ወሒድ የዕቅበተ ኢሥላም መጣጥፍት"Wahid Articles of Islamic Apologetics"
58.4K subscribers
68 photos
69 videos
19 files
1.72K links
ዳዒ ወሒድ በኢሥላም እና በክርስትና መካከል ያለውን ልዩነት እና አንድነት በንጽጽር የሚያስቀምጥ ወንድም ነው። ለዚህም የቋንቋ፣ የሰዋስው፣ የዐውድ፣ የተዛማች እና የሥነ አመክንዮ ሙግት በማቅረብ የሚታወቅ ተሟጋች እና ጦማሪ ነው። ለሙግቱ ነጥብ በዋነኝነት የሚጠቀምባቸው ቋንቋ ዐማርኛ፣ ግዕዝ፣ እንግሊዝኛ፣ ዐረቢኛ፣ ዕብራይስጥ እና ግሪክ ናቸው። መልካም የንባብ፣ የጥናት፣ የማነጻጸር ጊዜ ይሁንልዎ!
Download Telegram
የቁርኣን ዳራ መጽሐፍ ለምትፈልጉ ሁሉ ሠዑዲያህ ስለታተመ እዛው ያላችሁ ልጆች ወንድማችንን በዚህ ስልክ +966590748927 ወይም በቴሌ ግራም @Onlineamharicbooks ያግኙት!
አሏህ ተብቃቂ ነው!

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ፥ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።

3፥97 የካደም ሰው አላህ ከዓለማት ሁሉ የተብቃቃ ነው፡፡ وَمَن كَفَرَ فَإِنَّ اللَّهَ غَنِيٌّ عَنِ الْعَالَمِينَ

በቁርኣን ከተገለጹ የአሏህ ስሞች አንዱ "አል-ገኒይ" الْغَنِيّ ሲሆን "ተብቃቂው" ማለት ነው፥ አምላካችን አሏህ ከፍጥረቱ ምንም የማይከጅል የተብቃቃ በተቃራኒው ፍጥረቱ ግን ከእርሱ ከጃዮች ናቸው፦
22፥64 በሰማያት ውስጥ ያለው እና በምድር ውስጥ ያለው ሁሉ የእርሱ ብቻ ነው፡፡ አላህም እርሱ ተብቃቂው ምስጉኑ ነው፡፡ لَّهُ مَا فِي السَّمَاوَاتِ وَمَا فِي الْأَرْضِ ۗ وَإِنَّ اللَّهَ لَهُوَ الْغَنِيُّ الْحَمِيدُ
35፥15 እናንተ ሰዎች ሆይ! እናንተ ወደ አላህ ከጃዮች ናችሁ፥ አላህም እርሱ ተብቃቂው ምስጉኑ ነው፡፡ يَا أَيُّهَا النَّاسُ أَنتُمُ الْفُقَرَاءُ إِلَى اللَّهِ ۖ وَاللَّهُ هُوَ الْغَنِيُّ الْحَمِيدُ

እዚህ ድረስ ከተግባባን ዘንዳ አሏህ ከፍጥረቱ እርዳታ ይፈልጋልን? እረ በፍጹም ምንም አይፈልግም። የማይፈልግ ከሆነ "አሏህ እና መልእክተኛውን መርዳት" ምን ማለት ነው? "አሏህ እና መልእክተኛውን መርዳት" ማለት በጥቅሉ የአሏህ እና የመልእክተኛውን ዲን መርዳት ማለት ነው፦
59፥8 ለእነዚያ የአላህን ችሮታና ውዴታውን የሚፈልጉ፣ አላህን እና መልክተኛውንም የሚረዱ ኾነው ከአገሮቻቸውና ከገንዘቦቻቸው ለተወጡት ስደተኞች ድኾች ይሰጣል፡፡ እነዚያ እነርሱ እውነተኞቹ ናቸው፡፡ لِلْفُقَرَاءِ الْمُهَاجِرِينَ الَّذِينَ أُخْرِجُوا مِن دِيَارِهِمْ وَأَمْوَالِهِمْ يَبْتَغُونَ فَضْلًا مِّنَ اللَّهِ وَرِضْوَانًا وَيَنصُرُونَ اللَّهَ وَرَسُولَهُ ۚ أُولَـٰئِكَ هُمُ الصَّادِقُونَ

እዚህ ዐውድ ላይ "መልእክተኛ" የተባሉት ተወዳጁ ነቢያችን"ﷺ" ሲሆን እርሳቸውን መርዳት አካላዊ ሳይሆን ዲናዊ ከሆነ አሏህን መርዳት ማለት ዲኑን ለማስፋፋት ማስተማር ነው። እሩቅ ሳንሄድ ቀደምት መልእክተኞች በሕይወት እንደሌሉ እየታወቀ "መልክተኞቹን በሩቅ ኾኖ የሚረዳ" ማለት እነርሱ ያስተማሩትን ዲን መርዳት ማለት ነው፦
57፥25 አላህም ሃይማኖቱን እና "መልክተኞቹን በሩቅ ኾኖ የሚረዳውን ሰው" ሊለይ አወረደው፡፡ አላህ ብርቱ አሸናፊ ነውና፡፡ وَلِيَعْلَمَ اللَّهُ مَن يَنصُرُهُ وَرُسُلَهُ بِالْغَيْبِ ۚ إِنَّ اللَّهَ قَوِيٌّ عَزِيزٌ

ደግሞ ማንኛውንም የአሏህ መልእክተኛ መርዳት አሏህ መርዳት ማለት ነው፥ ዒሣ፦ "ረዳቶቼ" እነማን ናቸው? ሲል ሐዋርያት፦ "እኛ የአላህ ረዳቶች ነን" ማለታቸው በራሱ መልእክተኛው ይዞት የመጣውን መልእክት በማስፋፋት መርዳት አሏህን መርዳት ነው፦
3፥52 ዒሣ ከእነርሱ ክህደት በተሰማውም ጊዜ፡- «ወደ አላህ "ረዳቶቼ" እነማን ናቸው» አለ፥ ሐዋርያት፡- «እኛ የአላህ ረዳቶች ነን፤ በአላህ አምነናል፤ እኛም ትክክለኛ ታዛዦች መኾናችንን መስክር» አሉ፡፡ فَلَمَّا أَحَسَّ عِيسَىٰ مِنْهُمُ الْكُفْرَ قَالَ مَنْ أَنصَارِي إِلَى اللَّهِ ۖ قَالَ الْحَوَارِيُّونَ نَحْنُ أَنصَارُ اللَّهِ آمَنَّا بِاللَّهِ وَاشْهَدْ بِأَنَّا مُسْلِمُونَ
3፥81 አላህ የነቢያትን ቃል ኪዳን ከመጽሐፍ እና ከጥበብ ሰጥቻችሁ ከዚያም «ከእናንተ ጋር ላለው የሚያረጋግጥ መልክተኛ ቢመጣላችሁ በእርሱ በእርግጥ እንደምታምኑበት በእርግጥም "እንድትረዱት" ሲል በያዘ ጊዜ አስታውስ፡፡ وَإِذْ أَخَذَ اللَّهُ مِيثَاقَ النَّبِيِّينَ لَمَا آتَيْتُكُم مِّن كِتَابٍ وَحِكْمَةٍ ثُمَّ جَاءَكُمْ رَسُولٌ مُّصَدِّقٌ لِّمَا مَعَكُمْ لَتُؤْمِنُنَّ بِهِ وَلَتَنصُرُنَّهُ

"መልክተኛ ቢመጣላችሁ በእርሱ በእርግጥ እንደምታምኑበት በእርግጥም "እንድትረዱት" የሚለው ኃይለ-ቃል ይሰመርበት! መልእክተኛውን መርዳት ይዞት የመጣውን መልእክት ለሌላ በማስተላለፍ መርዳት ነው።
ሌላ ምሳሌ "አሏህ እና መልእክተኛውን መዋጋት" ማለት ቃል በቃል አሏህ መዋጋት እንዳልሆነ እና ዲኑን መዋጋት እንደሆነ ሁሉ አሏህ እና መልእክተኛው መርዳት ማለት ዲኑን መርዳት ማለት ነው፦
5፥33 የእነዚያ "አላህን እና መልክተኛውን የሚዋጉ" በምድርም ላይ ለማጥፋት የሚተጉ ሰዎች ቅጣት መገደል ወይም መሰቀል ወይም እጆቻቸውንና እግሮቻቸውን በማፈራረቅ መቆረጥ ወይም ከአገር መባረር ነው፡፡ إِنَّمَا جَزَاءُ الَّذِينَ يُحَارِبُونَ اللَّهَ وَرَسُولَهُ وَيَسْعَوْنَ فِي الْأَرْضِ فَسَادًا أَن يُقَتَّلُوا أَوْ يُصَلَّبُوا أَوْ تُقَطَّعَ أَيْدِيهِمْ وَأَرْجُلُهُم مِّنْ خِلَافٍ أَوْ يُنفَوْا مِنَ الْأَرْضِ
"አላህን እና መልክተኛውን የሚዋጉ" ማለት ዲኑን መዋጋት ከሆነ "አሏህ እና መልእክተኛውን መርዳት" ማለት ዲኑን መርዳት ማለት ነው። ስለዚህ አሏህን መርዳት ማለት ዲኑን መርዳት ማለት እንጂ ሌላ አንዳች ትርጉም የለውም፦
47፥7 እናንተ ያመናችሁ ሆይ! አላህን ብትረዱ ይረዳችኋል፥ ጫማዎቻችሁንም ያደላድላል፡፡ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا إِن تَنصُرُوا اللَّهَ يَنصُرْكُمْ وَيُثَبِّتْ أَقْدَامَكُمْ
22፥40 አላህም ሃይማኖቱን የሚረዳውን ሰው በእርግጥ ይረዳዋል፡፡ አላህ ብርቱ አሸናፊ ነውና፡፡ وَلَيَنصُرَنَّ اللَّهُ مَن يَنصُرُهُ ۗ إِنَّ اللَّهَ لَقَوِيٌّ عَزِيزٌ

አሏህን መርዳት አሏህ ፍጡራኑን በሚረዳበት ስሌት እና ቀመር መረዳት ትልቅ ስህተት ነው። አሏህ፦ "አስታውሱኝም አስታውሳችኋለሁ" ብሏል፥ ያ ማለት ሰው አሏህን መዘከር አምልኮ ሲሆን አሏህ ግን ሰውን መዘከሩ አምልኮ ሳይሆን የትንሳኤ ቀን ችላ እንደማይል ተስፋ ነው፦
2፥152 አስታውሱኝም አስታውሳችኋለሁና ለእኔም አመስግኑ፤ አትካዱኝም፡፡ فَاذْكُرُونِي أَذْكُرْكُمْ وَاشْكُرُوا لِي وَلَا تَكْفُرُونِ
45፥34 ይህንንም ቀናችሁን መገናኘትን እንደ ረሳችሁ ዛሬ እንረሳችኋለን፡፡ وَقِيلَ الْيَوْمَ نَنسَاكُمْ كَمَا نَسِيتُمْ لِقَاءَ يَوْمِكُمْ هَـٰذَا

እሩቅ ሳንሄድ ያህዌህ፦ ያከበሩኝን አከብራለሁና፥ የናቁኝም ይናቃሉና" ይላል፦
1 ሳሙኤል 2፥30 አሁን ግን ያህዌህ እንዲህ ይላል፦ ያከበሩኝን አከብራለሁና፥ የናቁኝም ይናቃሉና ይህ አይሆንልኝም።

ያህዌህን ማክበር አምልኮ ስለሆነ ያህዌህ ማክበሩስ አምልኮ ነው" ብሎ መፈሠር ይቻላልን? ንቀቱስ አንድ አይነት ነውን? ፈጣሪ ለፍጡር ሲሰጥ ፍጡራን የሚጎላቸውን ለመሙላት ነው፥ ፍጡር ለፈጣሪ የሚሰጠው ፈጣሪ ጎሎት ነውን? ከመቶ አሥር እጅ አሥራት ለያህዌህ ስጦታ ነውና፦
ሉቃስ 6፥38 “ስጡ ይሰጣችሁማል! በምትሰፍሩበት መስፈሪያ ተመልሶ ይሰፈርላችኋልና።
ዘሌዋውያን 27፥30 የምድርም አሥራት፥ ወይም የምድር ዘር ወይም የዛፍ ፍሬ ቢሆን፥ የያህዌህ ነው፥ ለያህዌህ የተቀደሰ ነው።

"ፈጣሪን ማክበር እና ለፈጣሪ መስጠት ፈጣሪ ተዋርዶ ወይም ጎድሎት ነው" እንደማትሉ ሁሉ "አሏህን መርዳት ማለት አቅም አንሶት ወይም ጎሎት ነው" ብላችሁ አትረዱት! በሰፈሩት ቁና መሰፈር ይሉካል እንደዚህ ነው። አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን! አሚን።

ከዐቃቤ አሥልምና ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
ሁለት አማራጭ

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ፥ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

91፥8 *"አመጽዋን እና ፍርሃትዋንም ባሳወቃት"*፡፡ فَأَلْهَمَهَا فُجُورَهَا وَتَقْوَاهَا

በቁርኣን "ነፍሥ" نَفْس ማለት “ራስነት”own self-hood” ማለት ሲሆን "ማንነት" ነው፥ አምላካችን አሏህ ለነፍሥ በኢህላም አመጽ ምን እንደሆነ እና አሏህ መፍራት ምን እንደሆነ አሳውቋታል፦
91፥8 *"አመጽዋን እና ፍርሃትዋንም ባሳወቃት"*፡፡ فَأَلْهَمَهَا فُجُورَهَا وَتَقْوَاهَا

እዚህ አንቀጽ ላይ "ባሳወቀ" ለሚለው የገባው ቃል "አልሀመ" أَلْهَمَ መሆኑን ልብ በል! "ኢልሃም" إِلْهَام የሚለው ቃል እራሱ "አልሀመ" أَلْهَمَ ከሚለው ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "ውሳጣዊ ግንዛቤ"intuition" ማለት ነው፦
ተፍሢሩል ኢብኑ ከሲር 91፥8 *ኢብኑ ዐባሥ "አመጽዋን እና ፍርሃትዋንም ባሳወቃት" የሚለውን ሲናገር፦ "ለእርሷ መልካም እና ክፉን ገልጾላታል"*። ሙጃሂድ፣ ቀታዳህ፣ ሶሓክ እና ሰውሪይ ተመሳሳይ ነገር ብለዋል፥ ሠዒድ ኢብኑ ጁበይር፦ "መልካም እና ክፉን ባሳወቃት" ብሏል"*።
قال ابن عباس : ( فألهمها فجورها وتقواها ) بين لها الخير والشر . وكذا قال مجاهد ، وقتادة ، والضحاك ، والثوري . وقال سعيد بن جبير : ألهمها الخير والشر .

"ፉጁር" فُجُور ማለት "አመጽ" ማለት ሲሆን ይህም አመጽ አሏህ ያዘዘውን መልካም ነገር ባለማድረግ እና የከለከለውን መጥፎ ነገር በማድረግ ማመጽ ነው፥ "ተቅዋ" تَقْوَا ማለት ደግሞ "አሏህን መፍራት" ማለት ሲሆን ይህም ፍርሃት አሏህ ያዘዘውን መልካም ነገር በማድረግ እና የከለከለውን መጥፎ ነገር ባለማድረግ መታዘዝ ነው።
ከዚያም ሰው ዐቅሉ ሲያመዛዝን አሏህ ነቢይ ልኮ በወሕይ "ይህ መልካም ነው" "ይህ መጥፎ ነው" በማለት ቅኑን መንገድ ከጠማማው መንገድ ይገልጥልናል፦
2፥256 በሃይማኖት ማስገደድ የለም፡፡ *ቅኑ መንገድ ከጠማማው በእርግጥ ተገለጠ*፡፡ لَا إِكْرَاهَ فِي الدِّينِ ۖ قَد تَّبَيَّنَ الرُّشْدُ مِنَ الْغَيِّ ۚ

አሏህ ያዘዘውን መልካም ነገር በማድረግ እና የከለከለውን መጥፎ ነገር ባለማድረግ አሏህ የሚፈራው "ሙተቂን" مُتَّقِين ሲባል በተቃራኒው አሏህ ያዘዘውን መልካም ነገር ባለማድረግ እና የከለከለውን መጥፎ ነገር በማድረግ ያመጸው አመጸኛ "ፉጃር" فُجَّار ይባላል፦
38፥28 *"በእውነቱ እነዚያን ያመኑትን እና መልካሞችን የሠሩትን በምድር ውስጥ እንደሚያጠፉት እናደርጋለን? ወይስ "አላህን ፊረዎቹን እንደ ከሓዲዎቹ እናደርጋለን?"* أَمْ نَجْعَلُ الَّذِينَ آمَنُوا وَعَمِلُوا الصَّالِحَاتِ كَالْمُفْسِدِينَ فِي الْأَرْضِ أَمْ نَجْعَلُ الْمُتَّقِينَ كَالْفُجَّارِ

“ዘንብ” ذَنب ማለት “ኃጢአት” ማለት ነው፥ “ኃጢአት” ማለት በሥነ-ኃጢአት ጥናት”hamartiology” አሏህ ያዘዘውን መልካም ነገር አለማድረግ፥ የከለከለውን ክፉ ነገር ማድረግ ነው። አምላካችን አሏህ ለሰው የሰጠው መልካም እና ክፋ የማሰብ፣ የመናገር፣ የማድረግ ነጻ ምርጫ በችሎታችን ልክ ነው፥ ያለ ችሎታችን ልክ አያስገድደንም፦
23፥62 *ማንኛይቱንም ነፍስ ችሎታዋን እንጂ አናስገድዳትም*፡፡ وَلَا نُكَلِّفُ نَفْسًا إِلَّا وُسْعَهَا
2፥286 *አላህ ነፍስን ከችሎታዋ በላይ አያስገድዳትም*፡፡ لَا يُكَلِّفُ اللَّهُ نَفْسًا إِلَّا وُسْعَهَا

"ዉሥዕ" وُسْع ማለት "ዐቅም" "ችሎታ" ማለት ሲሆን አንድ ሰው አንድን ነገር የማድረግ እና ያለማድረግ ችሎታ ከአሏህ የተሰጠ ነጻ ፈቃድ ነው፥ ከተሰጠው በላይ ለማድረግ ላለማድረግ የተገደደ ሰው አይጠየቅም። “የተገደደ ሰውም በእርሱ ላይ ኃጢኣት የለበትም” فَمَنِ اضْطُرَّ غَيْرَ بَاغٍ وَلَا عَادٍ فَلَا إِثْمَ عَلَيْهِ ተብሏልና፦
ሡነን ኢብኑ ማጃህ መጽሐፍ 10, ሐዲስ 2123
ኢብኑ ዐባሥ እንደተረከው፦ “ነቢዩም”ﷺ” አሉ፦ *”አላህ በኡማዬ ላይ ስህተት፣ መርሳት እና የገተደዱበትን ነገር አንስቷል”*። عَنِ ابْنِ عَبَّاسٍ، عَنِ النَّبِيِّ ـ صلى الله عليه وسلم ـ قَالَ ‏ “‏ إِنَّ اللَّهَ وَضَعَ عَنْ أُمَّتِي الْخَطَأَ وَالنِّسْيَانَ وَمَا اسْتُكْرِهُوا عَلَيْهِ
ሡነን አቢ ዳውድ መጽሐፍ 40, ሐዲስ 48
ዓኢሻህ "ረ.ዐ." እንደተረከው፦ "የአላህ መልዕክተኛ”ﷺ” እንዲህ አሉ፦ *"ብዕር ከሦስት ሰዎች ተነስቷል፥ እነርሱም፦ የተኛ ሰው እስኪነሳ ድረስ፣ ዕብደ ወደ ዐቅሉ እስኪመለስ ድረስ እና ልጅ እስኪጎሎብት ድረስ"*። عَنْ عَائِشَةَ، رضى الله عنها أَنَّ رَسُولَ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم قَالَ ‏ "‏ رُفِعَ الْقَلَمُ عَنْ ثَلاَثَةٍ عَنِ النَّائِمِ حَتَّى يَسْتَيْقِظَ وَعَنِ الْمُبْتَلَى حَتَّى يَبْرَأَ وَعَنِ الصَّبِيِّ حَتَّى يَكْبَرَ ‏

አሏህ ፍትሓዊ አምላክ ነው፥ ባለማወቅ ስህተትን ለሚሠሩ እና መልእክቱ ያልደረሳቸውን ሰዎች አይቀጣቸውም፦
2፥286 *"ጌታችን ሆይ! ”ብንረሳ ወይም ብንስት አትቅጣን” በሉ*፡፡ رَبَّنَا لَا تُؤَاخِذْنَا إِن نَّسِينَا أَوْ أَخْطَأْنَ
33፥5 *በእርሱ በተሳሳታችሁበትም ነገርም በእናንተ ላይ ኃጢአት የለባችሁም፥ ግን ልቦቻችሁ ዐዉቀው በሠሩት ኃጢአት አለባችሁ"*። አላህም መሃሪ አዛኝ ነው። وَلَيْسَ عَلَيْكُمْ جُنَاحٌۭ فِيمَآ أَخْطَأْتُم بِهِۦ وَلَٰكِن مَّا تَعَمَّدَتْ قُلُوبُكُمْ ۚ وَكَانَ ٱللَّهُ غَفُورًۭا رَّحِيمًا
17፥15 *መልእክተኛንም እስከምንልክ ድረስ የምንቀጣ አይደለንም*፡፡ وَمَا كُنَّا مُعَذِّبِينَ حَتَّىٰ نَبْعَثَ رَسُولًا
አምላካችን አሏህ በመልእክተኛው ወሕይ ከማውረዱ በፊት ልክ አንድ ሕጻን የእናት ሁለት ጡቶችን መርጦ እንዲጠባ በኢልሃም"innate knowledge" እንደሚያሳውቀው ሁሉ አንድ ነገር ኸይር ወይም ሸር መሆኑን ሁለቱንም ለአንድ ሰው በውሳጣዌ ግንዛቤ ያሳውቃል፦
90፥10 *ሁለት ”መንገዶችም” አልመራነውምን?"* وَهَدَيْنَٰهُ ٱلنَّجْدَيْنِ
76፥3 *"እኛ አመስጋኝ ወይም ከሐዲ ሲሆን ”መንገዱን መራነዉ”*። إِنَّا هَدَيْنَٰهُ ٱلسَّبِيلَ إِمَّا شَاكِرًۭا وَإِمَّا كَفُورًا

"ማመስገን" እና "አመስጋኝ" የሚለው ቃል "ማመን" እና "አማኝ" ለሚል ቃል ተለዋዋጭ ሆኖ የገባ ነው፥ ሰዎች በነቢይ በኩል መልእክቱ ደርሷቸው አመስግነው አመስጋኝ ቢሆኑ አሏህ ይወድላቸዋል ይጨምርላቸዋል። በተቃራኒው ክደው ከሓዲ ቢሆኑ አላህ ከእነርሱ የተብቃቃ ነው፥ ለባሪያዎቹም ከህደትን አይወድም። ይቀጣቸዋል፥ ቅጣቱ ብርቱ ነው፦
39፥7 *"ብትክዱ አላህ ከእናንተ የተብቃቃ ነው፥ ለባሪያዎቹም ከህደትን አይወድም፡፡ ብታመሰግኑ እርሱን ይወድላችኋል"*፡፡ إِن تَكْفُرُوا فَإِنَّ اللَّهَ غَنِيٌّ عَنكُمْ ۖ وَلَا يَرْضَىٰ لِعِبَادِهِ الْكُفْرَ ۖ وَإِن تَشْكُرُوا يَرْضَهُ لَكُمْ
14፥7 *ጌታችሁም «ብታመሰግኑ በእርግጥ እጨምርላችኋለሁ ብትክዱም እቀጣችኋለሁ፥ ቅጣቴ በእርግጥ ብርቱ ነውና» በማለት ባስታወቀ ጊዜ አስታውሱ"*፡፡ وَإِذْ تَأَذَّنَ رَبُّكُمْ لَئِن شَكَرْتُمْ لَأَزِيدَنَّكُمْ ۖ وَلَئِن كَفَرْتُمْ إِنَّ عَذَابِي لَشَدِيدٌ

"መሺኣህ" مَشِئَة የሚለው ቃል "ሻአ" شَاءَ ማለትም "ፈቀደ" ከሚለው ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "ፈቃድ" ማለት ነው፥ ስለዚህ ሰው አምኖ ለሚሠራው መልካም ሥራ አሊያም ክዶ ለሚሠራው መጥፎ ሥራ ነጻ ፈቃድ አለው፦
18፥29 *«እውነቱም ከጌታችሁ ነው፡፡ የሻም ሰው ይመን! የሻም ሰው ይካድ!»* በላቸው፡፡ وَقُلِ الْحَقُّ مِن رَّبِّكُمْ ۖ فَمَن شَاءَ فَلْيُؤْمِن وَمَن شَاءَ فَلْيَكْفُر
64፥2 *"እርሱ ያ የፈጠራችሁ ነው፡፡ ከእናንተም ከሓዲ አለ፥ ከእናንተም አማኝ አለ፡፡ አላህም በምትሠሩት ሁሉ ተመልካች ነው"*፡፡ هُوَ الَّذِي خَلَقَكُمْ فَمِنكُمْ كَافِرٌ وَمِنكُم مُّؤْمِنٌ ۚ وَاللَّهُ بِمَا تَعْمَلُونَ بَصِيرٌ

"የሻም ሰው ይመን! የሻም ሰው ይካድ" የሚለው ሰው የማማረጥ ነጻ ፈቃድ እንዳለው አመላካች ነው፥ በተጨማሪም "የሻም" ለሚለው የገባው ቃል "ሻአ" شَاءَ ነው። በዓለማችን ላይ "ካፊር" እና "ሙእሚን" ያለው ሰው በፈቃዱ በመረጠው ምርጫው ነው፥ አሏህ የምንሠራውን ሁሉ ተመልክቶ በምንሠራው ሥራ ይጠይቀናል፦
16፥93 *ትሠሩት ከነበራችሁትም ሁሉ በእርግጥ ትጠየቃላችሁ*፡፡ وَلَتُسْأَلُنَّ عَمَّا كُنتُمْ تَعْمَلُون
102፥8 ከዚያም *ከጸጋችሁ ሁሉ በዚያ ቀን ትጠየቃላችሁ*። ثُمَّ لَتُسْأَلُنَّ يَوْمَئِذٍ عَنِ النَّعِيمِ

“ነዒም” نَّعِيمِ ማለት “ጸጋ” ማለት ሲሆን ይህ የተሰጠን ጸጋ አድርግ የተባለውን የመታዘዝዝና ያለመታዘዝ፥ አታድርግ የተባለውን የመከልከልና ያለመከልከል ነጻ ፈቃድ"free will" ነው። ሰው በሚሠራው ሰናይ ሆነ እኩይ ሥራ ግብረገባዊ ተጠያቂነት"moral accountability" ያለው ፍጡር መሆኑ እነዚህ ሁለት አናቅጽ ፍንትው እና ቁልጭ አድርገው ያሳያሉ። አሏህ በሠራው እና በሚሠራው ሥራ አይጠየቅም፥ ሁለት ምርጫ ያላቸው ፍጡራን ግን በሚሠሩት ሥራ ይጠየቃሉ፦
21፥23 *ከሚሠራው ሁሉ አይጠየቅም፡፡ እነርሱ ግን ይጠየቃሉ*፡፡ لَا يُسْأَلُ عَمَّا يَفْعَلُ وَهُمْ يُسْأَلُونَ

ሰዎች በተሰጣቸው ነጻ ፈቃድ ይሠሩት የነበሩትን መልካም ነገር ይመነዳሉ፥ በተቃራኒው ይሠሩት የነበሩትን መጥፎ ነገር ይቀጣሉ፦
18፥180 *"ይሠሩት የነበሩትን ነገር በእርግጥ ይመነዳሉ"*፡፡ سَيُجْزَوْنَ مَا كَانُوا يَعْمَلُونَ
6፥120 *"እነዚያ ኃጢአትን የሚሠሩ ይሠሩት በነበሩት ነገር በእርግጥ ይቀጣሉ"*፡፡ نَّ الَّذِينَ يَكْسِبُونَ الْإِثْمَ سَيُجْزَوْنَ بِمَا كَانُوا يَقْتَرِفُونَ

አሏህ በነጻ ፈቃዳቸው ካመኑት እና መልካም ከሠሩት ሙተቂን ያድርገን! አሚን።

ከዐቃቤ እሥልምና ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
ዘቡር

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

17፥55 ጌታህም በሰማያትና በምድር ያለውን ሁሉ ዐዋቂ ነው፡፡ ከፊሉንም ነቢያት በከፊሉ ላይ በእርግጥ አብልጠናል፡፡ *”ለዳውድም ዘቡርን ሰጥተነዋል”*፡፡ وَرَبُّكَ أَعْلَمُ بِمَن فِي السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضِ ۗ وَلَقَدْ فَضَّلْنَا بَعْضَ النَّبِيِّينَ عَلَىٰ بَعْضٍ ۖ وَآتَيْنَا دَاوُودَ زَبُورًا

አላህ በቁርኣን ስማቸውን ካነሳቸው ሃያ አምስት ነቢያት መካከል አንዱ ዳውድ ሲሆን በስም ካነሳቸው አራት መጽሐፍት መካከል ደግሞ አንዱ ዘቡር ነው፦
17፥55 ጌታህም በሰማያትና በምድር ያለውን ሁሉ ዐዋቂ ነው፡፡ ከፊሉንም ነቢያት በከፊሉ ላይ በእርግጥ አብልጠናል፡፡ *”ለዳውድም ዘቡርን ሰጥተነዋል”*፡፡ وَرَبُّكَ أَعْلَمُ بِمَن فِي السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضِ ۗ وَلَقَدْ فَضَّلْنَا بَعْضَ النَّبِيِّينَ عَلَىٰ بَعْضٍ ۖ وَآتَيْنَا دَاوُودَ زَبُورًا
4፥163 እኛ ወደ ኑሕና ከርሱ በኋላ ወደ ነበሩት ነቢያት እንዳወረድን ወደ አንተም አወረድን፡፡ ወደ ኢብራሂምም፣ ወደ ኢስማዒልም፣ ወደ ኢስሓቅም፣ ወደ ያዕቆብም፣ ወደ ነገዶቹም፣ ወደ ዒሳም፣ ወደ አዩብም፣ ወደ ዩኑስም፣ ወደ ሃሩንና፣ ወደ ሱለይማንም አወረድን፡፡ *”ለዳውድም ዘቡርን ሰጠነው”*፡፡ إِنَّا أَوْحَيْنَا إِلَيْكَ كَمَا أَوْحَيْنَا إِلَىٰ نُوحٍ وَالنَّبِيِّينَ مِن بَعْدِهِ ۚ وَأَوْحَيْنَا إِلَىٰ إِبْرَاهِيمَ وَإِسْمَاعِيلَ وَإِسْحَاقَ وَيَعْقُوبَ وَالْأَسْبَاطِ وَعِيسَىٰ وَأَيُّوبَ وَيُونُسَ وَهَارُونَ وَسُلَيْمَانَ ۚ وَآتَيْنَا دَاوُودَ زَبُورًا
21፥105 *”ምድንም መልካሞቹ ባሮቼ ይወርሷታል ማለትን ከመገሰጫው በኋላ በዘቡር በእርግጥ ጽፈናል”*፡፡ وَلَقَدْ كَتَبْنَا فِي الزَّبُورِ مِن بَعْدِ الذِّكْرِ أَنَّ الْأَرْضَ يَرِثُهَا عِبَادِيَ الصَّالِحُونَ

“ከተብና” َكَتَبْنَا የሚለው ቃል “ቁልና” قُلْنَا ማለትም “አልን” ወይም “አውሐይና” َأَوْحَيْنَا ማለትም “አወረድን” በሚል ተለዋዋጭ ቃል የመጣ ነው። እዚህ ዐውድ ላይ “ዚክር” ذِكْر የተባለው ተውራት ሲሆን አላህ በተውራት፦ “ምድር ለአላህ ናትና፡፡ ከባሮቹ ለሚሻው ያወርሳታል፡፡ ምሰጉንዋም ፍጻሜ ለጥንቁቆቹ ናት” የሚል ቃል አውርዷል፦
21፥48 *”ለሙሳና ለሃሩንም እውነትንና ውሸትን የሚለይን ብርሃንንም ለጥንቁቆችም መገሰጫን በእርግጥ ሰጠናቸው”*፡፡ وَلَقَدْ آتَيْنَا مُوسَىٰ وَهَارُونَ الْفُرْقَانَ وَضِيَاءً وَذِكْرًا لِّلْمُتَّقِينَ
7፥128 ሙሳ ለሰዎቹ፡- «ለአላህ ተገዙ ታገሱም፡፡ *ምድር ለአላህ ናትና፡፡ ከባሮቹ ለሚሻው ያወርሳታል፡፡ ምሰጉንዋም ፍጻሜ ለጥንቁቆቹ ናት»* አላቸው፡፡ قَالَ مُوسَىٰ لِقَوْمِهِ اسْتَعِينُوا بِاللَّهِ وَاصْبِرُوا ۖ إِنَّ الْأَرْضَ لِلَّهِ يُورِثُهَا مَن يَشَاءُ مِنْ عِبَادِهِ ۖ وَالْعَاقِبَةُ لِلْمُتَّقِينَ

ከተውራት በኃላ በዘቡር “ምድንም መልካሞቹ ባሮቼ ይወርሷታል” የሚለው ንግግር በእርግጥ ተነግሯል። “ዘቡር” زَّبُور ማለት “ጽሑፍ”script” ማለት ነው፤ ይህ ቃል “ጽሑፍ” በሚል ስድስት ጊዜ መጥቷል፦
3፥184 ቢያስተባብሉህም ከአንተ በፊት በግልጽ ተዓምራት እና *”በጽሑፎች”*፣ በብሩህ መጽሐፍም የመጡት መልክተኞች በእርግጥ ተስተባብለዋል፡፡ فَإِن كَذَّبُوكَ فَقَدْ كُذِّبَ رُسُلٌ مِّن قَبْلِكَ جَاءُوا بِالْبَيِّنَاتِ وَالزُّبُرِ وَالْكِتَابِ الْمُنِير
16፥44 በግልጽ ማስረጃዎች እና *”በመጻሕፍት”* ላክናቸው፡፡ ወደ አንተም ለሰዎች ወደእነሱ የተወረደውን ልትገልጽላቸውና ያስተነትኑም ዘንድ ቁርኣንን አወረድን፡፡ بِالْبَيِّنَاتِ وَالزُّبُرِ ۗ وَأَنزَلْنَا إِلَيْكَ الذِّكْرَ لِتُبَيِّنَ لِلنَّاسِ مَا نُزِّلَ إِلَيْهِمْ وَلَعَلَّهُمْ يَتَفَكَّرُونَ
26፥196 እርሱም ቁርኣን በቀድሞዎቹ *”መጻሐፍት”* ውስጥ የተወሳ ነው፡፡ وَإِنَّهُ لَفِي زُبُرِ الْأَوَّلِين
35፥25 ቢያስተባብሉህም እነዚያ ከበፊታቸው የነበሩት በእርግጥ አስተባብለዋል፡፡ መልክተኞቻቸው በግልጽ ማስረጃዎችን፣ *”በጽሑፎችም”*፣ አብራሪ በኾነ መጽሐፍም መጥተዋቸዋል፡፡ وَإِن يُكَذِّبُوكَ فَقَدْ كَذَّبَ الَّذِينَ مِن قَبْلِهِمْ جَاءَتْهُمْ رُسُلُهُم بِالْبَيِّنَاتِ وَبِالزُّبُرِ وَبِالْكِتَابِ الْمُنِيرِ
54፥43 ከሓዲዎቻችሁ ከእነዚህ በላጮች ናቸውን? ወይስ ለእናንተ *”በመጽሐፎች”* ውስጥ የተነገረ ነፃነት አላችሁን? أَكُفَّارُكُمْ خَيْرٌ مِّنْ أُولَـٰئِكُمْ أَمْ لَكُم بَرَاءَةٌ فِي الزُّبُرِ
54፥52 የሠሩትም ነገር ሁሉ *”በመጽሐፎች”* ውስጥ ነው፡፡ وَكُلُّ شَيْءٍ فَعَلُوهُ فِي الزُّبُرِ

እነዚህ አናቅጽ ላይ “መጽሐፎች” “መጻሐፍት” “ጽሑፎች” “መጽሐፍት” ለሚለው የገባው “ዙቡር” زُّبُر ሲሆን የዘቡር ብዙ ቁጥር ሆኖ ነው። ነገር ግን እነዚህ አናቅጽ ላይ “ዙቡር” የሚለው ለዳውድ የተሰጠውን ዘቡር ሳይሆን “ኩቱብ” كُتُب ለሚለው ተለዋዋጭ ነው።
“ሚዝሙር” מִזְמוֹר በብዜት “ዘሚር” זָמִיר በነጠላ ተብሎ የተቀመጠው የዕብራይስጥ ቃል “ዘመረ” זָמַר ማለትም “አወደሰ” “አመሰገነ” ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን “ምስጋና” “ውዳሴ” “ማህሌት” “መዝሙር” “ዜማ” ማለት ነው።
ዘቡር የተሕሚድ፣ የተህሊል፣ የተሥቢሕ ነሺድ ነው፥ “ተሕሚድ” تحميد ማለት “አልሓምዱ ሊላህ” الحَمْد لله‌‎ ማለት ነው፣ “ተህሊል” تهليل‌‎ ማለት “ላ ኢላሃ ኢለላህ” لا اله الاّ الله ማለት ነው፣ “ተሥቢሕ” تسبيح‌‎ ማለት “ሡብሓን አላህ” سبحان الله ማለት ነው። “ነሺድ” نشيد ማለት “ዜማ” ማለት ሲሆን “ሙነሺድ” منشد ደግሞ “አዛሚ” ማለት ነው።
ዛሬ በመጽሐፉ ሰዎች እጅ ባሉት መዝሙራት ውስጥ የዳውድ ዘቡር ቅሪት ቢኖርም ነገር ግን ከዳድው መዝሙር ላይ የተጨመሩና የተቀነሱ ቃላት አሉ። ዛሬ ያሉት መዝሙራት የሰባት ሰዎች መዝሙራት ናቸው፤ እነርሱም፦ የዳዊት 73 መዝሙራት፣ የሰለሞን 2 መዝሙራት፣ የሙሴ 1 መዝሙር፣ የአሳፍ 12 መዝሙራት፣ የቆሬ 11 መዝሙራት፣ የሄማን 2 መዝሙራት፣ 49 መዝሙራት ደግሞ የማይታወቁ ሰዎች ናቸው።
ቁርኣን እውቅና የሰጠው ለዳዊት የተሰጠውን መዝሙር ብቻ ነው፣ ነገር ግን እነዚህን 150 መዝሙራት ሰብስቦ የጻፈው ዳዊት ሳይሆን በባቢሎን ምርኮ ጊዜ 586-538 BC የነበረ ሰው ነው፦
መዝሙር 137፥1 *”በባቢሎን ወንዞች አጠገብ በዚያ ተቀመጥን፤ ጽዮንንም ባሰብናት ጊዜ አለቀስን”*።

ዳዊት ደግሞ የነበረው ከባቢሎን ምርኮ በፊት ማለት ከ 384 ዓመት በፊት በ 1040–970 BC ነው። በባቢሎን ወንዞች አጠገብ በምርኮ ተቀመጦ ጽዮንንም ባሰባት ጊዜ ያለቀሰው ሰው ዳዊት ሳይሆን ሌላ ሰው ነው። የዚህ ሰው ንግግር የአምላክ ንግግር ነውን? በፍጹም! በዳዊት መዝሙር ላይ የተጨመረ ንግግር ነው። እንዲሁ በተቃራኒ ከዳዊት መዝሙር ላይ የተቀነሱ መዝሙራት አሉ። የምዕራብይቱ ቤተክርስቲያን እና አይሁዳውናን፦ “መዝሙራት 150 ብቻ ናቸው” ቢሉም ከ 150 በላይ ናቸው የሚሉ ምሁራን አልጠፉም፣ ማስረጃቸው የሰፕቱጀንት መዝሙራትና የምስራቋ ቤተክርስቲያን መዝሙራት 151 መዝሙራት ነው ያላቸው፣ የዐረማይኩ በርሺታ 152 መዝሙራት ሲኖረው፣ የሙት ባህር ጥቅል ደግሞ 155 መዝሙራት ነው።
ዋቢ መጽሐፍትን ይመልከቱ፦
1. James D. Nogalski, “From Psalm to Psalms to Psalter,” in An Introduction to Wisdom Literature and the Psalms: Festschrift Marvin E. Tate.
2. A Brief Introduction to the Old Testament: The Hebrew Bible in its Context. (Oxford University Press: Oxford 2009).
3. The Editing of the Hebrew Psalter (Chico, CA: Scholars Press, 1985).
4. Introduction to the Old Testament as Scripture (Philadelphia: Fortress, 1979)
5. Studies on the Book of Psalms (Edinburgh: T. & T. Clark, 1888).

ቁርኣን ከወረደበት ግብና አላማ፣ ፋይዳና ሚና አንዱ ከአላህ ወደ ነቢያት ያወረደውን መለኮታዊ እውነት ለማረጋገጥ እና በዚህ በወረደው እውነት ላይ ቀጥፈው የጨመሩትን ሐሰት ሊያርም ነው፤ ከአላህ ወደ ነቢያት ያወረደውን እውነትን ስለሚያረጋግጥ “ሙሰዲቃን” مُصَدِّقًا ማለትም “አረጋጋጭ” ሲባል፤ የሰዎች ንግግር የገቡበትን በማረሙ ደግሞ “ሙሃይሚን” مُهَيْمِنًا ማለትም “አራሚ” correcter” ወይም “ተቆጣጣሪ”supervisor” የሚል ስም አለው፦
5፥48 *ወደ አንተም መጽሐፉን ከበፊቱ ያለውን መጽሐፍ አረጋጋጭ ና በእርሱ ላይ ተጠባባቂ ሲኾን በእውነት አወረድን፡፡ በመካከላቸውም አላህ ባወረደው ሕግ ፍረድ*፡፡ وَأَنزَلْنَآ إِلَيْكَ ٱلْكِتَٰبَ بِٱلْحَقِّ مُصَدِّقًۭا لِّمَا بَيْنَ يَدَيْهِ مِنَ ٱلْكِتَٰبِ وَمُهَيْمِنًا عَلَيْهِ ۖ فَٱحْكُم بَيْنَهُم بِمَآ أَنزَلَ ٱللَّهُ

ከዐቃቤ እሥልምና ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
የሙዚቃ መሣሪያ

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ፥ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።

31፥6 ከሰዎችም ያለ ዕውቀት ሆኖ ከአላህ መንገድ ሊያሳስትና ማላገጫ አድርጎ ሊይዛት *”አታላይ ወሬን የሚገዛ አለ”*፡፡ እነዚያ ለእነርሱ አዋራጅ ቅጣት አላቸው፡፡ وَمِنَ النَّاسِ مَن يَشْتَرِي لَهْوَ الْحَدِيثِ لِيُضِلَّ عَن سَبِيلِ اللَّهِ بِغَيْرِ عِلْمٍ وَيَتَّخِذَهَا هُزُوًا ۚ أُولَـٰئِكَ لَهُمْ عَذَابٌ مُّهِينٌ

መልእክት በመልካም ንግግር ግጥም አድርጎ ለአገር፣ ለባልና ሚስት፣ ለወላጅ ማቅረብ እና ስንኝ መሰኘት ይቻላል። ነገር ግን መልእክት በመጥፎ ንግግር ግጥም አድርጎ ለአገር፣ ለባልና ሚስት፣ ለወላጅ ማቅረብ እና ስንኝ መሰኘት ከግብረገብ ውጪ ነው። ታዲያ ዘፈንሳ? አዎ ዘፈን በሙዚቃ እና በመሳሪያ የታጀቡ እንጉርጉሮ ነው፥ ዘፈን ሙዚቃ፣ የሙዚቃ መሳሪያ እና እንጉርጉሮ የታጀበት ስለሆነ ከሸይጧን ነው፦
31፥6 ከሰዎችም ያለ ዕውቀት ሆኖ ከአላህ መንገድ ሊያሳስትና ማላገጫ አድርጎ ሊይዛት *”አታላይ ወሬን የሚገዛ አለ”*፡፡ እነዚያ ለእነርሱ አዋራጅ ቅጣት አላቸው፡፡ وَمِنَ النَّاسِ مَن يَشْتَرِي لَهْوَ الْحَدِيثِ لِيُضِلَّ عَن سَبِيلِ اللَّهِ بِغَيْرِ عِلْمٍ وَيَتَّخِذَهَا هُزُوًا ۚ أُولَـٰئِكَ لَهُمْ عَذَابٌ مُّهِينٌ
ተፍሢሩል ኢብኑ ከሲር 31፥6
“ኢብኑ መሥዑድ እንደተናገረው፦ *”ከሰዎችም ከአላህ መንገድ ሊያሳስት ማላገጫ አድርጎ ሊይዛት አታላይ ወሬን የሚገዛ አለ” የሚለው ወሏሂ እርሱ “ዘፈን” ነው”*። كما قال ابن مسعود في قوله تعالى : ( ومن الناس من يشتري لهو الحديث ) قال : هو – والله – الغناء .

“ለህወል ሐዲስ” لَهْوَ الْحَدِيث ማለትም “አታላይ ወሬ” ማለት ሲሆን “ጊናእ” ነው፥ “ጊናእ” غِنَاء የሚለው ቃል “ገና” غَنَّى‎ ማለትም “ዘፈነ” ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን “ዘፈን” ማለት ነው። አምላካችን አላህ ኢብሊሥ የሚከተሉትን በድምጹ እንደሚያታልላቸው ተናግሯል። ይህም ድምጹ መደበሪያ፣ ዘፈን፣ ላግጣ እና ስላቅ ነው፦
17፥64 *ከእነርሱ የቻልከውንም ሰው በድምጽህ አታል*፡፡ وَاسْتَفْزِزْ مَنِ اسْتَطَعْتَ مِنْهُم بِصَوْتِكَ
ተፍሢሩል ኢብኑ ከሲር 17፥64
*”ከእነርሱ የቻልከውንም ሰው በድምጽህ አታል” የተባለው እርሱ ዘፈን ነው፥ ሙጃሒድም አለ፦ “ድምጽ የተባለው መደበሪያ፣ ዘፈን፣ ላግጣና ስላቅ ነው”*። واستفزز من استطعت منهم بصوتك قيل هو الغناء قال مجاهد باللهو والغناء أي استخفهم بذلك

"ሐላል” حَلَال ማለት “የተፈቀደ” ማለት ሲሆን “ሐራም” حَرَام ማለት “የተከለከለ” ማለት ነው። ዝሙት እና አስካሪ መጠጥ ሐራም እንደሆነ ሁሉ ሙዚቃም ከዝሙት እና ከአስካሪ መጠጥ ጋር ተያይዞ ክልክል መሆኑ በነቢያችን”ﷺ” ሐዲስ ተነግሯል፦
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 74, ሐዲስ 16
አቡ ዐሚር ወይም አቡ ማሊኩል አሽዐሪይ እንደተረከው፦ “ወሏሂ አልዋሸውም! ነቢዩ”ﷺ” እንዲህ ሲሉ ሰምቷል፦ *”ከኡመቴ ውስጥ ጥቂት ሰዎች ለራሳቸው ዝሙትን፣ ሐር ልብስን፣ አስካሪ መጠጥን እና የሙዚቃ መሣሪያ ሐላል የሚያደርጉ ይሆናሉ”*። قَالَ حَدَّثَنِي أَبُو عَامِرٍ ـ أَوْ أَبُو مَالِكٍ ـ الأَشْعَرِيُّ وَاللَّهِ مَا كَذَبَنِي سَمِعَ النَّبِيَّ صلى الله عليه وسلم يَقُولُ “‏ لَيَكُونَنَّ مِنْ أُمَّتِي أَقْوَامٌ يَسْتَحِلُّونَ الْحِرَ وَالْحَرِيرَ وَالْخَمْرَ وَالْمَعَازِفَ

አሏህ በሙዚቃ መሣሪያ የሚነሽዱትን ሰዎች ሂዳያህ ይስጣቸው! አሚን።

ከዐቃቤ አሥልምና ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
ዕንቍጣጣሽ

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ፥ እጅግ በጣም አዛኛ በሆነው፡፡

5፥77 «እናንተ የመጽሐፉ ባለቤቶች ሆይ! በሃይማኖታችሁ ከእውነት ሌላ የኾነን ማለፍ ወሰንን አትለፉ፡፡ በፊትም በእርግጥ የተሳሳቱትንና ከቀጥተኛው መንገድም አሁን የተሳሳቱን ሕዝቦች ከንቱ ዝንባሌዎች አትከተሉ» በላቸው፡፡ قُلْ يَا أَهْلَ الْكِتَابِ لَا تَغْلُوا فِي دِينِكُمْ غَيْرَ الْحَقِّ وَلَا تَتَّبِعُوا أَهْوَاءَ قَوْمٍ قَدْ ضَلُّوا مِن قَبْلُ وَأَضَلُّوا كَثِيرًا وَضَلُّوا عَن سَوَاءِ السَّبِيلِ

“ጳጉሜ” የሚለው ቃል “ኤጳጉሚኖስ” ἐπαγόμενοι ከሚለው ከግሪክ ቃል የተገኘ ሲሆን ትርጉሙ “ተጨማሪ” ወይም “የተጨመረ” ማለት ነው፥ ጳጉሜ የወር ስም ሲሆን በነባሮች 12 ወራት ላይ የተጨመረ 13ኛ ወር ነው። ይህም ወር በነሐሴ እና በመስከረም መካከል የሚገኝ የመጨረሻው ወር ሲሆን ጳጉሜ በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር በዘመነ-ሉቃስ ስድስት ቀናት ሲኖሩር በዘመነ-ዮሐንስ ወይም በዘመነ-ማቴዎስ አሊያም በዘመነ -ማርቆስ አምስት ቀናት ይሆናል።
ልብ በሉ ይህ ወር ከግሪክ ሄለኒዝም ጊዜ ከአሌክሳንድርያ ወደ ኢትዮጵያ የገባ እንጂ በዕብራውያን አቆጣጠር ወራት 12 ብቻ ነው። አምላካችን አሏህም የወሮች ቁጥር በጥብቁ ሰሌዳ ሰማያትንና ምድርን በፈጠረበት ቀን አሥራ ሁለት ወር ነው፦
9፥36 አላህ ዘንድ የወሮች ቁጥር፤ በአላህ መጽሐፍ ዉስጥ ሰማያትንና ምድርን በፈጠረበት ቀን አሥራ ሁለት ወር ነው። إِنَّ عِدَّةَ ٱلشُّهُورِ عِندَ ٱللَّهِ ٱثْنَا عَشَرَ شَهْرًۭا فِى كِتَٰبِ ٱللَّهِ يَوْمَ خَلَقَ ٱلسَّمَٰوَٰتِ وَٱلْأَرْضَ

ይህ የሚያሳየው የኢትዮጵያው ዘመን መለወጫ በልምድ ከግሪክ የመጣ ሰርጎገብ እንጂ አገር በቀል አይደለም፥ ከዚያም ባሻገር መለኮታዊ ትእዛዝ ያለው ሳይሆን ሰው ሠራሽ ቢድዓ ነው። ዓመተ-ምህረትን ያማከለ ዘመነ-ሉቃስ፣ ዘመነ-ዮሐንስ፣ ዘመነ-ማቴዎስ እና ዘመነ -ማርቆስ ሰው ሠራሽ ትምህርት እና ክርስትናዊ ይዘት ያለው ነው። በዛ ላይ የባዕድ አምልኮ የሚፈፀምበት ቀን ነው፥ በጳጉሜ ቀናት ማልዶ የወጣ ሰው እንዲራመዳቸው ታስቦ በጎረቤት መተላለፊያ እና ህዝብ በሚያዘወትራቸው መንገዶች ላይ ፍየሎች፣ ዶሮዎች፣ ድመቶች፣ ጥንቸሎች ወዘተ ታርደው ይጣላሉ። በደም የተነከሩ ሳንቲሞች፣ ብሮች፣ ጌጣ-ጌጦች እና የተለያዩ ቁሳቁሶች እዚህም እዚያም ወድቀው ይታያሉ፥ ይህ ቀን ሲያልቅ የቀኑ መጨረሻ ተጓግቶ ስለሚመጣ “ዕንቍ” ተባለ። የሚያመጣው ጣጣና መዘዝ ደግሞ “ጣጣሽ” ተባለ፥ በጥቅሉ “ዕንቍ-ጣጣሽ” ተባለ። ጥንቆላና ድግምት ከትልቁ ሽርክ የሚመደቡ የአሏህን ሐቅ የሚነካ ትልቅ በደል ነው።
ዕንቍጣጣሽን ማክበር አቆጣጠሩ አገራዊ ሳይሆን እምነታዊ መሠረት ያለው ሲሆን ከእርሱ ጋር የተያያዙት ባዕድ አምልኮ አስበን ከዚህ ሰው ሠራሽ በዓል እራሳችንን እንጠብቅ።
እናንተ ክርስቲያኖች ሆይ! በሃይማኖታችሁ ከእውነት ሌላ የኾነን ማለፍ ወሰንን አትለፉ! በፊትም በእርግጥ የተሳሳቱትን እና ከቀጥተኛው መንገድም አሁን የተሳሳቱን ሕዝቦች ከንቱ ዝንባሌዎች አትከተሉ፦
5፥77 «እናንተ የመጽሐፉ ባለቤቶች ሆይ! በሃይማኖታችሁ ከእውነት ሌላ የኾነን ማለፍ ወሰንን አትለፉ፡፡ በፊትም በእርግጥ የተሳሳቱትንና ከቀጥተኛው መንገድም አሁን የተሳሳቱን ሕዝቦች ከንቱ ዝንባሌዎች አትከተሉ» በላቸው፡፡ قُلْ يَا أَهْلَ الْكِتَابِ لَا تَغْلُوا فِي دِينِكُمْ غَيْرَ الْحَقِّ وَلَا تَتَّبِعُوا أَهْوَاءَ قَوْمٍ قَدْ ضَلُّوا مِن قَبْلُ وَأَضَلُّوا كَثِيرًا وَضَلُّوا عَن سَوَاءِ السَّبِيلِ

ከዐቃቤ እሥልምና ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
ምልጃ የሌለበት ቀን

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ፥ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

2፥254 እናንተ ያመናችሁ ሆይ! በእርሱ ውስጥ ቤዛ፣ ወዳጅነትም፣ ምልጃም የሌለበት ቀን ከመምጣቱ በፊት ከሰጠናችሁ ነገር ለግሱ፡፡ ከሓዲዎችም በዳዮቹ እነርሱ ናቸው፡፡ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا أَنفِقُوا مِمَّا رَزَقْنَاكُم مِّن قَبْلِ أَن يَأْتِيَ يَوْمٌ لَّا بَيْعٌ فِيهِ وَلَا خُلَّةٌ وَلَا شَفَاعَةٌ ۗ وَالْكَافِرُونَ هُمُ الظَّالِمُونَ

"ምልጃ" ሥስት ማንነቶችን ያቅፋል፥ እነርሱም፦
፨አንደኛው የሚማለደው ተማላጅ፣
፨ሁለተኛው የሚማልደው አማላጅ እና
፨ሦስተኛ የሚማለድለት ተመላጅ ናቸው።
አሏህ የሁሉም ነገር ፈጣሪና አስተናባሪ በመሆኑ የሚማለድ ተማላጅ ነው፥ በአሏህ ፈቃድ የሚያማልዱት አማላጆች ደግሞ መላእክት፣ ነቢያት እና ሰማዕታት ናቸው፦
2፥255 ያ እርሱ ዘንድ በፈቃዱ ቢኾን እንጅ የሚያማልድ ማነው? مَن ذَا الَّذِي يَشْفَعُ عِندَهُ إِلَّا بِإِذْنِهِ
21፥28 በፊታቸው ያለውንና በኋላቸው ያለውንም ሁሉ ያውቃል፡፡ ለወደደውም ሰው እንጅ ለሌላው አያማልዱም፡፡ እነርሱም እርሱን ከመፍራታቸው የተነሳ ተጨናቂዎች ናቸው፡፡ يَعْلَمُ مَا بَيْنَ أَيْدِيهِمْ وَمَا خَلْفَهُمْ وَلَا يَشْفَعُونَ إِلَّا لِمَنِ ارْتَضَىٰ وَهُم مِّنْ خَشْيَتِهِ مُشْفِقُونَ

"ለወደደውም ሰው እንጅ ለሌላው አያማልዱም" የሚለው ይሰመርበት! ዐውደ ንባቡ ስለ መላእክት እያወራ እንደሆነ አንባቢ ልብ ይለዋል። የሚማለድላቸው ተመላጆች ደግሞ አሏህ ዘንድ ቃል ኪዳን የያዙት አማንያን ናቸው፦
34፥23 ምልጃም እርሱ ለፈቀደለት ሰው ብቻ ቢሆን እንጂ እርሱ ዘንድ ምንም አትጠቅምም*፡፡ وَلَا تَنفَعُ الشَّفَاعَةُ عِندَهُ إِلَّا لِمَنْ أَذِنَ لَهُ
19፥87 *አልረሕማን ዘንድ ቃል ኪዳንን የያዘ ሰው ቢኾን እንጂ ማማለድን አይችሉም*፡፡ لَّا يَمْلِكُونَ الشَّفَاعَةَ إِلَّا مَنِ اتَّخَذَ عِندَ الرَّحْمَـٰنِ عَهْدًا
20፥109 በዚያ ቀን ለእርሱ አልረሕማን የፈቀደለትን እና ለእርሱም ቃልን የወደደለትን ሰው ቢኾን እንጅ ምልጃ አንድንም አትጠቅምም፡፡ يَوْمَئِذٍ لَّا تَنفَعُ الشَّفَاعَةُ إِلَّا مَنْ أَذِنَ لَهُ الرَّحْمَـٰنُ وَرَضِيَ لَهُ قَوْلًا

"በዚያ ቀን" የሚለው የፍርዱ ቀን ሲሆን በዚያን ቀን አሏህ የፈቀደላቸው መላእክት፣ ነቢያት እና ሰማዕታት ለምዕመናን ያማልዳሉ። ነገር ግን ለኩፋሮች ምንም ወዳጅ እና ተሰሚ አማላጅ የላቸውም፦
40፥18 ለበዳዮች ምንም ወዳጅ እና ተሰሚ አማላጅ የላቸውም፡፡ مَا لِلظَّالِمِينَ مِنْ حَمِيمٍ وَلَا شَفِيعٍ يُطَاع
2፥254 እናንተ ያመናችሁ ሆይ! በእርሱ ውስጥ ቤዛ፣ ወዳጅነትም፣ ምልጃም የሌለበት ቀን ከመምጣቱ በፊት ከሰጠናችሁ ነገር ለግሱ፡፡ ከሓዲዎችም በዳዮቹ እነርሱ ናቸው፡፡ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا أَنفِقُوا مِمَّا رَزَقْنَاكُم مِّن قَبْلِ أَن يَأْتِيَ يَوْمٌ لَّا بَيْعٌ فِيهِ وَلَا خُلَّةٌ وَلَا شَفَاعَةٌ ۗ وَالْكَافِرُونَ هُمُ الظَّالِمُونَ

"ቤዛ፣ ወዳጅነትም፣ ምልጃም የሌለበት ቀን" የፍርዱ ቀን ሲሆን ቤዛ፣ ወዳጅነትም፣ ምልጃም የሌለው ለኩፋሮች ስለሆነ ዐውዱ ላይ "ከሓዲዎችም በዳዮቹ እነርሱ ናቸው" በማለት ይናገራል። ያ የፍርዱ ቀን እነርሱም ከአሏህ እርዳታ የማይረዱበትን እና ምልጃን የማይቀበሉባት ቀን ነው፦
2፥48 ነፍስም ከነፍስ ምንንም የማትመነዳበትን፣ ከእርሷም ምልጃን የማይቀበሉባትን፣ ከእርሷም ቤዛ የማይያዝበትን፣ እነርሱም የማይረዱበትን ቀን ተጠንቀቁ፡፡ وَاتَّقُوا يَوْمًا لَّا تَجْزِي نَفْسٌ عَن نَّفْسٍ شَيْئًا وَلَا يُقْبَلُ مِنْهَا شَفَاعَةٌ وَلَا يُؤْخَذُ مِنْهَا عَدْلٌ وَلَا هُمْ يُنصَرُونَ

"የማይቀበሉ" ተብሎ በሦስተኛ መደብ በግስ መደብ የተጠቀሱት እና "እነርሱ" ተብሎ በሦስተኛ መደብ በስም መደብ የተጠቀሱት በዳዮቹ ከሓዲዎች እንጂ ምእመናንን አይጨምርም፥ በፍርዱ ቀን አሏህ የፈቀደለትን እና ለእርሱም ቃልን የወደደለትን ሙእሚን ቢኾን እንጅ ለከሓዲ ምልጃ አንድንም አትጠቅምም። ኩፋሮች የትንሳኤ ቀን፦ "በሰቀር ውስጥ ምን አገባችሁ? ተብለው ሲጠየቁ፦ "ከሰጋጆቹ አልነበርንም፣ ለድኾችም የምናበላ አልነበርንም፣ ከዘባራቂዎቹም ጋር እንዘባርቅ ነበርን፣ በፍርዱ ቀንም እናስተባብል ነበርን" ይላሉ። የአማላጆችም ምልጃ አትጠቅማቸውም፦
74፥48 የአማላጆችም ምልጃ አትጠቅማቸውም፡፡ فَمَا تَنفَعُهُمْ شَفَاعَةُ الشَّافِعِينَ

"ወዳጅነትም የሌለበት ቀን" የተባለው አሁንም ለኩፋሮች እንጂ ለሙእሚን በፍጹም አይደለም። "ሑላህ" خُلَّة ማለት "ወዳጅነት" ማለት ሲሆን "ኻሊል" خَلِيل ማለት ደግሞ "ወዳጅ" ማለት ነው፥ በዚያ ቀን ኩፋሮች አንዱ ለሌላው ጠላት ነው፦
43፥67 ወዳጆች በዚያ ቀን ከፊላቸው ለከፊሉ ጠላት ነው፡፡ አላህን ፈሪዎች ብቻ ሲቀሩ፡፡ الْأَخِلَّاءُ يَوْمَئِذٍ بَعْضُهُمْ لِبَعْضٍ عَدُوٌّ إِلَّا الْمُتَّقِينَ

"ወዳጆች" ለሚለው የገባው ቃል "አኺላእ" أَخِلَّاء ሲሆን "ኻሊል" خَلِيل ለሚለው ብዙ ቁጥር ነው፥ "አላህን ፈሪዎች ብቻ ሲቀሩ" የሚለው ይሰመርበት! አሏህን ፈሪዎች ምእመናንማ ከእነዚያ አላህ በእነርሱ ላይ ከለገሳቸው ከነቢያት፣ ከጻድቃንም፣ ከሰማዕታትም፣ ከመልካሞቹ ጋር ይወዳጃሉ፡፡ የእነዚያም ወዳጅነት አማረ፦
4፥69 አላህን እና መልክተኛውንም የሚታዘዝ ሰው እነዚያ ከእነዚያ አላህ በእነርሱ ላይ ከለገሳቸው ከነቢያት፣ ከጻድቃንም፣ ከሰማዕታትም፣ ከመልካሞቹ ጋር ይኾናሉ፡፡ የእነዚያም ጓደኝነት አማረ፡፡ وَمَن يُطِعِ اللَّهَ وَالرَّسُولَ فَأُولَـٰئِكَ مَعَ الَّذِينَ أَنْعَمَ اللَّهُ عَلَيْهِم مِّنَ النَّبِيِّينَ وَالصِّدِّيقِينَ وَالشُّهَدَاءِ وَالصَّالِحِينَ ۚ وَحَسُنَ أُولَـٰئِكَ رَفِيقًا

ስለዚህ "ምልጃም የሌለበት ቀን" የተባለው "ወዳጅነትም የሌለበት ቀን" በተባለበት ዐውድ ከሆነ እና ለምእመናን ምልጃ ሆነ ወዳጅነት ካላቸው ምልጃ እና ወዳጅነት የሌለበት ቀን ለኩፋሮች ነው፥ የፍርዱ ቀን ለኩፋሮች ቤዛ የሌለበት ቀን ነው። ሙጅሪም ከዚያ ቀን ስቃይ ነፍሱን በልጆቹ ሊበዥ ይመኛል፥ ቅሉ ግን ለእነርሱ ቤዛ የሌለበት ቀን ስለሆነ ከእሳት ቅጣት አይቤዥም፦
70፥11 ዘመዶቻቸውን ያዩዋቸዋል፡፡ አመጸኛው ከዚያ ቀን ስቃይ ነፍሱን በልጆቹ ሊበዥ ይመኛል፡፡ يُبَصَّرُونَهُمْ ۚ يَوَدُّ الْمُجْرِمُ لَوْ يَفْتَدِي مِنْ عَذَابِ يَوْمِئِذٍ بِبَنِيهِ
ምእመናን ግን በጀነት ስላሉ ከዚያ ቀን ስቃይ ተቤዥተዋል። ከእነዚያ ከካዱት ግን ቤዛ አይወሰድም፥ ለእነዚያም ለበደሉት ከሐድያን በምድር ያለው ሁሉ መላውም ከእርሱ ጋር መሰሉም ቢኖራቸው ኖሮ በትንሣኤ ቀን ከቅጣቱ ክፋት የተነሳ በእርሱ ነፍሶቻቸውን በተቤዡበት ነበር፦
57፥15 «ዛሬም ከእናንተ ቤዛ አይወስድም፥ ከእነዚያ ከካዱትም አይወሰድም፡፡ መኖሪያችሁ እሳት ናት፥ እርሷ ተገቢያችሁ ናት፡፡ ምን ትከፋም መመለሻ!» ይሏቸዋል፡፡ فَالْيَوْمَ لَا يُؤْخَذُ مِنكُمْ فِدْيَةٌ وَلَا مِنَ الَّذِينَ كَفَرُوا ۚ مَأْوَاكُمُ النَّارُ ۖ هِيَ مَوْلَاكُمْ ۖ وَبِئْسَ الْمَصِيرُ
39፥47 ለእነዚያም ለበደሉት በምድር ያለው ሁሉ መላውም ከእርሱ ጋር መሰሉም ቢኖራቸው ኖሮ በትንሣኤ ቀን ከቅጣቱ ክፋት የተነሳ በእርሱ ነፍሶቻቸውን በተቤዡበት ነበር፡፡ وَلَوْ أَنَّ لِلَّذِينَ ظَلَمُوا مَا فِي الْأَرْضِ جَمِيعًا وَمِثْلَهُ مَعَهُ لَافْتَدَوْا بِهِ مِن سُوءِ الْعَذَابِ يَوْمَ الْقِيَامَةِ

ይህቺ የካፊር ነፍስ ከነፍስ ምንንም ቤዛ የማይያዝበትን ቀን ተጠንቀቁ! እንግዲህ ቤዛ፣ ምልጃ፣ ወዳጅነት የሌለበት ቀን የተባለው ከዐውድ እና አጠቃላይ ከቁርኣን መልእክት አንጻር ለከሓዲ በዳዮች ብቻ ነው። የፍርዱ ቀን ሁሉም ነቢይ ለኡመቱ ወደ አላህ ምልጃ ያረጋል፥ የነቢያችን”ﷺ” ምልጃ በትንሳኤ ቀን የሚያገኘው ከልቡ ወይም ከነፍሱ፦ “ከአሏህ በስተቀር በእውነት የሚመለክ አምላክ የለም” ያለ ሰው ነው፦
ኢማም ሙሥሊም መጽሐፍ 1, ሐዲስ 402
አነሥ ኢብኑ ማሊክ እንደዘገበው የአሏህ ነቢይም”ﷺ” እንዲህ አሉ፦ "ሁሉም ነቢይ ለኡመቱ ወደ አላህ ጸሎት ያረጋል፥ በትንሳኤ ቀን የእኔ ጸሎት ለኡመቴ ምልጃ ነው*። عَنْ قَتَادَةَ، حَدَّثَنَا أَنَسُ بْنُ مَالِكٍ، أَنَّ نَبِيَّ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم قَالَ ‏ “‏ لِكُلِّ نَبِيٍّ دَعْوَةٌ دَعَاهَا لأُمَّتِهِ وَإِنِّي اخْتَبَأْتُ دَعْوَتِي شَفَاعَةً لأُمَّتِي يَوْمَ الْقِيَامَةِ ‏”‏
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 3, ሐዲስ 41
አቢ ሁረይራ እንደተረከው፦ *”እኔም፦ የአሏህ መልእክተኛ”ﷺ” ሆይ! በትንሳኤ ቀን ማነው እድለኛ ሰው የእርስዎን ምልጃ የሚያገኘው? አልኩኝ፤ የአላህ መልእክተኛም”ﷺ”፦ “አቢ ሁረይራ ሆይ! ንግግር ለመማር የአንተን ቆይታ ዐውቃለው፤ እንደማስበው ስለዚህ ጉዳይ ከአንተ በፊት ማንም አልጠየቀኝም። በትንሳኤ ቀን የእኔን ምልጃ የሚያገኝ እድለኛ ሰው ከልቡ ወይም ከነፍሱ፦ “ከአሏህ በስተቀር በእውነት የሚመለክ አምላክ የለም” ያለ ነው"። عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ، أَنَّهُ قَالَ قِيلَ يَا رَسُولَ اللَّهِ، مَنْ أَسْعَدُ النَّاسِ بِشَفَاعَتِكَ يَوْمَ الْقِيَامَةِ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم ‏ “‏ لَقَدْ ظَنَنْتُ يَا أَبَا هُرَيْرَةَ أَنْ لاَ يَسْأَلَنِي عَنْ هَذَا الْحَدِيثِ أَحَدٌ أَوَّلُ مِنْكَ، لِمَا رَأَيْتُ مِنْ حِرْصِكَ عَلَى الْحَدِيثِ، أَسْعَدُ النَّاسِ بِشَفَاعَتِي يَوْمَ الْقِيَامَةِ مَنْ قَالَ لاَ إِلَهَ إِلاَّ اللَّهُ، خَالِصًا مِنْ قَلْبِهِ أَوْ نَفْسِهِ ‏”‌‏.‏

ከዐቃቤ እሥልምና ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
ሙሐረም

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ፥ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።

9፥36 የወሮች ቁጥር አላህ ዘንድ በአላህ መጽሐፍ ውስጥ ሰማያትን እና ምድርን በፈጠረበት ቀን አሥራ ሁለት ወር ነው፡፡ إِنَّ عِدَّةَ الشُّهُورِ عِندَ اللَّهِ اثْنَا عَشَرَ شَهْرًا فِي كِتَابِ اللَّهِ يَوْمَ خَلَقَ السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضَ

“ወር” የሚለው ቃል “ሸህር” شَهْر ሲሆን በቁርኣን 12 ውስጥ ጊዜ ተጠቅሷል፥ የሚያጅበው የወሮች ቁጥር አሏህ ዘንድ በአሏህ መጽሐፍ አሥራ ሁለት ወር ነው፦
9፥36 የወሮች ቁጥር አላህ ዘንድ በአላህ መጽሐፍ ውስጥ ሰማያትን እና ምድርን በፈጠረበት ቀን አሥራ ሁለት ወር ነው፡፡ إِنَّ عِدَّةَ الشُّهُورِ عِندَ اللَّهِ اثْنَا عَشَرَ شَهْرًا فِي كِتَابِ اللَّهِ يَوْمَ خَلَقَ السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضَ

ከእነዚህ አሥራ ሁለት ወራት አራቱ የተከበሩ ወሮች ናቸው፥ እነርሱም፦ 1ኛው ወር ሙሐረም፣ 7ኛው ወር ረጀብ፣ 11ኛው ወር ዙል-ቀዕዳህ እና 12ኛው ወር ዙል-ሒጃህ ናቸው፦
9፥36 ከእነርሱ አራቱ የተከበሩ ናቸው፡፡ مِنْهَا أَرْبَعَةٌ حُرُمٌ
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 65 ሐዲስ 4662
አቡበከር”ረ.ዐ” እንደተረከው፦ ነቢዩም”ﷺ” አሉ፦ ”ዘመን አላህ ሰማያትን እና ምድር በፈጠረበት ቀን የቀድሞ ሁኔታ ይመለሳል፥ አንድ ዓመት ኣሥራ ሁለት ወር ነው። ከእነርሱም አራቱ የተከበሩ ናቸው፥ ሦስቱ ተከታታይ ዙል-ቀዒዳህ፣ ዙል-ሒጃህ፣ ሙሐረም ናቸው፥ አራተኛው በጀማዱ-ሣኒ እና በሻዕባን መካከል ያለው ረጀብ ነው። عَنْ أَبِي بَكْرَةَ، عَنِ النَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم قَالَ ‏ “‏ إِنَّ الزَّمَانَ قَدِ اسْتَدَارَ كَهَيْئَتِهِ يَوْمَ خَلَقَ اللَّهُ السَّمَوَاتِ وَالأَرْضَ، السَّنَةُ اثْنَا عَشَرَ شَهْرًا مِنْهَا، أَرْبَعَةٌ حُرُمٌ، ثَلاَثٌ مُتَوَالِيَاتٌ، ذُو الْقَعْدَةِ وَذُو الْحِجَّةِ وَالْمُحَرَّمُ وَرَجَبُ مُضَرَ الَّذِي بَيْنَ جُمَادَى وَشَعْبَانَ

"ሙሐረም" مُحَرَّم የሚለው ቃል "ሐረመ" حَرَّمَ ማለትም "ቀደሰ" "አከበረ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "የተቀደሰ" "የተከበረ" ማለት ነው። ከአራቱ ወራት ሙሐረም ክብር ያለው የአሏህ ወር ነው፦
ጃሚዒ አት-ቲርሚዚይ መጽሐፍ 8 ሐዲስ 59
አቢ ሁረይራህ”ረ.ዐ” እንደተረከው፦ “የአሏህ መልእክተኛ”ﷺ” እንዲህ ብለዋል፡- ”ከረመዷን ቀጥሎ ከጾሞች ሁሉ በላጩ የአሏህ ወር የሆነው ሙሐረም ነው። عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ، قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم ‏ “‏ أَفْضَلُ الصِّيَامِ بَعْدَ صِيَامِ شَهْرِ رَمَضَانَ شَهْرُ اللَّهِ الْمُحَرَّم

"ተቅዊም" تَّقْوِيم ማለት "የዘመን አቆጣጠር" ማለት ሲሆን ተቅዊም በሁለት ዐበይት ክፍል ይከፈላል፥ አንደኛው "ተቅዊሙ አሽ-ሸምሢያህ" تَّقْوِيم الشَمْسِيَّة ሲሆን ተቅዊሙ አሽ-ሸምሢያህ 365 ቀናት የያዘ የፀሐይ አቆጣጠር”solar calender” ነው። ሁለተኛው ደግሞ "ተቅዊሙል ቀመርያህ" تَّقْوِيم القَمَرِيَّة ሲሆን ተቅዊሙል ቀመርያ 354 ቀናትን የያዘ የጨረቃ አቆጣጠር”lunar calender” ነው። አምላካችን አሏህ ፀሐይ እና ጨረቃ የዓመታትን ቁጥርና ሒሳብን ማወቂያ እና መስፈሪያዎችን እንዳደረገ ተናግሯል፦
10፥5 እርሱ ያ ፀሐይን አንጻባራቂ ጨረቃንም አብሪ ያደረገ ነው፡፡ የዓመታትን ቁጥር እና ሒሳብን ታውቁ ዘንድም ለእርሱ መስፈሪያዎችን የለካ ነው፡፡ هُوَ الَّذِي جَعَلَ الشَّمْسَ ضِيَاءً وَالْقَمَرَ نُورًا وَقَدَّرَهُ مَنَازِلَ لِتَعْلَمُوا عَدَدَ السِّنِينَ وَالْحِسَابَ

በጨረቃ አቆጣጠር አዲስ ጨረቃ ሲታይ አዲሱ ወር ሙሐረም የወሮች መጀመሪያ ሆኖ ይጀምራል፥ ሙሐረም "የአሏህ ወር" የተባለበት አሏህ ሰማያትንና ምድርን በፈጠረበት ቀን አንድ ተብሎ ወር የተጀመረበት ወር ስለሆነ ነው። አሏህ ሰማያትን እና ምድርን በፈጠረበት ቀን አሥራ ሁለት ወር ሲሆን አሏህ ሰማያትን እና ምድርን በመካከላቸው ያለውንም ሁሉ በስድስት ቀናት ውስጥ በእርግጥ ፈጥሯል፦
50፥38 ሰማያትን እና ምድርን በመካከላቸው ያለውንም ሁሉ በስድስት ቀናት ውስጥ በእርግጥ ፈጠርን፡፡ وَلَقَدْ خَلَقْنَا السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضَ وَمَا بَيْنَهُمَا فِي سِتَّةِ أَيَّامٍ

በግሪክ ኮይኔ "ሄክሳ" ἑξα ወይም "ሔክስ" ἕξ ማለት "ስድስት" ማለት ሲሆን "ሔሜራ" ἡμέρᾱ ወይም "ሄሜሮስ" ἥμερος ደግሞ "ቀን" ማለት ነው፥ በጥቅሉ "አክሲማሮስ" ማለት "ስድስት ቀናት" ማለት ሲሆን አክሲማሮስ ስለ ስድስት ቀናት አፈጣጠር የሚያወራው ትምህርት ነው። በ4ኛው ክፍለ-ዘመን ከ 367-403 ድኅረ-ልደት የቆጵሮስ ኤጲጵ ቆጶስ የነበረው ኤጲፋንዮስ ያዘጋጀው መጽሐፍ እራሱ አክሲማሮስ ይባላል።
ከ 180-222 ድኅረ-ልደት ድረስ ለ 42 ዓመት የአሌክሳንድርያ ፓትርያርክ የነበረው ድሜጥሮስ የቀመረው የዘመን ቀመር “አቡሻኽር” ወይም “ባሕረ-ሐሳብ” ሲባል በዚህ የዘመን ቀመር ላይ ስለ “አዕዋዳት” ይናገራል፥ “አዕዋድ” ማለት “ዖደ” ማለትም “ዞረ” ከሚል የግዕዝ ቃል የተገኘ ሲሆን “ዙረት” ማለት ሲሆን በየጊዜው እየዞረ የሚመጣ ማለት ነው። የፀሐይ አቆጣጠር የሚዞረው 365 ቀናት የያዘው ሲሆን የጨረቃ አቆጣጠር የሚዞረው ደግሞ 354 ቀናት የያዘው ነው፥ የጨረቃ አቆጣጠር 11 ቀናት በመዘግየት ከፀሐይ አቆጣጠር ሲዘገይ "ሙሐረም" ወደ ኃላ ሲሆን ከፊት ለፊቱ ያለው ስሌት "መስከረም" ይሆናል። እሩቅ ሳንሄድ የሙሐረም አዲስ ጨረቃ ታይቶ አሥረኛው ቀን ዓሹራእ ነው፦
ኢማም ሙሥሊም መጽሐፍ 13, ሐዲስ 170
አል-ሐከም ኢብኑል አዕረኽ እንደተረከው፦ “ወደ ኢብኑ ዐባሥ”ረ.ዐ” ስሄድ እርሱ በዘምዘም ምንጭ አቅራቢያ በልብሱ ተቀምጦ ነበር፤ እኔም ለእርሱ፦ ” ስለ ዓሹራእ ጾም ንገረኝ! አልኩት፤ እርሱም፦ “የሙሐረም አዲስ ጨረቃ ስታይ ቁጠር፥ በዘጠነኛው ቀን ጾም መሆኑን አጢን” አለኝ። እኔም ለእርሱ፦ “ስለዚህ የአላህ መልእክተኛ”ﷺ” ያጤኑት ነበር? አልኩት፤ እርሱም፦ “አዎ” አለኝ። عَنِ الْحَكَمِ بْنِ الأَعْرَجِ، قَالَ انْتَهَيْتُ إِلَى ابْنِ عَبَّاسٍ – رضى الله عنهما – وَهُوَ مُتَوَسِّدٌ رِدَاءَهُ فِي زَمْزَمَ فَقُلْتُ لَهُ أَخْبِرْنِي عَنْ صَوْمِ عَاشُورَاءَ ‏.‏ فَقَالَ إِذَا رَأَيْتَ هِلاَلَ الْمُحَرَّمِ فَاعْدُدْ وَأَصْبِحْ يَوْمَ التَّاسِعِ صَائِمًا ‏.‏ قُلْتُ هَكَذَا كَانَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم يَصُومُهُ قَالَ نَعَمْ
“ዓሹራእ” عَاشُورَاء‎ የሚለው ቃል “ዐሽር” عَشْرٍ ማለትም “አሥር” ከሚል ቃል የመጣ ሲሆን “አሥረኛ” ማለት ነው። የአይሁድ ሰባተኛ ወር አሥረኛው ቀን ዓሹራእ ነው፦
ዘሌዋውያን 16፥30 በሰባተኛው ወር ከወሩም በአሥረኛው ቀን ራሳችሁን አስጨንቋት፥ የአገር ልጅም በእናንተ መካከል የተቀመጠም እንግዳ ሥራን ሁሉ አትሥሩበት።

በአይሁድ የመጀመሪያው ወር ኒሳን ማለትም አቢብ ወር ሲሆን ከዚያ ሰባተኛው ወር ቲሽሬ ነው፦
ዘጸአት 12፥2 ይህ ወር የወሮች መጀመሪያ ይሁናችሁ፤ የዓመቱም መጀመሪያ ወር ይሁናችሁ።

ከኒሳን ወር ሰባት ወር ስንቆጥር "ቲሽሬ" የሚባለው ወር መስከረም ነው፥ "ቲሽሬ" תִּשְׁרִי‎ ማለት "መጀመርያ" ማለት ነው። አይሁዳውያን ይህንን ወር "ሮሽ ሀ ሸናህ" רֹאשׁ הַשָּׁנָה ማለትም "የዓመቱ ርእስ፣ ጅማሮ፣ ራስ፣ አውራ" በማለት አዲስ ዓመት ይጀምራሉ። "ቲሽሬ" ወይም "ሮሽ ሀ ሸናህ" በፀሐይ አቆጣጠር "መስከረም" እና በጨረቃ አቆጣጠር "ሙሐረም" መሆኑን ፍንትው እና ቁልጭ አርጎ ያሳያል። "መስከረም" የሚለው ቃል እራሱ በትክክሉ "መዝከር" እና "ዓም" ከሚል ሁለት የግዕዝ ቃላት የተዋቀረ ሲሆን "የዓመቱ መታሰቢያ" ማለት ነው። ይህ የአይሁዳውያን ሰባተኛ ወር "ኤታኒም" ተብሏል፦
1 ነገሥት 8፥2 የእስራኤልም ሰዎች ኤታኒም በሚባል በሰባተኛው ወር በበዓሉ ጊዜ ወደ ንጉሡ ወደ ሰሎሞን ተከማቹ።

"ኤታኒም" אֵיתָנִים ማለት "ጥንት" "መሠረት" ማለት ሲሆን ከአደም እስከ ሙሣ ድረስ ሲገለገሉበት የነበረ የወር መጀመሪያ እንደሆነ አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ ገፅ 248-249 ላይ ገልጸዋል።
በፀሐይ አቆጣጠር የወሩ መጀመሪያ መስከረም ስለሆነ የምሥራቅ ኦርቶዶክስ በሚባሉት በቁስጥንጥንያ ኦርቶዶክስ፣ በእስክንድርያ ኦርቶዶክስ፣ በአንጾኪያ ኦርቶዶክስ፣ በኢየሩሳሌም ኦርቶዶክስ፣ በሰርቢያ ኦርቶዶክስ፣ በሩሲያ ኦርቶዶክስ፣ በግሪክ ኦርቶዶክስ ወዘተ... ዘንድ መስከረም የመጀመሪያው ወር ነው። መስከረምን የመጀመሪያ ወር አርጎ የሚቆጥር የዘመን አቆጣጠር የባዛንታይን የዘመን አቆጣጠር"Byzantine calendar" ይባላል፥ የምሥራቅ ኦርቶዶክስ ከ 691-1728 ድኅረ ልደት የባዛንታይን የዘመን አቆጣጠር ትጠቀም ነበር።
ጥር ላይ የሚጀምረው የግሪጎርያን የዘመን አቆጣጠር "ጃንዋሪይ" ግን "ጃኑስ" የተባለው ጣዖት የተወለደበት ወር ሲሆን የሮማ ካቶሊክ ከጣዖታውያኑ ቀይጦ ያመጣው ሰርጎ ገብ ነው።
ምን አለፋችሁ መስከረምን የመጀመሪያ ወር መሠረት ተደርጎ የጨረቃ አቆጣጠር ብታሰሉት የሙሥሊሞች የመጀመሪያ ወር ሙሐረምን ታገኛላችሁ። ባይብል ደግሞ የጨረቃ አቆጣጠርን ዕውቅና ይሰጣል፦
መዝሙረ ዳዊት 104፥19 ጨረቃን ለጊዜዎች አደረገ።
መጽሐፈ ሲራክ 43÷6 ጨረቃም ለሁሉም የዘመን መለኪያ ናት።

በሰማይ ጠፈር ላይ ያሉት ትልቁ ብርሃን ጸሐይ እና ትንሹ ብርሃን ጨረቃ ለምልክቶች፣ ለዘመኖች፣ ለዕለታት እና ለዓመታት ምልክት እንደሆኑ ዘፍጥረት ይናገራል፦
ዘፍጥረት 1፥14 እግዚአብሔርም አለ፦ ቀንና ሌሊትን ይለዩ ዘንድ ብርሃናት በሰማይ ጠፈር ይሁኑ፤ ለምልክቶች ለዘመኖች ለዕለታት ለዓመታትም ይሁኑ፤
ዘፍጥረት 1፥16 እግዚአብሔርም ”ሁለት ታላላቆች ብርሃናትን አደረገ፤ ትልቁ ብርሃን በቀን እንዲሠለጥን፥ ትንሹም ብርሃን በሌሊት እንዲሰለጥን አደረገ።

በተረፈ የፕሮቴስታንት ትችት ሾላ በድፍኑ ትችት እንጂ ታሪካዊ ዳራ የሚያመጡበት አንዳችም ቁብ የላቸውም። እነርሱ ሰፈር፦ "ሙሐረም መሠረት የለውም ወይም ከፓጋን የተቀዳ ነው" ብሎ አቧራ ማስነሳት መናኛ ምክንያት ነው፥ ሳይቀመጡ እግር መዘርጋት ለመፈንገል ነው። የተሻለ የታሪክ ፍሰት ሳይኖር ኢሥላም ላይ መንፈቅፈቅና መነፋረቅ ቋ ያለ ጉፋያ እና እንጉልፋቶ ትችት ነው። ስለዚህ ለክርስቲያኖች ያለን ምክር፦ "አንብቡ! መርምሩ! ዕወቁ! ካነበባችሁ፣ ከመረመራችሁ እና ካወቃችሁ መዳረሻችሁ ኢሥላም ነው" የሚል ነው።

ከዐቃቤ እሥልምና ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
እሥልምና በቃላት ተጀምሮ በቃላት የሚያልቅ ሳይሆን በእለት እለት የምትኖረው ሕይወት ነው።

ከቀመስኩት ሕይወት ወሒድ
እንኳን አደረሳችሁ!

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ፥ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

59፥7 *መልክተኛውም የሰጣችሁን ማንኛውንም ነገር ያዙት፡፡ ከእርሱም የከለከላችሁን ነገር ተከልከሉ*፡፡ አላህንም ፍሩ፡፡ አላህ ቅጣተ ብርቱ ነውና وَمَآ ءَاتَىٰكُمُ ٱلرَّسُولُ فَخُذُوهُ وَمَا نَهَىٰكُمْ عَنْهُ فَٱنتَهُوا۟ ۚ وَٱتَّقُوا۟ ٱللَّهَ ۖ إِنَّ ٱللَّهَ شَدِيدُ ٱلْعِقَابِ ፡፡

“ዒድ” عِيد የሚለው ቃል “ዓደ” عَادَ ማለትም “ተመላለሰ” ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን “ምልሰት” ማለት ነው፥ ይህ “መደሰቻ” ወይም “በዓል” በየዓመቱ ስለሚመላለስ ይህንን ስያሜ አግኝቷል። ነቢያችን”ﷺ” የነገሩን ዓመታዊ በዓል ሁለት ብቻና ብቻ ናቸው፥ እነርሱም፦ ዒዱል ፊጥር እና ዒዱል አድሓ ናቸው፦
ሡነን አቢ ዳዉድ መጽሐፍ 2, ሐዲስ 745
አነሥ ኢብኑ ማሊክ እንደተረከው፦ *"የአላህ መልእክተኛም”ﷺ” መዲና ሲገቡ የመዲና ሠዎች የሚደሰቱባቸው ሁለት በዓላት እንዳሏቸው አወቁ። እርሳቸውም እነዚህ ሁለቱ ቀናት ምንድን ናቸው? በማለት ጠየቁ፤ ሰዎችም በጃሂሊያ ጊዜ እንጫወትባቸው የነበሩ በዓላት ናቸው አሏቸው። የአላህ መልእክተኛም”ﷺ”፦ “አላህ ከእነርሱ የተሻሉ ሁለት ዒዶችን ሠጥቷችኋል፤ እነርሱም፦ ዒዱል ፊጥር እና ዒዱል አድሓን" አሏቸው*። عَنْ أَنَسٍ، قَالَ قَدِمَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم الْمَدِينَةَ وَلَهُمْ يَوْمَانِ يَلْعَبُونَ فِيهِمَا فَقَالَ ‏”‏ مَا هَذَانِ الْيَوْمَانِ ‏”‏ ‏.‏ قَالُوا كُنَّا نَلْعَبُ فِيهِمَا فِي الْجَاهِلِيَّةِ ‏.‏ فَقَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم ‏”‏ إِنَّ اللَّهَ قَدْ أَبْدَلَكُمْ بِهِمَا خَيْرًا مِنْهُمَا يَوْمَ الأَضْحَى وَيَوْمَ الْفِطْرِ ‏”‏ ‏.‏
ጃምዒ አት-ቲርሚዚይ መጽሐፍ 8, ሐዲስ 121
ዓኢሻህ”ረ.ዐ.” እንደተረከችው የአላህ መልእክተኛም”ﷺ” እንዲህ አሉ፦ *“ዒዱል ፈጥር ሰዎች ጾም የሚፈቱበት ነው፥ ዒዱል አደሐ ደግሞ መስዋዕት የሚያቀርቡበት ቀን ነው"*። عَنْ عَائِشَةَ، قَالَتْ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم ‏ “‏ الْفِطْرُ يَوْمَ يُفْطِرُ النَّاسُ وَالأَضْحَى يَوْمَ يُضَحِّي النَّاسُ ‏”‏
ጃምዒ አት-ቲርሚዚይ መጽሐፍ 8, ሐዲስ 91
አቡ ሰዒደል ኹድሪይ እንደተረከው፦ *"የአላህ መልእክተኛም”ﷺ” በሁለቱ በአል በኢደል አደሐ እና ኢደል ፈጥር መጾም ከልክለዋል"*። عَنْ أَبِي سَعِيدٍ الْخُدْرِيِّ، قَالَ نَهَى رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم عَنْ صِيَامَيْنِ يَوْمِ الأَضْحَى وَيَوْمِ الْفِطْرِ ‏.

ማንኛውም መመሪያ ቁርአን እና የነቢያችን”ﷺ” ሐዲስ ላይ ይገኛል። አላህም፦ “መልክተኛውም የሰጣችሁን ማንኛውንም ነገር ያዙት! ከእርሱም የከለከላችሁን ነገር ተከልከሉ” ብሎናል፦
59፥7 *መልክተኛውም የሰጣችሁን ማንኛውንም ነገር ያዙት፡፡ ከእርሱም የከለከላችሁን ነገር ተከልከሉ*፡፡ አላህንም ፍሩ፡፡ አላህ ቅጣተ ብርቱ ነውና وَمَآ ءَاتَىٰكُمُ ٱلرَّسُولُ فَخُذُوهُ وَمَا نَهَىٰكُمْ عَنْهُ فَٱنتَهُوا۟ ۚ وَٱتَّقُوا۟ ٱللَّهَ ۖ إِنَّ ٱللَّهَ شَدِيدُ ٱلْعِقَابِ ፡፡
ኢማም ቡኻርይ : መጽሐፍ 53, ሐዲስ 7
ዓኢሻህ”ረ.ዐ.” እንደተረከችው የአላህ መልእክተኛም”ﷺ” እንዲህ አሉ፦ *"“ማንኛውም ሰው ከትእዛዛችን ያልሆነ አንድ ነገር ቢፈጥር ተቀባይነት የለውም"*። عَنْ عَائِشَةَ ـ رضى الله عنها ـ قَالَتْ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم ‏ “‏ مَنْ أَحْدَثَ فِي أَمْرِنَا هَذَا مَا لَيْسَ فِيهِ فَهُوَ رَدٌّ ‏”‌‏.‏

በፀሐይ አቆጣጠር መስከረም እንዲሁ በጨረቃ አቆጣጠር ሙሐረም አዲስ ዓመት እና የወር መጀመሪያ ነው። ቅሉ ግን እነዚህን ዘመን መለወጫ በዓል አርጎ በመያዝ፣ ገና እና ፋሲካ "እንኳን አደረሳችሁ" መባባል ሸሪዓዊ መሠረት የሌለው፣ ቀደምት ሠለፎች ያላደረጉት እና ቢድዓህ ነው።
“ሑክም” حُكْم የሚለው ቃል”ሐከመ” حَكَمَ ማለትም “ፈረደ” ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን ፍርድ” “ሕግ” "መርሕ" ማለት ነው፥ “አሕካም” أَحْكَام‎ ደግሞ የሑክም ብዙ ቁጥር ሲሆን “ሕግጋት” ማለት ነው። በኢሥላም አሕካም በአምስት ዋና ዋና ክፍል ሲከፈሉ፥ ከአምስቱ አንዱ "ሐላል" ነው። "ሐላል" حَلاَل ማለት "የተፈቀደ" ማለት ነው፦
16፥116 *"በአላህም ላይ ውሸትን ልትቀጣጥፉ ምላሶቻችሁ በሚመጥኑት ውሸት «ይህ የተፈቀደ ነው፥ ይህም እርም ነው» አትበሉ"*፡፡ وَلَا تَقُولُوا لِمَا تَصِفُ أَلْسِنَتُكُمُ الْكَذِبَ هَـٰذَا حَلَالٌ وَهَـٰذَا حَرَامٌ لِّتَفْتَرُوا عَلَى اللَّهِ الْكَذِبَ
እዚህ አንቀጽ ላይ “የተፈቀደ” ለሚለው የገባው ቃል “ሐላል” حَلاَل መሆኑ አንባቢ ልብ ይለዋል። አንድ ጉዳይ ሐላል ወይም ሐራም ማለት የሚችለው የዓለማቱ ጌታ አሏህ በነቢዩ”ﷺ” ብቻ እና ብቻ ነው፥ ሐላል የሆነ ጉዳይ ሆነ ሐራም የሆነ ጉዳይ በሸሪዓችን በግልጽ የተቀመጡት ብቻ ናቸው፦
7፥157 *"መልካም ነገሮችንም ለነርሱ ይፈቅድላቸዋል፥ መጥፎ ነገሮችንም በእነርሱ ላይ እርም ያደርግባቸዋል"*፡፡ وَيُحِلُّ لَهُمُ الطَّيِّبَاتِ وَيُحَرِّمُ عَلَيْهِمُ الْخَبَائِثَ
ሡነን አቢ ዳውድ መጽሐፍ 23, ሐዲስ 4
አን-ኑዕማን ኢብኑ በሺር እንደተረከው፦ “የአሏህ መልእክተኛም”ﷺ” እንዲህ አሉ፦ “ሐላል ግልጽ ነው፥ ሐራምም ግልጽ ነው። በሁለቱ መካከል ያለው ግን አጠራጣሪ ነገር ነው”። قَالَ سَمِعْتُ النُّعْمَانَ بْنَ بَشِيرٍ، – وَلاَ أَسْمَعُ أَحَدًا بَعْدَهُ يَقُولُ – سَمِعْتُ رَسُولَ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم يَقُولُ ‏”‏ إِنَّ الْحَلاَلَ بَيِّنٌ وَإِنَّ الْحَرَامَ بَيِّنٌ وَبَيْنَهُمَا أُمُورٌ مُشْتَبِهَاتٌ ‏”‏

አንድ ጉዳይ በግልጽ መፈቀዱ እና መከልከሉ ካልተገለጸ "ተፈቅዷል" "ተከልክሏል" ማለት የለብንም፥ ያልተፈቀደ እና ያልተከለከለ ነገር ጉዳይ አጠራጣሪ ነው፥ ተወዳጁ ነቢያችን"ﷺ" ደግሞ፦ "የሚያጠራጥርህን ትተህ ወደ ማያጠራጥርህ ሂድ! እውነት ያረጋጋል፥ ውሸት ግን ያጠራጥራል" ብለውናል፦
ጃምዒ አት-ቲርሚዚይ መጽሐፍ 37, ሐዲስ 2708
አቢል ሐውራእ አሥ-ሠዕዲይ እንደተረከው፦ "እኔ ለሐሠን ኢብኑ ዐሊይ፦ "ከአሏህ መልእክተኛም"ﷺ" ምን ሐፈዝክ? ብዬ አልኩኝ፥ እርሱም፦ "ከአሏህ መልእክተኛም"ﷺ" እንዲህ ሲሉ ሐፈዝኩኝ፦ *"የሚያጠራጥርህን ትተህ ወደ ማያጠራጥርህ ሂድ! እውነት ያረጋጋል፥ ውሸት ግን ያጠራጥራል"*። عَنْ أَبِي الْحَوْرَاءِ السَّعْدِيِّ، قَالَ قُلْتُ لِلْحَسَنِ بْنِ عَلِيٍّ مَا حَفِظْتَ مِنْ رَسُولِ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم قَالَ حَفِظْتُ مِنْ رَسُولِ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم ‏ "‏ دَعْ مَا يَرِيبُكَ إِلَى مَا لاَ يَرِيبُكَ فَإِنَّ الصِّدْقَ طُمَأْنِينَةٌ وَإِنَّ الْكَذِبَ رِيبَةٌ ‏"‏

ቅሉ ግን ከዚያ በተቃራኒ ሸሪዓህ በመቃረን ከሃይማኖት አላህ በእርሱ ያልፈቀደውን ለእነርሱ የደነገጉ በአሏህ ላይ አሻርከዋል፦
42፥21 *"ከሃይማኖት አላህ በእርሱ ያልፈቀደውን ለእነርሱ “የደነገጉ” ተጋሪዎች ለእነርሱ አሏቸውን?"* أَمْ لَهُمْ شُرَكَاءُ شَرَعُوا لَهُم مِّنَ الدِّينِ مَا لَمْ يَأْذَن بِهِ اللَّهُ

እዚህ አንቀጽ ላይ “የደነገጉ” ለሚለው የገባው ቃል “ሸረዑ” شَرَعُوا ሲሆን መለኮታዊ ያልሆነ ከዝንባሌአቸው ሸሪዓህ መደንገጋቸው የሚያሳይ ቃል ነው። “ሸሪክ” شَرِيك ማለት “ተጋሪ” ማለት ነው፥ የሸሪክ ብዙ ቁጥር ደግሞ “ሹረካእ” شُرَكَاء ሲሆን “ተጋሪዎች” ማለት ነው፥ አሏህ በእርሱ ያልፈቀደውን ነገር ሐላል ማድረግ ለእነርሱ የደነገጉ በአላህ ሐቅ ላይ ተጋሪዎች አሏቸው። እነዚህ የአሏህን ሐቅ የሚጋሩ ሰዎች እራሳቸው ተሕሊል እና ተሕሪም በማድረጋቸው ጣዖታት ናቸው፦
4፥60 ወደ እነዚያ እነርሱ በአንተ ላይ በተወረደው እና ከአንተ በፊትም በተወረደው አምነናል ወደሚሉት አላየህምን? “በእርሱ እንዲክዱ በእርግጥ የታዘዙ ሲኾኑ ወደ ጣዖት መፋረድን ይፈልጋሉ”፡፡ أَلَمْ تَرَ إِلَى الَّذِينَ يَزْعُمُونَ أَنَّهُمْ آمَنُوا بِمَا أُنزِلَ إِلَيْكَ وَمَا أُنزِلَ مِن قَبْلِكَ يُرِيدُونَ أَن يَتَحَاكَمُوا إِلَى الطَّاغُوتِ وَقَدْ أُمِرُوا أَن يَكْفُرُوا بِهِ

አንድ ሰው አሏህ ካወረደው ውጪ፦ "ይህ ነገር ሐራም ነው፥ ይህ ነገር ሐላል ነው" ካለ እርሱ ጣዖት ነው። “ጧጉት” طَّٰغُوت የሚለው ቃል “ጦጋ” طَغَىٰ ማለትም “ወሰን አለፈ” ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን “በአላህ ሐቅ ላይ ወሰን ማለፍ” ማለት ነው። አምላካችን አሏህ ሸሪዓችን፦ "ሐላል ያለውን ሐላል፥ ሐራም ያለውን ሐራም" የምንለን ያድርገን! ዝንባሌአችንን ከመከተል ይጠብቀን! አሚን።

ከዐቃቤ እሥልምና ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
ሚርዛ ሑሤን ዐሊይ

ገቢር አንድ

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ፥ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

112፥3 አልወለደም፤ አልተወለደምም፡፡ لَمْ يَلِدْ وَلَمْ يُولَدْ

"በሃእ" بهاء ማለት "ክብር" ማለት ሲሆን "አብሃ" أبهى ደግሞ "በሃእ" بهاء ለሚለው ገላጭ ቅጽል ጡዘታዊ ደረጃ"superlative degree" ነው። በሃኢይ بهائی‎ ማለት "ባሃያዊ" ማለት ሲሆን በተሳሳተ አጠራር "ባሃኢ" ይባላሉ።
"በሃኡልላህ" بهاء الله ማለት "የአሏህ ክብር" ማለት ነው ሲሆን፦
፨"በሃኡልላህ" የሚለው ስም ልጁ "አብዱል በሃእ" ለአባቱ ለሚርዛ ሑሤን ዐሊይ ያወጣለት ስም ነው፣
፨በሃኡልላህ ሚርዛ ሑሤን ዐሊይ እራሱ በሕይወት ዘመኑ "በሃኡልላህ" የሚለውን ስም ዐያውቀውም፣
፨በተጨማሪም "በሃኡልላህ" የሚለው ስም በሚርዛ ሑሤን ዐሊይ ጽሑፎች ውስጥ የለም።
ሚርዛ ሑሤን ዐሊይ እንደ ጎርጎሮሳውያን አቆጣጠር በ1863 ድኅረ ልደት፦ "እኔ አሏህ ነኝ" ብሎ ማስተማር ጀመረ፦
"ከእኔ ከተከበርኩት እና ከጥበበኛው በቀር አምላክ የለም" አቅዳሥ ገፅ 43
"በዘላለማዊ ጌታ በበሃእ የታዘዘውን ምንም ይሁን ተቀበል" አቅዳሥ ገፅ 144
"ሁሉንም መልእክተኞች ልከናል፥ ሁሉንም መጽሐፍት አውርደናል" አቅዳሥ ገፅ 8
"ዘላለማዊ ጌታ በእስር ቤት ውስጥ ተዋሽቶበታል" ኢሥተደራት ገፅ 34
"ባሃእ ሆይ! የህልውና ፈጣሪ ሆይ! ምስጋና ሁሉ ለአንተ ነው" አል-ሙቢን ገፅ 34
"የአንተን ከፍ ያለ እና የተፈራ አምላክ ባሃእን ታዘዝ!" አል-ሙቢን ገፅ 190
"ባሃእ አንተ በጣም በጎ አድራጊ ጌታ ነህ" አል-ሙቢን ገፅ 297
"እኔ አሏህ ነኝ፥ ከእኔ በቀር አምላክ የለም፥ እኔ የሁሉ ነገር ጌታ ነኝ። ፍጡሮቼ ሆይ እኔን ብቻ አምልኩኝ" ታጀሊያት ገፅ 5

"በሃእ" بهاء የአሏህ ታላቅ ስም ሲሆን የሚርዛ ሑሤን ዐሊይ የቅባት ስሙ እንደሆነ እራሱ ይናገራል። ሚርዛ ሑሤን ዐሊይ "አሏሁ አብሃ" الله أبهى‎ እያለ እራሱን ያሞጋግስ ነበር፥ "አሏሁ አብሃ" الله أبهى‎ ማለት "አሏህ በሃእ ነው" ማለት ነው።
የሚርዛ ሑሤን ዐሊይ ልጅ ዐባሥ ኢፌንዲ እራሱን "ዐብዱል በሃእ" عبد البهاء ሲል ትርጉሙ "የበሃእ ባሪያ ወይም አምላኪ" ማለቱ ነበር፥ ልክ "ዐብደልላህ" عبد الله‎ ማለት "የአሏህ ባሪያ ወይም አምላኪ" እንደ ማለት ነው።
ሚርዛ ሑሤን ዐሊይ ሙሣን በሢና ተራራ ላይ ያናገረ እንዲሁ ተወዳጁ ነቢያችንን"ﷺ" በሲድረቱል ሙንተሃ ላይ ያናገረ አሏህ እራሱ እንደሆነ እና ከሟች ዓይኖች ተደብቆ የነበረው አሏህ እራሱ ሆኖ እንደመጣ ይናገራል፦
"እርሱ በእውነቱ የግልጸት ጎኅ የሆነውን፣ በሢና ላይ የተነጋገረውን፣ በእርሱ አማካኝነት የላቀ አድማስ እንዲያበራ የተደረገውን፣ በእርሱ ሢድረቱል ሙንተሃ ላይ የተናገረውን፣ በእርሱ አማካኝነት በሰማያት እና በምድር ላሉት ሁሉ፦ "እነሆ የሁሉ ባለቤት መጥቷል" መካከለኛ የግዴታ ጸሎት
"እርሱ ከሟች ዓይኖች ተደብቆ የነበረው መጥቷል" ቅስማት 13

ሚርዛ ሑሤን ዐሊይ መቃብሩ ላይ ለጉብኝነት እንዲህ ብለው እንዲጸልዩ ተናግሯል፦
"አምላኬ እና ወዳጄ ሆይ!... የሕይወት ቀናትህ ሁሉ በስቃይ ውቂያኖስ ውስጥ እንድትሰጥም ተደርገሃል፥ በአንድ ወቅት በእግር ብረት እና በሰንሰለት ታስረካል" የባሃኡሏህ ጉብኝነት ከሚል ጸሎት የተወሰደ

እውን የዓለማቱ ጌታ አሏህ በፍጡራኑ ስቃይ እና እስራት ደረሰበት እያላችሁን ነውን? ክርስቲያኖች፦ "ፈጣሪ ተወልዶ በፍጡሮቹ ተገደለ" ከሚሉት ትምህታቸው ልዩነቱን ትነግሩኝ?
አሏህ አንድ ነው፥ እርሱ ከማንነቱ እና ከምንነቱ ማንንም አልወለደም። ከእርሱ ማንነት እና ምንነት የተወለደ ማንም የለም፥ ከእርሱ የተወለደ ማንም አምላክ የለም፦
112፥1 በል «እርሱ አላህ አንድ ነው፡፡ قُلْ هُوَ اللَّهُ أَحَدٌ
112፥3 አልወለደም፤ አልተወለደምም፡፡ لَمْ يَلِدْ وَلَمْ يُولَدْ
23፥91 አላህ ምንም ልጅን አልወለደም፡፡ ከእርሱም ጋር አንድም አምላክ የለም፡፡ مَا اتَّخَذَ اللَّهُ مِن وَلَدٍ وَمَا كَانَ مَعَهُ مِنْ إِلَـٰهٍ
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 65, ሐዲስ 496
አቢ ሁረይራህ”ረ.ዐ.” እንደተረከው፦ “ነቢዩ”ﷺ” አሏህ እንዲህ አሉ፦ “አሏህም አለ፦ “የአደም ልጅ እኔን አስዋሸ፥ እንዲህ ለማድረግ መብት አልነበረውም፡፡ ደግሞም ሰደበኝ፥ እንዲህ ለማድረግም መብት አልነበረውም፡፡ እኔን ማስዋሸቱ የሚያመለክተው፦ “መጀመሪያ ላይ አድርጎ ዳግም አይሠራኝም” የሚለው ንግግሩ ነው፥ ለመሆኑ መጀመሪያ እርሱን መፍጠር ነው ወይስ ዳግም መሥራት ለእኔ ይበልጥ የሚቀል የነበረው? እኔን መሳደቡን የሚያመለክተው እንደፈጠረኝደግሞ፦ “አሏህ ልጅ ወልዷል” ማለቱ ነው፥ እኔ አንድ ነኝ፣ የሁሉ መጠጊያ ነኝ፣ አልወለድኩም፣ አልተወለድኩም፣ ለእኔ አንድም ብጤ የለኝም”፡፡ عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ ـ رضى الله عنه ـ عَنِ النَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم قَالَ ‏ “‏ قَالَ اللَّهُ كَذَّبَنِي ابْنُ آدَمَ وَلَمْ يَكُنْ لَهُ ذَلِكَ، وَشَتَمَنِي وَلَمْ يَكُنْ لَهُ ذَلِكَ، فَأَمَّا تَكْذِيبُهُ إِيَّاىَ فَقَوْلُهُ لَنْ يُعِيدَنِي كَمَا بَدَأَنِي، وَلَيْسَ أَوَّلُ الْخَلْقِ بِأَهْوَنَ عَلَىَّ مِنْ إِعَادَتِهِ، وَأَمَّا شَتْمُهُ إِيَّاىَ فَقَوْلُهُ اتَّخَذَ اللَّهُ وَلَدًا، وَأَنَا الأَحَدُ الصَّمَدُ لَمْ أَلِدْ وَلَمْ أُولَدْ وَلَمْ يَكُنْ لِي كُفْأً أَحَدٌ ‏”‌‏.‏

አሏህ ከሚሉት ነገር ጥራት ይገባውና ከወለደ በአንድነቱ ላይ ብዝኃነት ሊመጣ ነው፥ ከተወለደ ደግሞ መነሾ እና ጅማሮ ሊኖረውን ነው። ሚርዛ ሑሤን ዐሊይ ከአባቱ ከሚርዛ ዐባሥ ኑሪ እና ከእናቱ ከኸዲጃ ኸኑን የተወለደ ሲሆን አሏህ ግን አይወለድም፥ ሚርዛ ሑሤን ዐሊይ ከሦስት ሚስቶቹ 14 ልጆች የወለደ ሲሆን አሏህ ግን አይወልድም። ስለዚህ ሚርዛ ሑሤን ዐሊይ፦ "አሏህ ነኝ" ብሎ የተነሳው ትምህርቱ የሐሠት ትምህርት ነው።

ኢንሻሏህ ይቀጥላል....
ይህንን የበሃኢይን ፈሣድ ለሙሥሊሙ ኡማህ በመግለጥ እና በማጋለጥ ተደራሽነት እንዲኖረው ሼር አርጉ!

ከወንድም አሚን ሪድዋን
https://tttttt.me/Amin_redwan

ወሠላሙ ዐለይኩም
ሚርዛ ሑሤን ዐሊይ

ገቢር ሁለት

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ፥ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

33፥40 ሙሐመድ ከወንዶቻችሁ የአንድም ሰው አባት አይደለም፡፡ ግን የአላህ መልክተኛ እና የነቢያት መደምደሚያ ነው፡፡ አላህም በነገሩ ሁሉ ዐዋቂ ነው፡፡ مَّا كَانَ مُحَمَّدٌ أَبَا أَحَدٍ مِّن رِّجَالِكُمْ وَلَـٰكِن رَّسُولَ اللَّهِ وَخَاتَمَ النَّبِيِّينَ ۗ وَكَانَ اللَّهُ بِكُلِّ شَيْءٍ عَلِيمًا

ሚርዛ ሑሤን ዐሊይ እንደ ጎርጎሮሳውያን አቆጣጠር በ1863 ድኅረ ልደት ባግዳድ ላይ፦ "እኔ አሏህ ነኝ" ብሎ ሲያውጅ የባግዳድ ምሁራን በዕውቀት ሲያጣድፉት እና ሲያንቆራጥቱት፦ "ነቢይ ነኝ" ብሎ አረፈው።
“ነቢይ” نَبِيّ የሚለው ቃል “ነበአ” نَبَّأَ ማለትም “አወራ” ወይም “ተናገረ” ከሚል ሥርወ-ቃል ሲሆን “አውሪ” ወይም “ተናጋሪ” ማለት ነው፥ የነቢይ ብዙ ቁጥር ደግሞ “ነቢዩን” نَبِيُّون ወይም “አንቢያእ” أَنْبِيَاء ነው። አንድ ሰው ከአላህ ዘንድ “ነበእ” نَبَأ ማለትም “የሩቅ ወሬ” ወይም “የሩቅ ንግግር” ሲወርድለት ነቢይ ይሰኛል፦
66፥3 *”ነቢዩ ከሚስቶቹ ወደ አንዷ ወሬን በመሰጠረ ጊዜ አስታውስ፡፡ እርሱንም በነገረች እና አላህ እርሱን ማውራትዋን ባሳወቀው ጊዜ ከፊሉን አስታወቀ፤ ከፊሉንም ተወ፡፡ በእርሱም ባወራት ጊዜ «ይህን ማን ነገረህ?» አለች፡፡ «ዐዋቂው ፥ውስጠ ዐዋቂው ነገረኝ» አላት”*። وَإِذْ أَسَرَّ ٱلنَّبِىُّ إِلَىٰ بَعْضِ أَزْوَٰجِهِۦ حَدِيثًۭا فَلَمَّا نَبَّأَتْ بِهِۦ وَأَظْهَرَهُ ٱللَّهُ عَلَيْهِ عَرَّفَ بَعْضَهُۥ وَأَعْرَضَ عَنۢ بَعْضٍۢ ۖ فَلَمَّا نَبَّأَهَا بِهِۦ قَالَتْ مَنْ أَنۢبَأَكَ هَٰذَا ۖ قَالَ نَبَّأَنِىَ ٱلْعَلِيمُ ٱلْخَبِيرُ

በዚህ አንቀጽ ውስጥ “ማን ነገረህ” ለሚለው ቃል የገባው “መን አንበአከ” مَنْ أَنْبَأَكَْ ሲሆን መልሱ “ነበአኒየ” نَبَّأَنِيَ ማለትም “ነገረኝ” ማለት ነው። “አንበአከ” أَنْبَأَكَْ ሆነ “ነበአኒየ” نَبَّأَنِيَ የሁለቱም ግስ ርቢ “ነበአ” نَبَّأَ ነው። ስለዚህ “ነቢይ” ማለት ሁሉን ዐዋቂው፥ ውስጠ ዐዋቂው አላህ የሚያናግረው እና የሚነግረው ማለት ነው። ከዚያም ባሻገር መመሪያው እራሱ በራሱ የነቢይነት መደብ ውስጥ ነው፦
15፥49 *”ባሮቼን እኔ ይቅርባዩ መሓሪው እኔው ብቻ መኾኔን ንገራቸው”*፡፡ نَبِّئْ عِبَادِي أَنِّي أَنَا الْغَفُورُ الرَّحِيمُ

“ንገራቸው” نَبِّئْ ለሚለው ትእዛዛዊ ግስ አሁንም “ነበእ” نَبِّئْ ሲሆን “ነበአ” نَبَّأَ ከሚለው ሥርወ-ቃል የመጣ ነው። አንድ ነቢይ ለአማንያን በመልካም ለማዘዝ እና በመጥፎ ለመከልከል ያስጠነቅቃል፥ ለራሱም ዒባዳህ ምን ምን ማድረግ እንዳለበት አላህ ይነግረዋል።
“ረሡል” رَسُول የሚለው ቃል “አርሠለ” أَرْسَلَ ማለትም “ላከ” ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን “መልእክተኛ” ማለት ነው፥ የረሡል ብዙ ቁጥር ደግሞ “ሩሡል” رُسُل ነው። አንድ ነቢይ ሕግ ያለበት “ሪሣላህ” رِسَالَة ማለትም “መልእክት” ሲወርድለት ረሡል” ይሆናል። ረሡል ለአማንያን እና ለከሃድያን ለማስጠንቀቅ በሸሪዓህ ይላካል፦
22፥52 *”ከመልእክተኛ እና ከነቢይም”* ከአንተ በፊት አንድንም አልላክንም፥ ባነበበ ና ዝም ባለ ጊዜ፣ ሰይጣን በንባቡ ላይ ማጥመሚያን ቃል የሚጥል ቢሆን እንጂ። وَمَا أَرْسَلْنَا مِنْ قَبْلِكَ مِنْ رَسُولٍ وَلَا نَبِيٍّ إِلَّا إِذَا تَمَنَّىٰ أَلْقَى الشَّيْطَانُ فِي أُمْنِيَّتِهِ

እዚህ አንቀጽ ላይ “ነቢይ” نَبِيّ እና “ረሡል” رَسُول በሚሉት የማዕረግ ስሞች መካከል “ወ” وَ ማለትም “እና” የሚል መስተጻምር አለ፥ ይህም ነቢይ እና ረሡል ሁለት የተለያየ ደረጃ መሆኑን ቁልጭና ፍንትው አድርጎ ያሳያል። በተጨማሪም “አልላክንም” የሚለው አጽንዖታዊ ቃል “ቢሆን እንጂ” በሚል አፍራሽ ቃል በመምጣቱ ነብይ በመልካም እንዲያዝ በመጥፎ እንዲከለክል ለአማንያን እንደተላከ ሁሉ መልእክተኛ ደግሞ ለአማንያንና ለከሃድያን ለማስጠንቀቅና ለማብሰር ይላካል። መልእክተኛ መልክተኛ ለመሆን ነቢይነትን አሳልፎ ስለሆነ መልእክተኛ ሁሉ ነቢይ ነው፥ ነቢይ ሁሉ ግን መልእክተኛ አይደለም። ምክንያቱም ሪሣላ ሳይወርድለት ነቢይ ብቻ ሆኖ የሚቀር አለ፥ ለምሳሌ አደም የመጀመሪያው ነቢይ ሲሆን ኑሕ ደግሞ የመጀመሪያው ረሡል ነው፦
ኢማም አሕመድ መጽሐፍ 5, ሐዲስ 1781
አቡ ዘር እንደተረከው፦ *”የአላህ ነቢይ”ﷺ” ሆይ የመጀመሪያው ነቢይ ማን ነው? ብሎ አለ። እርሳቸውም፦ “አደም ነው” አሉ። እርሱም፦ “እርሱ ነቢይ ነበርን? ብሎ አለ። እርሳቸውም፦ “አዎ” አሉ”*። عَن أَبُو ذَرٍّ قُلْتُ : يَا نَبِيَّ اللَّهِ، فَأَيُّ الْأَنْبِيَاءِ كَانَ أَوَّلَ. قَالَ : ” آدَمُ “. قَالَ : قُلْتُ : يَا نَبِيَّ اللَّهِ، أَوَنَبِيٌّ كَانَ آدَمُ ؟ قَالَ : ” نَعَمْ،
ኢማም ቡኻሪይ መጽሐፍ 65, ሐዲስ 4476
አነሥ እንደተረከው፦ “ነቢዩም”ﷺ” አሉ፦ *”……(አደምም)፦ “ኑህ ጋር ሂዱ! እርሱ በምድር ላይ የተላከ የመጀመሪያው መልእክተኛ ነው፥ ወደ ምድር ባለቤቶች አላህ ልኮታል” ይላቸዋል”*። ائْتُوا نُوحًا فَإِنَّهُ أَوَّلُ رَسُولٍ بَعَثَهُ اللَّهُ إِلَى أَهْلِ الأَرْضِ‏.‏
ነቢያችን”ﷺ” የነቢያት መደምደሚያ ናቸው፥ ከነቢያችን”ﷺ” በኃላ ነቢይ ብቻ ሳይሆን ረሡልም አይመጣም። ነቢይነት እና መልእክተኝነት በእርሳቸው ተደምድሟል፦
33:40 ሙሐመድ ከወንዶቻችሁ የአንድንም ሰው አባት አይደለም። ነገር ግን የአላህ መልክተኛ እና *”የነቢያት መደምደሚያ” ነው”*፥ አላህም በነገሩ ሁሉ ዐዋቂ ነው። مَا كَانَ مُحَمَّدٌ أَبَا أَحَدٍ مِنْ رِجَالِكُمْ وَلَٰكِنْ رَسُولَ اللَّهِ وَخَاتَمَ النَّبِيِّينَ وَكَانَ اللَّهُ بِكُلِّ شَيْءٍ عَلِيمًا
ጃምዒ አት-ቲርሚዚይ መጽሐፍ 8, ሐዲስ 2272
አነሥ ኢብኑ ማሊክ እንደተረከው የአላህ መልእክተኛ”ﷺ” እንዲህ አሉ፦ *”በእርግጥም መልእክተኛነት እና ነቢይነት ተዘግቷል። ከእኔ በኃላ መልእክተኛም ነቢይም የለም*። حَدَّثَنَا أَنَسُ بْنُ مَالِكٍ، قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم ” إِنَّ الرِّسَالَةَ وَالنُّبُوَّةَ قَدِ انْقَطَعَتْ فَلاَ رَسُولَ بَعْدِي وَلاَ نَبِيَّ

ታዲያ “ነብይ እና ረሡም ከነቢያችን”ﷺ” በኃላ የለም” ከተባለ “ነብይ ነኝ” ወይም “መልእክተኛ ነኝ” ብለው የተነሱት ሚርዛ ጉላም አሕመድ የቃዲያኒይ መስራች፣ ሚርዛ ሑሤን ዐሊይ የባሃኢይ መሥራች፣ ዶክተር ራሺድ ኸሊፋክ የቁርኣኒያህ መስራች ምንድን ናቸው? ሲባል ኃሣዌ ነብይ እና መልእክተኛ ናቸው።
“ደጃል” دَّجَّال የሚለው ቃል “ደጀለ” دَجَلَ ማለትም “አጭበረበረ” ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን “አጭበርባሪ” ወይም “ሐሣዌ” ማለት ነው። እነዚህ ወደ ሠላሳ የሚቃረቡ ደጃሎች “እኔ የአላህ መልእክተኛ ነኝ” ወይም “እኔ የአላህ ነብይ ነኝ” ብለው እንደሚነሱ በነቢያችን"ﷺ" ተነግሯል፦
ኢማም ሙሥሊም መጽሐፍ 54, ሐዲስ 108
አቢ ሁረይራህ”ረ.ዐ.” እንደተረከው ነቢዩም”ﷺ” እንዲህ አሉ፦ “የመጨረሻይቱ ሰአት አትቆምም ሠላሳ የሚቃረቡ ደጃሎች ቀጣፊዎች ተነስተውስ፦ “እኔ የአላህ መልእክተኛ ነኝ” ብለው ቢናገሩ ቢሆን እንጂ”። عَنْ أَبِي، هُرَيْرَةَ عَنِ النَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم قَالَ ” لاَ تَقُومُ السَّاعَةُ حَتَّى يُبْعَثَ دَجَّالُونَ كَذَّابُونَ قَرِيبٌ مِنْ ثَلاَثِينَ كُلُّهُمْ يَزْعُمُ أَنَّهُ رَسُولُ اللَّهِ
ሡነን አቢ ዳውድ መጽሐፍ 37, ሐዲስ 13
የአላህ መልእክተኛ”ﷺ” እንዲህ አሉ፦ ከእኔ ዑማ ውስጥ ሠላሳ የሚያህሉ ቀጣፊዎች፦ “ነቢይ ነኝ” ብለው ይነሳሉ፥ ነገር ግን እኔ የነቢያት መደምደሚያ ነኝ። ከእኔ በኃላ ነቢይ የለም”። وَحَتَّى تَعْبُدَ قَبَائِلُ مِنْ أُمَّتِي الأَوْثَانَ وَإِنَّهُ سَيَكُونُ فِي أُمَّتِي كَذَّابُونَ ثَلاَثُونَ كُلُّهُمْ يَزْعُمُ أَنَّهُ نَبِيٌّ وَأَنَا خَاتَمُ النَّبِيِّينَ لاَ نَبِيَّ بَعْدِي

ሰው መነጻጸሪያ ነጥብ ሳይኖረው ፈጽሞና ጨልጦ ወደ ክህደት ሲገባ ማየት እጅጉን ያማል፥ ኢሥላም እውነትን በመግለጥ እና ሐሰትን በማጋለጥ እረገድ ፈር ቀዳጅ እና ፋና ወጊ ነው። ከእውነት በተቃራኒ ደግሞ የሐሰት ትምህርት የሚያራምዱ በዘመናችን የሚንቀሳቀሱ ቃዲያኒይ፣ በሃኢይ፣ ቁርአንያህ ወዘተ የደጃሎች ተከታዮች ናቸው፥ የእነዚህ አንጃዎች መሥራች፦ “ነቢይ ነኝ” ወይም “መልእክተኛ ነኝ” ብለው የተነሱት ሚርዛ ጉላም አሕመድ የአሕመዲያ መሥራች፣ ሚርዛ ሑሤን ዒሊይ የበሃኢይ መስራች፣ ዶክተር ራሺድ ኸሊፋህ የቁርኣንያ መሥራች ሲሆኑ እነዚህ ነቢያችን”ﷺ” ይመጣሉ ብለው ከተነበዩት ደጃሎች መካከል ናቸው። ስለዚህ በእሳት አትጫወት! አልያም እያየህ እሳት ውስጥ ግባበት!

ኢንሻሏህ ይቀጥላል....
ይህንን የበሃኢይን ፈሣድ ለሙሥሊሙ ኡማህ በመግለጥ እና በማጋለጥ ተደራሽነት እንዲኖረው ሼር አርጉ!

ከወንድም አሚን ሪድዋን
https://tttttt.me/Amin_redwan

ወሠላሙ ዐለይኩም