ወሒድ የዕቅበተ ኢሥላም መጣጥፍት"Wahid Articles of Islamic Apologetics"
58.4K subscribers
68 photos
69 videos
19 files
1.72K links
ዳዒ ወሒድ በኢሥላም እና በክርስትና መካከል ያለውን ልዩነት እና አንድነት በንጽጽር የሚያስቀምጥ ወንድም ነው። ለዚህም የቋንቋ፣ የሰዋስው፣ የዐውድ፣ የተዛማች እና የሥነ አመክንዮ ሙግት በማቅረብ የሚታወቅ ተሟጋች እና ጦማሪ ነው። ለሙግቱ ነጥብ በዋነኝነት የሚጠቀምባቸው ቋንቋ ዐማርኛ፣ ግዕዝ፣ እንግሊዝኛ፣ ዐረቢኛ፣ ዕብራይስጥ እና ግሪክ ናቸው። መልካም የንባብ፣ የጥናት፣ የማነጻጸር ጊዜ ይሁንልዎ!
Download Telegram
መለከት

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

39፥68 *በቀንዱም ይነፋል፥ በሰማያት ውስጥ ያለው ፍጡር እና በምድርም ውስጥ ያለው ፍጡር ሁሉ አላህ የሻው ሲቀር በድንጋጤ ይሞታል፡፡ ከዚያም በእርሱ ሌላ መንነፋት ይነፋል፥ ወዲያውም እነርሱ የሚሠራባቸውን የሚጠባበቁ ኾነው ቋሚዎች ይኾናሉ*፡፡ وَنُفِخَ فِي الصُّورِ فَصَعِقَ مَن فِي السَّمَاوَاتِ وَمَن فِي الْأَرْضِ إِلَّا مَن شَاءَ اللَّهُ ۖ ثُمَّ نُفِخَ فِيهِ أُخْرَىٰ فَإِذَا هُمْ قِيَامٌ يَنظُرُونَ

“ሱር” صُّور የሚለው ቃል “ሶወረ” صَوَّرَ ማለትም “ቀረፀ” ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን “ቅርፅ” ማለት ነው፥ ይህ ቅርፅ ነጋሪት የሚጎሰምበት የመለከት ቀንድ ነው። “ቀርን” قَرْن ማለት “ቀንድ” ማለት ሲሆን ለመለከት የሚቀረጽ ቀንድ ነው፦
ሡነን አቢዳውድ መጽሐፍ 42, ሐዲስ 147
ዐብደሏህ ኢብኑ ዐምር እንደተረከው፦ “ነቢዩም አሉ፦ *”ሱር የሚነፋበት ቀንድ ነው”*። عَنْ عَبْدِ اللَّهِ بْنِ عَمْرٍو، عَنِ النَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم قَالَ “‏ الصُّورُ قَرْنٌ يُنْفَخُ فِيهِ ‏”‏

በፍርድ ቀን ጠሪው መልአክ ወደ አስደንጋጭ ነገር በቀንዱ በሚጠራበትን ቀን በሰማያት ውስጥ ያለው ፍጡር እና በምድርም ውስጥ ያለው ፍጡር ሁሉ አላህ የሻው ሲቀር በድንጋጤ ይሞታል፦
53፥6 ከእነርሱም ዙር፡፡ *ጠሪው መልአክ ወደ አስደንጋጭ ነገር የሚጠራበትን ቀን አስታውስ*፡፡ فَتَوَلَّ عَنْهُمْ ۘ يَوْمَ يَدْعُ الدَّاعِ إِلَىٰ شَيْءٍ نُّكُرٍ
39፥68 *በቀንዱም ይነፋል፥ በሰማያት ውስጥ ያለው ፍጡር እና በምድርም ውስጥ ያለው ፍጡር ሁሉ አላህ የሻው ሲቀር በድንጋጤ ይሞታል፡፡ ከዚያም በእርሱ ሌላ መንነፋት ይነፋል፥ ወዲያውም እነርሱ የሚሠራባቸውን የሚጠባበቁ ኾነው ቋሚዎች ይኾናሉ*፡፡ وَنُفِخَ فِي الصُّورِ فَصَعِقَ مَن فِي السَّمَاوَاتِ وَمَن فِي الْأَرْضِ إِلَّا مَن شَاءَ اللَّهُ ۖ ثُمَّ نُفِخَ فِيهِ أُخْرَىٰ فَإِذَا هُمْ قِيَامٌ يَنظُرُونَ

“አስ-ሶዕቃህ” الصَّعْقَةُ የሚለው ቃል “ሶዒቀ” صَعِقَ ማለት “እራሱ ሳተ” ወይም “ምንም ሆነ” ከሚለው ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን “እራስን መሳት” ወይንም “ምንም መሆን” ማለት ነው። ፍጥረት በትንሳኤ ቀን ፊተኛው መነፋት ሲነፋ እራስን ይስታል ወይም ምንም ይሆናል፦
ሡነን አቢ ዳዉድ መጽሐፍ 2, ሐዲስ 658
አውሥ ኢብኑ አውሥ እንደተረከው፦ “የአላህ መልእክተኛ”ﷺ” እንዲህ አሉ፦ *”ከቀናችሁ በላጩ ቀን የጁሙዓህ ቀን ነው፥ በዚያ ቀን አደም ተፈጠረ፥ በዚያ ቀን ሞተ። በዚያ ቀንም መለከት ይነፋል፥ ሁሉ በድንጋጤ ይሞታል”*። عَنْ أَوْسِ بْنِ أَوْسٍ، قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم ‏”‏ إِنَّ مِنْ أَفْضَلِ أَيَّامِكُمْ يَوْمَ الْجُمُعَةِ فِيهِ خُلِقَ آدَمُ وَفِيهِ قُبِضَ وَفِيهِ النَّفْخَةُ وَفِيهِ الصَّعْقَةُ

“አኽራ” أُخْرَىٰ ማለት “ሌላ” ማለት ሲሆን “ሌላ መንነፋት” የሚለው ሁለተኛውን መነፋት ነው፥ በሁለቱ ማለትም በፊተኛው መነፋት እና በኃለኛው መነፋት መካከል ያለው ክፍተት አርባ ነው፦
ኢማም ቡኻሪይ መጽሐፍ 65, ሐዲስ 4814
አቢ ሁረይራህ እንደተረከው፦ “ነቢዩ”ﷺ” እንዲህ አሉ፦ *”በሁለቱ መነፋት ያለው ክፍተት አርባ ነው”*። قَالَ سَمِعْتُ أَبَا هُرَيْرَةَ، عَنِ النَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم قَالَ ‏ “‏ بَيْنَ النَّفْخَتَيْنِ أَرْبَعُونَ ‏”‌‏

ይህ አርባ ቀን ይሁን ወይም ወር አሊያም ዓመት ምንም አልተገለጸም። በሁለተኛው መነፋት የሚሠራባቸውን የሚጠባበቁ ኾነው ቋሚዎች ይኾናሉ፥ “ቂያማህ” قِيَٰمَة የሚለው ቃል “ቃመ” قَامَ ማለትም “ተነሣ” “ቆመ” ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን “ትንሣኤ” ማለት ነው። ጠሪው መልአክ በሚጠራበት ቀን ከመቃብራቸው ይወጣሉ፦
50፥41 *”የሚነገርህን አዳምጥም፡፡ ጠሪው ከቅርብ ስፍራ በሚጠራበት ቀን ከመቃብራቸው ይወጣሉ*፡፡ وَاسْتَمِعْ يَوْمَ يُنَادِ الْمُنَادِ مِن مَّكَانٍ قَرِيبٍ
50፥42 *ጩኸቲቱን በእውነት የሚሰሙበት ቀን ያ ከመቃብር የመውጫው ቀን ነው*፡፡ يَوْمَ يَسْمَعُونَ الصَّيْحَةَ بِالْحَقِّ ۚ ذَٰلِكَ يَوْمُ الْخُرُوجِ
36፥51 *”በቀንዱም ይነፋል፥ ወዲያውኑም እነርሱ ከመቃብሮቻቸው ወደ ጌታቸው በፍጥነት ይገሰግሳሉ*፡፡ وَنُفِخَ فِي الصُّورِ فَإِذَا هُم مِّنَ الْأَجْدَاثِ إِلَىٰ رَبِّهِمْ يَنسِلُونَ

ይህ በመለከት ሁለቱን መነፋት የሚነፋው መልአክ “የመለከት ባለቤት” ነው፥ “ሷሒብ” صَاحِب ማለት “ጓድ” ወይም “ባለቤት” ማለት ነው፥ ዩኑስ “ሷሒቡል ሑት” صَاحِب الْحُوت ሲባል “የዓሣው ባለቤት” እንደሚባል ሁሉ ይህ መልአክ “ሷሒቡ አስ-ሱር” صَاحِب الصُّور ማለት “የመለከት ባለቤት” ተብሏል፦
ሡነን አቢ ዳዉድ መጽሐፍ 32, ሐዲስ 31
አቢ ሠዒድ አል-ኹድሪይ እንደተረከው፦ *”የአላህ መልእክተኛ”ﷺ” “ሷሑበል ሱርን” አውስተዋል። በቀኙ ጂብሪል፥ በግራው ሚካኢል መሆናቸውን ተናግረዋል”*። عَنْ أَبِي سَعِيدٍ الْخُدْرِيِّ قَالَ ذَكَرَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم صَاحِبَ الصُّورِ فَقَالَ ‏ “‏ عَنْ يَمِينِهِ جِبْرَائِلُ وَعَنْ يَسَارِهِ مِيكَائِلُ ‏”‏

ይህ ሷሒቡ አስ-ሱር በሌላ ሐዲስ “ኢሥራፊል” ተብሏል፥ “ኢሥራፊል” إِسْرَافِيل ማለት “ሩፋኤል” ማለት ሲሆን ከአራቱ የመላእክት አለቃ አንዱ ነው፦
ሡነን አን-ነሣኢ መጽሐፍ 50 , ሐዲስ 92
ዓኢሻህ”ረ.ዐ.” እንደተረከችው፦ “የአላህ መልእክተኛ”ﷺ” እንዲህ ይሉ ነበር፦ *”አላህ ሆይ! የጂብሪል እና የሚካኢል ጌታ፣ የኢሥራፊል ጌታ በአንተ ከእሳት ቅጣት እና ከቀብር ቅጣት እጠበቃለው”*። عَنْ عَائِشَةَ، أَنَّهَا قَالَتْ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم ‏ “‏ اللَّهُمَّ رَبَّ جِبْرَائِيلَ وَمِيكَائِيلَ وَرَبَّ إِسْرَافِيلَ أَعُوذُ بِكَ مِنْ حَرِّ النَّارِ وَمِنْ عَذَابِ الْقَبْرِ
ይህ አቧራ የሚያስነሳ ጥያቄ አልነበረም። በባይብልም ቢሆን ወይም በትውፊት በፍርድ ቀን ሰባት የመላእክት አለቆች ሚካኤል፣ ገብርኤል፣ ሩፋኤል፣ ኡራኤል፣ ራጉኤል፣ ፋኑኤል(ጀርምኤል)፣ ሳቁኤል(ሰራኤል) ሰባት መለከት ተሰቷቸው ነጋሪት እንደሚነፉ ይናገራል፦
ማቴዎስ 24፥31 *”መላእክቱንም ከታላቅ መለከት ድምፅ ጋር ይልካቸዋል፥ ከሰማያትም ዳርቻ እስከ ዳርቻው ከአራቱ ነፋሳት ለእርሱ የተመረጡትን ይሰበስባሉ”*።
ራእይ 8፥2 *”በእግዚአብሔርም ፊት የሚቆሙትን ሰባቱን መላእክት አየሁ፥ ሰባትም መለከት ተሰጣቸው*።
ራእይ 8፥6 *”ሰባቱንም መለከት የያዙ ሰባቱ መላእክት ሊነፉ ተዘጋጁ”*።
ዳንኤል 10፥13 *”ከዋነኞቹ አለቆች አንዱ ሚካኤል ሊረዳኝ መጣ”*።
ኤፌሶን 3፥10 *”በሰማያዊ ስፍራ ውስጥ ላሉት “አለቆች” እና ሥልጣናት ትታወቅ ዘንድ”*።

ሚካኤል ከዋነኞቹ አለቆች አንዱ ነው፥ ሌሎች የመላእክት ስላሉ “ዋነኞቹ አለቆች” ብሎ አስቀምጦታል። “አለቆች” የሚለው የግሪኩ ቃል “አርኬስ” ἀρχαῖς ሲሆን “አርኬ” ἄρχω ማለትም “አለቃ” ለሚለው ብዙ ቁጥር ነው፥ በመላእክት አለቃ ድምፅ የፈጣሪ መለከት ሲነፋ ሙታንም የማይበሰብሱ ሆነው ይነሣሉ፦
1ኛ ቆሮንቶስ 15፥52 *”መለከት ይነፋልና ሙታንም የማይበሰብሱ ሆነው ይነሣሉ”*፥ እኛም እንለወጣለን።
1 ተሰሎንቄ 4፥16 ጌታ ራሱ በትእዛዝ *”በመላእክትም አለቃ ድምፅ በእግዚአብሔርም መለከት ከሰማይ ይወርዳልና፥ በክርስቶስም የሞቱ አስቀድመው ይነሣሉ*።

መልአክ በበድን አካል ላይ መንፋቱ ስትገረሙበት ነፋስ በበድን ላይ እፍ ብሎ እንደሚነፋ መነገሩ ተደመሙበት፦
ሕዝቅኤል 37፥9 እርሱም፦ *የሰው ልጅ ሆይ፥ ትንቢት ተናገር፥ ለነፋስ ትንቢት ተናገር! ለነፋስም፦ ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ ነፋስ ሆይ! ከአራቱ ነፋሳት ዘንድ ና፥ እነዚህም የተገደሉት በሕይወት ይኖሩ ዘንድ እፍ በልባቸው፡ በል! አለኝ*።

ነፋስ በተገደሉት በድን ላይ “እፍ” የሚለው እንዴት ነው? ይህንን መመለስ ከቻላችሁ ኢሥራፊል እንዴት እንደሚነፋ መረዳት ቀላል ነው። አላህ ሂዳያ ይስጣችሁ፥ ለእኛም ጽናቱን! አሚን።

ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
የአሏህ አብሮነት

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ፥ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።

8፥19 *"አሏህም ከምእምናን "ጋር" ነው"*፡፡ وَأَنَّ اللَّهَ مَعَ الْمُؤْمِنِينَ

አምላካችን አሏህ ነገርን ሁሉ ዐዋቂ ነው፥ እርሱ በነገሩ ሁሉ ላይ ተቆጣጣሪ ነው፦
64፥11 *"አላህም ነገሩን ሁሉ ዐዋቂ ነው"*፡፡ وَاللَّهُ بِكُلِّ شَيْءٍ عَلِيمٌ
4፥86 *”አላህ በነገሩ ሁሉ ላይ ተቆጣጣሪ ነው”*፡፡ إِنَّ اللَّهَ كَانَ عَلَىٰ كُلِّ شَيْءٍ حَسِيبًا

“ሸይእ” شَيْءٍ ማለት “ነገር” ማለት ሲሆን ፍጥረት ነው፥ ጊዜ እና ቦታ ፍጥረት ናቸው። አሏህ ነገርን ሁሉ ለማወቅ እና ለመቆጣጠር ጊዜ ማለትም ትላንት፣ ዛሬ፣ ነገር ወይም ቦታ ማለትም እርዝመት፣ ስፋት፣ ቁመት አይወስኑትም፥ እርሱ በነገር ሁሉ ላይ ቻይ ነው። እርሱ ፍጥረትን ሁሉ ያካበበ ነው፦
59፥6 *"አላህም በነገሩ ሁሉ ላይ ቻይ ነው"*፡፡ وَاللَّهُ عَلَىٰ كُلِّ شَيْءٍ قَدِيرٌ
41፥54 ንቁ! እነርሱ ከጌታቸው መገናኘት በመጠራጠር ውስጥ ናቸው፡፡ ንቁ! *"እርሱ በነገሩ ሁሉ ከባቢ ነው"*፡፡ أَلَا إِنَّهُمْ فِي مِرْيَةٍ مِّن لِّقَاءِ رَبِّهِمْ ۗ أَلَا إِنَّهُ بِكُلِّ شَيْءٍ مُّحِيطٌ

ጌታችን አሏህ ነገርን ሁሉ በችሎታው፣ በዕውቀቱ፣ በእዝነቱ፣ በእይታው፣ በመስማቱ ያካበበ ነው፦
40፥7 *"ጌታችን ሆይ! ነገሩን ሁሉ በእዝነት እና በዕውቀት ከበሃል"*። رَبَّنَا وَسِعْتَ كُلَّ شَيْءٍ رَّحْمَةً وَعِلْمًا
65፥12 አላህ በነገሩ ሁሉ ላይ ቻይ መኾኑን *"አላህም በነገሩ ሁሉ በዕውቀት ያካበበ"* ታውቁ ዘንድ ይህንን አሳወቃችሁ፡፡ لِتَعْلَمُوا أَنَّ اللَّهَ عَلَىٰ كُلِّ شَيْءٍ قَدِيرٌ وَأَنَّ اللَّهَ قَدْ أَحَاطَ بِكُلِّ شَيْءٍ عِلْمًا

አሏህ ሁሉን ነገር ያካበበው በባሕርያቱ ነው፥ የትም ብንሆን የምሠራውን ሁሉ ስለሚያውቅ፣ ስለሚሰማ፣ ስለሚመለከት ከእኛ ጋር ነው፦
57፥4 *"በምድር ውስጥ የሚገባውን፣ ከእርሷም የሚወጣውን፣ ከሰማይም የሚወርደውን በእርሷም ውስጥ የሚያርገውን ያውቃል፥ እርሱም የትም ብትኾኑ ከእናንተ ጋር ነው፡፡ አላህም የምትሠሩትን ሁሉ ተመልካች ነው"*፡፡ يَعْلَمُ مَا يَلِجُ فِي الْأَرْضِ وَمَا يَخْرُجُ مِنْهَا وَمَا يَنزِلُ مِنَ السَّمَاءِ وَمَا يَعْرُجُ فِيهَا ۖ وَهُوَ مَعَكُمْ أَيْنَ مَا كُنتُمْ ۚ وَاللَّهُ بِمَا تَعْمَلُونَ بَصِيرٌ

የዚህ አንቀጽ ዐውደ ምህዳሩ ላይ "ያውቃል" "ተመልካች" የሚሉት ባሕርያት አሏህ አብሮነቱን ያሳያሉ። "መዐ" مَعَ ማለት "ጋር" ማለት ሲሆን "ሐርፉል ጀር" حَرْفُ الْجَرِّ ማለት "መስተዋድድ"preposition" ነው፥ "ጋር" የሚለው "አብሮነትን" የሚያሳይ መስተዋድድ ነው። አሏህ ከበጎ ሠሪዎች ጋር፣ ከሚጠነቀቁት ጋር፣ ከታጋሾቹ ጋር፣ ከምእምናን ጋር ነው፦
29፥69 *"አላህም በእርግጥ ከበጎ ሠሪዎች ጋር ነው"*፡፡ وَإِنَّ اللَّهَ لَمَعَ الْمُحْسِنِينَ
9፥123 አላህም ከሚጠነቀቁት ጋር መኾኑን ዕወቁ፡፡ وَاعْلَمُوا أَنَّ اللَّهَ مَعَ الْمُتَّقِينَ
8፥66 *"አላህም ከታጋሾቹ ጋር ነው"*፡፡ وَاللَّهُ مَعَ الصَّابِرِينَ
8፥19 አላህም ከምእምናን ጋር ነው፡፡ وَأَنَّ اللَّهَ مَعَ الْمُؤْمِنِينَ

"ከበጎ ሠሪዎች ጋር ነው" ማለት "ከመጥፎ ሠሪዎች ጋር አይደለም" ማለት ነው፣ "ከሚጠነቀቁት ጋር ነው" ማለት "ከማይፈሩት ጋር አይደለም" ማለት ነው፣ "ከታጋሾቹ ጋር ነው" ማለት "ከትግስት የለሾች ጋር አይደለም" ማለት ነው፣ "ከምእምናን ጋር ነው" ማለት "ከከሃድያን ጋር አይደለም" ማለት ነው። አሏህ ኢሕሣን፣ ተቅዋእ፣ ሶብር፣ ኢማን ካላቸው ጋር በአብሮነት መሆኑን የሚያሳይ እንጂ ዛቱ ሁሉም ቦታ ውስጥ አለ ማለት አይደለም፦
20፥አላህም አለ «አትፍሩ! *"እኔ በእርግጥ ከእናንተ ጋር ነኝና፥ እሰማለሁ፤ አያለሁም"*፡፡ قَالَ لَا تَخَافَا ۖ إِنَّنِي مَعَكُمَا أَسْمَعُ وَأَرَىٰ

"አሏህ ከዐርሽ በላይ ነው" ብዬ ስፓስት አንዱ የክርስትና መምህር፦ "እግዚአብሔር ግን መላኤ ኩሉ ማለትም ሁሉም ቦታ የሚገኝ"omnipresent" ነው" የሚል ትምህርት ሲያስተምር ነበር። በፈጣሪ መኖር ሦስት ዓይነት እሳቤ አለ፥ እርሱም፦
1ኛ. "ፈጣሪ በፍጥረቱ ውስጥ ነው"Creator is inside of his Creation" የሚል እሳቤ ነው፥ "ፈጣሪ በፍጥረቱ ውስጥ ነው" የሚለው እሳቤ የሁሉ አምላክነት"Pantheism" እሳቤ ሲሆን ፈጣሪ ቤተክርስቲያ እንዳለ ሁሉ በእኩል መጠን እና ደረጃ ሽንት ቤት፣ መሸታ ቤት፣ ጠንቋይ ቤት ውስጥም አለ" የሚል የአውግስቲኖስ እሳቤ ነው፤ ይህ እሳቤ ዐበይት የክርስትና አንጃዎ ይቀበላሉ።

2. "ፍጥረት በፈጣሪ ውስጥ ነው"Creation is inside of his creator" የሚል እሳቤ ነው፥ "ፍጥረት በፈጣሪ ውስጥ ነው" የሚለው እሳቤ ሁሉ ነገር የፈጣሪ ምንነት፣ ማንነት እና ክፍል "Panentheism" ነው" የሚል እሳቤ ሲሆን ፈጣሪ ፍጡር ሆነ የሚል እሳቤ ያቀፈ ነው።

3. "ፈጣሪ ከፍጥረት ውጪ ነው"Creator is outside of his Creation" የሚል እሳቤ ነው፥ "ፈጣሪ ከፍጥረት ውጪ ነው" የሚል እሳቤ ፈጣሪ ከፍጥረት በላይ ይኖራል"Transcendent" የሚል እሳቤ ሲሆን የሙሥሊም አህሉ አሥ-ሡናህ ወል ጀማዓህ የምንቀበለው ይህንን እሳቤ ነው። አሏህ ከፍጡራን በኑባሬ ተነጥሎ ከፍጡራን ጋር በባሕርያቱ ይገናኛል፥ ይህ ኅሊና የሚቀበለው እሳቤ ነው።

ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
እንቅልፍ

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩኅ፥ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።

39፥42 *"አላህ ነፍሶችን በሞታቸው ጊዜ ይወስዳል፥ ያችንም ያልሞተችውን በእንቅልፏ ጊዜ ይወስዳታል"*፡፡ ٱللَّهُ يَتَوَفَّى ٱلْأَنفُسَ حِينَ مَوْتِهَا وَٱلَّتِى لَمْ تَمُتْ فِى مَنَامِهَا

እንቅልፍ ሰውነታችን በሽታ የመከላከል ዐቅሙን በከፍተኛ ሁኔታ ይጨምራል፣ የበላነውን ምግብ ከሰውነታችን ጋር በቀላሉ ውሕደት ይፈጥራል፣ አካላችን እረፍት በማግኘት ኃይልን ያሰባስባል፣ የአእምሮ የማስታወስ ብቃትን ያጎለብታል። ቅሉ ግን በኢሥላም እንቅልፍ ከዚህም ባሻገር ዘርፈ-ብዙ እና መጠነ-ሰፊ አንድምታ አለው፥ እረ እንቅልፍ እንደውም ከሕልም፣ ከሩሕ፣ ከሞት ጋር ጥብቅ ተዛምዶ አለው። አምላካችን አሏህ ሰውን ሲያሞት የሞት መልአክ ልኮ ሩሓችንን ይወስዳል፦
32፥11 *"«በእናንተ የተወከለው መልአከ ሞት ”ይወስዳችኃል”፡፡ ከዚያም ወደ ጌታችሁ ትመለሳላችሁ» በላቸው"*፡፡ قُلْ يَتَوَفَّىٰكُم مَّلَكُ ٱلْمَوْتِ ٱلَّذِى وُكِّلَ بِكُمْ ثُمَّ إِلَىٰ رَبِّكُمْ تُرْجَعُونَ

"ይወስዳችኃል" ለሚለው የገባው ቃል "የተወፋኩም" يَتَوَفَّىٰكُم ነው። "ነፍሥ" نَفْس ማለት እራሱ "ማንነት" ሲሆን የነፍሥ ብዙ ቁጥር "አንፉሥ" أَنْفُس ነው፥ የሰው ማንነት ደግሞ ወደ አፈር የሚሄድ ሟች አካል እና ወደ አሏህ የሚሄድ ሩሕ ነው። አሏህ ሩሕን በሞት ጊዜ ይወስዳል፦
39፥42 *"አላህ ነፍሶችን በሞታቸው ጊዜ ይወስዳል፥ ያችንም ያልሞተችውን በእንቅልፏ ጊዜ ይወስዳታል"*፡፡ ٱللَّهُ يَتَوَفَّى ٱلْأَنفُسَ حِينَ مَوْتِهَا وَٱلَّتِى لَمْ تَمُتْ فِى مَنَامِهَا

"ሞታቸው" ሲል ነፍሥ በአካል ሟች መሆኗን ሲያሳይ "ይወስዳል" ሲል ደግሞ ነፍስን በሩሕዋ ተወሳጅ መሆኗን ነው። "ሩሕ" رُّوح ማለት “መንፈስ” ማለት ሲሆን አሏህ ሩሓችንን በእንቅልፍ ጊዜ ወስዶ በንቃት ጊዜ ይመልሳል፦
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 97, ሐዲስ 97
አቡ ቀታዳህ እንደተረከው፦ "ከሶላት ሰዎች በተኙ ጊዜ የአሏህ ነቢይም"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ *"አሏህ በሚሻው ጊዜ ሩሓችሁን ይወስዳል፥ በሚሻው ጊዜ ይመልሳል"*። عَنْ عَبْدِ اللَّهِ بْنِ أَبِي قَتَادَةَ، عَنْ أَبِيهِ، حِينَ نَامُوا عَنِ الصَّلاَةِ، قَالَ النَّبِيُّ صلى الله عليه وسلم ‏ "‏ إِنَّ اللَّهَ قَبَضَ أَرْوَاحَكُمْ حِينَ شَاءَ، وَرَدَّهَا حِينَ شَاءَ ‏"‌‏
"አርዋሕ" أَرْوَاح ማለት "መንፈሶች" ማለት ሲሆን "ሩሕ" رُّوح ለሚለው ብዙ ቁጥር ነው፥ አሏህ ነፍሥን በእንቅልፏ ጊዜ ሲወስዳት ያለ ዓይን ታያለች፣ ያለ ጆሮ ትሰማለች፣ ያለ እግር ትሄዳለች፣ ያለ አፍ ትናገራለች፥ የሕልም ዓለም ሩሕ ከአካል ከተለየች በኃላ ያለውን ሕይወት ማሳያ ናሙና ነው። አምላካችን አሏህ በሌሊት ይወስደናል፥ ከዚያም በቀን ይቀሰቅሰናል፦
6፥60 *"እርሱም ያ በሌሊት የሚወስዷችሁ በቀንም የሠራችሁትን ሁሉ የሚያውቅ ከዚያም የተወሰነው ጊዜ ይፈፀም ዘንድ በእርሱ በቀን ውስጥ የሚቀሰቅሳችሁ ነው"*፡፡ وَهُوَ الَّذِي يَتَوَفَّاكُم بِاللَّيْلِ وَيَعْلَمُ مَا جَرَحْتُم بِالنَّهَارِ ثُمَّ يَبْعَثُكُمْ فِيهِ لِيُقْضَىٰ أَجَلٌ مُّسَمًّى

"የሚወስዷችሁ" ለሚለው የገባው ቃል "የተወፋኩም" يَتَوَفَّاكُم ነው፥ በቁርኣን ውስጥ "እንቅልፍ" ለሚለው የገባው የስም መደብ "ነውም" نَوْم "ኑዓሥ" نُّعَاس "ሩቁድ" رُقُود ነው። አሏህ ሩሕን በሌሊት እንቅልፍ ጊዜ ወስዶ አካላችንን ያሳርፋል፦
78፥9 *"እንቅልፋችሁንም ዕረፍት አደረግን"*፡፡ وَجَعَلْنَا نَوْمَكُمْ سُبَاتًا
10፥67 እርሱ ያ *"ሌሊትን በውስጡ ልታርፉበት፥ ቀንን ልትሠሩበት ብርሃን ያደረገላችሁ ነው፡፡ በዚህ ውስጥ ለሚሰሙ ሕዝቦች በእርግጥ ተአምራት አሉ"*፡፡ هُوَ الَّذِي جَعَلَ لَكُمُ اللَّيْلَ لِتَسْكُنُوا فِيهِ وَالنَّهَارَ مُبْصِرًا ۚ إِنَّ فِي ذَٰلِكَ لَآيَاتٍ لِّقَوْمٍ يَسْمَعُونَ

አምላካችን አሏህ በቀን ደግሞ ይቀሰቅሰናል፥ "በቀን ውስጥ የሚቀሰቅሳችሁ ነው" የሚለው ይሰመርበት። ሰው አካሉ በሌሊት እንቅልፍ እንደሚያርፍ እና በቀን እንደሚቀሰቀስ ሁሉ በሞትን ጊዜ አካሉ በትልቁ እንቅልፍ ያርፍ እና በትንሳኤ ቀን ይቀሰቀሳል፦
36፥51 *"በቀንዱም ይነፋል፥ ወዲያውኑም እነርሱ ከመቃብሮቻቸው ወደ ጌታቸው በፍጥነት ይገሰግሳሉ"*፡፡ وَنُفِخَ فِي الصُّورِ فَإِذَا هُم مِّنَ الْأَجْدَاثِ إِلَىٰ رَبِّهِمْ يَنسِلُونَ
36፥52 *«ወይ ጥፋታችን! ከእንቅልፋችን ማን ቀሰቀሰን? ይህ ያ አዛኙ ጌታ በእርሱ የቀጠረን እና መልክተኞቹ እውነትን የነገሩን ነው» ይላሉ*፡፡ قَالُوا يَا وَيْلَنَا مَن بَعَثَنَا مِن مَّرْقَدِنَا ۜ ۗ هَـٰذَا مَا وَعَدَ الرَّحْمَـٰنُ وَصَدَقَ الْمُرْسَلُونَ

እንቅልፍ ሩሕ እና አካል የሚለያዩበት ስለሆነ የሞት ወንድም ተብሏል፥ እንቅልፍ ትንሹ ሞት ስለሆነ ለዛ ነው የምሽት ዚክር ላይ "አሏህ ሆይ! በስምህ እሞታለው ሕያው እሆናለው" የንጋት ዚክር ላይ ደግሞ፦ "ለአሏህ ምስጋና ይሁን! ለዚያ ከአሞተን በኃላ ሕያው ላደረገን፥ መቀስቀስም ወደ እርሱ ነው" የምንለው፦
አል-ሙጀመል አውሠጥ ሐዲስ 938
ጃቢር ኢብኑ ዐብደሏህ እንደተረከው፦ "የአሏህ ነቢይም"ﷺ" እንዲህ ተጠየቁ፦ *"የአሏህ መልእክተኛ ሆይ! የጀናህ ባለቤቶች ይተኛሉን? የአሏህ መልእክተኛም"ﷺ" እንዲህ ሲሉ መለሱ፦ "እንቅልፍ የሞት ወንድም ነውና የጀናህ ባለቤቶች አይተኙም"*። عَنْ جَابِرِ بْنِ عَبْدِ اللَّهِ قَالَ سُئِلَ نَبِيُّ اللَّهِ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ فَقِيلَ يَا رَسُولَ اللَّهِ أَيَنَامُ أَهْلُ الْجَنَّةِ فَقَالَ رَسُولُ اللَّهِ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ النَّوْمُ أَخُو الْمَوْتِ وَأَهْلُ الْجَنَّةِ لا يَنَامُونَ
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 97, ሐዲስ 23
ሑዘይፋህ እንደተረከው፦ *"ነቢዩ"ﷺ" ወደ አልጋቸው በሄዱ ጊዜ፦ "አሏህ ሆይ! በስምህ እሞታለው ሕያው እሆናለው" ይሉ ነበር፥ በነቁ ጊዜ፦ "ለአሏህ ምስጋና ይሁን! ለዚያ ከአሞተን በኃላ ሕያው ላደረገን፥ መቀስቀስም ወደ እርሱ ነው"*። عَنْ حُذَيْفَةَ، قَالَ كَانَ النَّبِيُّ صلى الله عليه وسلم إِذَا أَوَى إِلَى فِرَاشِهِ قَالَ ‏"‏ اللَّهُمَّ بِاسْمِكَ أَحْيَا وَأَمُوتُ ‏"‌‏.‏ وَإِذَا أَصْبَحَ قَالَ ‏"‏ الْحَمْدُ لِلَّهِ الَّذِي أَحْيَانَا بَعْدَ مَا أَمَاتَنَا وَإِلَيْهِ النُّشُورُ ‏"‌‏

እውነት ነው! በእንቅልፍ ውስጥ ለሚሰሙ ሕዝቦች በእርግጥ ተአምራት አሉበት። አሏህ ከሚሰሙ ባሮቹ ያድርገን! አሚን።

ከዐቃቤ እሥልምና ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
የበርሚንግሀም ብራና

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ፥ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

10፥37 ይህም ቁርኣን ከአላህ ሌላ ከሆነ ፍጡር የተቀጠፈ ሊሆን አይገባውም። ግን ያንን ከእርሱ በፊት ያለውን የሚያረጋግጥ እና በመጽሐፉ ውስጥ ያለውን የሚዘረዝር በእርሱ ጥርጣሬ የሌለበት ሲሆን ከዓለማቱ ጌታ የተወረደ ነው፡፡ وَمَا كَانَ هَـٰذَا الْقُرْآنُ أَن يُفْتَرَىٰ مِن دُونِ اللَّهِ وَلَـٰكِن تَصْدِيقَ الَّذِي بَيْنَ يَدَيْهِ وَتَفْصِيلَ الْكِتَابِ لَا رَيْبَ فِيهِ مِن رَّبِّ الْعَالَمِينَ

የክርስትና ዐቃቤ እምነት ጄይ ስሚዝ፦ "የበርሚንግሀም ብራና ላይ የተጻፈው ቁርኣናዊ ጽሑፍ ከ 568 እስከ 645 ድኅረ-ልደት ስለሆነ ከነቢዩ"ﷺ" መወለድ 2 ዓመት በፊት ስለሆነ ቁርኣን እራሱ ከሌላ ሰው የተኮረጀ ነው፥ ያ ማለት ለነቢዩ"ﷺ" ወሕይ መምጣት ከመጀሩ ከ 610 ድኅረ ልደት በፊት 42 ዓመት ይቀድማል" በማለት ዐላዋቂ ሳሚ በመሆን ይዝረከረካል፥ ይህ የሚያሳብቀው ስለ "ረቅ" ያለው ግንዛቤ አናሳ መሆኑን ነው።

ስለ "ረቅ" ሥሩ የጠለቀ ግንዱ የዘለቀ ጥናት ግድ ይላል። "ረቅ" رَقّ የሚለው ቃል "ረቀ" رَقَّ ማለትም "አበራየ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "ብራና"Parchment" ማለት ነው፥ የረቅ ብዙ ቁጥር ደግሞ "ሩቁቅ" رُقُوق‎ ነው። አንድ ብራና የሚሠራው ከእንስሳ ቆዳ በተለይ ከበግ ቆዳ ሲሆን ብራና አንድ ጸሐፊ ከጻፈበት ጊዜ በፊት በቆዳነት ደረጃ ለረጅም ጊዜ ይቆያል፥ የብጥስጣሽ ወረቀት ጥናት"Fragmentology" ውስጥ የብራና ቆዳ ዕድሜ የካርበን መለኪያ"Radiocarbon dating" የሚባል ዐብይ ምርምር አለ። በዚህ ምርምር አንድ ቆዳ እንስሳው ሞቶ ቆዳ ከሆነበት ጊዜ ጀምሮ እንጂ ጽሑፉ ከተጻበትን ጊዜ ጀምሮ መቁጠር አይጀምርም፥ በካርበን 14"Carbon 14(Radio active) ሲመረመር አንድ ብራና ቆዳው 30 ወይም 40 ዓመት ሊቆይ እና ሊጻፈበት እንደሚችል በቅጡ ያትታል። ዋቢ መጽሐፍት ይመልከቱ፦
1. Aitken, Martin J. (2003). "Radiocarbon Dating". In Ellis, Linda (ed.). Archaeological Method and Theory. New York: Garland Publishing.
2. Arnold, J. R.; Libby, W. F. (1949). "Age Determinations by Radiocarbon Content: Checks with Samples of Known Age". Science.

ይህንን ከተረዳን ዘንዳ የበርሚንግሀም ብራና የቆዳው ዕድሜ በነሲብ እንደ ጎርጎሮሳውያን አቆጣጠር ከ 568 እስከ 645 ድኅረ ልደት ሲሆን ነቢያችን"ﷺ" ከመወለዳቸው ከ 2 ዓመት በፊት እና ከዱንያ ካለፉ 13 ዓመት ነው። የተገኘውም ጽሑፍ ከሡረቱል ከህፍ እስከ ሡረቱ አጥ-ጧሀ ነው፥ ይህ የተገኘው ጽሑፍ እንግሊዝ ውስጥ የበርሚንግሀም ዩንቨርስቲ በሚገኘው ላይብረሪ ይገኛል።

ስለዚህ ካርበን 14 የሚለካው የቆዳውን ዕድሜ ሆኖ ሳለ "የተጻፈበት ዕድሜ ነው" ብሎ መሞገት ስሑት ሙግት ነው። ለምሳሌ፦ በ 480 ድኅረ ልደት ኢትዮጵያ ከገቡት ተስዓቱ(ዘጠኙ) ቅዱሳን ከሚባሉት መነኮሳት መካከል አንዱ አባ ገሪማ ያዘጋጀው የግዕዝ እደ-ክታብ አለ፥ ይህ እደ ክታብ ኢትዮጵያ በትግራይ ክልል አባ ገሪማ ገዳም ውስጥ ሲገኝ በካርበን 14 በነሲብ ሲለካ እንደ ጎርጎሮሳውያን አቆጣጠር ከ 390 እስከ 570 ድኅረ ልደት ሲሆን ያ ማለት አባ ገሪማ ከመወለዱ ከ 50 ዓመት በፊት እና ከሞተ ከ 100 ዓመት በኃላ ማለት ነው። ስለዚህ የአባ ገሪማ ጽሐፍ ከሌላ አካል የተወሰደ ነው ማለት ነውን? ይህ የቂል አስተሳሰብ እንደሆነ ሁሉ "የበርሚንግሀም ብራና ላይ የተጻፈው ጽሑፍ ከነቢያችን"ﷺ" በፊት ነው" ብሎ መሞገት እጅግ ሲበዛ ቂልነት ነው። በለስ ቀናን ብሎ በተገኘው አጋጣሚ ለመተቸት መንጦልጦል እንዲህ ያዋርዳል፥ ቅሉ ግን ቁርኣን ከአሏህ ሌላ ከሆነ ፍጡር የተቀጠፈ ሊሆን አይገባውም፡፡ እንደውም ያንን ከእርሱ በፊት ያለውን የሚያረጋግጥ እና በመጽሐፉ ውስጥ ያለውን የሚዘረዝር በእርሱ ጥርጣሬ የሌለበት ሲሆን ከዓለማቱ ጌታ የተወረደ ነው፦
10፥37 ይህም ቁርኣን ከአላህ ሌላ ከሆነ ፍጡር የተቀጠፈ ሊሆን አይገባውም፡፡ ግን ያንን ከእርሱ በፊት ያለውን የሚያረጋግጥ እና በመጽሐፉ ውስጥ ያለውን የሚዘረዝር በእርሱ ጥርጣሬ የሌለበት ሲሆን ከዓለማቱ ጌታ የተወረደ ነው፡፡ وَمَا كَانَ هَـٰذَا الْقُرْآنُ أَن يُفْتَرَىٰ مِن دُونِ اللَّهِ وَلَـٰكِن تَصْدِيقَ الَّذِي بَيْنَ يَدَيْهِ وَتَفْصِيلَ الْكِتَابِ لَا رَيْبَ فِيهِ مِن رَّبِّ الْعَالَمِينَ

ከዐቃቤ እሥልምና ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
ሐበሻህ

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ፥ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

105፥1 “በዝሆኑ ባለቤቶች ጌታህ እንዴት እንደሠራ አላወቅህምን?” أَلَمْ تَرَ كَيْفَ فَعَلَ رَبُّكَ بِأَصْحَابِ الْفِيلِ

“ሐበሽ” حَبَشْ የሚለው ቃል “ሐበሸ” حَبَشَ ማለትም “ሰበሰበ” ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን “አሰባሳቢ” ማለት ነው፥ “ሐበሻህ” حَبَشَة ደግሞ የሐበሽ አንስታይ መደብ እና ብዙ ቁጥር ሆኖ የመጣ ነው። ሐበሻህ የሚለው ስም የመን ከሚኖሩ በመህራህ ሕዝቦች መካከል ሲኖሩ “የዕጣን አሰባሳቢዎች” ይባሉ የነበሩ ሕዝቦች ነበሩ፥ እነዚህ የመን ከሚኖሩ ከመህራህ ሕዝቦች ወደ ሰሜኑ ክፍል የተሰበሰቡ ሴማዊ ሕዝቦች ናቸው፤ “አቢሲኒያ” የሚለው የላቲኑ ቃል እራሱ “ሐበሻህ” حَبَشَة ከሚለው ቃል የመጣ ነው። እዚህ ድረስ ስለ ስሙ አመጣጥ እና ዳራ ካየን ዘንዳ በኢሥላም ታሪክ ውስጥ አውንታዊ እና አሉታዊ ጉልኅ ሚና ያላቸውን አራት ሐበሻዊ ሰዎች እንመለከታለን፦

ነጥብ አንድ
“ንጉሥ አብርሃ”
ሶሪያዊ ፍሬምናጥስ የአትናቴዎስን አንቀጸ-እምነት በ 350 ድኅረ-ልደት ወደ ሐበሻህ ይዞ ሲመጣ ዒዛና እና ሳይዛና የሚባሉት ሁለት ወንድማማች ነገሥታት ተቀብለውታል፥ ስማቸውም ዒዛና አብርሃ ሳይዛና ደግሞ አፅበሃ ተባለ። አብርሃ የአክሱም መንግሥት ንጉሥ ሲሆን እስከ የመን ድረስ ይገዛ ነበር፥ ይህ ንጉሥ በየመን በጃሂሊያህ ጊዜ ከአሏህ ቤት ጋር በማፎካከር ቤተክርስቲያን የመን ውስጥ ሠርቷል፦
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 63, ሐዲስ 49
ጀሪር ኢብኑ ዐብደሏህ እንደተረከው፦ “በዘመነ-ጃሂሊያ ዙል-ኻለሷህ የሚባል ቤት ነበረ፥ የቀኝ ቅጥ ወይም የግራ ቅጥ ተብሎ ይጠራ ነበር”። عَنْ جَرِيرِ بْنِ عَبْدِ اللَّهِ، قَالَ كَانَ فِي الْجَاهِلِيَّةِ بَيْتٌ يُقَالَ لَهُ ذُو الْخَلَصَةِ، وَكَانَ يُقَالُ لَهُ الْكَعْبَةُ الْيَمَانِيَةُ، أَوِ الْكَعْبَةُ الشَّأْمِيَّةُ

“ኻለሷህ” خَلَصَة ማለት “ቀሊሥ” قَلِسْ ማለት ነው፥ “ቀሊሥ” ከግሪኩ ኮይኔ “ኤክሌሺያ” εκκλεσια የመጣ ሲሆን በተለምዶ “ቤተ-ክርስቲያን” ይባል እንጂ “ጉባኤ” “ማኅበር” “ተጠርተው የወጡ” ማለት ነው። ይህንን ቤት ከከዕባ ጋር ለማመሳሰል “አል-ከዕበቱል የማኒያህ” الْكَعْبَةُ الْيَمَانِيَة ወይም “አል-ከዕበቱ አሽ-ሸእሚያህ” الْكَعْبَةُ الشَّأْمِيَّة ብሎታል። ይህ ንጉሥ ከእነ ጭፍሮቹ የአሏህ ቤት ለማፍረስ በ 570 ድኅረ-ልደት በዝሆን ጋልበው ወደ መካ መጡ፥ አሏህም እነዚህን የዝሆን ባለቤቶችን ተንኮል በጥፋት ውስጥ ከንቱ አደረገ፦
105፥1 “በዝሆኑ ባለቤቶች ጌታህ እንዴት እንደሠራ አላወቅህምን?” أَلَمْ تَرَ كَيْفَ فَعَلَ رَبُّكَ بِأَصْحَابِ الْفِيلِ
105፥2 ተንኮላቸውን በጥፋት ውስጥ ከንቱ አላደረገምን? أَلَمْ يَجْعَلْ كَيْدَهُمْ فِي تَضْلِيلٍ

አምላካችን አሏህ በእነርሱም ላይ ከተጠበሰ ጭቃ በኾነ ድንጋይ ማለትም በሸክላ”brick” የሚወረውሩባቸው መንጎች የኾኑን አዕዋፍን ላከ፥ እነርሱም ቅጠሉ እንደ ተበላ አዝመራም አደረጋቸው፦
105፥3 “በእነርሱም ላይ መንጎች የኾኑን አዕዋፍን ላከ”፡፡ وَأَرْسَلَ عَلَيْهِمْ طَيْرًا أَبَابِيلَ
105፥4 “ከተጠበሰ ጭቃ በኾነ ድንጋይ የምትወረውርባቸው የኾነችን አዕዋፍ”፡፡ تَرْمِيهِم بِحِجَارَةٍ مِّن سِجِّيلٍ
105፥5 “ቅጠሉ እንደ ተበላ አዝመራም አደረጋቸው”፡፡ فَجَعَلَهُمْ كَعَصْفٍ مَّأْكُولٍ

ከዚያ ጊዜ ጀምሮ ቁረይሾች ጊዜ ሲቆጥሩ እራሱ “ዓሙል ፊል” عامُ الْفِيلِ ማለትም “የዝሆን ዓመት” እያሉ ነበር።

ነጥብ ሁለት
“ሐበሻዊ ቢላል”
“አዛን” أَذَان የሚለው ቃል “አዚነ” أَذِنَ‎ ማለትም “ጠራ” ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን “ጥሪ” ማለት ነው፥ “ሙአዚን” مُؤَذِّن የሚለው ቃል ደግሞ “አዘነ” أَذَّنَ‎ ማለትም “ተጣራ” ከሚለው ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን “ጠሪ” ማለት ነው። የመጀመሪያው ሙአዚን ቢላል ኢብኑ ረባሕ ወይም ኢብን ሪያሕ”ረ.ዐ.” ሐበሻዊ ነው፥ ይህ ሶሓቢይ ለአላህ መልእክተኛም”ﷺ” ሙአዚን ነበረ። እኛም ሐበሾች በቢላል አዛን መገለጫችን ሆኗል፦
ሡነን አቢ ዳውድ መጽሐፍ 2, ሐዲስ 700
አሥ-ሣኢብ እንደተረከው፦ ”ለአላህ መልእክተኛም”ﷺ” ጠሪ አልነበራቸው አንድ ቢላል እንጂ”። عَنِ السَّائِبِ، قَالَ لَمْ يَكُنْ لِرَسُولِ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم إِلاَّ مُؤَذِّنٌ وَاحِدٌ بِلاَلٌ
ጃምዒ አት-ቲርሚዚይ መጽሐፍ 46, ሐዲስ 3936
አቢ ሁራይራህ እንደተረከው፦ “የአላህ መልእክተኛም”ﷺ” አሉ፦ ”ንግሥና ከቁረይሽ፣ ፍርድ ከአንሷር፣ አዛን ከሐበሻ፣ አማናህ ከየመን ነው”። عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ، قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم ‏ “‏ الْمُلْكُ فِي قُرَيْشٍ وَالْقَضَاءُ فِي الأَنْصَارِ وَالأَذَانُ فِي الْحَبَشَةِ وَالأَمَانَةُ فِي الأَزْدِ ‏”‏ ‏.‏ يَعْنِي الْيَمَنَ

ነጥብ ሦስት
“ንጉሥ አርማህ”
“ንጉሥ አርማህ” በነቢያችን”ﷺ” ሐዲስ “አስሐማህ አን-ነጃሺይ” أَصْحَمَةَ النَّجَاشِيِّ የሚባለው ነው፥ ይህ ንጉሥ የነቢያችን”ﷺ” ባልደረቦች ከ 615–616 ድኅረ-ልደት ተቀብሎ አስተናግዷል። ከዚያ ባሻገር ከመሥለምም አልፎ ጻዲቅ ሰው እንደሆነ ነቢያችን”ﷺ” ነግረውናል፦
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 23, ሐዲስ 78
ጃቢር ኢብኑ ዐብደሏህ”ረ.ዐ.” ሰምቶ እንደተረከው፦ “ነቢዩም”ﷺ” እንዲህ አሉ፦ ”ዛሬ ከሐበሻህ ጻዲቅ ሰው ሞቷል፥ ተነሱ! የግንዘት ጸሎት አድርጉ!”። أَنَّهُ سَمِعَ جَابِرَ بْنَ عَبْدِ اللَّهِ ـ رضى الله عنهما ـ يَقُولُ قَالَ النَّبِيُّ صلى الله عليه وسلم ‏ “‏ قَدْ تُوُفِّيَ الْيَوْمَ رَجُلٌ صَالِحٌ مِنَ الْحَبَشِ فَهَلُمَّ فَصَلُّوا عَلَيْهِ ‏”‌‏
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 63, ሐዲስ 103
ጃቢር”ረ.ዐ.” እንደተረከው፦ “አን-ነጃሺይ በሞተ ጊዜ “ነቢዩም”ﷺ” እንዲህ አሉ፦ ”ዛሬ ጻዲቅ ሰው ሞቷል፥ ተነሱ! ለወንድማችሁ ለአስሐማህ የግንዘት ጸሎት አድርጉ!”። عَنْ جَابِرٍ ـ رضى الله عنه ـ قَالَ النَّبِيُّ صلى الله عليه وسلم حِينَ مَاتَ النَّجَاشِيُّ ‏ “‏ مَاتَ الْيَوْمَ رَجُلٌ صَالِحٌ، فَقُومُوا فَصَلُّوا عَلَى أَخِيكُمْ أَصْحَمَةَ

“ሷሊሕ” صَالِح ማለት “ጻዲቅ” ማለት ነው፥ ንጉሡ ለሶሓባዎች ወንድም የተባለው በስጋ የሆነ ወንድምነት ሳይሆን ኢሥላማዊ ወንድምነት ነው። በኢሥላም “ሶላቱል ጀናዛህ” صَلَاة الجَنَازَة ማለትም “የግንዘት ጸሎት” የሚደረገው ለሙሥሊም ብቻ ነው፥ ለንጉሥ አርማህ ደግሞ የሶላቱል ጀናዛህ ክፍል የሆነው “ሶላቱል ጋኢብ” صَلَاة الغَائِبٌ ማለትም “የሩቅ ጀናዛህ” ተደርጓል፦
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 63, ሐዲስ 105
ጃቢር አብኑ ዐብደሏህ”ረ.ዐ.” እንደተረከው፦ ”ነቢዩም”ﷺ” አስሐማህ አን-ነጃሺይ ላይ የግንዘት ጸሎት አድርገዋል፥ አራት ተክቢራህ በእርሱ ላይ አድርገዋል”። عَنْ جَابِرِ بْنِ عَبْدِ اللَّهِ ـ رضى الله عنهما أَنَّ النَّبِيَّ صلى الله عليه وسلم صَلَّى عَلَى أَصْحَمَةَ النَّجَاشِيِّ، فَكَبَّرَ عَلَيْهِ أَرْبَعًا‏

ነጥብ አራት
“ዙ አሥ-ሡወይቀተይን”
ከየእጁጅ መእጁጅ በኃላ “አሏህ” “አሏህ” የሚል ሲጠፋ እና ቁርኣን ከሰዎች ልብ ሲወሰድ ከሐበሻህ የሚመጣ ሰው ዙ አሥ-ሡወይቀተይን የአሏህን ቤት ከዕባህን ያፈርሳል፦
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 25, ሐዲስ 82
አቢ ሁረይራህ”ረ.ዐ.” እንደተረከው፦ “የአሏህ መልእክተኛም”ﷺ” እንዲህ አሉ፦ “ከሐበሻህ የሆነ ዙ አሥ-ሡወይቀተይን ከዕባህን ያፈርሳል”። أَنَّ أَبَا هُرَيْرَةَ ـ رضى الله عنه ـ قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم ‏ “‏ يُخَرِّبُ الْكَعْبَةَ ذُو السُّوَيْقَتَيْنِ مِنَ الْحَبَشَةِ ‏”‌‏
ኢማም ሙሥሊም መጽሐፍ 54, ሐዲስ 73
አቢ ሁረይራህ እንደተረከው፦ “የአሏህ መልእክተኛም”ﷺ” እንዲህ አሉ፦ “ከሐበሻህ የሆነ ዙ አሥ-ሡወይቀተይን የአሏህ ዐዘ ወጀልን ቤት ያፈርሳል”። عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ، أَنَّ رَسُولَ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم قَالَ ‏ “‏ ذُو السُّوَيْقَتَيْنِ مِنَ الْحَبَشَةِ يُخَرِّبُ بَيْتَ اللَّهِ عَزَّ وَجَلَّ ‏”‏ ‏

“ዙ አሥ-ሡወይቀተይን” ذُو السُّوَيْقَتَيْنِ ማለት “ባለ ሁለት ትንሽ ቅልጥም” ወይም “ባለ ሁለት አጭር ቅልጥም” ማለት ነው፥ በተንኮል የአሏህን ቤት አፍርሶ የከዕባን ሀብት ለማውጣት የሚፈልግ ይህ ሰው ነው። እርሱ እንደዛ ነው ማለት ሐበሻውያን እንተናኮላለን ማለት አይደለም፥ ነቢያችን”ﷺ” ለሙሥሊሙ ማኅበረሰብ፦ “ሐበሻውያንን እስካልኳችሁ ድረስ አትንኳቸው” ብለዋል፦
ሡነን አቢ ዳውድ መጽሐፍ 39, ሐዲስ 19
ዐብደሏህ ኢብኑ ዐምር እንደተረከው፦ “ነቢዩም”ﷺ” እንዲህ አሉ፦ “ሐበሻውያንን እስካልኳችሁ ድረስ አትንኳቸው፥ የከዕባን ሀብት ለማውጣት የሚፈልግ ከሐበሻህ የሆነ ዙ አሥ-ሡወይቀተይን ቢሆን እንጂ ሌላ የለም”። عَنْ عَبْدِ اللَّهِ بْنِ عَمْرٍو، عَنِ النَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم قَالَ ‏ “‏ اتْرُكُوا الْحَبَشَةَ مَا تَرَكُوكُمْ فَإِنَّهُ لاَ يَسْتَخْرِجُ كَنْزَ الْكَعْبَةِ إِلاَّ ذُو السُّوَيْقَتَيْنِ مِنَ الْحَبَشَةِ ‏”‏

አሏህ እኛ ሐበሻውያንን የነቢዩ”ﷺ” ሡናህ የምንተገብር ያድርገን! አሚን።

ከዐቃቤ እሥልምና ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
ዓሹራእ

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ፥ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።

59፥7 መልክተኛውም የሰጣችሁን ማንኛውንም ነገር ያዙት፡፡ ከእርሱም የከለከላችሁን ነገር ተከልከሉ። وَمَا آتَاكُمُ الرَّسُولُ فَخُذُوهُ وَمَا نَهَاكُمْ عَنْهُ فَانتَهُوا

“ወር” የሚለው ቃል “ሸህር” شَهْر ሲሆን በቁርኣን 12 ጊዜ ሰፍሮ ይገኛል፦ (1ኛ. 2:185 2ኛ. 2፥194 3ኛ. 2፥196 4ኛ. 2፥217 5ኛ. 5፥2 6ኛ. 5፥97 7ኛ. 9፥36 8ኛ. 9:37 9ኛ. 34:12 10ኛ.46፥15 11ኛ.58፥4 12ኛ.97፥3)
የሚያጅበው የወሮች ቁጥር አላህ ዘንድ በአሏህ መጽሐፍ ዐሥራ ሁለት ወር ነው፥ እነዚህም፦
1ኛ ወር ሙሐረም
2ኛ ወር ሰፈር
3ኛ ወር ረቢዑል-አወል
4ኛ ወር ረቢዑ-ሣኒ
5ኛ ወር ጀማዱል-አወል
6ኛ ወር ጀማዱ-ሣኒ
7ኛ ወር ረጀብ
8ኛ ወር ሻዕባን
9ኛ ወር ረመዷን
10ኛ ወር ሸዋል
11ኛ ወር ዙል-ቀዒዳህ
12ኛ ወር ዙል-ሒጃህ ናቸው፦
9፥36 የወሮች ቁጥር አላህ ዘንድ በአላህ መጽሐፍ ውስጥ ሰማያትንና ምድርን በፈጠረበት ቀን ዐሥራ ሁለት ወር ነው፡፡ ከእነርሱ አራቱ የተከበሩ ናቸው፡፡ إِنَّ عِدَّةَ الشُّهُورِ عِندَ اللَّهِ اثْنَا عَشَرَ شَهْرًا فِي كِتَابِ اللَّهِ يَوْمَ خَلَقَ السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضَ مِنْهَا أَرْبَعَةٌ حُرُمٌ

ከእነዚህ 12 ወራት አራቱ የተከበሩ ወሮች፦
1ኛው ወር ሙሐረም
7ኛው ወር ረጀብ
11ኛው ወር ዙል-ቀዒዳህ
12ኛው ወር ዙል-ሒጃህ ናቸው፦
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 65 ሐዲስ 4662
አቡበከር”ረ.ዐ” እንደተረከው፦ ነቢዩም”ﷺ” አሉ፦ *”ዘመን አላህ ሰማያትን እና ምድር በፈጠረበት ቀን የቀድሞ ሁኔታ ይመለሳል፥ አንድ ዓመት ዐሥራ ሁለት ወር ነው። ከእነርሱም አራቱ የተከበሩ ናቸው፥ ሦስቱ ተከታታይ ዙል-ቀዒዳህ፣ ዙል-ሒጃህ፣ ሙሐረም ናቸው፥ አራተኛው በጀማዱ-ሣኒ እና በሻዕባን መካከል ያለው ረጀብ ነው። عَنْ أَبِي بَكْرَةَ، عَنِ النَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم قَالَ ‏ “‏ إِنَّ الزَّمَانَ قَدِ اسْتَدَارَ كَهَيْئَتِهِ يَوْمَ خَلَقَ اللَّهُ السَّمَوَاتِ وَالأَرْضَ، السَّنَةُ اثْنَا عَشَرَ شَهْرًا مِنْهَا، أَرْبَعَةٌ حُرُمٌ، ثَلاَثٌ مُتَوَالِيَاتٌ، ذُو الْقَعْدَةِ وَذُو الْحِجَّةِ وَالْمُحَرَّمُ وَرَجَبُ مُضَرَ الَّذِي بَيْنَ جُمَادَى وَشَعْبَانَ

ከእነዚህ አራት ወራት ደግሞ "ሙሐረም" ክብር ያለው የአሏህ ወር ነው፦
ጃሚዒ አት-ቲርሚዚይ መጽሐፍ 8 ሐዲስ 59
አቢ ሁረይራህ”ረ.ዐ” እንደተረከው፦ “የአሏህ መልክእተኛ”ﷺ” እንዲህ ብለዋል፡- ”ከረመዷን ቀጥሎ ከጾሞች ሁሉ በላጩ የአሏህ ወር የሆነው ሙሐረም ነው። عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ، قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم ‏ “‏ أَفْضَلُ الصِّيَامِ بَعْدَ صِيَامِ شَهْرِ رَمَضَانَ شَهْرُ اللَّهِ الْمُحَرَّم

“አሽ-ሸምሢያህ” الشَمْسِيَّة አቆጣጠር 365 ቀናት የያዘ የፀሐይ አቆጣጠር”solar calended” ሲሆን “አል-ቀመርያ” الْقَمَرِيَّة ደግሞ 354 ቀናትን የያዘ የጨረቃ አቆጣጠር”lunar calender” ነው፥ በጨረቃ አቆጣጠር አዲስ ጨረቃ ሲታይ አዲሱ ወር ሙሐረም ይጀምራል። የጨረቃ አቆጣጠር የዓመታትን ቁጥር መቀየሪያ፣ ጾምን መጾሚያ እና ሐጅን ማድረጊያ ምልክት ነው፦
10፥5 *እርሱ ያ ፀሐይን አንጻባራቂ ጨረቃንም አብሪ ያደረገ ነው፡፡ የዓመታትን ቁጥርና ሒሳብን ታውቁ ዘንድም ለእርሱ መስፈሪያዎችን የለካ ነው*፡፡ አላህ ይህንን በእውነት እንጂ በከንቱ አልፈጠረውም፡፡ ለሚያውቁ ሕዝቦች አንቀጾችን ያብራራል፡፡ هُوَ الَّذِي جَعَلَ الشَّمْسَ ضِيَاءً وَالْقَمَرَ نُورًا وَقَدَّرَهُ مَنَازِلَ لِتَعْلَمُوا عَدَدَ السِّنِينَ وَالْحِسَابَ ۚ مَا خَلَقَ اللَّهُ ذَٰلِكَ إِلَّا بِالْحَقِّ ۚ يُفَصِّلُ الْآيَاتِ لِقَوْمٍ يَعْلَمُون
2፥189 *ከለጋ ጨረቃዎች ይጠየቁሃል፤ “እነርሱ ለሰዎች ጥቅም ለሐጅም ማወቂያ፥ ለጊዜያቶች ምልክቶች ናቸው” በላቸው*፡፡ يَسْأَلُونَكَ عَنِ الْأَهِلَّةِ ۖ قُلْ هِيَ مَوَاقِيتُ لِلنَّاسِ وَالْحَج
ኢማም ሙሥሊም መጽሐፍ 13, ሐዲስ 170
አል-ሐከም ኢብኑል አዕረኽ እንደተረከው፦ “ወደ ኢብኑ ዐባሥ”ረ.ዐ” ስሄድ እርሱ በዘምዘም ምንጭ አቅራቢያ በልብሱ ተቀምጦ ነበር፤ እኔም ለእርሱ፦ *” ስለ ዓሹራ ጾም ንገረኝ! አልኩት፤ እርሱም፦ “የሙሐረም አዲስ ጨረቃ ስታይ ቁጠር፥ በዘጠነኛው ቀን ጾም መሆኑን አጢን” አለኝ። እኔም ለእርሱ፦ “ስለዚህ የአላህ መልእክተኛ”ﷺ” ያጤኑት ነበር? አልኩት፤ እርሱም፦ “አዎ” አለኝ*። عَنِ الْحَكَمِ بْنِ الأَعْرَجِ، قَالَ انْتَهَيْتُ إِلَى ابْنِ عَبَّاسٍ – رضى الله عنهما – وَهُوَ مُتَوَسِّدٌ رِدَاءَهُ فِي زَمْزَمَ فَقُلْتُ لَهُ أَخْبِرْنِي عَنْ صَوْمِ عَاشُورَاءَ ‏.‏ فَقَالَ إِذَا رَأَيْتَ هِلاَلَ الْمُحَرَّمِ فَاعْدُدْ وَأَصْبِحْ يَوْمَ التَّاسِعِ صَائِمًا ‏.‏ قُلْتُ هَكَذَا كَانَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم يَصُومُهُ قَالَ نَعَمْ

ከሙሐረም ወር ውስጥ ደግሞ አሥረኛው ቀን በላጭ ቀን ነው፥ ይህ ዐሥረኛው ቀን “ዓሹራእ” ይባላል። “ዓሹራእ” عَاشُورَاء‎ የሚለው ቃል “ዐሽር” عَشْرٍ ማለትም “ዐሥር” ከሚል ቃል የመጣ ሲሆን “ዐሥረኛ” ማለት ነው፥ ይህ ቀን በፈቃደኝነት የሚፆምበት ቀን ነው፦
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 30 ሐዲስ 107
ዓኢሻህ”ረ.ዐ.” እንደተረከችው፦ *”በጃህሊያህ ጊዜ የዓሹራን ቀን ቁሬይሾች ይጾሙ ነበር፥ በዚህ ቀን የአላህ መልእክተኛም”ﷺ” ወደ መዲና በመጡ ጊዜ ይፆሙ እና እንዲፆም ያዙ ነበር። የረመዷን ወር ጾም በተደነገገ ጊዜ ግን የዓሹራእ ቀን ጾም ያሻው የሚጾመው፥ ያሻው የማይጾመው ሆነ*። عَنْ عَائِشَةَ ـ رضى الله عنها ـ قَالَتْ كَانَ يَوْمُ عَاشُورَاءَ تَصُومُهُ قُرَيْشٌ فِي الْجَاهِلِيَّةِ، وَكَانَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم يَصُومُهُ، فَلَمَّا قَدِمَ الْمَدِينَةَ صَامَهُ، وَأَمَرَ بِصِيَامِهِ، فَلَمَّا فُرِضَ رَمَضَانُ تَرَكَ يَوْمَ عَاشُورَاءَ، فَمَنْ شَاءَ صَامَهُ، وَمَنْ شَاءَ تَرَكَهُ‏.‏
ጥቂት ቁሬይሾች በመዲና ላይ ያሉት አይሁዳዊያን ይህንን ቀን ይፆሙ ነበር፥ ይህ ቀን የኢሥራዒል ልጆች ከፈርዖን ነጻ የወጡበት ቀን ነው፦
ኢማም ሙሥሊም መጽሐፍ 13 ሐዲስ 162
ኢብኑ ዐባሥ”ረ.ዐ.” እንደተረከው፦ *”የአላህ መልእክተኛ”ﷺ” ወደ መዲና በመጡ ጊዜ አይሁዳውያን የዓሹራን ቀን ሲጾሙ አጤኑ፤ አይሁዳውያን ስለዚያ ቀንም ይጠይቁና፦ “አላህ ለሙሳ እና ለኢሥራዒል ልጆች በፈርዖን ላይ ድል የሰጠበት ነው” ብለው ይመልሱ ነበር። ነቢዩም”ﷺ”፦ “ከእናንተ ይልቅ እኛ ለሙሳ ቅርብ ነን” አሉ፤ ይህ ቀን እንዲጾም አዘዙን*። عَنِ ابْنِ، عَبَّاسٍ – رضى الله عنهما – قَالَ قَدِمَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم الْمَدِينَةَ فَوَجَدَ الْيَهُودَ يَصُومُونَ يَوْمَ عَاشُورَاءَ فَسُئِلُوا عَنْ ذَلِكَ فَقَالُوا هَذَا الْيَوْمُ الَّذِي أَظْهَرَ اللَّهُ فِيهِ مُوسَى وَبَنِي إِسْرَائِيلَ عَلَى فِرْعَوْنَ فَنَحْنُ نَصُومُهُ تَعْظِيمًا لَهُ ‏.‏ فَقَالَ النَّبِيُّ صلى الله عليه وسلم ‏ “‏ نَحْنُ أَوْلَى بِمُوسَى مِنْكُمْ ‏”‏ ‏.‏ فَأَمَرَ بِصَوْمِهِ

ሚሽነሪዎች በኢሥላም ያሉትን ሕግና ሥርዓት በመጽሐፋቸው መኖሩን ይጠይቃሉ፥ ከሌለ "ለምን የለም? ብለው ይጠይቃሉ። ካለ ደግሞ ያው "ተኮረጀ" ይላሉ፥ ግን የሚገርመው ነገር ስለ ዓሹራእ ቀን መጽሐፋቸው ላይ እያለ እንደማያነቡት ነው፦
ዘሌዋውያን 23፥34 ለእስራኤል ልጆች እንዲህ ብለህ ንገራቸው፦ *በዚህ በሰባተኛው ወር ከአሥራ አምስተኛው ቀን ጀምሮ ሰባት ቀን ለእግዚአብሔር የዳስ በዓል ይሆናል*።
ዘሌዋውያን 23፥42-43 ሰባት ቀን በዳሶች ውስጥ ትቀመጣላችሁ፤ *ከግብፅ ምድር ባወጣኋቸው ጊዜ የእስራኤልን ልጆች በዳስ ውስጥ እንዳስቀመጥኋቸው የልጅ ልጆቻችሁ ያውቁ ዘንድ፥ በእስራኤል ያሉት የአገር ልጆች ሁሉ በዳስ ውስጥ ይቀመጡ*፤ እኔ እግዚአብሔር አምላካችሁ ነኝ።

“ከግብፅ ምድር ባወጣኋቸው ጊዜ” የሚለው ኃይለ-ቃል ይሰመርበት! ያ ወር በዕብራውያን አቆጣጠር ሰባተኛው ወር ሲሆን በእኛ ሙሐረም ነው፥ የሚያጅበው በዚህ ወር በዐሥረኛው ቀን እንዲፆሙ መታዘዙ ነው፦
ዘኍልቍ 29፥7 ከዚህም *ከሰባተኛው ወር በአሥረኛው ቀን የተቀደሰ ጉባኤ ይሁንላችሁ፤ ሰውነታችሁን አስጨንቁት*፤ ከሥራ ሁሉ ምንም አታድርጉ።
ዘሌዋውያን 16፥30 *በሰባተኛው ወር ከወሩም በአስረኛው ቀን ራሳችሁን አስጨንቋት*፥ የአገር ልጅም በእናንተ መካከል የተቀመጠም እንግዳ ሥራን ሁሉ አትሥሩበት፤

“እራሳችሁን አስጨንቋት” ለሚለው ቃል የገባው “ወኢንኒተም” וְעִנִּיתֶ֖ם ሲሆን በኢንግሊሽ ትርጉም እና የተለያዩ ማብራሪያዎች ፆምን ታሳቢ እና ዋቢ ያደረገ እንደሆነ ገልጸዋል፥ አይሁዳውያን ይህንን ቀን እንደሚፆሙ እሙንና ቅቡል ነው። እኛም ነቢያችን”ﷺ” የሰጡንን ነገር ሁሉ እንድንይዝ አምላካችን አሏህ በተከበረው ቃሉ ነግሮናል፦
59፥7 መልክተኛውም የሰጣችሁን ማንኛውንም ነገር ያዙት፡፡ ከእርሱም የከለከላችሁን ነገር ተከልከሉ። وَمَا آتَاكُمُ الرَّسُولُ فَخُذُوهُ وَمَا نَهَاكُمْ عَنْهُ فَانتَهُوا

ስለዚህ በዚህ ቀን መፆሙ ሙስተሐብ ነው፥ በዚህ ቀን መፆሙ ያለው ትሩፋት የአሏህ መልዕክተኛ”ﷺ” ተጠይቀው “ያለፈውን አንድ ዓመት ወንጀል ያስምራል” ብለዋል፦
ሡነን ኢብኑ ማጃህ መጽሐፍ 7, ሐዲስ 1810
አቢ ቀታዳህ እንዳስተላለፉት፦ የአላህ መልእክተኛ”ﷺ” አሉ፦ *”የዓሹራእ ቀን መጾም ያለፈውን አንድ ዓመት ወንጀል ከአላህ ያስተሰርያል”*። عَنْ أَبِي قَتَادَةَ، قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ ـ صلى الله عليه وسلم ـ ‏ “‏ صِيَامُ يَوْمِ عَاشُورَاءَ إِنِّي أَحْتَسِبُ عَلَى اللَّهِ أَنْ يُكَفِّرَ السَّنَةَ الَّتِي قَبْلَهُ

አምላካችን አሏህ ከዓሹራእ ቀን ከሚገኝ ትሩፋት እና ስርጉት ተቋዳሽ ያርገን! አሚን።

ከዐቃቤ እሥልምና ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
የባይብል ግጭት

ጳውሎስ፦ "ከሕግ ሥራ የሆኑት ሁሉ በእርግማን በታች ናቸውና፥ ማንም በእግዚአብሔር ፊት በሕግ እንዳይጸድቅ ግልጥ ነው" ይለናል፦
ገላትያ 3፥11-12 ""ከሕግ ሥራ የሆኑት ሁሉ በእርግማን በታች ናቸውና"".. ጻድቅ በእምነት ይኖራል ተብሎአልና ማንም ""በእግዚአብሔር ፊት በሕግ እንዳይጸድቅ ግልጥ ነው""።

በተቃራኒው ያዕቆብ፦ "ሰው በእምነት ብቻ ሳይሆን በሥራ እንዲጸድቅ ታያላችሁ" ይለናል፦
ያዕቆብ 2፥24 ሰው በእምነት ብቻ ሳይሆን በሥራ እንዲጸድቅ ታያላችሁ።

ስለዚህ ከሕግ ሥራ የሆኑት ሁሉ በእርግማን በታች ስለሆኑ በእግዚአብሔር ፊት በሕግ ሥራ ማንም አይጸድቅም ጳውሎስ ሲለን፥ ያዕቆብ ደግሞ ሰው በሕግ ሥራ እንዲጸድቅ ታያላችሁ ይለናል። ይህንን ግጭት ለማስቀረት የአትናቴዎስ እና የማርቲን ሉተር የቀኖና መጽሐፍት ውስጥ የያዕቆብ መልእክት አይካተትም።
የቱ ነው ትክክል? "ማንም በእግዚአብሔር ፊት በሕግ እንዳይጸድቅ ግልጥ ነው" የሚለው ጳውሎስ ወይስ "ሰው በእምነት ብቻ ሳይሆን በሥራ እንዲጸድቅ ታያላችሁ" የሚለው ያዕቆብ?

ከዐቃቤ እሥልምና ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom
ስእለት

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

19፥26 *«ብይም፣ ጠጭም፣ ተደሰችም፣ ”እኔ ለአልረሕማን ዝምታን ተስያለሁ፤ ዛሬም ሰውን በፍጹም አላነጋግርም» በይ”*፡፡ فَكُلِي وَاشْرَبِي وَقَرِّي عَيْنًا ۖ فَإِمَّا تَرَيِنَّ مِنَ الْبَشَرِ أَحَدًا فَقُولِي إِنِّي نَذَرْتُ لِلرَّحْمَـٰنِ صَوْمًا فَلَنْ أُكَلِّمَ الْيَوْمَ إِنسِيًّا

“ነዝር” نَّذْر የሚለው ቃል "ነዘረ" نَّذَرَ‎ ማለትም "ተሳለ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን “ስእለት” ማለት ነው። "ነዝር" نَّذْر አንድ ሙእሚን በራሱ ተነሳሽነት በልቡ ነይቶ ለአሏህ የሚያቀርበው ብፅዓት ነው፥ “ብፅዓት” ማለት “ቃል መግባት” ማለት ነው። “ስእለት” የሚለው የግዕዙ ቃልም “ሰአለ” ማለትም “ለመነ” ወይም “ተማጸነ” ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን “ልመና” ወይም “ተማጽንዖ” ማለት ነው፥ ለአሏህ ቃል በመግባት አንድ ጉዳይ ስንለምንና ስንማጸን ያ ልመና ወይም ተማጽንዖ "ስእለት" ይሰኛል። ስእለት ያለማንም ጣልቅ ገብነት በራስ ተነሳሽነት ለአሏህ የሚደረግ አምልኮ ከሆነ፤ ለምንድን ነው አሏህ በመልአኩ መርየምን፦ “እኔ ለአልረሕማን ዝምታን ተስያለሁ፥ ዛሬም ሰውን በፍጹም አላነጋግርም» በይ” ያላት? ይህንን ጥያቄ በሰከነና በሰላ ልብ ማየት ያስፈልጋል፦
19፥26 «ብይም፣ ጠጭም፣ ተደሰችም፡፡ *”እኔ ለአልረሕማን ዝምታን ተስያለሁ፤ ዛሬም ሰውን በፍጹም አላነጋግርም» በይ”*፡፡ فَكُلِي وَاشْرَبِي وَقَرِّي عَيْنًا ۖ فَإِمَّا تَرَيِنَّ مِنَ الْبَشَرِ أَحَدًا فَقُولِي إِنِّي نَذَرْتُ لِلرَّحْمَـٰنِ صَوْمًا فَلَنْ أُكَلِّمَ الْيَوْمَ إِنسِيًّا

እንደሚታወቀው መርየም ያረገዘችው በጋብቻ ሳይሆን በአላህ ተአምር ነው፥ ወደ ዘመዶቿ ስትሄድ እርግዝናዋን በአላህ ተአምር እንደሆነ ብትናገር ስለማይቀበሏት በእርግዝናው ጉዳይ ላይ ዝምታን በመምረጧ ከጠየቋት ሰውን በፍጹም እንዳታናግር አሏህ አዘዛት። ይህም ትእዛዝ የአሁን ትእዛዛዊ ግስ “ቁሊ” قُولِي ማለትም “በይ” የሚል ነው፥ ነገር ግን እዚህ አንቀጽ ላይ የአሁን ትእዛዛዊ ግስ "ነዚሪ" نَّزِرِي ማለትም “ተሳይ” የሚል ሽታው እንኳን የለም። ስለዚህ ከመነሻው፦ “አሏህ ስእለት እንድትሳል አሳቡን አቀረበላት” የሚለው የሚሽነሪዎች አጉራ ዘለል ትችች አርቲ ቡርቲና ቶራ ቦራ ነው።
ሲቀጥል “ተስያለው” የሚለው ቃል “ነዘርቱ” نَذَرْتُ ሲሆን አላፊ ግስ መሆኑ በራሱ አሏህ እንዳትናገር ለእርሷ ከመናገሩ በፊት መሳሏን ፍንትውና ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ ነው።
ሢሰልስ አንድ ሰው ሳይበላ “በልቻለው” በል! ብለው ትርጉም አይኖረውን ማስዋሸትም ነው፥ ካልበላ “እበላለው” በል! ነው የሚባለው።
ሲያረብብ ስእለት አምልኮ ስለሆነ ልጇ ከመወለዱና ከመረገዙ በፊት “በሕፃንነቱ ሰዎቹን ያነጋግራል” የሚል ትንቢት ስላለ ዝምታን ተስላለች፦
3፥46 *«በሕፃንነቱ እና በጎልማሳነቱ ሰዎቹን ያነጋግራል፡፡ ከመልካሞቹም ነው»* አላት፡፡ وَيُكَلِّمُ النَّاسَ فِي الْمَهْدِ وَكَهْلًا وَمِنَ الصَّالِحِين

ስለዚህ ወደ እነርሱ ስትሄድ በዚህ ነጥብ ላይ፦ “እኔ ለአልረሕማን ዝምታን ተስያለሁ፤ ዛሬም ሰውን በፍጹም አላነጋግርም” በማለት ላቀረቡላት የእግዝናዋ ጥያቄ ወደ ልጇ በምልክት አመራች፥ እነርሱም፦ “በአንቀልባ ያለን ሕጻን እንዴት እናናግራለን!” አሉ። ያኔ ሕፃኑ፦ “እኔ የአላህ ባሪያ ነኝ፥ መጽሐፍን ሰጥቶኛል ነቢይም አድርጎኛል” አለ፦
19፥29 *ወደ እርሱም ጠቀሰች፡፡ «በአንቀልባ ያለን ሕጻን እንዴት እናናግራለን!» አሉ”*፡፡ فَأَشَارَتْ إِلَيْهِ ۖ قَالُوا كَيْفَ نُكَلِّمُ مَن كَانَ فِي الْمَهْدِ صَبِيًّا
19፥30 *”ሕፃኑም አለ «እኔ የአላህ ባሪያ ነኝ፡፡ መጽሐፍን ሰጥቶኛል ነቢይም አድርጎኛል»*፡፡ قَالَ إِنِّي عَبْدُ اللَّهِ آتَانِيَ الْكِتَابَ وَجَعَلَنِي نَبِيًّا

ነቢያችን”ﷺ” ይህ ክስተት ሲከሰትና ሲከናወን በቦታው አልነበሩም፥ ነገር ግን ያ በሰማያትና በምድር ውስጥ ያለን ምስጢር የሚያውቀው የዓለማቱ ጌታ አሏህ ተረከላቸው፦
25፥6 *”ያ በሰማያትና በምድር ውስጥ ያለን ምስጢር የሚያውቀው አወረደው*፡፡ እርሱ መሓሪ አዛኝ ነውና” በላቸው፡፡ قُلْ أَنزَلَهُ الَّذِي يَعْلَمُ السِّرَّ فِي السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضِ ۚ إِنَّهُ كَانَ غَفُورًا رَّحِيمًا
3፥44 *”ይህ ወደ አንተ የምናወርደው የኾነ ከሩቅ ወሬዎች ነው፡፡ መርየምንም ማን እንደሚያሳድግ ብርኦቻቸውን ለዕጣ በጣሉ ጊዜ እነርሱ ዘንድ አልነበርክም፡፡ በሚከራከሩም ጊዜ እነርሱ ዘንድ አልነበርክም”*፡፡ ذَٰلِكَ مِنْ أَنبَاءِ الْغَيْبِ نُوحِيهِ إِلَيْكَ ۚ وَمَا كُنتَ لَدَيْهِمْ إِذْ يُلْقُونَ أَقْلَامَهُمْ أَيُّهُمْ يَكْفُلُ مَرْيَمَ وَمَا كُنتَ لَدَيْهِمْ إِذْ يَخْتَصِمُونَ

“እነርሱ ዘንድ አልነበርክም” የሚለው ኃይለ-ቃል ይሰመርበት! እርሳቸው ባልነበሩበት ጊዜ የነበረውን ክስተት አምላካችን አሏህ እየነገራቸው መሆኑን ቁልጭ አርጎ የሚያሳይ ነው። “የምናወርደው” የሚለው ኃይለ-ቃል ደግሞ ከላይ ስለ መርየም እና በእርሷ ዙሪያ ያሉት የሩቅ ወሬዎች ለነቢያችን”ﷺ” የተወረደ ወሕይ መሆኑን ፍንትው አርጎ ያሳያል።
ሚሽነሪዎች ሆይ! ከርሞ ጥጃ አድሮ ቃሪያ በመሆን እንደ በቀቀን መደጋገም ተላላነት ነው፥ የቁም ነገሩን ዚቅ እና የጉዳዩ አውራ ካለማጤን የሚመጣ የልጅነት ክፉ ጠባይ ነውና የተውባህ በሩ ሳይዘጋ በአሏህ እና በመልክተኛውም፥ በዚያም ባወረደው ቁርኣን እመኑ! አሏህም በምትሠሩት ሁሉ ውስጠ ዐዋቂ ነው፦
64፥8 *”በአላህ እና በመልክተኛውም፥ በዚያም ባወረድነው ብርሃን እመኑ፡፡ «አላህም በምትሠሩት ሁሉ ውስጠ ዐዋቂ ነው»* በላቸው፡፡ فَآمِنُوا بِاللَّهِ وَرَسُولِهِ وَالنُّورِ الَّذِي أَنزَلْنَا ۚ وَاللَّهُ بِمَا تَعْمَلُونَ خَبِير

ከዐቃቤ እሥልምና ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
የቀድሞዎቹ ተረት

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

8፥31 *አንቀጾቻችንም በእነርሱ ላይ በተነበቡ ጊዜ «በእርግጥ ሰምተናል፤ በሻን ኖሮ የዚህን ብጤ ባልን ነበር፤ ይህ የመጀመሪያዎቹ ሰዎች ጽሑፍ ተረቶች እንጂ ሌላ አይደለም» ይላሉ*፡፡ وَإِذَا تُتْلَىٰ عَلَيْهِمْ آيَاتُنَا قَالُوا قَدْ سَمِعْنَا لَوْ نَشَاءُ لَقُلْنَا مِثْلَ هَـٰذَا ۙ إِنْ هَـٰذَا إِلَّا أَسَاطِيرُ الْأَوَّلِينَ

ብዙ ጊዜ ሚሽነሪዎች፦ "ቁርኣን የቀድሞ ሰዎች ተረት ነው" ይላሉ፤ ግን ይህ የሚያሳየው በደንብ አነማንበባቸው እና አንቀጽ የወረደበትን ምክንያት ጠንቅቆ ካለመረዳት የሚመጣ የተሳከረ ምልከታ ነው፤ እስቲ ይህንን ነጥብ በሰከነና በሰላ አዕምሮ እንመልከት። "ቂያማህ" قِيَٰمَة የሚለው ቃል "ቃመ" قَامَ ማለትም "ተነሣ" "ቆመ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "ትንሣኤ" ማለት ነው፤ ሰው ከሞተ እና ከበሰበሰ በኃላ በአላህ ጥበብ ተመልሶ ይቀሰቀሳል፤ አምላካችም አላህ ይህ የትንሣኤ ቀን እንደሚያመጣው አጽንኦት ለመስጠት በትንሳኤ ቀን ምሏል፦
23፥16 *ከዚያም እናንተ በትንሣኤ ቀን ትቀሰቀሳላችሁ*፡፡ ثُمَّ إِنَّكُمْ يَوْمَ الْقِيَامَةِ تُبْعَثُونَ
75፥1 ነገሩ ከሓዲዎች እንደሚሉት አይደለም፡፡ *በትንሣኤ ቀን እምላለሁ*፡፡ لَا أُقْسِمُ بِيَوْمِ الْقِيَامَةِ

ነገር ግን ይህንን የሞቶ መቀስቀስ እሳቤ ቁርኣን በወረደበት ጊዜ የነበሩት ሙሽሪኮች አስተባበሉ፤ እነዚያ በትንሣኤ የካዱትን በፍጹም የማይቀሰቀሱ መኾናቸውን አሰቡ፤ ይልቁንም እንዴት አጥንቶችና ብስብሶች በኾን ጊዜ እኛ አዲስ ፍጥረት ኾነን በእርግጥ ተቀስቃሾች ነንን? አሉ፦
64፥7 *እነዚያ የካዱትን በፍጹም የማይቀሰቀሱ መኾናቸውን አሰቡ፡፡ «አይደለም በጌታዬ እምላለሁ፡፡ በእርግጥ ትቀሰቀሳላችሁ፡፡ ከዚያም በሠራችሁት ሁሉ ትነገራላችሁ፡፡ ይህም በአላህ ላይ ቀላል ነው፡፡»* በላቸው፡፡زَعَمَ الَّذِينَ كَفَرُوا أَن لَّن يُبْعَثُوا ۚ قُلْ بَلَىٰ وَرَبِّي لَتُبْعَثُنَّ ثُمَّ لَتُنَبَّؤُنَّ بِمَا عَمِلْتُمْ ۚ وَذَٰلِكَ عَلَى اللَّهِ يَسِيرٌ
17፥49 አሉም *«እንዴት አጥንቶችና ብስብሶች በኾን ጊዜ እኛ አዲስ ፍጥረት ኾነን በእርግጥ ተቀስቃሾች ነንን?»* وَقَالُوا أَإِذَا كُنَّا عِظَامًا وَرُفَاتًا أَإِنَّا لَمَبْعُوثُونَ خَلْقًا جَدِيدًا

በትንሣኤ ላስተባበሉት ሙሽሪኮች ሁሉ እሳት ተዘጋጅቷል፤ አላህ ሰማያትንና ምድርን የፈጠረ ሲሆን እነርሱንም በመፍጠሩ ያልደከመው አላህ ሙታንን ሕያው በማድረግ ላይ ቻይ ነው፤ አላህ እነዚያም ትንሣኤን የካዱት ሰዎች በእሳት ላይ በሚቀረቡ ቀን፦ "ትክዱ በነበራችሁት ምክንያት ቅጣቱን ቅመሱ" ይላቸዋል፦
25፥11 *ይልቁንም በትንሣኤ አስተባበሉ፡፡ በትንሣኤ ላስተባበለም ሰው ሁሉ ነዳጅን እሳት አዘጋጅተናል*፡፡ بَلْ كَذَّبُوا بِالسَّاعَةِ ۖ وَأَعْتَدْنَا لِمَن كَذَّبَ بِالسَّاعَةِ سَعِيرًا
46፥33 *ያ ሰማያትንና ምድርን የፈጠረ እነርሱንም በመፍጠሩ ያልደከመው አላህ ሙታንን ሕያው በማድረግ ላይ ቻይ መኾኑን አላስተዋሉምን? በማስነሳት ቻይ ነው፡፡ እርሱ በነገሩ ሁሉ ላይ ቻይ ነውና*፡፡ أَوَلَمْ يَرَوْا۟ أَنَّ ٱللَّهَ ٱلَّذِى خَلَقَ ٱلسَّمَٰوَٰتِ وَٱلْأَرْضَ وَلَمْ يَعْىَ بِخَلْقِهِنَّ بِقَٰدِرٍ عَلَىٰٓ أَن يُحْـِۧىَ ٱلْمَوْتَىٰ ۚ بَلَىٰٓ إِنَّهُۥ عَلَىٰ كُلِّ شَىْءٍۢ قَدِيرٌۭ
46፥35 *እነዚያም የካዱት ሰዎች በእሳት ላይ በሚቀረቡ ቀን «ይህ እውነት አይደለምን?» ይባላሉ፡፡ «እውነት ነው፤ በጌታችን ይኹንብን» ይላሉ፡፡ አላህም «ትክዱ በነበራችሁት ምክንያት ቅጣቱን ቅመሱ» ይላቸዋል*፡፡ وَيَوْمَ يُعْرَضُ ٱلَّذِينَ كَفَرُوا۟ عَلَى ٱلنَّارِ أَلَيْسَ هَٰذَا بِٱلْحَقِّ ۖ قَالُوا۟ بَلَىٰ وَرَبِّنَا ۚ قَالَ فَذُوقُوا۟ ٱلْعَذَابَ بِمَا كُنتُمْ تَكْفُرُونَ

እነዚህ ሙሽሪኮች፦ ይህንን የትንሣኤ ተስፋ እኛምና ከፊት የነበሩት አባቶቻችንም በእርግጥ ተቀጥረንበታል አሉ፤ አባቶቻቸው ኢብራሂም፣ ኢስማኢል ስለ የትንሣኤ ቀጠሮ እንዳለ ተናግረዋል፤ ነገር ግን ስለ ትንሣኤ ተስፋ ያላቸው አመለካከት፦ "ይህ የመጀመሪያዎቹ ሰዎች ተረቶች እንጅ ሌላ አይደለም" የሚል ነው፦
27፥68 *«ይህንን* እኛም ከፊት የነበሩት አባቶቻችንም በእርግጥ ተቀጥረንበታል፡፡ *ይህ የመጀመሪያዎቹ ሰዎች ተረቶች እንጅ ሌላ አይደለም»* አሉ፡፡ لَقَدْ وُعِدْنَا هَٰذَا نَحْنُ وَءَابَآؤُنَا مِن قَبْلُ إِنْ هَٰذَآ إِلَّآ أَسَٰطِيرُ ٱلْأَوَّلِينَ
46፥17 ያንንም ለወላጆቹ *«ፎህ ለእናንተ ከእኔ በፊት የክፍል ዘመናት ሰዎች ሳይወጡ በእርግጥ ያለፉ ሲኾኑ ከመቃብር እንድወጣ ታስፈራሩኛላችሁን?»* ያለውን፤ ሁለቱም ወላጆቹ አላህን የሚለምኑ ሲኾኑ፦ *ባታምን ወዮልህ እመን፤ የአላህ ቀጠሮ እርግጠኛ ነው* ሲሉት *«ይህ የፊተኞቹ ሰዎች ጽሑፍ ተረቶች እንጅ ሌላ አይደለም»* የሚለውንም ሰው አስታውስ፡፡ وَالَّذِي قَالَ لِوَالِدَيْهِ أُفٍّ لَّكُمَا أَتَعِدَانِنِي أَنْ أُخْرَجَ وَقَدْ خَلَتِ الْقُرُونُ مِن قَبْلِي وَهُمَا يَسْتَغِيثَانِ اللَّهَ وَيْلَكَ آمِنْ إِنَّ وَعْدَ اللَّهِ حَقٌّ فَيَقُولُ مَا هَـٰذَا إِلَّا أَسَاطِيرُ الْأَوَّلِينَ

እዚህ አንቀጽ ላይ "አወሊን" أَوَّلِينْ ማለትም "የቀድሞቹ" የተባሉት አህለል ኪታቦች ሲሆኑ ይህ የትንሣኤ እሳቤና ተስፋ በእነርሱም ዘንድ ይገኛል፤ ነገር ግን ይህ የትንሣኤ እሳቤና ተስፋ ለሙሽሪኮች ተረት ነው፤ ስለ ትንሣኤ የሚናገረውን የአምላካችን የአላህ አንቀጾች በእነርሱ ላይ እየተነበበላቸው እነርሱ ግን የነበራቸው ማስተባበያ፦ "ተረት" ነው የሚል ነው፤ ለዛውም "የመጀመሪያዎቹ ሰዎች ተረቶች ናቸው" የሚል ነው፦
8፥31 *አንቀጾቻችንም በእነርሱ ላይ በተነበቡ ጊዜ «በእርግጥ ሰምተናል፤ በሻን ኖሮ የዚህን ብጤ ባልን ነበር፤ ይህ የመጀመሪያዎቹ ሰዎች ጽሑፍ ተረቶች እንጂ ሌላ አይደለም» ይላሉ*፡፡ وَإِذَا تُتْلَىٰ عَلَيْهِمْ آيَاتُنَا قَالُوا قَدْ سَمِعْنَا لَوْ نَشَاءُ لَقُلْنَا مِثْلَ هَـٰذَا ۙ إِنْ هَـٰذَا إِلَّا أَسَاطِيرُ الْأَوَّلِينَ
83፥13 *አንቀጾቻችን በእርሱ ላይ በተነበቡ ጊዜ «የመጀመሪያዎቹ ሰዎች ተረቶች ናቸው» ይላል*፡፡ إِذَا تُتْلَىٰ عَلَيْهِ آيَاتُنَا قَالَ أَسَاطِيرُ الْأَوَّلِينَ
68፥15 *በእርሱ ላይ አንቀጾቻችን በሚነበቡ ጊዜ «የመጀመሪያዎቹ ሰዎች ተረቶች ናቸው» ይላል*፡፡ إِذَا تُتْلَىٰ عَلَيْهِ آيَاتُنَا قَالَ أَسَاطِيرُ الْأَوَّلِين
“ቃሉ” َقَالُوا ማለትም “አሉ” የሚለው ኃይለ-ቃል ይሰመርበት፤ ትንሣኤን “የቀድሞዎቹ ተረት ነው” ያሉት ሙሽሪክ ከሃድያን እንደሆኑ አንባቢ ልብ ይለዋል፤ ስለ ትንሣኤ የሚናገሩትን የአላህ አንቀጾች በመካዳቸው እና “አጥንቶችና ብስብሶች በኾን ጊዜ እኛ አዲስ ፍጥረት ኾነን ተቀስቃሾች ነንን? ስላሉ ፍዳቸው እሳት ነው፦
17፥98 *ይህ ቅጣት እነርሱ በአንቀጾቻችን ስለ ካዱና «አጥንቶችና ብስብሶች በኾን ጊዜ እኛ አዲስ ፍጥረት ኾነን ተቀስቃሾች ነንን?» ስላሉም ፍዳቸው ነው*፡፡ ذَٰلِكَ جَزَاؤُهُم بِأَنَّهُمْ كَفَرُوا بِآيَاتِنَا وَقَالُوا أَإِذَا كُنَّا عِظَامًا وَرُفَاتًا أَإِنَّا لَمَبْعُوثُونَ خَلْقًا جَدِيدًا

ሙሽሪክ ከሃድያን አምላካችን አላህ ስለ ትንሣኤ የሚናገረው አንቀጽ ብቻ ሳይሆን በቀድሞዎቹ አህለል ኪታብ ያለውን የትንሣኤ እሳቤ ተረት ነው ብለዋል፤ ስለዚህ ይህ ሙግት ስሁት ሙግት ነው፤ ሚሽነሪዎች ሆይ! በቆፈራችሁት ጉድጓድ እራሳችሁን የምትቀብሩበት ነው፤ እውን ትንሣኤ ተረት ነውን? መልሳችሁ አይደለም እንደሚሆን እሙንና ቅቡል ነው።

በእርግጥም አላህ በነገሩ ሁሉ ላይ ቻይ ነው፤ የሚያሞት ሕያው የሚያደር እርሱ ነው፦
15፥6 ይህ አላህ እርሱ መኖሩ የተረጋገጠ፣ *እርሱም ሙታንን ሕያው የሚያደርግ፣ እርሱም በነገሩ ሁሉ ላይ ቻይ በመሆኑ ነው*፡፡ ذَٰلِكَ بِأَنَّ اللَّهَ هُوَ الْحَقُّ وَأَنَّهُ يُحْيِي الْمَوْتَىٰ وَأَنَّهُ عَلَىٰ كُلِّ شَيْءٍ قَدِيرٌ
36፥12 *እኛ ሙታንን እኛ በእርግጥ ሕያው እናደርጋለን*፡፡ ያስቀደሙትንም ሥራ ፈለጎቻቸውንም እንጽፋለን፡፡ ነገሩንም ሁሉ ገላጭ መሪ በኾነ መጽሐፍ ውስጥ አጠቃለልነው፡፡ إِنَّا نَحْنُ نُحْيِي الْمَوْتَىٰ وَنَكْتُبُ مَا قَدَّمُوا وَآثَارَهُمْ ۚ وَكُلَّ شَيْءٍ أَحْصَيْنَاهُ فِي إِمَامٍ مُّبِينٍ
15፥23 *እኛም ሕያው የምናደርግ እና የምናሞት እኛው ብቻ ነን*፡፡ እኛም ፍጡርን ሁሉ የምንወርስ ቀሪ ነን፡፡ وَإِنَّا لَنَحْنُ نُحْىِۦ وَنُمِيتُ وَنَحْنُ ٱلْوَٰرِثُونَ

አምላካችን አላህ ሕያውን ከሙት ያወጣል፤ ሙታንም ከሕያው ያወጣል። ምድርንም ከሞተች በኋላ ህያው ያደርጋታል፤ በተመሳሳይ ከመቃብር መውጣት እንደዚሁ ነው፦
30፥19 *ሕያውን ከሙት ያወጣል፡፡ ሙታንም ከሕያው ያወጣል፡፡ ምድርንም ከሞተች በኋላ ህያው ያደርጋታል፡፡ እንደዚሁም ከመቃብር ትወጣላችሁ*፡፡ يُخْرِجُ الْحَيَّ مِنَ الْمَيِّتِ وَيُخْرِجُ الْمَيِّتَ مِنَ الْحَيِّ وَيُحْيِي الْأَرْضَ بَعْدَ مَوْتِهَا ۚ وَكَذَٰلِكَ تُخْرَجُونَ
35፥9 *አላህም ያ ነፋሶችን የላከ ነው፡፡ ደመናዎችንም ትቀሰቅሳለች፤ ወደ ሙት ድርቅ አገርም እንነዳዋለን፡፡ በእርሱም ምድርን ከሞተች በኋላ ሕያው እናደርጋታለን፡፡ ሙታንንም መቀስቀስ እንደዚሁ ነው*፡፡ وَاللَّهُ الَّذِي أَرْسَلَ الرِّيَاحَ فَتُثِيرُ سَحَابًا فَسُقْنَاهُ إِلَىٰ بَلَدٍ مَّيِّتٍ فَأَحْيَيْنَا بِهِ الْأَرْضَ بَعْدَ مَوْتِهَا ۚ كَذَٰلِكَ النُّشُورُ
43፥11 *ያ ከሰማያ ውሃን በልክ ያወረደላችሁ ነው፡፡ በእርሱም የሞተችውን አገር ሕያው አደረግን፡፡ እንደዚሁ ከመቃብራችሁ ትወጣላችሁ*፡፡ وَالَّذِي نَزَّلَ مِنَ السَّمَاءِ مَاءً بِقَدَرٍ فَأَنشَرْنَا بِهِ بَلْدَةً مَّيْتًا ۚ كَذَٰلِكَ تُخْرَجُونَ
30፥50 *ምድርንም ከሞተች በኋላ እንዴት ሕያው እንደሚያደርጋት ወደ አላህ ችሮታ ፈለጎች ተመልከት፡፡ ይህ አድራጊ ሙታንንም በእርግጥ ሕያው አድራጊ ነው፡፡ እርሱም በነገሩ ሁሉ ላይ ቻይ ነው*፡፡ فَانظُرْ إِلَىٰ آثَارِ رَحْمَتِ اللَّهِ كَيْفَ يُحْيِي الْأَرْضَ بَعْدَ مَوْتِهَا ۚ إِنَّ ذَٰلِكَ لَمُحْيِي الْمَوْتَىٰ ۖ وَهُوَ عَلَىٰ كُلِّ شَيْءٍ قَدِيرٌ

ከዐቃቤ አሥልምና ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
አህለል ኪታብ እነማን ናቸው?

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ፥ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

3፥71 የመጸሐፉ ሰዎች ሆይ! “እዉነቱን በዉሸት” ለምን *ትቀላቅላላችሁ*? “እዉነቱንም” እናንተ የምታወቁ ስትሆኑ ለምን *ትደብቃላችሁ*? يَٰٓأَهْلَ ٱلْكِتَٰبِ لِمَ تَلْبِسُونَ ٱلْحَقَّ بِٱلْبَٰطِلِ وَتَكْتُمُونَ ٱلْحَقَّ وَأَنتُمْ تَعْلَمُونَ

“አህለል ኪታብ” أَهْلَ الْكِتَابِ መነሻ ቅጥያው “አህል” أَهْل ሲሆን፦
“አህለ” أَهْلَ በፈትሓህ ሲመጣ ተሳቢ ሙያን፣
“አህሊ” أَهْلِ በከስራ ሲመጣ አገናዛቢ ሙያን፣
“አህሉ” أَهْلُ በደማ ሲመጣ ባለቤት ሙያን የሚያመልክት ሲሆን ትርጉሙ “ሕዝብ” አሊያም “ባለቤት” የሚል ፍቺ አለው። “ኪታብ” كِتَٰب ማለት ደግሞ “መጽሐፍ” ማለት ነው፥ በጥቅሉ “አህለል ኪታብ” ማለት “የመጸሐፉ ሰዎች” “የመጸሐፉ ህዝብ” “የመጸሐፉ ባለቤት”The People of the Book” ማለት ነው። ይህ ቃል በቁርአን 49 ጊዜ ተደጋግሞ መጥቷል።
የመጽሐፉን ባለቤቶች የተባሉት ክርስቲያንና አይሁዳውያን እንደሆኑ እሙንና ቅቡል ነው። ከአህለል ኪታብ መካከል ቁርኣን በወረደበት ጊዜ የነበሩት ክርስቲያኖች፦ "አምላክ አንድም ሦስትም ነው" ስለሚሉ አምላካችን አላህ፦ "ሦስት ነው" አትለፉ! አላህ አንድ አምላክ ብቻ ነው" በማለት ይናገራል፦
4፥171 እናንተ የመጽሐፉ ሰዎች ሆይ! በሃይማኖታችሁ ወሰንን አትለፉ፡፡ በአላህም ላይ እውነትን እንጅ አትናገሩ፡፡ የመርየም ልጅ አልመሲሕ ዒሳ የአላህ መልክተኛ ወደ መርየም የጣላት «የኹን» ቃሉም ከእርሱ የኾነ መንፈስም ብቻ ነው፡፡ በአላህና በመልክተኞቹም እመኑ፡፡ *«ሦስት ነው» አትበሉም*፡፡ ተከልከሉ፤ ለእናንተ የተሻለ ይኾናልና፡፡ አላህ አንድ አምላክ ብቻ ነው፡፡ ለእርሱ ልጅ ያለው ከመኾን የጠራ ነው፡፡ በሰማያትና በምድር ያለ ሁሉ የርሱ ነው፡፡ መመኪያም በአላህ በቃ። يَٰٓأَهْلَ ٱلْكِتَٰبِ لَا تَغْلُوا۟ فِى دِينِكُمْ وَلَا تَقُولُوا۟ عَلَى ٱللَّهِ إِلَّا ٱلْحَقَّ ۚ إِنَّمَا ٱلْمَسِيحُ عِيسَى ٱبْنُ مَرْيَمَ رَسُولُ ٱللَّهِ وَكَلِمَتُهُۥٓ أَلْقَىٰهَآ إِلَىٰ مَرْيَمَ وَرُوحٌۭ مِّنْهُ ۖ فَـَٔامِنُوا۟ بِٱللَّهِ وَرُسُلِهِۦ ۖ وَلَا تَقُولُوا۟ ثَلَٰثَةٌ ۚ ٱنتَهُوا۟ خَيْرًۭا لَّكُمْ ۚ إِنَّمَا ٱللَّهُ إِلَٰهٌۭ وَٰحِدٌۭ ۖ سُبْحَٰنَهُۥٓ أَن يَكُونَ لَهُۥ وَلَدٌۭ ۘ لَّهُۥ مَا فِى ٱلسَّمَٰوَٰتِ وَمَا فِى ٱلْأَرْضِ ۗ وَكَفَىٰ بِٱللَّهِ وَكِيلًۭا

ቁርኣን በወረደበት ጊዜ የነበሩት ክርስቲያኖች፦ "ኢየሱስ አምላክ ነው፥ የአምላክ ልጅ" ስለሚሉ አምላካችን አላህ፦ "እነዚያ አላህ እርሱ የመርየም ልጅ አልመሲሕ ነው ያሉ በእርግጥ ካዱ፥ እነዚያንም "አላህ ልጅን ይዟል" ያሉትን ሊያስጠነቅቅበት አወረደው" በማለት ይናገራል፦
5፥17 *እነዚያ አላህ እርሱ የመርየም ልጅ አልመሲሕ ነው ያሉ በእርግጥ ካዱ*፡፡ لَّقَدْ كَفَرَ الَّذِينَ قَالُوا إِنَّ اللَّهَ هُوَ الْمَسِيحُ ابْنُ مَرْيَمَ
18፥4 *እነዚያንም «አላህ ልጅን ይዟል» ያሉትን ሊያስጠነቅቅበት አወረደው*፡፡ وَيُنذِرَ الَّذِينَ قَالُوا اتَّخَذَ اللَّهُ وَلَدًا

ቁርኣን በወረደበት ጊዜ የነበሩት ክርስቲያኖች አዲስ የፈጠሩዋትንም ምንኩስና ነበራቸው፥ አምላካችን አላህ፦ "አዲስ የፈጠሩዋትንም ምንኩስና በእነርሱ ላይ አልጻፍናትም" በማለት ይናገራል፦
57፥27 ከዚያም በዱካዎቻቸው ላይ መልክተኞቻችንን አስከታተልን፡፡ የመርየምን ልጅ ዒሳንም አስከተልን፡፡ ኢንጂልንም ሰጠነው፡፡ በእነዚያም በተከተሉት ሰዎች ልቦች ውሰጥ መለዘብንና እዝነትን አደረግን፡፡ *”አዲስ የፈጠሩዋትንም ምንኩስና በእነርሱ ላይ አልጻፍናትም፡፡ ግን የአላህን ውዴታ ለመፈለግ ሲሉ ፈጠሩዋት፡፡ ተገቢ አጠባበቋንም አልጠበቋትም*”፡፡ ከእነርሱም ለእነዚያ ላመኑት ምንዳቸውን ሰጠናቸው፡፡ ከእነርሱም ብዙዎቹ አመጸኞች ናቸው፡፡ ثُمَّ قَفَّيْنَا عَلَىٰ آثَارِهِم بِرُسُلِنَا وَقَفَّيْنَا بِعِيسَى ابْنِ مَرْيَمَ وَآتَيْنَاهُ الْإِنجِيلَ وَجَعَلْنَا فِي قُلُوبِ الَّذِينَ اتَّبَعُوهُ رَأْفَةً وَرَحْمَةً وَرَهْبَانِيَّةً ابْتَدَعُوهَا مَا كَتَبْنَاهَا عَلَيْهِمْ إِلَّا ابْتِغَاءَ رِضْوَانِ اللَّهِ فَمَا رَعَوْهَا حَقَّ رِعَايَتِهَا ۖ فَآتَيْنَا الَّذِينَ آمَنُوا مِنْهُمْ أَجْرَهُمْ ۖ وَكَثِيرٌ مِّنْهُمْ فَاسِقُونَ

በዘመናችን ያሉ አይሁድ እና ክርስቲያኖች ቁርኣን ከገለጻቸው ጋር ምንም ልዩነት የላቸው። ዛሬ ያሉትን ክርስቲያኖች መሠረታዊ ትምህርታቸው እና ተግባራቸው የተመሠረተው ከቁርኣን መውረድ በፊት በተደረጉ የተለያዩ ጉባኤዎች ነው። የመጽሐፉ ሰዎች ከአላህ የወረዱትን እውነት ከሰው ትምህርት ጋር በመቀላቀል እና የነበረውን እውነት በመቀነስ በርዘውታል፦
3፥71 የመጽሐፉ ሰዎች ሆይ! *”እውነቱን በውሸት ለምን ትቀላቅላላችሁ”* እውነቱንም እናንተ የምታውቁ ስትኾኑ ለምን *”ትደብቃላችሁ”*?። يَٰٓأَهْلَ ٱلْكِتَٰبِ لِمَ تَلْبِسُونَ ٱلْحَقَّ بِٱلْبَٰطِلِ وَتَكْتُمُونَ ٱلْحَقَّ وَأَنتُمْ تَعْلَمُونَ
2፥79 ለነዚያም መጽሐፉን በእጆቻቸው ለሚጽፉና ከዚያም በርሱ ጥቂትን ዋጋ ሊገዙበት «ይህ ከአላህ ዘንድ ነው» ለሚሉ ወዮላቸው፡፡ ለነርሱም ከዚያ እጆቻቸው ከጻፉት ወዮላቸው፡፡ ለነሱም ከዚያ ከሚያፈሩት ኃጢኣት ወዮላቸው፡፡ فَوَيْلٌۭ لِّلَّذِينَ يَكْتُبُونَ ٱلْكِتَٰبَ بِأَيْدِيهِمْ ثُمَّ يَقُولُونَ هَٰذَا مِنْ عِندِ ٱللَّهِ لِيَشْتَرُوا۟ بِهِۦ ثَمَنًۭا قَلِيلًۭا ۖ فَوَيْلٌۭ لَّهُم مِّمَّا كَتَبَتْ أَيْدِيهِمْ وَوَيْلٌۭ لَّهُم مِّمَّا يَكْسِبُونَ

መጽሐፉን በእጆቻቸው ጽፈው፥ ከአላህ ሳይሆን "ይህ ከአላህ ዘንድ ነው" ብለው የያዙትን የተበረዘ መጽሐፍ ባለቤት ናቸው። አይሁዳውን በ 90 ድኅረ-ልደት”AD” በጀሚኒያ ጉባኤ፥ ክርስቲያኖች በ 397 ድኅረ-ልደት”AD” በካርቴጅ ጉባኤ ጨምረዋል። ቀንሰዋል።

ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
መስዋዕት

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ፥ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

22፥34 *ለሕዝብም ሁሉ ወደ አላህ መስዋዕት ማቅረብን ደነገግን፡፡ ከቤት እንስሳት በሰጣቸው ሲሳይ ላይ የአላህን ስም ብቻ ያወሱ ዘንድ አዘዝናቸው፡፡ አምላካችሁም አንድ አምላክ ብቻ ነው፡፡ ለእርሱም ብቻ ታዘዙ*፡፡ ለአላህ ተዋራጆችንም አብስራቸው፡፡ وَلِكُلِّ أُمَّةٍ جَعَلْنَا مَنسَكًا لِّيَذْكُرُوا اسْمَ اللَّهِ عَلَىٰ مَا رَزَقَهُم مِّن بَهِيمَةِ الْأَنْعَامِ ۗ فَإِلَـٰهُكُمْ إِلَـٰهٌ وَاحِدٌ فَلَهُ أَسْلِمُوا ۗ وَبَشِّرِ الْمُخْبِتِينَ

አምላካችን አሏህ ለየሕዝቡ ሁሉ እነርሱ የሚሠሩበት የኾነን ሥርዓተ ሃይማኖት አድርጓል፦
22፥67 *ለየሕዝቡ ሁሉ እነርሱ የሚሠሩበት የኾነን ሥርዓተ ሃይማኖት አድርገናል*፡፡ لِّكُلِّ أُمَّةٍ جَعَلْنَا مَنسَكًا هُمْ نَاسِكُوهُ ۖ

“ሥርዓተ ሃይማኖት” ተብሎ የተቀመጠው ቃል “መንሠክ” مَنسَك ሲሆን “መስዋዕት” ማለት ነው፦
22፥34 *ለሕዝብም ሁሉ ወደ አላህ መስዋዕት ማቅረብን ደነገግን፡፡ ከቤት እንስሳት በሰጣቸው ሲሳይ ላይ የአላህን ስም ብቻ ያወሱ ዘንድ አዘዝናቸው፡፡ አምላካችሁም አንድ አምላክ ብቻ ነው፡፡ ለእርሱም ብቻ ታዘዙ*፡፡ ለአላህ ተዋራጆችንም አብስራቸው፡፡ وَلِكُلِّ أُمَّةٍ جَعَلْنَا مَنسَكًا لِّيَذْكُرُوا اسْمَ اللَّهِ عَلَىٰ مَا رَزَقَهُم مِّن بَهِيمَةِ الْأَنْعَامِ ۗ فَإِلَـٰهُكُمْ إِلَـٰهٌ وَاحِدٌ فَلَهُ أَسْلِمُوا ۗ وَبَشِّرِ الْمُخْبِتِينَ

“አምላካችሁም አንድ አምላክ ብቻ ነው” በማለት ከተናገር በኃላ “ለእርሱም ብቻ ታዘዙ” ይላል፥ “ታዘዙ” ለሚለው ቃል የተቀመጠው “አሥሊሙ” أَسْلِمُوا ሲሆን መስዋዕት ማቅረብ የኢስላም ክፍል መሆኑን ያሳያል። “መስዋዕት” የሚለው ቃል “ኑሡክ” نُسُك ሲሆን ለአሏህ ብቻ የሚቀርብ ዕርድ ነው፦
6፥162 *«ስግደቴ፣ መስዋዕቴም፣ ሕይወቴም፣ ሞቴም ለዓለማት ጌታ ለአላህ ነው»* በል፡፡ قُلْ إِنَّ صَلَاتِي وَنُسُكِي وَمَحْيَايَ وَمَمَاتِي لِلَّهِ رَبِّ الْعَالَمِينَ
2፥200 *የሐጅ ሥራዎቻችሁንም በፈጸማችሁ ጊዜ አባቶቻችሁን እንደምታወሱ ወይም ይበልጥ የበረታን ማውሳት አላህን አውሱ*፡፡ فَإِذَا قَضَيْتُم مَّنَاسِكَكُمْ فَاذْكُرُوا اللَّهَ كَذِكْرِكُمْ آبَاءَكُمْ أَوْ أَشَدَّ ذِكْرًا

“ሥራዎቻችሁ” ለሚለው ቃል የተቀመጠው “መናሢከኩም” مَنَاسِكَكُمْ ሲሆን “መስዋዕቶቻችሁ” ማለት ነው። መስዋዕት ለአሏህ ብቻ ማቅረብ መልካም ሥራ ነው፥ መልካም ሥራዎች ኃጢአቶችን ያስተሰርያሉ፦
11፥114 ሶላትንም በቀን ጫፎች ከሌሊትም ክፍሎች ፈጽም፡፡ *መልካም ሥራዎች ኃጢአቶችን ያስወገድዳሉና*፡፡ ይህ ለተገሳጮች ግሳጼ ነው፡፡ وَأَقِمِ الصَّلَاةَ طَرَفَيِ النَّهَارِ وَزُلَفًا مِّنَ اللَّيْلِ ۚ إِنَّ الْحَسَنَاتِ يُذْهِبْنَ السَّيِّئَاتِ ۚ ذَٰلِكَ ذِكْرَىٰ لِلذَّاكِرِينَ

ይህ የመስዋዕት ዕርድ ዛሬም በተከበረው 12ኛ ወር ዙል ሂጃህ ከአስኛው ቀን ማለዳ እስከ አስራ ሁለተኛው ምሽት ይቀርባል፦
2፥196 *ሐጅንና ዑምራንም ለአላህ ሙሉ፤ ብትታገዱም ከሀድይ የተገራውን መሰዋት አለባችሁ*፡፡ وَأَتِمُّوا الْحَجَّ وَالْعُمْرَةَ لِلَّهِ ۚ فَإِنْ أُحْصِرْتُمْ فَمَا اسْتَيْسَرَ مِنَ الْهَدْيِ
5፥97 *አላህ ከዕባን የተከበረውን ቤት ለሰዎች መቋቋሚያ አደረገ፣ የተከበረውን ወር ሀድዩን እና ባለ ምልክቶቹንም መንጋዎች አደረገ*፡፡ جَعَلَ اللَّهُ الْكَعْبَةَ الْبَيْتَ الْحَرَامَ قِيَامًا لِّلنَّاسِ وَالشَّهْرَ الْحَرَامَ وَالْهَدْيَ وَالْقَلَائِدَ
“ሀድይ” هَدْي ማለት “የዕርድ እንስሳ” ሲሆን ጊደር፣ በግ፣ ፍየል፣ ጥጃ፣ ግመል ነው። ይህ ለአሏህ የሚቀርበው መስዋዕት “ቁርባን” ይባላል፥ “ቁርባን” قُرْبَان የሚለው ቃል “ቀረበ” قَرَّبَ ማለትም “አቀረበ” ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን “መቃረቢያ” “አምሓ” “እጅ መንሻ” ማለት ነው፦
5፥27 በእነርሱም ላይ *የአደምን ሁለት ልጆች ወሬ ቁርባንን ባቀረቡ እና አላህ ከአንደኛቸው ተቀብሎ ከሌላው ባልተቀበለ ጊዜ የኾነውን በእውነት አንብብላቸው*፡፡ «በእርግጥ እገድልሃለሁ» አለው፡፡ ተገዳዩ «አላህ የሚቀበለው እኮ ከጥንቁቆቹ ብቻ ነው» አለ፡፡ وَاتْلُ عَلَيْهِمْ نَبَأَ ابْنَيْ آدَمَ بِالْحَقِّ إِذْ قَرَّبَا قُرْبَانًا فَتُقُبِّلَ مِنْ أَحَدِهِمَا وَلَمْ يُتَقَبَّلْ مِنَ الْآخَرِ قَالَ لَأَقْتُلَنَّكَ ۖ قَالَ إِنَّمَا يَتَقَبَّلُ اللَّهُ مِنَ الْمُتَّقِينَ

“ባቀረቡ” ለሚለው ቃል የተጠቀመው “ቀረባ” قَرَّبَا ሲሆን “ቁርባን” የሚለው ቃል የረባበት ሙሰና ግስ ነው። አምላካችን አሏህም ከነቢያችን”ﷺ” በፊት መልእክተኞች በተአምራት እና በቁርባን የመጡ እንደነበር “በላቸው” በሚል ቃል ተናግሯል፦
3፥183 እነዚያ ለማንኛውም መልክተኛ *«እሳት የምትበላው የኾነን ቁርባን እስከሚያመጣልን ድረስ ላናምን አላህ ወደኛ አዟል» ያሉ ናቸው፡፡«መልክተኞች ከእኔ በፊት በተዓምራት እና በዚያም ባላችሁት ቁርባን በእርግጥ መጥተውላችኋል*፡፡ እውነተኞች ከኾናችሁ ታዲያ ለምን ገደላችኋቸው» በላቸው፡፡ الَّذِينَ قَالُوا إِنَّ اللَّهَ عَهِدَ إِلَيْنَا أَلَّا نُؤْمِنَ لِرَسُولٍ حَتَّىٰ يَأْتِيَنَا بِقُرْبَانٍ تَأْكُلُهُ النَّارُ ۗ قُلْ قَدْ جَاءَكُمْ رُسُلٌ مِّن قَبْلِي بِالْبَيِّنَاتِ وَبِالَّذِي قُلْتُمْ فَلِمَ قَتَلْتُمُوهُمْ إِن كُنتُمْ صَادِقِينَ

“ኮህን” כֹּהֵן‎ የሚለው የዕብራይስጥ ቃል እና “ካህን” كَاهن የሚለው የዐረቢኛ ቃል “መስዋዕት አቅራቢ” ማለት ነው፥ ሀብተ-ክህነት መስዋዕት የማቅረብ ጸጋ ነው። አዳም ከመሳሳቱ በፊት ካህን ነበረ፦
ግዕዙ፦
ክሌመንት(ቀለሜንጦስ) 1፥43
ወእምዝ ሰሞዑ መላእክት ቃለ እግዚአብሔር ልዑል እንዘይብል፦ ” ኦ አዳም! ናሁ ረደይኩከ ንጉሠ፣ "ወካህነ"፣ ነቢየ፣ ወመስፍነ፣ ወመኮንነ ለኩሉ ፍጥረት ዘገበርኩ ለከ ይስምዑ ኩሉ ፍጥረት ወለቃልከ ይትእዘዙ ወታሕተ እዴከ ይኩን ለከ ለባሕቲትከ”

ትርጉም፦
በዚያን ጊዜም መላእክት የእግዚአብሔር ቃል ለአዳም እንዲህ ሲል ሰሙ፦ “አዳም ሆይ እነሆ ንጉሥ፣ "ካህን"፣ ነብይ፣ መስፍን እና መኮንን በፍጥረት ሁሉ ገዢ ስለ አንተ በፈጠርኩት ሁሉ እንድትሆን አደረኩህ፤ ፡ፍጥነት ሁሉ አንተን ይስሙ ለቃልህም ይታዘዙ ከእጅህ በታች ይሁኑ ይህንንም ሁሉ ለአንተ ብቻ ሰጠሁህ”*።

በኦርቶዶስ ትውፊት አዳም ከመሳሳቱ በፊት ካህን ሆኖ መስዋዕት ያቀርብ ከነበረ መስዋዕት ከውርስ ኃጢአት ጋር ግኑኝነት የለውም። ስለዚህ መስዋዕት የአምልኮ ክፍል ነው እንጂ ለውርስ ኃጢአት ማስተሰሪያ አይደለም። አዳም የማንን ኀጢአት ወርሶ ነው መስዋዕት ለማቅረብ ካህን የሆነው? መልሱ "መስዋዕት ማቅረብ የአምልኮ ነው" የሚል ነው።

ከዐቃቤ አሥልምና ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
ጽላት እና ታቦት

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

7፥145 *ለእርሱም በሰሌዳዎቹ ላይ ከነገሩ ሁሉ ግሳጼንና ለነገሩም ሁሉ ማብራራትን ጻፍንለት*፡፡ وَكَتَبْنَا لَهُ فِي الْأَلْوَاحِ مِن كُلِّ شَيْءٍ

“ጽሌ” ማለት “ሰሌዳ” “ፊደል” ማለት ነው፤ የጽሌ ብዙ ቁጥር “ጽላት” ሲሆን “ሰሌዳዎች” ወይም “ፊደሎች” ማለት ነው፤ በዕብራይስጥ ደግሞ “ላሁት” לֻחֹ֣ת ሲሆን በዐረቢኛ “ለውሕ” لَوْح ነው፣ አምላካችን አላህ ለሙሳ ቃላትን በፊደል ላይ ጽፎ እንደሰጠው በተከበረ ቃሉ ይናገራል፦
7፥145 *ለእርሱም በሰሌዳዎቹ ላይ ከነገሩ ሁሉ ግሳጼንና ለነገሩም ሁሉ ማብራራትን ጻፍንለት*፡፡ وَكَتَبْنَا لَهُ فِي الْأَلْوَاحِ مِن كُلِّ شَيْءٍ
7፥154 *ከሙሳም ቁጣው በበረደ ጊዜ ሰሌዳዎቹን በግልባጫቸው ውስጥ ለእነዚያ እነርሱ ጌታቸውን የሚፈሩ ለኾኑት መምሪያና እዝነት ያለባቸው ሲኾኑ ያዘ*፡፡ وَلَمَّا سَكَتَ عَن مُّوسَى الْغَضَبُ أَخَذَ الْأَلْوَاحَ ۖ وَفِي نُسْخَتِهَا هُدًى وَرَحْمَةٌ لِّلَّذِينَ هُمْ لِرَبِّهِمْ يَرْهَبُونَ

ይህን ድርጊት በፔንታተች በተመሳሳይ መልኩ ተመዝግቧል፦
ዘጸአት 24፥12 እግዚአብሔርም ሙሴን፦ ወደ እኔ ወደ ተራራው ውጣ፥ በዚያም ሁን፤ *እነርሱን ታስተምር ዘንድ እኔ የጻፍሁትን ሕግና ትእዛዝ የድንጋይም ጽላት እሰጥሃለሁ አለው*።

“ታቦት” ማለት “ማህደር” “ሰገባ” “ሳጥን” “ማደሪያ” ማለት ነው፣ በዕብራይስጥ ደግሞ “አሮውን” אֲר֖וֹן ሲሆን በዐረቢኛ “አት-ታቡት” التَّابُوتُ ነው፣ አምላካችን አላህ ስለ ታቡት እንዲህ ይለናል፦
2፥248 ነቢያቸውም ለእነርሱ፡- *«የንግሥናው ምልክት ከጌታችሁ የኾነ እርጋታ የሙሳ ቤተሰብና የሃሩን ቤተሰብ ከተውትም ቅርስ በውስጡ ያለበት መላእክት የሚሸከሙት ኾኖ “ሳጥኑ” ሊመጣላችሁ ነው*፡፡ አማኞች ብትኾኑ በዚህ ለእናንተ እርግጠኛ ምልክት አልለ» አላቸው፡፡ وَقَالَ لَهُمْ نَبِيُّهُمْ إِنَّ آيَةَ مُلْكِهِ أَن يَأْتِيَكُمُ التَّابُوتُ فِيهِ سَكِينَةٌ مِّن رَّبِّكُمْ وَبَقِيَّةٌ مِّمَّا تَرَكَ آلُ مُوسَىٰ وَآلُ هَارُونَ تَحْمِلُهُ الْمَلَائِكَةُ ۚ إِنَّ فِي ذَٰلِكَ لَآيَةً لَّكُمْ إِن كُنتُم مُّؤْمِنِينَ

“ሳጥኑ” ለሚለው ቃል የገባው “አት-ታቡት” التَّابُوتُ ነው፤ ይህ ቃል የሙሳ እናት ለጣለችው ሳጥን አገልግሎት ላይ ውሏል፦
20፥39 *«ሕፃኑን በሳጥኑ ውስጥ ጣይው*፡፡ እርሱንም ሳጥኑን በባሕር ላይ ጣይው፡፡ ባሕሩም በዳርቻው ይጣለው፡፡ ለእኔ ጠላት ለእርሱም ጠላት የኾነ ሰው ይይዘዋልና በማለት ባሳወቅን ጊዜ ለገስንልህ፡፡ أَنِ اقْذِفِيهِ فِي التَّابُوتِ فَاقْذِفِيهِ فِي الْيَمِّ فَلْيُلْقِهِ الْيَمُّ بِالسَّاحِلِ يَأْخُذْهُ عَدُوٌّ لِّي وَعَدُوٌّ لَّهُ ۚ وَأَلْقَيْتُ عَلَيْكَ مَحَبَّةً مِّنِّي وَلِتُصْنَعَ عَلَىٰ عَيْنِي

ይህንን እንዲህ በእንዲህ ካየን ዘንዳ ታቦት የጽላቱ ማህደር ወይም ሰገባ ሲሆን ይህን ድርጊት በፔንታተች በተመሳሳይ መልኩ ተመዝግቧል፦
ዘጸአት 25፥10 *ከግራር እንጨትም “ታቦትን” ይሥሩ፤ ርዝመቱ ሁለት ክንድ ተኩል፥ ወርዱም አንድ ክንድ ተኩል፥ ቁመቱም አንድ ክንድ ተኩል ይሁን*።
ዘዳግም 10፥5 *ተመልሼም ከተራራው ወረድሁ፥ “ጽላቶችንም በሠራሁት ታቦት ውስጥ አደረግኋቸው” እግዚአብሔርም እንዳዘዘኝ በዚያ ኖሩ*።
ይህ እንዲህ ከሆነ ይህ ጽላት እና ታቦት የት ገባ? በተለይ የአገራችን ሰዎች እንደሚተርኩልን ይህን የቃል ኪዳን ታቦት ወደ አቢሲኒያ በዘጠነኛው ክፍለ-ዘመን በሰለሞን ዘመነ-መንግሥት እንደገባ ይነገራል፣ ነገር ግን በዓለማችን ታሪክ ላይ ታቦቱ በባቢሎን ምርኮ ጊዜ እንደጠፋና ከዚያ በፊት ኢየሩሳሌም ውስጥ እንደነበረ ተዘግቧል፤ በተጨማሪ የእዝራ ሱቱኤል ጸሐፊ ታቦቱ በባቢሎን ምርኮ ጊዜ እንደተማረከና እንደጠፋ ይዘግባል፦
ዕዝራ ሱቱኤል 9፥21-23 *”ቤተ መቅደሳችን እንደፈረሰ አታይም? ግናይቱ እንደጠፍች ምስጋና እንደቀረ ዘውዳችን እንደወደቀ ተድላ ደስታችን እንደጠፍ የህጋች ማደሪያ *ታቦተ ፅዮን እንደተማረከች ንዋየ ቅዱሳት አንዳደፉ ምልኮታችን እንደቀረ። ከዚህ ሁሉ የሚበልጥ ታቦተ ፅዮን እንደጠፍች ቀረች*፤ ከእሷም ንዋየ ቅድሳቱ ተማርኮ ሄደ በጠላቶቻችን በባቢሎን እጅ ወደቅን”*።
2ኛ ዕዝራ 1፥54-56 *”እግዚአብሔርን የሚያገለግሉበት ንዋይ ቅድሳቱን ጥቃቅኑንም እና ታላላቁንም ዕቃ ሁሉ የእግዚአብሔር ማደሪያ ታቦትንም ከቤተ መንግሥት ዕቃ ቤትም ያለውን ሣጥኑን ሁሉ ማርከው ወደ ባቢሎን ወሰዱ። የእግዚአብሔር ማደሪያ ቤተ መቅደስንም አቃጠሉ የኢየሩሳሌምንም ቅጽሯን አፈረሱ ግምቧን በእሣት አቃጠሉ። በውጭ ያለውን ያማረውንም ዕቃዋን ሁሉ አጠፉ እግዚአብሔር በኤርምያስ አፍ የተናገረው ይደርስ ዘንድ።

እንደውም በተረፈ ኤርሚያስ ላይ የሚያገለግሉበትን ንዋየ-ቅዱሳት ሁሉ ጌታ እንዳዘዛቸው ለምድር ሰጧት ምድርም ያን ጊዜ ተቀብላ ዋጠችው ይለናል፦
ተረፈ ኤርሚያስ 8፥13 *”ባሮክ እና ኤርምያስም ወደ ቤተ መቅደስ ገቡ የሚያገለግሉበትን ዕቃ ሁሉ ጌታ እንዳዘዛቸው ለምድር ሰጧት ምድርም ያን ጊዜ ተቀብላ ዋጠችው”*።

የአገራችን ታሪክ የተፋለሰ መሆኑን የምናውቀው ይህ ጥቅስ ታቦተ ጽዮን በባቢሎናውያን እንደጠፋች መናገሩ ነው። ከዚያም ባሻገር ከሰለሞን 400 ዓመት በኋላ በኢዮስያስ ዘመነ-መንግሥት ታቦቱ በኢየሩሳሌም መኖሩን በዜና መዋዕል ላይ ተዘግቧል፦
ዜና መዋዕል ካልዕ 35፥3 እስራኤልንም ሁሉ ያስተምሩ ለነበሩት፥ ለእግዚአብሔርም ለተቀደሱት ሌዋውያን እንዲህ አለ፦ *ቅዱሱን ታቦት የእስራኤል ንጉሥ የዳዊት ልጅ ሰሎሞን በሠራው ቤት ውስጥ *አኑሩት*፤ ከዚህም በኋላ በትከሻችሁ ላይ ሸክም አይሆንባችሁም፤

ታቦተ ጽዮን አክሱም ላይ አለች የሚለው ትረካ ከክብረ ነገሥት ውጪ የታሪክ፣ የባይብል እና የሥነ-ቅርፅ መረጃ ሆነ ማስረጃ የለም። ታቦቱ እና ጽላቱ ቢኖሩም እንኳን በአዲስ ኪዳን ጥቅም የላቸውም። የአዲስ ኪዳን ታላቁ ጸሐፊ ጳውሎስ እንደሚነግረን ከሆነ ሙሴ ንዋየ-ቅዱሳቱን የሚሰራው የሚመጣውን ነገር እያየ እንደነበር ተዘግቧል፦
ዕብራውያን 8፥5 እነርሱም *ሙሴ ድንኳኒቱን ሊሠራ ሳለ እንደ ተረዳ፥ ለሰማያዊ ነገር ምሳሌና ጥላ የሚሆነውን ያገለግላሉ። በተራራው እንደ ተገለጠልህ ምሳሌ ሁሉን ታደርግ ዘንድ ተጠንቀቅ ብሎት ነበርና*።
ዘጸአት 25፥40 በተራራ ላይ *እንዳሳየሁህ ምሳሌ እንድትሠራ ተጠንቀቅ*።
የሐዋርያት ሥራ 7፥44 *እንዳየው ምስል አድርጎ ይሠራት ዘንድ ሙሴን ተናግሮ እንዳዘዘው፥ የምስክር ድንኳን ከአባቶቻችን ዘንድ በምድረ በዳ ነበረች*፤

ይህንን ጳውሎስ ታቦትና ጽላት “ጥላ”typology” እንደሆነ ይናገራል፤ ብሉይ ላይ የነበረው ኪዳን በአዲስ ኪዳን ተሽሯል፤ ይህም ኪዳን ጥላነቱ ታቦቱ የሰው አካል ሲሆን የሚጻፍበት ፊደል ደግሞ ለሰው ልብ ምሳሌ ሆኖ አዲሱ ኪዳን በልብ የሚጻፍ መሆኑኑን ይነግረናል፦
ኤርምያስ 31፥31 እነሆ፥ ከእስራኤል ቤትና ከይሁዳ ቤት ጋር *አዲስ ቃል ኪዳን* የምገባበት ወራት ይመጣል፥ ይላል እግዚአብሔር፤ ከግብጽ አገር አወጣቸው ዘንድ እጃቸውን በያዝሁበት ቀን ከአባቶቻቸው ጋር እንደ ገባሁት ያለ ቃል ኪዳን አይደለም፤ እነርሱ በኪዳኔ አልጸኑምና፥ እኔም ቸል አልኋቸው፥ ይላል እግዚአብሔር፡፡ ከእነዚያ ወራት በኋላ ከእስራኤል ቤት ጋር *የምገባው ቃል ኪዳን ይህ* ነውና፥ ይላል እግዚአብሔር፤ *ሕጌን በልቡናቸው አኖራለሁ*፥ *በልባቸውም እጽፈዋለሁ*፤ እኔም አምላክ እሆናቸዋለሁ እነርሱም ሕዝብ ይሆኑኛል።
ዕብራውያን 8፥10-13 ከዚያ ወራት በኋላ ከእስራኤል ቤት ጋር የምገባው ቃል ኪዳን ይህ ነውና ይላል ጌታ፤ *ሕጌን በልቡናቸው አኖራለሁ በልባቸውም እጽፈዋለሁ*፥ እኔም አምላክ እሆንላቸዋለሁ እነርሱም ሕዝብ ይሆኑልኛል። .. *አዲስ በማለቱ ፊተኛውን አስረጅቶአል፤ አሮጌና ውራጅ የሆነውስ ሊጠፋ ቀርቦአል*።

ብሉይ ማለት አሮጌ ማለት ነው። አሮጌ ያሰኘው አዲሱ ነው፣ አሮጌው ኪዳን ህጉ በድንጋይ ጽላት ላይ የተጻፈበት ኪዳን ሲሆን አዲሱ ደግሞ በልብ ጽላት ላይ የተጻፈበት ኪዳን ነው፣ በድንጋይ ላይ የተጻፈው ኪዳን አሮጌና ውራጅ እንደተባለ አስተውሉ፣ ከዚያም ባሻገር በአዲሱ ኪዳን አሮጌው ኪዳን ተሽሯል ይላል፦
2ኛ ቆሮ 3፥3 እናንተም በሕያው እግዚአብሔር መንፈስ እንጂ በቀለም አይደለም፥ *ሥጋ በሆነ በልብ ጽላት* እንጂ *በድንጋይ ጽላት* ያልተጻፈ፥ በእኛም የተገለገለ የክርስቶስ መልእክት እንደ ሆናችሁ የተገለጠ ነው።
2ኛ ቆሮ 3፥7 ዳሩ ግን የእስራኤል ልጆች ስለዚያ ስለ *ተሻረው* ስለ ፊቱ ክብር የሙሴን ፊት ትኩር ብለው መመልከት እስኪሳናቸው ድረስ፥ *ያ በፊደላት በድንጋዮች ላይ የተቀረጸ የሞት አገልግሎት* በክብር ከሆነ፥ የመንፈስ አገልግሎት እንዴት ይልቅ በክብር አይሆንም?
2ኛ ቆሮ 3፥13 *የዚያንም ይሻር* የነበረውን መጨረሻ ትኵር ብለው የእስራኤል ልጆች እንዳይመለከቱ፥ በፊቱ መጋረጃ እንዳደረገ እንደ ሙሴ አይደለንም።
2ኛ ቆሮ 3፥14 ነገር ግን አሳባቸው ደነዘዘ፡፡ ብሉይ ኪዳን ሲነበብ ያ መጋረጃ ሳይወሰድ እስከ ዛሬ ድረስ ይኖራልና፤ በክርስቶስ ብቻ *የተሻረ* ነውና።
ምን ትፈልጋለህ? በፊደላት በድንጋዮች ላይ የተቀረጸው ጽላት በልብ ጽላት ተሽሯል፣ ቤተመቅደሱም ሰው ሆኗል፦
1ኛ ቆሮ 3፥16-17 *የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ እንደ ሆናችሁ* የእግዚአብሔርም መንፈስ እንዲኖርባችሁ አታውቁምን? ማንም *የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስ ቢያፈርስ እግዚአብሔር እርሱን ያፈርሰዋል፤ የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ቅዱስ ነውና፥ ያውም እናንተ ናችሁ*።
1ኛ ቆሮ 6፥19-20 ወይስ *ሥጋችሁ ከእግዚአብሔር የተቀበላችሁት በእናንተ የሚኖረው የመንፈስ ቅዱስ ቤተ መቅደስ እንደ ሆነ አታውቁምን?*

አዲሱ ኪዳን ህጉ የተጻፈው በልብ ጽላት ላይ ከሆነ ቤተመቅደሱ የሰው አካል ከሆነ እግዚአብሔር ሰው በሰራው ቤተ መቅደስ አይኖርም ይለናል፦
የሐዋርያት ሥራ 17፥24 ዓለሙንና በእርሱ ያለውን ሁሉ የፈጠረ አምላክ እርሱ የሰማይና የምድር ጌታ ነውና እጅ በሠራው መቅደስ አይኖርም፤
የሐዋርያት ሥራ 7፥50 ነገር ግን ነቢዩ፦ ሰማይ ዙፋኔ ነው ምድርም የእግሬ መረገጫ ናት፤ ለእኔ ምን ዓይነት ቤት ትሠራላችሁ? ይላል ጌታ፥ ወይስ የማርፍበት ስፍራ ምንድር ነው? ይህንስ ሁሉ እጄ የሠራችው አይደለምን? እንዳለ፥ ልዑል *የሰው እጅ በሠራችው አይኖርም*።
ኢሳይያስ 66፥1 እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ ሰማይ ዙፋኔ ነው፥ ምድርም የእግሬ መረገጫ ናት፤ *የምትሠሩልኝ ቤት ምን ዓይነት ነው? የማርፍበትስ ስፍራ ምንድር ነው?*
ኤርምያስ 3፥16 በበዛችሁም ጊዜ በምድርም ላይ በረባችሁ ጊዜ፥ ይላል እግዚአብሔር፥ በዚያ ዘመን፦ *የእግዚአብሔር የቃል ኪዳኑ ታቦት ብለው ከእንግዲህ ወዲህ አይጠሩም* ልብ አያደርጉትም፥ አያስቡትምም፥ አይሹትምም፥ *ከእንግዲህ ወዲህም አይደረግም*።

የሚገርመው የአገራችን ክርስቲያኖች ከብሉይ ኪዳን ስንጠቅስ “ተሽሯል” ይሉናል፣ የተሻረው ታቦቱትና ጽላቱ እንጂ ሕጉ አይደለም። ሕጉማ በልብ ተጽፏል ተብሏል። የአገራችን ክርስቲያኖች ሕጉ ተሽሯል ይሉና የተጻፈበት ድንጋይ ሆነ የሚቀመጥበት ታቦት አልተሻረም ብለው ድርቅ ይላሉ፣ እራሳቸውን የሚያስጠጉበት ጳውሎስ በግልጽ የድንጋይ ጽላት እንደተሻረና አምላክ ሰው በሰራው ቤተመቅደስ እንደማይኖር ተናግሯል፣ ነገር ግን ዛሬ ያሉት ያገራችን ሰዎች ዛርኒሽ በተቀባ እንጨት ቀርጸው ታቦት ነው ብለው ለታቦቱ ሲሰግዱ፣ ሲለማመኑ፣ ሲማጸኑ፣ ሲሳሉ፣ ዕጣን ሲያጨሱ ይታያል፣ ይህ በትንቢት ስለ እነርሱ የተነገረው እየተፈጸመ ነውና በተውበት ወደ አላህ ተመለሱና አንዱን አምላክ በብቸኝነት አምልኩ፦
ኢሳይያስ 44፥15-19 *ለሰውም ማገዶ ይሆናል፤ ከእርሱም ወስዶ ይሞቃል፥ አንድዶም እንጀራ ይጋግርበታል፤ ከእርሱም አምላክ አበጅቶ ይሰግድለታል፥ የተቀረጸውንም ምስል ሠርቶ በእርሱ ፊት ይንበረከካል። ግማሹን በእሳት ያቃጥላል፥ በዚያ በግማሹ ሥጋ ይበላል፥ ሥጋም ይጠብስበትና ይጠግባል፤ ይሞቃልና፦ እሰይ ሞቅሁ፥ እሳቱን አይቻለሁ ይላል። የቀረውንም እንጨት አምላክ አድርጎ ምስል ይቀርጽበታል፤ በፊቱም ተጐንብሶ ይሰግዳል ወደ እርሱም እየጸለየ፦ አምላኬ ነህና አድነኝ ይላል። አያውቁም፥ አያስቡም፤ እንዳያዩ ዓይኖቻቸውን፥ እንዳያስተውሉ ልቦቻቸውን ጨፍነዋል። በልቡም ማንም አያስብም፦ ግማሽዋን በእሳት አቃጥያለሁ፥ በፍምዋም ላይ እንጀራን ጋግሬአለሁ፥ ሥጋም ጠብሼ በልቻለሁ፤ የቀረውንም አስጸያፊ ነገር አደርጋለሁን? ለዛፍስ ግንድ እሰግዳለሁን? እንዲልም እውቀትና ማስተዋል የለውም*።

ከዐቃቤ አሥልምና ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም