ወሒድ የዕቅበተ ኢሥላም መጣጥፍት"Wahid Articles of Islamic Apologetics"
58.3K subscribers
68 photos
69 videos
19 files
1.72K links
ዳዒ ወሒድ በኢሥላም እና በክርስትና መካከል ያለውን ልዩነት እና አንድነት በንጽጽር የሚያስቀምጥ ወንድም ነው። ለዚህም የቋንቋ፣ የሰዋስው፣ የዐውድ፣ የተዛማች እና የሥነ አመክንዮ ሙግት በማቅረብ የሚታወቅ ተሟጋች እና ጦማሪ ነው። ለሙግቱ ነጥብ በዋነኝነት የሚጠቀምባቸው ቋንቋ ዐማርኛ፣ ግዕዝ፣ እንግሊዝኛ፣ ዐረቢኛ፣ ዕብራይስጥ እና ግሪክ ናቸው። መልካም የንባብ፣ የጥናት፣ የማነጻጸር ጊዜ ይሁንልዎ!
Download Telegram
"ብጤ" ለሚለው የገባው ቃል "ኩፉው" كُفُو ሲሆን "አቻ" "እኩያ" "ወደር" ማለት ነው፥ ለአሏህ አንድም "አቻ" "እኩያ" "ወደር" የለውም። "አንድም" ለሚለው ለሚለው የገባው ቃል "አሐድ" أَحَدٌ ሲሆን "ሸኽስ" شَخْص በሚል የመጣ ነው፦
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 67, ሐዲስ 153
ዐብደሏህ እንደተረከው፦ "ነቢዩም"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ " "ከአላህ የበለጠ የሚቀና "አንድም" የለም"። عَنْ عَبْدِ اللَّهِ، عَنِ النَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم قَالَ ‏ "‏ مَا مِنْ أَحَدٍ أَغْيَرُ مِنَ اللَّهِ،
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 97, ሐዲስ 44
ዐብዱል ማሊክ እንደተናገረው፦ "ከአላህ የበለጠ የሚቀና "ማንነት" የለም። عَنْ عَبْدِ الْمَلِكِ ‏"‏ لاَ شَخْصَ أَغْيَرُ مِنَ اللَّهِ ‏"‌‏.‏

"አንድ" ለሚለው የገባው ቃል "አሐድ" أَحَدٌ ሲሆን "ማንነት" ለሚለው የገባው ቃል "ሸኽስ" شَخْص ነው፥ ስለዚህ አሏህ በማንነቱ አንድ ነው። ባል በሚስቱ እንዲሁ ንጉሥ በመንግሥቱ እንደሚቀና የፈጠረን አንድ አምላክ በአምልኮቱ ይቀናል፦
ዘጸአት 20፥6 እኔ ያህዌህ አምላክህ ቀናተኛ አምላክ ነኝና።

ገለቴ ከመንጨርጨር እና ከመንተክተክ ይልቅ መቅናት አውታዊ እንደሆነ ከራስህ መጽሐፍ ተረዳ! ስለዚህ አሏህ በአምልኮቱ መቅናቱ ላይ እርር እና ምርር አትበል። አሏህ፦ "ቁል" قُلْ በሚል ትእዛዛዊ ግሥ በአምልኮው አንድንም ማንነት እንዳናጋራ በአጽንዖት እና በአንክሮት ነግሮናል፦
18፥110 "በጌታውም አምልኮ አንድንም አያጋራ"። وَلَا يُشْرِكْ بِعِبَادَةِ رَبِّهِ أَحَدًا

"አንድንም" ሲል በአሏህ አምልኮ "አንድንም ማንነት" ማጋራት እንደሌለብን ያሳያል፥ አምልኮ የአሏህ ሐቅ እና ገንዘብ ብቻ ነው።
ተወዳጁ ነቢያች"ﷺ" አንድ ማንነት ስለነበሩ በቁርኣን "አሐድ" በሐዲስ "ሸኽስ" شَخْص ተብለዋል፦
54፥24 «ከእኛ የኾነን "አንድን" ሰው እንከተለዋለን? እኛ ያን ጊዜ በስህተትና በዕብደት ውስጥ ነን» አሉ፡፡ فَقَالُوا أَبَشَرًا مِّنَّا وَاحِدًا نَّتَّبِعُهُ إِنَّا إِذًا لَّفِي ضَلَالٍ وَسُعُرٍ
ጃምዒ አት-ቲርሚዚይ መጽሐፍ 43, ሐዲስ 24
አነሥ እንደተረከው፦ "በእነርሱ ዘንድ ከአሏህ መልእክተኛ"ﷺ" የበለጠ ተወዳጅ "ማንነት" አልነበረም"። عَنْ أَنَسٍ، قَالَ لَمْ يَكُنْ شَخْصٌ أَحَبَّ إِلَيْهِمْ مِنْ رَسُولِ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم

መቼም ነቢያች"ﷺ" አንድ ማንነት ብቻ ነበሩ እንጂ ሥላሴ አልነበሩም። ሌላው ተሰምሮ ሊጤንበት የሚገባው ነጥብ "አለዚ" اَلَّذِي ኢሥሙል መውሱል ሲሆን ሙፍረድ ለሆነ ማንነት የምንጠቀምበት ነው፥ ከአንድ በላይ ለሆኑ ማንነቶች የምንጠቀምበት በሙሰና "አለዘይኒ" اَللَّذَيْنِ በጀምዕ "አለዚነ" اَلَّذِينَ ነው። አሏህ አንድ ማንነት ስለሆነ "አለዚ" اَلَّذِي ብቻ ተብሏል፦
7፥54 ጌታችሁ "ያ" ሰማያትን እና ምድርን በስድስት ቀኖች ውስጥ የፈጠረ አላህ ነው፡፡ إِنَّ رَبَّكُمُ اللَّهُ الَّذِي خَلَقَ السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضَ فِي سِتَّةِ أَيَّامٍ

"ያ" ለሚለው አንጻራዊ ተውላጠ ስም የገባው "አለዚ" اَلَّذِي እንደሆነ አስምርበት! ይህንን የሰዋስው ሙግት አፍጦና አፋጦ፤ አግጦና አንጋጦ ስታነቡ ቆሌ ተገፎ እና ቆሽት አሮ፦ "ሰማይ ተንዶ ሊናጫነኝ ነው፥ ምድር ተከፍቶ ሊውጠኝ ነው" ከምትሉ አውንታዊ መረዳት ይዛችሁ ልባችሁን ብትከፍቱ መልካም ነው። አምላካችን አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይስጠን! አሚን።

ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
ኢፍጣር

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ፥ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

33፥35 "ጦመኛ ወንዶች እና ጦመኛ ሴቶችም፣ ብልቶቻቸውን ጠባቂዎች ወንዶች እና ጠባቂ ሴቶችም፣ አላህን በብዙ አውሺዎች ወንዶች እና አውሺዎች ሴቶችም አላህ ለእነርሱ ምሕረትን እና ታላቅን ምንዳ አዘጋጅቶላቸዋል"፡፡ وَالصَّائِمِينَ وَالصَّائِمَاتِ وَالْحَافِظِينَ فُرُوجَهُمْ وَالْحَافِظَاتِ وَالذَّاكِرِينَ اللَّهَ كَثِيرًا وَالذَّاكِرَاتِ أَعَدَّ اللَّهُ لَهُم مَّغْفِرَةً وَأَجْرًا عَظِيمًا

“ፊጥር” فِطْر የሚለው ቃል "ፈጦረ" فَطَرَ ማለትም "ገደፈ" ከሚል ሥርወ ቃል የመጣ ሲሆን “ጦም መግደፊያ" ማለት ነው፥ የፊጥር ብዙ ቁጥር ደግሞ “ፉጡር” فُطُور ነው። ለምሳሌ፦ የረመዷን ጦም ማብቂያ በዓል እራሱ "ዒዱል ፊጥር" عِيدُ ٱلْفِطْر ይባላል፥ "ዘካቱል ፊጥር" زَكَاة الفِطْر ደግሞ ለመሣኪን በዒዱል ፊጥር ቀን ለማስፈጠሪያነት የሚውል ገንዘብ ነው። በተመሳሳይ “ኢፍጣር” إِفْطَار የሚለው ቃል "አፍጦረ" أَفْطَرَ ማለትም "አፈጠረ" ከሚል ሥርወ ቃል የመጣ ሲሆን “ጦም መግደፍ" ማለት ነው፥ ጦመኛን ያስፈጠረ ጦመኛው ከሚያገኘውን ምንዳ ምንም ሳይቀነስ ጦመኛው ሊያገኘው የሚችለውን ምንዳ ያገኛል፦
ሡነን ኢብኑ ማጃህ መጽሐፍ 7, ሐዲስ 109
ዘይድ ኢብኑ ኻሊድ አል ጁሀኒይ እንደተረከው፦ የአሏህ መልእክተኛ"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "ጦመኛን ያስፈጠረ ጦመኛው ከሚያገኘውን ምንዳ ምንም ሳይቀነስ ጦመኛው ሊያገኘው የሚችለውን ምንዳ ያገኛል"። عَنْ زَيْدِ بْنِ خَالِدٍ الْجُهَنِيِّ، قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ ـ صلى الله عليه وسلم ـ ‏ "‏ مَنْ فَطَّرَ صَائِمًا كَانَ لَهُ مِثْلُ أَجْرِهِمْ مِنْ غَيْرِ أَنْ يَنْقُصَ مِنْ أُجُورِهِمْ شَيْئًا ‏"‏ ‏.‏

አደባባይ ላይ እዩልኝ እና ስሙልኝ በማለት ከመበሻሸቅ፣ ከመነታረክ፣ እልህ ከመገባባት፣ ከመፎካከር ይልቅ ከወለጋ ተፈናቅለው ደብረ ብርሃን በካምፕ ውስጥ ያሉትን የወሎ ሙሥሊሞችን ማስፈጠር አንርሳ! እነዚህ ተፈናቃዮች ዱንያህ ላይ ተስፋ ቆርጠው አኺራቸውን በመጠባበቅ ላይ በሞት እና በሕይወት መካከል ያሉ የሊላሂ ወንድሞቻችን እና እኅቶቻችን ናቸው። እውነት ለአሏህ ከተባለ እነዚህን ስደተኞች ባለን አቅም መጎብኘቱ እውነተኛ አጅር አለው። አሏህ ይቀበላችሁ!

አምላካችን አሏህ ጦመኛ ወንድ ባሪያውን "ሷኢም" صَّائِم ሲለው ጦመኛ ሴት ባሪያውን ደግሞ "ሷኢማህ" صَّائِمَة ይላታል፥ ለእነርሱ ምሕረትን እና ታላቅን ምንዳ አዘጋጅቶላቸዋል፦
33፥35 "ጦመኛ ወንዶች እና ጦመኛ ሴቶችም፣ ብልቶቻቸውን ጠባቂዎች ወንዶች እና ጠባቂ ሴቶችም፣ አላህን በብዙ አውሺዎች ወንዶች እና አውሺዎች ሴቶችም አላህ ለእነርሱ ምሕረትን እና ታላቅን ምንዳ አዘጋጅቶላቸዋል"፡፡ وَالصَّائِمِينَ وَالصَّائِمَاتِ وَالْحَافِظِينَ فُرُوجَهُمْ وَالْحَافِظَاتِ وَالذَّاكِرِينَ اللَّهَ كَثِيرًا وَالذَّاكِرَاتِ أَعَدَّ اللَّهُ لَهُم مَّغْفِرَةً وَأَجْرًا عَظِيمًا

አሏህ "ሷኢሚን" صَّآئِمِين እና "ሷኢማት" صَّآئِمَٰت ከሚላቸው ባሮቹ ያድርገን! አሚን።

ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
የዘካህ አወጣጥ

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ፥ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።

2፥110 ሶላትንም አስተካክላችሁ ስገዱ፡፡ ዘካንም ስጡ፡፡ وَأَقِيمُوا الصَّلَاةَ وَآتُوا الزَّكَاةَ

የዘካ ገንዘብ ከተቀማጭ ላይ ከመቶ 2.5 % የሚሰጥ ነው፥ ነቢያችን”ﷺ” ከሁለት መቶ ዲርሀም 5 ዘካህ እንደሚወጣ ተናግረዋል። ያ ማለት የዘካህ ሒሳብ በመቶ ዲርሀም 2.5 ይሆናል፥ ስሌቱ 5፥2=2.5 ነው፦
ሡነን አቢ ዳውድ መጽሐፍ 9, ሐዲስ 18 ዐሊይ”ረ.ዐ” እንደተረከው፦ “ነቢዩም”ﷺ” እንዲህ አሉ፦ ”ሁለት መቶ ዲርሀም ለአንተ በሆነች ጊዜና ዓመት ከሞላች አምስት ደራሂም ይወጣል፥ በአንተ ምንም ነገር አይሆንም ሃያ ዲናር እስኪሆን ድረስ”። عَنْ عَلِيٍّ، – رضى الله عنه – عَنِ النَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم بِبَعْضِ أَوَّلِ هَذَا الْحَدِيثِ قَالَ ‏”‏ فَإِذَا كَانَتْ لَكَ مِائَتَا دِرْهَمٍ وَحَالَ عَلَيْهَا الْحَوْلُ فَفِيهَا خَمْسَةُ دَرَاهِمَ وَلَيْسَ عَلَيْكَ شَىْءٌ – يَعْنِي فِي الذَّهَبِ – حَتَّى يَكُونَ لَكَ عِشْرُونَ دِينَارًا

በዚህ ሐዲስ መሠረት የአንድ ሰው ካፒታል 20 ዲናር ወይም 200 ዲርሀም ሲሆን ዘካህ ይወጅበታል። በሸሪዓህ የዘካህ አነስተኛ የክፍያ መጠን “ኒሷብ” نِصاب ይባላል፥ ይህም ኒሷብ የሚለካው 20 ዲናር ወይም 200 ዲርሀም ሲሆን ነው። “ዲናር” دِينَار‎ ማለት “የወርቅ ሳንቲም”gold coin” ማለት ሲሆን “ዲርሀም” دِرْهَم‎ ማለት ደግሞ “የብር ሳንቲም”silver coin” ማለት ነው። ይህ በጥንት ጊዜ የሸቀጥ ገንዘብ”commodity money” ነው። “ዲናር” እና “ዲርሀም” የሚለኩት በሚስቃል ነው፥ “ሚስቃል” مِثْقَال የሚለው ቃል “ሰቀለ” ثَقَلَ ማለትም “ከበደ” ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን “ክብደት” ማለት ነው።
1 ሚስቃል ወርቅ 4.25 ግራም ነው፥ 20 ሚስቃል ወርቅ ደግሞ 4,25x 20 = 85 ግራም ወርቅ ይሆናል ማለት ነው።
1 ሚስቃል ብር 2.975 ግራም ነው፥ 200 ሚስቃል ብር ደግሞ 2.975x 200= 595 ግራም ብር ይሆናል ማለት ነው።

በዘካህ ላይ የሚወጅበው ኒሷብ 85 ግራም ወርቅ ወይም 595 ግራም ብር ነው።
አንድ ሙሥሊም ያስቀመጠው ካፒታል ዓመት ከሞላው እና ያም ካፒታል 85 ግራም ወርቅ ወይም 595 ግራም ብር ያክል ከሆነ ዘካህ ማውጣት ግዴታው ነው።
ዘካቱል ማል የሚወጣበት አነስተኛ ዋጋ የብር ኒሷብ ስለሆነ አብላጫው ምሁራን የብር ኒሷብን መሠረት ባደረገ መልኩ ከዚያ እንዲወጣ ፈትዋ ሰተዋል፥ ስለዚህ አንድ ሰው ዓመት የተቀመጠ 89,250 ብር(ገንዘብ) እና ከዛ በላይ ካለው ዘካህ ማውጣት ግዴታ አለበት።

እንዴት? ካላችሁ የብር ኒሷብ ወደ ወረቀት ገንዘብ”Fiat money” ለመቀየር ብርን ዛሬ ባለው የወቅቱ ግብይት ለናሙና ያክል መሥራት ይቻላል። በኢትዮጵያ አንድ ግራም ብር"silver" አሁን ባለኝ መረጃ 150 ብር"ገንዘብ" ነው፥ ስናሰላው 150×595= 89,250 ብር(ገንዘብ) ይሆናል።
ለምሳሌ፦ እኔ 100 ሺህ ብር ቢኖረኝ ከ 100 ሺህ ብር ላይ 2.5 % ዘካህ ሲሰላ 2,500 ይወጅብብኛል፥ ስናሰላው 100,000×2.5፥100= 2,500 ይሆናል።
ዘካህን መስጠት አንርሳ፦
2፥110 ሶላትንም አስተካክላችሁ ስገዱ፡፡ ዘካንም ስጡ፡፡ وَأَقِيمُوا الصَّلَاةَ وَآتُوا الزَّكَاةَ

አምላካችን አሏህ ዘካን ከሚሰጡ ባሮቹ ያድርገን! አሚን።

ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
የሰው ሸይጧን

በነገራችን ላይ በረመዷን ኩፋሩል ጂን የሆኑ ሸይጧናት ይታሰራሉ።
ቅሉ ግን የማይታሰሩ የሰው ሸይጧናት አሉ፥ "ሸይጧን" شَّيْطَان የሚለው ቃል “ሸጠነ” شَّطَنَ ማለትም “ራቀ” ወይም “ተገለለ” ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን ከአሏህ ራሕመት “የተገለለ” ወይም “የራቀ” ማለት ነው፥ ሸያጢን ከአሏህ ራሕመት የራቁ ከጂንም ከሰውም ሊሆኑ ይችላል፦
6፥112 እንደዚሁም ለነቢያት ሁሉ ከሰው እና ከጂን የኾኑን ሰይጣናት ጠላት አደረግን፡፡ وَكَذَٰلِكَ جَعَلْنَا لِكُلِّ نَبِيٍّ عَدُوًّا شَيَاطِينَ الْإِنسِ وَالْجِن
114፥6 «ከጂኒዎችም ከሰዎችም ሰይጣናት እጠበቃለሁ» በል። مِنَ الْجِنَّةِ وَالنَّاسِ
23፥97 በልም «ጌታዬ ሆ! ከሰይጣናት ጉትተጎታዎች በአንተ እጠበቃለሁ» ፡፡ وَقُل رَّبِّ أَعُوذُ بِكَ مِنْ هَمَزَاتِ الشَّيَاطِينِ

እነርሱ ስላልታሠሩ ኢሥቲዓዛህ ማድረግ ግድ ይላል። በረመዷኑ በተለይ በዚህ አሥር ቀናት ውስጥ ሥራዬ ብለው ሰው እና ሰውን በማሰዳደብ እና በማጋጨት የሚያዞላልሙ በሥራቸው ኢብሊሥ የሚቀናባቸው ይመስለኛል። ላይክ እና ኮሜንት ለመሰብሰብ የግድ ሰውን ማጋጨት እኩይ ተግባር ነውና እንታቀብ!
አሏህ ሁላችንንም ያስተካክለን! አሚን።
በነገራችን ላይ እኛ ኢትዮጵያውያን አሳባችንን በቅንነት ከማንሸራሸር እና የሌላውን አሳብ በነጻነት ከመስማት ይልቅ ስድብ ይቀናናል። ቀጣይ ትውልድ ከእኛ ምን እንደሚማር አሏህ ይሁነን። በዚሁ ከቀጠልን መጠፋፋታችን ነው።
በተሳዳቢዎች ጦስ ሙሥሊሙን አንዱ የጽንፍ ክንፍ በዘሩ ይገለዋል፥ ሌላው የጽንፍ ክንፍ በሃይማኖቱ ይገለዋል።
አሏህ ይድረስልን! በዳዮችን የእጃቸው ይስጣቸው።
ይጋጫልን?

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

4፥82 ቁርኣንን አያስተነትኑምን? ከአላህ ሌላ ዘንድ በነበረ ኖሮ በእርሱ ውስጥ ብዙን መለያየት ባገኙ ነበር፡፡ أَفَلَا يَتَدَبَّرُونَ الْقُرْآنَ ۚ وَلَوْ كَانَ مِنْ عِندِ غَيْرِ اللَّهِ لَوَجَدُوا فِيهِ اخْتِلَافًا كَثِيرًا

ጥያቄ፦
"አሏህ መልእክተኞች እኩል አድርጓል ወይስ አላደረገም?
A. እኩል አድርጓል፦
2፥285 "ከመልእክተኞቹ በአንድም መካከል አንለይም" لَا نُفَرِّقُ بَيْنَ أَحَدٍ مِّن رُّسُلِهِ

B. እኩል አላደረገም፦
2፥253 "እነዚህን መልእክተኞች ከፊላቸውን በከፊሉ ላይ አበለጥን"፡፡ تِلْكَ الرُّسُلُ فَضَّلْنَا بَعْضَهُمْ عَلَىٰ بَعْضٍ

መልስ፦
ለአይሁዳውያን፦ «አላህም ባወረደው ሁሉ እመኑ» በተባሉ ጊዜ «በእኛ ላይ በተወረደው ብቻ እናምናለን» ይላሉ፥ "በእኛ ላይ በተወረደው" ለሚሉት ለነቢያት ወሕይ አረጋጋጭ የሆነው ቁርኣን በመካድ በከፊሉ በማመን እና በከፊሉ በመካድ አስተባብለዋል፦
2፥91 ለእነርሱ «አላህም ባወረደው ሁሉ እመኑ» በተባሉ ጊዜ «በእኛ ላይ በተወረደው ብቻ እናምናለን» ይላሉ፥ ከእርሱ በኋላ ያለው እርሱ ከእነርሱ ጋር ላለው አረጋጋጭ እውተኛ ሲኾን ይክዳሉ፡፡ وَإِذَا قِيلَ لَهُمْ آمِنُوا بِمَا أَنزَلَ اللَّهُ قَالُوا نُؤْمِنُ بِمَا أُنزِلَ عَلَيْنَا وَيَكْفُرُونَ بِمَا وَرَاءَهُ وَهُوَ الْحَقُّ مُصَدِّقًا لِّمَا مَعَهُمْ

አምላካችን አሏህ ተወዳጁ ነቢያችንን "ቁል" قُلْ በሚል ትእዛዛዊ ግሥ በእርሳቸው ላይ በተወረደው ቁርኣን እና ከእርሳቸው በፊት በነበሩት ነቢያት ላይ በተወረደው ወሕይ "አመንን" እንዲሉ አዟል፦
3፥84 በል፦ "በአላህ እና በእኛ ላይ በተወረደው አመንን" قُلْ آمَنَّا بِاللَّهِ وَمَا أُنزِلَ عَلَيْنَا
3፥84 "በኢብራሂም፣ በኢስማዒል፣ በኢስሓቅ፣ በያዕቆብ፣ በነገዶችም ላይ በተወረደው፣ ለሙሳሣ እና ለዒሣ በተሰጡት፣ በዚያም ለነቢያት ሁሉ ከጌታቸው በተሰጠው አመንን"። وَمَا أُنزِلَ عَلَىٰ إِبْرَاهِيمَ وَإِسْمَاعِيلَ وَإِسْحَاقَ وَيَعْقُوبَ وَالْأَسْبَاطِ وَمَا أُوتِيَ مُوسَىٰ وَعِيسَىٰ وَالنَّبِيُّونَ مِن رَّبِّهِمْ

አምላካችን አሏህ ለዚያ ነው፦ "መልእክተኛው ከጌታው ወደ እርሱ በተወረደው አመነ" በማለት የነገረን፦
2፥285 መልእክተኛው ከጌታው ወደ እርሱ በተወረደው አመነ፡፡ آمَنَ الرَّسُولُ بِمَا أُنزِلَ إِلَيْهِ مِن رَّبِّهِ

ሌላ አንቀጽ ላይ ደግሞ አምላካችን አሏህ የተወዳጁ ነቢያችን ተከታዮች ምእመናን "ቁሉ" قُولُوا በሚል ትእዛዛዊ ግሥ በእነርሱ ላይ በተወረደው ቁርኣን እና ከእርሳቸው በፊት በነበሩት ነቢያት ላይ በተወረደው ወሕይ "አመንን" እንዲሉ አዟል፦
2፥136 በሉ፦ "በአላህ እና ወደ እኛ በተወረደው አመንን" قُولُوا آمَنَّا بِاللَّهِ وَمَا أُنزِلَ إِلَيْنَا
2፥136 ወደ ኢብራሂም፣ ወደ ኢስማዒል፣ ወደ ኢስሐቅ፣ ወደ ያዕቁብ እና ወደ ነገዶቹም በተወረደው፣ በዚያም ለሙሣ እና ለዒሣ በተሰጡት፣ በዚያም ለነቢያት ሁሉ ከጌታቸው በተሰጡት አመንን"። وَمَا أُنزِلَ إِلَىٰ إِبْرَاهِيمَ وَإِسْمَاعِيلَ وَإِسْحَاقَ وَيَعْقُوبَ وَالْأَسْبَاطِ وَمَا أُوتِيَ مُوسَىٰ وَعِيسَىٰ وَمَا أُوتِيَ النَّبِيُّونَ مِن رَّبِّهِمْ

አምላካችን አሏህ ለዚያ ነው፦ "ምእመናን እንደዚሁ አመኑ" በማለት የነገረን፦
2፥285 ምእመናን እንደዚሁ አመኑ፡፡ وَالْمُؤْمِنُونَ

"ሁሉም" ማለትም ተወዳጁ ነቢያችን እና ምእመናን «ከመልእክተኞቹ በአንድም መካከል አንለይም» የሚሉ ሲኾኑ አመኑ፦
2፥285 ሁሉም በአላህ፣ በመላዕክቱም፣ በመጻሕፍቱም፣ በመልእክተኞቹም «ከመልእክተኞቹ በአንድም መካከል አንለይም» የሚሉ ሲኾኑ አመኑ፡፡ كُلٌّ آمَنَ بِاللَّهِ وَمَلَائِكَتِهِ وَكُتُبِهِ وَرُسُلِهِ لَا نُفَرِّقُ بَيْنَ أَحَدٍ مِّن رُّسُلِهِ
3፥84 "ከእነርሱ መካከል አንድንም አንለይም" نُفَرِّقُ بَيْنَ أَحَدٍ مِّنْهُمْ
2፥136 "ከእነርሱ መካከል አንድንም አንለይም" نُفَرِّقُ بَيْنَ أَحَدٍ مِّنْهُمْ

በሁሉም ነቢያት ላይ የተወረደው የመልእክቱ ጭብጥ ተውሒድ ስለሆነ ከእነርሱ መካከል አንድንም ሳንለይ እናምናለን፥ "ላ ኢላሀ ኢላ አና" لَا إِلَـٰهَ إِلَّا أَنَا የሚለው መገሰጫ ለነቢያችን እና ከእርሳቸው በፊት በነበሩት ነቢያት ላይ የወረደ መገሰጫ ነው፦
21፥24 «አስረጃችሁን አምጡ፡፡ ይህ መገሰጫ እኔ ዘንድ ያለው ከእኔ በፊትም የነበረ መገሰጫ ነው» በላቸው፡፡ قُلْ هَاتُوا بُرْهَانَكُمْ ۖ هَـٰذَا ذِكْرُ مَن مَّعِيَ وَذِكْرُ مَن قَبْلِي
21፥25 ከአንተ በፊትም፦ "እነሆ ከእኔ ሌላ አምላክ የለምና አምልኩኝ" በማለት ወደ እርሱ የምናወርድለት ቢኾን እንጂ ከመልእክተኛ አንድንም አላክንም፡፡ وَمَا أَرْسَلْنَا مِن قَبْلِكَ مِن رَّسُولٍ إِلَّا نُوحِي إِلَيْهِ أَنَّهُ لَا إِلَـٰهَ إِلَّا أَنَا فَاعْبُدُونِ

"ዚክር" ذِكْر ማለት "መገሰጫ" ማለት ሲሆን ለሁሉም መልእክተኞች የወረደውን መልእክት ተህሊል ስለሆነ አይሁዳውያን በመልእክተኞቹ መካከል ሳይለዩ ማመን ሲገባቸው በተቃራኒው በመካድ «በከፊሉም እናምናለን በከፊሉም እንክዳለን» የሚሉ እነዚያ በእውነት ከሓዲዎቹ እነርሱ ናቸው። ለእነርሱ አዋራጅን ቅጣት አሏህ አዘጋጅቷል፦
4፥150 እነዚያ በአላህ እና በመልእክተኞቹ የሚክዱ፣ በአላህ እና በመልእክተኞቹም መካከል መለየትን የሚፈልጉ፣ «በከፊሉም እናምናለን በከፊሉም እንክዳለን» የሚሉ፣ በዚህም መካከል መንገድን ሊይዙ የሚፈልጉ እነዚያ በእውነት ከሓዲዎቹ እነርሱ ናቸው፡፡ ለከሓዲዎችም አዋራጅን ቅጣት አዘጋጅተናል፡፡ إِنَّ الَّذِينَ يَكْفُرُونَ بِاللَّهِ وَرُسُلِهِ وَيُرِيدُونَ أَن يُفَرِّقُوا بَيْنَ اللَّهِ وَرُسُلِهِ وَيَقُولُونَ نُؤْمِنُ بِبَعْضٍ وَنَكْفُرُ بِبَعْضٍ وَيُرِيدُونَ أَن يَتَّخِذُوا بَيْنَ ذَٰلِكَ سَبِيلًا أُولَـٰئِكَ هُمُ الْكَافِرُونَ حَقًّا ۚ وَأَعْتَدْنَا لِلْكَافِرِينَ عَذَابًا مُّهِينًا
ስለዚህ ከመነሻው "ከመልእክተኞቹ በአንድም መካከል አንለይም" ያለው አሏህ ሳይሆን አሏህ ተወዳጁ ነቢያችን እና ምእመናን እንዲሉ ያዘዘው ትእዛዝ ነው፥ "ከመልእክተኞቹ በአንድም መካከል አንለይም" ብለው የሚያምኑት ምእመናን ሆነው ሳለ አሏህ "ከመልእክተኞቹ በአንድም መካከል አንለይም" ብሎ እንደተናገረ አርጎ መረዳት ዓረፍተነገሩን ከዐውዱ ማፋታት ነው። "አመነ" آمَنَ እና "አመና" آمَنَّا የሚል ኃይለ ቃል ከአንቀጹ በማውጣት እና የራስን አሳብ መክተት በሥነ አፈታት ጥናት"hermeneutics" ፈቲሆት"exegesis" ሳይሆን ሰጊዎት"eisegesis" ነው።
አሏህ እኛን፦ "ከመልእክተኞቹ በአንድም መካከል አንለይም" "በሉ" ያለበት ምክንያት አይሁዳውያን አላህ ከባሮቹ በሚሻው ሰው ላይ ከችሮታው ማውረዱን በምቀኝነት በመካዳቸው ነው፦
2፥90 ነፍሶቻቸውን በእርሱ የሸጡበት ነገር ከፋ! እርሱም አላህ ከባሮቹ በሚሻው ሰው ላይ ከችሮታው ማውረዱን በመመቅኘት አላህ ባወረደው ነገር መካዳቸው ነው፡፡ بِئْسَمَا اشْتَرَوْا بِهِ أَنفُسَهُمْ أَن يَكْفُرُوا بِمَا أَنزَلَ اللَّهُ بَغْيًا أَن يُنَزِّلَ اللَّهُ مِن فَضْلِهِ عَلَىٰ مَن يَشَاءُ مِنْ عِبَادِهِ

እዚህ አንቀጽ ላይ "ችሮታ" ለሚለው የገባ ቃል "ፈድል" فَضْل ሲሆን ሲሆን "ስጦታ" "ችሮታ" "ጸጋ"Bounty” ማለት ነው፥ ሥርወ-ቃሉ "ፈዶለ" فَضَّلَ ማለትም" ሰጠ" "ቸረ" ነው። አምላካችን አሏህ በሚያወርደው ፈድል መልእክተኞች ከፊላቸውን በከፊሉ ላይ አብልጧል፦
2፥253 እነዚህን መልእክተኞች ከፊላቸውን በከፊሉ ላይ አበለጥን፡፡ تِلْكَ الرُّسُلُ فَضَّلْنَا بَعْضَهُمْ عَلَىٰ بَعْضٍ
17፥55 ከፊሉንም ነቢያት በከፊሉ ላይ በእርግጥ አበለጥን፡፡ وَلَقَدْ فَضَّلْنَا بَعْضَ النَّبِيِّينَ عَلَىٰ بَعْضٍ

እነዚህ አናቅጽ ላይ "አበለጥን" ለሚለው የገባ ቃል "ፈዶልና" فَضَّلْنَا መሆኑን ልብ ብለካልን? አንደ መልእክተኛ ጋር የተወረደለት ፈድል ሌላው ጋር ሰለሌለ ከፍሉ በከፊሉ ላይ ይበላለጣሉ፥ ለምሳሌ፦ አሏህ ሙሣን በቀጥታ ሲያናግር ሌላውን በመልአክ ወይም በራእይ በማናገር ከፊላቸውን በከፊሉ ላይ አብልጧል፦
2፥253 ከእነርሱ ውስጥ አላህ ያነጋገረው አለ፡፡ مِّنْهُم مَّن كَلَّمَ اللَّهُ
4፥164 አላህ ሙሣን ማነጋገርን አነጋገረው፡፡ وَكَلَّمَ اللَّهُ مُوسَىٰ تَكْلِيمًا

ይህ የደረጃ ልዩነት እንጂ የኑባሬ ልዩነት አይደለም። ለምሳሌ፦ አሏህ ለመርየምን ልጅ ለዒሣ ግልጽ ተአምራትን በመስጠት እና በቅዱሱ መንፈስ በማበረታታት አብልጧል፦
2፥253 ከፊሎቻቸውንም በደረጃዎች ከፍ አደረገ፡፡ የመርየምን ልጅ ዒሣን ግልጽ ተአምራትን ሰጠነው፥ በቅዱሱ መንፈስም አበረታነው፡፡ وَرَفَعَ بَعْضَهُمْ دَرَجَاتٍ ۚ وَآتَيْنَا عِيسَى ابْنَ مَرْيَمَ الْبَيِّنَاتِ وَأَيَّدْنَاهُ بِرُوحِ الْقُدُسِ
2፥87 የመርየምን ልጅ ዒሣን ግልጽ ተአምራትን ሰጠነው፡፡ በቅዱሱ መንፈስም አበረታነው፡፡ وَآتَيْنَا عِيسَى ابْنَ مَرْيَمَ الْبَيِّنَاتِ وَأَيَّدْنَاهُ بِرُوحِ الْقُدُسِ

ግጭት ማለት አሏህ እኛን፦ "እኩል አርጋችሁ እመኑ" ብሎን በተቃራኒው "አንዱን መልእክተኛ ከሌላው አስብልጡ" ቢለን ወይም አሏህ፦ "መልእክተኞች ከፊላቸውን በከፊሉ ላይ አበለጥን" ብሎ "ከመልእክተኞቹ በአንድም መካከል ስንለይ እኩል አርገናል" ቢል ኖሮ ግጭት ነበር። ነገር ግን ቁርኣን የፈጣሪያችን የአሏህ ንግግር ስለሆነ እና የሰው ንግግር ስላልገባበት የእርስ በእርስ ግጭት የለውም፦
4፥82 ቁርኣንን አያስተነትኑምን? ከአላህ ሌላ ዘንድ በነበረ ኖሮ በእርሱ ውስጥ ብዙን መለያየት ባገኙ ነበር፡፡ أَفَلَا يَتَدَبَّرُونَ الْقُرْآنَ ۚ وَلَوْ كَانَ مِنْ عِندِ غَيْرِ اللَّهِ لَوَجَدُوا فِيهِ اخْتِلَافًا كَثِيرًا

"ኢኽቲላፍ" اخْتِلَاف ማለት "ግጭት" ማለት ሲሆን ቁርኣን ከአሏህ ዘንድ በግልጠተ መለኮት የመጣ የአሏህ ንግግር ስለሆነ እርስ በእርስ አይጋጭም። አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛን ጽናቱን ይስጠን! አሚን።

ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
ከዕባህ

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

105፥1 በዝሆኑ ባለቤቶች ጌታህ እንዴት እንደሠራ አላወቅህምን? أَلَمْ تَرَ كَيْفَ فَعَلَ رَبُّكَ بِأَصْحَابِ الْفِيلِ

"ከዕባህ" كَعْبَة ማለት "አንኳር“cube" ማለት ሲሆን አንኳር "ምልዓት" ነው፥ ምልአት ባለ ሦስት ቅጥ ነው። ይህም ቁመት፣ ርዝምት እና ስፋት ነው፥ አምላካችን አሏህ ከዕባን የተቀደሰ ወይም የተከበረ ቤት አደረገው፦
5፥97 "ከዕባን የተከበረውን ቤት፣ ክልክል የኾነውንም ወር፣ መስዋዕቱንና ባለ ምልክቶቹንም መንጋዎች አላህ ለሰዎች መቋቋሚያ አደረገ፡፡ جَعَلَ ٱللَّهُ ٱلْكَعْبَةَ ٱلْبَيْتَ ٱلْحَرَامَ قِيَٰمًۭا لِّلنَّاسِ وَٱلشَّهْرَ ٱلْحَرَامَ وَٱلْهَدْىَ وَٱلْقَلَٰٓئِدَ
3፥96 ለሰዎች መጀመሪያ የተኖረዉ ቤት ቡሩክ እና ለዓለማት ሁሉ መመሪያ ሲኾን ያ በበካህ ያለው ነው። إِنَّ أَوَّلَ بَيْتٍۢ وُضِعَ لِلنَّاسِ لَلَّذِى بِبَكَّةَ مُبَارَكًۭا وَهُدًۭى لِّلْعَٰلَمِينَ

ከዕባህ ለሰዎች መጀመሪያ የተኖረዉ ቤት ቡሩክ እና ለዓለማት ሁሉ መመሪያ ሆኖ ሳለ የአክሱም መንግሥት ንጉሥ ካሌብ እስከ የመን ድረስ ይገዛ ነበር። በጃሂሊያህ ጊዜ የካሌብ ጦር መሪ አብረሃህ አል አሽረም በ 527 ድኅረ ልደት በየመን ውስጥ ከአሏህ ቤት ጋር በማፎካከር ቤተክርስቲያን አሠርቷል፦
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 63, ሐዲስ 49
ጀሪር ኢብኑ ዐብደሏህ እንደተረከው፦ “በዘመነ-ጃሂሊያ ዙል-ኸለሷህ የሚባል ቤት ነበረ፥ የቀኝ ከዕባህ ወይም የግራ ከዕባህ ተብሎ ይጠራ ነበር”። عَنْ جَرِيرِ بْنِ عَبْدِ اللَّهِ، قَالَ كَانَ فِي الْجَاهِلِيَّةِ بَيْتٌ يُقَالَ لَهُ ذُو الْخَلَصَةِ، وَكَانَ يُقَالُ لَهُ الْكَعْبَةُ الْيَمَانِيَةُ، أَوِ الْكَعْبَةُ الشَّأْمِيَّةُ

“ኸለሷህ” خَلَصَة ማለት “ቀሊሥ” قَلِسْ ማለት ነው፥ “ቀሊሥ” ከግሪኩ ኮይኔ “ኤክሌሲያ” εκκλεσια የመጣ ሲሆን በተለምዶ “ቤተ ክርስቲያን” ይባል እንጂ “ጉባኤ” “ማኅበር” “ተጠርተው የወጡ” ማለት ነው። ይህንን ቤት ከከዕባ ጋር ለማመሳሰል “አል ከዕበቱል የማኒያህ” الْكَعْبَةُ الْيَمَانِيَة ወይም “አል ከዕበቱሽ ሸእሚያህ” الْكَعْبَةُ الشَّأْمِيَّة ብሎታል። በ 570 ድኅረ ልደት "አብረሃህ አል አሽረም" أَبْرَهَة ٱلْأَشْرَم እና ጭፍሮቹ የአሏህ ቤት ለማፍረስ በዝሆን ጋልበው ወደ መካ መጡ፥ አሏህም እነዚህን የዝሆን ባለቤቶችን ተንኮል በጥፋት ውስጥ ከንቱ አደረገ፦
105፥1 በዝሆኑ ባለቤቶች ጌታህ እንዴት እንደሠራ አላወቅህምን? أَلَمْ تَرَ كَيْفَ فَعَلَ رَبُّكَ بِأَصْحَابِ الْفِيلِ
105፥2 ተንኮላቸውን በጥፋት ውስጥ ከንቱ አላደረገምን? أَلَمْ يَجْعَلْ كَيْدَهُمْ فِي تَضْلِيلٍ

አምላካችን አሏህ በእነርሱም ላይ ከተጠበሰ ጭቃ በኾነ ድንጋይ ማለትም በሸክላ”brick” የሚወረውሩባቸው መንጎች የኾኑን አዕዋፍን በመላክ ቅጠሉ እንደ ተበላ አዝመራም አደረጋቸው፦
105፥3 “በእነርሱም ላይ መንጎች የኾኑን አዕዋፍን ላከ”፡፡ وَأَرْسَلَ عَلَيْهِمْ طَيْرًا أَبَابِيلَ
105፥4 “ከተጠበሰ ጭቃ በኾነ ድንጋይ የምትወረውርባቸው የኾነችን አዕዋፍ”፡፡ تَرْمِيهِم بِحِجَارَةٍ مِّن سِجِّيلٍ
105፥5 “ቅጠሉ እንደ ተበላ አዝመራም አደረጋቸው”፡፡ فَجَعَلَهُمْ كَعَصْفٍ مَّأْكُولٍ

ከዚያ ጊዜ ጀምሮ ቁረይሾች ጊዜ ሲቆጥሩ እራሱ “ዓሙል ፊል” عامُ الْفِيلِ ማለትም “የዝሆን ዓመት” እያሉ ነበር።
የአብረሃህ አል አሽረም አድራጎት ይህን ያህል ከተወገዘ ዘንዳ ከዕባን አስመስሎ ሠርቶ "ከዕባህ ነው" ማለት ከላይ እንዳየነው ዋጋ ያስከፍላል፥ የአላባ ሙሥሊሞች በቅንነት ኢሥላምን ለማስተዋወቅ ብለው የከዕባህ ቅርጽ በጊዜአዊነት መሥራታቸው ለማስተማሪያነት እንጂ በቋሚነት መሥጂድ ለማድረግ አልነበረም። ስህተታቸውን በትህትና ከማረም ይልቅ በስድብ ማጥረግረግ ጉዳዩን እንዲጦዝ እና እልክ መግባባት አርጎታል፥ ይህ ደግሞ አሏህ አደራ እንድንባባል ካዘዘን ጋር ይጋጫል፦
90፥17 ከዚያም ከነዚያ ከአመኑትና በመታገስ አደራ ከተባባሉት፣ በማዘንም አደራ ከተባባሉት ሰዎች አልኾነም፡፡ ثُمَّ كَانَ مِنَ الَّذِينَ آمَنُوا وَتَوَاصَوْا بِالصَّبْرِ وَتَوَاصَوْا بِالْمَرْحَمَةِ
103፥3 እነዚያ ያመኑትና መልካሞችን የሠሩት፣ በእውነትም አደራ የተባባሉት፣ በመታገስም አደራ የተባባሉት ብቻ ሲቀሩ፡፡ إِلَّا الَّذِينَ آمَنُوا وَعَمِلُوا الصَّالِحَاتِ وَتَوَاصَوْا بِالْحَقِّ وَتَوَاصَوْا بِالصَّبْرِ

አንድ ሰው ሐቅ ስለያዘ ብቻ ሐቁን ለማስተላለፍ ስድብ መፍትሄ አይሆንም፥ ከዚያ ይልቅ አደራ መባባል በሐቅ ብቻ ሳይሆን በትግስት እና በማዘንም ጭምር ቢሆን የተሳሳተው ሰው ከስህተቱ ሊመለስ ዝግጁ ይሆናል። ኢሻሏህ ጠርዝ ይዘው የሚጠዛጠዙ እነዚህ ሁለቱም ጽንፎች ከዚህ ድርጊታቸው እንደሚታረሙ ተስፋ አለኝ!
አምላካችን አሏህ ለሁላችንም ሂዳያህ ይስጠን! አሚን።

ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
አሥ-ሠላሙ ዐለይኩም ወራሕመቱላሂ ወበረካቱሁ!

እንኳን የዒዱል ፊጥር በሰላም አደረሳችሁ!
ተናፍቆ የሚመጣ እና ሳይጠገብ የሚሄድ ብቸኛው ወር የረመዷን ወር ነው።

አሏህ ከእኛም ከእናንተ መልካም ሥራዎችን ይቀበለን! አሚን።

ዒድ ሙባረክ!
ስለ ሸዋል ይህንን ያንብቡ እና ለሌሎች ወንድሞች እና እኅቶች ሼር ያርጉ፦ https://tttttt.me/Wahidcom/2757
ተሥሊስ

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

4፥171 «ሦስት ነው» አትበሉ! ተከልከሉ! ለእናንተ የተሻለ ይኾናልና፡፡ አላህ አንድ አምላክ ብቻ ነው፡፡ وَلَا تَقُولُوا ثَلَاثَةٌ ۚ انتَهُوا خَيْرًا لَّكُمْ ۚ إِنَّمَا اللَّهُ إِلَـٰهٌ وَاحِدٌ

"መለኮት" ማለት "አምላክነት" ማለት ነው፥ "እግዚአብሔር" የሚለው ቃል ደግሞ በግሪክ "ቴዎስ" θεός ሲሆን "አምላክ"God" ማለት ነው። በጥቅሉ "መለኮት" "እግዚአብሔር" "አምላክ" ተመሳሳይ ነገር ለማሳየት የመጣ ሲሆን በሥላሴ እሳቤ፦
1. ወላዲ ማንነት አምላክ፣
2. ተወላዲ ማንነት አምላክ፣
3. ሰራጺ ማንነት አምላክ
ከሆነ ወላዲ አምላክ፣ ተወላዲ አምላክ፣ ሰራጺ አምላክ አለ ማለት ነው፦
ሰይፈ ሥላሴ ዘሰኞ ምዕራፍ 2 ቁጥር 42
"በጽርሐ አርያም ለሚኖር ልዩ ሦስት ለሚሆን አምላክ ሰላምታ ይገባል"

"ልዩ ሦስት ለሚሆን አምላክ" የሚለው ይሰመርበት! "ሦስት ለሚሆን አምላክ" በግዕዙ "ሥሉስ አምላክ" ነው። ወላዲ አምላክ "አብ" ተወላዲ አምላክ እና ሰራጺ አምላክ ካልሆነ፣ ተወላዲ አምላክ "ወልድ" ወላዲ አምላክ እና ሰራጺ አምላክ ካልሆነ፣ ሰራጺ አምላክ "መንፈስ ቅዱስ" ወላዲ አምላክ እና ተወላዲ አምላክ ካልሆነ ስንት አምላክ አለ? መልሱ ሦስት አምላክ ይሆናል። ምክንያቱም ወላዲ አምላክ፣ ተወላዲ አምላክ፣ ሰራጺ አምላክ ሦስት ነው፥ እነርሱም፦ በግዕዙ "ሦሉስ አምላክ" ሲሉ ትርጉሙ "ሦስት አምላክ" ማለት ነው፦
ሰይፈ ሥላሴ ዘረቡዕ ምዕራፍ 4 ቁጥር 31
“መለኮት በአካል ሦስት ሲሆን በባሕርይ አንድ ነው”።

"መለኮት በአካል ሦስት ሲሆን" የሚለው ይሰመርበት! "መለኮት በአካል ሦስት ነው" ማለት የጤንነት ነውን? አምላክ አባት(እግዚአብሔር አብ)፣ አምላክ ልጅ(እግዚአብሔር ወልድ)፣ አምላክ መንፈስ ቅዱስ(እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ) የሚባሉ በአካል ሦስት አምላክ"tritheism" ናቸው። አምላክነት ሦስቱ አካላት የሚጋሩት ባሕርይ እንጂ "ማንነት ነው" ብለው አያምኑም፦
ሰይፈ ሥላሴ ዘሐሙስ ምዕራፍ 5 ቁጥር 17
"ሦስት የእሳት ባሕርይ ነገር ግን አንድ ብርሃን ነው"።

"ሦስት የእሳት ባሕርይ" የሚለው ይሰመርበት! "ሦስት የእሳት ባሕርይ" ካለ አንድ ብርሃን ሳይሆን ሦስት ብርሃናት ናቸው፦
ሃይማኖተ አበው ምዕራፍ 10 ቁጥር 6
"ዕውቀትን የሚገልጹ ብርሃናት ናቸው"።

"ብርሃናት" የብርሃን ብዙ ቁጥር ነው፥ አንዱ ብርሃን አብ ሁለቱ ብርሃናትን ወልድ እና መንፈስ ቅዱስን አስገኘ ማለት የጤንነት አይደለም፦
ሃይማኖተ አበው ምዕራፍ 10 ቁጥር 12
"አብ ብርሃን ነው፣ ከአብ የተወለደ ቃሉ ወልድ ከብርሃን የተገኘ ብርሃን ነው፣ እንዲሁ ከአብ የሠረፀ መንፈስ ቅዱስም ከብርሃን የተገኘ ብርሃን ነው"።

ከአንዱ ብርሃን ከአብ ወልድ የሚባል ብርሃን በመወለድ ተገኘ እና ከአንዱ ብርሃን ከአብ መንፈስ ቅዱስ የሚባል ብርሃን በመሥረፅ ተገኘ የሚል ትምህርት በግልጽ "ሦስት ፀሐይ" ብለው አስቀምጠዋል፦
ሰይፈ ሥላሴ ዘረቡዕ ምዕራፍ 4 ቁጥር 21
"ሦስት ፀሐይ አንድ ብርሃን.. ነው"።
ሰይፈ ሥላሴ ዘሐሙስ ምዕራፍ 5 ቁጥር 21
"ሦስት የብርሃን አዕማድ በመጠን ግን..አንድ ነው"።

ዶክተር ዛኪር፣ ዶክተር ቢላል እና ዶክተር ፊሊፕ ሦስት ዶክተር እንጂ አንድ ዶክተር አይደሉም፥ ግን አንድ ዶክትሬት ይጋራሉ። በተመሳዳይ እግዚአብሔር አብ፣ እግዚአብሔር ወልድ እና እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ሦስት እግዚአብሔር እንጂ አንድ እግዚአብሔር አይደሉም፥ ግን አንድ እግዚአብሔርነትን ይጋራሉ፦
ሰይፈ ሥላሴ ዘማክሰኞ ምዕራፍ 3 ቁጥር 21
"ቅዱስ፣ ቅዱስ፣ ቅዱስ እግዚአብሔር ሦስት ሲሆን አንድ፥ አንድ ሲሆን ሦስት የሚሆን እርሱ አንድ ቅዱስ ነው"።

"እግዚአብሔር ሦስት ሲሆን" የሚለው ይሰመርበት! "አንድ ቅዱስ ነው" ካላችሁ በኃላ "ሥሉስ ቅዱስ" ማለትም "ሦስት ቅዱስ" ማለታችሁ የጤና ነውን? "ቅድስት ሥላሴ" ማለትም "ቅዱሶች ሦስነት" ለምን ትላላችሁ? በነገራችን ላይ "ቅድስት" የሚለው ቃል "ቅዱሳን" "ቅዱሶች" የሚለውን ለመተካት የሚጠቀሙበት ነው፦
ሃይማኖተ አበው ምዕራፍ 82 ቁጥር 14
"ሥሉስ ቅዱስ ያልተፈጠሩ ናቸው"

"ሦስት ቅዱስ" "አንድ ቅዱስ" እርስ በእርሱ ይጋጫል። እንደ እናንተ ትምህርት አምላክ ከማርያም ሲወለድ የተወለደው አንዱ አምላክ ነው ወይስ ሁለተኛው ልጅ የሆነ አምላክ? አንዱ አምላክ ከሆነ አብ እና መንፈስ ቅዱስ አብረው ተወልደዋል? ምክንያቱም ማርያም የመለኮት እናት ናት ስለሚል፦
ሰይፈ ሥላሴ ዘእሑድ ምዕራፍ 8 ቁጥር 73
"በመለኮት እናት በድንግል ማርያም"።

ሁለተኛው ልጅ የሆነው አምላክ ከሆነ ያልተወለዱ ሁለት አባት እና መንፈስ ቅዱስ የሆኑ አምላክ አሉን? ከማርያም የተነሳው ሥጋ መለኮትን ገንዘብ ሲያደርግ ሙሉ መለኮትን ነው ወይስ የአብ ተወላዲ መለኮትን?
ያለው አማራጭ ሦስት አምላክ ስለሆነ በግልጽ "አምላካችን ያለ መለየት ሦስት ነው" ብለው አርፈውታል፦
ሃይማኖተ አበው ምዕራፍ 99 ቁጥር 11
“አምላካችን ያለ መለየት ሦስት ነው”።

"ኡሲያ" οὐσία የሚለው ቃል "ሃልዎት" "ኑባሬ" "ህላዌ"essence" የሚል ትርጉም አለው፥ "በአካል ሦስት ህላዌ" ማለት የጤንነት አይደለም፦
ሃይማኖተ አበው ምዕራፍ 34 ቁጥር 22
“በአካል ሦስት "ህላዌ" በመለኮት አንድ ህላዌ ነው”።
በእርግጥም "ሦስት ለሚሆን አምላክ፣ ሦስት ቅዱስ፣ ሦስት ልዑላን፣ ሦስት ጌቶች፣ ሦስት ነገሥታት፣ ሦስት ገዢዎች" ብላችሁ ካስተማራችሁ በግልጽ መድብለ አማልክታውያን ናችሁ፦
፨ሰይፈ ሥላሴ ዘሐሙስ ምዕራፍ 5 ቁጥር 22-23
“ሦስት ልዑላን ገዢዎች፥ ሦስት ጌቶች ናቸው”።
፨ ሰይፈ ሥላሴ ዘሐሙስ ምዕራፍ 5 ቁጥር 26
“ሦስት ነገሥታት አንድ አገዛዝ ናቸው”።
፨ ሰይፈ ሥላሴ ዘረቡዕ ምዕራፍ 4 ቁጥር 54
“እነዚህ ገዢዎች በገጽ ሦስት በፈቃድ አንድ ናቸው”።

"ገጽ" ማለት "ፊት" ማለት ነው፥ ባለ ሦስት ፊት አምላክ የዐረማውያን እንጂ የአብርሃም አምላክ በፍጹም አይደለም፦
ሰይፈ ሥላሴ ዘሐሙስ ምዕራፍ 5 ቁጥር 24
"ሦስት ገጽ አንድ አመለካከት ናቸው"።

ሥላሴ አካላቸው የተለያዩ ከሆኑ አካላቸው አንድ ዓይነት ወይስ የተለያየ? አንድ ዓይነት ከሆነ ምን ዓይነት አንድ ዓይነት? ከተለየስ ምን ዓይነት የተለየ አካል ነው? ገጽታቸውን ሦስት አርጎ ያለያየ ምን ዓይነት ገጽታ ይሆን? "መለኮት ሦስትም አንድም ነው" ማለት የጤና አይደለም፦
ሰይፈ ሥላሴ ዘቀዳሚት ምዕራፍ 7 ቁጥር 68
"ለመለኮት ሦስትነት ምስጋና ይገባል"።
ሰይፈ ሥላሴ ዘቀዳሚት ምዕራፍ 7 ቁጥር 69
"ለመለኮት አንድነት ምስጋና ይገባል"።
ገድለ ተክለ ሃይማኖት 60(61)፥12
"የመለኮት ሦስትነት መቆፈሪያ ልቡን በኮሰተረው እና በቆፈረው ጊዜ"።

በምድር ላይ ያለው እያንዳንዱ ሰው የራሱ ገጽ ያለው ሲሆን በስም፣ በአካል፣ በግብር ስምንት ቢልዮን ነው፥ ግን የሁሉም ምንነት አንድ ምንነት ስለሆነ ስምንት ቢልዮን ሰው አንድ ሰው አይባልም። ስምንት ቢልዮን ሰዎች ያሰኘው በማንነት እከሌ እየተባለ ስለሚለያይ ነው፥ አምላክ በማንነት እከሌ እየተባለ በስም፣ በአካል፣ በግብር ከተለያየ አንድ ሳይሆን ብዙ ነው። በሦስት ፊቶች የተለያየ መለኮት፣ ጌታ፣ ንጉሥ፣ አምላክ እና ፈጣሪ መድብለ አማልክት እንጂ ሌላ አይደለም፦
ሰይፈ ሥላሴ ዘእሑድ ምዕራፍ 8 ቁጥር 41
"ሥስት የምትሆን ጌታዬ፣ ንጉሤ፣ አምላኬ፣ ፈጣሪዬ ሆይ! ለአዳራሽህ መብራት ለመመላለሻህም ፀሐይ አትፈልግም"።
መልክአ ሥላሴ ቁጥር 39
“ሥሉስ ቅዱስ ሆይ! የአደም እና የሔዋን "ፈጣሪዎቻቸው" እንደመሆናችሁ የምርኮኞች ነጻ አውጪ የሆነ ኃይላችሁ የጣዖታትን ሐሰተኝነት አጋለጠ"።

ሥላሴ "ፈጣሪዎች" ከተባሉ ስንት ፈጣሪ ሊኖር ነው? እነርሱም በድፍረት፦ "ኤሎሂም" ማለት "አማልክት" ማለት ነውና "አማልክት" የተባለው ሥላሴን አምልካች ነው" በማለታቸው ሥላሴ "አማልክት" መሆናቸው በግልጽ ነግረውናል። ሳያቅማሙም "ሦስት በአንድ የሆነ አምላክ"Triune God" ይሉታል፣ በአገራችን "ሥላሴ" ማለት "ሦስትነት" ማለት ነው፣ በዐረብ ክርስቲያኖች ዘንድ "ተሥሊስ" تَسْلِيث‎ ይሉታል። በፕሮቴስታንት ዘንድ ደግሞ፦ "አብ እራሱን የቻለ አእምሮ፣ ፈቃድ እና ስሜት አለው፣ ወልድ እራሱን የቻለ አእምሮ፣ ፈቃድ እና ስሜት አለው፣ መንፈስ ቅዱስ እራሱን የቻለ አእምሮ፣ ፈቃድ እና ስሜት አለው" ይላሉ፥ ይህ በኦርቶዶክስ ሦስት አማልክት ነው፦
መጽሐፈ ሜላድ 6፥38 ሦስት ልብ፣ ሦስት ቃል፣ ሦስት እስትንፋስ የሚል ግን ሦስት አማልክት አመለከ"።

"ለበወ" ማለት "አወቀ" ማለት ከሆነ ሦስቱ ማንንነቶች የየራሳቸው ዕውቀት ካላቸው እና እርስ በእርስ የሚነጋገሩ ከሆነ ሦስት ልብ ይሆናል፥ በፕሮቴስታንት ልክ እንደ አርጌናሳውያን አብ ወልድን እና መንፈስ ቅዱስን የሚገዛቸው አስተዳዳሪያቸው ነው፦
1ኛ ቆሮንቶስ 15፥28 አዲሱ መደበኛ ትርጉም ማብራሪያ፦ "ወልድ ለአብ የሚገዛው በአስተዳደር ረገድ ሲሆን..በሥላሴ አካላት መካከል አብ የበላይ አስተዳዳሪ ነው"

እንግዲህ ሥላሴ ሰው በማመኑ የሚድንበት እና በመካዱ የሚጠፋበት አንቀጸ እምነት ቢሆን ኖሮ ነቢያት እና ሐዋርያት በግልጽ ልክ እንደ ተውሒድ ያስቀምጡልን ነበር። ነገር ግን በግልጠተ መለኮት ውስጥ የሥላሴ አሳቡ ስለሌለ «ሦስት ነው» አትበሉ! ተከልከሉ! ለእናንተ የተሻለ ይኾናልና፡፡ አሏህ አንድ አምላክ ብቻ ነው፦
4፥171 «ሦስት ነው» አትበሉ! ተከልከሉ! ለእናንተ የተሻለ ይኾናልና፡፡ አላህ አንድ አምላክ ብቻ ነው፡፡ وَلَا تَقُولُوا ثَلَاثَةٌ ۚ انتَهُوا خَيْرًا لَّكُمْ ۚ إِنَّمَا اللَّهُ إِلَـٰهٌ وَاحِدٌ

አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛን ጽናቱን ይስጠን! አሚን። 

ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
የባሕርይ እናት

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

3፥36 «እኔም እርስዋን እና ዝርያዋን ከተረገመው ሰይጣን በአንተ እጠብቃቸዋለሁ» وَإِنِّي أُعِيذُهَا بِكَ وَذُرِّيَّتَهَا مِنَ الشَّيْطَانِ الرَّجِيمِ

የመርየም እናት፦ "እርስዋን እና ዝርያዋን" በማለቷ ዒሣ የመርየም ዘር እንደሆነ ቁርኣን አስረግጦ እና ረግጦ ያሳያል፦
3፥36 «እኔም እርስዋን እና ዝርያዋን ከተረገመው ሰይጣን በአንተ እጠብቃቸዋለሁ» وَإِنِّي أُعِيذُهَا بِكَ وَذُرِّيَّتَهَا مِنَ الشَّيْطَانِ الرَّجِيمِ

"ዙሪያህ" ذُرِّيَّة ማለት "ዘር"offspring" ማለት ሲሆን "ዙሪያህ" ذُرِّيَّة በሚለው መድረሻ ቅጥያ ላይ "ሃ" هَا የሚለው አንስታይ አገናዛቢ ተውላጠ ስም መርየምን አመላካች ስለሆነ ዒሣ የመርየም ዘር መሆኑን ቁልጭ እና ፍንትው አርጎ ያሳያል። "ባሕርይ" ማለት "ምንነት" ማለት ሲሆን ለምሳሌ፦ የእኔ እናት ለእኔ የባሕርይ እናት ናት፥ ምክንያቱም የእኔ መገኛ እናቴ ስለሆነች እና እርሷን አህዬ እና መስዬ ከማንነቷ ማንነት ከምንነቷ ምንነት ወስጃለው፥ በተመሳሳይ የኢየሱስ መገኛው እናቱ ማርያም ስለሆነች ከእርሷ ምንነት ምንነት ወስዶ እና ከእርሷ ማንነት ማንነት ወስዶ ሰው ሆኗል።
ይህ ሆኖ ሳለ በዐበይት ክርስትና ኢየሱስ "ከአብ ባሕርይ ባሕርይን እንዲሁ ከአካሉ አካልን ወስዶ የተገኘ አምላክ" ተብሎ ይታመናል፦
ሃይማኖተ አበው 74፥8 "ከባሕርይ አምላክ የተገኘ የባሕርይ አምላክ"።
ሃይማኖተ አበው 70፥17 "ከአብ ባሕርይ የተገኘ አምላክ"።
ሃይማኖተ አበው 78፥8 "አካል ዘእምአካል ባሕርይ ዘእምባሕርይ የተወለደው ልደት የማይመረመር ነው"።
ሃይማኖተ አበው 121፥10 "ከአብ አካል ዘእምአካል ባሕርይ ዘእምባሕርይ ተወልዶ የመጣ አምላክ"።

ኢየሱስ ከአብ ተገኘ ሲባል ምን ማለት ነው? የሚለውን ጥያቄ ርዕስ እንዳያስቀይስ ሙግቱን አጥበበነው እውን ማርያም ለመለኮት የባሕርይ እናቱ ናትን? መለኮት ከማርያም ለሁለተኛ ጊዜ ተገኝቷልን? ይህንን ነጥብ እስቲ እንመልከት፦
ሃይማኖተ አበው 74፥13 "የመለኮት መገኘት ከድንግል አይደለም፥ ከአብ ከተወለደ በኃላ ለመለኮት ሁለተኛ ልደት አይሻምና"።

ስለዚህ ከማርያም ተፀንሶ የተወለደው ሰው ብቻ እና ብቻ ነው፥ ማርያም መለኮትን ከወለደች ሁለተኛ ልደት አይሆንምን? መለኮትን ካልወለደች እና መለኮት ከእርሷ ካልተገኘ የአምላክ እናት አይደለችም ማለት ነው። ወይም ማርያም ለመለኮት የጸጋ እናት እንጂ የባሕርይ እናቱ አይደለች ይሆን? ውስብስብ ትምህርት ነው፦
ሰይፈ ሥላሴ ዘእሑድ ምዕራፍ 8 ቁጥር 73
"በመለኮት እናት በድንግል ማርያም"።

ማርያም ለመለኮት የባሕርይ እናቱ ናትን? መለኮትስ ለማርያም የባሕርይ ልጇ ነውን? "አዎ" ካላችሁን መለኮትነቱን አስገኝታለችን? እርሱስ መለኮትነቱ ከእርሷ ተገኝቷልን?
እሺ ይሁን እንበልና መለኮት አንድ ከሆነ ማርያም የሥላሴን መለኮት ወልዳለችን? ወይስ የወለደችው የወልድን መለኮት ብቻ ነው? የአብ እና የመንፈስ ቅዱስ መለኮትነት ካልወለደች ስንት መለኮት ሊኖር ነው? ማርያም "ቴዎቶኮስ" ናትን? "ቴዎቶኮስ" Θεοτόκος የሚለው ቃል "ቴዎስ" Θεός እና "ቶኮስ" τόκος ከሚል ሁለት ቃላት የተዋቀረ ሲሆን "ወላዲተ መለኮት" "የመለኮት ወላጅ" ማለት ነው፥ መለኮት ከእሷ ሳይገኝ እንዴት ወልዳ እናቱ ትሆናለች? በነገራችን ላይ "መለኮት" ማለት በቀላሉ "አምላክ" ማለት ነው።

የቁስጥንጥንያው ኤጲስ ቆጶስ ንስጥሮስ "ማርያም የወለደች ሰው ብቻ ነው" ብሎ ኢየሱስን ምንታዌ ከማድረግ ባሻገር ከማርያም ተፀንሶ የተወለደውን ሰው የሥላሴ አራተኛ አባል አርጎ ሲያርፈው ይህንን የሥላሴን ርባቤ "እንፈታለን" ብሎ የእስክንድርያው ኤጲስ ቆጶስ ቄርሎስ ሁለት አካላት የአብ ልጅ መለኮታዊ አካል እና የማርያም ልጅ ሰዋዊ አካል አንድ አካል ሆኑ በማለት ማርያምን "ቴዎቶኮስ" ብሏታል፦
ሃይማኖተ አበው 49፥15 "ቅድስት ሥላሴን እንዴት አራተኛ አካል ያደርጋሉ? እንዲህ ያለ የተነቀፈ ነገር ሊነገር አይገባውም"።

ንስጥሮስ እና ፕሮቴስታንት፣ የይሆዋ ምስክር፣ ሰባተኛው ቀን የመገለጣውያን ቤተክርስቲያን"The Seventh-day Adventist Church" የሚባሉ አንጃዎች "ማርያም "ኽሪስቶቶኮስ" ብቻ ናት" ብለው ያምናሉ፥ "ኽሪስቶቶኮስ" Χριστοτόκος የሚለው ቃል "ኽሪስቶስ" χρῑστός እና "ቶኮስ" τόκος ከሚል ሁለት ቃላት የተዋቀረ ሲሆን "ወላዲተ ክርስቶስ" "የክርስቶስ ወላጅ" ማለት ነው። ክርስቶስ ደግሞ የአምላክ እንጂ አምላክ አይደለም፦
1ኛ ቆሮንቶስ 3፥23 ክርስቶስ የአምላክ ነው። Χριστὸς δὲ Θεοῦ.
ሉቃስ 9፥20 እናንተስ እኔ ማን እንደ ሆንሁ ትላላችሁ? አላቸው። ጴጥሮስም መልሶ፦ "የአምላክ ክርስቶስ ነህ" አለ። εἶπεν δὲ αὐτοῖς Ὑμεῖς δὲ τίνα με λέγετε εἶναι; Πέτρος δὲ ἀποκριθεὶς εἶπεν Τὸν Χριστὸν τοῦ Θεοῦ.

በእርግጥም ማርያም የክርስቶስ ኢየሱስ የባሕርይ እናቱ ናት። መለኮት ግን አስገኝ እንጂ ከፍጡር ሆነ ከመለኮት የሚገኝ አይደለም፥ መለኮት መነሻ፣ ምንጭ እና መገኛ ካለው መለኮት እንዴት ይባላል? መነሻ እና ጅማሮ ያለው እኮ ፍጡር ብቻ ነው።
አምላካችን ሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይስጠን! አሚን።

ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
አሥ ሠላሙ ዐለይኩም ሙሥሊም ወንድሞቼ እና እኅቶቼ እንዲሁ ክርስቲያን ወገኖች ሰላም ብያለው!

እውን ኢየሱስ የባሕርይ አምላክ ነውን? የሚለው ይህ መጽሐፌ አዲስ አበባ በለገሃር እና በሜክሲኮ መካከል ኮሜርስ ወይም ከጃፋር መጽሐፍ መደብር በስተቀኝ "ኮሜርስ የመጽሐፍ መደብር" በሚባለው ውስጥ ይገኛል። ለበለጠ መረጃ 0920781016 ዐብዱ ብለው ይደውሉ!

ሌሎቻችሁ ተደራሽነት እንዲኖረው በየታይም ላይናችሁ፣ በየጉሩፑ፣ በየፔጁ፣ በየቻናሉ፣ በየኮሜንቱ ሼር እና ፓስት በማድረግ የአጅሩ ተካፋይ ይሁኑ!
የእግዚአብሔር አካል

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።

42፥11 የሚመስለው ምንም "ነገር" የለም፡፡ እርሱም ሰሚው ተመልካቹ ነው፡፡ لَيْسَ كَمِثْلِهِ شَيْءٌ ۖ وَهُوَ السَّمِيعُ الْبَصِيرُ

አምላካችን አሏህ ከፍጡራኑ ጋር የማይመሳሰል የራሱ ባሕርያት አሉት፥ እርሱን የሚመስል ምንም ነገር የለም፦
42፥11 የሚመስለው ምንም "ነገር" የለም፡፡ እርሱም ሰሚው ተመልካቹ ነው፡፡ لَيْسَ كَمِثْلِهِ شَيْءٌ ۖ وَهُوَ السَّمِيعُ الْبَصِيرُ

እዚህ አንቀጽ ላይ "ሚስል" مِثْل በሚለው ቃል ላይ መነሻ ቅጥያ ሆኖ የገባው "ከ" كَ የሚል መስተዋድድ "በጭራሽ" ማለት ነው፥ "ነገር" በሚለው ቃል ውስጥ ሁሉም ፍጡራን የሚካተቱ ሲሆኑ ከፍጡራን መካከል እርሱን የሚመስል ብጤ በጭራሽ የለም። እዚሁ አንቀጽ ላይ አሏህ "ሰሚ እና ተመልካች" እንደሆነ ተገልጿል፥ ሰውም "ሰሚ እና ተመልካች" እንደሆነ ሌላ አንቀጽ ላይ ተገልጿል፦
76፥2 እኛ ሰውን በሕግ ግዳጅ የምንፈትነው ስንኾን ቅልቅሎች ከኾኑ የፍትወት ጠብታ ፈጠርነው፡፡ ሰሚ ተመልካችም አደረግነው*፡፡ إِنَّا خَلَقْنَا الْإِنسَانَ مِن نُّطْفَةٍ أَمْشَاجٍ نَّبْتَلِيهِ فَجَعَلْنَاهُ سَمِيعًا بَصِيرًا

የአሏህ መስማት እና ማየት ከፍጡራን ጋር እንደማይመሳሰል እና እንደማይነጻጸር ሁሉ የፈጣሪ ባሕርዮት ከፍጡራን ባሕርዮት ጋር አይመሳሰለም አይነጻጸርም።
በኢሥላም ያለውን የአሏህ ሲፋት በመጠኑ እዚህ ድረስ ካየን ዘንዳ በባይብል እግዚአብሔር የአካል ክፍል የሆኑት ከንፈር እና ምላስ አለው፦
ኢሳይያስ 30፥27 "ከንፈሮቹም" ቍጣን የሞሉ ናቸው፥ "ምላሱም" እንደምትበላ እሳት ናት።

"ከንፈሮች" የሚለው "ከንፈር" ለሚል ብዙ ቁጥር ሲሆን የላይኛው ከንፈር እና የታችኛው ከንፈር ያመለክታል፥ ምላስ ግን በነጠላ ስለሆነ አንድ ብቻ ይመስላል። "ባት" ሲባል ደንግጠህ "የግድ ሥጋ መሆን አለበት" ካልክ ከንፈር እና ምላስ የግድ ሥጋ መሆን አለበት ብዬ እሞግትካለው፥ በሰፈሩት ቁና መሰፈር ግድ ነውና። እግዚአብሔር የአካል ክፍሎች የሆኑት ዓይኖች፣ ቅንድቦች እና ጆሮዎች አሉት፦
መዝሙር 11፥4 "ዓይኖቹ" ወደ ድሃ ይመለከታሉ፥ "ቅንድቦቹም" የሰው ልጆችን ይመረምራሉ።
1 ጴጥሮስ 3፥12 የጌታ ዓይኖች ወደ ጻድቃን ናቸውና፥ "ጆሮዎቹም" ለጸሎታቸው ተከፍተዋል።

"ዓይኖች" "ቅንድቦች" እና "ጆሮዎች" የተባሉት "ዓይን" "ቅንድብ" "ጆሮ" ለሚሉት ብዙ ቁጥር ስለሆነ ቢያንስ ከአንድ በላይ ዓይኖች፣ ቅንድቦች እና ጆሮዎች አሉት፥ ሰው ላይ ያየሁት ዓይኖች፣ ቅንድቦች እና ጆሮዎች ሥጋ ስለሆኑ "የእግዚአብሔር ዓይኖች፣ ቅንድቦች እና ጆሮዎች ሥጋ ናቸው" ብዬ ደረቅ ንትርክ መነታረክ አላቃተኝም። እግዚአብሔር የአካል ክፍሎች የሆኑት አፍንጫ እና አፍ አሉት፦
ዘጸአት 15፥8 "በአፍንጫህ" እስትንፋስ ውኆች ተከመሩ።
መዝሙር 33፥6 ሠራዊታቸውም ሁሉ "በአፉ" እስትንፋስ።

ሰው የሚተነፍስበት አፍንጫ እና አፍ ሥጋ ስለሆነ "እግዚአብሔር የሚተነፍስበት አፍንጫ እና አፍ ሥጋ ነው" ብዬ ጉንጭ አልፋ ንትርክ መነታረክ አላቃተኝም። እግዚአብሔር የአካል ክፍሎች የሆኑት ክንድ፣ ብብት፣ እግሮች፣ እጆች፣ ጣቶች አሉት፦
ኢሳይያስ 40፥11 ጠቦቶቹን "በክንዱ" ሰብስቦ "በብብቱ" ይሸከማል።
መዝሙር 132፥7 "እግሮቹ" በሚቆሙበት ስፍራ እንሰግዳለን።
መዝሙር 119፥73 "እጆችህ" ሠሩኝ አበጃጁኝም።
መዝሙር 8፥3 "የጣቶችህን" ሥራ ሰማዮችን ባየሁ ጊዜ፥

ባሻዬ እኔ የማውቀው ክንድ፣ ብብት፣ እግሮች፣ እጆች፣ ጣቶች ሥጋ ናቸው፥ እና እግዚአብሔር ልክ እንደ ሰው ክንድ፣ ብብት፣ እግሮች፣ እጆች፣ ጣቶች አሉትን? "አይ ክንድ፣ ብብት፣ እግሮች፣ እጆች፣ ጣቶች፣ አፍንጫ፣ አፍ፣ ዓይኖች፣ ቅንድቦች፣ ጆሮዎች፣ ምላስ፣ ከንፈሮች ትርጉም አላቸው" ካላችሁ በጥቅስ መሞገት እንጂ ከኪስ እየመዘዙ እንቶ ፈንቶ ማውራት ውኃ የማያነሳ እና የማይቋጥር ሙግት ነው። ምክንያቱም እነዚህ የአካል ክፍሎች ትርጉም መስጠት ሠለስቱ ምዕት ከልክለዋል፦
ሃይማኖተ አበው ምዕራፍ 19 ቁጥር 33
“ለእግዚአብሔር ዓይኖች እና ጆሮዎች እንዳሉት መጽሐፍት የተናገሩት እና የቀሩት እንዳሉት ስለ እግዚአብሔር የተነገረው ሁሉ የታመነ እውነተኛ እንደሆነ እናምናለን፥ ነገር ግን አይመረመርም አይታሰብም”።

"ሠለስቱ ምዕት" ማለት በ 325 ድኅረ ልደት በኒቂያ ጉባኤ የተሰበሰቡት 318 ሊቃውንት ናቸው፥ እነርሱ፦ "የቀሩት" ያሉት ከዓይኖች እና ከጆሮዎች ሌላ የተገለጹትን የአካል ክፍሎች ነው፦
ሃይማኖተ አበው ምዕራፍ 28 ቁጥር 30
“ለእግዚአብሔር ዓይን፣ ጆሮ፣ እጅ፣ እግር እንዳለው የተነገረው ሁሉ ስለ እግዚአብሔር በከበሩ መጻሕፍት የተጻፈ ሁሉ የታመነ የተረዳ ነው፥ የተናገርነው ሁሉ አለው። ነገር ግን አይመረመርም አይታወቅም”።

እርማችሁን አውጡ! ጆሮ፣ እጅ፣ እግር እንዳለ እንቅጩን ፍርጥ አርገው ተናግረዋል። ለእግዚአብሔር እጅ፣ ጥፍር፣ እግር እንዳለው አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ በመጽሐፈ ምሥጢር ተናግሯል፦
መጽሐፈ ምሥጢር ምዕራፍ 1 ቁጥር 62
“እግዚአብሔር እጆች እና ክንድ፣ ጥፍር እንዳለው ዕወቁ”።
ጭራሽ አዳም ላይ ያሉ የአካል ክፍሎች ሁሉ ሥላሴ ላይ እንዳሉ እና በተጠቃሽነት ራስ፣ ፊት፣ ጆሮዎች፣ ዓይኖች፣ አፍንጫ፣ ከንፈር፣ እጆች፣ እግሮች እና ብብቶች እንዳሉት መጽሐፈ ሜላድ በግልጽ እና በማያሻማ መልኩ አስቀምጦታል፦
መጽሐፈ ሜላድ ዘወርኃ ግንቦት ቁጥር 7
በአዳም ላይ ያለው መልክ ሁሉ በአብ፣ በወልድ እና በመንፈስ ቅዱስ ላይ አለ፥ ራስም ቢሆን፣ ገጽ(ፊት) ቢሆን፣ ጆሮዎች እና ዓይኖች ቢሆኑም፣ አፍንጫ እና ከንፈር ቢሆን፣ እጆች እና እግሮች፣ ብብቶች ቢሆኑ ለአብ፣ ለወልድ እና ለመንፈስ ቅዱስ ሙሉ አካል አላቸው። ሃይማኖታቸው የቀና ሦስት መቶ አሥራ ስምንቱ ሊቃውንት አባቶቻችን እንደተናገሩት ለእግዚአብሔር ዓይኖች፣ ጆሮዎች፣ እጆች እና እግሮች ሌሎች የቀሩት አካላት እንዳሉት እናምናለን።

መልአክ ሥላሴ የተባለው የኦርቶዶክስ መጽሐፍ ሥላሴ "ደም" "ወርች" "ጎን" "ከርስ" "ኩላሊት" "ወገብ" "አብራክ" "ተረከዝ" "ጫማ" "ጥፍር" "ጣት" እንዳላቸው ይናገራል፦
"ደም"
ሥሉስ ቅዱስ ሆይ! "ስርየተ ደማችሁ" ስርየተ ኃጢኣት ነውና የነፍሴን ቤት መቃን በስርየት "ደማችሁ" እርጩት።

"ወርች"
አብ፣ ወልድ፣ መንፈስ ቅዱስ ሆይ! የአዳምን ወርች ላጸና መለኮታዊ "ወርቾቻችሁ" ሰላምታ ይገባል።

"ጎን"
አብ፣ ወልድ፣ መንፈስ ቅዱስ ሆይ! የወርቅ አስፈላጊያቸው ላይደለ መለኮታዊ "ጎኖቻችሁ" ሰላምታ ይገባል።

"ከርስ"
“አብ፣ ወልድ፣ መንፈስ ቅዱስ ሆይ! የፍጡራንን ሆድ ለፈጠረ ለማይመረመር "ከርሳችሁ" ሰላምታ ይገባል።”

"ኩላሊት"
አብ፣ ወልድ፣ መንፈስ ቅዱስ ሆይ! በህላዌ አካል ትክክል ለሚሆኑ "ኩላሊታችሁ" ሰላምታ ይገባል።

"ወገብ"
አብ፣ ወልድ፣ መንፈስ ቅዱስ ሆይ! መታጠቂያው የቸርነት ሰቅ ለሆነው "ወገባችሁ" ሰላምታ ይገባል።

"አብራክ"
“አብ፣ ወልድ፣ መንፈስ ቅዱስ ሆይ! የፍጥረት ሁሉ አብራክ ለሚያሰግድ "አብራካችሁ" ሰላምታ ይገባል።

"ተረከዝ"
“አብ፣ ወልድ፣ መንፈስ ቅዱስ ሆይ! ብርሃናት ለተጎናፀፈው "ተረከዛችሁ" ሰላምታ ይገባል።

"ጫማ"
አብ፣ ወልድ፣ መንፈስ ቅዱስ ሆይ! ለሚራመድ "ጫማችሁ" ሰላምታ ይገባል።

"ጥፍር"
አብ፣ ወልድ፣ መንፈስ ቅዱስ ሆይ! "ከጥፍሮቻችሁ" ጋር ያለመነጣጠል ተባብረው ተመሳስለው ላሉ "ጣቶቻችሁ" ሰላምታ ይገባል።

"ወርች" ማለት ለከብት "የፊት እግር" ሲሆን ለሰው "ባት" ነው፣ "ከርስ" ማለት "ማኅፀን" ወይም "ሆድ" ማለት ነው፣ "አብራክ" ማለት ተራክቦ የሚደረግበት "የዘር ከረጢት ነው። "ደም" እና "ኩላሊት" ሥጋ ነው፥ ሌሎቹ ይሁኑ እሺ! "ከርስ" ምን ያረግላቸዋል? ምግብ ይበላሉ ወይስ ያረግዛሉ? "አብራክ" ምን ያረግላቸዋል? ተራክቦ ያረጋሉ? የእኛን ዓሣ ስትጎረጉሩ የእናንተን ዘንዶ አወጣንባችሁ።
አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይስጠን! አሚን።

ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
ዕቅበተ ኢሥላም

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

16፥125 ወደ ጌታህ መንገድ በጥበብ እና በመልካም ግሳጼ ጥራ፡፡ ادْعُ إِلَىٰ سَبِيلِ رَبِّكَ بِالْحِكْمَةِ وَالْمَوْعِظَةِ الْحَسَنَةِ

"ደዕዋህ” دَعْوَة የሚለው ቃል “ደዓ” دَعَا ማለትም “ጠራ” ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን “ጥሪ” ማለት ነው። ይህ ጥሪ ወደ አሏህ ሲሆን ሰዎች አሏህን ብቻ እንዲያመልኩ እና በእርሱ ላይ ማንንምና ምንንም ነገር እንዳያጋሩ በማስተማር ወደ አሏህ መጣራት “ደዕዋህ” دَعْوَة ይባላል፦
16፥125 ወደ ጌታህ መንገድ በጥበብ እና በመልካም ግሳጼ ጥራ፡፡ ادْعُ إِلَىٰ سَبِيلِ رَبِّكَ بِالْحِكْمَةِ وَالْمَوْعِظَةِ الْحَسَنَةِ

"ደፋዒያህ" دَفَاعِيَّة የሚለው ቃል "ዳፈዐ" دَافَعَ ማለትም "መከተ" "ዐቀበ" ከሚል ሥርወ ቃል የመጣ ሲሆን "ምከታ" "ዕቅበት" ማለት ነው፥ "ደፋዒየቱል ኢሥላም" دَفَاعِيَّة الإِسْلَام ማለት "መካቴ ኢሥላም" "ዕቅበተ ኢሥላም"Islamic apologetics" ማለት ነው።
ዕቅበተ ኢሥላም ሦስት እረድፍ አለው፦
1ኛ. አውንታዊ ትምህርት"affirmative teaching"
የኢሥላምን መልእክት ለሌሎች ማስተላለፍ፣
2ኛ. የመከላከል ትምህርት"defensive teaching"
በኢሥላም ላይ የሚሰነዘሩ ትችት መልስ መስጠት፣
3ኛ. የማጥቃት ትምህርት"offensive teaching"
የሌላ እምነት ተከታዮችን የሚያምኑበትን ነገር በማነጻጸር እውነትን መግለጥ እና ሐሰትን ማጋለጥ ነው።

ከዚህ ተነስተን ወሒድ ዕቅበተ ኢሥላም ማኅበር"Wahid islamic apologetics society" የዕቅበተ ኢሥላም ሥራ ከዐማርኛ ባሻገር፦
፨በኦሮምኛ፣
፨በትግሪኛ፣
፨በጉራጊኛ፣
፨በአፋሪኛ፣
፨በሱማሊኛ፣
፨በሲዳምኛ፣
፨በስልጥኛ፣
፨በሀላቢኛ፣
፨በከንባትኛ፣
፨በወላይትኛ፣
፨በኮንሴኛ፣
፨በሀዲይኛ ለመሥራት አስበናል። ኢንሻሏህ!
ይህንን ግምት ውስጥ አስገብታችሁ ከዐማርኛ ወደ ገዛ ቋንቋችሁ የመተርጎም ክህሎት ያላችሁ ልጆች ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን አድሚናት በውስጥ ያነጋግሩ፦
እኅት ረምላን፦ https://tttttt.me/REMLANEG
እኅት ሰላምን፦ http://tttttt.me/SeuweSe
አኅት ዘሃራን፦ https://tttttt.me/Zhara_mustefa
እኅት አበባ፦ http://tttttt.me/temariwalji
እኅት ነስርያን፦ https://tttttt.me/Nesriyaaa

ወጀዛኩሙሏህ ኸይራ!

ከማኅበሩ ድኅረ ምሩቃን እና የቦርድ
ልጅን አልያዘም

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

39፥4 አላህ ልጅን መያዝ በፈለገ ኖሮ ከሚፈጥረው ውስጥ የሚሻውን ይመርጥ ነበር፡፡ ጥራት ተገባው፡፡ እርሱ አሸናፊው አንዱ አላህ ነው፡፡ لَّوْ أَرَادَ اللَّهُ أَن يَتَّخِذَ وَلَدًا لَّاصْطَفَىٰ مِمَّا يَخْلُقُ مَا يَشَاءُ ۚ سُبْحَانَهُ ۖ هُوَ اللَّهُ الْوَاحِدُ الْقَهَّارُ

አምላካችን አሏህ በእርሱ ባሕርይ ላይ መውለድ እና መወለድ የለውም፥ "አሏህ ወለደ" ያሉት እነርሱም በእርግጥ ውሸታሞች ናቸው፦
112፥3 አልወለደም፤ አልተወለደምም፡፡ لَمْ يَلِدْ وَلَمْ يُولَدْ
37፥152 «አላህ ወለደ፡፡» አሉ፥ እነርሱም በእርግጥ ውሸታሞች ናቸው፡፡ وَلَدَ اللَّهُ وَإِنَّهُمْ لَكَاذِبُونَ
43፥15 ከባሮቹም ለእርሱ ቁራጭን ልጅ አደረጉለት፡፡ ሰው በእርግጥ ግልጽ ከሓዲ ነው፡፡ وَجَعَلُوا لَهُ مِنْ عِبَادِهِ جُزْءًا ۚ إِنَّ الْإِنسَانَ لَكَفُورٌ مُّبِينٌ

ከአንዱ አምላህ ባሕርይ ባሕርይን ወስዶ፣ ከአካሉ አካልን ወስዶ፣ እርሱን አህሎና መስሎ ከእርሱ ወጣ፣ ተወለደ፣ ተገኘ በማለት አሏህን ወላዲ መሢሑን ተወላዲ በማድረግ ለአሏህ ቁራጭን አደረጉለት።
ፈጣሪ እምቅድመ ዓለም "ወለደ" ከሚሉት በተጨማሪ አንዳንድ የክርስትና አንጃዎች "ፈጣሪ ልጅ ይዟል" የሚል አስተምህሮት በጥንት ጊዜ ነበረ፥ ለምሳሌ፦ ኖላዊ ዘሄርማስ(የሄርሜኑ እረኛ)፣ ኢቦናይታውያን ክርስቲያን እና በበባዛንታይኑ ቴዎዶስ እና በአንጾኪያው በጳውሎስ ሳምሳጤ የተጀመረው ዳይናሚክ ሞናርኪዝም"Adoptionism" ሁሉም "ፈጣሪ ልጅ ይዟል" ብለዋል። ነገር ግን አሏህ ምንም ልጅን አልያዘም፦
19፥88 «አር-ረሕማንም ልጅን ያዘ» አሉ፡፡ وَقَالُوا اتَّخَذَ الرَّحْمَـٰنُ وَلَدًا
23፥91 አላህ ምንም ልጅን አልያዘም፡፡ ከእርሱም ጋር አንድም አምላክ የለም፡፡ مَا اتَّخَذَ اللَّهُ مِن وَلَدٍ وَمَا كَانَ مَعَهُ مِنْ إِلَـٰهٍ

"ኢተኸዘ" اتَّخَذَ የሚሉት "ወለደ" وَلَدَ ከሚለውን እሳቤ ለመሸሽ ያመጡት እሳቤ ነው፥ "መያዝ" እና "መውለድ" ልዩነት አለው፦
28፥9 የፈርዖንም ሚስት፦ "ለእኔ ለአንተም የዓይኔ መርጊያ ነው፤ አትግደሉት፡፡ ሊጠቅመን ወይም "ልጅ አድርገን ልንይዘው ይከጀላልና" አለች፡፡ وَقَالَتِ امْرَأَتُ فِرْعَوْنَ قُرَّتُ عَيْنٍ لِّي وَلَكَ ۖ لَا تَقْتُلُوهُ عَسَىٰ أَن يَنفَعَنَا أَوْ نَتَّخِذَهُ وَلَدًا
12፥21 ያም ከምስር የገዛው ሰው ለሚስቱ፦ «መኖሪያውን አክብሪ! ሊጠቅመን ወይም "ልጅ አድርገን ልንይዘው" ይከጀላልና» አላት፡፡ وَقَالَ الَّذِي اشْتَرَاهُ مِن مِّصْرَ لِامْرَأَتِهِ أَكْرِمِي مَثْوَاهُ عَسَىٰ أَن يَنفَعَنَا أَوْ نَتَّخِذَهُ وَلَدًا

የፈርዖን ሚስት ለፈርዖን ስለ ሙሣ፦ "ልጅ አድርገን ልንይዘው ይከጀላል" ስትል "እንወልደዋለን" ማለቷ አይደለም፥ የተወለደን ልጅ ማደጎ አርጎ መያዟን የሚያመለክት ነው። በተመሳሳይ ዮሡፍን ያም ከምስር የገዛው ሰው ለሚስቱ፦ "ልጅ አድርገን ልንይዘው ይከጀላል" ሲላት "እንወልደዋለን" ማለቱ አይደለም፥ የተወለደን ልጅ ማደጎ አርጎ መያዟን የሚያመለክት ነው። እዚህ ድረስ ከተግባባን አሏህ በማደጎ ልጅ መያዝ አይፈልግም፥ ቢፈልግ ኖሮ ግን "ከ-ሚፈጥረው" ውስጥ መርጦ ይይዝ ነው፦
39፥4 አላህ ልጅን መያዝ በፈለገ ኖሮ "ከ-ሚፈጥረው" ውስጥ የሚሻውን ይመርጥ ነበር፡፡ ጥራት ተገባው፡፡ እርሱ አሸናፊው አንዱ አላህ ነው፡፡ لَّوْ أَرَادَ اللَّهُ أَن يَتَّخِذَ وَلَدًا لَّاصْطَفَىٰ مِمَّا يَخْلُقُ مَا يَشَاءُ ۚ سُبْحَانَهُ ۖ هُوَ اللَّهُ الْوَاحِدُ الْقَهَّارُ
"ከ-ሚፈጥረው" የሚለውን ይሰመርበት! "የኽሉቁ" يَخْلُقُ የሚለው ፊዕሉል ሙዷሪዕ "የተኺዘ" يَتَّخِذَ ከሚለው ጋር መምጣቱ በራሱ "መያዝ" ልክ እንደ መውለድ የባሕርይ ጉዳይ ሳይሆን ሳይወልዱ ወደ ራስ በማስጠጋት ከሚፈጥረው ፍጡራን መያዝ ነው፥ ጥራት ይገባው! እርሱ አሸናፊው አንዱ አሏህ ነው፡፡ በሌላ አንቀጽ ደግሞ "ከ-እኛ ዘንድ" በማለት እርሱ ዘንድ "ከ-ተፈጠሩ ፍጥረታት" መያዝ ቢፈልግ ልጅ መያዝ ይችል ነበር፥ ነገር ግን ጥራት ይገባው! ይህ ለእርሱ ተገቢ አይደለም፦
21፥17 መጫወቻን "ልንይዝ" ብንፈልግ ኖሮ "ከ-እኛ ዘንድ" በያዝነው ነበር፡፡ ግን ሠሪዎች አይደለንም፡፡ لَوْ أَرَدْنَا أَن نَّتَّخِذَ لَهْوًا لَّاتَّخَذْنَاهُ مِن لَّدُنَّا إِن كُنَّا فَاعِلِينَ

እዚህ አንቀጽ "መጫወቻ" ለሚለው የገባው ቃል "ለህው" لَهْو ሲሆን "መደሰቻ" "መጠቀሚያ" "የዓይን ማረፊያ እና መርጊያ" ማለት ነው፥ ልጅ ለወላጅ ሆነ ለአሳዳጊ መደሰቻ ነው።
21፥17 ላይ በመጀመሪያ መደብ ያለውን ሐረግ የሚፈታልን 39፥4 ላይ በሦስተኛ መደብ ያለው ሐረግ ነው፥ በመጀመሪያ መደብ "አረድና" أَرَدْنَا ብሎ በሦስተኛ መደብ "አራደ" أَرَادَ ይለናል። "ከእኛ ዘንድ" የሚለውን "ከ-ሚፈጥረው" በማለት ይፈታልናል፥ "ከእኛ ዘንድ" የሚለውን ሚሽነሪዎች "ከእኛ ውስጥ" በማለት የአሏህ እኛነትን ብዙ አካላት እንደሆነ ለማመልከት ያጭበረብሩበታል። ነገር ግን "ዘንድ" እና "ውስጥ" የሚባሉትን መስተዋድድ በቅጡ ካለመረዳት የመጣ የተሳከረ፣ የደፈረሰ፣ የተንሸዋረረ ምልከታ ነው፦
19፥5 «እኔም ከበኋላዬ ዘመዶቼን በእርግጥ ፈራሁ፡፡ ሚስቴም መካን ነበረች ስለዚህ "ከ-አንተ ዘንድ" ለእኔ ልጅን ስጠኝ፡፡ وَإِنِّي خِفْتُ الْمَوَالِيَ مِن وَرَائِي وَكَانَتِ امْرَأَتِي عَاقِرًا فَهَبْ لِي مِن لَّدُنكَ وَلِيًّا

ዘከሪያ፦ "ከ-አንተ ዘንድ" ሲል "ከ-አንተ ውስጥ" ማለቱ አልነበረም፥ ቅሉ ግን ልጅ ከአሏህ ዘንድ የሚሰጥ ነው። አሏህ ልክ እንደ ፈርዖን ሚስት እና እንደ ያም ከምስር እንደ ገዛው ሰው መጫወቻ ልጅ መያዝ ቢፈልግ ኖሮ ከሚፈጥረው መያዝ ይችል ነበር፥ ነገር ግን ይህ ለእርሱ ተገቢ እንዳልሆነ እራሱ ተናግሯል። "መጫወቻን ልንይዝ ብንፈልግ ኖሮ ከእኛ ዘንድ በያዝነው ነበር" ሲል ዐውደ ንባቡ ላይ ከፈጠራቸው እርሱ ዘንድ ያሉትም መላእክት ያመለክታል፥ ቁረይሾችም "አልረሕማንም ከመላእክት ልጅን ያዘ" ብለዋልና፦
21፥19 በሰማያትና በምድር ያለው ሁሉም የእርሱ ነው፡፡ "እርሱ ዘንድ" ያሉትም መላእክት" እርሱን ከማምለክ አይኮሩም፡፡ አይሰለቹምም፡፡ وَلَهُ مَن فِي السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضِ ۚ وَمَنْ عِندَهُ لَا يَسْتَكْبِرُونَ عَنْ عِبَادَتِهِ وَلَا يَسْتَحْسِرُونَ
21፥26 «አልረሕማንም ከመላእክት ልጅን ያዘ» አሉ፡፡ ጥራት ተገባው፡፡ አይደለም መላእክት የተከበሩ ባሮች ናቸው፡፡ وَقَالُوا اتَّخَذَ الرَّحْمَـٰنُ وَلَدًا ۗ سُبْحَانَهُ ۚ بَلْ عِبَادٌ مُّكْرَمُونَ

"እርሱ ዘንድ" "አንተ ዘንድ" "እኛ ዘንድ" የሚለው እርሱ ዘንድ ያሉትን ፍጡራን ለማመልከት የመጣ ነው፥ ጥቅሉ ግን በአሏህ ባሕርይ መውለድ የሚባል ባሕርይ ካለመኖር ባሻገር ሳይወልድ እንደ ማደጎ ከሚፈጥረው መጫወቻ ልጅ መያዝ አይፈልግም። አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛን ጽናቱን ይስጠን! አሚን።

ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
ዛፍ ይናገራልን?

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።

55፥6 ሐረግ እና ዛፍ ለእርሱ ይሰግዳሉ፡፡ وَالنَّجْمُ وَالشَّجَرُ يَسْجُدَانِ

ከጂን የኾኑ ጭፈሮች ቁርኣንን አዳምጠው "እኛ አስደናቂ የኾነን ቁርኣን ሰማንም" ማለታቸው ወደ ተወዳጁ ነቢያችን"ﷺ" ተወርዷል፦
72፥1 በል «እነሆ ከጂን የኾኑ ጭፈሮች ቁርኣንን አዳመጡ፡፡‹እኛ አስደናቂ የኾነን ቁርኣን ሰማንም› አሉ ማለት ወደ እኔ ተወረደ፡፡ قُلْ أُوحِيَ إِلَيَّ أَنَّهُ اسْتَمَعَ نَفَرٌ مِّنَ الْجِنِّ فَقَالُوا إِنَّا سَمِعْنَا قُرْآنًا عَجَبًا

"ተወረደ" ለሚለው የገባው የግሥ መደብ "ኡሒየ" أُوحِيَ ሲሆን "ወሕይ" وَحْي ማለት እራሱ "ግልጠተ መለኮት"Divine revelation" ማለት ነው፥ ከጂኒ የኾኑን ጭፍሮች ቁርኣንን የሚያዳምጡ ሆነው ወደ ነቢያችን"ﷺ" ዞረዋል፦
46፥29 ከጂኒ የኾኑን ጭፍሮች ቁርኣንን የሚያዳምጡ ሲኾኑ ወደ አንተ ባዞርን ጊዜም አስታውስ! በተጣዱትም ጊዜ "ዝም ብላችሁ አዳምጡ" ተባባሉ፡፡ በተጨረሰም ጊዜ አስጠንቃቂዎች ኾነው ወደ ሕዝቦቻቸው ተመለሱ፡፡ وَإِذْ صَرَفْنَا إِلَيْكَ نَفَرًا مِّنَ الْجِنِّ يَسْتَمِعُونَ الْقُرْآنَ فَلَمَّا حَضَرُوهُ قَالُوا أَنصِتُوا ۖ فَلَمَّا قُضِيَ وَلَّوْا إِلَىٰ قَوْمِهِم مُّنذِرِينَ

በተጨረሰም ጊዜ አስጠንቃቂዎች ኾነው ወደ ሕዝቦቻቸው ተመለሱ፥ በሌሊት ጂኒዎች ቁርኣንን መስማታቸውን ለነቢዩ"ﷺ" የተናገረው ዛፍ ነው፦
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 63 ሐዲስ 85
ዐብዱ ራሕማን እንደተረከው፦ "እኔም መሥሩቅን፦ "በሌሊት ጂኒዎች ቁርኣንን መስማታቸውን ለነቢዩ"ﷺ" ማን ነገራቸው? ብዬ ጠየኩት፥ እርሱም፦ "አባትህ ዐብደሏህ፦ "ለነቢዩ"ﷺ" ስለ እነርሱ የተናገረው ዛፍ ነው" አለኝ። حَدَّثَنِي عُبَيْدُ اللَّهِ بْنُ سَعِيدٍ، حَدَّثَنَا أَبُو أُسَامَةَ، حَدَّثَنَا مِسْعَرٌ، عَنْ مَعْنِ بْنِ عَبْدِ الرَّحْمَنِ، قَالَ سَمِعْتُ أَبِي قَالَ، سَأَلْتُ مَسْرُوقًا مَنْ آذَنَ النَّبِيَّ صلى الله عليه وسلم بِالْجِنِّ لَيْلَةَ اسْتَمَعُوا الْقُرْآنَ‏.‏ فَقَالَ حَدَّثَنِي أَبُوكَ ـ يَعْنِي عَبْدَ اللَّهِ ـ أَنَّهُ آذَنَتْ بِهِمْ شَجَرَةٌ‏.‏

ዛፍ በራሱ የሚናገር እና የሚሰማ ማንነት አይደለም፥ አምላካችን አሏህ ግን ዛፉን ጂኒዎች ቁርኣንን መስማታቸውን ለነቢዩ"ﷺ" እንዲናገር ካረገው በኃላ በቁርኣን ግልጠተ መለኮት ጂኒዎች "እኛ አስደናቂ የኾነን ቁርኣን ሰማንም" ማለታቸውን ወደ ነቢያችን"ﷺ" ወሕይ አድርጎ አወረደ እንጂ እናንተ እንደምትቀጥፉት ዛፉ አሏህ ሆኖ አይደለም። ዛፍ እራሱ ፍጡር ሆኖ ለአሏህ የሚሰግድ ተክል ነው፦
55፥6 ሐረግ እና ዛፍ ለእርሱ ይሰግዳሉ፡፡ وَالنَّجْمُ وَالشَّجَرُ يَسْجُدَانِ

አሏህ ዛፍን እንዲናገር ማድረጉ ከገረማችሁ እና የሐዲሱን አሳብ ማጣመም ከፈለጋችሁ እንግዲያውስ "እባቡ ሰይጣን ነው" ማለት ነው፦
ዘፍጥረት 3፥1 እባብም ያህዌህ አምላክ ከፈጠረው ከምድር አውሬ ሁሉ ይልቅ "ብልህ" ነበረ። וְהַנָּחָשׁ֙ הָיָ֣ה עָר֔וּם מִכֹּל֙ חַיַּ֣ת הַשָּׂדֶ֔ה אֲשֶׁ֥ר עָשָׂ֖ה יְהוָ֣ה אֱלֹהִ֑ים

በዐማርኛ ትርጉም ላይ "ተንኮለኛ" ብለው ያስቀመጡት የዕብራይስጡ ቃል "አሩም" עָרוּם ሲሆን "ብልህ"prudent" ማለት ነው፥ ምሳሌ 12፥23 ተመልከት! እባቡ የምድር አውሬ ነው። ሴቲቱን ሲያነጋግር የነበረውም ይህ የምድር አውሬ ነው፥ ሴቲቱን ስላሳሳተ ተብሎ የተረገመው ይህ እባብ ነው፦
ዘፍጥረት 3፥14 ያህዌ አምላክም እባቡን አለው፦ "ይህን ስላደረግህ ከእንስሳት ከምድር አራዊትም ሁሉ ተለይተህ አንተ የተረገምህ ትሆናለህ፤ በሆድህም ትሄዳለህ፥ አፈርንም በሕይወትህ ዘመን ሁሉ ትበላለህ"።

የዘፍጥረት ዐውደ ንባቡን"contextual passage" ውስጥ ስለ ሰይጣን የሚናገር ምንም ሽታው የለው። ስድሳ ስድስቱ መጽሐፍ ላይ ዲያብሎስ አዳምን እና ሔዋንን እንዳሳሳተ የሚናገር ምንም ጥቅስ የለም፥ ነገር ግን መቃቢያን ላይ ዲያብሎስ አዳምን እና ሔዋንን ሸንግሎ እንዳሳሳታቸው ይናገራል፦
1ኛ መቃብያን 19፥6 ዲያብሎስም “እንደ ፈጣሪያችሁ እንደ እግዚአብሔር ትሆናላችሁ” ብሎ ሸንግሎ አባታችን አዳምን እና እናታችንን ሔዋንን ወደ እርሱ ስሕተት ወሰዳቸው።

ዲያብሎስ የምድር አውሬ የሆነው እባብ ነውን? ዲያብሎስ ጥንተ ተፈጥሮው ከጂን ወይም እንደ እናንተ እምነት ከመላእክት አይደለምን? መልሱ፦ "እባቡ ዲያብሎስ ሳይሆን ዲያብሎስ በእባቡ ተጠቅሞ አሳሳታቸው" ከሆነ እንግዲያውስ ዛፉ አሏህ ሆኖ ሳይሆን አሏህ ዛፉን እንዲናገር ማድረግ ምን ያቅተዋል? በባይብል እኮ ፈጣሪ አህያ እና ድንጋይ እንዲናገሩ የሚያደርግ ነው፦
2 ጴጥሮስ 2፥16 ቃል የሌለው "አህያ" በሰው ቃል ተናግሮ የነቢዩን እብድነት አገደ።
ኢያሱ 24፥27 እነሆ የተናገረንን የያህዌን ቃል ሁሉ ሰምቶአልና "ይህ ድንጋይ" ይመሰክርብናል።

ድንጋይ በጥንተ ተፈጥሮው የሚሰማ እና የሚናገር እንዳልሆነ ቅቡል ቢሆንም ቅሉ ግን በተአምር የያህዌን ቃል ሰምቶ መናገሩ እሙን ነው። አሏህ በትንሳኤ ቀን እኮ መስማት እና መናገር የማይችለውን የሰውን ቆዳ እንዲሰማ እና እንዲናገር ያደርጋል፦
41፥21 ለቆዳዎቻቸውም «በእኛ ላይ ለምን መሰከራችሁብን?» ይላሉ፡፡ «ያ አንዳቹን ነገር ሁሉ ያናገረው አላህ አናገረን፡፡ እርሱም በመጀመሪያ ጊዜ ፈጠራችሁ፡፡ ወደእርሱም ትመለሳላችሁ» ይሏቸዋል፡፡ وَقَالُوا لِجُلُودِهِمْ لِمَ شَهِدتُّمْ عَلَيْنَا ۖ قَالُوا أَنطَقَنَا اللَّهُ الَّذِي أَنطَقَ كُلَّ شَيْءٍ وَهُوَ خَلَقَكُمْ أَوَّلَ مَرَّةٍ وَإِلَيْهِ تُرْجَعُونَ

ስለዚህ "ዛፍ እንዴት ይናገራል" ተብሎ መታመስ እና መተራመስ አስፈላጊ አይደለም። አምላካችን አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይስጠን! አሚን።

ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም