ወሒድ የዕቅበተ ኢሥላም መጣጥፍት"Wahid Articles of Islamic Apologetics"
58.4K subscribers
68 photos
69 videos
19 files
1.72K links
ዳዒ ወሒድ በኢሥላም እና በክርስትና መካከል ያለውን ልዩነት እና አንድነት በንጽጽር የሚያስቀምጥ ወንድም ነው። ለዚህም የቋንቋ፣ የሰዋስው፣ የዐውድ፣ የተዛማች እና የሥነ አመክንዮ ሙግት በማቅረብ የሚታወቅ ተሟጋች እና ጦማሪ ነው። ለሙግቱ ነጥብ በዋነኝነት የሚጠቀምባቸው ቋንቋ ዐማርኛ፣ ግዕዝ፣ እንግሊዝኛ፣ ዐረቢኛ፣ ዕብራይስጥ እና ግሪክ ናቸው። መልካም የንባብ፣ የጥናት፣ የማነጻጸር ጊዜ ይሁንልዎ!
Download Telegram
ሰባቱ ሰማያት

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ፥ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

65፥12 *"አላህ ያ ሰባት ሰማያትን የፈጠረ ነው"*፡፡ اللَّهُ الَّذِي خَلَقَ سَبْعَ سَمَاوَاتٍ

"ሠማእ" سَّمَاء የሚለው ቃል "ሠማ" سَمَا ማለትም "ከፍ አለ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "ከፍታ" ወይም "አርያም" አሊያም "ሰማይ" ማለት ነው፥ አምላካችን አሏህ ሰማይን ጭስ"gas" አርጎ ከፈጠራት በኃላ በጭስ ደረጃ እያለች ለእርሷ እና ለምድር፦ "ወዳችሁም ኾነ ወይም ጠልታችሁ ኑ" አላቸው፥ እነርሱም፦ "ታዛዦች ኾነን መጣን" አሉ፦
41፥11 *”ከዚያም ወደ ሰማይ እርሷ ጭስ ኾና ሳለች አሰበ፡፡ ለእርሷም ለምድርም «ወዳችሁም ኾነ ወይም ጠልታችሁ ኑ» አላቸው”*፡፡ «ታዛዦች ኾነን መጣን» አሉ፡፡ ثُمَّ اسْتَوَىٰ إِلَى السَّمَاءِ وَهِيَ دُخَانٌ فَقَالَ لَهَا وَلِلْأَرْضِ ائْتِيَا طَوْعًا أَوْ كَرْهًا قَالَتَا أَتَيْنَا طَائِعِينَ

“ሳለች” የሚለው ኃይለ-ቃል ይሰመርበት! በጭስ ደረጃ የነበረችውን ሰማይ ሰባት ሰማያት አደረጋቸው፦
41፥12 በሁለት ቀኖችም ውስጥ *”ሰባት ሰማያትም አደረጋቸው”*፡፡ فَقَضَاهُنَّ سَبْعَ سَمَاوَاتٍ فِي يَوْمَيْنِ
2፥29 እርሱ ያ በምድር ያለውን ሁሉ ለእናንተ የፈጠረ ነው፡፡ *ከዚያም ወደ ሰማይ አሰበ፥ ”ሰባት ሰማያትም አደረጋቸው”*፡፡ هُوَ الَّذِي خَلَقَ لَكُم مَّا فِي الْأَرْضِ جَمِيعًا ثُمَّ اسْتَوَىٰ إِلَى السَّمَاءِ فَسَوَّاهُنَّ سَبْعَ سَمَاوَاتٍ ۚ

"ሠማዋት" سَمَاوَات የሚለው ቃል የሠማእ ብዙ ቁጥር ሲሆን "ሰማያት" ማለት ነው፥ አምላካችን አሏህ ሰባት ጊዜ፦ "ሠብዐ ሠማዋት" سَبْعَ سَمَاوَات ማለትም "ሰባት ሰማያት" በማለት ተናግሯል፦
65፥12 *"አላህ ያ ሰባት ሰማያትን የፈጠረ ነው"*፡፡ اللَّهُ الَّذِي خَلَقَ سَبْعَ سَمَاوَاتٍ
2፥29 *"ሰባት ሰማያትም አደረጋቸው”*፡፡ فَسَوَّاهُنَّ سَبْعَ سَمَاوَاتٍ
67፥3 *"ያ ሰባት ሰማያት የተነባበሩ ኾነው የፈጠረ ነው"*፡፡ الَّذِي خَلَقَ سَبْعَ سَمَاوَاتٍ طِبَاقًا
41፥12 በሁለት ቀኖችም ውስጥ *”ሰባት ሰማያትም አደረጋቸው”*፡፡ فَقَضَاهُنَّ سَبْعَ سَمَاوَاتٍ فِي يَوْمَيْنِ
71፥15 *"አላህ ሰባት ሰማያት አንዱ ካንዱ በላይ ሲኾን እንዴት እንደፈጠረ አታዩምን?"* أَلَمْ تَرَوْا كَيْفَ خَلَقَ اللَّهُ سَبْعَ سَمَاوَاتٍ طِبَاقًا
17፥44 *"ሰባቱ ሰማያት እና ምድርም በውስጣቸውም ያለው ሁሉ ለእርሱ ያጠራሉ"*፡፡ تُسَبِّحُ لَهُ السَّمَاوَاتُ السَّبْعُ وَالْأَرْضُ وَمَن فِيهِنَّ
23፥86 *«የሰባቱ ሰማያት ጌታ እና የታላቁ ዐርሽ ጌታ ማን ነው» በላቸው*፡፡ قُلْ مَن رَّبُّ السَّمَاوَاتِ السَّبْعِ وَرَبُّ الْعَرْشِ الْعَظِيمِ
አምላካችን አሏህ እነዚህን ሰማያት "ሰባት ብርቱዎች" እና "ሰባት መንገዶች" ይላቸዋል፦
78፥12 *"ከበላያችሁም ሰባት ብርቱዎች ገነባን"*፡፡ وَبَنَيْنَا فَوْقَكُمْ سَبْعًا شِدَادًا
23፥17 *"በእርግጥም ከበላያችሁ ሰባት መንገዶችን ፈጠርን"*፡፡ وَلَقَدْ خَلَقْنَا فَوْقَكُمْ سَبْعَ طَرَائِقَ

"ጦራኢቅ" طَرَائِق ብዜት ሲሆን "መንገዶች" ማለት ነው፥ "ጦሪቅ" طَرِيق ማለትም "መንገድ" ለሚለው ነጠላ ቃል ብዜት ነው። ነቢያችን"ﷺ" የመጀመሪያው ሰማይ ከሆነ ከአሥ-ሠማኡ አድ-ዱንያህ እስከ ሰባተኛው ሰማይ ድረስ ያሉትን እነዚህን ሰባት መንገዶች በለይለቱል ኢሥራእ ወል ሚራጅ ጊዜ ተጉዘዋል፦
ሪያዱ አስ-ሷሊሒን መጽሐፍ 1, ሐዲስ 184
ስለ ኢሥራእ በዝነኛ ሐዲስ አነሥ”ረ. ዐ.” እንደተረከው፦ “የአላህ መልክተኛ”ﷺ” እንዲህ አሉ፦ *"ጂብሪል ከእኔ ጋር ወደ ቅርቢቱ ሰማይ ወጣ፥ እንዲከፈት ተጠየቀ። ዘበኛው፦ "ይህ ማን ነው? ብሎ ጠየቀ፥ ጂብሪልም፦ "ጂብሪል" አለ። "ከአንተ ጋር ያለውስ? እርሱም፦ "ሙሐመድ ነው" አለ። ከዚያም በተመሳሳይ ወደ ሁለተኛ፣ ወደ ሦስተኛ፣ ወደ አራተኛ እና ወደተቀሩት ሰማያት ሁሉ ወጣ። የሁሉም ሰማይ በር ላይ "ይህ ማን ነው? ተብሎ ተጠየቀ፥ "ጂብሪል ነው" ተባለ"*። عن أنس رضي الله عنه في حديثه المشهور في الإسراء قال‏:‏ قال رسول الله صلى الله عليه وسلم ‏:‏ ‏ "‏ثم صعد بي جبريل إلي السماء الدنيا فاستفتح، فقيل‏:‏ من هذا‏؟‏ قال‏:‏ جبريل، قيل‏:‏ومن معك‏؟‏ قال‏:‏ محمد‏.‏ ثم صعد إلي السماء الثانية والثالثة والرابعة وسائرهن، ويقال في باب كل سماء‏:‏ من هذا‏؟‏ فيقول‏:‏ جبريل‏"‏

የቅርቢቱ ሰማይ ውስጥ ካሉት ከበረዶ ጋራ፣ ከኦዞን እና ከከዋክብት በላይ የቅርቢቱ ሰማይ ክፍል ሆኖ አንደኛው ሰማይ ይጀምራል፥ ሰባተኛው ሰማይ መላእክት ይኖሩበታል፦
53፥26 *"በሰማያት ውስጥ ካለ መልአክም ብዙዎች ሊማለዱለት ለሚሻው እና ለሚወደው ሰው ከፈቀደ በኋላ ቢኾን እንጅ ምልጃቸው ምንም አትጠቅምም"*፡፡ وَكَم مِّن مَّلَكٍ فِي السَّمَاوَاتِ لَا تُغْنِي شَفَاعَتُهُمْ شَيْئًا إِلَّا مِن بَعْدِ أَن يَأْذَنَ اللَّهُ لِمَن يَشَاءُ وَيَرْضَىٰ

ዝናብ ከሰማይ ወደ ምድር ከገባ በኃላ ወደ ሰማይ በትነተ ስርገት እንደሚወጣ ሁሉ መላእክትን ከአሏህ በመላክ ከሰማያት ወርደው ተመልሰው ወደ ሰማያት ያርጋሉ፦
78፥2 *"በምድር ውስጥ የሚገባውን ሁሉ ከእርሷም የሚወጣውን ከሰማይም የሚወርደውን በእርሷም ውስጥ የሚያርገውን ሁሉ ያውቃል"*፡፡ እርሱም አዛኙ መሓሪው ነው፡፡ يَعْلَمُ مَا يَلِجُ فِي الْأَرْضِ وَمَا يَخْرُجُ مِنْهَا وَمَا يَنزِلُ مِنَ السَّمَاءِ وَمَا يَعْرُجُ فِيهَا ۚ وَهُوَ الرَّحِيمُ الْغَفُورُ

ቁርኣን "ሰማይ" ሲል አንዳንዴ "ሰባቱ ሰማያትን" ያመለክታል አንዳንዴ "ቅርቢቱን ሰማይ" ያመለክታል፥ የትኛውን እንደሚያመለክት የዐውደ-ንባቡ ፍሰት ይወስነዋል።
በባይብልም ቢሆን ብዙ ሰማዮች እንዳሉ ለማመልከት "ሰማያት" በሚል ብዙ ቁጥር ይጠቀማል፥ የቁጥራቸው መጠን ስንት እንደሆነ ባይገለጽም ከአራት በላይ እንደሆኑ ይገልጻል፦
ዘዳግም 10፥14 *"እነሆ፥ ሰማይ ሰማየ ሰማያትም፥ ምድርም በእርስዋም ያለው ሁሉ የአምላክህ የያህዌህ ነው"*።
2ኛ ዜና መዋዕልዕ 2፥6 *"ነገር ግን ሰማይ እና ከሰማያት በላይ ያለ ሰማይ ይይዘው ዘንድ አይችልምና"*።
ነህምያ 9፥6 *"አንተ ብቻ ያህዌህ ነህ፤ ሰማዩን እና የሰማያት ሰማይን ሠራዊታቸውንም ሁሉ፥ ምድሩንና በእርስዋ ላይ ያሉትን ሁሉ፥ ባሕሮቹንና በእነርሱ ውስጥ ያለውን ሁሉ፥ ፈጥረሃል"*።

እነዚህ ሦስት አናቅጽ ላይ "ሰማይ" ሲል አንድ ሰማይ እንዳለ አመላካች ነው፣ "ሰማያት" ሲል ሁለትዮች ያልሆኑ በትንሹ ሦስት ሰማያት እንዳሉ አመላካች ነው፣ ከሰማያት በላይ ያለው "ሰማይ" ደግሞ አንድ ሰማይ እንዳለ አመላካች ነው። በትንሹ አምስት ሰማያት ተገልጸዋል፥ በአይሁዳውያን እና በክርስትና ትውፊት ደግሞ ሰባት ሰማያት እንዳሉ ይታመናል።

ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
የመጨረሻይቱም ዓለም

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ፥ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

12፥57 *"የመጨረሻይቱም ዓለም ምንዳ ለእነዚያ ላመኑት እና ይጠነቀቁ ለነበሩት የበለጠ ነው"*፡፡ وَلَأَجْرُ الْآخِرَةِ خَيْرٌ لِّلَّذِينَ آمَنُوا وَكَانُوا يَتَّقُونَ

"ዱንያ" دُّنْيَا የሚለው ቃል "አድና" أَدْنَى‎ ማለትም "ቅርብ" ለሚለው ተባዕታይ መደብ አንስታይ መደብ ሲሆን "ቅርቢቱ" ማለት ነው፥ “አኺራ” آخِرَةِ የሚለው ቃል "አኺር" آخِر ማለትም "መጨረሻ" ለሚለው ተባዕታይ መደብ አንስታይ መደብ ሲሆን "መጨረሻይቱ" ማለት ነው። ከቅርቢቱ ሰማይ ጀምሮ እስከ ሰባተኛው ሰማይ ድረስ ያለው ዓለም "አኺራ" آخِرَةِ ወይም "የመጨረሻይቱ ዓለም" ነው፦
12፥57 *"የመጨረሻይቱም ዓለም ምንዳ ለእነዚያ ላመኑት እና ይጠነቀቁ ለነበሩት የበለጠ ነው"*፡፡ وَلَأَجْرُ الْآخِرَةِ خَيْرٌ لِّلَّذِينَ آمَنُوا وَكَانُوا يَتَّقُونَ

ሰዎች ሲፈረድባቸው የሚያገኙት ፍዳ እና ሲፈረድላቸው የሚያገኙት ምንዳ የሚቀጠሩበት አኺራ ሰማይ ነው፦
51፥ 22 *"ሲሳያችሁ እና የምትቀጠሩትም ፍዳ እና ምንዳ በሰማይ ውስጥ ነው"*፡፡ وَفِي السَّمَاءِ رِزْقُكُمْ وَمَا تُوعَدُونَ

"ሲሳያችሁም በሰማይ ውስጥ ነው" ማለት ፍራፍሬን ሲሳይ ለማድረግ ከቅርቢቱ ሰማይ የሚወርደውን ውኃ ያመለክታል፦
40፥13 *"ለእናንተም ከሰማይ ሲሳይን የሚያወርድላችሁ ነው"*፡፡ وَيُنَزِّلُ لَكُم مِّنَ السَّمَاءِ رِزْقًا
2፥22 *"ከሰማይም ውኃን ያወረደ በእርሱም(በውኃ) ከፍሬዎች ለእናንተ ሲሳይን ያወጣ ነው"*፡፡ وَأَنزَلَ مِنَ السَّمَاءِ مَاءً فَأَخْرَجَ بِهِ مِنَ الثَّمَرَاتِ رِزْقًا لَّكُمْ

"የምትቀጠሩትም ፍዳ እና ምንዳ በሰማይ ውስጥ ነው" ማለት የምትቀጠሩት ሁሉ በእርግጥ መጪ ነው፥ በፍርዱ ቀን ሰማይም የምትከፈት እና ባለ ደጃፎች የምትሆንበት ቀን ነው ማለት ነው፦
6፥134 *"የምትቀጠሩት ሁሉ በእርግጥ መጪ ነው፡፡ እናንተም አምላጮች አይደላችሁም"*፡፡ إِنَّ مَا تُوعَدُونَ لَآتٍ ۖ وَمَا أَنتُم بِمُعْجِزِينَ
78፥19 ሰማይም በምትከፈት እና ባለ ደጃፎችም በምትኾንበት ቀን ነው"*፡፡ وَفُتِحَتِ السَّمَاءُ فَكَانَتْ أَبْوَابًا
ጃምዒ አት-ቲርሚዚይ መጽሐፍ 48, ሐዲስ 221
አቢ ሁረይራህ”ረ. ዐ.” እንደተረከው፦ “የአላህ መልክተኛ”ﷺ” እንዲህ አሉ፦ *"አንድ የአሏህ ባሪያ ዐበይት ኃጢአቶችን እስከተከለከለ ድረስ ጥርት አድርጎ፦ "ላ ኢላሀ ኢለል ሏህ" በጭራሽ አይልም፥ ወደ ዙፋኑ እስኪደርስ ድረስ የሰማይ ደጆች የሚከፈቱለት ቢሆን እንጂ"*። عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ، رضى الله عنه قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم ‏ "‏ مَا قَالَ عَبْدٌ لاَ إِلَهَ إِلاَّ اللَّهُ قَطُّ مُخْلِصًا إِلاَّ فُتِحَتْ لَهُ أَبْوَابُ السَّمَاءِ حَتَّى تُفْضِيَ إِلَى الْعَرْشِ مَا اجْتَنَبَ الْكَبَائِرَ ‏"‏

በኢኽላስ “ላ ኢላሀ ኢለል ሏህ” لَا إِلٰهَ إِلَّا اللّٰه ያለ ሰው የሰማይ ደጆች ይከፈቱለታል፥ "ኢኽላስ" إِخْلَاص የሚለው ቃል "አኽለሶ" أَخْلَصَ‎ ማለትም "አጠራ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን እውነት ለማንገሥ ሐሠትን ለማርከሥ የሚደረግ "መተናነስ" እና ከሙገሳና ከወቀሳ ነጻ ሆኖ ለአሏህ ውዴታ የሚደረግ "ማጥራት" ማለት ነው። ኢኽላስ ያለው የአሏህ ባሪያ ደግሞ "ሙኽሊስ" مُخْلِص ይባላል፥ የሰማይ ደጆች የሚከፈቱለት እስከ ዐርሽ ሥር እስካለው እስከ ጀናቱል ፊርደውሥ ድረስ ነው። ነገር ግን በአሏህ አናቅጽ ያስተባበሉ እና የኮሩ የሰማይ ደጃፎች አይከፈቱላቸውም፥ ግመል በመርፌ ቀዳዳ እስከሚገባም ድረስ ጀናህ አይገቡም፦
7፥40 *"እነዚያ አንቀጾቻችንን ያስተባበሉ ከእርሷም የኮሩ ለእነርሱ የሰማይ ደጃፎች አይከፈቱላቸውም፥ ግመል በመርፌ ቀዳዳ እስከሚገባም ድረስ ጀናህ አይገቡም"*፡፡ إِنَّ الَّذِينَ كَذَّبُوا بِآيَاتِنَا وَاسْتَكْبَرُوا عَنْهَا لَا تُفَتَّحُ لَهُمْ أَبْوَابُ السَّمَاءِ وَلَا يَدْخُلُونَ الْجَنَّةَ حَتَّىٰ يَلِجَ الْجَمَلُ فِي سَمِّ الْخِيَاطِ ۚ

"የሰማይ ደጃፎች አይከፈቱላቸውም፥ ግመል በመርፌ ቀዳዳ እስከሚገባም ድረስ ጀናህ አይገቡም" የሚለው ኃይለ-ቃል የሚከፈቱት የሰማይ ደጆች የሚገባበት ጀናህ መሆኑን ፍንትው አድርጎ ያሳያል። የመጨረሻይቱም አገር ለእነዚያ ለተጠነቀቁት በእርግጥ የተሻለች ናት፦
12፥109 *"የመጨረሻይቱም አገር ለእነዚያ ለተጠነቀቁት በእርግጥ የተሻለች ናት"* አታውቁምን? وَلَدَارُ الْآخِرَةِ خَيْرٌ لِّلَّذِينَ اتَّقَوْا ۗ أَفَلَا تَعْقِلُونَ

አሏህ የመጨረሻይቱ አገር ከሚገቡት ሙተቂን ባሮቹ ያድርገን! አሚን።

ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
ጀናቱል ፊርደውሥ

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ፥ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

23፥11 *"እነዚያ ፊርደውሥን የሚወርሱ ናቸው፥ እነርሱ በእርሷ ውስጥ ዘውታሪዎች ናቸው"*፡፡ الَّذِينَ يَرِثُونَ الْفِرْدَوْسَ هُمْ فِيهَا خَالِدُونَ

"ጀናህ" جَنَّة የሚለው ቃል “ጀንነ” جَنَّ ማለትም “ሰወረ” ወይም “ደበቀ” ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን “የተሰወረ” ወይም “የተደበቀ” ማለት ነው፥ የጀናህ ብዙ ቁጥር ደግሞ "ጀናት" جَنَّات‎ ነው። ለምሳሌ “ጂኒ” جِنِّيّ ማለት እራሱ “ስውር” ወይም “ድብቅ” ማለት ነው፥ “ጀነ” جَنَّ የሚለው ቃል በግስ መደብ ረቂቅነትን፣ ምጡቅነትን፣ ስውርነትን ለማመልከት ገብቷል፦
6፥76 ሌሊቱም በእርሱ ላይ *”ባጨለመ”* ጊዜ ኮከብን አየ፡፡ «ይህ ጌታዬ ነው» አለ፡፡ በጠለቀም ጊዜ፡- «ጠላቂዎችን አልወድም» አለ፡፡ فَلَمَّا جَنَّ عَلَيْهِ اللَّيْلُ رَأَىٰ كَوْكَبًا ۖ قَالَ هَـٰذَا رَبِّي ۖ فَلَمَّا أَفَلَ قَالَ لَا أُحِبُّ الْآفِلِينَ

እዚህ አንቀጽ ላይ “አጨለመ” ለሚለው ቃል “ጀነ” جَنَّ ሲሆን “ሸፈነ” “ደበቀ” ሰወረ” ማለት ነው። “መጅኑን” مَجْنُون‎ በቋንቋ ደረጃ ከሄድን እራሱ “ጀነ” جَنَّ‎ ማለትም “ሰወረ” ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን ዐቅሉ “የተሰወረ” “የተደበቀ” ማለት ነው፦
68፥2 *”አንተ በጌታህ ጸጋ የተጎናጸፍክ ስትኾን ዕብድ አይደለህም”*፡፡ مَا أَنتَ بِنِعْمَةِ رَبِّكَ بِمَجْنُونٍ

እዚህ አንቀጽ ላይ “ዕብድ” ለሚለው ቃል የገባው “መጅኑን” مَجْنُون‎ መሆኑን ልብ አድርግ! እሩቅ ሳንሄድ ማኅፀን ውስጥ ያለውን “ሽል” ለዓይናችን የተደበቀ ስለሆነ “አጂናህ” أَجِنَّة ማለትም “ስውር” ወይም “ድብቅ” ተብሏል፦
53፥32 *ከምድር በፈጠራችሁ ጊዜ እናንተም በእናቶቻችሁ ማኅፀኖች ውስጥ “ሽሎች” በኾናችሁ ጊዜ እርሱ በእናንተ ሁኔታ ዐዋቂ ነው*፡፡ هُوَ أَعْلَمُ بِكُمْ إِذْ أَنشَأَكُم مِّنَ الْأَرْضِ وَإِذْ أَنتُمْ أَجِنَّةٌ فِي بُطُونِ أُمَّهَاتِكُمْ ۖ فَلَا تُزَكُّوا أَنفُسَكُمْ

እዚህ አንቀጽ ላይ “ሽሎች” ለሚለው ቃል የገባው “አጂናህ” أَجِنَّة መሆኑን ልብ አድርግ! "ጀናህ" جَنَّة የሚለው ቃል በሌላ ቦታ "አትክልት" በሚል ይመጣል፦
13፥4 *በምድርም የተጎራበቱ ቁርጥራጮች አሉ፥ ከወይኖችም "አትክልቶች" አዝርዕቶችም መንታዎችና መንታዎች ያልኾኑ ዘንባባዎችም አሉ። በአንድ ውሃ ይጠጣሉ"*። وَفِي الْأَرْضِ قِطَعٌ مُّتَجَاوِرَاتٌ وَجَنَّاتٌ مِّنْ أَعْنَابٍ وَزَرْعٌ وَنَخِيلٌ صِنْوَانٌ وَغَيْرُ صِنْوَانٍ يُسْقَىٰ بِمَاءٍ وَاحِدٍ

እዚህ አንቀጽ ላይ "አትክልቶች" ለሚለው የገባው ቃል "ጀናት" جَنَّات‎ መሆኑን አንባቢ ልብ ይለዋል፥ እዚህ ድረስ ከተግባባን በመጨረሻይቱ ዓለም ከሰው ልጆችን እይታ የተሰወረች እና የተደበቀች የአትክልት ስፍራ "ጀናህ" جَنَّة ትባላለች። ጀናህ መቶ ጀረዎች አሏት፥ ደረጃዎቿም ልክ የሰማይ እና የምድር እርቀት ያክል ነው። ጀናህ ትልቁ ደረጃዋ ፊርደውሥ ነው፦
6፥132 *"ለሁሉም ከሠሩት ሥራ የተበላለጡ ደረጃዎች አሏቸው፡፡ ጌታህም ከሚሠሩት ሁሉ ዘንጊ አይደለም"*፡፡ وَلِكُلٍّ دَرَجَاتٌ مِّمَّا عَمِلُوا ۚ وَمَا رَبُّكَ بِغَافِلٍ عَمَّا يَعْمَلُونَ
20፥75 *"በጎ ሥራዎችን በእርግጥ የሠራ ምእመን ኾኖ የመጣውም ሰው እነዚያ ለእነሱ ከፍተኛ ደረጃዎች አሏቸው"*፡፡ وَمَن يَأْتِهِ مُؤْمِنًا قَدْ عَمِلَ الصَّالِحَاتِ فَأُولَـٰئِكَ لَهُمُ الدَّرَجَاتُ الْعُلَىٰ
ሡነን ኢብኑ ማጃህ መጽሐፍ 37, ሐዲስ 4474
ሙዓዝ ኢብኑ ጀበል የአሏህ መልእክተኛ"ﷺ" እንዲህ ሲሉ ሰማው ብሎ እንደተረከው፦ "እርሳቸውም አሉ፦ *"ጀናት መቶ ጀረዎች አሏት፥ ደረጃዎቿም ያላቸው እርቀት ልክ የሰማይ እና የምድር እርቀት ያክል ነው። ከፍተኛ ደረጃዋ ፊርደውሥ ነው፥ የእርሷ ማእከል ፊርደውሥ ነው። ዐርሽም ከፊርደውሥ በላይ ነው፥ ከፊርደውሥ የጀናህ ወንዞች ይፈልቃሉ። አሏህን በጠየቃችሁት ጊዜ ስለ ፊርደውሥ ጠይቁት"*። أَنَّ مُعَاذَ بْنَ جَبَلٍ، قَالَ سَمِعْتُ رَسُولَ اللَّهِ ـ صلى الله عليه وسلم ـ يَقُولُ ‏ "‏ الْجَنَّةُ مِائَةُ دَرَجَةٍ كُلُّ دَرَجَةٍ مِنْهَا مَا بَيْنَ السَّمَاءِ وَالأَرْضِ وَإِنَّ أَعْلاَهَا الْفِرْدَوْسُ وَإِنَّ أَوْسَطَهَا الْفِرْدَوْسُ وَإِنَّ الْعَرْشَ عَلَى الْفِرْدَوْسِ مِنْهَا تُفَجَّرُ أَنْهَارُ الْجَنَّةِ فَإِذَا مَا سَأَلْتُمُ اللَّهَ فَسَلُوهُ الْفِرْدَوْسَ ‏"‏ ‏.‏

የሰባተኛው ሰማይ መጨረሻ ሊታለፍ የማይችል ድንበራዊ ዛፍ "ሲድረቱል ሙንተሃ" سِدْرَة الْمُنْتَهَى ነው፥ በሰባተኛ ሰማይ ከዕባህ ንድፍ የሆነበት ሰባ ሺህ መላእክት አምልኮ የሚፈጽሙበት የደመቀው ቤት "በይቱል መዕሙር" بَيْت الْمَعْمُور አለ። በሰባተኛው ሰማይ ካለው ከፊርደውሥ የጀናህ ወንዞች ይፈልቃሉ፥ "ፊርደውሥ" فِرْدَوْس ማለት "ላዕላይ" "ከፍተኛ" "ላይኛው" ማለት ሲሆን "ጀናቱል ፊርደውሥን" جَنَّاتُ الْفِرْدَوْس እነዚያ ያመኑ እና መልካም ሥራዎችን የሠሩ፣ እነዚያም እነርሱ ለአደራዎቻቸው እና ለቃል ኪዳናቸው ጠባቂዎች የሆኑት፣ እነዚያም እነርሱ በስግደቶቻቸው ላይ የሚጠባበቁ የሆኑት የሚወርሷት ነው፦
18፥107 *"እነዚያ ያመኑ እና መልካም ሥራዎችን የሠሩ የፊርደውሥ ገነቶች ለእነርሱ መስፈሪያ ናቸው"*፡፡ إِنَّ الَّذِينَ آمَنُوا وَعَمِلُوا الصَّالِحَاتِ كَانَتْ لَهُمْ جَنَّاتُ الْفِرْدَوْسِ نُزُلًا
23፥11 *"እነዚያ ፊርደውሥን የሚወርሱ ናቸው፥ እነርሱ በእርሷ ውስጥ ዘውታሪዎች ናቸው"*፡፡ الَّذِينَ يَرِثُونَ الْفِرْدَوْسَ هُمْ فِيهَا خَالِدُونَ

ቁርኣን ይህንን ሁሉ የሰማያት ዕውቀት እንዴት አዥጎደጎደው? ስንባል መልሳችን፦ "ያ በሰማያት ውስጥ ያለውን ምሥጢር የሚያውቀው አሏህ ወደ ነቢዩ"ﷺ" ያወረደው ዕውቀት ነው" የሚል ይሆናል፦
25፥6 *«ያ በሰማያትና በምድር ውስጥ ያለን ምሥጢር የሚያውቀው አወረደው፥ እርሱ መሓሪ አዛኝ ነውና» በላቸው*፡፡ قُلْ أَنزَلَهُ الَّذِي يَعْلَمُ السِّرَّ فِي السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضِ ۚ إِنَّهُ كَانَ غَفُورًا رَّحِيمًا

አሏህ ባወረደው ዕውቀት ተጠቃሚዎች ያድርገን! ጀናቱል ፊርደውሥን ይወፍቀን! አሚን።

ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
ሲድረቱል ሙንተሃ

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ፥ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

53፥14 *"በሲድረቱል ሙንተሃ አጠገብ አይቶታል"*። عِندَ سِدْرَةِ الْمُنتَهَىٰ

"ሢድር" سِدْر የዛፍ ዓይነት ሲሆን በመካከለኛው ምሥራቅ አካባቢ የሚበቅል ተክል ነው፦
34፥16 *"በአትክልቶቻቸውም ሁለት አትክልቶች፣ ባለመርጋጋ ፍሬዎችን፣ ባለጠደቻ እና ከሢድር ባለጥቂት ዛፎችን ለወጥናቸው"*፡፡ وَبَدَّلْنَاهُم بِجَنَّتَيْهِمْ جَنَّتَيْنِ ذَوَاتَيْ أُكُلٍ خَمْطٍ وَأَثْلٍ وَشَيْءٍ مِّن سِدْرٍ قَلِيلٍ

እዚህ አንቀጽ ላይ "አትክልት" ለሚለው ቃል የገባው "ጀናህ" جَنَّة ነው፥ ይህንን የሢድር ተክል አላግባብ መቁረጥ አሏህ ዘንድ ያስቀጣል፦
ሡነን አቢ ዳውድ 43, ሐዲስ 467
ዐብደሏህ አብኑ ሑብሺይ እንደተረከው፦ "የአሏህ መልእክተኛም"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ *"ማንም ሢድርን የቀጠፈ አሏህ ጭንቅላቱን በእሳት ውስጥ ያመጣዋል"*። عَنْ عَبْدِ اللَّهِ بْنِ حُبْشِيٍّ، قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم ‏ "‏ مَنْ قَطَعَ سِدْرَةً صَوَّبَ اللَّهُ رَأْسَهُ فِي النَّارِ ‏"‏

ስለ ሢድር ይህን ያክል ካየን ዘንዳ በሰባተኛ ሰማይ ላይ አስሓቡል የሚን እሾህ በሌለው ሢድር ውስጥ ይሆናሉ፦
56፥27 *"የቀኝም ጓዶች ምንኛ የከበሩ የቀኝ ጓዶች!"* وَأَصْحَابُ الْيَمِينِ مَا أَصْحَابُ الْيَمِينِ
56፥28 *"በተቀፈቀፈ እሾህ በሌለው ሢድር ውስጥ ናቸው"*፡፡ فِي سِدْرٍ مَّخْضُودٍ

በሰባተኛ ሰማይ ላይ የተጠቀሰው ሢድር በመካከለኛው ምሥራቅ አካባቢ ከሚበቅለው ዛፍ ጋር በስም እንጂ በቅርፅ እና በይዘት አንድ አይደሉም። የስም መመሳሰል የባሕርይ መመሳሰልን አያመለክትም፥ ለምሳሌ "ኤፍራጥስ" እና "ናይል" ወንዝ ምድር ላይ እንዳሉ ሁሉ ከፊርደውሥ ከሚፈልቁ ወንዞች ሁለቱ ስማቸው "ፉራት" فُرَات እና "ኒል" نِّيل የሚባሉ አሉ። ልክ እንደዚሁ መካከለኛው ምሥራቅ አካባቢ የሚበቅለው ዛፍ ሢድር እና ሰባተኛ ሰማይ ላይ ያለው ሢድር በስም እንጂ በቅርፅ እና በይዘት አንድ አይደሉም።
"ሢድር" سِدْر ተባዕታይ መደብ ሲሆን አንስታይ መደቡ "ሢድራህ" سِدْرَة ነው፥ ነቢያችን"ﷺ" በለይለቱል ኢሥራእ ወልሚራጅ ጊዜ ወደዚህ ሢድር ደርሰዋል፦
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 74, ሐዲስ 36
አነሥ ኢብኑ ማሊክ እንደተረከው፦ "የአሏህ መልእክተኛም"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ *"አራቱን ወንዞች ባየሁ ጊዜ ወደ ሢድራን ወጣሁኝ"*። عَنْ أَنَسِ بْنِ مَالِكٍ، قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم ‏ "‏ رُفِعْتُ إِلَى السِّدْرَةِ فَإِذَا أَرْبَعَةُ أَنْهَارٍ،

ነቢያችን"ﷺ" ይህ ሢድር በመላእክት፣ በብርሃን እና በቀለም ዓይነት ሲሸፈን ጂብሪልን አዩት፦
53፥16 *"አሥ-ሢድራህን የሚሸፍን ነገር በሚሸፍናት ጊዜ አየው"*፡፡ إِذْ يَغْشَى السِّدْرَةَ مَا يَغْشَىٰ

ጂብሪል ወደ ነቢያችን"ﷺ" የሚመጣው በሚወዱት ባልደረባ በዲሕያህ ኢብኑ ኸሊፋህ በሚባል ሰው ተመስሎ ነው፦
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 66, ሐዲስ 2
አቡ ዑስማን እንደተረከው፦ *"ጂብሪል ወደ ነቢዩ"ﷺ" ሲመጣ ኡሙ ሠላማህ ከእርሳቸው ጋር ነበረች፥ ጂብሪል መናገር ጀመረ። ነቢዩም"ﷺ"፦ "ኡሙ ሠላማህ ይህ ማን ነው? አሉ፥ እርሷም፦ "ይህ ዲሕያህ ነው" አለች። ጂብሪል በሄደ ጊዜ እርሷም፦ "ወሏሂ! በነቢዩ"ﷺ" ሑጥባህ ላይ ስለ ጂብሪል ዜና እስኪነግሩን ድረስ ከዲሕያህ በስተቀር ሌላ ማንንም አላሰብኩም ነበር"*። عَنْ أَبِي عُثْمَانَ، قَالَ أُنْبِئْتُ أَنَّ جِبْرِيلَ، أَتَى النَّبِيَّ صلى الله عليه وسلم وَعِنْدَهُ أُمُّ سَلَمَةَ فَجَعَلَ يَتَحَدَّثُ فَقَالَ النَّبِيُّ صلى الله عليه وسلم لأُمِّ سَلَمَةَ ‏ "‏ مَنْ هَذَا ‏"‌‏.‏ أَوْ كَمَا قَالَ قَالَتْ هَذَا دِحْيَةُ‏.‏ فَلَمَّا قَامَ قَالَتْ وَاللَّهِ مَا حَسِبْتُهُ إِلاَّ إِيَّاهُ حَتَّى سَمِعْتُ خُطْبَةَ النَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم يُخْبِرُ خَبَرَ جِبْرِيلَ أَوْ كَمَا قَالَ،
በተፈጥሮ ቅርፁ ግን ለመጀመሪያ ጊዜ በመንገድ ጉዞ እያሉ ጂብሪል ወርዶ በሰማይ እና በምድር መካከል ተቀምጦ አይተውታል፦
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 78, ሐዲስ 238
ጃቢ ኢብኑ ዐብደሏህ እንደተረከው፦ "የአሏህ መልእክተኛ"ﷺ" እንዲህ ሲሉ ሰማው ብሎ እንደተረከው፦ "እርሳቸውም እንዲህ አሉ፦ *"ከዚያም ወሕይ ወደ እኔ ተቋረጦ ነበር፥ ድንገት እየተጓዝኩኝ እያለ ከሰማይ ድምፅ ሰማሁኝ። እራሴን ቀና አድርጌ ወደ ሰማይ ስመለከት በሒራእ ዋሻ የጎበኘኝ መልአክ በሰማይ እና በምድር መካከል በመንበር ላይ ተቀምጦ አየሁት"*። عَنِ جَابِرُ بْنُ عَبْدِ اللَّهِ، أَنَّهُ سَمِعَ رَسُولَ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم يَقُولُ ‏ "‏ ثُمَّ فَتَرَ عَنِّي الْوَحْىُ، فَبَيْنَا أَنَا أَمْشِي سَمِعْتُ صَوْتًا مِنَ السَّمَاءِ، فَرَفَعْتُ بَصَرِي إِلَى السَّمَاءِ فَإِذَا الْمَلَكُ الَّذِي جَاءَنِي بِحِرَاءٍ قَاعِدٌ عَلَى كُرْسِيٍّ بَيْنَ السَّمَاءِ وَالأَرْضِ ‏"‌‏.‏

ለሁለተኛ ጊዜ ያዩት ደግሞ ሲድረቱል ሙንተሃ ላይ ነው፥ የሰባተኛው ሰማይ መጨረሻ ሊታለፍ የማይችል ድንበራዊ ዛፍ "ሲድረቱል ሙንተሃ" سِدْرَة الْمُنْتَهَى ነው፦
53፥14 *"በሲድረቱል ሙንተሃ አጠገብ አይቶታል"*። عِندَ سِدْرَةِ الْمُنتَهَىٰ
53፥15 *"እርሷ ዘንድ መኖሪያይቱ ጀናህ ያለች ስትኾን"*፡፡ عِندَهَا جَنَّةُ الْمَأْوَىٰ
ተፍሢሩል ኢብኑ ከሲር
53፥13-15 *"በሌላይቱም መውረድ ጊዜ በእርግጥ አይቶታል፣ በሲድረቱል ሙንተሃ አጠገብ አይቶታል፣ እርሷ ዘንድ መኖሪያይቱ ጀናህ ያለች ስትኾን" የአሏህ መልእክተኛም"ﷺ" አሉ፦ "ጂብሪልን አይቼዋለው፥ ስድስት መቶ ክንፍ አለው"*።  وَلَقَدْ رَءَاهُ نَزْلَةً أُخْرَى - عِندَ سِدْرَةِ الْمُنتَهَى - عِندَهَا جَنَّةُ الْمَأْوَى قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله «رَأَيْتُ جِبْرِيلَ وَلَهُ سِتُّمِائَةِ جَنَاحٍ »

ሲድረቱል ሙንተሃ ዘንድ ሙተቂን የሚኖቱባት ጀናህ አለች። "ሙንተሃ" مُنتَهَىٰ የሚለው ቃል "ነሃ" نَهَىٰ ማለትም "ከለከለ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "ክልክል" ማለት ነው፥ የሰባተኛው ሰማይ ድንበሩ የሢድራህ ዛፍ ናት። ይህቺን ዛፍ ማለፍ ክልክል ስለሆነ "ሲድረቱል ሙንተሃ" سِدْرَة الْمُنْتَهَى ትባላለች። የብርታት ባለቤት የኾነውን ጂብሪል በላይኛውና በግልጹ አድማስ በሲድረቱል ሙንተሃ ላይ ኾኖ ተደላድሎ እና ሲወርድ አዩት፦
53፥6 *"የዕውቀት ባለቤት የኾነው ተደላደለም"*፡፡ ذُو مِرَّةٍ فَاسْتَوَىٰ
53፥7 *"እርሱ በላይኛው አድማስ ኾኖ"*፡፡ وَهُوَ بِالْأُفُقِ الْأَعْلَىٰ
81፥23 *"በግልጹ አድማስም በእርግጥ አይቶታል"*፡፡ وَلَقَدْ رَآهُ بِالْأُفُقِ الْمُبِينِ

ይህ የብርታት ባለቤት ዐውደ-ንባቡ ላይ የአሏህ ባለሟል እና ታማኝ የተባለው መልአክ እንደሆነ እሙንና ቅቡል ነው፦
81፥20 *"የኃይል ባለቤት በዙፋኑ ባለቤት ዘንድ ባለሟል የኾነ ነው፡፡ ذِي قُوَّةٍ عِندَ ذِي الْعَرْشِ مَكِينٍ
81፥21 *"በዚያ ስፍራ ትእዛዙ ተሰሚ፤ ታማኝ የኾነ ነው"*፡፡ مُّطَاعٍ ثَمَّ أَمِينٍ

በተጨማሪም "በሌላይቱም መውረድ" የሚለው ኃይለ-ቃል ጂብሪል በተፈጥሮ ቅርፁ ሁለት ጊዜ መውረዱን ፍትውና ቁልጭ አድርጎ ያስረዳል፦
53፥13 *"በሌላይቱም መውረድ ጊዜ በእርግጥ አይቶታል"*፡፡ وَلَقَدْ رَآهُ نَزْلَةً أُخْرَىٰ
53፥8 *"ከዚያም ቀረበ፤ ወረደም"*፡፡ ثُمَّ دَنَا فَتَدَلَّىٰ
ኢማም ሙሥሊም መጽሐፍ 1, ሐዲስ 342
አቢ ሁራይራህ እንደተረከው፦ *"በሌላይቱም መውረድ ጊዜ በእርግጥ አይቶታል" ጂብሪልን አይተውታል"*። عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ، ‏{‏ وَلَقَدْ رَآهُ نَزْلَةً أُخْرَى‏}‏ قَالَ رَأَى جِبْرِيلَ ‏.‏

ነቢያችን"ﷺ" ሲድረቱል ሙንተሃ ላይ ከጌታው ታምራቶች ታላላቆች ከሆኑትን አንዱን ጂብሪልን በተፈጥሮ ቅርፁ ባለ ስድስት መቶ ክንፍ ያለው ሆኖ አይተውታል፦
53፥18 *"ከጌታው ታምራቶች ታላላቆቹን በእርግጥ አየ"*፡፡ لَقَدْ رَأَىٰ مِنْ آيَاتِ رَبِّهِ الْكُبْرَىٰ
ኢማም ሙሥሊም መጽሐፍ 1, ሐዲስ 332
ዐብደሏህ እንደተረከው፦ *"ከጌታው ታምራቶች ታላላቆቹን በእርግጥ አየ" ጂብሪልን በተፈጥሮ ቅርፁ ባለ ስድስት መቶ ክንፍ ያለው ሆኖ አይተውታል"*።  عَنْ عَبْدِ اللَّهِ، قَالَ ‏{‏ لَقَدْ رَأَى مِنْ آيَاتِ رَبِّهِ الْكُبْرَى‏}‏ قَالَ رَأَى جِبْرِيلَ فِي صُورَتِهِ لَهُ سِتُّمِائَةِ جَنَاحٍ ‏.‏

አሏህ በሰባተኛ ሰማይ ላይ በሢድር ከሚኖሩት አስሓቡል የሚን ያድርገን! አሚን።

ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
ከዋክብት

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ፥ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

37፥6 *"እኛ ቅርቢቱን ሰማይ በከዋክብት ጌጥ አጌጥናት"*፡፡ إِنَّا زَيَّنَّا السَّمَاءَ الدُّنْيَا بِزِينَةٍ الْكَوَاكِبِ

"ሚስባሕ" مِصْبَاح የሚለው ቃል "ሶበሐ" صَبَحَ ማለትም "በራ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "መብራት" ማለት ነው፥ "መሷቢሕ" مَصَابِيح የሚስባሕ ብዙ ቁጥር ሲሆን "መብራቶች" ማለት ነው። አምላካችን አሏህ ቅርቢቱን ሰማይ በመብራቶች አጊጧታል፦
41፥12 *"ቅርቢቱንም ሰማይ በመብራቶች አጌጥን፥ ጠበቅናትም"*፡፡ وَزَيَّنَّا السَّمَاءَ الدُّنْيَا بِمَصَابِيحَ وَحِفْظًا
67፥5 *"ቅርቢቱን ሰማይም በእርግጥ በመብራቶች አጌጥናት፥ ለሰይጣናትም መቀጥቀጫዎች አደረግናት"*፡፡ وَلَقَدْ زَيَّنَّا السَّمَاءَ الدُّنْيَا بِمَصَابِيحَ وَجَعَلْنَاهَا رُجُومًا لِّلشَّيَاطِينِ
50፥6 *"ወደ ሰማይም ከበላያቸው ስትኾን ለእርሷ ምንም ቀዳዳዎች የሌሏት ኾና እንዴት እንደ ገነባናት እና እንዳጌጥናት አልተመለከቱምን?* أَفَلَمْ يَنظُرُوا إِلَى السَّمَاءِ فَوْقَهُمْ كَيْفَ بَنَيْنَاهَا وَزَيَّنَّاهَا وَمَا لَهَا مِن فُرُوجٍ

ቅርቢቱ ሰማይ “ኦዞን”ozone" በተባለ የኦክስጅን ቅንብር ምንም ዓይነት ቀዳዳዎች ሳይኖር የተገነባች ናት፥ ያጌጠችው ደግሞ በመብራቶች ነው። እነዚህ መብራቶች ከዋክብት ናቸው፥ "ከውከብ" كَوْكَب ማለት "ኮከብ" ማለት ሲሆን "ከዋኪብ" كَوَاكِبِ ማለት ደግሞ "ከዋክብት" ማለት ነው። ኮከብ በግስበት ጓጉሎና ታምቆ የተያዘ እጅግ ግዙፍ፣ ደማቅ እና ሞቃት የሆነ ከፍተኛ ኮረንቲ ያዘለ የፕላዝማ ስብስብ ነው፥ አምላካችን አሏህ ቅርቢቱን ሰማይ መብራቶች በሆኑ ከዋክብት አጊጧታል፦
37፥6 *"እኛ ቅርቢቱን ሰማይ በከዋክብት ጌጥ አጌጥናት"*፡፡ إِنَّا زَيَّنَّا السَّمَاءَ الدُّنْيَا بِزِينَةٍ الْكَوَاكِبِ
37፥7 *"አመጸኛም ከሆነ ሰይጣን ሁሉ መጠበቅን ጠበቅናት"*፡፡ وَحِفْظًا مِّن كُلِّ شَيْطَانٍ مَّارِدٍ

ቅርቢቱ ሰማይ የላይኛው ክፍል ሸያጢን እንዳይደርሱ በጠባቂ መላእክት ትጠበቃለች፥ መጀመሪያይቱ ሰማይ ላይ ጠባቂዎች መላእክት አሉ። እነዚህ ብርቱ ጠባቂያን መላእክት ሸያጢን ወደ እዛ ከመጡ በተወርዋሪ ከዋክብት ይቀጠቅጧቸዋል፦
67፥5 *"ቅርቢቱን ሰማይም በእርግጥ በመብራቶች አጌጥናት፥ ለሰይጣናትም መቀጥቀጫዎች አደረግናት"*፡፡ وَلَقَدْ زَيَّنَّا السَّمَاءَ الدُّنْيَا بِمَصَابِيحَ وَجَعَلْنَاهَا رُجُومًا لِّلشَّيَاطِينِ

"አደረግናት" የሚለው ቅርቢቱን ሰማይ ሲሆን መቀጥቀጫዎች የተባሉት ደግሞ ተወርዋሪ ኮከቦች ናቸው፥ "ሩጁም" رُجُم ማለት እራሱ "ተወርዋሪ ኮከቦች"shooting stars" ማለት ነው። ጂኒዎች፦ "እኛም ሰማይን ለመድረስ ፈለግን፥ ብርቱ ጠባቂዎችን እና ችቦዎችንም ተሞልታ አገኘናት" ማለታቸውን አሏህ ነግሮናል፦
72፥8 *"እኛም ሰማይን ለመድረስ ፈለግን፥ ብርቱ ጠባቂዎችን እና ችቦዎችንም ተሞልታ አገኘናት"*፡፡ وَأَنَّا لَمَسْنَا السَّمَاءَ فَوَجَدْنَاهَا مُلِئَتْ حَرَسًا شَدِيدًا وَشُهُبًا

"ሺሃብ" شِهَاب ማለት "ችቦ" ማለት ሲሆን የሺሃብ ብዙ ቁጥር ደግሞ "ሹሁብ" شُهُب ሲሆን "ችቦዎች" ማለት ነው፥ እነዚህ አብሪ ችቦዎች ተወርዋሪ ከዋክብት ናቸው። መላእክት የሚነጋገሩት ለመስማት ከሸያጢን ሲመጡ ጠባቂዎቹ መላእክት በችቦዎች ይቀጠቅጧቸዋል፦
15፥17 *"ከተባረረ ሰይጣንም ሁሉ ጠብቀናታል"*፡፡ وَحَفِظْنَاهَا مِن كُلِّ شَيْطَانٍ رَّجِيمٍ
15፥18 *"ግን ወሬ መስማትን የሚሰርቅ ወዲየውኑ አብሪ ችቦ ይከተለዋል"*፡፡ إِلَّا مَنِ اسْتَرَقَ السَّمْعَ فَأَتْبَعَهُ شِهَابٌ مُّبِينٌ

አምላካችን አሏህ በቅርቢቱ ሰማይ ላይ ከዋክብትን ያረጋቸው በረጨት ነው፥ “ረጨት” ማለት የከዋክብት ስብስብ"galaxy" ሲሆን የእኛ ረጨት “ፍኖተ-ሃሊብ”Milky Way” ረጨት ይባላል። ይህ ረጨት ውፍረቱ 1000 የብርሃን ዓመት ይገመታል፥ ከአንዱ ጫፍ እስከሌላኛው ጫፍ ያለው ርቀት በዲያሜትር ሲለካ እንኳን እራሱ 100,000 የብርሃን ዓመት ይሆናል። የሚያጅበው በውስጡ ከ100 እስከ 400 ቢልዮን ከዋክብቶች እንደያዘ ይገመታል፥ ይህ አንዱ ኅብረ-ከዋክብት"constellation" ደግሞ "ቡርጅ" بُرْج ይባላል። በቅርቢቱ ሰማይ ብዙ ረጨቶች ስላሉ አምላካችን አሏህ "ቡሩጅ" بُرُوج በማለት ነግሮናል፦
85፥1 *"የቡርጆች ባለቤት በኾነችው ሰማይ እምላለሁ"*፡፡ وَالسَّمَاءِ ذَاتِ الْبُرُوجِ
15፥16 *"በሰማይም ላይ ቡርጆችን በእርግጥ አድርገናል፥ ለተመልካቾችም አጊጠናታል"*፡፡ وَلَقَدْ جَعَلْنَا فِي السَّمَاءِ بُرُوجًا وَزَيَّنَّاهَا لِلنَّاظِرِينَ
25፥61 *"ያ በሰማይ ቡሩጆችን ያደረገ እና በእርሷም ፀሐይን ሲራጅ እና ጨረቃን ሙኒር ያደረገ ጌታ ክብሩ በጣም ላቀ"*፡፡ تَبَارَكَ الَّذِي جَعَلَ فِي السَّمَاءِ بُرُوجًا وَجَعَلَ فِيهَا سِرَاجًا وَقَمَرًا مُّنِيرًا

በሥነ-ፈለክ ጥናት ሁለት ከዋክብት የያዘው መንትያ ኮከብ"Sirius" በቁርኣን "ሺዕራ" شِّعْرَىٰ ይባላል፥ አምላካችን አሏህ የሁለቱ መንትያ ኮከብ ጌታ እንደሆነ ይነግረናል፦
53፥49 *"እነሆ እርሱም የሺዕራ ጌታ ነው"*፡፡ وَأَنَّهُ هُوَ رَبُّ الشِّعْرَىٰ

በቁርኣን ሌላው "ከውከብ" كَوْكَب ለሚለው ቃል ተለዋዋጭ ቃል ሆኖ የገባው "ነጅም" نَّجْم ሲሆን የነጅም ብዙ ቁጥር ደግሞ "ኑጁም" نُّجُوم ነው፦
81፥2 *"ከዋክብትም በረገፉ ጊዜ"*። وَإِذَا النُّجُومُ انكَدَرَتْ
82፥2 *"ከዋክብትም በረገፉ ጊዜ"*። وَإِذَا الْكَوَاكِبُ انتَثَرَتْ

በፍርድ ቀን ከዋክብት ይረግፋሉ። በ 81፥2 ላይ "ከዋክብት" ለሚለው "ኑጁም" نُّجُوم ተብሎ ሲቀመጥ በ 82፥2 ላይ "ከዋክብት" ለሚለው ደግሞ "ከዋኪብ" كَوَاكِبِ ተብሎ ተቀምጧል፥ አንዱ ለሌላው ተለዋዋጭ”inter-change ነው። እንግዲህ ስለ ከዋክብት ከብዙ በጥቂት ይህንን ይመስላል፥ የአእምሮ ባለቤቶች ቆመው፣ ተቀምጠውም እና በጎኖቻቸው ተጋድመውም የአሏህን ፍጥረት የሚያስተነትኑ ናቸው። አምላካችን አሏህ በፈጠረው ፍጥረት የምናስተነትን የአእምሮ ባለቤት ያድርገን! አሚን።

ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
ገይብ

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ፥ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

2፥3 *ለእነዚያ በሩቁ ነገር የሚያምኑ፣ ሶላትንም ደንቡን ጠብቀው የሚሰግዱ እና ከሰጠናቸውም ሲሳይ የሚቸሩ ለኾኑት መሪ ነው"*። الَّذِينَ يُؤْمِنُونَ بِالْغَيْبِ وَيُقِيمُونَ الصَّلَاةَ وَمِمَّا رَزَقْنَاهُمْ يُنفِقُونَ

"ገይብ" غَيْب የሚለው ቃል "ጋበ" غَابَ ማለትም "ተደበቀ" "ተሸሸገ" "ራቀ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "ድብቅ" "ሽሽግ" "ሩቅ" ማለት ነው፦
34፥48 *«ጌታዬ እውነትን ያወርዳል፡፡ ሩቆችን ሁሉ ሁሉ ዐዋቂ ነው» በላቸው*፡፡ قُلْ إِنَّ رَبِّي يَقْذِفُ بِالْحَقِّ عَلَّامُ الْغُيُوبِ

"ሩቆች" ለሚለው የገባው ቃል "ጉዩብ" غُيُوب ሲሆን "ገይብ" غَيْب ለሚለው ብዙ ቁጥር ነው፥ ቁርኣን ላይ ብዙ ቦታ "የሩቅ ነገር" "የሩቅ ወሬ" "የሩቅ ሚሥጥር" የሚለው "ገይብ" غَيْب የሚለው ቃል ለመተካት ነው። የሰው ዐቅል ያልደረሰበት የሰማያት እና የምድር ገይብ አሏህ ዐዋቂ ነው፥ ከአሏህ በስተቀር በሰማያት እና በምድር ያለ ማንኛውም ፍጡር ገይብን አያውቅም፦
35፥38 *"አላህ የሰማያትን እና የምድርን የሩቅ ምሥጢር በእርግጥ ዐዋቂ ነው"፡፡ እርሱ በልቦች ውስጥ ያለን ሁሉ ዐዋቂ ነውና*፡፡ إِنَّ اللَّهَ عَالِمُ غَيْبِ السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضِ ۚ إِنَّهُ عَلِيمٌ بِذَاتِ الصُّدُورِ
27፥65 *«ከአሏህ በስተቀር በሰማያት እና በምድር ያለው ማንም ሩቅን ምሥጢርን አያውቅም፡፡ መቼ እንደሚቀሰቀሱም አያውቁም» በላቸው*፡፡ قُل لَّا يَعْلَمُ مَن فِي السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضِ الْغَيْبَ إِلَّا اللَّهُ ۚ وَمَا يَشْعُرُونَ أَيَّانَ يُبْعَثُونَ

ይህ አሏህ ብቻ የሚያውቀው ገይብ "ገይቡል ሙጥለቅ" غَيْب ٱلْمُطْلَق ይባላል፥ አምላካችን አሏህ ወደ መረጠው ነቢይ የሚያወርደው ገይብ ደግሞ "ገይቡ አን-ኒሥቢይ" غَيْب ٱلْنِسْبِي ይባላል። አምላካችን አሏህ ይህንን ገይቡ አን-ኒሥቢይ ከመልእክተኛ ለወደደው ቢኾን እንጂ ለማንም አያሳውቅም፦
72፥26 *«እርሱ ”የሩቅ ምሥጢር” ዐዋቂ ነው፡፡ በሚሥጢሩም ላይ አንድንም አያሳውቅም፡፡»* عَٰلِمُ ٱلْغَيْبِ فَلَا يُظْهِرُ عَلَىٰ غَيْبِهِۦٓ أَحَدًا
72፥27 *ከመልእክተኛ ለወደደው ቢኾን እንጂ*፡፡ إِلَّا مَنِ ٱرْتَضَىٰ مِن رَّسُولٍۢ

አምላካችን አሏህ ወደ ነቢይ የሚያወርደው ገይቡ አን-ኒሥቢይ በሦስት ይከፈላል፥ እርሱም፦ ገይቡል ማዲ፣ ገይቡል ሙዷሪዕ እና ገይቡል ሙሥተቅበል ነው። ይህንን ነጥብ በነጥብ እንመልከት፦

ነጥብ አንድ
"ገይቡል ማዲ"
"ገይቡል ማዲ" غَيْب الْمَاضِي ማለት "ያለፈ ሩቅ ነገር" ማለት ነው፥ ድርጊቱ ከዚህ በፊት አላፊ የሆነ ክስተት ነው። አምላካችን አሏህ ከነቢያችን"ﷺ" መኖር በፊት የተከሰተውን የሩቅ ነገር "ነቁሱ ዐለይከ" نَقُصُّ عَلَيْكَ ማለትም “እንተርክልሃለን” በማለት ይናገራል፦
20፥99 *”እንደዚሁ በእርግጥ ካለፉት ወሬዎች በአንተ ላይ እንተርካለን”*፡፡ كَذَٰلِكَ نَقُصُّ عَلَيْكَ مِنْ أَنبَاءِ مَا قَدْ سَبَقَ

"ነቢይ" نَبِيّ የሚለው ቃል “ነበአ” نَبَّأَ ማለትም "አወራ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን “አውሪ” ማለት ነው፥ ከአሏህ የሚመጣለት "ወሬ" ደግሞ "ነበእ" نَبَأ ይባላል። ይህም ወሬ "ገይብ" ነው፥ አምላካችን አሏህ ወደ ነቢያችን"ﷺ" ያወረደው ወሬ ገይብ ነው፦
3፥44 *"ይህ ወደ አንተ የምናወርደው የኾነ ከሩቅ ወሬዎች ነው"*፡፡ ذَٰلِكَ مِنْ أَنبَاءِ الْغَيْبِ نُوحِيهِ إِلَيْكَ
12፥102 *"ይህ ወደ አንተ የምናወርደው የኾነ ከሩቅ ወሬዎች ነው"*፡፡ ذَٰلِكَ مِنْ أَنبَاءِ الْغَيْبِ نُوحِيهِ إِلَيْكَ

"ወሬዎች" ለሚለው የገባው ቃል "አንባእ" أَنبَاء ሲሆን "ነበእ" نَبَأ ለሚለው ብዙ ቁጥር ነው፥ "የምናወርደው" ለሚለው የገባው ቃል "ኑሒ" نُوحِي ሲሆን የሚወርደው የሩቅ ወሬ "ወሕይ" وَحْى መሆኑን አመላካች ነው። ከእርሳቸው በፊት ያለው ክስተት ሲከሰት በቦታው የሉም፥ ነገር ግን በጊዜና በቦታ ዕውቀቱ የማይገደበው አላህ “አስታውስ” በማለት ተርኮላቸዋል፦
38፥71 ጌታህ *«ለመላእክት እኔ ሰውን ከጭቃ ፈጣሪ ነኝ ባለ ጊዜ» አስታውስ*፡፡ إِذْ قَالَ رَبُّكَ لِلْمَلَائِكَةِ إِنِّي خَالِقٌ بَشَرًا مِّن طِينٍ
ነጥብ ሁለት
“ገይቡል ሙዷሪዕ”
“ገይቡል ሙዷሪዕ” غَيْب ٱلْمُضَارِع ማለት “የአሁን ሩቅ ነገር” ማለት ነው፥ ቁርኣን ሲወርድ ከሕዋስ ባሻገር እየተፈጸመ ያለ ክስተት ነው። ለምሳሌ ይህንን አንቀጽ እንመልከት፦
66፥3 *”ነቢዩ ከሚስቶቹ ወደ አንዷ ወሬን በመሠጠረ ጊዜ አስታውስ፡፡ እርሱንም በነገረች እና አላህ እርሱን ማውራትዋን ባሳወቀው ጊዜ ከፊሉን አስታወቀ፤ ከፊሉንም ተወ፡፡ በእርሱም ባወራት ጊዜ «ይህን ማን ነገረህ?» አለች፡፡ «ዐዋቂው ፥ውስጠ ዐዋቂው ነገረኝ» አላት”*። وَإِذْ أَسَرَّ ٱلنَّبِىُّ إِلَىٰ بَعْضِ أَزْوَٰجِهِۦ حَدِيثًۭا فَلَمَّا نَبَّأَتْ بِهِۦ وَأَظْهَرَهُ ٱللَّهُ عَلَيْهِ عَرَّفَ بَعْضَهُۥ وَأَعْرَضَ عَنۢ بَعْضٍۢ ۖ فَلَمَّا نَبَّأَهَا بِهِۦ قَالَتْ مَنْ أَنۢبَأَكَ هَٰذَا ۖ قَالَ نَبَّأَنِىَ ٱلْعَلِيمُ ٱلْخَبِيرُ

"ነገረክ" ለሚለው የገባው ቃል "አንበአ-ከ" أَنۢبَأَكَ
መሆኑ እና "ነገረኝ" ለሚለው የገባው ቃል "ነበአ-ኒየ" نَبَّأَنِيَ መሆኑ አንባቢ ልብ ይለዋል። ሐፍሷህ”ረ.ዐ.”፦ "ይህን ማን ነገረህ? ስትላቸው ነቢያችንም”ﷺ”፦ "ዐዋቂው፥ ውስጠ ዐዋቂው ነገረኝ" ማለታቸው በራሱ "ነቢይ" ማለት "ሁሉን ዐዋቂው፥ ውስጠ ዐዋቂው አሏህ የሚያናግረው እና የሚነግረው" ማለት መሆኑን ያሳያል። ነቢያችን"ﷺ" ከሕዋስ ባሻገር በሐፍሷህ እና በዓኢሻህ መካከል የነበረውን ገይብ ያወቁት ሁሉን ዐዋቂውና ውስጠ ዐዋቂው አሏህ ነግሯቸው ነው።

ነጥብ ሦስት
“ገይቡል ሙሥተቅበል”
“ገይቡል ሙሥተቅበል” غَيْب ٱلْمُسْتَقْبَل ማለት “የወደፊት ሩቅ ነገር” ማለት ሲሆን መጪው ክስተት ነው፥ ይህም ድርጊቱ ገና ያልተፈጸመ ወደፊት የሚከሰት ነው። አምላካችን አሏህ ወደፊት በትንሳኤ ቀን ስለሚኖረው ቅጣት "በላቸው" በማለት ይናገራል፦
22፥72 *«ከዚህ ይልቅ የከፋን ነገር ልንገራችሁን?» በላቸው”፡፡ «እርሷም እሳት ናት፡፡ አላህ ለእነዚያ ለካዱት ሰዎች ቀጥሯታል፥ ምን ትከፋም መመለሻ»*። قُلْ أَفَأُنَبِّئُكُم بِشَرٍّ مِّن ذَٰلِكُمُ ۗ النَّارُ وَعَدَهَا اللَّهُ الَّذِينَ كَفَرُوا ۖ وَبِئْسَ الْمَصِيرُ

“ልንገራችሁ” ለሚለው ቃል የገባው “ነበኡኩም” نَبِّئُكُم ሲሆን “ነበአ” نَبَّأَ ከሚለው ሥርወ-ቃል የመጣ ነው። ነቢያችን”ﷺ” ከተላኩት ተልእኮ አንዱ የእሳት ቅጣት እንዳለ ለማስጠንቀቅ እና አሏህን በገይብ እንድንፈራው ነው፦
36፥11 *"የምታስጠነቅቀው ግሳጼን የተከተለን እና አር-ረሕማንን በሩቅ የፈራን ሰው ብቻ ነው፥ በምሕረትና በመልካም ምንዳም አብስረው"*፡፡ إِنَّمَا تُنذِرُ مَنِ اتَّبَعَ الذِّكْرَ وَخَشِيَ الرَّحْمَـٰنَ بِالْغَيْبِ ۖ فَبَشِّرْهُ بِمَغْفِرَةٍ وَأَجْرٍ كَرِيمٍ

እንግዲህ ስለ ገይብ ከብዙ በጥቂቱ ካየን ዘንዳ ቁርኣን ከወረደበት ግብና አላማ አንዱ ለእነዚያ በገይብ የሚያምኑ ለኾኑት መሪ ለመሆን ነው፥ አሏህ ለባሮቹ በገይብ ሆነው ሳሉ ተስፋ ቃል የገባላቸውን የመኖሪያን ጀናት ይገባሉ፦
2፥3 *"ለእነዚያ በሩቁ ነገር የሚያምኑ፣ ሶላትንም ደንቡን ጠብቀው የሚሰግዱ እና ከሰጠናቸውም ሲሳይ የሚቸሩ ለኾኑት መሪ ነው"*። الَّذِينَ يُؤْمِنُونَ بِالْغَيْبِ وَيُقِيمُونَ الصَّلَاةَ وَمِمَّا رَزَقْنَاهُمْ يُنفِقُونَ
19፥61 *"የመኖሪያን ገነቶች ያችን አልረሕማን ለባሮቹ "በሩቅ" ኾነው ሳሉ ተስፋ ቃል የገባላቸውን ይገባሉ፡፡ እርሱ ተስፋው ተፈጻሚ ነውና"*። جَنَّاتِ عَدْنٍ الَّتِي وَعَدَ الرَّحْمَـٰنُ عِبَادَهُ بِالْغَيْبِ ۚ إِنَّهُ كَانَ وَعْدُهُ مَأْتِيًّا

አምላካችን አሏህ በገይብ ከሚያምኑት ባሮቹ አድርጎ በጀናህ ያስገባን! አሚን።

ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
አሏህ ከዐርሽ በላይ ነው!

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ፥ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

20፥5 *እርሱ አር-ረሕማን ከዐርሹ ላይ "የተደላደለ" ነው*። ٱلرَّحْمَٰنُ عَلَى ٱلْعَرْشِ ٱسْتَوَىٰ

አምላካችን አሏህ እራሱን በቁርአን ውስጥ ከወሰፈበት ወስፍ መካከል እርሱ ከዐርሽ በላይ መሆኑን ነው፦
20፥5 *እርሱ አር-ረሕማን ከዐርሹ ላይ "የተደላደለ" ነው*። ٱلرَّحْمَٰنُ عَلَى ٱلْعَرْشِ ٱسْتَوَىٰ

እዚህ አንቀጽ ላይ "የተደላደለ" ለሚለው ቃል የገባው “ኢሥተዋ” اسْتَوَىٰ ሲሆን የቋንቋ ሊሒቃን፦ "ኢሥተዋ" የሚለው ቃል በተለየየ ዓይነት ትርጉም ይመጣል" ይላሉ፤ ይህ ትርጉም ለሁለት ከፍለው ያዩታል፥ አንዱ “ሙቀየድ” ሲሆን ሌላው “ሙጥለቅ” ነው።
"ሙጥለቅ” مُطْلَق ማለትም “ያልተገደበ”un-restricted” ሆኖ ሲመጣ ነው፥ ለምሳሌ “ኢሥተዋ” ከሚለው ቃል በፊትና በኃላ ምንም መስተዋድድ ሳይመጣ ኢስተዋእ ሳይገደብ ሲቀር “በሰለ” “ተስተካከለ” “ሞላ” በሚል ቃል ይመጣል፦
28:14 ብርታቱንም በደረሰ እና *በተስተካከለ* ጊዜ ጥበብንና ዕውቀትን ሰጠነው፡፡ እንዲሁም መልካም ሠሪዎችን እንመነዳለን፡፡ وَلَمَّا بَلَغَ أَشُدَّهُۥ وَٱسْتَوَىٰٓ ءَاتَيْنَٰهُ حُكْمًۭا وَعِلْمًۭا ۚ وَكَذَٰلِكَ نَجْزِى ٱلْمُحْسِنِينَ

ሁለተኛው ደግሞ “ሙቀየድ” مُقَيَّد ማለትም “የተገደበ”restricted” ማለት ሲሆን “ኢሥተዋ” ከሚለው ቃል በፊትና በኃላ መስተዋድድ ሲመጣ ነው፥ ለምሳሌ "ኢሥተዋ" ከሚለው ቃል በኃላ “ኢላ” إِلَى ማለትም “ወደ” የሚለው መስተዋድድ ከመጣ “አሰበ” በሚል ይመጣል፦
2፥29 እርሱ ያ በምድር ያለውን ሁሉ ለእናንተ የፈጠረ ነው፡፡ ከዚያም ወደ ሰማይ *አሰበ*፤ ሰባት ሰማያትም አደረጋቸው፡፡ እርሱም በነገሩ ሁሉ ዐዋቂ ነው። هُوَ ٱلَّذِى خَلَقَ لَكُم مَّا فِى ٱلْأَرْضِ جَمِيعًۭا ثُمَّ ٱسْتَوَىٰٓ إِلَى ٱلسَّمَآءِ فَسَوَّىٰهُنَّ سَبْعَ سَمَٰوَٰتٍۢ ۚ وَهُوَ بِكُلِّ شَىْءٍ عَلِيمٌۭ

ነገር ግን ሱረቱ ጣሀ 20፥5 ላይ አላህ ከዐርሽ በላይ ለመሆኑ የዋለው “ኢሥተዋ” የሚለው ቃል ላይ “ዐላ” عَلَى በሚል መስተዋድድ መምጣቱ “ተዓላ” تَعَالَى ማለትም “ከፍ አለ” የሚል ትርጉም ይኖረዋል። የነቢያችን”ﷺ” የቅርብ ዘመድ እና ሶሐቢይ የሆነው ኢብኑ ዐባሥ ሲሆን የእርሱ ተማሪ ሙጃሂድ "ኢሥተዋ" የሚለውን “ዓላ” عَلاَ ማለትም "በላይ" በማለት ፈሥሮታል፦
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 97, ሐዲስ 51 ኪታቡል ተውሒድ ባብ 22
ሙጃሂድም አለ፦ *”ኢሥተዋ” ማለት “ዓላ ዐለል ዐርሽ” ማለት ነው”*። وَقَالَ مُجَاهِدٌ: {اسْتَوَى} عَلاَ عَلَى الْعَرْشِ

አምላካችን አላህም እራሱን በሶስተኛ መደብ “አል-አዕላ” الْأَعْلَى መሆኑን ተናግሯል፦
87፥1 *ከሁሉ በላይ የሆነዉን* ጌታህን ስም አሞግሥ። سَبِّحِ ٱسْمَ رَبِّكَ ٱلْأَعْلَى

ይህም የሚያሳየው አላህ ከፍጥረት ሁሉ በላይ መሆኑን ነው፥ አላህ በፈጠረው ፍጥረታት ላይ ሁሉ የበላይ ታላቅ ስለሆነ እራሱን “አል-ዓሊይ” العَلِيّ ብሏል፦
42፥4 በሰማያትና በምድር ያለው ሁሉ የእርሱ ነው፥ *እርሱም የሁሉ በላይ ታላቅ ነው”* لَهُ مَا فِي السَّمَاوَاتِ وَمَا فِي الْأَرْضِ ۖ وَهُوَ الْعَلِيُّ الْعَظِيمُ

አላህ ከትልቁ ፍጥረት ከዐርሽ በላይ እንዴት እንደሚኖር ከይፊያው አልተገለጸም፤ “ከይፊያህ” كَيْفِيَّة ማለትም “እንዴትነት”howness ማለት ነው፦
አል-ኢሥቲዝካር መጽሐፍ 2, ቁጥር 529
ዐብደላህ ኢብኑ ናፊዕ እንደዘገበው፦ *"ማሊክ አላህ ይርሓመውና ስለ የአላህ አዘ ወጀል ንግግር፦ "እርሱ አር-ረሕማን ከዐርሹ ላይ የተደላደለ ነው" ብሎ ጠየቀ። አንድም ሰው፦ "እንዴት ነው የተደላደለው? አለ። ማሊክም፦ "መደላደሉ የታወቀ ነው፥ "እንዴትነቱ" ግን ዐይታወቅም" እንዴትነቱን መጠየቅ ግን ቢድዓ ነው። አንተም በዚህ እኩይ ጥያቄ መለከፍህን አያለው" አለ*። عَنْ عَبْدِ اللَّهِ بْنِ نَافِعٍ قَالَ سُئِلَ مَالِكٌ رحمه الله عَنْ قَوْلِ اللَّهِ عَزَّ وَجَلَّ الرَّحْمَنُ عَلَى الْعَرْشِ اسْتَوَى قَالَ كَيْفَ اسْتَوَى فَقَالَ اسْتِوَاؤُهُ مَعْلُومٌ وَكَيْفِيَّتُهُ مَجْهُولَةٌ وَسُؤَالُكُ عَنْ هَذَا بِدْعَةٌ وَأَرَاكَ رَجُلَ سُوءٍ
ታላቁ ሙፈሢር ኢሥማዒል አብኑ ከሲር "ኢሥተዋ" የሚለውን እውነታውን ያለ እንዴትነት፣ ያለ ማመሳሰል፣ ያለ ትርጉም አልባ እንደሚቀበሉ ተናግረዋል፦
አት-ተፍሢሩል አብኑ ከሲር ሱሩቱል አዕራፍ 7፥54
*አላህ እንዳለው፦ "እርሱ ከዐርሽ በላይ ነው" በሚለው ትርጉም ላይ ሰዎች ብዙ የግጭት አመለካከት አላቸው፥ ምንም ይሁን እኛ ከቀደምት መዝሃብ ከሠለፉ-ሷሊሑን ከማሊክ፣ ከአል-አውዛዒይ፣ ከአስ-ሰውሪይ፣ ከአል-ለይስ ኢብኑ ሠዒድ፣ ከአሽ-ሻፊሪይ፣ ከአሕመድ፣ ከኢሥሐቅ ኢብኑ ራህወያህ እና ከተቀሩት የኢሥላም የጥንትና የአሁን ምሁራን ተከትለን እንወስዳለን። "ኢሥተዋ" የሚለውን ቀጥተኛ ትርጉም እውነታውን ያለ እንዴትነት፣ ያለ ማመሳሰል፣ ያለ ትርጉም አልባ እንቀበላለን። እንዲሁ ለእነዚያ አላህን ከፍጥረቱ ጋር እኩል ለሚያደርጉት ውድቅ በማድረግ እና ለአላህ ምንንም ሳናመሳስል እናምናለን። "የሚመስለው ምንም ነገር የለም፡፡ እርሱም ሰሚው ተመልካቹ ነው" 42፥11 ። ከኢማሞች ለተጠቃሽ ያክል የኢማም ቡኻሪይ አስተማሪ ኑዐይም ኢብኑ ሐመዱል ኹዛዒይ፦ "ማንም አላህን ከፍጥረቱ ያመሳሰለ ከፍሯል፥ ማንም አላህ ስለራሱ የወሰፈውን ባሕርይ ያስተባበለ ከፍሯል" ብሏል*። وأما قوله تعالى : ( ثم استوى على العرش ) فللناس في هذا المقام مقالات كثيرة جدا ، ليس هذا موضع بسطها ، وإنما يسلك في هذا المقام مذهب السلف الصالح : مالك ، والأوزاعي ، والثوري ، والليث بن سعد ، والشافعي ، وأحمد بن حنبل ، وإسحاق بن راهويه وغيرهم ، من أئمة المسلمين قديما وحديثا ، وهو إمرارها كما جاءت من غير تكييف ولا تشبيه ولا تعطيل . والظاهر المتبادر إلى أذهان المشبهين منفي عن الله ، فإن الله لا يشبهه شيء من خلقه ، و ( ليس كمثله شيء وهو السميع البصير ) [ الشورى : 11 ] بل الأمر كما قال الأئمة - منهم نعيم بن حماد الخزاعي شيخ البخاري - : " من شبه الله بخلقه فقد كفر ، ومن جحد ما وصف الله به نفسه فقد كفر

አምላካችን አሏህ የታላቁ ዐርሽ ጌታ ነው፦
27፥26 አላህ ከእርሱ ሌላ አምላክ የለም፡፡ *የታላቁ ዐርሽ ጌታ ነው*፡፡ اللَّهُ لَا إِلَـٰهَ إِلَّا هُوَ رَبُّ الْعَرْشِ الْعَظِيمِ
9፥129 ቢያፈገፍጉም አላህ በቂዬ ነው፡፡ ከእርሱ ሌላ አምላክ የለም፡፡ በእርሱ ላይ ተጠጋሁ እርሱም *"የታላቁ ዐርሽ" ጌታ ነው* በላቸው፡፡ فَإِن تَوَلَّوْا فَقُلْ حَسْبِيَ اللَّهُ لَا إِلَـٰهَ إِلَّا هُوَ ۖ عَلَيْهِ تَوَكَّلْتُ ۖ وَهُوَ رَبُّ الْعَرْشِ الْعَظِيمِ

"ዐዚም" عَظِيم ማለት "ታላቅ" ወይም "ትልቅ" ማለት ነው። ትልቁ ፍጥረት ዐርሽ ነው። ታላቁ ሙፈሢር ኢብኑ ከሲር "የታላቁ ዐርሽ ጌታ ነው" የሚለውን አንቀጽ ሲያብራሩ እንዲህ ይላሉ፦
አት-ተፍሢሩል ኢብኑ ከሲር 9፥128
*"የታላቁ ዐርሽ ጌታ ነው" እርሱ ንጉሥ፣ የሁሉ ነገር ፈጣሪ እና የታላቁ ዐርሽ ጌታ ነው። ያ እርሱ(ዐርሽ) የፍጥረታት ጣሪያ ነው። ሰማያት፣ ምድር፣ በውስጣቸው ያለ፣ በመካከላቸውም ያለ ሁሉም ፍጥረት ከዐርሽ ሥር ለአላህ ተዓላ ተገዢ ነው። ዕውቀቱ ሁሉን ነገር ያካበበ ነው፣ እርሱ በሁሉ ነገር ላይ መመኪያ ነው"*። ( وهو رب العرش العظيم ) أي : هو مالك كل شيء وخالقه ، لأنه رب العرش العظيم ، الذي هو ، سقف المخلوقات وجميع الخلائق من السماوات والأرضين وما فيهما وما بينهما تحت العرش مقهورون بقدرة الله تعالى ، وعلمه محيط بكل شيء ، وقدره نافذ في كل شيء ، وهو على كل شيء وكيل

እዚህ ተፍሢር ላይ"ሠቅፍ" سَقْف ማለት "መጠናቀቂያ" "ማብቂያ" "ጣሪያ" ማለት ነው፥ "ኸልቅ" خَلْق ማለት ደግሞ "ፍጥረት" ማለት ሲሆን የፍጥረት መጠናቀቂያ፣ ማብቂያ፣ ጣሪያው ዐርሽ ነው። "መኽሉቅ" مَخْلُوق‎ ማለት "ፍጡር" ማለት ሲሆን ዘመካን ነው፥ "ዘመካን" زَمَكَان ማለት የዘማንና የመካን ቃላት ውቅር ነው። "ዘማን" زَمَان ማለት "ጊዜ"time" ማለት ነው፥ "መካን" مَكَان ደግሞ "ቦታ"space" ማለት ነው። አላህ ደግሞ ጊዜና ቦታ ከሚጠናቀቅነት ከዐርሽ በላይ ሆኖ ሁሉን ነገር ያካበበ "ኻሊቅ" خَالِق‎ ማለትም "ፈጣሪ" ነው። እንግዲህ እኛም ከላይ ያሉትን የቀደምት ሠለፍ አረዳድ ያለ ተክዪፍ፣ ያለ ተሽቢህ፣ ያለ ተሕሪፍ፣ ያለ ተዕጢል "አላህ ከዙፋኑ በላይ ነው" ብለን እናምናለን።
1. “ተክዪፍ” تَكْيِيف ማለት "እንዴት ብሎ መፈላሰፍ" ነው፣
2. "ተሽቢህ" تَشبِيه‎ ማለት "ከፍጡር ጋር ማመሳሰል" ነው፣
3. "ተሕሪፍ" تَحْرِيف ማለት "ትርጉሙን ማዛባት" ነው፣
4. “ተዕጢል” تَعْطِيل ማለት "ትርጉም የለሽ ማድረግ" ነው።
ስለዚህ አላህ በቅዱስ ቃሉ በወሰፈው መሠረት፦
ሁኔታው እንዲህ ነው ሳንል
ከፍጡራን ጋር ሳናመሳስል
ትርጉሙን ምንም ሳንቀይር
ትርጉም አልባ ሳናደርግ
"አላህ ከዐርሽ በላይ ነው" ብለን እናምናለን።

ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
አሏህ ከሰማይ በላይ ነው!

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ፥ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።

67፥16 *"በሰማይ ላይ ያለ በእናንተ ምድርን ቢደረባባችሁ ወዲያውም እርሷ የምታረገርግ ብትኾን ትተማመናላችሁን? አትፈሩምን?* أَأَمِنتُم مَّن فِي السَّمَاءِ أَن يَخْسِفَ بِكُمُ الْأَرْضَ فَإِذَا هِيَ تَمُورُ

“ሠማእ” سَّمَاء የሚለው ቃል “ሠማ” سَمَا ማለትም “ከፍ አለ” ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን “ከፍታ” ወይም “አርያም” ነው፦
88፥18 *“ወደ ሰማይም እንዴት ከፍ እንደ ተደረገች”*። وَإِلَى السَّمَاءِ كَيْفَ رُفِعَتْ

ቁርኣን ላይ “ሠማእ” سَّمَاء የሚለው ቃል "ሠማዋት” سَمَاوَات የሚባሉትን ሰባት ሰማያት ለማመልከት ይመጣል። የሰማያት የመጨረሻው ሰማይ ሰባተኛው ሰማይ ነው፥ ያ ሰማይ መጠናቀቂያው ዐርሽ ነው፥ አምላካችን አሏህ ከአርያም በላይ ነው፦
ጃምዒ አት-ቲርሚዚይ መጽሐፍ 47, ሐዲስ 3519
አነሥ እንደተረከው፦ "ስለ ዘይነብ ቢንት ጀሕሽ፦ "ዘይድም ከእርሷ ጉዳይን በፈጸመ ጊዜ እርሷን አጋባንህ" የሚለው አንቀጽ በወረደ ጊዜ እርሷ በነቢዩ”ﷺ” ባለቤቶች ፊት በኩራት፦ *“እናንተን ቤተሰቦቻችሁ ዳርዋችሁ፥ እኔን ግን ከሰባት ሰማያት በላይ ያለው አላህ ዳረኝ” እያለች ትናገር ነበር"*። عَنْ أَنَسٍ، قَالَ نَزَلَتْ هَذِهِ الآيَةُ فِي زَيْنَبَ بِنْتِ جَحْشٍ ‏:‏ ‏(‏فلَمَّا قَضَى زَيْدٌ مِنْهَا وَطَرًا زَوَّجْنَاكَهَا ‏)‏ قَالَ فَكَانَتْ تَفْتَخِرُ عَلَى أَزْوَاجِ النَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم تَقُولُ زَوَّجَكُنَّ أَهْلُكُنَّ وَزَوَّجَنِي اللَّهُ مِنْ فَوْقِ سَبْعِ سَمَوَاتٍ ‏

እዚህ ሐዲስ ላይ "በላይ" ለሚለው የገባው ቃል "ፈውቅ" فَوْق ነው፥ ነቢያችን"ﷺ" አንዲት እንስትን፦ "አሏህ የት ነው ያለው? ብለው ጠይቀዋት "ከሰማይ በላይ" ብላ ስትመልስ "አማኝ" ናት ብለዋል፦
ሡነን አቢ ዳውድ መጽሐፍ 22, ሐዲስ 41
ሙዓዊያህ ኢብኑ አል-ሐከሙ አሥ-ሡለይሚይ እንደተረከው፦ "የአሏህ መልእክተኛ ሆይ! ለእኔ በጥፊ የመታኃት ሴት አገልጋይ አለችኝ" አልኩኝ፥ ይህ ጉዳይ የአሏህን መልእክተኛን"ﷺ" አሳዘነ። እኔም፦ "ነጻ ማውጣት የለብኝምን? አልኩኝ፥ እርሳቸው፦ "ወደ እኔ አምጣት" አሉት። እኔም አመጣኃት፥ እርሳቸውም፦ *"አሏህ የት ነው ያለው? ብለው ጠየቋት። እርሷም፦ "ከሰማይ በላይ" አለች፥ እርሳቸውም፦ "እኔ ማን ነኝ? ብለው ጠየቋት። እርሷም፦ "አንተ የአሏህ መልእክተኛ ነህ" አለች፥ ነጻ አውጣት! እርሷ አማኝ ነች" አሉ"*። عَنْ مُعَاوِيَةَ بْنِ الْحَكَمِ السُّلَمِيِّ، قَالَ قُلْتُ ‏:‏ يَا رَسُولَ اللَّهِ جَارِيَةٌ لِي صَكَكْتُهَا صَكَّةً ‏.‏ فَعَظَّمَ ذَلِكَ عَلَىَّ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم فَقُلْتُ أَفَلاَ أُعْتِقُهَا قَالَ ‏:‏ ‏"‏ ائْتِنِي بِهَا ‏"‏ ‏.‏ قَالَ ‏:‏ فَجِئْتُ بِهَا قَالَ ‏:‏ ‏"‏ أَيْنَ اللَّهُ ‏"‏ ‏.‏ قَالَتْ ‏:‏ فِي السَّمَاءِ ‏.‏ قَالَ ‏:‏ ‏"‏ مَنْ أَنَا ‏"‏ ‏.‏ قَالَتْ ‏:‏ أَنْتَ رَسُولُ اللَّهِ ‏.‏ قَالَ ‏:‏ ‏"‏ أَعْتِقْهَا فَإِنَّهَا مُؤْمِنَةٌ ‏"‏
እዚህ ሐዲስ ላይ "ላይ" ወይም "በላይ" ለሚለው የገባው ቃል “ፊ” فِي ሲሆን “ፊ” فِي ሁል ጊዜ “ውስጥ” ማለት ብቻ ሳይሆን እንደየ ዐውዱ የተለያየ ትርጉም ይዞ ይመጣል፥ ለምሳሌ “ቢ” بـِ ማለትም “በ” በሚል መጥቷል፦
2፥154 *"በ-አላህ መንገድ የሚገደሉትን ሰዎችም «ሙታን ናቸው» አትበሉ፡፡ በእውነቱ ሕያዋን ናቸው፤ ግን አታውቁም"*፡፡ وَلَا تَقُولُوا لِمَن يُقْتَلُ فِي سَبِيلِ اللَّهِ أَمْوَاتٌ ۚ بَلْ أَحْيَاءٌ وَلَـٰكِن لَّا تَشْعُرُونَ

"ፊ" ሠቢሊሏህ" فِي سَبِيلِ اللَّه የሚለው ኃይለ-ቃል ይሰመርበት! “ፊ” فِي ሌላ ቦታ "ዐን" عَنْ ማለትም “ስለ”about" በሚል መጥቷል፦
19፥34 ይህ የመርየም ልጅ ዒሣ ነው፡፡ ያ "ስለ" እርሱ የሚከራከሩበት እውነተኛ ቃል ነው፡፡ ذَٰلِكَ عِيسَى ابْنُ مَرْيَمَ ۚ قَوْلَ الْحَقِّ الَّذِي فِيهِ يَمْتَرُونَ

"ፊ-ሂ" فِيهِ የሚለው ኃይለ-ቃል አሁንም ይሰመርበት! “ፊ” فِي ሌላ ቦታ “ፈውቅ” فَوْق ማለትም “በላይ” በሚል መጥቷል፥ ለምሳሌ ፈርዐውን፦ "በዘምባባም ግንዶች ላይ እሰቅላችኋለሁ" ብሏል፦
20፥71 *"በዘምባባም ግንዶች ላይ እሰቅላችኋለሁ"*፡፡ وَلَأُصَلِّبَنَّكُمْ فِي جُذُوعِ النَّخْلِ

እዚህ አንቀጽ ላይ "ላይ" ለሚለው የገባው ቃል "ፊ" فِي ሲሆን “ፈውቅ” فَوْق ለማለት ነው፥ ስለዚህ "ፊሥ ሠማእ" فِي السَّمَاء ማለት "በሰማይ ውስጥ" ማለት ሳይሆን "ከሰማይ በላይ" ወይም "በሰማይ ላይ" ማለት ነው፦
67፥16 *"በሰማይ ላይ ያለ በእናንተ ምድርን ቢደረባባችሁ ወዲያውም እርሷ የምታረገርግ ብትኾን ትተማመናላችሁን? አትፈሩምን?* أَأَمِنتُم مَّن فِي السَّمَاءِ أَن يَخْسِفَ بِكُمُ الْأَرْضَ فَإِذَا هِيَ تَمُورُ
67፥17 *"ወይም በሰማይ ላይ ያለ በእናንተ ላይ ጠጠርን ያዘለች ነፋስን ቢልክባችሁ ትተማመናላችሁን? አትፈሩምን? ማስጠንቀቄም እንዴት እንደኾነ ወደፊት ታውቃላችሁ"*፡፡ أَمْ أَمِنتُم مَّن فِي السَّمَاءِ أَن يُرْسِلَ عَلَيْكُمْ حَاصِبًا ۖ فَسَتَعْلَمُونَ كَيْفَ نَذِيرِ

እነዚህ ሁለት አናቅጽ ላይ "መን" مَّن የሚለው ኢሥሙል መውሱል "ማንነት" ያለው ኑባሬን ያሳያል፥ ይህም ከሰማይ በላይ ያለው ማንነት ምድርን መገለባበጥ እና ጠጠርን ያዘለች ነፋስን መላክ የሚችል ማንነት ነው። በሉጥ ጊዜ ምድርን የገባበጠ እና ጠጠርን ያዘለች ነፋስን የላከ እራሱ አሏህ ነው፦
15፥74 *"ላይዋንም ከታችዋ አደረግን፡፡ በእነሱም ላይ የሸክላ ደንጊያዎችን አዘነብንባቸው"*፡፡ فَجَعَلْنَا عَالِيَهَا سَافِلَهَا وَأَمْطَرْنَا عَلَيْهِمْ حِجَارَةً مِّن سِجِّيلٍ
54፥34 *"እኛ በእነርሱ ላይ ጠጠርን ያዘለች ነፋስን ላክን፡፡ የሉጥ ቤተሰቦች ብቻ ሲቀሩ እነርሱንስ በሌሊት መጨረሻ ላይ አዳንናቸው*፡፡ إِنَّا أَرْسَلْنَا عَلَيْهِمْ حَاصِبًا إِلَّا آلَ لُوطٍ ۖ نَّجَّيْنَاهُم بِسَحَرٍ
17፥68 *"የየብሱን በኩል ምድርን በእናንተ መገልበጡን ወይም ጠጠርን የያዘ ነፋስን በእናንተ ላይ መላኩን ከዚያም ለእናንተ ጠባቂ አለማግኘታችሁን አትፈሩምን?* أَفَأَمِنتُمْ أَن يَخْسِفَ بِكُمْ جَانِبَ الْبَرِّ أَوْ يُرْسِلَ عَلَيْكُمْ حَاصِبًا ثُمَّ لَا تَجِدُوا لَكُمْ وَكِيلًا

"አሏህ ከሰማይ በላይ ነው" ብሎ ማመን የሙእሚን ዓይተኛ ጠባይ ነው፥ አሏህ እስከመጨረሻው ሙእሚን ከሚላቸው ባሮቹ ያድርገን! አሚን።

ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
የአሏህ አብሮነት

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ፥ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።

8፥19 *"አሏህም ከምእምናን "ጋር" ነው"*፡፡ وَأَنَّ اللَّهَ مَعَ الْمُؤْمِنِينَ

አምላካችን አሏህ ነገርን ሁሉ ዐዋቂ ነው፥ እርሱ በነገሩ ሁሉ ላይ ተቆጣጣሪ ነው፦
64፥11 *"አላህም ነገሩን ሁሉ ዐዋቂ ነው"*፡፡ وَاللَّهُ بِكُلِّ شَيْءٍ عَلِيمٌ
4፥86 *”አላህ በነገሩ ሁሉ ላይ ተቆጣጣሪ ነው”*፡፡ إِنَّ اللَّهَ كَانَ عَلَىٰ كُلِّ شَيْءٍ حَسِيبًا

“ሸይእ” شَيْءٍ ማለት “ነገር” ማለት ሲሆን ፍጥረት ነው፥ ጊዜ እና ቦታ ፍጥረት ናቸው። አሏህ ነገርን ሁሉ ለማወቅ እና ለመቆጣጠር ጊዜ ማለትም ትላንት፣ ዛሬ፣ ነገር ወይም ቦታ ማለትም እርዝመት፣ ስፋት፣ ቁመት አይወስኑትም፥ እርሱ በነገር ሁሉ ላይ ቻይ ነው። እርሱ ፍጥረትን ሁሉ ያካበበ ነው፦
59፥6 *"አላህም በነገሩ ሁሉ ላይ ቻይ ነው"*፡፡ وَاللَّهُ عَلَىٰ كُلِّ شَيْءٍ قَدِيرٌ
41፥54 ንቁ! እነርሱ ከጌታቸው መገናኘት በመጠራጠር ውስጥ ናቸው፡፡ ንቁ! *"እርሱ በነገሩ ሁሉ ከባቢ ነው"*፡፡ أَلَا إِنَّهُمْ فِي مِرْيَةٍ مِّن لِّقَاءِ رَبِّهِمْ ۗ أَلَا إِنَّهُ بِكُلِّ شَيْءٍ مُّحِيطٌ

ጌታችን አሏህ ነገርን ሁሉ በችሎታው፣ በዕውቀቱ፣ በእዝነቱ፣ በእይታው፣ በመስማቱ ያካበበ ነው፦
40፥7 *"ጌታችን ሆይ! ነገሩን ሁሉ በእዝነት እና በዕውቀት ከበሃል"*። رَبَّنَا وَسِعْتَ كُلَّ شَيْءٍ رَّحْمَةً وَعِلْمًا
65፥12 አላህ በነገሩ ሁሉ ላይ ቻይ መኾኑን *"አላህም በነገሩ ሁሉ በዕውቀት ያካበበ"* ታውቁ ዘንድ ይህንን አሳወቃችሁ፡፡ لِتَعْلَمُوا أَنَّ اللَّهَ عَلَىٰ كُلِّ شَيْءٍ قَدِيرٌ وَأَنَّ اللَّهَ قَدْ أَحَاطَ بِكُلِّ شَيْءٍ عِلْمًا

አሏህ ሁሉን ነገር ያካበበው በባሕርያቱ ነው፥ የትም ብንሆን የምሠራውን ሁሉ ስለሚያውቅ፣ ስለሚሰማ፣ ስለሚመለከት ከእኛ ጋር ነው፦
57፥4 *"በምድር ውስጥ የሚገባውን፣ ከእርሷም የሚወጣውን፣ ከሰማይም የሚወርደውን በእርሷም ውስጥ የሚያርገውን ያውቃል፥ እርሱም የትም ብትኾኑ ከእናንተ ጋር ነው፡፡ አላህም የምትሠሩትን ሁሉ ተመልካች ነው"*፡፡ يَعْلَمُ مَا يَلِجُ فِي الْأَرْضِ وَمَا يَخْرُجُ مِنْهَا وَمَا يَنزِلُ مِنَ السَّمَاءِ وَمَا يَعْرُجُ فِيهَا ۖ وَهُوَ مَعَكُمْ أَيْنَ مَا كُنتُمْ ۚ وَاللَّهُ بِمَا تَعْمَلُونَ بَصِيرٌ

የዚህ አንቀጽ ዐውደ ምህዳሩ ላይ "ያውቃል" "ተመልካች" የሚሉት ባሕርያት አሏህ አብሮነቱን ያሳያሉ። "መዐ" مَعَ ማለት "ጋር" ማለት ሲሆን "ሐርፉል ጀር" حَرْفُ الْجَرِّ ማለት "መስተዋድድ"preposition" ነው፥ "ጋር" የሚለው "አብሮነትን" የሚያሳይ መስተዋድድ ነው። አሏህ ከበጎ ሠሪዎች ጋር፣ ከሚጠነቀቁት ጋር፣ ከታጋሾቹ ጋር፣ ከምእምናን ጋር ነው፦
29፥69 *"አላህም በእርግጥ ከበጎ ሠሪዎች ጋር ነው"*፡፡ وَإِنَّ اللَّهَ لَمَعَ الْمُحْسِنِينَ
9፥123 አላህም ከሚጠነቀቁት ጋር መኾኑን ዕወቁ፡፡ وَاعْلَمُوا أَنَّ اللَّهَ مَعَ الْمُتَّقِينَ
8፥66 *"አላህም ከታጋሾቹ ጋር ነው"*፡፡ وَاللَّهُ مَعَ الصَّابِرِينَ
8፥19 አላህም ከምእምናን ጋር ነው፡፡ وَأَنَّ اللَّهَ مَعَ الْمُؤْمِنِينَ

"ከበጎ ሠሪዎች ጋር ነው" ማለት "ከመጥፎ ሠሪዎች ጋር አይደለም" ማለት ነው፣ "ከሚጠነቀቁት ጋር ነው" ማለት "ከማይፈሩት ጋር አይደለም" ማለት ነው፣ "ከታጋሾቹ ጋር ነው" ማለት "ከትግስት የለሾች ጋር አይደለም" ማለት ነው፣ "ከምእምናን ጋር ነው" ማለት "ከከሃድያን ጋር አይደለም" ማለት ነው። አሏህ ኢሕሣን፣ ተቅዋእ፣ ሶብር፣ ኢማን ካላቸው ጋር በአብሮነት መሆኑን የሚያሳይ እንጂ ዛቱ ሁሉም ቦታ ውስጥ አለ ማለት አይደለም፦
20፥አላህም አለ «አትፍሩ! *"እኔ በእርግጥ ከእናንተ ጋር ነኝና፥ እሰማለሁ፤ አያለሁም"*፡፡ قَالَ لَا تَخَافَا ۖ إِنَّنِي مَعَكُمَا أَسْمَعُ وَأَرَىٰ

"አሏህ ከዐርሽ በላይ ነው" ብዬ ስፓስት አንዱ የክርስትና መምህር፦ "እግዚአብሔር ግን መላኤ ኩሉ ማለትም ሁሉም ቦታ የሚገኝ"omnipresent" ነው" የሚል ትምህርት ሲያስተምር ነበር። በፈጣሪ መኖር ሦስት ዓይነት እሳቤ አለ፥ እርሱም፦
1ኛ. "ፈጣሪ በፍጥረቱ ውስጥ ነው"Creator is inside of his Creation" የሚል እሳቤ ነው፥ "ፈጣሪ በፍጥረቱ ውስጥ ነው" የሚለው እሳቤ የሁሉ አምላክነት"Pantheism" እሳቤ ሲሆን ፈጣሪ ቤተክርስቲያ እንዳለ ሁሉ በእኩል መጠን እና ደረጃ ሽንት ቤት፣ መሸታ ቤት፣ ጠንቋይ ቤት ውስጥም አለ" የሚል የአውግስቲኖስ እሳቤ ነው፤ ይህ እሳቤ ዐበይት የክርስትና አንጃዎ ይቀበላሉ።

2. "ፍጥረት በፈጣሪ ውስጥ ነው"Creation is inside of his creator" የሚል እሳቤ ነው፥ "ፍጥረት በፈጣሪ ውስጥ ነው" የሚለው እሳቤ ሁሉ ነገር የፈጣሪ ምንነት፣ ማንነት እና ክፍል "Panentheism" ነው" የሚል እሳቤ ሲሆን ፈጣሪ ፍጡር ሆነ የሚል እሳቤ ያቀፈ ነው።

3. "ፈጣሪ ከፍጥረት ውጪ ነው"Creator is outside of his Creation" የሚል እሳቤ ነው፥ "ፈጣሪ ከፍጥረት ውጪ ነው" የሚል እሳቤ ፈጣሪ ከፍጥረት በላይ ይኖራል"Transcendent" የሚል እሳቤ ሲሆን የሙሥሊም አህሉ አሥ-ሡናህ ወል ጀማዓህ የምንቀበለው ይህንን እሳቤ ነው። አሏህ ከፍጡራን በኑባሬ ተነጥሎ ከፍጡራን ጋር በባሕርያቱ ይገናኛል፥ ይህ ኅሊና የሚቀበለው እሳቤ ነው።

ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
መሢሑ አድ-ደጃል

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ፥ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።

33፥63 *"ሰዎች ከሰዓቲቱ ይጠይቁሃል፡፡ «ዕውቀትዋ አላህ ዘንደ ብቻ ነው» በላቸው! የሚያሳወቅህም ምንድን ነው? ሰዓቲቱ በቅርብ ጊዜ ልትኾን ይከጀላል"*፡፡ يَسْأَلُكَ النَّاسُ عَنِ السَّاعَةِ ۖ قُلْ إِنَّمَا عِلْمُهَا عِندَ اللَّهِ ۚ وَمَا يُدْرِيكَ لَعَلَّ السَّاعَةَ تَكُونُ قَرِيبًا

ስለ ሰዓቲቱ ምልክት አምላካችን አሏህ ለነቢያችን"ﷺ" ካሳወቃቸው ነገር ነው፥ ከሰዓቲቱ ዐበይት ምልክት አንዱ ደግሞ ስለ መሢሑ አድ-ደጃል መምጣት ነው፦
33፥63 *"ሰዎች ከሰዓቲቱ ይጠይቁሃል፡፡ «ዕውቀትዋ አላህ ዘንደ ብቻ ነው» በላቸው! የሚያሳወቅህም ምንድን ነው? ሰዓቲቱ በቅርብ ጊዜ ልትኾን ይከጀላል"*፡፡ يَسْأَلُكَ النَّاسُ عَنِ السَّاعَةِ ۖ قُلْ إِنَّمَا عِلْمُهَا عِندَ اللَّهِ ۚ وَمَا يُدْرِيكَ لَعَلَّ السَّاعَةَ تَكُونُ قَرِيبًا

"መሢሕ" مَسِيح የሚለው ቃል "መሠሐ” مَسَحَ ማለትም “አበሰ” "አሸ" “ቀባ” ከሚል ሥርወ-ቃል የተገኘ ሲሆን “የታበሰ" "የታሸ" "የተቀባ" ማለት ነው፦
38፥33 *«በእኔ ላይ መልሷት» አለ ባትዎችዋን እና አንገቶችዋን "ማበስ" ያዘ*፡፡ رُدُّوهَا عَلَىَّ ۖ فَطَفِقَ مَسْحًۢا بِٱلسُّوقِ وَٱلْأَعْنَاقِ

እዚህ አንቀጽ ላይ“ማበስ” ለሚለው የገባው የስም መደብ “መሥሕ” مَسْح ነው፥ ደጃል ዐይኑ "የታበሰ" ነው፦
ኢማም ሙሥሊም መጽሐፍ 54, ሐዲስ 129
አነሥ ኢብኑ ማሊክ እንደተረከው የአላህ መልእክተኛም”ﷺ” እንዲህ አሉ፦ *”ደጃል ዓይኑ የታበሰ ነው፥ በዓይኖቹ መካከል “ካፊር” የሚል ጽሑፍ አለ። ከዚያም “ከፈረ” የሚል አነባነብ ሁሉም ሙሥሊም ያነበዋል”*። عَنْ أَنَسِ بْنِ مَالِكٍ، قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم ‏”‏ الدَّجَّالُ مَمْسُوحُ الْعَيْنِ مَكْتُوبٌ بَيْنَ عَيْنَيْهِ كَافِرٌ ‏”‏ ‏.‏ ثُمَّ تَهَجَّاهَا ك ف ر ‏”‏ يَقْرَؤُهُ كُلُّ مُسْلِمٍ ‏”‏

እዚህ ሐዲስ ላይ “የታበሰ” ለሚለው ቃል የገባው “መምሡሑ” مَمْسُوحُ የሚለው ቃል መሆኑ አንባቢ ልብ ይለዋል፥ ዒሣ ኢብኑ መርየም በሽተኞችን፣ ህሙማንን እና ሙታንን በማበስ፣ በማሸት እና በመቀባት ከበሽታቸው በአሏህ ፈቃድ ያሽራቸው ስለነበረ እና በአሏህ የተሾመ ነቢይ ስለሆነ "አል-መሢሕ" الْمَسِيح የሚል የማዕረግ ስም አለው፦
5፥75 *"የመርየም ልጅ አል-መሢሕ ከበፊቱ መልክተኞች በእርግጥ ያለፉ የኾነ መልክተኛ እንጅ ሌላ አይደለም"*፡፡ مَّا الْمَسِيحُ ابْنُ مَرْيَمَ إِلَّا رَسُولٌ قَدْ خَلَتْ مِن قَبْلِهِ الرُّسُلُ

“ደጃል” دَّجَّال የሚለው ቃል “ደጀለ” دَجَلَ ማለትም “አጭበረበረ” "ዋሸ" "ቀጠፈ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "አጭበርባሪ" "ውሸተኛ" "ቀጣፊ" ማለት ነው፦
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 96, ሐዲስ 82
ሙሐመድ ኢብኑ ሙንከዲር እንደተረከው፦ *"ጃቢር ኢብኑ ዐብደሏህ በአሏህ ምሎ፦ "ኢብኑ አስ-ሷኢድ ደጃል ነው" ሲል ተመልክቻለው፥ እኔም፦ "በአሏህ ትምላለህን? አልኩኝ። እርሱም፦ "ዑመር ከነቢዩ"ﷺ" ዘንድ ሆኖ በዚህ ጉዳይ ሲምል አይቻለው፥ ነቢዩ"ﷺ" ማለቱን አላስተባበሉም" አለ"*። عَنْ مُحَمَّدِ بْنِ الْمُنْكَدِرِ، قَالَ رَأَيْتُ جَابِرَ بْنَ عَبْدِ اللَّهِ يَحْلِفُ بِاللَّهِ أَنَّ ابْنَ الصَّائِدِ الدَّجَّالُ، قُلْتُ تَحْلِفُ بِاللَّهِ‏.‏ قَالَ إِنِّي سَمِعْتُ عُمَرَ يَحْلِفُ عَلَى ذَلِكَ عِنْدَ النَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم فَلَمْ يُنْكِرْهُ النَّبِيُّ صلى الله عليه وسلم‏.‏
ኢማም ሙሥሊም መጽሐፍ 54, ሐዲስ 112
አቢ ሠዒድ እንደተረከው፦ *"የአሏህ መልእክተኛም"ﷺ" ኢብኑ አስ-ሷኢድን ተገናኙት፥ አቡበከር እና ዑመር በመዲና መንገዶች ነበሩ። እርሳቸውም፦ "እኔ የአላህ መልእክተኛ መሆኔን ትመሰክራለህን? አሉት፥ እርሱም፦ "እኔ የአላህ መልእክተኛ መሆኔን ትመሰክራለህን? አለ። እርሳቸውም፦ "በአሏህ፣ በመላእክቱ እና በመጽሐፍቱ አምናለው" አሉት"*። عَنْ أَبِي سَعِيدٍ، قَالَ لَقِيَهُ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم وَأَبُو بَكْرٍ وَعُمَرُ فِي بَعْضِ طُرُقِ الْمَدِينَةِ فَقَالَ لَهُ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم ‏"‏ أَتَشْهَدُ أَنِّي رَسُولُ اللَّهِ ‏"‏ ‏.‏ فَقَالَ هُوَ أَتَشْهَدُ أَنِّي رَسُولُ اللَّهِ فَقَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم ‏"‏ آمَنْتُ بِاللَّهِ وَمَلاَئِكَتِهِ وَكُتُبِهِ

እዚህ ሐዲስ ላይ ኢብኑ አስ-ሷኢድ። ደጃል" የተባለበት "እኔ የአሏህ መልእክተኛ ነኝ" ስላለ ነው፥ ነቢያችን"ﷺ" የመጨረሻ ነቢይ ሆነው ሳለ ይህንን በማለቱ ደጃል ተብሏል። ከአኺሩ አዝ-ዘማን ንዑሣን ምልክቶች አንዱ ሠላሳ የሚያክሉ ሐሠተኛ ነቢያት፦ "እኔ የአሏህ መልእክተኛ ነኝ" ብለው መነሳታቸው ነው። እነዚህ ሐሠተኛ ነቢያት "ደጃሉን" دَجَّالُونَ ተብለዋል፦
ሡነን አቢ ዳውድ መጽሐፍ 37, ሐዲስ 13
የአላህ መልእክተኛ”ﷺ” እንዲህ አሉ፦ *”ከእኔ ዑማ ውስጥ ሠላሳ የሚያህሉ ቀጣፊዎች፦ “ነብይ ነኝ” ብለው ይነሳሉ፥ ነገር ግን እኔ የነብያት መደምደሚያ ነኝ። ከእኔ በኃላ ነብይ የለም”*። وَحَتَّى تَعْبُدَ قَبَائِلُ مِنْ أُمَّتِي الأَوْثَانَ وَإِنَّهُ سَيَكُونُ فِي أُمَّتِي كَذَّابُونَ ثَلاَثُونَ كُلُّهُمْ يَزْعُمُ أَنَّهُ نَبِيٌّ وَأَنَا خَاتَمُ النَّبِيِّينَ لاَ نَبِيَّ بَعْدِي
ኢማም ሙሥሊም መጽሐፍ 54, ሐዲስ 108
አቢ ሁረይራህ እንደተረከው ነቢዩም”ﷺ” እንዲህ አሉ፦ *“የመጨረሻይቱ ሰዓት አትቆምም ሠላሳ የሚቃረቡ "አጨርባሪዎች" ቀጣፊዎች ተነስተውስ፦ “እኔ የአሏህ መልእክተኛ ነኝ” ብለው ቢናገሩ ቢሆን እንጂ”*። عَنْ أَبِي، هُرَيْرَةَ عَنِ النَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم قَالَ ” لاَ تَقُومُ السَّاعَةُ حَتَّى يُبْعَثَ دَجَّالُونَ كَذَّابُونَ قَرِيبٌ مِنْ ثَلاَثِينَ كُلُّهُمْ يَزْعُمُ أَنَّهُ رَسُولُ اللَّهِ
እዚህ ሐዲስ ላይ "አጨርባሪዎች" ለሚለው የገባው ቃል "ደጃሉን" دَجَّالُونَ ሲሆን "ደጃል" دَّجَّال ለሚለው ቃል ብዙ ቁጥር ነው። እዚህ ድረስ ከተግባባን "መሢሑ አድ-ደጃል" مَسِيح الدَّجَّال በጥቅሉ "አጭበርባሪ መሢሕ" "ሐሠተኛ መሢሕ" "ሐሣዌ መሢሕ" ማለት ነው፥ ከአኺሩ አዝ-ዘማን ዐበይት ምልክቶች አንዱ የመሢሑ አድ-ደጃል መምጣት ነው። መካህ እና መዲናህ ሲቀር ደጃል የማያካልለው አገር የለም፦
ኢማም ሙሥሊም መጽሐፍ 54, ሐዲስ 153
አነሥ ኢብኑ ማሊክ እንደተረከው፦ "የአሏህ መልእክተኛም እንዲህ አሉ፦ *"መካህ እና መዲናህ ሲቀር በደጃል የማይካለል አገር የለም"*። حَدَّثَنِي أَنَسُ بْنُ مَالِكٍ، قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم ‏ "‏ لَيْسَ مِنْ بَلَدٍ إِلاَّ سَيَطَؤُهُ الدَّجَّالُ إِلاَّ مَكَّةَ وَالْمَدِينَةَ

በአደም እና በሰዓቲቱ መቆም መካከል ባለው ፍጥረት እንደ ጀጃል ፈተና ታላቅ ፈተና የለም። ዐበይት ነቢያት ስለዚህ ሐሳዌ መሢሕ ሕዝባቸውን አስጠንቅቀዋል፦
ሪያዱ አስ-ሷሊሒን መጽሐፍ 18, ሐዲስ 7
ዒምራን ኢብኑ ሑሶይን"ረ.ዐ." እንደተረከው፦ "የአሏህ መልእክተኛ"ﷺ" እንዲህ ሲሉ ሰምቼ ነበር፥ እርሳቸው እንዲህ አሉ፦ *"በአደም አፈጣጠር እና በሰዓቲቱ መቆም መካከል ባለው ፍጥረት እንደ ጀጃል ፈተና ታላቅ ፈተና የለም"*። عِمْرَانَ بْنُ حُصَيْنٍ رَضِيَ اللَّهُ عَنْهُ قَالَ: سَمِعْتُ رَسُولَ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم يَقُولُ ‏ "‏ مَا بَيْنَ خَلْقِ آدَمَ إِلَى قِيَامِ السَّاعَةِ خَلْقٌ أَكْبَرُ مِنَ الدَّجَّالِ ‏"‏
ኢማም ሙሥሊም መጽሐፍ 60, ሐዲስ 12
አቡ ዑመር"ረ.ዐ."እንደተረከው፦ *"የአሏህ መልእክተኛ"ﷺ" በሰዎች መካከል ቆመው እና አሏህን እንደሚገባው አመስግነው ከዚያም ስለ ደጃል አነሱ። እንዲህም አሉ፦ "እኔ ስለ ደጃል አስጠንቅቄአችኃለው፥ ከነቢይ ለሕዝቦቹ ያስጠነቀቀ ቢሆን እንጂ አንድም የለም"*። وَقَالَ ابْنُ عُمَرَ ـ رضى الله عنهما قَامَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم فِي النَّاسِ فَأَثْنَى عَلَى اللَّهِ بِمَا هُوَ أَهْلُهُ، ثُمَّ ذَكَرَ الدَّجَّالَ، فَقَالَ ‏ "‏ إِنِّي لأُنْذِرُكُمُوهُ، وَمَا مِنْ نَبِيٍّ إِلاَّ أَنْذَرَهُ قَوْمَهُ،

በግሪክ ኮይኔ “አፓካሊፕስ” ἀποκάλυψις ማለት “የተደበቀን ነገር መግለጥ” ማለት ሲሆን የኢየሱስ አፓልካሊስ ቅሪት በሚባለው ራእይ ላይ መሢሑ አድ-ደጃል ሐሰተኛ ነቢይ ተብሎ ተቀምጧል፦
ራእይ 16፥13 "*ከዘንዶውም አፍ፣ ከአውሬው አፍ እና ከሐሰተኛውም ነቢይ አፍ ጓጕንቸሮች የሚመስሉ ሦስት ርኵሳን መናፍስት ሲወጡ አየሁ"*።
ራእይ 19፥20 *"አውሬውም ተያዘ፥ በእርሱም ፊት ተአምራትን እያደረገ የአውሬውን ምልክት የተቀበሉትን ለምስሉም የሰገዱትን ያሳተ ሐሰተኛው ነቢይ ከእርሱ ጋር ተያዘ"*።

ዘንዶ የተባለው ኢብሊሥ ሲሆን፣ አውሬ የተባለው የሮም(የአውሮፓ) መንግሥት ሲሆን፣ ሐሠተኛ ነቢይ የተባለው ደግሞ የአውሬውን ምልክት የተቀበሉትን ለምስሉም የሰገዱትን ያሳተ ሐሰተኛው መሢሕ ነው፥ 666 የስም ቁጥር ነው፦
ራእይ 15፥2 *”በአውሬው እና በምስሉም በስሙም ቍጥር”* ላይ ድል ነሥተው የነበሩት የእግዚአብሔርን በገና ይዘው በብርጭቆ ባሕር ላይ ሲቆሙ አየሁ።
ራእይ 13፥18 *"አእምሮ ያለው የአውሬውን ቍጥር ይቍጠረው፤ ቍጥሩ የሰው ቍጥር ነውና፥ ቍጥሩም ስድስት መቶ ስድሳ ስድስት ነው"*።

የስሙ ቁጥር 666 ነው፥ የኦርቶዶክስ አንድምታ ይህንን በጥሩ ሁኔታ ያስቀምጧል፦
ራእይ 13፥18 አንድምታ፦ “ስሙም በዕብራይስጥ “መርምያዋዖስ” በግዕዝ ደግሞ “ፀራዊ” ማለትም “ተቃዋሚ” ወይም “ሐሳዊ” ማለትም “ሐሰተኛ” የሚል ነው።

በዕብራይስጥ "መርምያዋዖስ" ר‎ע‎ו‎י‎מרמ‎ ማለት "ሐሳዌ" ማለት ሲሆን ይህንን ስም በዕብራይስጥ ፊደላት፦
1. "ሜም" מ‎ ቁጥሩ "40" ነው፣
2. "ሬስ" ר‎ ቁጥሩ "200" ነው፣
3. "ሜም" מ‎ ቁጥሩ "40" ነው፣
4. "ዮድ" י‎ ቁጥሩ "10" ነው፣
5. "ዋው" ו‎ ቁጥሩ "6" ነው፣
6. "ዓይን" ע‎ ቁጥሩ "70" ነው፣
7. "ሲን" ר‎ ቁጥሩ "300" ነው፣
ድምር 666 ይሆናል።

አይሁድ የሚጠብቁት እውነተኛው ነቢይ መሢሑ ኢየሱስ ሆኖ ሳለ ይህ ሐሰተኛ ሰው፦ "ነቢይ እና መሢሕ ነኝ" ብሎ ያጭበረብራል። እንግዲህ ስለ መሢሑ አድ-ደጃል በግርድፉ እና በሌጣው ስላስቀመጥኩኝ እንጂ ደርዝ እና ፈርጅ ባለው መልኩ ላስቀምጥ ብል ቦታ አይበቃኝም፥ ቅሉና ጥቅሉ ግን ስለ እርሱ እሳቤውን ለመረዳት ይህ መጣጥፍ በቂ ነው። አሏህ ከመሢሑ አድ-ደጃል ፊትና ይጠብቀን! አሚን።

ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
ነቢዩ ኢድሪሥ

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ፥ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።

19፥56 *"በመጽሐፉ ኢድሪሥን አውሳ! እርሱ እውነተኛ ነቢይ ነበርና"*፡፡ وَاذْكُرْ فِي الْكِتَابِ إِدْرِيسَ ۚ إِنَّهُ كَانَ صِدِّيقًا نَّبِيًّا

"ሚዕራጅ" مِعْرَاج የሚለው ቃል "ዐረጀ" عَرَجَ ማለትም "ወጣ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "መውጣት" ማለት ነው፥ የሰባቱ ሰማያት "መወጣጫ" ደግሞ "መዓሪጅ" مَعَارِج ይባላል፦
70፥3 *"የመሰላሎች ባለቤት ከኾነው አላህ"*፡፡ مِّنَ اللَّهِ ذِي الْمَعَارِجِ

አምላካችን አሏህ የሰባቱ ሰማያት መወጣጫዎች ባለቤት ሲሆን ተወዳጁ ነቢያችንን"ﷺ" ወደ ሰባቱ ሰማያት እንዲወጡ አድርጓል፥ ነቢያችንም"ﷺ" አራተኛ ሰማይ ላይ ነቢዩ ኢድሪስን አይተውቷል፦
ጃምዒ አት-ቲርሚዚይ መጽሐፍ 47, ሐዲስ 3451
ሸይባን ከቀታዳህ ሰምቶ እንደተረከው፦ *"በአሏህን ንግግር፦ "ወደ ከፍተኛም ስፍራ አነሳነው" የሚለውን አነሥ ኢብኑ ማሊክ እንደተረከው፦ "የአሏህ ነቢይ"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "በተወጣው ጊዜ አራተኛ ሰማይ ላይ ኢድሪሥን አየሁት"*። حَدَّثَنَا شَيْبَانُ، عَنْ قَتَادَةَ، فِي قَوْلِهِ ‏:‏ ‏(‏ورَفَعْنَاهُ مَكَانًا عَلِيًّا ‏)‏ قَالَ حَدَّثَنَا أَنَسُ بْنُ مَالِكٍ، أَنَّ نَبِيَّ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم قَالَ ‏"‏ لَمَّا عُرِجَ بِي رَأَيْتُ إِدْرِيسَ فِي السَّمَاءِ الرَّابِعَةِ ‏"‏

"ተወጣው" ለሚለው የገባው ቃል "ዑሪጀ" عُرِجَ መሆኑን አንባቢል ልብ ይለዋል። አምላካችን አሏህ ስለ ኢድሪሥ ሲናገር፦ "ወደ ከፍተኛም ስፍራ አነሳነው" በማለት ይህ "ከፍተኛ ስፍራ" አራተኛ ሰማይ መሆኑ እሙንና ቅቡል ነው፦
19፥57 *"ወደ ከፍተኛም ስፍራ አነሳነው"*፡፡ وَرَفَعْنَاهُ مَكَانًا عَلِيًّا
ተፍሢሩል ኢብኑ ከሲር 19፥57 "ኢብኑ አቢ ነጂሕ እንደተናገረው፦ "ሙጃሂድ በንግግሩ እንዲህ አለ፦ *"ወደ ከፍተኛም ስፍራ አነሳነው" የሚለው ኢድሪሥ አልሞተም፥ ልክ እንደ ዒሣ ማረግ አርጓል"*።
ሡፍያን ከመንሱር እንደተረከው ሙጃሂድም አለ፦ *"ወደ ከፍተኛም ስፍራ አነሳነው" የሚለው ኢድሪሥ ወደ አራተኛ ሰማይ አርጓል"*።
وقال ابن أبي نجيح ، عن مجاهد في قوله : ( ورفعناه مكانا عليا ) قال : إدريس رفع ولم يمت ، كما رفع عيسى .
وقال سفيان ، عن منصور ، عن مجاهد : ( ورفعناه مكانا عليا ) قال : رفع إلى السماء الرابعة .

"ረፈዐ" رَفَعَ ማለት "አረገ" ማለት ነው፥ አምላካችን አሏህ ዒድሪሥን፦ "አነሳነው" ለሚለው የገባው ቃል "ረፈዕና-ሁ" رَفَعْنَاهُ ነው። ስለ ዒሣም ሲናገር፦ "አነሳው" ለሚለው የገባው ቃል "ረፈዐ-ሁ" رَّفَعَهُ ነው፦
4፥158 *"ይልቁንስ አላህ ዒሣን ወደ እርሱ አነሳው፥ አላህም አሸናፊ ጥበበኛ ነው"*፡፡ بَل رَّفَعَهُ اللَّهُ إِلَيْهِ ۚ وَكَانَ اللَّهُ عَزِيزًا حَكِيمًا

ሚሽነሪዎች በቁርኣን ዒሣ ማረጉን እንደ አምላክነት ሲረዱት የኢድሪሥን ማረግ ሲያውቁ ምን ይውጣቸው ይሆን? ቅሉ ግን ኢድሪሥ ከታጋሾቹ የሆነ ነቢይ እንደሆነ ሁሉ ዒሣም ነቢይ ነው፦
21፥85 *"ኢስማዒልንም ኢድሪስንም ዙልኪፍልንም አስታውስ፡፡ ሁሉም ከታጋሾቹ ናቸው"*፡፡ وَإِسْمَاعِيلَ وَإِدْرِيسَ وَذَا الْكِفْلِ ۖ كُلٌّ مِّنَ الصَّابِرِينَ
19፥56 *"በመጽሐፉ ኢድሪሥን አውሳ! እርሱ እውነተኛ ነቢይ ነበርና"*፡፡ وَاذْكُرْ فِي الْكِتَابِ إِدْرِيسَ ۚ إِنَّهُ كَانَ صِدِّيقًا نَّبِيًّا
ተፍሢሩል ጀላለይን 19፥56 *"በመጽሐፉ ኢድሪሥን አውሳ! እርሱም የኑሕ አያት ነው፥ "እርሱ እውነተኛ ነቢይ ነበርና"*።
{ وَٱذْكُرْ فِى ٱلْكِتَٰبِ إِدْرِيسَ } هو جدّ أبي نوح { إِنَّهُ كَانَ صِدِّيقاً نَّبِيّاً }.

"ኢድሪሥ" إِدْرِيس የሚለው ቃል "ደረሠ" دَرَسَ ማለትም "ተማረ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "አስተማሪ" ማለት ነው፥ የመጣለት ወሕይ ደግሞ "ደርሥ" دَرْس ማለትም "ትምህርት" ይባላል። አሏህ ይህንን ሰው ወሕይ ስላወረደለት ኢድሪሥ አለው፥ የቤተሰቡ ስም ደግሞ "አኽኑኽ" أخنُوخ ሲሆን "ሄኖክ" ማለት ነው። በባይብል የኑሕ ቅድመ-አያት በቁርኣን ኢድሪሥ የተባለው ሄኖክ ሲሆን ሄኖክ ሞትን ሳያይ ፈጣሪ እንደወሰደው ይናገራል፦
ዘፍጥረት 5፥24 *"ሄኖክም አካሄዱን ከእግዚአብሔር ጋር ስላደረገ አልተገኘም፤ እግዚአብሔር ወስዶታልና"*።
ዕብራውያን 11፥5 *"ሄኖክ ሞትን እንዳያይ በእምነት ተወሰደ፥ እግዚአብሔርም ስለ ወሰደው አልተገኘም። ሳይወሰድ እግዚአብሔርን ደስ እንዳሰኘ ተመስክሮለታልና"*።
በተለይ ዐረቢኛው ባይብል፦ "አሏህ ወስዶታል" أنَّ اللهَ رَفَعَهُ إلَيْهِ ይላል፥ "ረፈዐ-ሁ" رَفَعَهُ የሚለው ይሰመርበት። ሄኖክ ከአዳም ሰባተኛ ትውልድ ሲሆን ትንቢት የተናገረ ነቢይ ነው፦
ይሁዳ 1፥14 *"ከአዳም ጀምሮ ሰባተኛ የሆነ ሄኖክ፦ እነሆ ጌታ ከአእላፋት ቅዱሳኑ ጋር መጥቶአል"*።
ይሁዳ 1፥15 *"በሁሉ ላይ እንዲፈርድ፥ በኃጢአተኝነትም ስላደረጉት ስለ ኃጢአተኛ ሥራቸው ሁሉ ዓመፀኞችም ኃጢአተኞች በእርሱ ላይ ስለ ተናገሩ ስለ ጭከና ነገር ሁሉ ኃጢአተኞችን ሁሉ እንዲወቅስ" ብሎ ለእነዚህ ደግሞ ትንቢት ተናገረ"*።

ሄኖክ ግልጠተ-መለኮት የመጣለት በዐረማይክ ሲሆን እርሱ የመጣለት የመጀመሪያው ግልጠተ-መለኮት ሥረ-መሠረቱ በዘመናችን የለም። ቅሉ ግን የእርሱን ግልጠተ-መለኮት መሠረት ያደረገ የኮፒ ቅሪት በ 1948 ድኅረ-ልደት ከሙት ባሕር አጠገብ የቁምራን አራተኛ ዋሻ የተገኘው 11 የዐረማይክ ብጥስጣሽ ሲሆን የቁምራን አንደኛ ዋሻ የተገኘው ደግሞ 3 የዕብራይስጥ ብጥስጣሽ ነው፥ ይህም መጽሐፍ ዕድሜው ከ 300–200 ቅድመ-ልደት አካባቢ እንደሆነ ይገመታል። በተጨማሪም የግሪክ ብጥስጣሽ በ 6ኛው ክፍለ-ዘመን የነበረ በ 1892 ድኅረ-ልደት ተገኝቷል፥ እንዲሁ የላቲን ብጥስጣሽ በ 8ኛው ክፍለ-ዘመን የነበረ በ 1893 ድኅረ-ልደት ተገኝቷል።

በአገራችን ያለው መጽሐፈ ሄኖክ ግን መቼ እንተጻፈ እና በማን እንደተጻፈ አይታወቅም፥ "በግዕዝ ቋንቋ ሄኖክ እራሱ ተናገረ ወይም ጻፈ" የሚባለው ትርክት ቆዳን ለማስወደድ እንጂ አንድም የለዘብተኛ ሊሕቃን ማስረጃ የለም። በአገራችን ያለው መጽሐፈ ሄኖክ ውስጡ ያለው ሽታ ሄኖክ እንዳልተናገረው እና እንዳልጻፈው ያሳብቃል፦
፨ የዚህ መጽሐፍ ተናጋሪ እና ጸሐፊ በ 1፥1ላይ ስለ ሄኖክ እና ሄኖክ የተናገረው በመንገር እና በ 4፥1 ላይ ከሄኖክ እርገት በኃላ ስላለው ታሪክ ይነግረናል።

፨ የዚህ መጽሐፍ ተናጋሪ እና ጸሐፊ ኖኅ የተወለደው ሄኖክ ከተወሰደ 169 ዓመት በኃላ ሆኖ ሳለ በ 18፥1 ላይ "ኖኅ" የሚል ቃል በመጠቀም እና ኖኅ ሄኖክን እንዳናገረው በ 18፥3 ላይ ይናገራል።

፨ የዚህ መጽሐፍ ተናጋሪ እና ጸሐፊ በ 32፥2-3 ላይ "ባቢሎን" "አማሌቅ" "ሶርያ" "ኤዶም" "ሞአብ" "አሞን" እያለ ከሄኖክ ስንት ዘመን በኃላ የተፈጠሩትን አገር እና ሰዎች ይናገራል።

፨ የዚህ የዚህ መጽሐፍ ተናጋሪ እና ጸሐፊ በ18፥18 ላይ "አብርሃም" እያለ ከሄኖክ ስንት ዘመን በኃላ ያለውን ሰው ይናገራል፥ ጭራሽ በ 32፥3-4 ላይ ከአብርሃም በኃላ የተወለዱት "ሞአብ" "አሞን" ሆነው ሳለ አብርሃም ከእነርሱ እንደተወለደ ይናገራል።

፨ የዚህ መጽሐፍ ተናጋሪ እና ጸሐፊ በ 32፥5-13 ላይ ከሄኖክ እርገት በኃላ የተፈጠሩትን "እስማኤል" "ይስሐቅ" "ያዕቆብ" "ኤሳው" "አሥራ ሁለቱ ነገደ እስራኤል" "ግብጻውያን" "ምድያማውያን" እያለ መናገሩ በራሱ ጸሐፊውና ተናጋሪው ሄኖክ አለመሆኑን ያሳብቃል።

፨ የዚህ መጽሐፍ ተናጋሪ እና ጸሐፊ በ 1፥5 ላይ እስራኤል፣ ደብረ-ሲና፣ ሙሴ፣ አሮን፣ ሰባው ሽማግሌዎች እያለ መናገሩ በራሱ ሄኖክ አለመሆኑን ያሳብቃል።

፨ የዚህ መጽሐፍ ተናጋሪ እና ጸሐፊ በ 25፥27 ላይ "ኤርትራ" እያለ ይናገራል፥ በ 34፥48 ላይ ደግሞ "ኢያሱ" እና "ከነዓን" እያለ ከግብጽ ነጻነት በኃላ ያለውን ታሪክ ይናገራል።

፨ የዚህ መጽሐፍ ተናጋሪ እና ጸሐፊ በ 32፥57 ላይ "ሳሙኤል" እና "ሳኦል" በማለት፣ በ 32፥65-66 ላይ "ዳዊት" እና "ሰልሞን" በማለት፣ በ 32፥73 ላይ "ኤልያስ" በማለት ከመሳፍንት ዘመን በኃላ ያለውን ታሪክ ይናገራል።

፨ የዚህ መጽሐፍ ተናጋሪ እና ጸሐፊ በ 12፥12 ላይ እና ሌሎችም ብዙ አናቅጽ ላይ "ክርስቶስ" እያለ ይጠቀማል፥ "ክርስቶስ" χριστός የግሪክ ቃል ሲሆን በሄኖክ ዘመን የግሪክ ቋንቋ ይቅርና ግሪካውያንም አልተፈጠሩም። በ 33፥42 ላይ ደግሞ "ሮማውያን" "ሐዋርያት" "ዮሐንስ" እያለ የአዲስ ኪዳንን ታሪክ ይናገራል።

፨ የዚህ መጽሐፍ ተናጋሪ እና ጸሐፊ በ 21፥47 ላይ "ጳጉሜ" እያለ ይጠቀማል፥ "ጳጉሜ" የሚለው ቃል “ኤጳጉሚኖስ” ἐπαγόμενοι ከሚለው ከግሪክ ቃል የተገኘ ሲሆን በሄኖክ ዘመን የግሪክ ቋንቋ ይቅርና ግሪካውያንም አልተፈጠሩም። ይህ ጉድ ሳይበቃ በ 6፥24 ላይ እና ሌሎችም ብዙ አናቅጽ ላይ "ሥላሴ" እያለ ይጠቀማል፥ እንደሚታወቀው "ሥላሴ" የሚለው የግዕዙ ቃል አገልግሎት ላይ የዋለው ከኒቂያ ጉባኤ እና ከቆስጠንጢኒያ ጉባኤ በኃላ ሆኖ ሳለ ይህ ቃል መግባቱ በራሱ ሄኖክን ማስዋሸት ነው።

፨ የዚህ መጽሐፍ ተናጋሪ እና ጸሐፊ በ 26፥3 ላይ "ፀሐይ እና ጨረቃ መጠናቸው እኩል ነው" ይለናል፥ የፀሐይ መጠን 69634 ኪሎ ሜትር ሲሆን የጨረቃ መጠን 17371 ኪሎ ሜትር መሆኑ እራሱ ሄኖክን ማስዋሸት ነው።

ስለዚህ "የመጽሐፈ ሄኖክ ተናጋሪ እና ጸሐፊ ሄኖክ ነው" ብሎ አቧራ ማስነሳት መናኛ ምክንያት ነው፥ ሳይቀመጡ እግር መዘርጋት ለመፈንገል ነው። እዚህ ድረስ ካየን ዘንዳ ቁርኣን ከእርሱ በፊት ከወረዱት መጽሐፍት በስም የጠቀሳቸው መጽሐፍት ሦስት ናቸው፥ እነርሱም፦ ተውራት፣ ዘቡር እና ኢንጂል ናቸው። ቁርኣን ዕውቅና ሳይሰጣቸው በዝምታ ያለፋቸው እና በአይሁዳውያንና በክርስቲያኖች እጅ ያሉትን መጽሐፍት ሳናስተባብል ሳንቀበል በዝምታ እናልፈዋለን፥ ስለ መጽሐፈ ሄኖክ ያለን እይታ በዚህ ልክና መልክ ነው። በተረፈ ሾላ በድፍኑ፦ "በመጽሐፈ ሄኖክ እመኑ" ማለት አንዳችም ቁብ የለውም፥ ይህንን መርዶ ስትሰሙ እህህና አሄሄ እያሉ መንፈቅፈቅና መነፋረቅ የጨባራ ለቅሶና ተስካር ነው። "አሞኛችሁ ዘንድ ዓይናችሁን ጨፍኑ" ማለት ቋ ያለ ጉፋያ እና እንጉልፋቶ ሙግት ነው።

ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
ዙል-ቀርነይን

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ፥ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።

18፥83 *"ስለ ዙል-ቀርነይንም ይጠይቁካል፡፡ «በእናንተ ላይ ከእርሱ ወሬን አነባለሁ» በላቸው"*፡፡ وَيَسْأَلُونَكَ عَن ذِي الْقَرْنَيْنِ ۖ قُلْ سَأَتْلُو عَلَيْكُم مِّنْهُ ذِكْرًا

"ቀርን" قَرْن ማለት “ቀንድ” ማለት ሲሆን "ሱር" صُّور ማለትም "መለከት" በሚል ቃሉ አገልግሏል፦
ሡነን አቢዳውድ መጽሐፍ 42, ሐዲስ 147
ዐብደሏህ ኢብኑ ዐምር እንደተረከው፦ “ነቢዩም አሉ፦ *”ሱር የሚነፋበት ቀርን ነው”*። عَنْ عَبْدِ اللَّهِ بْنِ عَمْرٍو، عَنِ النَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم قَالَ “‏ الصُّورُ قَرْنٌ يُنْفَخُ فِيهِ ‏”‏

"ቀርን" قَرْن በሌላ ትርጉሙ "ክፍለ-ዘመን" ወይም "ትውልድ" በሚል ትርጉም መጥቷል፦
10፥13 *ከእናንተ በፊት የነበሩትንም "የክፍለ ዘመናት" ሰዎች መልክተኞቻቸው በማስረጃዎች የመጧቸው ሲኾኑ በበደሉና የማያምኑም በኾኑ ጊዜ በእርግጥ አጠፋናቸው*፡፡ وَلَقَدْ أَهْلَكْنَا الْقُرُونَ مِن قَبْلِكُمْ لَمَّا ظَلَمُوا ۙ وَجَاءَتْهُمْ رُسُلُهُم بِالْبَيِّنَاتِ وَمَا كَانُوا لِيُؤْمِنُوا

"ቀርነይን" قَرْنَيْن ማለት ደግሞ የቀርን ሙሰና ሲሆን "ሁለት ቀንዶች" ወይም "ሁለት ክፍለ-ዘመናት" ማለት ነው፥ ለምሳሌ "ዙል-ቀርነይን" ذِي الْقَرْنَيْن ማለት "የሁለቱ ቀንዶች ባለቤት" ወይም "የሁለቱ ክፍለ-ዘመናት ባለቤት" ማለት ነው፦
18፥83 *"ስለ ዙል-ቀርነይንም ይጠይቁካል፡፡ «በእናንተ ላይ ከእርሱ ወሬን አነባለሁ» በላቸው"*፡፡ وَيَسْأَلُونَكَ عَن ذِي الْقَرْنَيْنِ ۖ قُلْ سَأَتْلُو عَلَيْكُم مِّنْهُ ذِكْرًا

ዙል-ቀርነይን ምስራቅን እና ምዕራብን ያካለለ ሁለት መንግሥት ያቀፈ ንጉሥ ሲሆን የእርሱ መንግሥት ከ 550 ቅድመ-ልደት"BC"–330 ቅድመ-ልደት BC ለሁለት ክፍለ-ዘመናት የቆየ ነው። "ዐን" عَن ማለት "ስለ"about" ማለት ሲሆን በወቅቱ አይሁዳውያን "ስለ" ዙል-ቀርነይን ነቢያችንን"ﷺ" ጠይቀዋል፦
"አል-ዋሒድይ አሥባቡ አን-ኑዙል 18፥83 *"የላቀው አሏህ ንግግር፦ "ስለ ዙል-ቀርነይንም ይጠይቁካል" ስለሚለው አንቀጽ ቀታዳህ እንዲህ አለ፦ "አይሁዳውያን ነቢዩን"ﷺ" ስለ
ዙል-ቀርነይን ሲጠይቁ የላቀው አሏህ ይህቺን አንቀጽ አወረደ"*።
قوله تعالى: {وَيَسْأَلُونَكَ عَن ذِي ٱلْقَرْنَيْنِ} الآية.
قال قتادة: إن اليهود سألوا النبي صلى الله عليه وسلم عن ذي القرنين، فأنزل الله تعالى هذه الآيات.

አይሁዳውያን ጥያቄውን ያነሱት ከራሳቸው ዳራ ተነስተው ነው፥ በራሳቸው ዳራ በዳንኤል ላይ "ሉው ቀራናዪም" לֹ֣ו קְרָנָ֑יִם ማለትም "ባለ ሁለት ቀንዶች" የሚባል ንጉሥ ስላለ ነው፦
ዳንኤል 8፥3 ዓይኔን አንሥቼ አየሁ፥ እነሆም *"ሁለት ቀንዶች የነበሩት" አንድ አውራ በግ በወንዙ ፊት ቆሞ ነበር"*። ואשא עיני ואראה והנה איל אחד עמד לפני האבל ולו קרנים והקרנים גבהות והאחת גבהה מן השנית והגבהה עלה באחרנה׃

የዳንኤል ትንቢት ዐውደ-ንባቡ ላይ ሁለቱ ቀንዶች የተባሉት ሁለቱ የሜዶን እና የፋርስ መንግሥታት መሆናቸው ታውቋል፦
ዳንኤል 8፥20 *"ባየኸው በአውራው በግ ላይ የነበሩ ሁለቱ ቀንዶች "እነርሱ የሜዶን እና የፋርስ ነገሥታት" ናቸው"*። האיל אשר־ראית בעל הקרנים מלכי מדי ופרס׃

ይህ ባለ ሁለት ቀንዶች መንግሥት ወደ ምዕራብ ወደ ሰሜንም ወደ ደቡብም በቀንዱ ሲጐሽም ነበር፥ አራዊት ማለትም መንግሥታት ሁሉ ይቋቋሙት ዘንድ አልቻሉም፦
ዳንኤል 8፥4 *"አውራውም በግ ወደ ምዕራብ ወደ ሰሜንም ወደ ደቡብም በቀንዱ ሲጐሽም አየሁ፤ አራዊትም ሁሉ ይቋቋሙት ዘንድ አልቻሉም፥ ከእጁም የሚያድን አልነበረም፤ እንደ ፈቃዱም አደረገ፥ ራሱንም ታላቅ አደረገ"*።

አይሁዳውያን ስለ ዙል-ቀርነይን ለጠየቁት ጥያቄ አምላካችን አሏህም፦ "በእናንተ ላይ ከእርሱ ወሬን አነባለሁ"በል!" ብሏል፥ አሏህ "ዐን-ሁ" عَنهُ ማለትም "ስለ እርሱ" ሳይሆን "ሚን-ሁ" مِّنْهُ ማለትም "ከ-እርሱ" በማለት ትርክቱን ይጀምራል። "ከ-እርሱ" ማለት ትርክቱ በከፊል መሆኑን ቁልጭ አርጎ ያሳያል፥ "ወሬ" ተብሎ የተቀመጠው ቃል "ዚክራ" ذِكْرًا ሲሆን ነቢያችን"ﷺ" ከ-እርሱ "ማስታወሻ" የሚያነቡት ከአሏህ የሚወርድላቸው “ገይቡል ማዲ” غَيْب الْمَاضِي ማለትም “ያለፈ ሩቅ ነገር” ነው። አምላካችን አሏህ ለዙል-ቀርነይን በምድር ላይ በማመቻተት ከነገሩም ሁሉ መዳረሻ መንገድን ሰጠው፦
18፥84 *"እኛ ለእርሱ በምድር አስመቸነው፡፡ ከነገሩም ሁሉ መዳረሻ መንገድን ሰጠነው"*፡፡ إِنَّا مَكَّنَّا لَهُ فِي الْأَرْضِ وَآتَيْنَاهُ مِن كُلِّ شَيْءٍ سَبَبًا
ወደ ፀሐይ መጥለቂያ ወደ ምዕራብ ሲደርስ አምላካችን አሏህ፦ "ዙል-ቀርነይን ሆይ! ወይም በመግደል ትቀጣለህ ወይም በእነርሱ መልካም ነገርን መማረክን ትሠራለህ" አለው፥ እርሱም፦ "የበደለውን ሰውማ ወደፊት እንቀጣዋለን፥ ከዚያም ወደ ጌታው ይመለሳል፡፡ ብርቱንም ቅጣት ይቀጣዋል" አለ፦
18፥86 *ወደ ፀሐይ መግቢያም በደረሰ ጊዜ ጥቁር ጭቃ ባላት ምንጭ ውስጥ ስትጠልቅ አገኛት፥ ባጠገቧም ሕዝቦችን አገኘ፡፡ «ዙል-ቀርነይን ሆይ! ወይም በመግደል ትቀጣለህ ወይም በእነርሱ መልካም ነገርን መማረክን ትሠራለህ» አልነው"*። حَتَّىٰ إِذَا بَلَغَ مَغْرِبَ الشَّمْسِ وَجَدَهَا تَغْرُبُ فِي عَيْنٍ حَمِئَةٍ وَوَجَدَ عِندَهَا قَوْمًا ۗ قُلْنَا يَا ذَا الْقَرْنَيْنِ إِمَّا أَن تُعَذِّبَ وَإِمَّا أَن تَتَّخِذَ فِيهِمْ حُسْنًا
18፥87 *«የበደለውን ሰውማ ወደፊት እንቀጣዋለን፥ ከዚያም ወደ ጌታው ይመለሳል፡፡ ብርቱንም ቅጣት ይቀጣዋል» አለ"*፡፡ قَالَ أَمَّا مَن ظَلَمَ فَسَوْفَ نُعَذِّبُهُ ثُمَّ يُرَدُّ إِلَىٰ رَبِّهِ فَيُعَذِّبُهُ عَذَابًا نُّكْرًا

አሏህ ለዙል-ቀርነይን፦ "በመግደል ትቀጣለህ" ሲለው ዙል-ቀርነይን ደግሞ አንድ ማንነት ሆኖ ሳለ በግነት እኛነት፦ "እንቀጣዋለን" ብሎ ተናገረ፥ ዙልቀርነይን የበደለን ሰው ወደፊት በዱንያህ ከቀጣው በኃላ በአኺራ ወደ አሏህ ሲመለስ ደግሞ አሏህ ብርቱ ቅጣት ይቀጣዋል። በተቃራኒው ያመነም ሰውማ መልካምንም ሥራ የሠራ ለእርሱ ከምንዳ በኩል መልካሚቱ ገነት አለችው፥ ለዚህ ሰው ዙል-ቀርነይን ቀላል ሥራ እንዲሠራ ያዘዋል፦
18፥88 *«ያመነም ሰውማ መልካምንም ሥራ የሠራ ለእርሱ ከምንዳ በኩል መልካሚቱ ገነት አለችው፡፡ ለእርሱም ከትእዛዛችን ገርን ነገር እናዘዋለን» አለ"*፡፡ وَأَمَّا مَنْ آمَنَ وَعَمِلَ صَالِحًا فَلَهُ جَزَاءً الْحُسْنَىٰ ۖ وَسَنَقُولُ لَهُ مِنْ أَمْرِنَا يُسْرًا

አሁንም ዙል-ቀርነይን አንድ ማንነት ሆኖ ሳለ በግነት እኛነት፦ "ከትእዛዛችን" "እናዘዋለን" ማለቱን ልብ በል! ከዚያ መንገዱን ወደ ፀሐይ መውጫ ወደ ምስራቅ ቀጥሎ ወደ ሰሜን ሲጓዝ በሁለቱ ጋራዎችም መካከል በደረሰ ጊዜ በአቅራቢያቸው ንግግርን ለማወቅ የማይቃረቡ ሕዝቦችን አገኘ፥ እነርሱም፦ "ዙል-ቀርነይን ሆይ! የእጁጅ እና መእጁጅ በምድር ላይ አበላሺዎች ናቸውና በእኛ እና በእነርሱ መካከል ግድብን ታደርግልን ዘንድ ግብርን እናድርግልህን?" አሉ፦
18፥93 *"በሁለቱ ጋራዎችም መካከል በደረሰ ጊዜ በአቅራቢያቸው ንግግርን ለማወቅ የማይቃረቡ ሕዝቦችን አገኘ"*፡፡ حَتَّىٰ إِذَا بَلَغَ بَيْنَ السَّدَّيْنِ وَجَدَ مِن دُونِهِمَا قَوْمًا لَّا يَكَادُونَ يَفْقَهُونَ قَوْلًا
18፥94 *«ዙል-ቀርነይን ሆይ! የእጁጅና መእጁጅ በምድር ላይ አበላሺዎች ናቸውና በእኛ እና በእነርሱ መካከል ግድብን ታደርግልን ዘንድ ግብርን እናድርግልህን?» አሉ"*፡፡ قَالُوا يَا ذَا الْقَرْنَيْنِ إِنَّ يَأْجُوجَ وَمَأْجُوجَ مُفْسِدُونَ فِي الْأَرْضِ فَهَلْ نَجْعَلُ لَكَ خَرْجًا عَلَىٰ أَن تَجْعَلَ بَيْنَنَا وَبَيْنَهُمْ سَدًّا

እርሱም፦ "ጌታዬ በእርሱ ያስመቸኝ ሀብት ከእናንተ ግብር በላጭ ነው፥ ስለዚህ በጉልበት እገዙኝ፣ በእናንተ እና በእነርሱ መካከል ብርቱን ግድብ አደርጋለሁና የብረትን ታላላቅ ቁራጮች ስጡኝ፣ አናፉ፣ የቀለጠውን ነሐስ ስጡኝ በእርሱ ላይ አፈስበታለሁና" አላቸው፦
18፥95 *አለ «ጌታዬ በእርሱ ያስመቸኝ ሀብት ከእናንተ ግብር በላጭ ነው፥ ስለዚህ በጉልበት እገዙኝ! በእናንተ እና በእነርሱ መካከል ብርቱን ግድብ አደርጋለሁና"*፡፡ قَالَ مَا مَكَّنِّي فِيهِ رَبِّي خَيْرٌ فَأَعِينُونِي بِقُوَّةٍ أَجْعَلْ بَيْنَكُمْ وَبَيْنَهُمْ رَدْمًا
18፥96 *«የብረትን ታላላቅ ቁራጮች ስጡኝ» አላቸው፡፡ በሁለቱ ኮረብታዎች መካከልም ባስተካከለ ጊዜ አናፉ አላቸው፡፡ ብረቱን እሳትም ባደረገው ጊዜ «የቀለጠውን ነሐስ ስጡኝ፤ በእርሱ ላይ አፈስበታለሁና» አላቸው*፡፡ آتُونِي زُبَرَ الْحَدِيدِ ۖ حَتَّىٰ إِذَا سَاوَىٰ بَيْنَ الصَّدَفَيْنِ قَالَ انفُخُوا ۖ حَتَّىٰ إِذَا جَعَلَهُ نَارًا قَالَ آتُونِي أُفْرِغْ عَلَيْهِ قِطْرًا

ዙል-ቀርነይን የእጁጅ እና መእጁጅን በሁለቱ ኮረብታዎች መካከል በብረትና በነሐስ ግድብ ዘግቶባቸዋል፥ ይህ ቦታ እራሱ ከሰው እይታ መሰወሩ በራሱ ገይብ ነው። የአሏህ ቀጠሮ ሲመጣ ግድቡ ትክክለኛ ሜዳ ይሆንና የእጁጅ እና መእጁጅ ከየተረተሩ የሚንደረደሩ ሆነው ይወጣሉ፦
18፥97 *"የእጁጅ እና መእጁጅ ሊወጡትም አልቻሉም፥ ለእርሱ መሸንቆርንም አልቻሉም"*፡፡ فَمَا اسْطَاعُوا أَن يَظْهَرُوهُ وَمَا اسْتَطَاعُوا لَهُ نَقْبًا
18፥98 *"«ይህ ግድብ ከጌታዬ ችሮታ ነው፡፡ የጌታየም ቀጠሮ በመጣ ጊዜ ትክክል ምድር ያደርገዋል፡፡ የጌታዬም ቀጠሮ ተረጋገጠ ነው» አለ"*፡፡ قَالَ هَـٰذَا رَحْمَةٌ مِّن رَّبِّي ۖ فَإِذَا جَاءَ وَعْدُ رَبِّي جَعَلَهُ دَكَّاءَ ۖ وَكَانَ وَعْدُ رَبِّي حَقًّا
21፥96 *"የእጁጅ እና መእጁጅም እነርሱ ከየተረተሩ የሚንደረደሩ ሲኾኑ ግድባቸው በተከፈተች ጊዜ"*። حَتَّىٰ إِذَا فُتِحَتْ يَأْجُوجُ وَمَأْجُوجُ وَهُم مِّن كُلِّ حَدَبٍ يَنسِلُونَ

አምላካችን አሏህ ስለ ዙል-ቀርነይን የነገረን አስፈላጊ የሆኑትን በከፊል ብቻ ነው፥ እኛም "ኢሥራኢሊያህ" إِسْرَائِيلِيَّة የሆነ ተጓዳኝ መልእክት ጠቅሰን እና አጣቅሰን አቅርበናል። "ኢሥራኢሊያት" إِسْرَائِيلِيَّات የሆኑ ተጓዳኝ መልእክት ጠቅሰን እና አጣቅሰን በእማኝነትና በአስረጂነት ማቅረብ ሐራም አይደለም፦
ሡነን አቢ ዳውድ መጽሐፍ 26, ሐዲስ 22
አቢ ሁረይራህ እንደተረከው፦ "የአሏህ መልእክተኛም"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ *"ከበኒ ኢሥራኢል ተጓዳኝ ነገር ተናገሩ! ያንን ማድረጉ ሐራም አይደለም"*። عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ، قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم ‏ "‏ حَدِّثُوا عَنْ بَنِي إِسْرَائِيلَ وَلاَ حَرَجَ ‏"‏ ‏

ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም