَب ማለት "ግብረገብ" ማለት ሲሆን ሰው ግን ነጻ ፈቃድ ስላለው በሚሠራው መልካም ሥራ ስለሚነዳ እና በሚሠራው ክፉ ሥራ ስለሚቀጣ ልቅ ሆኖ አልተተወም፦
75፥36 ሰው ልቅ ኾኖ መተውን ያስባልን? أَيَحْسَبُ الْإِنسَانُ أَن يُتْرَكَ سُدًى
ይህ ግብረገባዊ ሙግት"moral argument" ነው፥ "መሥኡሉል አደብ” مَسْؤُول الاَدَب ማለት “ግብረገባዊ ተጠያቂነት”moral accountability” ማለት ሲሆን ሰው በተሰጠው ጸጋ ለሚሠራው ሥራ ተጠያቂ መሆኑ በራሱ ጠያቂ ፈጣሪ መኖሩ ማረጋገጫ ነው፦
21፥23 ከሚሠራው ሁሉ አይጠየቅም፡፡ እነርሱ ግን ይጠየቃሉ፡፡ لَا يُسْأَلُ عَمَّا يَفْعَلُ وَهُمْ يُسْأَلُونَ
16፥93 ትሠሩት ከነበራችሁትም ሁሉ በእርግጥ ትጠየቃላችሁ፡፡ وَلَتُسْأَلُنَّ عَمَّا كُنتُمْ تَعْمَلُون
102፥8 ከዚያም ከጸጋችሁ ሁሉ በዚያ ቀን ትጠየቃላችሁ። ثُمَّ لَتُسْأَلُنَّ يَوْمَئِذٍ عَنِ النَّعِيمِ
አምላካችን አሏህ ከሙልሒድ ኢልሓድ ይጠብቀን! አሚን።
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
30፥30 ወደ እውነት ተዘንባይ ኾነህም ፊትህን ለሃይማኖት ቀጥ አድርግ፡፡ የአላህን ፍጥረት ያችን አላህ ሰዎችን በእርስዋ ላይ የፈጠረባትን ሃይማኖት ያዟት፡፡ فَأَقِمْ وَجْهَكَ لِلدِّينِ حَنِيفًا ۚ فِطْرَتَ اللَّهِ الَّتِي فَطَرَ النَّاسَ عَلَيْهَا
ኢማም ሙሥሊም መጽሐፍ 46, ሐዲስ 38
አቢ ሙዓዊያህ እንደተረከው፦ ነቢዩም”ﷺ” አሉ፦ "ማንም የሚወለድ ሰው በአንደበቱ እስከሚል ድረስ በአል-ፊጥራህ ላይ ሆኖ እንጂ አይወለድም። عَنْ أَبِي مُعَاوِيَةَ قَالَ النَّبِيُّ صلى الله عليه وسلم " إِلاَّ عَلَى هَذِهِ الْمِلَّةِ حَتَّى يُبَيِّنَ عَنْهُ لِسَانُهُ " .
አሏህ በፊጥራህ ጊዜ ከአደም ልጆች ከጀርቦቻቸው ዘሮቻቸውን በማውጣት፦ "ጌታችሁ አይደለሁምን" ብሎ አስመስክሯል፦
7፥172 "ጌታህም ከአደም ልጆች ከጀርቦቻቸው ዘሮቻቸውን ባወጣና፦ «ጌታችሁ አይደለሁምን?» ሲል በራሳቸው ላይ ባስመሰከራቸው ጊዜ የኾነውን አስታውስ፡፡ «ጌታችን ነህ መሰከርን» አሉ፡፡ «በትንሣኤ ቀን ከዚህ ኪዳን ዘንጊዎች ነበርን እንዳትሉ፡፡» وَإِذْ أَخَذَ رَبُّكَ مِن بَنِي آدَمَ مِن ظُهُورِهِمْ ذُرِّيَّتَهُمْ وَأَشْهَدَهُمْ عَلَىٰ أَنفُسِهِمْ أَلَسْتُ بِرَبِّكُمْ ۖ قَالُوا بَلَىٰ ۛ شَهِدْنَا ۛ أَن تَقُولُوا يَوْمَ الْقِيَامَةِ إِنَّا كُنَّا عَنْ هَـٰذَا غَافِلِينَ
ሰው በተፈጥሮው የአምልኮ ፍላጎት እና ዝንባሌ ያለው ፍጡር የሆነው በዚህ ምክንያት ነው፥ ሰው በፊጥራህ ጊዜ "ጌታችን ነህ መሰከርን" ማለታቸው በታኅታይ ሕሊና"subconscious" የተቀመጠ ሲሆን በትንሳኤ ቀን ይህ ውስጣችን ያለው ምሥጢር ይገለጻል፦
100፥10 "በልቦች ውስጥ ያለውም ሁሉ በተገለጸ ጊዜ እንዴት እንደሚኾን፡፡ وَحُصِّلَ مَا فِي الصُّدُورِ
86፥9 "ምሥጢሮች በሚገለጡበት ቀን"፡፡ يَوْمَ تُبْلَى السَّرَائِرُ
፨ "ዐቅል" عَقْل ማለት "አእምሮ" ማለት ሲሆን አሏህ ስለመኖሩ ማረጋገጫ የሥነ አመክንዮ ሙግት"logical argument" ነው፦
51፥21 በነፍሶቻችሁም ውስጥ ምልክቶች አሉ፤ ታዲያ አትመለከቱምን? وَفِي أَنفُسِكُمْ ۚ أَفَلَا تُبْصِرُونَ
የሰው ውሳጣዊ ተፈጥሮ በሥነ አመክንዮ ፈጣሪ እንዳለ ምስክርነት ነው፥ በነፍሶቻችን ውስጥ ያሉት የአስተሳሰብ ቅኝት"mindset" ተአምራት ሲሆኑ ከተመለከትን የአሏህን መኖር ፍትንው አርገው ያረጋግጣሉ፦
91፥8 አመጽዋን እና ፍርሃትዋንም ባሳወቃት፡፡ فَأَلْهَمَهَا فُجُورَهَا وَتَقْوَاهَا
እዚህ አንቀጽ ላይ "ባሳወቀ" ለሚለው የገባው ቃል "አልሀመ" أَلْهَمَ መሆኑን ልብ በል! "ኢልሃም" إِلْهَام የሚለው ቃል እራሱ "አልሀመ" أَلْهَمَ ከሚለው ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን “ውሳጣዊ ግንዛቤ ወይም ዕውቀ-ልቦና”intuition” ማለት ነው፥ ለነፍስ በመልካም መታዘዝ እና በክፉን ማመጽ በውስጧ ያሳወቃት መኖሩ በራሱ የአሏህ መኖር የሕሊና ምስክርነት ነው።
፨ "ነቅል" نَقْل ማለት "ግልጠተ መለኮት" ማለት ሲሆን በነቢያቱ በኩል የመጣ ማረጋገጫ ነው፥ "ላ ኢላሀ ኢለል ሏህ" لَا إِلَـٰهَ إِلَّا اللَّه የሚለው መርሕ የሁሉም ነቢያት መርሕ ነው፦
21፥25 ከአንተ በፊትም እነሆ፦ "ከእኔ ሌላ አምላክ የለምና አምልኩኝ" በማለት ወደ እርሱ የምናወርድለት ቢኾን እንጅ ከመልእክተኛ አንድንም አላክንም፡፡ وَمَا أَرْسَلْنَا مِن قَبْلِكَ مِن رَّسُولٍ إِلَّا نُوحِي إِلَيْهِ أَنَّهُ لَا إِلَـٰهَ إِلَّا أَنَا فَاعْبُدُونِ
20፥14 እኔ አላህ እኔ ነኝ ያለ እኔ አምላክ የለምና አምልከኝ፡፡ ሶላትንም በእርሷ እኔን ለማውሳት ስገድ፡፡ إِنَّنِي أَنَا اللَّهُ لَا إِلَـٰهَ إِلَّا أَنَا فَاعْبُدْنِي وَأَقِمِ الصَّلَاةَ لِذِكْرِي
በነቢያቱ በኩል ወሕይ በማውረድ "ከእኔ ሌላ አምላክ የለምና አምልኩኝ" እያለ የሚናገር ነባቢ መለኮት መኖሩ፣ ሰዎች የሚመሩበትን ሙሐከማት መስጠቱ እና "ሰማያትን እና ምድርን በመካከላቸው ያለውንም ሁሉ በስድስት ቀናት ውስጥ በእርግጥ ፈጠርን" ማለቱ በራሱ የሥነ መለኮት ሙግት"theological argument" ነው፦
50፥38 ሰማያትን እና ምድርን በመካከላቸው ያለውንም ሁሉ በስድስት ቀናት ውስጥ በእርግጥ ፈጠርን፡፡ ድካምም ምንም አልነካንም፡፡ وَلَقَدْ خَلَقْنَا السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضَ وَمَا بَيْنَهُمَا فِي سِتَّةِ أَيَّامٍ وَمَا مَسَّنَا مِن لُّغُوبٍ
፨ "አደብ" اَدَب ማለት "ግብረገብ" ማለት ሲሆን ሰው ግን ነጻ ፈቃድ ስላለው በሚሠራው መልካም ሥራ ስለሚነዳ እና በሚሠራው ክፉ ሥራ ስለሚቀጣ ልቅ ሆኖ አልተተወም፦
75፥36 ሰው ልቅ ኾኖ መተውን ያስባልን? أَيَحْسَبُ الْإِنسَانُ أَن يُتْرَكَ سُدًى
ይህ ግብረገባዊ ሙግት"moral argument" ነው፥ "መሥኡሉል አደብ” مَسْؤُول الاَدَب ማለት “ግብረገባዊ ተጠያቂነት”moral accountability” ማለት ሲሆን ሰው በተሰጠው ጸጋ ለሚሠራው ሥራ ተጠያቂ መሆኑ በራሱ ጠያቂ ፈጣሪ መኖሩ ማረጋገጫ ነው፦
21፥23 ከሚሠራው ሁሉ አይጠየቅም፡፡ እነርሱ ግን ይጠየቃሉ፡፡ لَا يُسْأَلُ عَمَّا يَفْعَلُ وَهُمْ يُسْأَلُونَ
16፥93 ትሠሩት ከነበራችሁትም ሁሉ በእርግጥ ትጠየቃላችሁ፡፡ وَلَتُسْأَلُنَّ عَمَّا كُنتُمْ تَعْمَلُون
102፥8 ከዚያም ከጸጋችሁ ሁሉ በዚያ ቀን ትጠየቃላችሁ። ثُمَّ لَتُسْأَلُنَّ يَوْمَئِذٍ عَنِ النَّعِيمِ
አምላካችን አሏህ ከሙልሒድ ኢልሓድ ይጠብቀን! አሚን።
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
ነፍስ
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
75፥2 ራሷን ወቃሽ በኾነች ነፍስም እምላለሁ፡፡ وَلَا أُقْسِمُ بِالنَّفْسِ اللَّوَّامَةِ
"ነፍሥ" نَّفْس የሚለው ቃል "እራስ"own self" ማለት ነው፥ ለምሳሌ፦ "ቀተለ ነፍሠ-ሁ" قَتَلَ نَفْسَهُ ስንል "እራሱን አጠፋ" ማለት ነው፣ "ረአይቱ ነፍሢ ፊል መርኣህ" رَأَيْتُ نَفْسِي فِي ٱلْمِرْآةِ ስንል "እራሴን በመስታዎት አየሁኝ" ማለት ነው። "ዶሚሩ አን-ነፍሢያህ" ضَمِير الْنَفْسِيَّة ማለት እራሱ "ድርብ ተውላጠ-ስም”reflexive pronoun” ማለት ነው፥ ለምሳሌ፦ ተወዳጁ ነቢያችንን"ﷺ" አምላካችን አሏህ ያዘዛቸው ላይ "እራሴ" ሲሉ "ነፍሢ” نَفْسِي በማለት እንዲሉ ተናግሯል፦
7፥188 በላቸው፦ "አላህ የሻውን በስተቀር "ለ-"እራሴ" ጥቅምንም ጉዳትንም ማምጣት አልችልም፡፡ قُل لَّا أَمْلِكُ لِنَفْسِي نَفْعًا وَلَا ضَرًّا إِلَّا مَا شَاءَ اللَّهُ ۚ
በዚህ አንቀጽ ላይ "እራሴ"my-self" ለሚለው የገባው ቃል "ነፍሢ" نَفْسِي መሆኑ ልብ አድርግ! ይህ ያቀረብነው ናሙና በመጀመርያ መደብ ሲሆን አሏህ በሁለተኛ መደብ "እራስህ" ለማለት "ነፍሢከ" نَفْسِكَ በማለት ይናገራል፦
4፥79 ከደግም የሚያገኝህ ከአላህ ነው፤ ከፉዉም የሚደርስብህ "ከ-"እራስህ" ነው። مَّا أَصَابَكَ مِنْ حَسَنَةٍ فَمِنَ اللَّهِ ۖ وَمَا أَصَابَكَ مِن سَيِّئَةٍ فَمِن نَّفْسِكَ ۚ وَأَرْسَلْنَاكَ لِلنَّاسِ رَسُولًا ۚ وَكَفَىٰ بِاللَّهِ شَهِيدًا
በዚህ አንቀጽ ላይ "ራስህ"your-self" ለሚለው የገባው ቃል "ነፍሢከ" نَفْسِكَ ነው። አሏህ በሦስተኛ መደብ "እራሱ"him-self" ለማለት "ነፍሢሂ" نَفْسِهِ በማለት ይናገራል፦
2፥207 ከሰዎችም ውስጥ የአላህን ውዴታ ለመፈለግ "እራሱን" የሚሸጥ ሰው አለ፡፡ አላህም ለባሮቹ በጣም ርኅሩህ ነው፡፡ وَمِنَ النَّاسِ مَن يَشْرِي نَفْسَهُ ابْتِغَاءَ مَرْضَاتِ اللَّهِ
ስለዚህ በጥቅሉ "ነፍሥ" نَّفْس ማለት "ሁለንተናዊ ማንነት"wholly identity" ማለት ነው፥ አንድ ሰው ሌላውን ሰው ሲገድል "ነፍሰ ገዳይ" ይባላል፦
17፥33 ያቺንም አላህ ያወገዛትን ነፍስ ያለ ሕግ አትግደሉ፡፡ وَلَا تَقْتُلُوا النَّفْسَ الَّتِي حَرَّمَ اللَّهُ إِلَّا بِالْحَقِّ
እዚህ አንቀጽ ላይ "ላ ተቅተሉ አን-ነፍሥ" لَا تَقْتُلُوا النَّفْس ማለት "ነፍስን አትግደሉ" ማለት ነው፥ በዚህ ዐውድ "ነፍሥ" نَّفْس የሚለው "አካል" የሚለውን ለማመልከት የገባ ነው፦
39፥6 ከአንዲት ነፍስ ፈጠራችሁ፡፡ ከዚያም ከእርሷ መቀናጆዋን አደረገ፡፡ خَلَقَكُم مِّن نَّفْسٍ وَاحِدَةٍ ثُمَّ جَعَلَ مِنْهَا زَوْجَهَا
እዚህ አንቀጽ ላይ "አንዲት ነፍሥ" የተባለው አደም ሲሆን "መቀናጆዋን" የተባለችው ከአደም የተፈጠረችው ሐዋን ነው፥ እኛ ሆንን እናታችን ሐዋ ከአደም የተፈጠረው አካላችን ነው። ሩሓችን ግን ከአፈር ሳይሆን ከአሏህ ነው፦
17፥85 ስለ ሩሕ ይጠይቁሃል፥ «ሩሕ ከጌታዬ ነገር ነው፥ ከዕውቀትም ጥቂትን እንጂ አልተሰጣችሁም» በላቸው፡፡ وَيَسْأَلُونَكَ عَنِ الرُّوحِ ۖ قُلِ الرُّوحُ مِنْ أَمْرِ رَبِّي وَمَا أُوتِيتُم مِّنَ الْعِلْمِ إِلَّا قَلِيلًا
39፥62 አላህ የነገሩ ሁሉ ፈጣሪ ነው፡፡ እርሱም በነገሩ ሁሉ ላይ አስተናባሪ ነው፡፡ اللَّهُ خَالِقُ كُلِّ شَيْءٍ ۖ وَهُوَ عَلَىٰ كُلِّ شَيْءٍ وَكِيلٌ
"ሩሕ ከጌታዬ ነገር ነው" የሚለው ኃይለ-ቃል በራሱ ሩሕ "ነገር" ውስጥ ስለሚካተት እና አሏህ የሁሉ “ነገር” ፈጣሪ ስለሆነ የማንም ሰው ሩሕ ፍጡር ነው። "ነፍሥ" نَّفْس የሚለው "ሩሕ" رُّوح በሚል ዐውድ ለማመልከት መጥቷል፦
39፥42 አላህ ነፍሶችን በሞታቸው ጊዜ ይወስዳል፥ ያችንም ያልሞተችውን በእንቅልፏ ጊዜ ይወስዳታል፡፡ ٱللَّهُ يَتَوَفَّى ٱلْأَنفُسَ حِينَ مَوْتِهَا وَٱلَّتِى لَمْ تَمُتْ فِى مَنَامِهَا
"አንፉሥ" أَنفُس የነፍሥ ብዙ ቁጥር ሲሆን በሞት ጊዜ የሚሄደውን መንፈሳችንን ለማልከት የገባ ነው፥ "ሩሕ" رُّوح ማለት “መንፈስ” ማለት ሲሆን "ያችንም ያልሞተችውን በእንቅልፏ ጊዜ ይወስዳታል" ማለት አሏህ ሩሓችንን በእንቅልፍ ጊዜ ወስዶ በንቃት ጊዜ ይመልሳል፦
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 97, ሐዲስ 97
አቡ ቀታዳህ እንደተረከው፦ "ከሶላት ሰዎች በተኙ ጊዜ የአሏህ ነቢይም"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "አሏህ በሚሻው ጊዜ ሩሓችሁን ይወስዳል፥ በሚሻው ጊዜ ይመልሳል"። عَنْ عَبْدِ اللَّهِ بْنِ أَبِي قَتَادَةَ، عَنْ أَبِيهِ، حِينَ نَامُوا عَنِ الصَّلاَةِ، قَالَ النَّبِيُّ صلى الله عليه وسلم " إِنَّ اللَّهَ قَبَضَ أَرْوَاحَكُمْ حِينَ شَاءَ، وَرَدَّهَا حِينَ شَاءَ "
"አርዋሕ" أَرْوَاح ማለት "መንፈሶች" ማለት ሲሆን "ሩሕ" رُّوح ለሚለው ብዙ ቁጥር ነው፥ አሏህ ነፍሥን በእንቅልፏ ጊዜ ሲወስዳት ያለ ዓይን ታያለች፣ ያለ ጆሮ ትሰማለች፣ ያለ እግር ትሄዳለች፣ ያለ አፍ ትናገራለች።
ስለዚህ በኢሥላም አስተምህሮት ከወላጆች የሚወሰደው አካል እንጂ መንፈስ ስላልሆነ "ከወላጆች ነፍስ ይወሰዳል" ከተባለ አካልን ታሳቢ ባደረገ እንጂ መንፈስን ዋቢ ባደረገ መልኩ ከወላጆች ነፍስ አይወሰድም፥ "አካልን ከወላጆቻችን አካል እንደተገኘ ሁሉ መንፈሳችን ከወላጆቻችን መንፈስ የተገኘ"traduction" ነው" የሚል ተስተምህሮት ዲኑል ኢሥላም ውስጥ የለም። በጥቅሉ ነፍሥ "እራስነት"own self-hood" ነው፦
75፥2 ራሷን ወቃሽ በኾነች ነፍስም እምላለሁ፡፡ وَلَا أُقْسِمُ بِالنَّفْسِ اللَّوَّامَةِ
89፥27 ለአመነች ነፍስም፦ «አንቺ የረካሺው ነፍስ ሆይ! يَا أَيَّتُهَا النَّفْسُ الْمُطْمَئِنَّةُ
89፥28 ወዳጅ ተወዳጅ ኾነሽ ወደ ጌታሽ ተመለሺ፡፡ ارْجِعِي إِلَىٰ رَبِّكِ رَاضِيَةً مَّرْضِيَّةً
89፥29 በባሮቼም ውስጥ ግቢ፡፡ فَادْخُلِي فِي عِبَادِي
89፥30 ገነቴንም ግቢ» ትባላለች፡፡ وَادْخُلِي جَنَّتِي
አምላካችን አሏህ ያመነችን ነፍስ "ገነቴንም ግቢ" ሲላት አጠቃላይ አካላዊ እና መንፈሳዊ ማንነት ያላትን ነው። አሏህ "ገነቴንም ግቢ" ከሚላት ነፍስ ያድርገን! አሚን።
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
75፥2 ራሷን ወቃሽ በኾነች ነፍስም እምላለሁ፡፡ وَلَا أُقْسِمُ بِالنَّفْسِ اللَّوَّامَةِ
"ነፍሥ" نَّفْس የሚለው ቃል "እራስ"own self" ማለት ነው፥ ለምሳሌ፦ "ቀተለ ነፍሠ-ሁ" قَتَلَ نَفْسَهُ ስንል "እራሱን አጠፋ" ማለት ነው፣ "ረአይቱ ነፍሢ ፊል መርኣህ" رَأَيْتُ نَفْسِي فِي ٱلْمِرْآةِ ስንል "እራሴን በመስታዎት አየሁኝ" ማለት ነው። "ዶሚሩ አን-ነፍሢያህ" ضَمِير الْنَفْسِيَّة ማለት እራሱ "ድርብ ተውላጠ-ስም”reflexive pronoun” ማለት ነው፥ ለምሳሌ፦ ተወዳጁ ነቢያችንን"ﷺ" አምላካችን አሏህ ያዘዛቸው ላይ "እራሴ" ሲሉ "ነፍሢ” نَفْسِي በማለት እንዲሉ ተናግሯል፦
7፥188 በላቸው፦ "አላህ የሻውን በስተቀር "ለ-"እራሴ" ጥቅምንም ጉዳትንም ማምጣት አልችልም፡፡ قُل لَّا أَمْلِكُ لِنَفْسِي نَفْعًا وَلَا ضَرًّا إِلَّا مَا شَاءَ اللَّهُ ۚ
በዚህ አንቀጽ ላይ "እራሴ"my-self" ለሚለው የገባው ቃል "ነፍሢ" نَفْسِي መሆኑ ልብ አድርግ! ይህ ያቀረብነው ናሙና በመጀመርያ መደብ ሲሆን አሏህ በሁለተኛ መደብ "እራስህ" ለማለት "ነፍሢከ" نَفْسِكَ በማለት ይናገራል፦
4፥79 ከደግም የሚያገኝህ ከአላህ ነው፤ ከፉዉም የሚደርስብህ "ከ-"እራስህ" ነው። مَّا أَصَابَكَ مِنْ حَسَنَةٍ فَمِنَ اللَّهِ ۖ وَمَا أَصَابَكَ مِن سَيِّئَةٍ فَمِن نَّفْسِكَ ۚ وَأَرْسَلْنَاكَ لِلنَّاسِ رَسُولًا ۚ وَكَفَىٰ بِاللَّهِ شَهِيدًا
በዚህ አንቀጽ ላይ "ራስህ"your-self" ለሚለው የገባው ቃል "ነፍሢከ" نَفْسِكَ ነው። አሏህ በሦስተኛ መደብ "እራሱ"him-self" ለማለት "ነፍሢሂ" نَفْسِهِ በማለት ይናገራል፦
2፥207 ከሰዎችም ውስጥ የአላህን ውዴታ ለመፈለግ "እራሱን" የሚሸጥ ሰው አለ፡፡ አላህም ለባሮቹ በጣም ርኅሩህ ነው፡፡ وَمِنَ النَّاسِ مَن يَشْرِي نَفْسَهُ ابْتِغَاءَ مَرْضَاتِ اللَّهِ
ስለዚህ በጥቅሉ "ነፍሥ" نَّفْس ማለት "ሁለንተናዊ ማንነት"wholly identity" ማለት ነው፥ አንድ ሰው ሌላውን ሰው ሲገድል "ነፍሰ ገዳይ" ይባላል፦
17፥33 ያቺንም አላህ ያወገዛትን ነፍስ ያለ ሕግ አትግደሉ፡፡ وَلَا تَقْتُلُوا النَّفْسَ الَّتِي حَرَّمَ اللَّهُ إِلَّا بِالْحَقِّ
እዚህ አንቀጽ ላይ "ላ ተቅተሉ አን-ነፍሥ" لَا تَقْتُلُوا النَّفْس ማለት "ነፍስን አትግደሉ" ማለት ነው፥ በዚህ ዐውድ "ነፍሥ" نَّفْس የሚለው "አካል" የሚለውን ለማመልከት የገባ ነው፦
39፥6 ከአንዲት ነፍስ ፈጠራችሁ፡፡ ከዚያም ከእርሷ መቀናጆዋን አደረገ፡፡ خَلَقَكُم مِّن نَّفْسٍ وَاحِدَةٍ ثُمَّ جَعَلَ مِنْهَا زَوْجَهَا
እዚህ አንቀጽ ላይ "አንዲት ነፍሥ" የተባለው አደም ሲሆን "መቀናጆዋን" የተባለችው ከአደም የተፈጠረችው ሐዋን ነው፥ እኛ ሆንን እናታችን ሐዋ ከአደም የተፈጠረው አካላችን ነው። ሩሓችን ግን ከአፈር ሳይሆን ከአሏህ ነው፦
17፥85 ስለ ሩሕ ይጠይቁሃል፥ «ሩሕ ከጌታዬ ነገር ነው፥ ከዕውቀትም ጥቂትን እንጂ አልተሰጣችሁም» በላቸው፡፡ وَيَسْأَلُونَكَ عَنِ الرُّوحِ ۖ قُلِ الرُّوحُ مِنْ أَمْرِ رَبِّي وَمَا أُوتِيتُم مِّنَ الْعِلْمِ إِلَّا قَلِيلًا
39፥62 አላህ የነገሩ ሁሉ ፈጣሪ ነው፡፡ እርሱም በነገሩ ሁሉ ላይ አስተናባሪ ነው፡፡ اللَّهُ خَالِقُ كُلِّ شَيْءٍ ۖ وَهُوَ عَلَىٰ كُلِّ شَيْءٍ وَكِيلٌ
"ሩሕ ከጌታዬ ነገር ነው" የሚለው ኃይለ-ቃል በራሱ ሩሕ "ነገር" ውስጥ ስለሚካተት እና አሏህ የሁሉ “ነገር” ፈጣሪ ስለሆነ የማንም ሰው ሩሕ ፍጡር ነው። "ነፍሥ" نَّفْس የሚለው "ሩሕ" رُّوح በሚል ዐውድ ለማመልከት መጥቷል፦
39፥42 አላህ ነፍሶችን በሞታቸው ጊዜ ይወስዳል፥ ያችንም ያልሞተችውን በእንቅልፏ ጊዜ ይወስዳታል፡፡ ٱللَّهُ يَتَوَفَّى ٱلْأَنفُسَ حِينَ مَوْتِهَا وَٱلَّتِى لَمْ تَمُتْ فِى مَنَامِهَا
"አንፉሥ" أَنفُس የነፍሥ ብዙ ቁጥር ሲሆን በሞት ጊዜ የሚሄደውን መንፈሳችንን ለማልከት የገባ ነው፥ "ሩሕ" رُّوح ማለት “መንፈስ” ማለት ሲሆን "ያችንም ያልሞተችውን በእንቅልፏ ጊዜ ይወስዳታል" ማለት አሏህ ሩሓችንን በእንቅልፍ ጊዜ ወስዶ በንቃት ጊዜ ይመልሳል፦
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 97, ሐዲስ 97
አቡ ቀታዳህ እንደተረከው፦ "ከሶላት ሰዎች በተኙ ጊዜ የአሏህ ነቢይም"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "አሏህ በሚሻው ጊዜ ሩሓችሁን ይወስዳል፥ በሚሻው ጊዜ ይመልሳል"። عَنْ عَبْدِ اللَّهِ بْنِ أَبِي قَتَادَةَ، عَنْ أَبِيهِ، حِينَ نَامُوا عَنِ الصَّلاَةِ، قَالَ النَّبِيُّ صلى الله عليه وسلم " إِنَّ اللَّهَ قَبَضَ أَرْوَاحَكُمْ حِينَ شَاءَ، وَرَدَّهَا حِينَ شَاءَ "
"አርዋሕ" أَرْوَاح ማለት "መንፈሶች" ማለት ሲሆን "ሩሕ" رُّوح ለሚለው ብዙ ቁጥር ነው፥ አሏህ ነፍሥን በእንቅልፏ ጊዜ ሲወስዳት ያለ ዓይን ታያለች፣ ያለ ጆሮ ትሰማለች፣ ያለ እግር ትሄዳለች፣ ያለ አፍ ትናገራለች።
ስለዚህ በኢሥላም አስተምህሮት ከወላጆች የሚወሰደው አካል እንጂ መንፈስ ስላልሆነ "ከወላጆች ነፍስ ይወሰዳል" ከተባለ አካልን ታሳቢ ባደረገ እንጂ መንፈስን ዋቢ ባደረገ መልኩ ከወላጆች ነፍስ አይወሰድም፥ "አካልን ከወላጆቻችን አካል እንደተገኘ ሁሉ መንፈሳችን ከወላጆቻችን መንፈስ የተገኘ"traduction" ነው" የሚል ተስተምህሮት ዲኑል ኢሥላም ውስጥ የለም። በጥቅሉ ነፍሥ "እራስነት"own self-hood" ነው፦
75፥2 ራሷን ወቃሽ በኾነች ነፍስም እምላለሁ፡፡ وَلَا أُقْسِمُ بِالنَّفْسِ اللَّوَّامَةِ
89፥27 ለአመነች ነፍስም፦ «አንቺ የረካሺው ነፍስ ሆይ! يَا أَيَّتُهَا النَّفْسُ الْمُطْمَئِنَّةُ
89፥28 ወዳጅ ተወዳጅ ኾነሽ ወደ ጌታሽ ተመለሺ፡፡ ارْجِعِي إِلَىٰ رَبِّكِ رَاضِيَةً مَّرْضِيَّةً
89፥29 በባሮቼም ውስጥ ግቢ፡፡ فَادْخُلِي فِي عِبَادِي
89፥30 ገነቴንም ግቢ» ትባላለች፡፡ وَادْخُلِي جَنَّتِي
አምላካችን አሏህ ያመነችን ነፍስ "ገነቴንም ግቢ" ሲላት አጠቃላይ አካላዊ እና መንፈሳዊ ማንነት ያላትን ነው። አሏህ "ገነቴንም ግቢ" ከሚላት ነፍስ ያድርገን! አሚን።
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
ከሞት በኃላ
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
39፥42 አላህ ነፍሶችን በሞታቸው ጊዜ ይወስዳል፥ ያችንም ያልሞተችውን በእንቅልፏ ጊዜ ይወስዳታል፡፡ ٱللَّهُ يَتَوَفَّى ٱلْأَنفُسَ حِينَ مَوْتِهَا وَٱلَّتِى لَمْ تَمُتْ فِى مَنَامِهَا
አሏህ ሩሓችንን በእንቅልፏ ጊዜ ሲወስዳት ያለ ውጫዊ ነገር በውሳጣዊ ነገር ታያለች፣ ትሰማለች፣ ትሄዳለች፣ ትናገራለች፥ የሕልም ዓለም ሩሕ ከአካል ከተለየች በኃላ ያለውን ሕይወት ማሳያ ናሙና ነው። አምላካችን አሏህ በሌሊት ይወስደናል፥ ከዚያም በቀን ይቀሰቅሰናል፦
6፥60 "እርሱም ያ በሌሊት "የሚወስዳችሁ" በቀንም የሠራችሁትን ሁሉ የሚያውቅ ከዚያም የተወሰነው ጊዜ ይፈፀም ዘንድ በእርሱ በቀን ውስጥ "የሚቀሰቅሳችሁ" ነው"፡፡ وَهُوَ الَّذِي يَتَوَفَّاكُم بِاللَّيْلِ وَيَعْلَمُ مَا جَرَحْتُم بِالنَّهَارِ ثُمَّ يَبْعَثُكُمْ فِيهِ لِيُقْضَىٰ أَجَلٌ مُّسَمًّى
"የሚወስዷችሁ" ለሚለው የገባው ቃል "የተወፋኩም" يَتَوَفَّاكُم ሲሆን "የሚያስተኛችሁ" ማለትም ነው። አምላካችን አሏህ በቀን ደግሞ ይቀሰቅሰናል፥ "በቀን ውስጥ የሚቀሰቅሳችሁ ነው" የሚለው ይሰመርበት! አሏህ ሩሓችንን በእንቅልፍ ጊዜ ወስዶ በንቃት ጊዜ ይመልሳል፦
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 97, ሐዲስ 97
አቡ ቀታዳህ እንደተረከው፦ "ከሶላት ሰዎች በተኙ ጊዜ የአሏህ ነቢይም"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "አሏህ በሚሻው ጊዜ ሩሓችሁን ይወስዳል፥ በሚሻው ጊዜ ይመልሳል"። عَنْ عَبْدِ اللَّهِ بْنِ أَبِي قَتَادَةَ، عَنْ أَبِيهِ، حِينَ نَامُوا عَنِ الصَّلاَةِ، قَالَ النَّبِيُّ صلى الله عليه وسلم " إِنَّ اللَّهَ قَبَضَ أَرْوَاحَكُمْ حِينَ شَاءَ، وَرَدَّهَا حِينَ شَاءَ "
ሰው የመንፈስ እና የአካል ሁለትዮች"bi-partite" ቀዋሚ ማንነት ሲሆን አካሉ በሌሊት እንቅልፍ እንደሚያርፍ እና በቀን እንደሚቀሰቀስ ሁሉ በሞትን ጊዜ አካሉ በትልቁ እንቅልፍ ያርፍ እና በትንሳኤ ቀን ይቀሰቀሳል፦
36፥51 በቀንዱም ይነፋል፥ ወዲያውኑም እነርሱ ከመቃብሮቻቸው ወደ ጌታቸው በፍጥነት ይገሰግሳሉ፡፡ وَنُفِخَ فِي الصُّورِ فَإِذَا هُم مِّنَ الْأَجْدَاثِ إِلَىٰ رَبِّهِمْ يَنسِلُونَ
36፥52 «ወይ ጥፋታችን! ከእንቅልፋችን ማን ቀሰቀሰን? ይህ ያ አዛኙ ጌታ በእርሱ የቀጠረን እና መልእክተኞቹ እውነትን የነገሩን ነው» ይላሉ፡፡ قَالُوا يَا وَيْلَنَا مَن بَعَثَنَا مِن مَّرْقَدِنَا ۜ ۗ هَـٰذَا مَا وَعَدَ الرَّحْمَـٰنُ وَصَدَقَ الْمُرْسَلُونَ
እንቅልፍ ሩሕ እና አካል የሚለያዩበት ስለሆነ የሞት ወንድም ተብሏል፥ እንቅልፍ ትንሹ ሞት ስለሆነ ለዛ ነው የምሽት ዚክር ላይ "አሏህ ሆይ! በስምህ እሞታለው ሕያው እሆናለው" የንጋት ዚክር ላይ ደግሞ፦ "ለአሏህ ምስጋና ይሁን! ለዚያ ከአሞተን በኃላ ሕያው ላደረገን፥ መቀስቀስም ወደ እርሱ ነው" የምንለው፦
አል-ሙጀመል አውሠጥ መጽሐፍ 1, ሐዲስ 938
ጃቢር ኢብኑ ዐብደሏህ እንደተረከው፦ "የአሏህ ነቢይም"ﷺ" እንዲህ ተጠየቁ፦ "የአሏህ መልእክተኛ ሆይ! የጀናህ ባለቤቶች ይተኛሉን? የአሏህ መልእክተኛም"ﷺ" እንዲህ ሲሉ መለሱ፦ "እንቅልፍ የሞት ወንድም ነውና የጀናህ ባለቤቶች አይተኙም"። عَنْ جَابِرِ بْنِ عَبْدِ اللَّهِ قَالَ سُئِلَ نَبِيُّ اللَّهِ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ فَقِيلَ يَا رَسُولَ اللَّهِ أَيَنَامُ أَهْلُ الْجَنَّةِ فَقَالَ رَسُولُ اللَّهِ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ النَّوْمُ أَخُو الْمَوْتِ وَأَهْلُ الْجَنَّةِ لا يَنَامُونَ
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 97, ሐዲስ 23
ሑዘይፋህ እንደተረከው፦ "ነቢዩ"ﷺ" ወደ አልጋቸው በሄዱ ጊዜ፦ "አሏህ ሆይ! በስምህ እሞታለው ሕያው እሆናለው" ይሉ ነበር፥ በነቁ ጊዜ፦ "ለአሏህ ምስጋና ይሁን! ለዚያ ከአሞተን በኃላ ሕያው ላደረገን፥ መቀስቀስም ወደ እርሱ ነው"። عَنْ حُذَيْفَةَ، قَالَ كَانَ النَّبِيُّ صلى الله عليه وسلم إِذَا أَوَى إِلَى فِرَاشِهِ قَالَ " اللَّهُمَّ بِاسْمِكَ أَحْيَا وَأَمُوتُ ". وَإِذَا أَصْبَحَ قَالَ " الْحَمْدُ لِلَّهِ الَّذِي أَحْيَانَا بَعْدَ مَا أَمَاتَنَا وَإِلَيْهِ النُّشُورُ "
"ያችንም ያልሞተችውን በእንቅልፏ ጊዜ ይወስዳታል" ማለት ሩሕ በእንቅልፍ ጊዜ መወሰዷን ሲያመለክት "አላህ ነፍሶችን በሞታቸው ጊዜ ይወስዳል" ማለት ደግሞ በሞት ጊዜ አካል ወደ አፈር ሲመለስ ሩሕ ወደ አሏህ ይወሰዳል፦
39፥42 አላህ ነፍሶችን በሞታቸው ጊዜ ይወስዳል፥ ያችንም ያልሞተችውን በእንቅልፏ ጊዜ ይወስዳታል፡፡ ٱللَّهُ يَتَوَفَّى ٱلْأَنفُسَ حِينَ مَوْتِهَا وَٱلَّتِى لَمْ تَمُتْ فِى مَنَامِهَا
እዚህ አንቀጽ ላይ "ይወስዳል" ለሚለው የገባው ቃል "የተወፈ" يَتَوَفَّى ሲሆን አሏህ መለኩል መውትን በመላክ ነፍስን ይወስዳል፦
32፥11 «በእናንተ የተወከለው መልአከ ሞት ይወስዳችኋል፡፡ ከዚያም ወደ ጌታችሁ ትመለሳላችሁ» በላቸው፡፡ قُلْ يَتَوَفَّاكُم مَّلَكُ الْمَوْتِ الَّذِي وُكِّلَ بِكُمْ ثُمَّ إِلَىٰ رَبِّكُمْ تُرْجَعُونَ
"የተወፋኩም" يَتَوَفَّاكُم ማለት "ይወስዳችኋል" ማለት ሲሆን "መለኩል መውት" مَلَكُ المَوت ማለት "መልአከ ሞት" ወይም "የሞት መልአክ" ማለት ነው። "ሞት" የሚለው ቃል ተዛራፊ እንጂ ባለቤትን አያመለክትም፥ መልአከ ሞት የሚባሉት መላእክት ብዙ ናቸው፦
6፥61 አንዳችሁንም ሞት በመጣበት ጊዜ የሞት መልእክተኞቻችን እነርሱ ትእዛዛትን የማያጓድሉ ሲኾኑ ይወስዱታል፡፡ حَتَّىٰ إِذَا جَاءَ أَحَدَكُمُ الْمَوْتُ تَوَفَّتْهُ رُسُلُنَا وَهُمْ لَا يُفَرِّطُونَ
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
39፥42 አላህ ነፍሶችን በሞታቸው ጊዜ ይወስዳል፥ ያችንም ያልሞተችውን በእንቅልፏ ጊዜ ይወስዳታል፡፡ ٱللَّهُ يَتَوَفَّى ٱلْأَنفُسَ حِينَ مَوْتِهَا وَٱلَّتِى لَمْ تَمُتْ فِى مَنَامِهَا
አሏህ ሩሓችንን በእንቅልፏ ጊዜ ሲወስዳት ያለ ውጫዊ ነገር በውሳጣዊ ነገር ታያለች፣ ትሰማለች፣ ትሄዳለች፣ ትናገራለች፥ የሕልም ዓለም ሩሕ ከአካል ከተለየች በኃላ ያለውን ሕይወት ማሳያ ናሙና ነው። አምላካችን አሏህ በሌሊት ይወስደናል፥ ከዚያም በቀን ይቀሰቅሰናል፦
6፥60 "እርሱም ያ በሌሊት "የሚወስዳችሁ" በቀንም የሠራችሁትን ሁሉ የሚያውቅ ከዚያም የተወሰነው ጊዜ ይፈፀም ዘንድ በእርሱ በቀን ውስጥ "የሚቀሰቅሳችሁ" ነው"፡፡ وَهُوَ الَّذِي يَتَوَفَّاكُم بِاللَّيْلِ وَيَعْلَمُ مَا جَرَحْتُم بِالنَّهَارِ ثُمَّ يَبْعَثُكُمْ فِيهِ لِيُقْضَىٰ أَجَلٌ مُّسَمًّى
"የሚወስዷችሁ" ለሚለው የገባው ቃል "የተወፋኩም" يَتَوَفَّاكُم ሲሆን "የሚያስተኛችሁ" ማለትም ነው። አምላካችን አሏህ በቀን ደግሞ ይቀሰቅሰናል፥ "በቀን ውስጥ የሚቀሰቅሳችሁ ነው" የሚለው ይሰመርበት! አሏህ ሩሓችንን በእንቅልፍ ጊዜ ወስዶ በንቃት ጊዜ ይመልሳል፦
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 97, ሐዲስ 97
አቡ ቀታዳህ እንደተረከው፦ "ከሶላት ሰዎች በተኙ ጊዜ የአሏህ ነቢይም"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "አሏህ በሚሻው ጊዜ ሩሓችሁን ይወስዳል፥ በሚሻው ጊዜ ይመልሳል"። عَنْ عَبْدِ اللَّهِ بْنِ أَبِي قَتَادَةَ، عَنْ أَبِيهِ، حِينَ نَامُوا عَنِ الصَّلاَةِ، قَالَ النَّبِيُّ صلى الله عليه وسلم " إِنَّ اللَّهَ قَبَضَ أَرْوَاحَكُمْ حِينَ شَاءَ، وَرَدَّهَا حِينَ شَاءَ "
ሰው የመንፈስ እና የአካል ሁለትዮች"bi-partite" ቀዋሚ ማንነት ሲሆን አካሉ በሌሊት እንቅልፍ እንደሚያርፍ እና በቀን እንደሚቀሰቀስ ሁሉ በሞትን ጊዜ አካሉ በትልቁ እንቅልፍ ያርፍ እና በትንሳኤ ቀን ይቀሰቀሳል፦
36፥51 በቀንዱም ይነፋል፥ ወዲያውኑም እነርሱ ከመቃብሮቻቸው ወደ ጌታቸው በፍጥነት ይገሰግሳሉ፡፡ وَنُفِخَ فِي الصُّورِ فَإِذَا هُم مِّنَ الْأَجْدَاثِ إِلَىٰ رَبِّهِمْ يَنسِلُونَ
36፥52 «ወይ ጥፋታችን! ከእንቅልፋችን ማን ቀሰቀሰን? ይህ ያ አዛኙ ጌታ በእርሱ የቀጠረን እና መልእክተኞቹ እውነትን የነገሩን ነው» ይላሉ፡፡ قَالُوا يَا وَيْلَنَا مَن بَعَثَنَا مِن مَّرْقَدِنَا ۜ ۗ هَـٰذَا مَا وَعَدَ الرَّحْمَـٰنُ وَصَدَقَ الْمُرْسَلُونَ
እንቅልፍ ሩሕ እና አካል የሚለያዩበት ስለሆነ የሞት ወንድም ተብሏል፥ እንቅልፍ ትንሹ ሞት ስለሆነ ለዛ ነው የምሽት ዚክር ላይ "አሏህ ሆይ! በስምህ እሞታለው ሕያው እሆናለው" የንጋት ዚክር ላይ ደግሞ፦ "ለአሏህ ምስጋና ይሁን! ለዚያ ከአሞተን በኃላ ሕያው ላደረገን፥ መቀስቀስም ወደ እርሱ ነው" የምንለው፦
አል-ሙጀመል አውሠጥ መጽሐፍ 1, ሐዲስ 938
ጃቢር ኢብኑ ዐብደሏህ እንደተረከው፦ "የአሏህ ነቢይም"ﷺ" እንዲህ ተጠየቁ፦ "የአሏህ መልእክተኛ ሆይ! የጀናህ ባለቤቶች ይተኛሉን? የአሏህ መልእክተኛም"ﷺ" እንዲህ ሲሉ መለሱ፦ "እንቅልፍ የሞት ወንድም ነውና የጀናህ ባለቤቶች አይተኙም"። عَنْ جَابِرِ بْنِ عَبْدِ اللَّهِ قَالَ سُئِلَ نَبِيُّ اللَّهِ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ فَقِيلَ يَا رَسُولَ اللَّهِ أَيَنَامُ أَهْلُ الْجَنَّةِ فَقَالَ رَسُولُ اللَّهِ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ النَّوْمُ أَخُو الْمَوْتِ وَأَهْلُ الْجَنَّةِ لا يَنَامُونَ
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 97, ሐዲስ 23
ሑዘይፋህ እንደተረከው፦ "ነቢዩ"ﷺ" ወደ አልጋቸው በሄዱ ጊዜ፦ "አሏህ ሆይ! በስምህ እሞታለው ሕያው እሆናለው" ይሉ ነበር፥ በነቁ ጊዜ፦ "ለአሏህ ምስጋና ይሁን! ለዚያ ከአሞተን በኃላ ሕያው ላደረገን፥ መቀስቀስም ወደ እርሱ ነው"። عَنْ حُذَيْفَةَ، قَالَ كَانَ النَّبِيُّ صلى الله عليه وسلم إِذَا أَوَى إِلَى فِرَاشِهِ قَالَ " اللَّهُمَّ بِاسْمِكَ أَحْيَا وَأَمُوتُ ". وَإِذَا أَصْبَحَ قَالَ " الْحَمْدُ لِلَّهِ الَّذِي أَحْيَانَا بَعْدَ مَا أَمَاتَنَا وَإِلَيْهِ النُّشُورُ "
"ያችንም ያልሞተችውን በእንቅልፏ ጊዜ ይወስዳታል" ማለት ሩሕ በእንቅልፍ ጊዜ መወሰዷን ሲያመለክት "አላህ ነፍሶችን በሞታቸው ጊዜ ይወስዳል" ማለት ደግሞ በሞት ጊዜ አካል ወደ አፈር ሲመለስ ሩሕ ወደ አሏህ ይወሰዳል፦
39፥42 አላህ ነፍሶችን በሞታቸው ጊዜ ይወስዳል፥ ያችንም ያልሞተችውን በእንቅልፏ ጊዜ ይወስዳታል፡፡ ٱللَّهُ يَتَوَفَّى ٱلْأَنفُسَ حِينَ مَوْتِهَا وَٱلَّتِى لَمْ تَمُتْ فِى مَنَامِهَا
እዚህ አንቀጽ ላይ "ይወስዳል" ለሚለው የገባው ቃል "የተወፈ" يَتَوَفَّى ሲሆን አሏህ መለኩል መውትን በመላክ ነፍስን ይወስዳል፦
32፥11 «በእናንተ የተወከለው መልአከ ሞት ይወስዳችኋል፡፡ ከዚያም ወደ ጌታችሁ ትመለሳላችሁ» በላቸው፡፡ قُلْ يَتَوَفَّاكُم مَّلَكُ الْمَوْتِ الَّذِي وُكِّلَ بِكُمْ ثُمَّ إِلَىٰ رَبِّكُمْ تُرْجَعُونَ
"የተወፋኩም" يَتَوَفَّاكُم ማለት "ይወስዳችኋል" ማለት ሲሆን "መለኩል መውት" مَلَكُ المَوت ማለት "መልአከ ሞት" ወይም "የሞት መልአክ" ማለት ነው። "ሞት" የሚለው ቃል ተዛራፊ እንጂ ባለቤትን አያመለክትም፥ መልአከ ሞት የሚባሉት መላእክት ብዙ ናቸው፦
6፥61 አንዳችሁንም ሞት በመጣበት ጊዜ የሞት መልእክተኞቻችን እነርሱ ትእዛዛትን የማያጓድሉ ሲኾኑ ይወስዱታል፡፡ حَتَّىٰ إِذَا جَاءَ أَحَدَكُمُ الْمَوْتُ تَوَفَّتْهُ رُسُلُنَا وَهُمْ لَا يُفَرِّطُونَ
እነዚህ የሞት መላእክት በጥቅሉ "አን ናዚዓት" እና "አን-ናሺጧት" ይባላሉ፥ "አን ናዚዓት" النَّازِعَات ማለት "በኃይል ወሳጆች" "ሩሕን ከአካል በኃይል አውጪዎች" ማለት ሲሆን አን-ናዚዓት በመባል የሚታወቁት የሞት መላእክት የከሓድያንን ሩሕ በኃይል አውጪዎች ናቸው። አን ናዚዓት ከሓድያንን የሚወስዷቸው ኾነው በመጡባቸው ጊዜ "ከአላህ ሌላ ትገዟቸው የነበራችሁት የት አሉ?» ይሏቸዋል፡፡ «ከእኛ ተሰወሩን» ይላሉ፥ እነርሱም ከሓዲያን እንደነበሩ በራሳቸው ላይ ይመሰክራሉ፦
79፥1 በኃይል አውጪዎች በኾኑት"። وَالنَّازِعَاتِ غَرْقًا
7፥37 የሞት መልእክተኞቻችንም "የሚወስዷቸው" ኾነው በመጡባቸው ጊዜ «ከአላህ ሌላ ትገዟቸው የነበራችሁት የት አሉ?» ይሏቸዋል፡፡ «ከእኛ ተሰወሩን» ይላሉ፡፡ እነርሱም ከሓዲያን እንደነበሩ በራሳቸው ላይ ይመሰክራሉ፡፡ حَتَّىٰ إِذَا جَاءَتْهُمْ رُسُلُنَا يَتَوَفَّوْنَهُمْ قَالُوا أَيْنَ مَا كُنتُمْ تَدْعُونَ مِن دُونِ اللَّهِ ۖ قَالُوا ضَلُّوا عَنَّا وَشَهِدُوا عَلَىٰ أَنفُسِهِمْ أَنَّهُمْ كَانُوا كَافِرِينَ
8፥50 መላእክት እነዚያንም የካዱትን ፊቶቻቸውን እና ጀርባዎቻቸውን እየመቱ «የቃጠሎንም ስቃይ ቅመሱ» እያሉ በሚወስዷቸው ጊዜ ብታይ ኖሮ አስደንጋጭን ነገር ታይ ነበር፡፡ وَلَوْ تَرَىٰ إِذْ يَتَوَفَّى الَّذِينَ كَفَرُوا ۙ الْمَلَائِكَةُ يَضْرِبُونَ وُجُوهَهُمْ وَأَدْبَارَهُمْ وَذُوقُوا عَذَابَ الْحَرِيقِ
"አን-ናሺጧት" النَّاشِطَات ማለት "በቀስታ ወሳጆች" "ሩሕን ከአካል በቀስታ መዘማዦች" ማለት ሲሆን አን-ናሺጧት በመባል የሚታወቁት የሞት መላእክት የአማንያንን ሩሕ በቀስታ አውጪዎች ናቸው። አን-ናሺጧት አማንያንን፦ "ሰላም በእናንተ ላይ" እያሉ የሚወስዷቸው ናቸው፡፡ "ትሠሩት በነበራችሁት ሥራ ገነትን ግቡ" ይባላሉ፦
79፥2 "በቀስታ መምዘዝንም መዘማዦች በኾኑት"። وَالنَّاشِطَاتِ نَشْطًا
16፥32 እነዚያ በመልካም ኹኔታ ላይ ኾነው መላእክት «ሰላም በእናንተ ላይ» እያሉ የሚወስዷቸው ናቸው፡፡ «ትሠሩት በነበራችሁት ሥራ ገነትን ግቡ» ይባላሉ፡፡ الَّذِينَ تَتَوَفَّاهُمُ الْمَلَائِكَةُ طَيِّبِينَ ۙ يَقُولُونَ سَلَامٌ عَلَيْكُمُ ادْخُلُوا الْجَنَّةَ بِمَا كُنتُمْ تَعْمَلُونَ
ከሞት በኃላ ሩሕ ሲወሰድ የሞት መላእክት እና ሩሓችን መነጋገራቸው በራሱ ሩሕ በሞት ጊዜ የሚወሰድ እንጂ ከአካል ጋር በአፈር የሚበሰብስ አለመሆኑን በቂ ማሳያ ነው። አምላካችን አሏህ "ትሠሩት በነበራችሁት ሥራ ገነትን ግቡ" ከሚላት የጀነት ባለቤቶች ያድርገን! አሚን።
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
79፥1 በኃይል አውጪዎች በኾኑት"። وَالنَّازِعَاتِ غَرْقًا
7፥37 የሞት መልእክተኞቻችንም "የሚወስዷቸው" ኾነው በመጡባቸው ጊዜ «ከአላህ ሌላ ትገዟቸው የነበራችሁት የት አሉ?» ይሏቸዋል፡፡ «ከእኛ ተሰወሩን» ይላሉ፡፡ እነርሱም ከሓዲያን እንደነበሩ በራሳቸው ላይ ይመሰክራሉ፡፡ حَتَّىٰ إِذَا جَاءَتْهُمْ رُسُلُنَا يَتَوَفَّوْنَهُمْ قَالُوا أَيْنَ مَا كُنتُمْ تَدْعُونَ مِن دُونِ اللَّهِ ۖ قَالُوا ضَلُّوا عَنَّا وَشَهِدُوا عَلَىٰ أَنفُسِهِمْ أَنَّهُمْ كَانُوا كَافِرِينَ
8፥50 መላእክት እነዚያንም የካዱትን ፊቶቻቸውን እና ጀርባዎቻቸውን እየመቱ «የቃጠሎንም ስቃይ ቅመሱ» እያሉ በሚወስዷቸው ጊዜ ብታይ ኖሮ አስደንጋጭን ነገር ታይ ነበር፡፡ وَلَوْ تَرَىٰ إِذْ يَتَوَفَّى الَّذِينَ كَفَرُوا ۙ الْمَلَائِكَةُ يَضْرِبُونَ وُجُوهَهُمْ وَأَدْبَارَهُمْ وَذُوقُوا عَذَابَ الْحَرِيقِ
"አን-ናሺጧት" النَّاشِطَات ማለት "በቀስታ ወሳጆች" "ሩሕን ከአካል በቀስታ መዘማዦች" ማለት ሲሆን አን-ናሺጧት በመባል የሚታወቁት የሞት መላእክት የአማንያንን ሩሕ በቀስታ አውጪዎች ናቸው። አን-ናሺጧት አማንያንን፦ "ሰላም በእናንተ ላይ" እያሉ የሚወስዷቸው ናቸው፡፡ "ትሠሩት በነበራችሁት ሥራ ገነትን ግቡ" ይባላሉ፦
79፥2 "በቀስታ መምዘዝንም መዘማዦች በኾኑት"። وَالنَّاشِطَاتِ نَشْطًا
16፥32 እነዚያ በመልካም ኹኔታ ላይ ኾነው መላእክት «ሰላም በእናንተ ላይ» እያሉ የሚወስዷቸው ናቸው፡፡ «ትሠሩት በነበራችሁት ሥራ ገነትን ግቡ» ይባላሉ፡፡ الَّذِينَ تَتَوَفَّاهُمُ الْمَلَائِكَةُ طَيِّبِينَ ۙ يَقُولُونَ سَلَامٌ عَلَيْكُمُ ادْخُلُوا الْجَنَّةَ بِمَا كُنتُمْ تَعْمَلُونَ
ከሞት በኃላ ሩሕ ሲወሰድ የሞት መላእክት እና ሩሓችን መነጋገራቸው በራሱ ሩሕ በሞት ጊዜ የሚወሰድ እንጂ ከአካል ጋር በአፈር የሚበሰብስ አለመሆኑን በቂ ማሳያ ነው። አምላካችን አሏህ "ትሠሩት በነበራችሁት ሥራ ገነትን ግቡ" ከሚላት የጀነት ባለቤቶች ያድርገን! አሚን።
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
በርዘኽ
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
23፥100 ከስተፊታቸውም እስከሚቀሰቀሱበት ቀን ድረስ "ግርዶ" አለ፡፡ وَمِن وَرَائِهِم بَرْزَخٌ إِلَىٰ يَوْمِ يُبْعَثُونَ
አምላካችን አሏህ ሕያው አርጎ እንደፈጠረን በሞት የሚያሞተን እርሱ ነው፥ ካሞተን በኃላ ሁላችንም ወደ እርሱ እንመለሳለን፦
22፥23 እኛም ሕያው የምናደርግ እና የምናሞት እኛው ብቻ ነን፡፡ وَإِنَّا لَنَحْنُ نُحْيِي وَنُمِيتُ
10፥56 እርሱ ሕያው ያደርጋል ያሞታልም፥ ወደ እርሱም ትመለሳላችሁ፡፡ هُوَ يُحْيِي وَيُمِيتُ وَإِلَيْهِ تُرْجَعُونَ
5፥105 የሁላችሁም መመለሻ ወደ አላህ ብቻ ነው፡፡ ትሠሩትም የነበራችሁትን ሁሉ ይነግራችኋል፡፡ إِلَى اللَّهِ مَرْجِعُكُمْ جَمِيعًا فَيُنَبِّئُكُم بِمَا كُنتُمْ تَعْمَلُونَ
"ቀብር" قَبْر የሚለው ቃል "ቀበረ" قَبَرَ ማለትም "ሸፈነ" "ደበቀ" "ሸሸገ" "ቀበረ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "ሽፍን" "ድብቅ" "ሽሽግ" "ቀብር" ማለት ነው፥ "ቀብር" አጠቃላይ ከሞት በኃላ ከአምስቱ የስሜት ህዋሳት ባሻገር ተሸፍኖ፣ ተደብቆ፣ ተሸሽጎ፣ ተቀብሮ ያለ የአኺራህ የመጀመሪያው ደረጃ ነው፦
ጃምዒ አት-ቲርሚዚይ መጽሐፍ 36, ሐዲስ 5
የዑስማን ነጻ ባሪያ ሃኒእ ሰምቶ እንደተረከው፦ "ዑስማን መቃብር ላይ ሲቆሙ ፂሙ በእንባ እስኪርስ ድረስ አለቀሰ፥ ለእርሱም፦ "ጀነት እና እሳት ሲዘከሩ ሳታለቅስ ለዚህ ለምን ታለቅሳለህ? ተባለ፥ እርሱም እንዲህ አለ፦ "የአሏህ መልእክተኛ"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "በእርግጥ ቀብር የአኺራህ መጀመሪያ ደረጃ ነው። ስለዚህ አንድ ሰው ከቀብር የዳነ ከሆነ ከዚያ በኋላ የሚመጣው ከቀብር የበለጠ ቀላል ነው፥ አንድ ሰው ከቀብር ካልዳነ ከዚያ በኋላ የሚመጣው ከቀብር የከፋ ነው። أَنَّهُ سَمِعَ هَانِئًا، مَوْلَى عُثْمَانَ قَالَ كَانَ عُثْمَانُ إِذَا وَقَفَ عَلَى قَبْرٍ بَكَى حَتَّى يَبُلَّ لِحْيَتَهُ فَقِيلَ لَهُ تُذْكَرُ الْجَنَّةُ وَالنَّارُ فَلاَ تَبْكِي وَتَبْكِي مِنْ هَذَا فَقَالَ إِنَّ رَسُولَ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم قَالَ " إِنَّ الْقَبْرَ أَوَّلُ مَنَازِلِ الآخِرَةِ فَإِنْ نَجَا مِنْهُ فَمَا بَعْدَهُ أَيْسَرُ مِنْهُ وَإِنْ لَمْ يَنْجُ مِنْهُ فَمَا بَعْدَهُ أَشَدُّ مِنْهُ "
"አኺራህ" آخِرَة ማለት "ቀጣይ ዓለም" ማለት ሲሆን ከሞት በኃላ ያለው ዓለም ነው። አን ናዚዓት እና አን-ናሺጧት በተባሉ የሞት መላእክት ስንወሰድ በቀብር "አል ሙንከር" الْمُنْكَر እና "አን ነኪር" الْنَّكِير የተባሉ መላእክት ለሰው፦ "ጌታህ ማን ነው? ዲንህ ምንድን ነው? ነቢይህ ማን ነው?” ብለው ይጠይቃሉ። አማኝም ከሆነ፦ "ጌታዬ አሏህ ነው፣ ዲኔ ኢሥላም ነው፣ ነቢዬም የአሏህ መልእክተኛ"ﷺ" ነው" ብሎ ሲመልስ ለእርሱ ጀነት እዲገባ ይከፈትለታል፥ ከሓዲ ከሆነ፦ "ዐላውቅም፣ ዐላውቅም፣ ዐላውቅም" ብሎ ሲመልስ ለእርሱ እሳት እዲገባ ይከፈትለታል፦
ሡነን አቢ ዳውድ መጽሐፍ 42, ሐዲስ 158
ጃምዒ አት-ቲርሚዚይ መጽሐፍ 10, ሐዲስ 107
"በርዘኽ" بَرْزَخ ማለት ሁለት ነገርን እንዳይገናኝ በመካከላቸው ያለ "ጋራጅ"partition" ነው፥ ለምሳሌ፦ ጥቁር ባሕር፣ ባልቲክ ባሕር፣ ቀይ ባሕር፣ ሜድትራኒያን ባሕር፣ ፓስፊክ ውቂያኖስ፣ አትላንቲክ ውቂያኖስ እና የሕንድ ውቂያኖስ በውስጣቸው መራራ ውኃ እና ጣፋጭ ውኃ ይዘዋል። እነዚህ ሁለቱ ባሕሮች እንዳይገናኙ በመካከላቸው በርዘኽ አለ፦
55፥19 ሁለቱን ባሕሮች የሚገናኙ ሲኾኑ ለቀቃቸው፡፡ مَرَجَ الْبَحْرَيْنِ يَلْتَقِيَانِ
55፥20 እንዳይገናኙ በመካከላቸው "ጋራጅ" አለ፡፡ አንዱ ባንዱ ላይ ወሰን አያልፉም፡፡ بَيْنَهُمَا بَرْزَخٌ لَّا يَبْغِيَانِ
እዚህ አንቀጽ ላይ "ጋራጅ" ለሚለው የገባው ቃል "በርዘኽ" بَرْزَخ ሲሆን "ግርዶ" "መለያ" "ክልል" ማለት ነው። በተመሳሳይም ሁሉም ሰው ወደ አሏህ ከተመለሰ በኃላ አማንያን ያሉበት ጀናህ እና ከሓዲያን ያሉበት እሳት በመካከላቸው እንዳይገናኙ እስከ ትንሣኤ ቀን ድረስ በርዘኽ አለ፦
23፥100 ከስተፊታቸውም እስከሚቀሰቀሱበት ቀን ድረስ "ግርዶ" አለ፡፡ وَمِن وَرَائِهِم بَرْزَخٌ إِلَىٰ يَوْمِ يُبْعَثُونَ
እዚህ አንቀጽ ላይ "ግርዶ" ለሚለው የገባው ቃል "በርዘኽ" بَرْزَخ ሲሆን ልክ የእናት ማኅፀን ከፅንስ እስከ ልደት ጊዜአዊ መቆያ እንደሆነ ሁሉ በርዘኽም ከሞት እስከ ትንሳኤ ቀን ድረስ ያለ መካከለኛ ቀጠና"intermediate zone" ነው። በጊዜአዊ መቆያ የገነት ሰዎች እና የእሳት ሰዎች የንግግር ልውውጥ ያረጋሉ፦
7፥44 የገነትም ሰዎች የእሳትን ሰዎች፦ «ጌታችን ቃል የገባልንን እውነት ኾኖ አገኘን፡፡ ጌታችሁ የዛተባችሁንስ እውነት ኾኖ አገኛችሁትን?» ሲሉ ይጣራሉ፡፡ «አዎን አገኘን» ይላሉ፡፡ በመካከላቸውም «የአላህ ርግማን በበደለኞች ላይ ይኹን» ሲል ለፋፊ ይለፍፋል፡፡ وَنَادَىٰ أَصْحَابُ الْجَنَّةِ أَصْحَابَ النَّارِ أَن قَدْ وَجَدْنَا مَا وَعَدَنَا رَبُّنَا حَقًّا فَهَلْ وَجَدتُّم مَّا وَعَدَ رَبُّكُمْ حَقًّا ۖ قَالُوا نَعَمْ ۚ فَأَذَّنَ مُؤَذِّنٌ بَيْنَهُمْ أَن لَّعْنَةُ اللَّهِ عَلَى الظَّالِمِينَ
7፥50 የእሳትም ሰዎች የገነትን ሰዎች፦ «በእኛ ላይ ከውኃ አፍስሱብን ወይም አላህ ከሰጣችሁ ሲሳይ ጣሉልን» ብለው ጠሩዋቸዋል፡፡ እነርሱም «አላህ በከሓዲዎች ላይ እርም አድርጓቸዋል» ይሏቸዋል፡፡ وَنَادَىٰ أَصْحَابُ النَّارِ أَصْحَابَ الْجَنَّةِ أَنْ أَفِيضُوا عَلَيْنَا مِنَ الْمَاءِ أَوْ مِمَّا رَزَقَكُمُ اللَّهُ ۚ قَالُوا إِنَّ اللَّهَ حَرَّمَهُمَا عَلَى الْكَافِرِينَ
የገነትም ሰዎች የእሳትን ሰዎችን የእሳትም ሰዎች የገነትን ሰዎችን ቢያነጋግሩም በመካከላቸውም እንዳይገናኙ "ግርዶሽ" አለ፦
7፥46 በመካከላቸውም "ግርዶሽ" አለ። وَبَيْنَهُمَا حِجَابٌ
አምላካችን አሏህ ከእሳት ቅጣት ይጠብቀን! የጀነት ያድርገን! አሚን።
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
23፥100 ከስተፊታቸውም እስከሚቀሰቀሱበት ቀን ድረስ "ግርዶ" አለ፡፡ وَمِن وَرَائِهِم بَرْزَخٌ إِلَىٰ يَوْمِ يُبْعَثُونَ
አምላካችን አሏህ ሕያው አርጎ እንደፈጠረን በሞት የሚያሞተን እርሱ ነው፥ ካሞተን በኃላ ሁላችንም ወደ እርሱ እንመለሳለን፦
22፥23 እኛም ሕያው የምናደርግ እና የምናሞት እኛው ብቻ ነን፡፡ وَإِنَّا لَنَحْنُ نُحْيِي وَنُمِيتُ
10፥56 እርሱ ሕያው ያደርጋል ያሞታልም፥ ወደ እርሱም ትመለሳላችሁ፡፡ هُوَ يُحْيِي وَيُمِيتُ وَإِلَيْهِ تُرْجَعُونَ
5፥105 የሁላችሁም መመለሻ ወደ አላህ ብቻ ነው፡፡ ትሠሩትም የነበራችሁትን ሁሉ ይነግራችኋል፡፡ إِلَى اللَّهِ مَرْجِعُكُمْ جَمِيعًا فَيُنَبِّئُكُم بِمَا كُنتُمْ تَعْمَلُونَ
"ቀብር" قَبْر የሚለው ቃል "ቀበረ" قَبَرَ ማለትም "ሸፈነ" "ደበቀ" "ሸሸገ" "ቀበረ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "ሽፍን" "ድብቅ" "ሽሽግ" "ቀብር" ማለት ነው፥ "ቀብር" አጠቃላይ ከሞት በኃላ ከአምስቱ የስሜት ህዋሳት ባሻገር ተሸፍኖ፣ ተደብቆ፣ ተሸሽጎ፣ ተቀብሮ ያለ የአኺራህ የመጀመሪያው ደረጃ ነው፦
ጃምዒ አት-ቲርሚዚይ መጽሐፍ 36, ሐዲስ 5
የዑስማን ነጻ ባሪያ ሃኒእ ሰምቶ እንደተረከው፦ "ዑስማን መቃብር ላይ ሲቆሙ ፂሙ በእንባ እስኪርስ ድረስ አለቀሰ፥ ለእርሱም፦ "ጀነት እና እሳት ሲዘከሩ ሳታለቅስ ለዚህ ለምን ታለቅሳለህ? ተባለ፥ እርሱም እንዲህ አለ፦ "የአሏህ መልእክተኛ"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "በእርግጥ ቀብር የአኺራህ መጀመሪያ ደረጃ ነው። ስለዚህ አንድ ሰው ከቀብር የዳነ ከሆነ ከዚያ በኋላ የሚመጣው ከቀብር የበለጠ ቀላል ነው፥ አንድ ሰው ከቀብር ካልዳነ ከዚያ በኋላ የሚመጣው ከቀብር የከፋ ነው። أَنَّهُ سَمِعَ هَانِئًا، مَوْلَى عُثْمَانَ قَالَ كَانَ عُثْمَانُ إِذَا وَقَفَ عَلَى قَبْرٍ بَكَى حَتَّى يَبُلَّ لِحْيَتَهُ فَقِيلَ لَهُ تُذْكَرُ الْجَنَّةُ وَالنَّارُ فَلاَ تَبْكِي وَتَبْكِي مِنْ هَذَا فَقَالَ إِنَّ رَسُولَ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم قَالَ " إِنَّ الْقَبْرَ أَوَّلُ مَنَازِلِ الآخِرَةِ فَإِنْ نَجَا مِنْهُ فَمَا بَعْدَهُ أَيْسَرُ مِنْهُ وَإِنْ لَمْ يَنْجُ مِنْهُ فَمَا بَعْدَهُ أَشَدُّ مِنْهُ "
"አኺራህ" آخِرَة ማለት "ቀጣይ ዓለም" ማለት ሲሆን ከሞት በኃላ ያለው ዓለም ነው። አን ናዚዓት እና አን-ናሺጧት በተባሉ የሞት መላእክት ስንወሰድ በቀብር "አል ሙንከር" الْمُنْكَر እና "አን ነኪር" الْنَّكِير የተባሉ መላእክት ለሰው፦ "ጌታህ ማን ነው? ዲንህ ምንድን ነው? ነቢይህ ማን ነው?” ብለው ይጠይቃሉ። አማኝም ከሆነ፦ "ጌታዬ አሏህ ነው፣ ዲኔ ኢሥላም ነው፣ ነቢዬም የአሏህ መልእክተኛ"ﷺ" ነው" ብሎ ሲመልስ ለእርሱ ጀነት እዲገባ ይከፈትለታል፥ ከሓዲ ከሆነ፦ "ዐላውቅም፣ ዐላውቅም፣ ዐላውቅም" ብሎ ሲመልስ ለእርሱ እሳት እዲገባ ይከፈትለታል፦
ሡነን አቢ ዳውድ መጽሐፍ 42, ሐዲስ 158
ጃምዒ አት-ቲርሚዚይ መጽሐፍ 10, ሐዲስ 107
"በርዘኽ" بَرْزَخ ማለት ሁለት ነገርን እንዳይገናኝ በመካከላቸው ያለ "ጋራጅ"partition" ነው፥ ለምሳሌ፦ ጥቁር ባሕር፣ ባልቲክ ባሕር፣ ቀይ ባሕር፣ ሜድትራኒያን ባሕር፣ ፓስፊክ ውቂያኖስ፣ አትላንቲክ ውቂያኖስ እና የሕንድ ውቂያኖስ በውስጣቸው መራራ ውኃ እና ጣፋጭ ውኃ ይዘዋል። እነዚህ ሁለቱ ባሕሮች እንዳይገናኙ በመካከላቸው በርዘኽ አለ፦
55፥19 ሁለቱን ባሕሮች የሚገናኙ ሲኾኑ ለቀቃቸው፡፡ مَرَجَ الْبَحْرَيْنِ يَلْتَقِيَانِ
55፥20 እንዳይገናኙ በመካከላቸው "ጋራጅ" አለ፡፡ አንዱ ባንዱ ላይ ወሰን አያልፉም፡፡ بَيْنَهُمَا بَرْزَخٌ لَّا يَبْغِيَانِ
እዚህ አንቀጽ ላይ "ጋራጅ" ለሚለው የገባው ቃል "በርዘኽ" بَرْزَخ ሲሆን "ግርዶ" "መለያ" "ክልል" ማለት ነው። በተመሳሳይም ሁሉም ሰው ወደ አሏህ ከተመለሰ በኃላ አማንያን ያሉበት ጀናህ እና ከሓዲያን ያሉበት እሳት በመካከላቸው እንዳይገናኙ እስከ ትንሣኤ ቀን ድረስ በርዘኽ አለ፦
23፥100 ከስተፊታቸውም እስከሚቀሰቀሱበት ቀን ድረስ "ግርዶ" አለ፡፡ وَمِن وَرَائِهِم بَرْزَخٌ إِلَىٰ يَوْمِ يُبْعَثُونَ
እዚህ አንቀጽ ላይ "ግርዶ" ለሚለው የገባው ቃል "በርዘኽ" بَرْزَخ ሲሆን ልክ የእናት ማኅፀን ከፅንስ እስከ ልደት ጊዜአዊ መቆያ እንደሆነ ሁሉ በርዘኽም ከሞት እስከ ትንሳኤ ቀን ድረስ ያለ መካከለኛ ቀጠና"intermediate zone" ነው። በጊዜአዊ መቆያ የገነት ሰዎች እና የእሳት ሰዎች የንግግር ልውውጥ ያረጋሉ፦
7፥44 የገነትም ሰዎች የእሳትን ሰዎች፦ «ጌታችን ቃል የገባልንን እውነት ኾኖ አገኘን፡፡ ጌታችሁ የዛተባችሁንስ እውነት ኾኖ አገኛችሁትን?» ሲሉ ይጣራሉ፡፡ «አዎን አገኘን» ይላሉ፡፡ በመካከላቸውም «የአላህ ርግማን በበደለኞች ላይ ይኹን» ሲል ለፋፊ ይለፍፋል፡፡ وَنَادَىٰ أَصْحَابُ الْجَنَّةِ أَصْحَابَ النَّارِ أَن قَدْ وَجَدْنَا مَا وَعَدَنَا رَبُّنَا حَقًّا فَهَلْ وَجَدتُّم مَّا وَعَدَ رَبُّكُمْ حَقًّا ۖ قَالُوا نَعَمْ ۚ فَأَذَّنَ مُؤَذِّنٌ بَيْنَهُمْ أَن لَّعْنَةُ اللَّهِ عَلَى الظَّالِمِينَ
7፥50 የእሳትም ሰዎች የገነትን ሰዎች፦ «በእኛ ላይ ከውኃ አፍስሱብን ወይም አላህ ከሰጣችሁ ሲሳይ ጣሉልን» ብለው ጠሩዋቸዋል፡፡ እነርሱም «አላህ በከሓዲዎች ላይ እርም አድርጓቸዋል» ይሏቸዋል፡፡ وَنَادَىٰ أَصْحَابُ النَّارِ أَصْحَابَ الْجَنَّةِ أَنْ أَفِيضُوا عَلَيْنَا مِنَ الْمَاءِ أَوْ مِمَّا رَزَقَكُمُ اللَّهُ ۚ قَالُوا إِنَّ اللَّهَ حَرَّمَهُمَا عَلَى الْكَافِرِينَ
የገነትም ሰዎች የእሳትን ሰዎችን የእሳትም ሰዎች የገነትን ሰዎችን ቢያነጋግሩም በመካከላቸውም እንዳይገናኙ "ግርዶሽ" አለ፦
7፥46 በመካከላቸውም "ግርዶሽ" አለ። وَبَيْنَهُمَا حِجَابٌ
አምላካችን አሏህ ከእሳት ቅጣት ይጠብቀን! የጀነት ያድርገን! አሚን።
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
ታላቁ ገደል
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
23፥100 ከስተፊታቸውም እስከሚቀሰቀሱበት ቀን ድረስ "ግርዶ" አለ፡፡ وَمِن وَرَائِهِم بَرْزَخٌ إِلَىٰ يَوْمِ يُبْعَثُونَ
በኢሥላም ስለ በርዘኽ ያለው እሳቤ ከብዙ በጥቂቱ አይተን ነበር። በባይብልም ደግሞ ስለ በርዘኽ እንዲህ ይናገራል፦
ሉቃስ 16፥26 ከዚህም ሁሉ ጋር ከዚህ ወደ እናንተ ሊያልፉ የሚፈልጉ እንዳይችሉ፥ ወዲያ ያሉ ደግሞ ወደ እኛ እንዳይሻገሩ በእኛ እና በእናንተ መካከል ታላቅ "ገደል" ተደርጎአል" አለ።
የገነት ሰዎች ከሲኦል ሰዎች እንዳይተላለፉ እና እንዳይሻገሩ በመካከላቸው ያለው ገደል ምንድን ነው? ባለ ጠጋው በሲኦልም በሥቃይ ሳለ አሻቅቦ አብርሃምን በሩቅ ማየቱ በራሱ ሲኦል እና ገነት ከሞት በኃላ እስከ ትንሳኤ ቀን ድረስ ጊዜአዊ መቆያ ከሆነ በመካከላቸው ያለው ገደል በርዘኽ ነው፦
ሉቃስ 16፥22 ድሀውም ሞተ፥ መላእክትም ወደ አብርሃም እቅፍ ወሰዱት።
ሉቃስ 16፥23 ባለ ጠጋው ደግሞ ሞተና ተቀበረ፥ በሲኦልም በሥቃይ ሳለ አሻቅቦ አብርሃምን በሩቅ አየ አልዓዛርንም በእቅፉ።
"መላእክትም ወደ አብርሃም እቅፍ ወሰዱት" የሚለው በራሱ ልክ እንደ አን ናዚዓት እና አን-ናሺጧት መላእክት መኖራቸውን ጉልኅ ማሳያ ነው፥ አብርሃም ያለበት ስፍራ ደግሞ ገነት ነው፦
1ኛ መቃብያን 3፥38 መላእክትም የጣሉዋቸው ሰዎች ሲያዩ ተቀብለው ነፍሳቸውን ይስሐቅ፣ አብርሃም፣ ያዕቆብ ወዳሉበት ተድላ እና ደስታ ወደሚገኝበት ወደ ገነት ወሰዷቸው ።
1ኛ መቃብያን 6፥2 የእግዚአብሔርን ፈቃድ አድርገዋልና ይስሐቅ፣ አብርሃም፣ ያዕቆብ፣ ሰሎሞን፣ ዳዊት እና ሕዝቅያስ ማደሪያቸው ብርሃን የሆነች እና ያማሩ ነገሥታት ሁሉ ባሉበት በገነት ማደሪያቸውን በማይመረመር ብርሃን ያበራል ።
"በአዳም የተነሳ ሁሉም ነፍሳት ሲኦል ገብተው ኢየሱስ ከሲኦል አወጣቸው" የሚለው ትምህርት ባይብላዊ ማስረጃ የሌለው ከመሆንም ባሻገር ከመቃብያን አሳብ ጋር ይጋጫል። ድሀው ሲሞት የሄደበት የአብርሃም እቅፍ ገነት ከተባለ እና ባለ ጠጋው ሲሞት የሄደበት ሲኦል ከተባለ፣ ባለ ጠጋው በሲኦልም በሥቃይ ሳለ አሻቅቦ አብርሃምን በሩቅ አልዓዛርንም በእቅፉ ካየ፣ አብርሃም በገነት ባለ ጠጋው በሲኦል ሆነው የንግግር ልውጥውጥ ካደረገ እና ሁለቱ እንዳይገናኙ ገደል ካለ ለምን ይሆን ክርስቲያን ሚሽነሪዎች በኢሥላም ያለውን የበርዘኽ እሳቤ የሚሳለቁበት? ስንል ሚሽነሪዎች የራሳቸውን መጽሐፍ ጠንቅቀው አለማወቃቸውን እያሳበቀባቸው ነው። የሁሉም ሰው መንፈስ ወደ ፈጣሪ ይመለሳል፦
መክብብ 12፥7 አፈርም(ሥጋም) ወደ ነበረበት ምድር ሳይመለስ፥ መንፈስም ወደ ሰጠው ወደ አምላክ ሳይመለስ ፈጣሪህን አስብ። וְיָשֹׁ֧ב הֶעָפָ֛ר עַל־הָאָ֖רֶץ כְּשֶׁהָיָ֑ה וְהָר֣וּחַ תָּשׁ֔וּב אֶל־הָאֱלֹהִ֖ים אֲשֶׁ֥ר נְתָנָֽהּ׃
ከአፈር የመጣው ሥጋ ወደ አፈር ሲመለስ መንፈስ ደግሞ ወደ አምላክ ይመለሳል። "ሩአሕ" רוּחַ ማለት "መንፈስ" ማለት ሲሆን በቁርኣን መንፈስ በእሳት ሲቀጣ "በእኛ ላይ ከውኃ አፍስሱብን" ማለታቸውን ስትሳለቁ በባይብል መንፈስ በእሳት ሲቀጣ "በዚህ ነበልባል እሣቀያለሁና የጣቱን ጫፍ በውኃ ነክሮ መላሴን እንዲያበርድልኝ አልዓዛርን ስደድልኝ" ማለቱን ስታውቁ ምን ይውጣችሁ ይሆን? "እሳት፣ ውኃ፣ ጣት፣ ምላስ የሩቅ ነገር ምሥጢር ናቸው" ካላችሁ እንግዲያውስ ውኃ እና እሳት የሩቅ ነገር ምሥጢር ናቸው፦
ሉቃስ 16፥24 እርሱም እየጮኸ፦ "አብርሃም አባት ሆይ! ማረኝ፥ በዚህ ነበልባል እሣቀያለሁና የጣቱን ጫፍ በውኃ ነክሮ መላሴን እንዲያበርድልኝ አልዓዛርን ስደድልኝ" አለ።
አምላካችን አሏህ ከእሳት ቅጣት ይጠብቀን! የጀነት ያድርገን! አሚን።
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
23፥100 ከስተፊታቸውም እስከሚቀሰቀሱበት ቀን ድረስ "ግርዶ" አለ፡፡ وَمِن وَرَائِهِم بَرْزَخٌ إِلَىٰ يَوْمِ يُبْعَثُونَ
በኢሥላም ስለ በርዘኽ ያለው እሳቤ ከብዙ በጥቂቱ አይተን ነበር። በባይብልም ደግሞ ስለ በርዘኽ እንዲህ ይናገራል፦
ሉቃስ 16፥26 ከዚህም ሁሉ ጋር ከዚህ ወደ እናንተ ሊያልፉ የሚፈልጉ እንዳይችሉ፥ ወዲያ ያሉ ደግሞ ወደ እኛ እንዳይሻገሩ በእኛ እና በእናንተ መካከል ታላቅ "ገደል" ተደርጎአል" አለ።
የገነት ሰዎች ከሲኦል ሰዎች እንዳይተላለፉ እና እንዳይሻገሩ በመካከላቸው ያለው ገደል ምንድን ነው? ባለ ጠጋው በሲኦልም በሥቃይ ሳለ አሻቅቦ አብርሃምን በሩቅ ማየቱ በራሱ ሲኦል እና ገነት ከሞት በኃላ እስከ ትንሳኤ ቀን ድረስ ጊዜአዊ መቆያ ከሆነ በመካከላቸው ያለው ገደል በርዘኽ ነው፦
ሉቃስ 16፥22 ድሀውም ሞተ፥ መላእክትም ወደ አብርሃም እቅፍ ወሰዱት።
ሉቃስ 16፥23 ባለ ጠጋው ደግሞ ሞተና ተቀበረ፥ በሲኦልም በሥቃይ ሳለ አሻቅቦ አብርሃምን በሩቅ አየ አልዓዛርንም በእቅፉ።
"መላእክትም ወደ አብርሃም እቅፍ ወሰዱት" የሚለው በራሱ ልክ እንደ አን ናዚዓት እና አን-ናሺጧት መላእክት መኖራቸውን ጉልኅ ማሳያ ነው፥ አብርሃም ያለበት ስፍራ ደግሞ ገነት ነው፦
1ኛ መቃብያን 3፥38 መላእክትም የጣሉዋቸው ሰዎች ሲያዩ ተቀብለው ነፍሳቸውን ይስሐቅ፣ አብርሃም፣ ያዕቆብ ወዳሉበት ተድላ እና ደስታ ወደሚገኝበት ወደ ገነት ወሰዷቸው ።
1ኛ መቃብያን 6፥2 የእግዚአብሔርን ፈቃድ አድርገዋልና ይስሐቅ፣ አብርሃም፣ ያዕቆብ፣ ሰሎሞን፣ ዳዊት እና ሕዝቅያስ ማደሪያቸው ብርሃን የሆነች እና ያማሩ ነገሥታት ሁሉ ባሉበት በገነት ማደሪያቸውን በማይመረመር ብርሃን ያበራል ።
"በአዳም የተነሳ ሁሉም ነፍሳት ሲኦል ገብተው ኢየሱስ ከሲኦል አወጣቸው" የሚለው ትምህርት ባይብላዊ ማስረጃ የሌለው ከመሆንም ባሻገር ከመቃብያን አሳብ ጋር ይጋጫል። ድሀው ሲሞት የሄደበት የአብርሃም እቅፍ ገነት ከተባለ እና ባለ ጠጋው ሲሞት የሄደበት ሲኦል ከተባለ፣ ባለ ጠጋው በሲኦልም በሥቃይ ሳለ አሻቅቦ አብርሃምን በሩቅ አልዓዛርንም በእቅፉ ካየ፣ አብርሃም በገነት ባለ ጠጋው በሲኦል ሆነው የንግግር ልውጥውጥ ካደረገ እና ሁለቱ እንዳይገናኙ ገደል ካለ ለምን ይሆን ክርስቲያን ሚሽነሪዎች በኢሥላም ያለውን የበርዘኽ እሳቤ የሚሳለቁበት? ስንል ሚሽነሪዎች የራሳቸውን መጽሐፍ ጠንቅቀው አለማወቃቸውን እያሳበቀባቸው ነው። የሁሉም ሰው መንፈስ ወደ ፈጣሪ ይመለሳል፦
መክብብ 12፥7 አፈርም(ሥጋም) ወደ ነበረበት ምድር ሳይመለስ፥ መንፈስም ወደ ሰጠው ወደ አምላክ ሳይመለስ ፈጣሪህን አስብ። וְיָשֹׁ֧ב הֶעָפָ֛ר עַל־הָאָ֖רֶץ כְּשֶׁהָיָ֑ה וְהָר֣וּחַ תָּשׁ֔וּב אֶל־הָאֱלֹהִ֖ים אֲשֶׁ֥ר נְתָנָֽהּ׃
ከአፈር የመጣው ሥጋ ወደ አፈር ሲመለስ መንፈስ ደግሞ ወደ አምላክ ይመለሳል። "ሩአሕ" רוּחַ ማለት "መንፈስ" ማለት ሲሆን በቁርኣን መንፈስ በእሳት ሲቀጣ "በእኛ ላይ ከውኃ አፍስሱብን" ማለታቸውን ስትሳለቁ በባይብል መንፈስ በእሳት ሲቀጣ "በዚህ ነበልባል እሣቀያለሁና የጣቱን ጫፍ በውኃ ነክሮ መላሴን እንዲያበርድልኝ አልዓዛርን ስደድልኝ" ማለቱን ስታውቁ ምን ይውጣችሁ ይሆን? "እሳት፣ ውኃ፣ ጣት፣ ምላስ የሩቅ ነገር ምሥጢር ናቸው" ካላችሁ እንግዲያውስ ውኃ እና እሳት የሩቅ ነገር ምሥጢር ናቸው፦
ሉቃስ 16፥24 እርሱም እየጮኸ፦ "አብርሃም አባት ሆይ! ማረኝ፥ በዚህ ነበልባል እሣቀያለሁና የጣቱን ጫፍ በውኃ ነክሮ መላሴን እንዲያበርድልኝ አልዓዛርን ስደድልኝ" አለ።
አምላካችን አሏህ ከእሳት ቅጣት ይጠብቀን! የጀነት ያድርገን! አሚን።
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
የጦም ትሩፋት
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
2፥184 የምታውቁ ብትኾኑ መጾማችሁም ለእናንተ የበለጠ ነው። وَأَن تَصُومُوا خَيْرٌ لَّكُمْ ۖ إِن كُنتُمْ تَعْلَمُونَ
"ዒባደቱል ዐመልያ" عِبَادَة العَمَلِيَّة ማለት "የገቢር አምልኮ" ማለት ነው፥ "ዐመል"عَمَل የሚለው ቃል "ዐሚለ" عَمِلَ ማለትም "ገበረ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "ገቢር" "ድርጊት" ማለት ነው። በድርጊት ከሚፈጸሙ አምልኮ መካከል አንዱ ጦም ነው፥ "ሶውም" صَوْم ማለት ከፈጅር እስከ መግሪብ ከምግብ እና ከመጠጥ ተከልክሎ ተቅዋእ መቀበያ ነው፦
2፥183 እናንተ ያመናችሁ ሆይ! ጦም በእነዚያ ከእናንተ በፊት በነበሩት ላይ እንደ ተጻፈ በእናንተም ላይ ተጻፈ፥ ልትጠነቀቁ ይከጀላልና፡፡ يَٰٓأَيُّهَا ٱلَّذِينَ ءَامَنُوا۟ كُتِبَ عَلَيْكُمُ ٱلصِّيَامُ كَمَا كُتِبَ عَلَى ٱلَّذِينَ مِن قَبْلِكُمْ لَعَلَّكُمْ تَتَّقُونَ
ጦም የምንጦምበትን ምክንያት ደግሞ ለማመልከት "ለዐለኩም ተተቁን" لَعَلَّكُمْ تَتَّقُون ማለትም "ተቅዋእ ታገኙ ዘንድ" ይለናል፥ የጦም ትሩፋቱ ተቅዋእ ለማግኘት ነው። አሏህን እንድናከብረውና እንድናመሰግነው ጦምን ደነገገልን፥ ጦም የምጦመው አሏህን በመጠነ ሰፊ አምልኮ ልናከብረው እና ልናመሰግነው ነው፦
2፥185 ቁጥሮችንም ልትሞሉ አላህንም ቅኑን መንገድ ስለመራችሁ ታከብሩት እና ታመሰግኑት ዘንድ ይህን ደነገግንላችሁ፡፡ وَلِتُكْمِلُوا الْعِدَّةَ وَلِتُكَبِّرُوا اللَّهَ عَلَىٰ مَا هَدَاكُمْ وَلَعَلَّكُمْ تَشْكُرُونَ
“ታከብሩት እና “ታመሰግኑት” ዘንድ የሚለው ኃይለ-ቃል ይሰመርበት! "ተክቢር" تَكْبِير በአምልኮ "አሏሁ አክበር" اَللّٰهُ أَكْبَرْ ማለት ሲሆን “ሊቱከብሩ” َلِتُكَبِّرُوا ማለት ይህንኑ ያሳያል። "ተሽኩር" تَشْكُر በአምልኮ አሏህን የምናመሰግንበት ነው፥ አላህ “ሻኪር” شَاكِر ማለትም “ተመስጋኝ” ሲሆን ባሮቹ ደግሞ “ሸኩር” شَكُور ማለት እርሱን “አመስጋኝ” ናቸው፥ "ተሽኩሩን" تَشْكُرُون ማለቱ ይህንን ያሳያል። ጦም በኢማን እና በኢሕቲሣብ ከተጦመ ያለፈውን ኃጢአት ይቅር ያስብላል፦
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 32, ሐዲስ 1
አቢ ሁረይራህ"ረ.ዐ." እንደተረከው፦ "ነቢዩም"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "ማንም ረመዷንን በኢማን እና በኢሕቲሣብ የጦመ ያለፈውን ኃጢአቱ ይቅር ይባልለታል"። عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ ـ رضى الله عنه ـ عَنِ النَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم قَالَ " مَنْ صَامَ رَمَضَانَ إِيمَانًا وَاحْتِسَابًا غُفِرَ لَهُ مَا تَقَدَّمَ مِنْ ذَنْبِهِ
"ኢሕቲሣብ" احْتِسَاب ማለት "ከአሏህ ዘንድ ትሩፋት አገኛለው" ብሎ መነየት ነው፥ ጦም ከምግብ እና ከመጠጥ መከልከል ብቻ ሳይሆን ውድቅ ንግግር እና ከመጥፎ ድርጊትም መቆጠብ ነው፦
ሡነን ኢብኑ ማጃህ መጽሐፍ 7, ሐዲስ 52
አቢ ሁረይራህ እንደተረከው፦ "የአሏህ መልእክተኛም"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "ማንም መጥፎ እና ዐላዋቂ ንግግርን ያልተወ እና በዚህ የሚሠራ ምግቡን እና መጠጡን መተው አሏህ አይፈልገውም"። عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ، قَالَ: قَالَ رَسُولُ اللَّهِ ـ صلى الله عليه وسلم ـ " مَنْ لَمْ يَدَعْ قَوْلَ الزُّورِ، وَالْجَهْلَ، وَالْعَمَلَ بِهِ، فَلاَ حَاجَةَ لِلَّهِ فِي أَنْ يَدَعَ طَعَامَهُ وَشَرَابَهُ " .
ጦም በትንሳኤ ቀን ለአሏህ ባሪያ ከጀሃነም እሳት መጠለያ እና ሸፋዓህ ነው፦
ሡነን አን-ነሣኢ መጽሐፍ 22, ሐዲስ 145
ዓኢሻህ እንደተረከችው፦ "ነቢዩም"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "ጦም ከጀሃነም እሳት መጠለያ ነው"። عَنْ عَائِشَةَ، عَنِ النَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم قَالَ " الصِّيَامُ جُنَّةٌ مِنَ النَّارِ
ሚሽካቱል መሷቢሕ መጽሐፍ 7, ሐዲስ 7
ዐብደሏህ ኢብኑ ዐምር እንደተረከው፦ “የአሏህ መልእክተኛ”ﷺ” እንዲህ አሉ፦ “ጦም እና ቁርኣን በትንሳኤ ቀን ለአሏህ ባሪያ ያማልዳሉ። ጦምም፦ “ጌታ ሆይ! በመዓልት ምግብ እና ፍላጎትን ለከለከልኩት ላማልደው” ይላል፥ ቁርኣንም፦ “ጌታ ሆይ! በሌሊት እንቅልፍ ለከለከልኩት ላማልደው” ይላል፥ እናም ያማልዳሉ”። عَنْ عَبْدِ اللَّهِ بْنِ عَمْرٍو أَنَّ رَسُولَ اللَّهِ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ قَالَ الصِّيَامُ وَالْقُرْآنُ يَشْفَعَانِ لِلْعَبْدِ يَوْمَ الْقِيَامَةِ يَقُولُ الصِّيَامُ أَيْ رَبِّ مَنَعْتُهُ الطَّعَامَ وَالشَّهَوَاتِ بِالنَّهَارِ فَشَفِّعْنِي فِيهِ وَيَقُولُ الْقُرْآنُ مَنَعْتُهُ النَّوْمَ بِاللَّيْلِ فَشَفِّعْنِي فِيهِ قَالَ فَيُشَفَّعَانِ
“
በእርግጥ የጦም ትሩፋቱ ብዙ ነው። የጦም ምንዳ ያለ ግምት ነው፥ የጦምን አጅር አሏህ የትንሳኤ ቀን ይከፍለናል፦
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 77, ሐዲስ 142
አቢ ሁረይራህ"ረ.ዐ." እንደተረከው፦ ነቢዩም"ﷺ" አሏህ እንዲህ አለ አሉ፦ "የአደም ልጅ ሥራው ለራሱ ነው፥ ጦም ሲቀር። ጦም ለእኔ ነው፥ ምንዳውንም እኔ እከፍለዋለው። ከጦመኛ አፍ የሚወጣ ጠረን አሏህ ዘንድ ከሚስክ ጠረን የተሻለ ነው"። عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ ـ رضى الله عنه ـ عَنِ النَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم قَالَ " كُلُّ عَمَلِ ابْنِ آدَمَ لَهُ، إِلاَّ الصَّوْمَ فَإِنَّهُ لِي، وَأَنَا أَجْزِي بِهِ، وَلَخَلُوفُ فَمِ الصَّائِمِ أَطْيَبُ عِنْدَ اللَّهِ مِنْ رِيحِ الْمِسْكِ ".
"ሚሥክ" مِسْك ማለት መዓዛው የሚያውድ መልካም ጠረን ያለው ሽታ ነው፥ ከጦመኛ አፍ የሚወጣ ክርፋት ሰው ዘንድ ደስ የማይል ቢሆንም ለአሏህ ተብሎ የተደረገ አምልኮ እስከሆነ ድረስ እርሱ ዘንድ ያለው ደረጃ ከሚሥክ መዓዛ ይበልጣል። አምላካችን አሏህ በጦማቸው ከሚጠቀሙ ባሮቹ ያድርገን! አሚን።
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
2፥184 የምታውቁ ብትኾኑ መጾማችሁም ለእናንተ የበለጠ ነው። وَأَن تَصُومُوا خَيْرٌ لَّكُمْ ۖ إِن كُنتُمْ تَعْلَمُونَ
"ዒባደቱል ዐመልያ" عِبَادَة العَمَلِيَّة ማለት "የገቢር አምልኮ" ማለት ነው፥ "ዐመል"عَمَل የሚለው ቃል "ዐሚለ" عَمِلَ ማለትም "ገበረ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "ገቢር" "ድርጊት" ማለት ነው። በድርጊት ከሚፈጸሙ አምልኮ መካከል አንዱ ጦም ነው፥ "ሶውም" صَوْم ማለት ከፈጅር እስከ መግሪብ ከምግብ እና ከመጠጥ ተከልክሎ ተቅዋእ መቀበያ ነው፦
2፥183 እናንተ ያመናችሁ ሆይ! ጦም በእነዚያ ከእናንተ በፊት በነበሩት ላይ እንደ ተጻፈ በእናንተም ላይ ተጻፈ፥ ልትጠነቀቁ ይከጀላልና፡፡ يَٰٓأَيُّهَا ٱلَّذِينَ ءَامَنُوا۟ كُتِبَ عَلَيْكُمُ ٱلصِّيَامُ كَمَا كُتِبَ عَلَى ٱلَّذِينَ مِن قَبْلِكُمْ لَعَلَّكُمْ تَتَّقُونَ
ጦም የምንጦምበትን ምክንያት ደግሞ ለማመልከት "ለዐለኩም ተተቁን" لَعَلَّكُمْ تَتَّقُون ማለትም "ተቅዋእ ታገኙ ዘንድ" ይለናል፥ የጦም ትሩፋቱ ተቅዋእ ለማግኘት ነው። አሏህን እንድናከብረውና እንድናመሰግነው ጦምን ደነገገልን፥ ጦም የምጦመው አሏህን በመጠነ ሰፊ አምልኮ ልናከብረው እና ልናመሰግነው ነው፦
2፥185 ቁጥሮችንም ልትሞሉ አላህንም ቅኑን መንገድ ስለመራችሁ ታከብሩት እና ታመሰግኑት ዘንድ ይህን ደነገግንላችሁ፡፡ وَلِتُكْمِلُوا الْعِدَّةَ وَلِتُكَبِّرُوا اللَّهَ عَلَىٰ مَا هَدَاكُمْ وَلَعَلَّكُمْ تَشْكُرُونَ
“ታከብሩት እና “ታመሰግኑት” ዘንድ የሚለው ኃይለ-ቃል ይሰመርበት! "ተክቢር" تَكْبِير በአምልኮ "አሏሁ አክበር" اَللّٰهُ أَكْبَرْ ማለት ሲሆን “ሊቱከብሩ” َلِتُكَبِّرُوا ማለት ይህንኑ ያሳያል። "ተሽኩር" تَشْكُر በአምልኮ አሏህን የምናመሰግንበት ነው፥ አላህ “ሻኪር” شَاكِر ማለትም “ተመስጋኝ” ሲሆን ባሮቹ ደግሞ “ሸኩር” شَكُور ማለት እርሱን “አመስጋኝ” ናቸው፥ "ተሽኩሩን" تَشْكُرُون ማለቱ ይህንን ያሳያል። ጦም በኢማን እና በኢሕቲሣብ ከተጦመ ያለፈውን ኃጢአት ይቅር ያስብላል፦
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 32, ሐዲስ 1
አቢ ሁረይራህ"ረ.ዐ." እንደተረከው፦ "ነቢዩም"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "ማንም ረመዷንን በኢማን እና በኢሕቲሣብ የጦመ ያለፈውን ኃጢአቱ ይቅር ይባልለታል"። عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ ـ رضى الله عنه ـ عَنِ النَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم قَالَ " مَنْ صَامَ رَمَضَانَ إِيمَانًا وَاحْتِسَابًا غُفِرَ لَهُ مَا تَقَدَّمَ مِنْ ذَنْبِهِ
"ኢሕቲሣብ" احْتِسَاب ማለት "ከአሏህ ዘንድ ትሩፋት አገኛለው" ብሎ መነየት ነው፥ ጦም ከምግብ እና ከመጠጥ መከልከል ብቻ ሳይሆን ውድቅ ንግግር እና ከመጥፎ ድርጊትም መቆጠብ ነው፦
ሡነን ኢብኑ ማጃህ መጽሐፍ 7, ሐዲስ 52
አቢ ሁረይራህ እንደተረከው፦ "የአሏህ መልእክተኛም"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "ማንም መጥፎ እና ዐላዋቂ ንግግርን ያልተወ እና በዚህ የሚሠራ ምግቡን እና መጠጡን መተው አሏህ አይፈልገውም"። عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ، قَالَ: قَالَ رَسُولُ اللَّهِ ـ صلى الله عليه وسلم ـ " مَنْ لَمْ يَدَعْ قَوْلَ الزُّورِ، وَالْجَهْلَ، وَالْعَمَلَ بِهِ، فَلاَ حَاجَةَ لِلَّهِ فِي أَنْ يَدَعَ طَعَامَهُ وَشَرَابَهُ " .
ጦም በትንሳኤ ቀን ለአሏህ ባሪያ ከጀሃነም እሳት መጠለያ እና ሸፋዓህ ነው፦
ሡነን አን-ነሣኢ መጽሐፍ 22, ሐዲስ 145
ዓኢሻህ እንደተረከችው፦ "ነቢዩም"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "ጦም ከጀሃነም እሳት መጠለያ ነው"። عَنْ عَائِشَةَ، عَنِ النَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم قَالَ " الصِّيَامُ جُنَّةٌ مِنَ النَّارِ
ሚሽካቱል መሷቢሕ መጽሐፍ 7, ሐዲስ 7
ዐብደሏህ ኢብኑ ዐምር እንደተረከው፦ “የአሏህ መልእክተኛ”ﷺ” እንዲህ አሉ፦ “ጦም እና ቁርኣን በትንሳኤ ቀን ለአሏህ ባሪያ ያማልዳሉ። ጦምም፦ “ጌታ ሆይ! በመዓልት ምግብ እና ፍላጎትን ለከለከልኩት ላማልደው” ይላል፥ ቁርኣንም፦ “ጌታ ሆይ! በሌሊት እንቅልፍ ለከለከልኩት ላማልደው” ይላል፥ እናም ያማልዳሉ”። عَنْ عَبْدِ اللَّهِ بْنِ عَمْرٍو أَنَّ رَسُولَ اللَّهِ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ قَالَ الصِّيَامُ وَالْقُرْآنُ يَشْفَعَانِ لِلْعَبْدِ يَوْمَ الْقِيَامَةِ يَقُولُ الصِّيَامُ أَيْ رَبِّ مَنَعْتُهُ الطَّعَامَ وَالشَّهَوَاتِ بِالنَّهَارِ فَشَفِّعْنِي فِيهِ وَيَقُولُ الْقُرْآنُ مَنَعْتُهُ النَّوْمَ بِاللَّيْلِ فَشَفِّعْنِي فِيهِ قَالَ فَيُشَفَّعَانِ
“
በእርግጥ የጦም ትሩፋቱ ብዙ ነው። የጦም ምንዳ ያለ ግምት ነው፥ የጦምን አጅር አሏህ የትንሳኤ ቀን ይከፍለናል፦
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 77, ሐዲስ 142
አቢ ሁረይራህ"ረ.ዐ." እንደተረከው፦ ነቢዩም"ﷺ" አሏህ እንዲህ አለ አሉ፦ "የአደም ልጅ ሥራው ለራሱ ነው፥ ጦም ሲቀር። ጦም ለእኔ ነው፥ ምንዳውንም እኔ እከፍለዋለው። ከጦመኛ አፍ የሚወጣ ጠረን አሏህ ዘንድ ከሚስክ ጠረን የተሻለ ነው"። عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ ـ رضى الله عنه ـ عَنِ النَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم قَالَ " كُلُّ عَمَلِ ابْنِ آدَمَ لَهُ، إِلاَّ الصَّوْمَ فَإِنَّهُ لِي، وَأَنَا أَجْزِي بِهِ، وَلَخَلُوفُ فَمِ الصَّائِمِ أَطْيَبُ عِنْدَ اللَّهِ مِنْ رِيحِ الْمِسْكِ ".
"ሚሥክ" مِسْك ማለት መዓዛው የሚያውድ መልካም ጠረን ያለው ሽታ ነው፥ ከጦመኛ አፍ የሚወጣ ክርፋት ሰው ዘንድ ደስ የማይል ቢሆንም ለአሏህ ተብሎ የተደረገ አምልኮ እስከሆነ ድረስ እርሱ ዘንድ ያለው ደረጃ ከሚሥክ መዓዛ ይበልጣል። አምላካችን አሏህ በጦማቸው ከሚጠቀሙ ባሮቹ ያድርገን! አሚን።
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
ቀልብ
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
37፥84 ወደ ጌታው "በ-ንጹሕ ልብ” በመጣ ጊዜ የኾነውን አስታውስ፡፡፡ إِذْ جَاءَ رَبَّهُ بِقَلْبٍ سَلِيمٍ
"ቀልብ" قَلْب የሚለው ቃል "ቀለበ" قَلَبَ ማለትም "ለበወ" "ኀለየ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "ልብ" "ኃልዮ" ማለት ነው፥ "ልብ" የሚለው የግዕዝ ቃል "ለበወ" ማለትም "አጤነ" "አስተዋለ" "አመዛዘነ" "ዐወቀ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "ማጤኛ" "ማስተዋያ" "ማመዛዘኛ" "ማወቂያ" የሚል ፍቺ አለው። "ፉአድ" فُؤَاد ስሜትን"emotion" የያዘ የውስጥ ክፍል ሲሆን "ዐቅል" عَقْل ደግሞ አመክንዮን"intellect" የያዘ የውስጥ ክፍል ነው፥ ፉኣድን እና ዐቅልን አመዛዝኖ የሚይዝ ውሳጣዊ ክፍል "ቀልብ" قَلْب ነው። "ቁሉብ" قُلُوب ደግሞ የቀልብ ብዙ ቁጥር ሲሆን "ልቦች" ማለት ነው፦
15፥51 አላህም "በልቦቻችሁ" ውስጥ ያለውን ሁሉ ያውቃል፡፡ አላህም ዐዋቂ ታጋሽ ነው፡፡ وَاللَّهُ يَعْلَمُ مَا فِي قُلُوبِكُمْ ۚ وَكَانَ اللَّهُ عَلِيمًا حَلِيمًا
"ነፍሥ" نَفْس ማለት "እራስነት"own self" ማለት ሲሆን አንፉሥ" أَنْفُس የነፍሥ ብዙ ቁጥር ነው፥ ነፍሥ በሰው ውስጥ ያለውን ልብ ለማመልከት ይመጣል፦
2፥284 በ"ነፍሶቻችሁ" ውስጥ ያለውን ብትገልጹ ወይም ብትደብቁት አላህ በእርሱ ይቆጣጠራችኋል"፡፡ وَإِن تُبْدُوا مَا فِي أَنفُسِكُمْ أَوْ تُخْفُوهُ يُحَاسِبْكُم بِهِ اللَّهُ ۖ
"ቁሉቢኩም" قُلُوبِكُمْ የሚለው "አንፉሢኩም" أَنفُسِكُمْ በሚል ተለዋዋጭ ከመጣ ዘንዳ ቀልብ ወይም ነፍስ ውስጥ ያለው ሀብት እውነተኛ ሀብት ሲሆን ይህም ውሳጣዊ ሀብት ነው፦
ሶሒሕ ኢብኑ ሒባን መጽሐፍ 1 ሐዲስ 3055
አቢ ሁረይራህ እንደተረከው፦ "የአሏህ መልእክተኛም"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "ሀብት በውጪ አይኖርም፥ እውነተኛ ሀብት የነፍሥ ሀብት ብቻ ነው"። عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ عَنْ رَسُولِ اللهِ صَلى الله عَلَيه وسَلم أَنَّهُ قَالَ لَيْسَ الْغِنَى عَنْ ظَهْرٍ إِنَّمَا الْغِنَى غِنَى النَّفْسِ
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 81, ሐዲስ 35
አቢ ሁረይራህ”ረ.ዐ” እንደተረከው ነቢዩም”ﷺ” አሉ፦ "ሀብት ማለት መጠነ ሰፊ ንብረት መያዝ አይደለም፥ ነገር ግን ሀብት ማለት የነፍሥ ሀብት ነው። عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ، عَنِ النَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم قَالَ “ لَيْسَ الْغِنَى عَنْ كَثْرَةِ الْعَرَضِ، وَلَكِنَّ الْغِنَى غِنَى النَّفْسِ ”.
የውስጥ ሀብት እምነት፣ እሳቤ፣ አሳብ፣ የአስተሳሰብ ቅኝነት፣ ጥልቅ አመለካከት፣ ዕውቀት ነው፥ የውስጥ ድህነት ክህደት፣ ጭፍንነት፣ ጸለምተኝነት፣ ድንቁርና፣ መሃይምነት ነው። እውነተኛ ሀብትም ሆነ ድህነት በልብ ውስጥ ያለ ነው፦
አል-ሙዕጀመል ከቢር መጽሐፍ 4, ሐዲስ 154
አቢ ዘር እንደተረከው፦ "የአሏህ መልእክተኛም"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "አቢ ዘር ሆይ! "የተትረፈረፈ ገንዘብ ሀብት ነው" ትላለህን? እኔም፦ "አዎ" አልኩኝ፥ እርሳቸውም፦ "የገንዘብ አለመኖር ድህነት ነው" ትላለህን? እኔም፦ "አዎ" አልኩኝ፥ እርሳቸውም ይህንን ሦስት ጊዜ ደጋገሙት። ከዚያም "የአሏህ መልእክተኛም"ﷺ"፦ "ሀብት በልብ ውስጥ ነው፥ ድህነትም በልብ ውስጥ ነው" አሉ"። عن أبي ذر قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ يَا أَبَا ذَرٍّ تَقُولُ كَثْرَةُ الْمَالِ الْغِنَى قُلْتُ نَعَمْ قَالَ تَقُولُ قِلَّةُ الْمَالِ الْفَقْرُ قُلْتُ نَعَمْ قَالَ ذَلِكَ ثَلاثًا ثُمَّ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ الْغِنَى فِي الْقَلْبِ وَالْفَقْرُ فِي الْقَلْبِ.
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
37፥84 ወደ ጌታው "በ-ንጹሕ ልብ” በመጣ ጊዜ የኾነውን አስታውስ፡፡፡ إِذْ جَاءَ رَبَّهُ بِقَلْبٍ سَلِيمٍ
"ቀልብ" قَلْب የሚለው ቃል "ቀለበ" قَلَبَ ማለትም "ለበወ" "ኀለየ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "ልብ" "ኃልዮ" ማለት ነው፥ "ልብ" የሚለው የግዕዝ ቃል "ለበወ" ማለትም "አጤነ" "አስተዋለ" "አመዛዘነ" "ዐወቀ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "ማጤኛ" "ማስተዋያ" "ማመዛዘኛ" "ማወቂያ" የሚል ፍቺ አለው። "ፉአድ" فُؤَاد ስሜትን"emotion" የያዘ የውስጥ ክፍል ሲሆን "ዐቅል" عَقْل ደግሞ አመክንዮን"intellect" የያዘ የውስጥ ክፍል ነው፥ ፉኣድን እና ዐቅልን አመዛዝኖ የሚይዝ ውሳጣዊ ክፍል "ቀልብ" قَلْب ነው። "ቁሉብ" قُلُوب ደግሞ የቀልብ ብዙ ቁጥር ሲሆን "ልቦች" ማለት ነው፦
15፥51 አላህም "በልቦቻችሁ" ውስጥ ያለውን ሁሉ ያውቃል፡፡ አላህም ዐዋቂ ታጋሽ ነው፡፡ وَاللَّهُ يَعْلَمُ مَا فِي قُلُوبِكُمْ ۚ وَكَانَ اللَّهُ عَلِيمًا حَلِيمًا
"ነፍሥ" نَفْس ማለት "እራስነት"own self" ማለት ሲሆን አንፉሥ" أَنْفُس የነፍሥ ብዙ ቁጥር ነው፥ ነፍሥ በሰው ውስጥ ያለውን ልብ ለማመልከት ይመጣል፦
2፥284 በ"ነፍሶቻችሁ" ውስጥ ያለውን ብትገልጹ ወይም ብትደብቁት አላህ በእርሱ ይቆጣጠራችኋል"፡፡ وَإِن تُبْدُوا مَا فِي أَنفُسِكُمْ أَوْ تُخْفُوهُ يُحَاسِبْكُم بِهِ اللَّهُ ۖ
"ቁሉቢኩም" قُلُوبِكُمْ የሚለው "አንፉሢኩም" أَنفُسِكُمْ በሚል ተለዋዋጭ ከመጣ ዘንዳ ቀልብ ወይም ነፍስ ውስጥ ያለው ሀብት እውነተኛ ሀብት ሲሆን ይህም ውሳጣዊ ሀብት ነው፦
ሶሒሕ ኢብኑ ሒባን መጽሐፍ 1 ሐዲስ 3055
አቢ ሁረይራህ እንደተረከው፦ "የአሏህ መልእክተኛም"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "ሀብት በውጪ አይኖርም፥ እውነተኛ ሀብት የነፍሥ ሀብት ብቻ ነው"። عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ عَنْ رَسُولِ اللهِ صَلى الله عَلَيه وسَلم أَنَّهُ قَالَ لَيْسَ الْغِنَى عَنْ ظَهْرٍ إِنَّمَا الْغِنَى غِنَى النَّفْسِ
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 81, ሐዲስ 35
አቢ ሁረይራህ”ረ.ዐ” እንደተረከው ነቢዩም”ﷺ” አሉ፦ "ሀብት ማለት መጠነ ሰፊ ንብረት መያዝ አይደለም፥ ነገር ግን ሀብት ማለት የነፍሥ ሀብት ነው። عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ، عَنِ النَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم قَالَ “ لَيْسَ الْغِنَى عَنْ كَثْرَةِ الْعَرَضِ، وَلَكِنَّ الْغِنَى غِنَى النَّفْسِ ”.
የውስጥ ሀብት እምነት፣ እሳቤ፣ አሳብ፣ የአስተሳሰብ ቅኝነት፣ ጥልቅ አመለካከት፣ ዕውቀት ነው፥ የውስጥ ድህነት ክህደት፣ ጭፍንነት፣ ጸለምተኝነት፣ ድንቁርና፣ መሃይምነት ነው። እውነተኛ ሀብትም ሆነ ድህነት በልብ ውስጥ ያለ ነው፦
አል-ሙዕጀመል ከቢር መጽሐፍ 4, ሐዲስ 154
አቢ ዘር እንደተረከው፦ "የአሏህ መልእክተኛም"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "አቢ ዘር ሆይ! "የተትረፈረፈ ገንዘብ ሀብት ነው" ትላለህን? እኔም፦ "አዎ" አልኩኝ፥ እርሳቸውም፦ "የገንዘብ አለመኖር ድህነት ነው" ትላለህን? እኔም፦ "አዎ" አልኩኝ፥ እርሳቸውም ይህንን ሦስት ጊዜ ደጋገሙት። ከዚያም "የአሏህ መልእክተኛም"ﷺ"፦ "ሀብት በልብ ውስጥ ነው፥ ድህነትም በልብ ውስጥ ነው" አሉ"። عن أبي ذر قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ يَا أَبَا ذَرٍّ تَقُولُ كَثْرَةُ الْمَالِ الْغِنَى قُلْتُ نَعَمْ قَالَ تَقُولُ قِلَّةُ الْمَالِ الْفَقْرُ قُلْتُ نَعَمْ قَالَ ذَلِكَ ثَلاثًا ثُمَّ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ الْغِنَى فِي الْقَلْبِ وَالْفَقْرُ فِي الْقَلْبِ.
መጥፎ ሥራ የሚያሠራን ከልብ የተቀመጠው እውነተኛ ድህነት ነው፥ መልካም ሥራ የሚያሠራን ከልብ የተቀመጠው እውነኛው ሀብት ነው። አምላካችን አሏህ የሚመለከተው ልባችንን እና ሥራችንን እንጂ ቅርጻችንን እና ገንዘባችንን አይደለም፦
ኢማም ሙሥሊም መጽሐፍ 45, ሐዲስ 42
አቢ ሁረይራህ እንደተረከው፦ "የአሏህ መልእክተኛ"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "አሏህ ወደ ቅርጻችሁ እና ገንዘባችሁ አይመለከትም፥ ነገር ግን ወደ ልባችሁ እና ሥራችሁ ይመለከታል"፡፡ عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ، قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم " إِنَّ اللَّهَ لاَ يَنْظُرُ إِلَى صُوَرِكُمْ وَأَمْوَالِكُمْ وَلَكِنْ يَنْظُرُ إِلَى قُلُوبِكُمْ وَأَعْمَالِكُمْ "
ልብ የምንነይትበት የኒያህ መቀመጫ ነው፥ ሥራ የሚለካው በኒያህ ስለሆነ ሥራችን የልባችን ውጤት ነው። ጽድቅ መልካም ሥነ ምግባር"ethics" ሲሆን በግልጠተ መለኮት በኩል ከሥነ መለኮት የሚመጣ ነው፥ በተቃራኒው ኃጢአት በልብህ ውስጥ የሚሸረብ ነው፦
ኢማም ሙሥሊም መጽሐፍ, 45, ሐዲስ 16
አን ነዋሥ ኢብኑ ሠዕማል አል አንሷሪይ እንደተረከው፦ "እኔም "የአሏህ መልእክተኛ"ﷺ" ስለ ጽድቅ እና ኃጢአት ጠየኳቸው፥ እርሳቸውም፦ "ጽድቅ መልካም ሥነ ምግባር ነው፥ ኃጢአት በልብህ ውስጥ የሚሸረብ ነው" አሉ"። عَنِ النَّوَّاسِ بْنِ سَمْعَانَ الأَنْصَارِيِّ، قَالَ سَأَلْتُ رَسُولَ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم عَنِ الْبِرِّ وَالإِثْمِ فَقَالَ " الْبِرُّ حُسْنُ الْخُلُقِ وَالإِثْمُ مَا حَاكَ فِي صَدْرِكَ " .
ኢማም ሙሥሊም መጽሐፍ, 45, ሐዲስ 17
አን ነዋሥ ኢብኑ ሠዕማል አል አንሷሪይ እንደተረከው፦ "የአሏህ መልእክተኛም"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "ጽድቅ መልካም ሥነ ምግባር ነው፥ ኃጢአት በነፍስ ውስጥ የሚሸረብ ነው"። عَنِ النَّوَّاسِ بْنِ سَمْعَانَ الأَنْصَارِيِّ، قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم " الْبِرُّ حُسْنُ الْخُلُقِ وَالإِثْمُ مَا حَاكَ فِي نَفْسِكَ "
"ልብ" እና "ነፍስ" በአንድ ዐውድ ላይ ተለዋዋጭ ቃል ሆኖ መምጣቱ በራሱ ነፍስ ውሳጣዊ ልብን ያመለክታል፥ ልብ ይህን ያክል በሰው ሕይወት ላይ አውንታዊ ሆነ አሉታዊ ተጽዕኖ አለው። ጀነት ወደ አሏህ በንጹሕ ልብ ለመጣ ትቀረባለች፥ ለምሳሌ፦ ኢብራሂም ወደ ጌታው በንጹሕ ልብ የመጣ ሰው ነው፦
50፥33 አልረሕማንን በሩቁ ኾኖ ለፈራ እና "በ-ንጹሕ ልብ" ለመጣ ትቀረባለች፡፡ مَّنْ خَشِيَ الرَّحْمَـٰنَ بِالْغَيْبِ وَجَاءَ بِقَلْبٍ مُّنِيبٍ
37፥84 ወደ ጌታው "በ-ንጹሕ ልብ” በመጣ ጊዜ የኾነውን አስታውስ፡፡፡ إِذْ جَاءَ رَبَّهُ بِقَلْبٍ سَلِيمٍ
26፥89 ወደ አላህ "በ-ንጹሕ ልብ" የመጣ ሰው ቢኾን እንጂ፡፡ إِلَّا مَنْ أَتَى اللَّهَ بِقَلْبٍ سَلِيمٍ
እነዚህ አናቅጽ ላይ "ንጹሕ" ተብሎ የተቀመጠው ቃል "ሠሊም" سَلِيم ነው፥ አንድ በኢሥላም ልቡን ሢያሠልም ልቡ ውስጥ "ሠላም" سَلَام ስላለ ልቡ ሠሊም ስትሆን እርሱ ደግሞ "ሣሊም" سَالِم ይሆናል፦
ኢማም አሕመድ መጽሐፍ 1, ሐዲስ 17027
ዐምር ኢብኑ ዐባሣህ እንደተረከው፦ "አንድ ሰው የአሏህ መልእክተኛም"ﷺ" ሆይ! ኢሥላም ምንድን ነው? ብሎ ጠየቀ፥ እርሳቸውም"ﷺ"፦ "ልብህን ለአሏህ ዐዘ ወጀል ማሥለም ነው" አሉት"። عَنْ عَمْرِو بْنِ عَبَسَةَ قَالَ قَالَ رَجُلٌ يَا رَسُولَ اللَّهِ مَا الْإِسْلَامُ قَالَ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ أَنْ يُسْلِمَ قَلْبُكَ لِلَّهِ عَزَّ وَجَلَّ
አንድ ሰው ልቡን ለአሏህ ካሠለመ ጀነት ይገባል፥ ልቡን ለአሏህ ያሠለመ ሰው ከጀሀነም ይድናል፦
አል አደቡል ሙፍረድ መጽሐፍ 1, ሐዲስ 260
አቢ ሁረይራህ እንደተረከው፦ "የአሏህ መልእክተኛ"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "ነፍሴ በእጁ በሆነው እምላለው፥ እስካልሠለማችሁ ድረስ ጀነት አትገቡም"። عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ، عَنِ النَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم قَالَ: وَالَّذِي نَفْسِي بِيَدِهِ، لاَ تَدْخُلُوا الْجَنَّةَ حَتَّى تُسْلِمُوا
ኢማም ሙሥሊም መጽሐፍ 12, ሐዲስ 163
ዐምር ኢብኑ አል ዓስ እንደተረከው፦ "የአሏህ መልእክተኛ"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "የሠለመ ዳነ"። عَنْ عَمْرِو بْنِ الْعَاصِ أَنَّ رَسُولَ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم قَالَ " قَدْ أَفْلَحَ مَنْ أَسْلَمَ " .
አምላካችን አሏህ በልባችን ውስጥ ያለውን እውነተኛ ሀብት እንድንጠቀም ይርዳን! በሠሊም ቀልብ ወደ እርሱ የምንመጣ ያድርገን! አሚን።
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
ኢማም ሙሥሊም መጽሐፍ 45, ሐዲስ 42
አቢ ሁረይራህ እንደተረከው፦ "የአሏህ መልእክተኛ"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "አሏህ ወደ ቅርጻችሁ እና ገንዘባችሁ አይመለከትም፥ ነገር ግን ወደ ልባችሁ እና ሥራችሁ ይመለከታል"፡፡ عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ، قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم " إِنَّ اللَّهَ لاَ يَنْظُرُ إِلَى صُوَرِكُمْ وَأَمْوَالِكُمْ وَلَكِنْ يَنْظُرُ إِلَى قُلُوبِكُمْ وَأَعْمَالِكُمْ "
ልብ የምንነይትበት የኒያህ መቀመጫ ነው፥ ሥራ የሚለካው በኒያህ ስለሆነ ሥራችን የልባችን ውጤት ነው። ጽድቅ መልካም ሥነ ምግባር"ethics" ሲሆን በግልጠተ መለኮት በኩል ከሥነ መለኮት የሚመጣ ነው፥ በተቃራኒው ኃጢአት በልብህ ውስጥ የሚሸረብ ነው፦
ኢማም ሙሥሊም መጽሐፍ, 45, ሐዲስ 16
አን ነዋሥ ኢብኑ ሠዕማል አል አንሷሪይ እንደተረከው፦ "እኔም "የአሏህ መልእክተኛ"ﷺ" ስለ ጽድቅ እና ኃጢአት ጠየኳቸው፥ እርሳቸውም፦ "ጽድቅ መልካም ሥነ ምግባር ነው፥ ኃጢአት በልብህ ውስጥ የሚሸረብ ነው" አሉ"። عَنِ النَّوَّاسِ بْنِ سَمْعَانَ الأَنْصَارِيِّ، قَالَ سَأَلْتُ رَسُولَ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم عَنِ الْبِرِّ وَالإِثْمِ فَقَالَ " الْبِرُّ حُسْنُ الْخُلُقِ وَالإِثْمُ مَا حَاكَ فِي صَدْرِكَ " .
ኢማም ሙሥሊም መጽሐፍ, 45, ሐዲስ 17
አን ነዋሥ ኢብኑ ሠዕማል አል አንሷሪይ እንደተረከው፦ "የአሏህ መልእክተኛም"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "ጽድቅ መልካም ሥነ ምግባር ነው፥ ኃጢአት በነፍስ ውስጥ የሚሸረብ ነው"። عَنِ النَّوَّاسِ بْنِ سَمْعَانَ الأَنْصَارِيِّ، قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم " الْبِرُّ حُسْنُ الْخُلُقِ وَالإِثْمُ مَا حَاكَ فِي نَفْسِكَ "
"ልብ" እና "ነፍስ" በአንድ ዐውድ ላይ ተለዋዋጭ ቃል ሆኖ መምጣቱ በራሱ ነፍስ ውሳጣዊ ልብን ያመለክታል፥ ልብ ይህን ያክል በሰው ሕይወት ላይ አውንታዊ ሆነ አሉታዊ ተጽዕኖ አለው። ጀነት ወደ አሏህ በንጹሕ ልብ ለመጣ ትቀረባለች፥ ለምሳሌ፦ ኢብራሂም ወደ ጌታው በንጹሕ ልብ የመጣ ሰው ነው፦
50፥33 አልረሕማንን በሩቁ ኾኖ ለፈራ እና "በ-ንጹሕ ልብ" ለመጣ ትቀረባለች፡፡ مَّنْ خَشِيَ الرَّحْمَـٰنَ بِالْغَيْبِ وَجَاءَ بِقَلْبٍ مُّنِيبٍ
37፥84 ወደ ጌታው "በ-ንጹሕ ልብ” በመጣ ጊዜ የኾነውን አስታውስ፡፡፡ إِذْ جَاءَ رَبَّهُ بِقَلْبٍ سَلِيمٍ
26፥89 ወደ አላህ "በ-ንጹሕ ልብ" የመጣ ሰው ቢኾን እንጂ፡፡ إِلَّا مَنْ أَتَى اللَّهَ بِقَلْبٍ سَلِيمٍ
እነዚህ አናቅጽ ላይ "ንጹሕ" ተብሎ የተቀመጠው ቃል "ሠሊም" سَلِيم ነው፥ አንድ በኢሥላም ልቡን ሢያሠልም ልቡ ውስጥ "ሠላም" سَلَام ስላለ ልቡ ሠሊም ስትሆን እርሱ ደግሞ "ሣሊም" سَالِم ይሆናል፦
ኢማም አሕመድ መጽሐፍ 1, ሐዲስ 17027
ዐምር ኢብኑ ዐባሣህ እንደተረከው፦ "አንድ ሰው የአሏህ መልእክተኛም"ﷺ" ሆይ! ኢሥላም ምንድን ነው? ብሎ ጠየቀ፥ እርሳቸውም"ﷺ"፦ "ልብህን ለአሏህ ዐዘ ወጀል ማሥለም ነው" አሉት"። عَنْ عَمْرِو بْنِ عَبَسَةَ قَالَ قَالَ رَجُلٌ يَا رَسُولَ اللَّهِ مَا الْإِسْلَامُ قَالَ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ أَنْ يُسْلِمَ قَلْبُكَ لِلَّهِ عَزَّ وَجَلَّ
አንድ ሰው ልቡን ለአሏህ ካሠለመ ጀነት ይገባል፥ ልቡን ለአሏህ ያሠለመ ሰው ከጀሀነም ይድናል፦
አል አደቡል ሙፍረድ መጽሐፍ 1, ሐዲስ 260
አቢ ሁረይራህ እንደተረከው፦ "የአሏህ መልእክተኛ"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "ነፍሴ በእጁ በሆነው እምላለው፥ እስካልሠለማችሁ ድረስ ጀነት አትገቡም"። عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ، عَنِ النَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم قَالَ: وَالَّذِي نَفْسِي بِيَدِهِ، لاَ تَدْخُلُوا الْجَنَّةَ حَتَّى تُسْلِمُوا
ኢማም ሙሥሊም መጽሐፍ 12, ሐዲስ 163
ዐምር ኢብኑ አል ዓስ እንደተረከው፦ "የአሏህ መልእክተኛ"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "የሠለመ ዳነ"። عَنْ عَمْرِو بْنِ الْعَاصِ أَنَّ رَسُولَ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم قَالَ " قَدْ أَفْلَحَ مَنْ أَسْلَمَ " .
አምላካችን አሏህ በልባችን ውስጥ ያለውን እውነተኛ ሀብት እንድንጠቀም ይርዳን! በሠሊም ቀልብ ወደ እርሱ የምንመጣ ያድርገን! አሚን።
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
ተዋዱዕ
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
22፥34 ለአላህ ተዋራጆችንም አብስራቸው፡፡ وَبَشِّرِ الْمُخْبِتِينَ
"ተዋዱዕ تَوَاضُع የሚለው ቃል "ተዋደዐ" تَوَاضَعَ ማለትም "ተናነሰ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "መተናነስ"humility" ወይም "ትህትና"humbles" ማለት ነው፦
ጃምዒ አት-ቲርሚዚይ መጽሐፍ 27, ሐዲስ 135
አቢ ሁረይራህ እንደተረከው፦ "የአሏህ መልእክተኛ"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "ሶደቃህ ሀብትን አይቀንስም፣ አሏህ አንድን ሰው ይቅርታ በማለቱ ክብርን እንጂ ሌላን አይጨምርለትም፣ አሏህ ከፍ የሚደርገው ቢሆን እንጂ ለአሏህ ራሱን የሚተናነስ የለም"። عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ، أَنَّ رَسُولَ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم قَالَ " مَا نَقَصَتْ صَدَقَةٌ مِنْ مَالٍ وَمَا زَادَ اللَّهُ رَجُلاً بِعَفْوٍ إِلاَّ عِزًّا وَمَا تَوَاضَعَ أَحَدٌ لِلَّهِ إِلاَّ رَفَعَهُ اللَّهُ " .
እዚህ ሐዲስ ላይ "የሚተናነስ" ለሚለው የግሥ መደብ የገባው ቃል "ተዋደዐ" تَوَاضَعَ ሲሆን ተዋዱዕ የሌለው ልብ ላይ ነቢያችን"ﷺ" ኢሥቲዓዛ አርገዋል፦
ሡነን አን-ነሣኢ መጽሐፍ 50, ሐዲስ 15
ዐብደሏህ ኢብኑ ዐምር እንደተረከው፦ "ነቢዩ"ﷺ" ከአራት ነገር በአሏህ ይጠበቁ ነበር፥ እነርሱም ከማይጠቅም ዕውቀት፣ ከማይተናነስ ልብ፣ ከማይሰማ ዱዓእ እና ከማትረካ ነፍስ ናቸው"። عَنْ عَبْدِ اللَّهِ بْنِ عَمْرٍو، أَنَّ النَّبِيَّ صلى الله عليه وسلم كَانَ يَتَعَوَّذُ مِنْ أَرْبَعٍ مِنْ عِلْمٍ لاَ يَنْفَعُ وَمِنْ قَلْبٍ لاَ يَخْشَعُ وَدُعَاءٍ لاَ يُسْمَعُ وَنَفْسٍ لاَ تَشْبَعُ .
እዚህ ሐዲስ ላይ "ማይተናነስ" ለሚለው የግሥ መደብ የገባው ቃል "ላ የኽሸዑ" لاَ يَخْشَعُ ሲሆን የስም መደቡ "ኹሹዕ" خُشُوع ነው፥ ኹሹዕ ያለው በሶላት ላይ የሚቆም የአሏህ ባሪያ "ኻሺዕ" خَاشِع ይባላል፦
2፥45 በትእግስት እና በሶላትም ተረዱ! እርሷም ሶላት በ-"ፈሪዎች" ላይ እንጂ በሌላው ላይ በእርግጥ ከባድ ናት፡፡ وَاسْتَعِينُوا بِالصَّبْرِ وَالصَّلَاةِ ۚ وَإِنَّهَا لَكَبِيرَةٌ إِلَّا عَلَى الْخَاشِعِينَ
23፥2 እነዚያ እነርሱ በሶላታቸው ውስጥ አሏህን "ፈሪዎች" የሆኑት፡፡ الَّذِينَ هُمْ فِي صَلَاتِهِمْ خَاشِعُونَ
እነዚህ አናቀጽ ላይ "ፈሪዎች" ለሚለው የገባው ቃል "ኻሺዒን" خَاشِعِين ሲሆን "ትሁታን" "ተናናሾች" "ተዋራጆች" ማለት ነው፥ ሶላት ላይ ለመቆም ቀላል የሚያደርገው ለአሏህ መተናነስን፣ መጎባደድን፣ ዝቅ ማድረግን፣ መዋረድን ነው። መተናነስ ለአሏህ ተብሎ የሚደረግ ዒባደቱል ቀልቢያ ነው፦
7፥55 ጌታችሁን "ተዋርዳችሁ" በድብቅም ለምኑት፡፡ ادْعُوا رَبَّكُمْ تَضَرُّعًا وَخُفْيَةً
2፥150 አትፍሩዋቸውም፤ ፍሩኝም። فَلَا تَخْشَوْهُمْ وَاخْشَوْنِي
አምላካችን አሏህ "ኢኽሸውኒ" خْشَوْنِي ማለቱ በራሱ መተናነስ የአምልኮ ክፍል መሆኑን ያሳያል። መተናነስ ከትህትና ወደ ልዕልና፣ ከዕርደት ወደ ዕርገት፣ ከቀንበር ወደ መንበር አሸጋግሮ ለጀነት የሚያስበስር ነው፦
22፥34 ለአላህ ተዋራጆችንም አብስራቸው፡፡ وَبَشِّرِ الْمُخْبِتِينَ
21፥90 ለእኛ ተዋራጆችም ነበሩ፡፡ وَكَانُوا لَنَا خَاشِعِينَ
ሌላው ለሰው የምንተናነሰው መተናነስ ትህትና ሲሆን "ኸፍድ" ነው፥ "ኸፍድ" خَفْض የሚለው ቃል "ኸፈደ" خَفَضَ ማለትም "ዝቅ አለ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "ዝቅታ"lowliness" ማለት ነው፦
17፥24 ለሁለቱም(ለወላጆች) ከእዝነትህ የመዋረድን ክንፍ ዝቅ አድርግላቸው፡፡ وَاخْفِضْ لَهُمَا جَنَاحَ الذُّلِّ مِنَ الرَّحْمَةِ
26፥215 ከምእምናንም ለተከተሉህ ሰዎች ክንፍህን ዝቅ አድርግ፡፡ وَاخْفِضْ جَنَاحَكَ لِمَنِ اتَّبَعَكَ مِنَ الْمُؤْمِنِينَ
እነዚህ አናቀጽ ላይ "ዝቅ አርግ" ለሚለው የገባው ትእዛዛዊ ግሥ "ኢኽፊድ" اخْفِضْ ነው፥ ኸፍድ የተዋዱዕ ክፍል ነው፦
ሡነን አቢ ዳውድ መጽሐፍ 43, ሐዲስ 123
ዒያድ ኢብኑ ሒማር እንደተረከው፦ "የአሏህ መልእክተኛ"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "አሏህ ወደ እኔ፦ "ተናነሱ፣ አንዱ ሌላውን አይጨቁን፣ አንዱ በሌላው ላይ አይኩራ"የሚለውን ገልጧል"። عَنْ عِيَاضِ بْنِ حِمَارٍ، أَنَّهُ قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم " إِنَّ اللَّهَ أَوْحَى إِلَىَّ أَنْ تَوَاضَعُوا حَتَّى لاَ يَبْغِيَ أَحَدٌ عَلَى أَحَدٍ وَلاَ يَفْخَرَ أَحَدٌ عَلَى أَحَدٍ " .
አምላካችን አሏህ በተዋዱዕ ኻሺዒን ከሚላቸው ባሮቹ ያድርገን! አሚን።
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
22፥34 ለአላህ ተዋራጆችንም አብስራቸው፡፡ وَبَشِّرِ الْمُخْبِتِينَ
"ተዋዱዕ تَوَاضُع የሚለው ቃል "ተዋደዐ" تَوَاضَعَ ማለትም "ተናነሰ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "መተናነስ"humility" ወይም "ትህትና"humbles" ማለት ነው፦
ጃምዒ አት-ቲርሚዚይ መጽሐፍ 27, ሐዲስ 135
አቢ ሁረይራህ እንደተረከው፦ "የአሏህ መልእክተኛ"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "ሶደቃህ ሀብትን አይቀንስም፣ አሏህ አንድን ሰው ይቅርታ በማለቱ ክብርን እንጂ ሌላን አይጨምርለትም፣ አሏህ ከፍ የሚደርገው ቢሆን እንጂ ለአሏህ ራሱን የሚተናነስ የለም"። عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ، أَنَّ رَسُولَ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم قَالَ " مَا نَقَصَتْ صَدَقَةٌ مِنْ مَالٍ وَمَا زَادَ اللَّهُ رَجُلاً بِعَفْوٍ إِلاَّ عِزًّا وَمَا تَوَاضَعَ أَحَدٌ لِلَّهِ إِلاَّ رَفَعَهُ اللَّهُ " .
እዚህ ሐዲስ ላይ "የሚተናነስ" ለሚለው የግሥ መደብ የገባው ቃል "ተዋደዐ" تَوَاضَعَ ሲሆን ተዋዱዕ የሌለው ልብ ላይ ነቢያችን"ﷺ" ኢሥቲዓዛ አርገዋል፦
ሡነን አን-ነሣኢ መጽሐፍ 50, ሐዲስ 15
ዐብደሏህ ኢብኑ ዐምር እንደተረከው፦ "ነቢዩ"ﷺ" ከአራት ነገር በአሏህ ይጠበቁ ነበር፥ እነርሱም ከማይጠቅም ዕውቀት፣ ከማይተናነስ ልብ፣ ከማይሰማ ዱዓእ እና ከማትረካ ነፍስ ናቸው"። عَنْ عَبْدِ اللَّهِ بْنِ عَمْرٍو، أَنَّ النَّبِيَّ صلى الله عليه وسلم كَانَ يَتَعَوَّذُ مِنْ أَرْبَعٍ مِنْ عِلْمٍ لاَ يَنْفَعُ وَمِنْ قَلْبٍ لاَ يَخْشَعُ وَدُعَاءٍ لاَ يُسْمَعُ وَنَفْسٍ لاَ تَشْبَعُ .
እዚህ ሐዲስ ላይ "ማይተናነስ" ለሚለው የግሥ መደብ የገባው ቃል "ላ የኽሸዑ" لاَ يَخْشَعُ ሲሆን የስም መደቡ "ኹሹዕ" خُشُوع ነው፥ ኹሹዕ ያለው በሶላት ላይ የሚቆም የአሏህ ባሪያ "ኻሺዕ" خَاشِع ይባላል፦
2፥45 በትእግስት እና በሶላትም ተረዱ! እርሷም ሶላት በ-"ፈሪዎች" ላይ እንጂ በሌላው ላይ በእርግጥ ከባድ ናት፡፡ وَاسْتَعِينُوا بِالصَّبْرِ وَالصَّلَاةِ ۚ وَإِنَّهَا لَكَبِيرَةٌ إِلَّا عَلَى الْخَاشِعِينَ
23፥2 እነዚያ እነርሱ በሶላታቸው ውስጥ አሏህን "ፈሪዎች" የሆኑት፡፡ الَّذِينَ هُمْ فِي صَلَاتِهِمْ خَاشِعُونَ
እነዚህ አናቀጽ ላይ "ፈሪዎች" ለሚለው የገባው ቃል "ኻሺዒን" خَاشِعِين ሲሆን "ትሁታን" "ተናናሾች" "ተዋራጆች" ማለት ነው፥ ሶላት ላይ ለመቆም ቀላል የሚያደርገው ለአሏህ መተናነስን፣ መጎባደድን፣ ዝቅ ማድረግን፣ መዋረድን ነው። መተናነስ ለአሏህ ተብሎ የሚደረግ ዒባደቱል ቀልቢያ ነው፦
7፥55 ጌታችሁን "ተዋርዳችሁ" በድብቅም ለምኑት፡፡ ادْعُوا رَبَّكُمْ تَضَرُّعًا وَخُفْيَةً
2፥150 አትፍሩዋቸውም፤ ፍሩኝም። فَلَا تَخْشَوْهُمْ وَاخْشَوْنِي
አምላካችን አሏህ "ኢኽሸውኒ" خْشَوْنِي ማለቱ በራሱ መተናነስ የአምልኮ ክፍል መሆኑን ያሳያል። መተናነስ ከትህትና ወደ ልዕልና፣ ከዕርደት ወደ ዕርገት፣ ከቀንበር ወደ መንበር አሸጋግሮ ለጀነት የሚያስበስር ነው፦
22፥34 ለአላህ ተዋራጆችንም አብስራቸው፡፡ وَبَشِّرِ الْمُخْبِتِينَ
21፥90 ለእኛ ተዋራጆችም ነበሩ፡፡ وَكَانُوا لَنَا خَاشِعِينَ
ሌላው ለሰው የምንተናነሰው መተናነስ ትህትና ሲሆን "ኸፍድ" ነው፥ "ኸፍድ" خَفْض የሚለው ቃል "ኸፈደ" خَفَضَ ማለትም "ዝቅ አለ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "ዝቅታ"lowliness" ማለት ነው፦
17፥24 ለሁለቱም(ለወላጆች) ከእዝነትህ የመዋረድን ክንፍ ዝቅ አድርግላቸው፡፡ وَاخْفِضْ لَهُمَا جَنَاحَ الذُّلِّ مِنَ الرَّحْمَةِ
26፥215 ከምእምናንም ለተከተሉህ ሰዎች ክንፍህን ዝቅ አድርግ፡፡ وَاخْفِضْ جَنَاحَكَ لِمَنِ اتَّبَعَكَ مِنَ الْمُؤْمِنِينَ
እነዚህ አናቀጽ ላይ "ዝቅ አርግ" ለሚለው የገባው ትእዛዛዊ ግሥ "ኢኽፊድ" اخْفِضْ ነው፥ ኸፍድ የተዋዱዕ ክፍል ነው፦
ሡነን አቢ ዳውድ መጽሐፍ 43, ሐዲስ 123
ዒያድ ኢብኑ ሒማር እንደተረከው፦ "የአሏህ መልእክተኛ"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "አሏህ ወደ እኔ፦ "ተናነሱ፣ አንዱ ሌላውን አይጨቁን፣ አንዱ በሌላው ላይ አይኩራ"የሚለውን ገልጧል"። عَنْ عِيَاضِ بْنِ حِمَارٍ، أَنَّهُ قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم " إِنَّ اللَّهَ أَوْحَى إِلَىَّ أَنْ تَوَاضَعُوا حَتَّى لاَ يَبْغِيَ أَحَدٌ عَلَى أَحَدٍ وَلاَ يَفْخَرَ أَحَدٌ عَلَى أَحَدٍ " .
አምላካችን አሏህ በተዋዱዕ ኻሺዒን ከሚላቸው ባሮቹ ያድርገን! አሚን።
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም