ወሒድ የዕቅበተ ኢሥላም መጣጥፍት"Wahid Articles of Islamic Apologetics"
58.3K subscribers
68 photos
69 videos
19 files
1.72K links
ዳዒ ወሒድ በኢሥላም እና በክርስትና መካከል ያለውን ልዩነት እና አንድነት በንጽጽር የሚያስቀምጥ ወንድም ነው። ለዚህም የቋንቋ፣ የሰዋስው፣ የዐውድ፣ የተዛማች እና የሥነ አመክንዮ ሙግት በማቅረብ የሚታወቅ ተሟጋች እና ጦማሪ ነው። ለሙግቱ ነጥብ በዋነኝነት የሚጠቀምባቸው ቋንቋ ዐማርኛ፣ ግዕዝ፣ እንግሊዝኛ፣ ዐረቢኛ፣ ዕብራይስጥ እና ግሪክ ናቸው። መልካም የንባብ፣ የጥናት፣ የማነጻጸር ጊዜ ይሁንልዎ!
Download Telegram
ነጃሺይ

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ፥ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

5፥83 *"ወደ መልክተኛውም የተወረደውን ቁርኣን በሰሙ ጊዜ እውነቱን ከማወቃቸው የተነሳ ዓይኖቻቸው እንባን ሲያፈሱ ታያለህ፡፡ «ጌታችን ሆይ! አመንን ከመስካሪዎቹም ጋር ጻፈን » ይላሉ"*፡፡ وَإِذَا سَمِعُوا مَا أُنزِلَ إِلَى الرَّسُولِ تَرَىٰ أَعْيُنَهُمْ تَفِيضُ مِنَ الدَّمْعِ مِمَّا عَرَفُوا مِنَ الْحَقِّ ۖ يَقُولُونَ رَبَّنَا آمَنَّا فَاكْتُبْنَا مَعَ الشَّاهِدِينَ

"አል-ሐበሻህ" الْحَبَشَة ማለት "አሰባሳቢው" ማለት ሲሆን የመን ከሚኖሩ በመህራህ ሕዝቦች መካከል ሲኖሩ "የዕጣን አሰባሳቢዎች" ይባሉ የነበሩ ናቸው። "አል-ሐበሻህ" የመን ከሚኖሩ ከመህራህ ሕዝቦች ወደ ሰሜኑ ክፍል የተሰበሰቡ ሴማዊ ሕዝቦች መጠሪያ ነው። ስለ አል-ሐበሻህ በግርድፉና በሌጣው ካየን ዘንዳ ቁርኣን ሲወርድ በአል-ሐበሻህ ውስጥ ስለ ነገሠው ንጉሥ ደርዝና ፈርጅ ባለው መልኩ እንዳስሳለን።
"ነጃሺይ" نَّجَاشِيَّ ማለት "ንጉሥ" ማለት ሲሆን ወደ ጠቃሽ አመልካች መስተአምር "አል" ال ተደርጎ ሲነበብ "አን-ነጃሺይ" النَّجَاشِيَّ ሲሆን "ንጉሡ"the king" ማለት ነው። ይህ ንጉሥ እንደ ጎርጎሮሳውያን አቆጣጠት ከ 614–631 ድኅረ-ልደት በአክሱም መንግሥት የነገሠ ንጉሥ ነው፥ ስሙም በዐረቢኛ አነባነብ "አስሐማህ" أَصْحَمَة ሲባል፥ በአገራችን "አርማህ" ይባላል። "ንጉሥ አርማህ" በነቢያችን"ﷺ" ሐዲስ በጥቅሉ "አስሐማህ አን-ነጃሺይ" أَصْحَمَةَ النَّجَاشِيِّ ይባላል። ይህ ንጉሥ የነቢያችን"ﷺ" ባልደረቦች ከ 615–616 ድኅረ-ልደት ተቀብሎ አስተናግዷል፥ እንዲሁ እርሱ እና ሹማምንቱ ወደ መልክተኛውም የተወረደውን ሱረቱል መርየምን በሰሙ ጊዜ እውነቱን ከማወቃቸው የተነሳ ዓይኖቻቸው እንባን አንብተዋል፦
5፥83 *"ወደ መልክተኛውም የተወረደውን ቁርኣን በሰሙ ጊዜ እውነቱን ከማወቃቸው የተነሳ ዓይኖቻቸው እንባን ሲያፈሱ ታያለህ፡፡ «ጌታችን ሆይ! አመንን ከመስካሪዎቹም ጋር ጻፈን » ይላሉ"*፡፡ وَإِذَا سَمِعُوا مَا أُنزِلَ إِلَى الرَّسُولِ تَرَىٰ أَعْيُنَهُمْ تَفِيضُ مِنَ الدَّمْعِ مِمَّا عَرَفُوا مِنَ الْحَقِّ ۖ يَقُولُونَ رَبَّنَا آمَنَّا فَاكْتُبْنَا مَعَ الشَّاهِدِينَ

የንጉሡ መሥለም የኢሥላም ጠል"Islamophobia" አቀንቃኝ የሆነው ዲያቆን ዳንኤል ክብረት እንደዋሸው የአክራሪዎች ፈጠራ ሳይሆን "ጌታችን ሆይ! አመንን ከመስካሪዎቹም ጋር ጻፈን" ብለው በቁርኣኑ ማመናቸውን አምላካችን አላህ በቅዱስ ቃሉ እንደነገረን ነው። ከመጽሐፉም ባለቤቶች ለአላህ ፈሪዎች በአላህ አንቀጾችም ጥቂትን ዋጋ የማይለወጡ እነ ነጃሺይ እና ሹማምንቱ በአላህ እና በዚያ ወደ እኛ በተወረደው ቁርኣን አምነዋል፦
3፥199 *"ከመጽሐፉም ባለቤቶች ለአላህ ፈሪዎች በአላህ አንቀጾችም ጥቂትን ዋጋ የማይለወጡ ሲኾኑ በአላህ እና በዚያ ወደ እናንተ በተወረደው፥ በዚያም ወደ እነርሱ በተወረደው የሚያምኑ ሰዎች አሉ፡፡ እነዚያ ለእነርሱ በጌታቸው ዘንድ ምንዳቸው አላቸው*፡፡ አላህ ምርመራው ፈጣን ነው፡፡ وَإِنَّ مِنْ أَهْلِ الْكِتَابِ لَمَن يُؤْمِنُ بِاللَّهِ وَمَا أُنزِلَ إِلَيْكُمْ وَمَا أُنزِلَ إِلَيْهِمْ خَاشِعِينَ لِلَّهِ لَا يَشْتَرُونَ بِآيَاتِ اللَّهِ ثَمَنًا قَلِيلًا ۗ أُولَـٰئِكَ لَهُمْ أَجْرُهُمْ عِندَ رَبِّهِمْ ۗ إِنَّ اللَّهَ سَرِيعُ الْحِسَابِ

በአላህ እና በዚያ ወደ እኛ በተወረደው ቁርኣን ካመኑ ሠልመዋል ማለት ነው። በነቢያችንም"ﷺ" ሐዲስ ላይ ነቢያችን"ﷺ" ነጃሺይ ከመስለምም አልፎ ጻዲቅ ሰው እንደሆነ ነግረውናል፦
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 63, ሐዲስ 103
ጃቢር እንደተረከው፦ "አን-ነጃሺይ በሞተ ጊዜ "ነቢዩም"ﷺ" አሉ፦ *"ዛሬ ጻዲቅ ሰው ሞቷል፥ ተነሱ! ለወንድማችሁ ለአስሐማህ የግንዘት ጸሎት አድርጉ!"*። عَنْ جَابِرٍ ـ رضى الله عنه ـ قَالَ النَّبِيُّ صلى الله عليه وسلم حِينَ مَاتَ النَّجَاشِيُّ ‏ "‏ مَاتَ الْيَوْمَ رَجُلٌ صَالِحٌ، فَقُومُوا فَصَلُّوا عَلَى أَخِيكُمْ أَصْحَمَةَ

"ሷሊሕ" صَالِح ማለት "መልካም" ወይም ጻዲቅ" ማለት ሲሆን የሷሊሕ ብዙ ቁጥር "ሷሊሒን" صَّالِحِين ማለትም "መልካሞች" ወይም "ጻድቃን" ማለት ነው፦
3፥114 በአላህና በመጨረሻው ቀን ያምናሉ፡፡ በጽድቅ ነገርም ያዛሉ፡፡ ከመጥፎ ነገርም ይከለክላሉ፡፡ በበጎ ሥራዎችም ይጣደፋሉ፡፡ እነዚያም ከመልካሞቹ ናቸው፡፡ يُؤْمِنُونَ بِاللَّهِ وَالْيَوْمِ الْآخِرِ وَيَأْمُرُونَ بِالْمَعْرُوفِ وَيَنْهَوْنَ عَنِ الْمُنكَرِ وَيُسَارِعُونَ فِي الْخَيْرَاتِ وَأُولَـٰئِكَ مِنَ الصَّالِحِينَ
2፥130 ከኢብራሂምም ሕግጋት እራሱን የበደለ ሰው ካልኾነ በስተቀር የሚያፈገፍግ ማነው? ማንም የለም። በቅርቢቱም ዓለም በእርግጥ መረጥነው፥ *በመጨረሻይቱም ዓለም እርሱ ከመልካሞቹ ነው*፡፡ وَمَن يَرْغَبُ عَن مِّلَّةِ إِبْرَاهِيمَ إِلَّا مَن سَفِهَ نَفْسَهُ ۚ وَلَقَدِ اصْطَفَيْنَاهُ فِي الدُّنْيَا ۖ وَإِنَّهُ فِي الْآخِرَةِ لَمِنَ الصَّالِحِينَ

አስሐማህ አን-ነጃሺይ "ሷሊሕ" መባሉን አስተውል። ከዚያ በመቀጠል እርሱ የነቢያችን"ﷺ" ባልደረቦች የሃይማኖት ወንድም ስለሆነ "አኺኩም" أَخِيكُمْ ማለትም "ወንድማችሁ" ተብሏል። ምእመናን ደግሞ ወንድማማቾች ናቸው፦
49፥10 *"ምእመናን ወንድማማቾች ናቸው"*፡፡ إِنَّمَا الْمُؤْمِنُونَ إِخْوَةٌ
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 63, ሐዲስ 106
አቢ ሁረይራህ"ረ.ዐ." እንደተረከው፦ "የአላህ መልእክተኛም"ﷺ" ለባልደረቦቻቸው ስለ ስለዚያ ቀን ስለሞተበት ስለ ሐበሻው አን-ነጃሺይ ሞት እንደነገሯቸው፦ *"ለወንድማችሁ ኢሥቲግፋር አርጉ!"*። أَنَّ أَبَا هُرَيْرَةَ ـ رضى الله عنه ـ أَخْبَرَهُمَا أَنَّ رَسُولَ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم نَعَى لَهُمُ النَّجَاشِيَّ صَاحِبَ الْحَبَشَةِ فِي الْيَوْمِ الَّذِي مَاتَ فِيهِ، وَقَالَ ‏ "‏ اسْتَغْفِرُوا لأَخِيكُمْ ‏"‌‏
በኢሥላም "ሶላቱል ጀናዛህ" صَلَاة الجَنَازَة ማለትም "የግንዘት ጸሎት" የሚደረገው ለሙሥሊም ብቻ ነው። ለንጉሥ አርማህ ደግሞ የሶላቱል ጀናዛህ ክፍል የሆነው "ሶላቱል ጋኢብ" صَلَاة الغَائِبٌ ማለትም "የሩቅ ጀናዛህ" ተደርጓል፦
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 63, ሐዲስ 105
ጃቢር አብኑ ዐብደሏህ እንደተረከው፦ "ነቢዩም"ﷺ" አስሐማህ አን-ነጃሺይ ላይ የግንዘት ጸሎት አድርገዋል፥ አራት ተክቢራህ በእርሱ ላይ አድርገዋል"*። عَنْ جَابِرِ بْنِ عَبْدِ اللَّهِ ـ رضى الله عنهما أَنَّ النَّبِيَّ صلى الله عليه وسلم صَلَّى عَلَى أَصْحَمَةَ النَّجَاشِيِّ، فَكَبَّرَ عَلَيْهِ أَرْبَعًا‏

ከላይ የተዘረዘሩት ሐዲሳት ንጉሥ አርማህ የአላህ ጥሪ ተውሒድን እንደተቀበለ ፍንትውና ቁልጭ አድርጎ ያሳያሉ። ስለዚህ የኢሥላም ጠል አቀንቃኝ የሆነው ዲያቆን ዳንኤል ክብረት በማኅበራዊ መገናኛ-ብዙኃን ላይ የነዛው ጨባጣና ለማጣ ወሬ እንዲህ ድባቅ ይገባል። አስሐማህ አን-ነጃሺይ መሥለሙ በዓለም የሚገኝ መላው ሙሥሊም ሁሉ የሚቀበለው እውነታ ነው። ይህን እውነታ አለመቀበል ትችላለክ፥ ግን ይህ ትርክት የአክራሪዎች እንጂ የሁሉም ሙሥሊም እንዳይደለ ለመቅጠፍ የሞከርከው ቅጥፈት ለዛሬ አልተሳካልህም። በአፈ-ጮሌነት ቤተ-መንግሥት እንደገባከው በአፈ-ጮሌነት ጀነት አትገባም። አላህ ሂዳያህ ይስጥህ፥ ለእኛም ጽናቱን! አሚን።

ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
ሙሲባህ

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

42፥30 *”ከመከራም ማንኛውም ያገኛችሁ ነገር እጆቻችሁ በሠሩት ምክንያት ነው”*፡፡ ከብዙውም ይቅር ይላል፡፡ وَمَا أَصَابَكُم مِّن مُّصِيبَةٍ فَبِمَا كَسَبَتْ أَيْدِيكُمْ وَيَعْفُو عَن كَثِيرٍ

አላህ “አል-ዐሊም” العَلِيم ማለትም “ሁሉን ዐዋቂ ነው፤ “ዒልም” عِلْم ማለትም “ዕውቀት” ደግሞ የእርሱ ባህርይ ነው፤ አላህ ሁሉን ነገር ያካበበው በዕውቀቱ ነው፦
65፥12 አላህ በነገር ሁሉ ቻይ መሆኑን አላህም *በነገሩ ሁሉ በእውቀት ያካበበ መሆኑን ታውቁ ዘንድ ይህንን አሳወቃችሁ*። أَنَّ اللَّهَ عَلَىٰ كُلِّ شَيْءٍ قَدِيرٌ وَأَنَّ اللَّهَ قَدْ أَحَاطَ بِكُلِّ شَيْءٍ عِلْمًا

እዚህ አንቀፅ ላይ የምንመለከተው የአላህ “ዕውቀት” እና “ሸይእ” شَيْء ማለት “ነገር’thing” ሁለት ጉዳዮች መሆናቸውን ነው፥ “ዕውቀት” ምንም ነገር ሳይኖር የአላህ ባህርይ ሲሆን “ነገር” ደግሞ “ፍጡር” ነው፥ “ነገር” ደግሞ ጊዜና ቦታ ሁሉ ነው። አምላካችን አላህ ስለ አንድ ነገር ዕውቀት በመጽሐፍ ውስጥ ከሁሉ ነገር መከሰት፣ መደረግ እና መከናወን በፊት መዝግቦቷል፦
50፥4 ከእነርሱ ምድር የምታጎድለውን በእርግጥ *ዐውቀናል፡፡ እኛም ዘንድ ጠባቂ መጽሐፍ አለ*፡፡ قَدْ عَلِمْنَا مَا تَنقُصُ الْأَرْضُ مِنْهُمْ ۖ وَعِندَنَا كِتَابٌ حَفِيظٌ
22፥70 አላህ *በሰማይና በምድር ውስጥ ያለን ሁሉ በእርግጥ የሚያውቅ መኾኑን አታውቅምን? ይህ በመጽሐፍ ውስጥ የተመዘገበ ነው*፡፡ ይህ በአላህ ላይ ገር ነው፡፡ أَلَمْ تَعْلَمْ أَنَّ اللَّهَ يَعْلَمُ مَا فِي السَّمَاءِ وَالْأَرْضِ ۗ إِنَّ ذَٰلِكَ فِي كِتَابٍ ۚ إِنَّ ذَٰلِكَ عَلَى اللَّهِ يَسِيرٌ
ኢማም ቡኻሪይ መጽሐፍ 54, ሐዲስ 414
የአላህ መልእክተኛ”ﷺ” አሉ፦ በመጀመሪያ ምንም ነገር ሳይኖር አላህ ነበረ፤ ከዚያ ዙፋኑን በውሃ ላይ ነበረ፤ *ከዚያ ሁሉን ነገር በመጽሐፍ ጻፈ*፤ ከዚያ ሰማያትንና ምድርን ፈጠረ። كَانَ اللَّهُ وَلَمْ يَكُنْ شَىْءٌ غَيْرُهُ، وَكَانَ عَرْشُهُ عَلَى الْمَاءِ، وَكَتَبَ فِي الذِّكْرِ كُلَّ شَىْءٍ، وَخَلَقَ السَّمَوَاتِ وَالأَرْضَ ‏”‌‏.

“ለውሐል መሕፉዝ” لَوحَ المَّحْفُوظ ማለት “የተጠበቀው ሰሌዳ”preserved tablet” ማለት ሲሆን አላህ በለውሐል መሕፉዝ ላይ ድርጊቱን የከተበው ስለሚያውቀው እንጂ እንዲከናወን አይደለም።
ለምሳሌ ሀራም ነገር ማድረግ ከልክሏል፤ ያንን የከለከለው አንድ ሰው ከማድረጉ በፊት አላህ የከተበው ስለሚያውቀው እንጂ ያ ሰው እንዲያደርገው አይደለም፤ ያ ቢሆንማ አላህ እንዲያደርግ መከልከሉና በማድረጉ መቅጣቱ ትርጉም አይኖረውም ነበር። ስለዚህ አምላካችን አላህ አንድ ክስተት ከመከሰቱ ቢፊት፣ አንድ ድርጊት ከመደረጉ በፊት፣ አንድ ክንውን ከመከናወኑ በፊት ስለሚያውቀው ያንን ዕውቀት በተጠበቀው ሰሌዳ ከትቦታል፦
57፥22 በምድርም በነፍሶቻችሁም መከራ ማንንም አትነካም *ሳንፈጥራት በፊት በመጽሐፍ የተመዘገበች ብትኾን እንጅ*፡፡ ይህ በአላህ ላይ ገር ነው፡፡ مَا أَصَابَ مِن مُّصِيبَةٍ فِي الْأَرْضِ وَلَا فِي أَنفُسِكُمْ إِلَّا فِي كِتَابٍ مِّن قَبْلِ أَن نَّبْرَأَهَا ۚ إِنَّ ذَٰلِكَ عَلَى اللَّهِ يَسِيرٌ

“ሙሲባህ” مُّصِيبَة ማለት “መከራ” ማለት ሲሆን ይህ ሙሲባህ ክስተት ሆኖ ከመከሰቱ ቢፊት፣ ድርጊት ሆኖ ከመደረጉ በፊት፣ ክንውን ሆኖ ከመከናወኑ በፊት አላህ ስለዚያ ሙሲባህ ስለሚያውቀው ያንን ዕውቀት በተጠበቀው ሰሌዳ ከትቦታል። ያ ሙሲባህ የሚከሰተው አላህ ስለፈቀደ ነው፦
64፥11 *”መከራም ማንንም አይነካም በአላህ ፈቃድ ቢኾን እንጅ”*፤ በአላህም የሚያምን ሰው ልቡን ለትዕግስት ይመራዋል፤ አላህም ነገሩን ሁሉ ዐዋቂ ነው፡፡ مَا أَصَابَ مِن مُّصِيبَةٍ إِلَّا بِإِذْنِ اللَّهِ ۗ وَمَن يُؤْمِن بِاللَّهِ يَهْدِ قَلْبَهُ ۚ وَاللَّهُ بِكُلِّ شَيْءٍ عَلِيمٌ

የአላህ ፈቃድ በሁለት መልክ ለፍጡራን ተቀድሯል፤ አንዱ ያለፈቃዳቸው ሲሆን ሁለተኛው በተሰጣቸው ነጻ ፈቃድ ላይ ነው። የመጀመሪያው ፍጥረት ሲፈጠር ያለፈቃዱ በአላህ ፈቃድ የተፈጠረ ነው። ሰው በመወለድ፣ በሞት፣ በመተኛት፣ በማስነጠስ ምርጫ የለውም፦
28፥68 *ጌታህም የሚሻውን ይፈጥራል፤ ይመርጣልም፡፡ ለእነርሱ ለፍጡራን ምርጫ የላቸውም*፡፡ وَرَبُّكَ يَخْلُقُ مَا يَشَاءُ وَيَخْتَارُ ۗ مَا كَانَ لَهُمُ الْخِيَرَة

ለምሳሌ ሞት ሙሲባህ ነው፤ ግን መሞት አያስጠይቅም አያስቀጣም። ሁለተኛው ሙሲባህ ግን በተሰጠው ነጻ ፈቃድና ምርጫ የምናመጣው ስለሆነ ያስጠይቃል፦
21፥23 *ከሚሠራው ሁሉ አይጠየቅም፡፡ እነርሱ ፍጥረቶቹ ግን ይጠየቃሉ*፡፡ لَا يُسْأَلُ عَمَّا يَفْعَلُ وَهُمْ يُسْأَلُونَ
16፥93 *ትሠሩት ከነበራችሁትም ሁሉ በእርግጥ ትጠየቃላችሁ*፡፡ وَلَتُسْأَلُنَّ عَمَّا كُنتُمْ تَعْمَلُون
102፥8 ከዚያም *ከጸጋችሁ ሁሉ በዚያ ቀን ትጠየቃላችሁ*። ثُمَّ لَتُسْأَلُنَّ يَوْمَئِذٍ عَنِ النَّعِيمِ

“ነዒም” نَّعِيمِ ማለት “ጸጋ” ማለት ነው፤ በተሰጠን ነጻ ፈቃድና ምርጫ የምንሰራው መልካም ሥራ ሆነ ክፉ ሥራ ያስጠይቀናል ወይም ያስመነዳናል። ሁሉም ሙሲባህ ሳይሆን በተሰጠን ነጻ ምርጫ ከሙሲባህ የሚነካን እጆቻችን በሠሩት ፈሣድ ነው፦
42፥30 *”ከመከራም ማንኛውም ያገኛችሁ ነገር እጆቻችሁ በሠሩት ምክንያት ነው”*፡፡ ከብዙውም ይቅር ይላል፡፡ وَمَا أَصَابَكُم مِّن مُّصِيبَةٍ فَبِمَا كَسَبَتْ أَيْدِيكُمْ وَيَعْفُو عَن كَثِيرٍ
30፥41 *”የሰዎች እጆች በሠሩት ኃጢኣት ምክንያት የዚያን የሠሩትን ከፊሉን ያቀምሳቸው ዘንድ መከራው በየብስና በባሕር ተሰራጨ”*፡፡ እነርሱ ሊመለሱ ይከጀላልና፡፡ ظَهَرَ الْفَسَادُ فِي الْبَرِّ وَالْبَحْرِ بِمَا كَسَبَتْ أَيْدِي النَّاسِ لِيُذِيقَهُم بَعْضَ الَّذِي عَمِلُوا لَعَلَّهُمْ يَرْجِعُونَ
“ኃጢኣት” ተብሎ የተቀመጠው ቃል “ፈሣድ” ሲሆን “ፈሣድ” فَسَاد ማለት “ጥፋት” “ብክለት” “ብልሽት” ማለት ነው፥ ይህንን ድርጊት የሚተገብሩ ግለሰቦች ደግሞ “ሙፍሢድ” مُفْسِد ማለትም “አጥፊ” “አበላሺ” “በካይ” ይባላሉ። ሙሲባህ ሳይሆን “ከ”ሙሲባህ ሰዎችን የሚያገኘው የሰዎች እጆች በሠሩ ፈሣድ ነው። ለምሳሌ በምድሪቱ ላይ ረሃብ ያለው ምግብ ታጥቶ አሊያም ለእህል የሚሆን ተስማሚ የእርሻ ቦታ ታጥቶ ሳይሆን ክፋት፣ ጭካኔ፣ ስግብግብነት፣ ጥላቻ ስላለ ነው። በምድሪቱ ላይ ድህነት ያለው 80% የሚሆነውን የምድራችን ሃብት 20% የሚሆኑ የምድራችም ሃብታሞች በሞኖፓልና በስግብግብነት ስለያዙት ነው።
አላህም በሰጠህ ሀብት የመጨረሻይቱን አገር ፈልግ፤ ከቅርቢቱም ዓለም ፋንታህን አትርሳ፥ አላህም ወደ አንተ መልካምን እንዳደረገልህ ለሰዎች መልካምን አድርግ፤ በምድርም ውስጥ ፈሣድን አትፈልግ፡፡ አላህ ሙፍሠዲንን አይወድምና፦
28፥77 *”አላህም በሰጠህ ሀብት የመጨረሻይቱን አገር ፈልግ፤ ከቅርቢቱም ዓለም ፋንታህን አትርሳ፤ አላህም ወደ አንተ መልካምን እንዳደረገልህ ለሰዎች መልካምን አድርግ፤ በምድርም ውስጥ ማጥፋትን አትፈልግ፡፡ አላህ አጥፊዎችን አይወድምና”*። وَابْتَغِ فِيمَا آتَاكَ اللَّهُ الدَّارَ الْآخِرَةَ ۖ وَلَا تَنسَ نَصِيبَكَ مِنَ الدُّنْيَا ۖ وَأَحْسِن كَمَا أَحْسَنَ اللَّهُ إِلَيْكَ ۖ وَلَا تَبْغِ الْفَسَادَ فِي الْأَرْضِ ۖ إِنَّ اللَّهَ لَا يُحِبُّ الْمُفْسِدِينَ

ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
እውነተኛ አምላክ

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ፥ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።

28፥75 ከሕዝቦችም ሁሉ መስካሪን እናወጣለን፡፡ *"ያን ጊዜ እውነተኛውም አምላክነት ለአላህ ብቻ መኾኑን ያውቃሉ"*፡፡ ይቀጣጥፉት የነበሩትም ከእነርሱ ይጠፋቸዋል፡፡ وَنَزَعْنَا مِن كُلِّ أُمَّةٍ شَهِيدًا فَقُلْنَا هَاتُوا بُرْهَانَكُمْ فَعَلِمُوا أَنَّ الْحَقَّ لِلَّهِ وَضَلَّ عَنْهُم مَّا كَانُوا يَفْتَرُونَ

እውነተኛ አምላክ አንዱ አምላክ አላህ ብቻ ነው። ክርስቲያኖች፦ "ኢየሱስ እውነተኛ አምላክ ነው" ይላሉ። የትንሳኤ ቀን እውነተኛውም አምላክነት ለአላህ ብቻ መኾኑን ያውቃሉ፥ ይቀጣጥፉት የነበሩትም ከእነርሱ ይጠፋቸዋል፦
28፥75 ከሕዝቦችም ሁሉ መስካሪን እናወጣለን፡፡ *"ያን ጊዜ እውነተኛውም አምላክነት ለአላህ ብቻ መኾኑን ያውቃሉ"*፡፡ ይቀጣጥፉት የነበሩትም ከእነርሱ ይጠፋቸዋል፡፡ وَنَزَعْنَا مِن كُلِّ أُمَّةٍ شَهِيدًا فَقُلْنَا هَاتُوا بُرْهَانَكُمْ فَعَلِمُوا أَنَّ الْحَقَّ لِلَّهِ وَضَلَّ عَنْهُم مَّا كَانُوا يَفْتَرُونَ

ኢየሱስ በአንድ ወቅት ወደ አምላኩ ሲጸልይ እውነተኛ አምላክ ብቻውን የሆነው አምላኩ እንደሆነ ተናግሯል፦
ዮሐንስ 17፥3 *"እውነተኛ አምላክ ብቻህን የሆንህ አንተን እና የላክኸውን ኢየሱስ ክርስቶስን ያውቁ ዘንድ ይህች የዘላለም ሕይወት ናት*። αὕτη δέ ἐστιν ἡ αἰώνιος ζωή, ἵνα γινώσκωσιν σὲ τὸν μόνον ἀληθινὸν θεὸν καὶ ὃν ἀπέστειλας Ἰησοῦν Χριστόν.

የተጠቀምኩት 1980 አዲስ ትርጉም ነው፥ "አንተ ሰው ብቻ ነህ" ማለት እና "አንተ ብቻህን ሰው ነህ" ማለት ይለያያል። ግሪኩ ያስቀመጠው አብ ብቻውን እውነተኛ አምላክ እንደሆነ ነው። ኢየሱስ ደግሞ የእዚያ እውነተኛ አምላክ መልእክተኛ ስለሆነ "ካይ" καὶ ማለትም "እና" በሚል መስተጻምር "አንተ" ከተባለው ማንነት ከአብ ተነጥሏል። እንደ ባይብሉ ኢየሱስ እውነተኛ አምላክ ሳይሆን የእውነተኛ አምላክ ልጅ ነው፥ የመጣውና የተላከው ልጁ እንጂ አምላክ አልመጣም። አልተላከም፦
የሐዋርያት ሥራ 13፥23 *”ከዚህም ሰው ዘር “አምላክ” Θεὸς እንደ ተስፋው ቃል ለእስራኤል መድኃኒትን እርሱም ኢየሱስን አመጣ”*።
ገላትያ 4፥4 ነገር ግን የዘመኑ ፍጻሜ በደረሰ ጊዜ *“አምላክ” Θεὸς ከሴት የተወለደውን ከሕግም በታች የተወለደውን ልጁን ላከ"*።

አምላክ ኢየሱስን ላከ ወይም አመጣ እንጂ እራሱ አልተላከም። አልመጣም። በስጋ የመጣው ልጁ ስለሆነ "የአምላክ ልጅ እንደ መጣ" ይለናል፦
1ኛ ዮሐንስ 5፥20 *የአምላክም ልጅ እንደ መጣ፥ እውነተኛም የሆነውን እናውቅ ዘንድ ልቡናን እንደ ሰጠን እናውቃለን፤ እውነተኛም የሆነው በልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ አለን። ይህ እውነተኛ አምላክና የዘላለም ሕይወት ነው*። οἴδαμεν δὲ ὅτι ὁ υἱὸς τοῦ θεοῦ ἥκει, καὶ δέδωκεν ἡμῖν διάνοιαν ἵνα γινώσκωμεν τὸν ἀληθινόν: καὶ ἐσμὲν ἐν τῷ ἀληθινῷ, ἐν τῷ υἱῷ αὐτοῦ Ἰησοῦ Χριστῷ. οὗτός ἐστιν ὁ ἀληθινὸς θεὸς καὶ ζωὴ αἰώνιος.

የግሪኩን በማመሳከር ለመጠቀም ሞክሬአለው። እዚህ አንቀጽ መነሻ ላይ "የአምላክም ልጅ እንደ መጣ" የሚለው ይሰመርበት። እውነተኛም አብ በእርሱ በልጁ አለን። ልጁ ስለ እውነተኛው አብ አስተምሯል፥ "በ" የሚለው መስተዋድድ መነሻ ያለው "እርሱ" ኢየሱስን ካመለከተ "እውነተኛ"the True One" የተባለው ደግሞ አብ ነው፥ ልጁ እውነተኛም የሆነውን እናውቅ ዘንድ ዕውቀትን በትምህርቱ ውስጥ እንደ ሰጠን እናውቃለን፦
ዮሐንስ 8፥26 ዳሩ ግን የላከኝ *እውነተኛ* ἀληθινῷ ነው እኔም ከእርሱ የሰማሁትን ይህን ለዓለም እናገራለሁ አላቸው።
ዮሐንስ 7፥28 እኔም በራሴ አልመጣሁም ነገር ግን እናንተ የማታውቁት የላከኝ *እውነተኛ* ἀληθινῷ ነው።

ይህንን ዕውቀት ያስተማረን የእዛ የእውነተኛው አብ ልጁ ነው። ግሪኩ "ሁኦ አውቶዩ" Υἱῷ αὐτοῦ ማለትም "የእርሱ ልጅ"his son" ይለናል። ልጅ የተባለው ኢየሱስ ከሆነ "የ" የሚለው አገናዛቢ መነሻ የሆነለት "አውቶስ" αὐτός ማለትም "እርሱ" ማን ነው? እርግጥ ነው። አብ ነው፥ ቀጥሎ "እርሱ" የሚለውን ተክቶ የመጣው አመልካች "ሆአውቶስ" οὗτός ማለትም "ይህ"this" አብን የሚያመለክት ነው። "ይህ እውነተኛ አምላክና የዘላለም ሕይወት" የተባለው አብ ነው፥ ኅዳጉም ዮሐንስ 17፥3 ይጠቁማል። በጣም ስመ-ጥርና ገናና ኮሜንታተር እውነተኛ አምላክ የተባለው ኢየሱስ ሳይሆን አብ ነው ብለው ሳያቅማሙ አስቀምጠዋል፦
1 John 5፥20 Christ has revealed the one true God, the source of eternal life ‘This is the true God’ does not refer to Jesus” "ክርስቶስ የዘላለም ሕይወት ምንጭ አንድ እውነተኛው አምላክ ገልጧል፥ ይህ እውነተኛ አምላክ ኢየሱስን አያመለክትም።

ዋቢ ኮሜንተሪይ ይመልከቱ፦
1.Grammatical Analysis of the Greek New Testament, Zerwick/Grosvenor, Rome Biblical Institue, 1981.
2.Peake’s Commentary on the Bible, Thomas Nelson and Sons, reprint of 1964.

አዲሱ መደበኛ የግርጌ ማስታወሻ ላይ 1ኛ ዮሐንስ 5፥20 "እውነተኛ አምላክ" የሚለው እግዚአብሔር አብን እንደሚያመለክት አስፍሯል። ደግሞ "ኢየሱስ ክርስቶስ" የሚለው ኃይለ-ቃል በደንገል 22፣ በደንገል 90፣ በደንገል 52፣ ኮዴክስ አሌክሳንድሪየስ ላይ፣ ኮዴክስ ኤፍሬማይ ላይ፣ ላቲን ቩልጌት ላይ የለም። ከሌለ በሌለ ነገር ላይ ተመስርተን እንዴት ቴኦሎጂን ቴኦሎጃይዝ ማድረግ ይቻላል? ዋቢ ማብራሪያ ይመልከቱ፦
Gill’s Exposition of the Whole Bible Commentary. 1 John 5፥20

የ 1ኛ ዮሐንስ 5፥20 ዐውድም ሲዘጋ፦ "ልጆች ሆይ፥ *ከጣዖታት* εἰδώλων ራሳችሁን ጠብቁ" በማለት ነው። ዐውዱ እውነተኛ አምላክን ከጣኦዖት መራቅ ጋር አያይዞ መናገሩ በራሱ እውነተኛ አምላክ የተባለው አብ መሆኑን ቁልጭ አድርጎ ያሳያል። ምክንያቱም ከጣኦታት ዘወር የሚባልበት እውነተኛ አምላክን እና ልጁ ኢየሱስ ሁለት ኑባሬዎች እንደሆኑ በሌላ ጥቅስ ላይ መረጃ ስላለን ነው፦
1ተሰሎንቄ 1፥9-10 *እነርሱ ራሳቸው ወደ እናንተ መግባታችን እንዴት እንደነበረ ስለ እኛ ይናገራሉና፤ ለሕያው እና *ለእውነተኛ አምላክም* Θεῷ ζῶντι καὶ ἀληθινῷ ታገለግሉ ዘንድ፥ ከሙታንም ያስነሳውን *ልጁን* እርሱንም ኢየሱስን ከሚመጣው ቍጣ የሚያድነንን ከሰማይ ትጠብቁ ዘንድ፥ *ከጣዖቶች* εἰδώλων ወደ አምላክ Θεὸν እንዴት ዘወር እንዳላችሁ ይናገራሉ*።
"እውነተኛ አምላክ" ካለ በኃላ "የእርሱ ልጅ"his son" ይለናል። "ልጅ" የተባለው ኢየሱስ "እርሱ" የተባለው በግልጽ "እውነተኛ አምላክ" ነው። አይሁዶችም እውነተኛ አምላክ የሚሉት ጥንት ሲመለክ የነበረውን ያህዌን ብቻ ነው፦
ኤርሚያስ 10፥10 ያህዌህ וַֽיהוָ֤ה ግን *እውነተኛ አምላክ* אֱמֶת, הוּא-אֱלֹהִים ነው፤ እርሱም ሕያው አምላክና የዘላለም ንጉሥ ነው፤
2ኛ ዜና 15፥3 እስራኤልም ብዙ ዘመን ያለ *እውነተኛ አምላክ* אֱמֶת, הוּא-אֱלֹהִים ፥ ያለ አስተማሪም ካህን፥ ያለ ሕግም ይኖሩ ነበር።

ያ እውነተኛ አምላክ ያህዌህ ለእስራኤላውያን አምላካቸው ለኢየሱስ አባቱ እንደሆነ ተናግሯል፦
ዘዳግም 6፥4 *እስራኤል ሆይ፥ ስማ፤ አምላካችን ያህዌህ አንድ ያህዌህ ነው”*።
ዮሐንስ 8፥54 *”እናንተ አምላካችን የምትሉት አባቴ ነው”*።

ስለዚህ እውነተኛ አምላክ የተባለው ኢየሱስን የላከው እንጂ የተላከው ኢየሱስ በፍጹም አይደለም። "ሆአውቶስ" οὗτός ማለትም "ይህ"this" የሚለው አመልካች ተውላጠ-ስም "ኢየሱስ" ከሚለው በኃላ ስለመጣ ኢየሱስ ነው ማለት ከእናቱ ማኅፀን ጀምሮ አንካሳ የነበረው ሰው የማዕዘን ራስ የሆነው ይህ ድንጋይ ነው እንደ ማለት ነው፦
ሐዋ. ሥራ 4፥10-11 *እናንተ በሰቀላችሁት እግዚአብሔርም ከሙታን ባስነሣው በናዝሬቱ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ይህ ደኅና ሆኖ በፊታችሁ እንደ ቆመ፥ ለእናንተ ለሁላችሁ ለእስራኤልም ሕዝብ ሁሉ የታወቀ ይሁን። እናንተ ግንበኞች የናቃችሁት፥ የማዕዘን ራስ የሆነው "ይህ" οὗτός ድንጋይ ነው*።

ስለ ከእናቱ ማኅፀን ጀምሮ አንካሳ ስለነበረ ሰው አውርቶ "በአራት ነጥብ" (።) ከዘጋ በኃላ "ይህ" የሚለው ስለ ኢየሱስ እንደሆነ ሁሉ ስለ ኢየሱስ አውርቶ በአራት ነጥብ ከዘጋ በኃላ ይህ የሚለው ስለ ስለ አብ ነው። በኢሥላም እውነተኛ አምላክ አላህ ብቻ ነው፥ እነዚያ መሲሢሑን “አላህ ነው” ያሉ በእርግጥ ካዱ። ይህ በአላህ አምላክነትን ላይ ሰውን ማሻረክ ነው፥ እነሆ በአላህ ላይ የሚያጋራ ሰው አላህ በእርሱ ላይ ገነትን በእርግጥ እርም ስላደረገበት እና መኖሪያውም እሳት ስለሆነች መሲሢሑን “አላህ ነው” የምትሉ የተውበት በሩ ሳይዘጋ በተውበት ወደ አላህ ተመለሱ፦
5፥72 *” «አላህ እርሱ የመርየም ልጅ አልመሲሕ ነው» ያሉ በእርግጥ ካዱ፡፡ አልመሲህም አለ፡- «የእስራኤል ልጆች ሆይ! ጌታዬንና ጌታችሁን አላህን ተገዙ፡፡» እነሆ! በአላህ የሚያጋራ ሰው አላህ በርሱ ላይ ገነትን በእርግጥ እርም አደረገ፡፡ መኖሪያውም እሳት ናት፡፡ ለበዳዮችም ምንም ረዳቶች የሏቸውም”*፡፡ لَقَدْ كَفَرَ الَّذِينَ قَالُوا إِنَّ اللَّهَ هُوَ الْمَسِيحُ ابْنُ مَرْيَمَ ۖ وَقَالَ الْمَسِيحُ يَا بَنِي إِسْرَائِيلَ اعْبُدُوا اللَّهَ رَبِّي وَرَبَّكُمْ ۖ إِنَّهُ مَن يُشْرِكْ بِاللَّهِ فَقَدْ حَرَّمَ اللَّهُ عَلَيْهِ الْجَنَّةَ وَمَأْوَاهُ النَّارُ ۖ وَمَا لِلظَّالِمِينَ مِنْ أَنصَارٍ

ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
ሁለት አምላክ

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

16፥51 አላህም አለ፦ *"ሁለት አማልክትን አትያዙ"*፡፡ እርሱ *"አንድ አምላክ ብቻ ነው፡፡ እኔንም ብቻ ፍሩ"*፡፡ وَقَالَ ٱللَّهُ لَا تَتَّخِذُوٓا۟ إِلَٰهَيْنِ ٱثْنَيْنِ ۖ إِنَّمَا هُوَ إِلَٰهٌۭ وَٰحِدٌۭ ۖ فَإِيَّٰىَ فَٱرْهَبُونِ

"ሸይእ" شَىْء ማለት "ነገር"thing" ማለት ሲሆን ማንኛውንም ነገር ሁሉ የፈጠረ አንድ አምላክ አላህ ብቻ ነው፦
39:62 አላህ *"የነገሩ ሁሉ ፈጣሪ ነው"*። እርሱም በነገሩ ሁሉ ላይ አስተናባሪ ነው። ٱللَّهُ خَٰلِقُ كُلِّ شَىْءٍۢ ۖ وَهُوَ عَلَىٰ كُلِّ شَىْءٍۢ وَكِيلٌۭ
40:62 ይሃችሁ፣ ጌታችሁ አላህ ነው፤ *"የነገር ሁሉ ፈጣሪ ነው"*፤ ከእርሱ ሌላ አምላክ የለም፤ ታዲያ ከእምነት ወዴት ትመለሳላችሁ?። ذَٰلِكُمُ ٱللَّهُ رَبُّكُمْ خَٰلِقُ كُلِّ شَىْءٍۢ لَّآ إِلَٰهَ إِلَّا هُوَ ۖ فَأَنَّىٰ تُؤْفَكُونَ
6:102 ይህ ጌታችሁ አላህ ነው፡፡ ከእርሱ በቀር አምላክ የለም፡፡ *"ነገርን ሁሉ ፈጣሪ ነው"*፡፡ ስለዚህ አምልኩት፡፡ እርሱም በነገሩ ሁሉ ላይ ተጠባባቂ ነው፡፡ بَدِيعُ ٱلسَّمَٰوَٰتِ وَٱلْأَرْضِ ۖ أَنَّىٰ يَكُونُ لَهُۥ وَلَدٌۭ وَلَمْ تَكُن لَّهُۥ صَٰحِبَةٌۭ ۖ وَخَلَقَ كُلَّ شَىْءٍۢ ۖ وَهُوَ بِكُلِّ شَىْءٍ عَلِيمٌۭ
13፥16 *«አላህ ሁሉን ነገር ፈጣሪ ነው"*፡፡ እርሱም አንዱ አሸናፊው ነው» በል፡፡ قُلِ ٱللَّهُ خَٰلِقُ كُلِّ شَىْءٍۢ وَهُوَ ٱلْوَٰحِدُ ٱلْقَهَّٰرُ

ያ ማለት ከነገር ሁሉ ተቃራኒ ነገርን የፈጠረው አላህ ብቻ ነው፤ ለምሳሌ ሰማይንና ምድርን፣ ብርሃንንና ጨለማን፣ ሞትና ህይወትን፣ ወንድና ሴትን ሁሉ ማለት ነው፦
51፥49 ትገነዘቡም ዘንድ *"ከነገሩ ሁሉ ሁለት ተቃራኒ ዓይነትን ፈጠርን"*፡፡ وَمِن كُلِّ شَىْءٍ خَلَقْنَا زَوْجَيْنِ لَعَلَّكُمْ تَذَكَّرُونَ
6፥1 ምስጋና ለዚያ *"ሰማያትንና ምድርን ለፈጠረው፤ ጨለማዎችንና ብርሃንንም"* ላደረገው ለአላህ የተገባ ነው፡፡ ٱلْحَمْدُ لِلَّهِ ٱلَّذِى خَلَقَ ٱلسَّمَٰوَٰتِ وَٱلْأَرْضَ وَجَعَلَ ٱلظُّلُمَٰتِ وَٱلنُّورَ
67፥1 ያ የትኛችሁ ሥራው ይበልጥ ያማረ መኾኑን ሊሞክራችሁ *"ሞትንና ሕይወትን የፈጠረ ነው"*፡፡ እርሱም አሸናፊው መሓሪው ነው፡፡ ٱلَّذِى خَلَقَ ٱلْمَوْتَ وَٱلْحَيَوٰةَ لِيَبْلُوَكُمْ أَيُّكُمْ أَحْسَنُ عَمَلًۭا ۚ وَهُوَ ٱلْعَزِيزُ ٱلْغَفُورُ
75፥39 ከእርሱም *"ሁለት ዓይነቶችን ወንድና ሴትን አደረገ"*፡፡ فَجَعَلَ مِنْهُ ٱلزَّوْجَيْنِ ٱلذَّكَرَ وَٱلْأُنثَىٰٓ

ይህ ሆኖ ሳለ ግን ዞራስተርያን ወይም ኖስቲዝም፦ "ሰማይን፣ ብርሃንን፣ ህይወትን፣ ወንድን የፈጠረው "አሁራ" የተባለው አምላክ ነው ሲሉ፤ በተቃራኒው ምድርን፣ ጨለማን፣ ሞት፣ ሴትን የፈጠረው "አንግራ" የተባለው አምላክ ነው ብለው ሁለት አምላክ ያመልካሉ፤ ይህ የሁለት አምላክ ጥምረት ትምህርት "ዱአ-ቴእይዝም"duotheism" ይባላል፤ "ዱአ-ቴእይዝም" δυοθεισμός ማለት የሁለት ቃላት ውቅር ነው፤ "ዱአ" δυο "ሁለት" እና "ቴኦስ" θεισμός "አምላክ" የሚል ትርጉም ነው፤ ትርጉሙም "ሁለት አምላክ"dual deity" ማለት ነው፤ ይህንን ትምህርት ቁርአን ክፉኛ ይቃወማል፦
16፥51 አላህም አለ፦ *"ሁለት አማልክትን አትያዙ"*፡፡ እርሱ *"አንድ አምላክ ብቻ ነው፡፡ እኔንም ብቻ ፍሩ"*፡፡ وَقَالَ ٱللَّهُ لَا تَتَّخِذُوٓا۟ إِلَٰهَيْنِ ٱثْنَيْنِ ۖ إِنَّمَا هُوَ إِلَٰهٌۭ وَٰحِدٌۭ ۖ فَإِيَّٰىَ فَٱرْهَبُونِ

ይህ ትምህርት ከሥላሴ የሚለየው አምላክ በምንነት ሆነ በማንነት ሁለት ነው ሲሉ፤ ሥላሴያውያን ደግሞ በማንነት ሦስት በምንነት አንድ ናቸው ብለው ያምናሉ፤ ነገር ግን አንዱ አምላክ በማንነት ሆነ በምንነት አንድ ነው፤ በምንነቱ ሆነ በማንነቱ ተጋሪ የለውም፦
18፥110 ወደ እኔ የሚወረድልኝ "አምላካችሁ አንድ አምላክ ብቻ ነው፤ እኔም ቢጤያችሁ ሰው ብቻ ነኝ" ማለት ነው፤ የጌታውንም መገናኘት የሚፈልግ ሰው፤ መልካም ሥራን ይሥራ፡፡ በጌታውም አምልኮ *"አንድንም"* አያጋራ» በላቸው፡፡ قُلْ إِنَّمَآ أَنَا۠ بَشَرٌۭ مِّثْلُكُمْ يُوحَىٰٓ إِلَىَّ أَنَّمَآ إِلَٰهُكُمْ إِلَٰهٌۭ وَٰحِدٌۭ ۖ فَمَن كَانَ يَرْجُوا۟ لِقَآءَ رَبِّهِۦ فَلْيَعْمَلْ عَمَلًۭا صَٰلِحًۭا وَلَا يُشْرِكْ بِعِبَادَةِ رَبِّهِۦٓ أَحَدًۢا
አንድ አምላክ" በሚለው ቃል ላይ "አንድ" የሚለውን የተጠቀመበት "ዋሒድ" وَٰحِد ሲሆን አላህ በምንነቱ ላይ ምንም ምንነት ተጋሪ እንደሌለው ያሳያል፤ "አንድንም አያጋራ" በሚለው ቃል የተጠቀመበት ቃል "አሐድ" أَحَد ሲሆን በአላህ ምንነት ላይ ማንም ማንነት ተጋሪ እንደሌለ ያሳያል፦
72፥20 «እኔ የምግገዛው ጌታየን ብቻ ነው፡፡ በእርሱም *"አንድንም"* አላጋራም» በል፡፡ قُلْ إِنَّمَآ أَدْعُوا۟ رَبِّى وَلَآ أُشْرِكُ بِهِۦٓ أَحَدًۭا
112፥1 በል «እርሱ አላህ *"አንድ"* ነው፡፡ قُلْ هُوَ ٱللَّهُ أَحَدٌ

"አላህ አንድ ነው" በሚለው ቃል ላይ "አንድ" የሚለው "አሐድ" أَحَد መሆኑ በራሱ አላህ አንድ ማንነት ብቻ መሆኑን ቁልጭ አድርጎ ያሳያል፤ ከእርሱ ማንነት ጋር መለኮትን የሚጋራ አንድም ማንነት የለም፦
112፥4 ለእርሱም *"አንድም"* ብጤ የለውም፡፡ وَلَمْ يَكُن لَّهُۥ كُفُوًا أَحَدٌۢ

"ለም" لَمْ ማለት "አፍራሽ ቃል"negative particle" ሲሆን ለማንነት የሚመጣ አፍራሽ ቃል ነው፤ ለእርሱ ማንም ብጤ የሌለው መሆኑን ያሳያል፤ "ለይሠ" لَيْسَ ማለት "አፍራሽ ቃል"negative particle" ሲሆን ለምንነት የሚመጣ አፍራሽ ቃል ነው፤ አላህ የሚመስለው ምንም ምንነት የለም፦
42፥11 *የሚመስለው ምንም ነገር የለም*፡፡ እርሱም *ሰሚው ተመልካቹ* ነው፡፡ لَيْسَ كَمِثْلِهِۦ شَىْءٌۭ ۖ وَهُوَ ٱلسَّمِيعُ ٱلْبَصِيرُ

ይህንን ጥልልና ጥንፍፍ ያለ የተውሒድ ትምህርት ከተረዳን በክርስትናው አንጃ ውስጥ የይሆዋ ምስክሮች ደግሞ፦ "ዓለማት ከመፈጠራቸው በፊት ያህዌህ ኢየሱስ ፈጠረውና በኢየሱስ ሁሉን ነገር ፈጠረ" ብለው ያምናሉ፤ ይህ እንጥል ከመቧጠጥ ምንም አይተናነስም፤ ኢየሱስን አናመልክም ሲሉ ተውሒደል ኡሉሂያን ሲያሟሉ፤ ግን ዓለማትን ሲፈጥር ግን አጋዥ ነበረው ብሎ ማለት ተውሒደ አር-ሩቡቢያን ላይ ማሻረክ ነው፤ ከአላህ ጋር በምንነት ተለይቶ ግን ፍጥረትን ሲፈጥር ሆነ ዓለማትን ሲያስተናብር የሚያግዘው አጋዥ የለውም፤ ወደ አላህ በንስሃ ተመለሱ እንላለን፦
34፥22 እነዚያን ከአላህ ሌላ የምታስቧቸውን ጥሩ፡፡ በሰማያትም በምድርም ውስጥ *"የብናኝ ክብደት ያክል ምንንም አይችሉም"*፡፡ ለእነርሱም በሁለቱም ውስጥ *"ምንም ሽርክና የላቸውም"*፡፡ ከእነርሱም ለእርሱ *"ምንም አጋዥ የለውም"*» በላቸው፡፡ قُلِ ٱدْعُوا۟ ٱلَّذِينَ زَعَمْتُم مِّن دُونِ ٱللَّهِ ۖ لَا يَمْلِكُونَ مِثْقَالَ ذَرَّةٍۢ فِى ٱلسَّمَٰوَٰتِ وَلَا فِى ٱلْأَرْضِ وَمَا لَهُمْ فِيهِمَا مِن شِرْكٍۢ وَمَا لَهُۥ مِنْهُم مِّن ظَهِيرٍۢ

ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
አል-መሢሕ

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ፥ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

3፥45 መላእክት ያሉትን አስታውስ፡- «መርየም ሆይ! *አላህ ከእርሱ በኾነው ቃል ስሙ፦ አል-መሲሕ ዒሣ የመርየም ልጅ በዚህ ዓለምና በመጨረሻውም ዓለም የተከበረ ከባለሟሎችም በኾነ ያበስርሻል*፡፡» إِذْ قَالَتِ الْمَلَائِكَةُ يَا مَرْيَمُ إِنَّ اللَّهَ يُبَشِّرُكِ بِكَلِمَةٍ مِّنْهُ اسْمُهُ الْمَسِيحُ عِيسَى ابْنُ مَرْيَمَ وَجِيهًا فِي الدُّنْيَا وَالْآخِرَةِ وَمِنَ الْمُقَرَّبِينَ

አምላካችን አላህ በመልአኩ ለመርየም ያበሰራት ቃል ልጇ፦ "ስሙ፦ አልመሲሕ ዒሳ የመርየም ልጅ እንደሆነ፥ በዚህ ዓለምና በመጨረሻውም ዓለም የተከበረ ከባለሟሎችም እንደሆነ ነው፦
3፥45 መላእክት ያሉትን አስታውስ፡- «መርየም ሆይ! *አላህ ከእርሱ በኾነው ቃል ስሙ፦ አል-መሲሕ ዒሣ የመርየም ልጅ በዚህ ዓለምና በመጨረሻውም ዓለም የተከበረ ከባለሟሎችም በኾነ ያበስርሻል*፡፡» إِذْ قَالَتِ الْمَلَائِكَةُ يَا مَرْيَمُ إِنَّ اللَّهَ يُبَشِّرُكِ بِكَلِمَةٍ مِّنْهُ اسْمُهُ الْمَسِيحُ عِيسَى ابْنُ مَرْيَمَ وَجِيهًا فِي الدُّنْيَا وَالْآخِرَةِ وَمِنَ الْمُقَرَّبِينَ

"ዩበሺሩኪ ቢከሊማህ" يُبَشِّرُكِ بِكَلِمَةٍ ማለት "በቃል ያበስርሻል" ማለት ነው፥ ይህም የምስራች ቃል ስሙ፦ "አል-መሲሕ ዒሣ" መባሉ ነው። እዚህ አንቀጽ ላይ ሚሽነሪዎች፦ "አል-መሲሕ" الْمَسِيح የዒሣ "ስሙ" መባሉ "ስህተት ነው" ይላሉ። ምክንያታችሁ ምንድን ነው? ስንላቸው፥ "አል" الْ የሚለው "መዕሪፍ" مَعْرِف ማለትም "ጠቃሽ አመልካች መስተአምር"definite article" ካለበት ስም አይደለም" ብለው አረፉት፥ ይህ የሚያሳየው ስለ ስም ያላቸው ግንዛቤ ዜሮ እንደሆነ ነው። “ኢሥም” اِسْم የሚለው ቃል “ሠማ” سَمَّى ማለትም “ጠራ” “ሰየመ” ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን “መጠሪያ” ወይም “ስም” ማለት ነው፥ የኢሥም ብዙ ቁጥር “አሥማእ” أَسْمَاء‎ ነው። “ስም” የአንድ ማንነት ወይም ምንነት “መጠሪያ” ነው። ለምሳሌ “አሏህ” ٱللَّه የሚለው ስም “ኢሥሙል ዐለም” اِسْم العَلَم ማለትም “የተጸውዖ ስም”proper name” ቢሆንም በቁርኣን የተገለጹ “አል-ኻሊቅ” الْخَالِق “አል-ባሪእ” الْبَارِئُ “አል-ገኒይ” الْغَنِيّ “አል-ሙሰዊር” الْمُصَوِّرُ ወዘተ የሚባሉ “ኢሥሙል መዕሪፍ” اِسْم اللمَعْرِف አሉት፦
29፥24 *”እርሱ አላህ ፈጣሪው ከኢምንት አስገኚው ቅርጽን አሳማሪው ነው፤ ለእርሱ መልካሞች ስሞች አሉት”*። هُوَ اللَّهُ الْخَالِقُ الْبَارِئُ الْمُصَوِّرُ لَهُ الْأَسْمَاءُ الْحُسْنَى

እዚህ አንቀጽ ላይ የተጠቀሱት ስሞች “አል-ኻሊቅ” الْخَالِق “አል-ባሪእ” الْبَارِئُ “አል-ሙሰዊር” الْمُصَوِّرُ ላይ "አል" الْ የሚል መዕሩፍ እንዳላቸው ልብ አድርግ። ልክ እንደዚሁ “ዒሣ” عِيسَى የሚለው ስም “ኢሥሙል ዐለም” اِسْم العَلَم ማለትም “የተጸውዖ ስም”proper name” ሲሆን "አል-መሲሕ" الْمَسِيح ደግሞ “ኢሥሙል መዕሪፍ” اِسْم اللمَعْرِف ነው።
ይህንን ለመረዳት ከባይብል አንዳንድ ናሙናዎችን እያየን እናነጻጽራለን፦
ማቴዎስ 24፥5 ብዙዎች፦ *እኔ ክርስቶስ ነኝ እያሉ በስሜ ይመጣሉና*፤ ብዙዎችንም ያስታሉ።

"ክርስቶስ" የማዕረግ ስም ነው፥ ግን ለኢየሱስ ስሙ ስለሆነ "በስሜ" በማለት "ክርስቶስ" ስሙ መሆኑን አስረግጦ ነግሮናል። በተጨማሪም የማዕረግ ስም ስለሚተረጎም "ክርስቶስ" Χριστός የሚለው የግሪኩ ቃል ከዕብራይስጥ "ሀ-መሢአሕ" המשיח የተተረጎመ ነው። "መሢአሕ" ስም ሆኖ ሳለ "ሀ" ה የሚል ጠቃሽ አመልካች መስተአምር ይጠቀማል፦
ማርቆስ 8፥29 እናንተስ እኔ ማን እንደ ሆንሁ ትላላችሁ? ብሎ ጠየቃቸው። ጴጥሮስም፦ *አንተ ክርስቶስ ὁ Χριστός ነህ* ብሎ መለሰለት።

"ክርስቶስ" Χριστός የሚለው ቃል ላይ "ሆ" ὁ የሚል ጠቃሽ አመልካች መስተአምር ስለተጠቀመ "ክርስቶስ" ስም አለመሆኑ ማስረጃ ሊሆን አይችልም። ሌላ ናሙና በኢሳይያስ ዘመን የተወለድ ሕጻን ስሙ "ምርኮ ፈጠነ፥ ብዝበዛ ቸኰለ" ተብሏል፦
ኢሳይያስ 8፥4 *ስሙን፦ ምርኮ ፈጠነ፥ ብዝበዛ ቸኰለ" ብለህ ጥራው" አለኝ*።

ለሕጻኑ ማዕረጉ "ስሙ" እንደተባለ ልብ አድርግ። ሌላ ናሙና "ዔሳው" የይስሐቅ ልጅ የተጸውዖ ስም ሲሆን ቅጽል ስሙ "ኤዶም" ነው፦
ዘፍጥረት 25፥30 ዔሳውም ያዕቆብን፦ ከዚህ ከቀዩ ወጥ አብላኝ፥ እኔ እጅግ ደክሜአለሁና አለው፤ ስለዚህ *"ስሙ ኤዶም ተባለ"*።

"ኤዶም" ማዕረግ ሆኖ ሳለ "ስሙ" መባሉን አንባቢ ልብ ይለዋል። ሌላ ናሙና አዳም ለእንስሳት ሁሉ፥ ለሰማይ ወፎችም ሁሉ፥ ለምድር አራዊትም ሁሉ ስም አወጣላቸው። ከእንስሳት መካከል አንበሳ እና አህያ ናቸው፦
ዘፍጥረት 2፥20 *አዳምም ለእንስሳት ሁሉ፥ ለሰማይ ወፎችም ሁሉ፥ ለምድር አራዊትም ሁሉ ስም አወጣላቸው"*።
1ኛ ነገሥት 13፥28 ሄደም፥ ሬሳውም በመንገድ ወድቆ፥ በሬሳውም አጠገብ *አህያው וַֽחֲמוֹר֙ እና አንበሳው* וְהָ֣אַרְיֵ֔ה ቆመው፥ አንበሳው ሬሳውን ሳይበላው፥ አህያውንም ሳይሰብረው አገኘ።

እዚህ አንቀጽ ላይ "ሙውር" מוֹר֙ ማለትም "አህያ" በሚል ቃል እና "አርየህ" אַרְיֵ֔ה ማለትም "አንበሳ" በሚል ቃል መነሻ ላይ "ሀ" ה የሚል ውስን መስተአምር ይጠቀማል። ውስን መስተአምር መኖሩ "አንበሳ" እና "አህያ" ስም አለመሆናቸውን እንደማያሳይ ሁሉ "መሲሕ مَسِيح በሚለው ቃል መነሻ ላይ "አል" الْ የሚል ውስን መስተአምር መኖሩ "አል-መሢሕ" ስም አለመሆኑ አያሳይም። የተገባባን ይመስለኛል።

ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
የምስራቹ ቃል

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ፥ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

3፥45 መላእክት ያሉትን አስታውስ፡- «መርየም ሆይ! *አላህ ከእርሱ በኾነው ቃል ስሙ፦ አል-መሲሕ ዒሣ የመርየም ልጅ በዚህ ዓለምና በመጨረሻውም ዓለም የተከበረ ከባለሟሎችም በኾነ ያበስርሻል*፡፡» إِذْ قَالَتِ الْمَلَائِكَةُ يَا مَرْيَمُ إِنَّ اللَّهَ يُبَشِّرُكِ بِكَلِمَةٍ مِّنْهُ اسْمُهُ الْمَسِيحُ عِيسَى ابْنُ مَرْيَمَ وَجِيهًا فِي الدُّنْيَا وَالْآخِرَةِ وَمِنَ الْمُقَرَّبِينَ

“ቡሽራ” بُشْرَىٰ የሚለው ቃል “በሸረ” بَشَّرَ ማለትም “አበሰረ” ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን “የምስራች” ማለት ነው። አምላካችን አላህ በመልአኩ ለመርየም አብስሯታል፦
3፥45 መላእክት ያሉትን አስታውስ፡- «መርየም ሆይ! *አላህ ከእርሱ በኾነው ቃል ስሙ፦ አል-መሲሕ ዒሣ የመርየም ልጅ በዚህ ዓለምና በመጨረሻውም ዓለም የተከበረ ከባለሟሎችም በኾነ ያበስርሻል*፡፡» إِذْ قَالَتِ الْمَلَائِكَةُ يَا مَرْيَمُ إِنَّ اللَّهَ يُبَشِّرُكِ بِكَلِمَةٍ مِّنْهُ اسْمُهُ الْمَسِيحُ عِيسَى ابْنُ مَرْيَمَ وَجِيهًا فِي الدُّنْيَا وَالْآخِرَةِ وَمِنَ الْمُقَرَّبِينَ

እዚህ አንቀጽ ላይ "ያበስርሻል" ለሚለው ቃል የገባው "ዩበሺሩኪ" يُبَشِّرُكِ መሆኑን አስተው። "ዩበሺሩኪ ቢከሊማህ" يُبَشِّرُكِ بِكَلِمَةٍ ማለት "በቃል ያበስርሻል" ማለት ነው፥ ይህም ከአላህ የሆነው የምስራች ቃል፦ "ስሙ አል-መሲሕ ዒሣ የመርየም ልጅ በዚህ ዓለምና በመጨረሻውም ዓለም የተከበረ ከባለሟሎችም በኾነ ያበስርሻል" የሚል ነው። መርየምም በዚህ በጌታዋን ቃላት እና በመጽሐፍቱ አምናለች፥ ከታዛዦቹም ነበረች፦
66፥12 የዒምራንን ልጅ መርየምንም ያችን ብልቷን የጠበቀችውን ምሳሌ አደረገ፡፡ በእርሱም ውስጥ ከመንፈሳችን ነፋን፡፡ *በጌታዋ ቃላት እና በመጻሕፍቱም አረጋገጠች፡፡ ከታዛዦቹም ነበረች*፡፡ وَمَرْيَمَ ابْنَتَ عِمْرَانَ الَّتِي أَحْصَنَتْ فَرْجَهَا فَنَفَخْنَا فِيهِ مِن رُّوحِنَا وَصَدَّقَتْ بِكَلِمَاتِ رَبِّهَا وَكُتُبِهِ وَكَانَتْ مِنَ الْقَانِتِينَ

"ሶደቀት" صَدَّقَتْ የሚለው "አመነት" آمَنَتْ በሚል እንደመጣ አንባቢ ልብ ይለዋል። ከጌታዋ የሆነው የምስራች ቃል በሰማች ጊዜ አምናለች፥ መርየም በጌታዋ ቃላት እንደተበሰረችው ሁሉ ዘከርያም ከእርሷ በፊት ከአላህ በኾነው የምስራች ቃል ተበስሯል፦
3፥39 እርሱም በጸሎት ማድረሻው ክፍል ቆሞ ሲጸልይ *መላእክትም፦ «አላህ በየሕያ ከአላህ በኾነ ቃል የሚያረጋግጥ ጌታም ድንግልም ከደጋጎቹ ነቢይም ሲኾን ያበስርሃል» በማለት ጠሩት*፡፡ فَنَادَتْهُ الْمَلَائِكَةُ وَهُوَ قَائِمٌ يُصَلِّي فِي الْمِحْرَابِ أَنَّ اللَّهَ يُبَشِّرُكَ بِيَحْيَىٰ مُصَدِّقًا بِكَلِمَةٍ مِّنَ اللَّهِ وَسَيِّدًا وَحَصُورًا وَنَبِيًّا مِّنَ الصَّالِحِينَ

መልአኩ ለመርየም "ዩበሺሩኪ" يُبَشِّرُكِ ማለትም "ያበስርሻል" እንዳላት ሁሉ ለዘከርያም "ዩበሺሩከ" يُبَشِّرُكَ ማለትም "ያበስርሃል" ብሎታል።

ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
አጅነቢይ መጨበጥ

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

17፥32 *ዝሙትንም አትቅረቡ፡፡ እርሱ በእርግጥ መጥፎ ሥራ ነውና፡፡ መንገድነቱም ከፋ*! وَلَا تَقْرَبُوا الزِّنَىٰ ۖ إِنَّهُ كَانَ فَاحِشَةً وَسَاءَ سَبِيلًا

"አጅነቢይ" أَجْنَبِيّ ማለት "ባዕድ" ማለት ሲሆን አንድ ሙሥሊም ወይም አንዲት ሙሥሊም በተቃራኒ ፆታ ያሉትን ለመጨበጥ ወይም ጸጉሯን ለማየት ሐላል ያልሆነ ሰው ማለት ነው።
አንድ ሙሥሊም ወንድ ጸጉሯ ለማየት ሆነ እጇን ለመጨበጥ ሐላል የሆኑለት እንስት እናቱ፣ አክስቱ፣ እህቱ፣ የወንድሙን ሴት ልጅ፣ የእህቱን ሴት ልጅ፣ ሚስቱ፣ ሴት ልጁ፣ የሚስቱ እናት ናቸው።
አንዲት ሙሥሊም ሴት ጸጉሯ ለማሳየት ሆነ ለመጨበጥ ሐላል የሆኑላት ተባዕት አባቷ፣ አጎቷ፣ ወንድሟ፣ የወንድሟ ወንድ ልጅ፣ የእህቷ ወንድ ልጅ፣ ባሏ፣ ወንድ ልጇ፣ የባሏ አባት ናቸው።
አንድ ሙሥሊም ወንድ ጸጉሯ ለማየት ሆነ እጇን ለመጨበጥ ሐራም የሆኑበት እንስት የአጎት ልጅ፣ የአክስት ልጅ፣ የወንድም ሚስት፣ የሚስት እህት፣ የጎረቤት ሴት፣ የአብነት ሴት፣ የአስኳላ ሴት፣ የሥራ ባልደረባ ሴት ወዘተ ናቸው።
አንዲት ሙሥሊም ሴት ጸጉሯ ለማሳየት ሆነ ለመጨበጥ ሐራም የሆኑባትት ተባዕት የአጎት ልጅ፣ የአክስት ልጅ፣ የእህት ባል፣ የባል ወንድም፣ የጎረቤት ወንድ፣ የአብነት ወንድ፣ የአስኳላ ወንድ፣ የሥራ ባልደረባ ወንድ ወዘተ ናቸው።

አጅነቢይ ማለት ምን ማለት እንደሆነ ቋንቋዊ እና ሃይማኖታዊ ፍቺውን ከተመለከትን ዘንዳ የሁላችንም አርአያ የሆኑት ተወዳጁ ነቢያችን"ﷺ" አጅነቢይ ሴቶችን በእጃቸው አይጨብጡም ነበር፦
ኢማም ሙሥሊም መጽሐፍ 33, ሐዲስ 131
ዓኢሻህ እንደተረከችው፦ *"የአላህ መልእክተኛም"ﷺ" አጅነቢይ ሴቶችን በእጃቸው አይጨብጡም ነበር"*። أَنَّ عَائِشَةَ، أَخْبَرَتْهُ عَنْ بَيْعَةِ النِّسَاءِ، قَالَتْ مَا مَسَّ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم بِيَدِهِ امْرَأَةً

"ቢ-የድ-ሂ" بِيَدِهِ ማለትም "በ-እጁ" የሚለው ይሰመርበት። በመላው ዓለም የሚገኙ ሙሥሊሞች ይህንን የነቢያችንን"ﷺ" ፈለግ በመከተል አጅነቢይ የሆነን ወንድ ወይም ሴት አይጨብጡም፦
33፥21 ለእናንተ አላህንና የመጨረሻውን ቀን የሚከጅል ለሆነ ሰው፣ አላህንም በብዙ ለሚያወሳ *በአላህ መልዕክተኛ መልካም መከተል አላችሁ*፡፡ لَّقَدْ كَانَ لَكُمْ فِي رَسُولِ اللَّهِ أُسْوَةٌ حَسَنَةٌ لِّمَن كَانَ يَرْجُو اللَّهَ وَالْيَوْمَ الْآخِرَ وَذَكَرَ اللَّهَ كَثِيرًا

"በአላህ መልዕክተኛ መልካም መከተል አላችሁ" የሚለው ኃይለ-ቃል ይሰመርበት። በኢሥላም ሐራም የሚባለው ዝሙት ብቻ ሳይሆን ወደዚያ ሊያመሩ የሚችሉ ቅድመ-ሁኔታዎች ሁሉ ክልክል ናቸው፦
17፥32 *ዝሙትንም አትቅረቡ፡፡ እርሱ በእርግጥ መጥፎ ሥራ ነውና፡፡ መንገድነቱም ከፋ*! وَلَا تَقْرَبُوا الزِّنَىٰ ۖ إِنَّهُ كَانَ فَاحِشَةً وَسَاءَ سَبِيلًا

"ሰቢል" سَبِيل ማለት "መንገድ" ማለት ሲሆን ወደ ዝሙት ሊገፋፉ፣ ሊነሽጡ፣ ሊወሰውሱ የሚችሉ ነገሮች ሁሉ ያጠቃልላል።
በተረፈ በባይብል ሾላ በድፍኑ ዝሙት ኃጢአት ነው ይላል እንጂ "የዝሙት መቃረቢያዎች ኃጢአት ናቸው" የሚልበት አንዳችም ቁብ የለውም። ስለዚህ እዛ ሰፈር፦ "አጅነቢይን መጨበጥ ለምን ክልክል ሆነ" ብሎ አቧራ ማስነሳት መናኛ ምክንያት ነው፥ ሳይቀመጡ እግር መዘርጋት ለመፈንገል ነው። ባይብል ላይ የተሻለ እሳቤ ሳይኖር ኢሥላም ላይ መንፈቅፈቅና መነፋረቅ ቋ ያለ ጉፋያ እና እንጉልፋቶ ትችት ነው።

ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
እውነተኛ ቃል

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ፥ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

19፥34 *ይህ የመርየም ልጅ ዒሣ ነው፡፡ ያ “በ”እርሱ የሚከራከሩበት እውነተኛ ቃል ነው*፡፡ ذَٰلِكَ عِيسَى ٱبْنُ مَرْيَمَ ۚ قَوْلَ ٱلْحَقِّ ٱلَّذِى فِيهِ يَمْتَرُونَ

አምላካችን አላህ የዒሣን አፈጣጠር ከኣደም አፈጣጠር ጋር እንደሚመሳሰል በተከበረው ንግግሩ እንዲህ ይናገራል፦
3፥59 *”አላህ ዘንድ የዒሣ ምሳሌ እንደ ኣደም ብጤ ነው፡፡ ከአፈር ፈጠረው፡፡ ከዚያም ለ”እርሱ” «ኹን» አለው፤ ኾነም”*፡፡ إِنَّ مَثَلَ عِيسَىٰ عِندَ ٱللَّهِ كَمَثَلِ ءَادَمَ ۖ خَلَقَهُۥ مِن تُرَابٍۢ ثُمَّ قَالَ لَهُۥ كُن فَيَكُونُ

“ኸለቀ” خَلَقَ ማለትም “ፈጠረ” በሚለው ግስ መዳረሻ ቅጥያ ላይ “ሁ” هُۥ ማለት “እርሱ” የሚል ተሳቢ ተውላጠ-ስም አለ፥ ይህም የስም ምትክ “ኣደም” ءَادَم የሚለውን የተጸውዖ ስም ተክቶ የመጣ ነው። አላህ ኣደምን ያለ አባት እና እናት ከአፈር "ኹን" በሚለው ቃል እንደፈጠረው ሁሉ ዒሣን ያለ አባት ከመርየም "ኹን" በሚለው ቃል ፈጥሮታል፦
3፥47 *፡-ጌታዬ ሆይ! ሰው ያልነካኝ ስኾን ለኔ እንዴት ልጅ ይኖረኛል? አለች፡፡ ነገሩ እንዳልሽው ነው፡፡ አላህ የሚሻውን ይፈጥራል፤ አንዳችን በሻ ጊዜ ለእርሱ ኹን ይለዋል፤ ወዲውኑም ይኾናል አላት*፡፡ قَالَتْ رَبِّ أَنَّىٰ يَكُونُ لِي وَلَدٌ وَلَمْ يَمْسَسْنِي بَشَرٌ ۖ قَالَ كَذَٰلِكِ اللَّهُ يَخْلُقُ مَا يَشَاءُ ۚ إِذَا قَضَىٰ أَمْرًا فَإِنَّمَا يَقُولُ لَهُ كُن فَيَكُونُ

አምላካችን አላህ ስለ ዒሣ አፈጣጠር እና ተልእኮ ከ 45-61 ከተረከልን በኃላ ይህ ትርክት "እውነተኛ ታሪክ ነው" ይለናል፦
3፥62 *”ይህ እርሱ በእርግጥ እውነተኛ ታሪክ ነው”*፡፡ አምላክም ከአላህ በስተቀር ምንም የለም፡፡ አላህም እርሱ በእርግጥ አሸናፊው ጥበበኛው ነው፡፡ إِنَّ هَٰذَا لَهُوَ ٱلْقَصَصُ ٱلْحَقُّ ۚ وَمَا مِنْ إِلَٰهٍ إِلَّا ٱللَّهُ ۚ وَإِنَّ ٱللَّهَ لَهُوَ ٱلْعَزِيزُ ٱلْحَكِيمُ

"እውነተኛ ታሪክ ነው" የተባለው ዒሣ ሳይሆን አምላካችን አላህ ስለ ዒሣ የነገረን ትርክት ነው። አላህ በሱረቱል ዐለ-ዒምራን ላይ ያለውን የተንጠለጠለ ትርክት በሱረቱል መርየም ላይ ስለ አፈጣጠሩ እና ስለ ተልእኮው አፈጣጠር ደጋሚ ይነግረናል፦
19፥20 *«ሰው ያልነካኝ ሆኜ አመንዝራም ሳልሆን ለእኔ እንዴት ልጅ ይኖረኛል!» አለች*፡፡ قَالَتْ أَنَّىٰ يَكُونُ لِي غُلَامٌ وَلَمْ يَمْسَسْنِي بَشَرٌ وَلَمْ أَكُ بَغِيًّا
19፥21 *አላት «ነገሩ እንደዚህሽ ነው፡፡» ጌታሽ «እርሱ በእኔ ላይ ገር ነው፡፡ ለሰዎችም ታምር ከእኛም ችሮታ ልናደርገው ይህንን ሠራን የተፈረደም ነገር ነው» አለ*፡፡ قَالَ كَذَٰلِكِ قَالَ رَبُّكِ هُوَ عَلَيَّ هَيِّنٌ ۖ وَلِنَجْعَلَهُ آيَةً لِّلنَّاسِ وَرَحْمَةً مِّنَّا ۚ وَكَانَ أَمْرًا مَّقْضِيًّا

አምላካችን አላህ ስለ ዒሣ አፈጣጠር እና ተልእኮ ከ 20-33 ከተረከልን በኃላ ይህ ትርክት "እውነተኛ ቃል ነው" ይለናል፦
19፥34 *ይህ የመርየም ልጅ ዒሣ ነው፡፡ ያ “በ”እርሱ የሚከራከሩበት እውነተኛ ቃል ነው*፡፡ ذَٰلِكَ عِيسَى ٱبْنُ مَرْيَمَ ۚ قَوْلَ ٱلْحَقِّ ٱلَّذِى فِيهِ يَمْتَرُونَ

“የምተሩነ” يَمْتَرُونَ ማለት “የሚከራከሩበት” ማለት ነው። ብዙ ሰዎች በዒሣ ምንነት ቢከራከሩበትም አላህ ስለ ዒሣ የነገረን ግን እውነተኛ ንግግር ነው። "ሂ" هِ ማለትም "እርሱ" የተባለው ዒሣ ሲሆን “እርሱ” በሚለው መነሻ ቅጥያ ላይ “ፊ” فِي የሚል መስተዋድድ ሲኖር “ስለ”about” ማለት ነው፦ That is Jesus, son of Mary. ˹And this is˺ a word of truth, *“about”* which they dispute.

ስለዚህ ስለ ዒሣ የሚከራከሩበት ግን አላህ የነገረን ቃል እውነት ነው፥ "እውነተኛ ታሪክ" ማለት ስለ ዒሣ የተነገረን እውነተኛ ታሪክ ነው ማለት እንደሆነ ሁሉ "እውነተኛ ቃል" ማለት ስለ ዒሣ የተነገረን እውነተኛ ቃል ነው ማለት ነው። ዒሣ ታሪክ እንዳልሆነም ሁሉ ቃልም አይደለም። የመጣጥፉ ጭብጥ "ዒሣ እውነተኛ ቃል ነው" አልተባለም" የሚል ነው፥ ባይሆን አላህ ስለ ዒሣ የነገረን ቃል እውነተኛ ቃል ነው።

ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
ዕውቀት

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

96፥5 *ሰውን ያላወቀውን ሁሉ ያሳወቀ ሲኾን*፡፡ عَلَّمَ ٱلْإِنسَٰنَ مَا لَمْ يَعْلَمْ

“ዒልም” عِلْم‎ ማለት “ዕውቀት” ማለት ሲሆን “ጀህል” جَهْل ማለት ደግሞ “መሃይምነት” ማለት ነው። ዕውቀት የእምነት መሠረት ነው፥ ያለ ዕውቀት በጭፍንነት የምንከተለው ነገር ጥፋት ነው፦
17፥36 *"ለአንተም በእርሱ ዕውቀት የሌለህን ነገር አትከተል፡፡ መስሚያ፣ ማያም፣ ልብም እነዚህ ሁሉ ባለቤታቸው ከእነርሱ ተጠያቂ ነውና"*፡፡ وَلَا تَقْفُ مَا لَيْسَ لَكَ بِهِ عِلْمٌ ۚ إِنَّ السَّمْعَ وَالْبَصَرَ وَالْفُؤَادَ كُلُّ أُولَـٰئِكَ كَانَ عَنْهُ مَسْئُولًا

ዕውቀት ለማግኘት ደግሞ ማንበብ ጉልህ ሚና አለው። አምላካችን አላህ በጂብሪል ለነቢያችን”ﷺ” “ኢቅራ” اقْرَأْ ማለትም “አንብብ” ብሎ አዟቸዋል፦
96፥1 *”አንብብ በዚያ ሁሉን በፈጠረው ጌታህ ስም”*፡፡ اقْرَأْ بِاسْمِ رَبِّكَ الَّذِي خَلَقَ

“ኢቅራ” ትእዛዛዊ ግስ ሲሆን ቁርኣን ሲጀምር የሚነበበው “ሁሉን በፈጠረው ጌታህ ስም” ነው፥ ከአንድ ሱራህ በስተቀር እያንዳንዱ ሱራህ ከሌላው ሱራህ የሚለየው እና የሚጀምረው “በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩኅ በጣም አዛኝ በኾነው” በሚል ነው፦
ሡነን አቢ ዳውድ መጽሐፍ 2, ሐዲስ 398
ኢብኑ ዐባሥ እንደተረከው፦ *”ነቢዩ”ﷺ” ሁለት ሱራዎች አይለያዩ በመካከላቸው “በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ በጣም አዛኝ በሆነው” የሚለው ቃል ወደ እርሳቸው ቢወርድላቸው እንጂ”*። عَنِ ابْنِ عَبَّاسٍ، قَالَ كَانَ النَّبِيُّ صلى الله عليه وسلم لاَ يَعْرِفُ فَصْلَ السُّورَةِ حَتَّى تُنَزَّلَ عَلَيْهِ ‏{‏ بِسْمِ اللَّهِ الرَّحْمَنِ الرَّحِيمِ ‏}

“ቱነዘለ ዐለይሂ” تُنَزَّلَ عَلَيْهِ ማለትም “ወደ እርሳቸው ቢወርድላቸው” የሚለው ኃይለ-ቃል ይሰመርበት። “በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ በጣም አዛኝ በሆነው” ከአላህ ወደ ነቢያችን”ﷺ” እኛ እንድናነበው የወረደ ነው፦
29፥45 ከመጽሐፍ *ወደ አንተ የተወረደውን አንብብ*፡፡ اتْلُ مَا أُوحِيَ إِلَيْكَ مِنَ الْكِتَابِ
18፥27 ከጌታህም መጽሐፍ *ወደ አንተ የተወረደውን አንብብ*፡፡ وَاتْلُ مَا أُوحِيَ إِلَيْكَ مِن كِتَابِ رَبِّك

ቁርኣንን በማንበብ የሚገኘው ዕውቀት "ነቅል" ይባላል፥ "ነቅል" نَقْل የሚለው ቃል "ነቀለ"نَقَلَ ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን ከአላህ በነቢይ የሚተላለፍ ዕውቀት ነው። አምላካችን አላህ ቁርኣንን በነቢዩ ዐሳወቀ፥ "ዐለመ" عَلَّمَ ማለት "ዐሳወቀ" ማለት ነው። አላህ የማናውቀውን ሁሉ በቁርኣን ስላሳወቀን፥ እርሱ ዘንድ በላጩ ነገር ቁርኣንን ዐውቆ ማሳወቅ ነው፦
55፥2 *"ቁርኣንን አስተማረ"*፡፡ عَلَّمَ الْقُرْآنَ
4፥113 *አላህም በአንተ ላይ መጽሐፍንና ጥበብን አወረደ፡፡ የማታውቀውንም ሁሉ አስተማረህ*፡፡ የአላህም ችሮታ በአንተ ላይ ታላቅ ነው፡፡ وَأَنزَلَ اللَّهُ عَلَيْكَ الْكِتَابَ وَالْحِكْمَةَ وَعَلَّمَكَ مَا لَمْ تَكُن تَعْلَمُ ۚ وَكَانَ فَضْلُ اللَّهِ عَلَيْكَ عَظِيمًا
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 66, ሐዲስ 49
ዑስማን"ረ.ዐ." እንደተረከው፦ "ነቢዩ"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ *"ከእናንተ በላጩ ቁርኣንን ዐውቆ ያሳወቀ ነው"*። نْ عُثْمَانَ ـ رضى الله عنه ـ عَنِ النَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم قَالَ ‏ "‏ خَيْرُكُمْ مَنْ تَعَلَّمَ الْقُرْآنَ وَعَلَّمَهُ

በመቀጠል አሁንም አምላካችን አላህ "አንብብ" የሚል ለሁለተኛ ጊዜ ያዛል፥ አላህ ሰውን ያላወቀውን ሁሉ በቀለም ያሳወቀው ቸር ጌታ ነው፦
96፥3 *"አንብብ! ጌታህ በጣም ቸር ሲኾን"*። اقْرَأْ وَرَبُّكَ الْأَكْرَمُ
96፥4 *"ያ በብርዕ ያስተማረ"*፡፡ ٱلَّذِى عَلَّمَ بِٱلْقَلَمِ
96፥5 *ሰውን ያላወቀውን ሁሉ ያሳወቀ ሲኾን*፡፡ عَلَّمَ ٱلْإِنسَٰنَ مَا لَمْ يَعْلَمْ

"ቀለም" قَلَم የሚለው ቃል "ቀለመ" قَلَمَ‎ ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "ብዕር" ማለት ነው። በቀለም ዕውቀት በማንበብ የምናገኘው ዕውቀት "ዐቅል" ይባላል፥ "ዐቅል" عَقْل የሚለው ቃል "ዐቀለ"عَقَلَ ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን በቀለም የሚተላለፍ ዕውቀት ነው። አምላካችን አላህ ሰውን ሲፈጥረው ቋንቋ መናገርን ዐሳወቀው፥ "ዐለመ" عَلَّمَ ማለት አሁንም "ዐሳወቀ" ማለት ነው፦
55፥3 *"ሰውን ፈጠረ"*፡፡ خَلَقَ ٱلْإِنسَٰنَ
55፥4 *መናገርን አስተማረው*፡፡ عَلَّمَهُ الْبَيَانَ
2፥31 *አደምንም ስሞችን ሁሏንም አስተማረው*፡፡ وَعَلَّمَ ءَادَمَ ٱلْأَسْمَآءَ كُلَّهَا

አምላካችን አላህ ለኣደም የነገርን ስም ዐሳወቀው፥ ይህንን ዕውቀት በማንበብ መፈለግ የሁሉም ሙሥሊም ግዴታ ነው፥ "አንብብ" የሚለው ትእዛዝ ቀዳማይ ተደራሲነቱ ለነቢያችን"ﷺ" ቢሆንም ደኃራይ ተደራሲነቱ ለመላው የሰው ዘር በሙሉ ነው፦
ሡነን ኢብኑ ማጃህ መጽሐፍ 1, ሐዲስ 229
አነሥ ኢብኑ ማሊክ እንደተረከው፦ "የአላህ መልእክተኛም"*" አሉ፦ *"ዕውቀት መፈለግ በሁሉም ሙሥሊም ላይ ግዴታ ነው"*። عَنْ أَنَسِ بْنِ مَالِكٍ قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ طَلَبُ الْعِلْمِ فَرِيضَةٌ عَلَى كُلِّ مُسْلِمٍ

እውነት ነው፤ ዕውቀትን በማንበብ ማግኘት ይቻላል፥ ቀጣዩ ይህንን ዕውቀት በጥበብ መጠቀም ነው። ጥበብን የተሰጠው ሰው ብዙን መልካም ነገር በእርግጥ ተሰጦታል፦
2፥269 *ለሚሻው ሰው ጥበብን ይሰጣል፤ ጥበብንም የሚሰጠው ሰው ብዙን መልካም ነገር በእርግጥ ተሰጠ*፡፡ የአእምሮዎች ባለቤቶች እንጂ ሌላው አይገሰጽም፡፡ يُؤْتِى ٱلْحِكْمَةَ مَن يَشَآءُ ۚ وَمَن يُؤْتَ ٱلْحِكْمَةَ فَقَدْ أُوتِىَ خَيْرًۭا كَثِيرًۭا ۗ وَمَا يَذَّكَّرُ إِلَّآ أُو۟لُوا۟ ٱلْأَلْبَٰبِ

ይህ ሁሉ የሚሆነው አላህ የሻ እንደሆነ ነው፥ አላህ ለሚሻው ሰው ጥበብን ይሰጣል። ይህ ዲን የነቅል ዕውቀት እሳቤ ሆነ የዐቅል ዕውቀት እሳቤ አቅፏል፥ አላህ መልካም የሻለት ሰው ዱኑን ያስገነዝበዋል፦
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 57, ሐዲስ 25
ሙዓዊያህ እንደተረከው፦ "የአላህ መልእክተኛ"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ *"አላህ መልካም የሻለት ሰው ዱኑን ያስገነዝበዋል"*። أَنَّهُ سَمِعَ مُعَاوِيَةَ، قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم ‏ "‏ مَنْ يُرِدِ اللَّهُ بِهِ خَيْرًا يُفَقِّهْهُ فِي الدِّينِ،

አምላካችን አላህ እርሱ በቁርኣኑ የገለጠውን ዲኑል ኢሥላምን ያስገንዝበን! አሚን።

ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
የተረሳው ጂሃድ

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ፥ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

2፥190 *እነዚያንም የሚጋደሉዋችሁን በአላህ መንገድ ተጋደሉ፡፡ ወሰንንም አትለፉ፤ አላህ ወሰን አላፊዎን አይወድምና*፡፡ وَقَاتِلُوا فِي سَبِيلِ اللَّهِ الَّذِينَ يُقَاتِلُونَكُمْ وَلَا تَعْتَدُوا ۚ إِنَّ اللَّهَ لَا يُحِبُّ الْمُعْتَدِينَ

“ጂሃድ” جِهَاد የሚለው ቃል “ጃሀደ” جَٰهَدَ ማለትም “ታገለ” ወይም “ጣረ” አሊያም “ተጋደለ” ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን “ትግል” ወይም “ጥረት” አሊያም “ገድል” ማለት ነው። እውነትን ለማንገስ ሐሰትን ለማርከስ፥ ከሙገሳ እና ከወቀሳ ነጻ ሆኖ በአላህ መንገድ በልቡ፣ በምላሱ እና በእጁ የሚታገል ሙጃሂድ” ْمُجَاهِد ይባላል፥ በብዜት ደግሞ “ሙጃሂዲን” مُجَٰهِدِين ይባላሉ። የመጀመሪያው ጂሃድ ከራስ ጋር የሚደረግ ትግል ነው። ተዝኪያህ ከራሳችን ዝንባሌ ጋር የሚደረግ ጂሃድ ነው፦
ጃምዒ አት-ቲርሚዚይ መጽሐፍ 22, ሐዲስ 3
ፈዷላህ ኢብኑ ዑበይድ እንደተረከው፦ “የአላህ መልእክተኛም”ﷺ” እንዲህ ሲሉ ሰምቻለው፦ *”ከራሱ ነፍስ ጋር የታገለ ሙጃሂድ ነው”*። فَضَالَةَ بْنَ عُبَيْدٍ، وَسَمِعْتُ رَسُولَ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم يَقُولُ ‏”‏ الْمُجَاهِدُ مَنْ جَاهَدَ نَفْسَهُ

እዚህ ሐዲስ ላይ “የታገለ” ለሚለው የገባው ቃል “ጃሀደ” جَاهَدَ መሆኑን ልብ አድርግ። ነፍስን ለማጥራት ተዝኪያህ ማድረግም “ጁሁድ” جُهْد ነው፥ ሸይኩል ኢሥላም ኢብኑ ተይሚያህ ረሒመሁሏህ ስለ ጂሃዱ አን-ነፍሥ ሲናገሩ እንዲህ ብለዋል፦
ረውደቱል ሙሒቢን 1/478
*”ከነፍስ እና ከስሜት ጋር የሚደረግ ጂሃድ ከኩፋር እና ከሙናፊቂ ጋር ለሚደረግ ጂሃድ መሠረት ነው። እርሱ(ሙሥሊም) እነርሱን ከመታገሉ በፊት ቅድሚያ ነፍሱና ስሜቱን መታገል ይቀድማልና”*። جِهَادُ النَّفْسِ وَالْهَوَى أَصْلُ جِهَادِ الْكُفَّارِ وَالْمُنَافِقِينَ فَإِنَّهُ لَا يَقْدِرُ عَلَى جِهَادِهِمْ حَتَّى يُجَاهِدَ نَفْسَهُ وَهَوَاهُ أَوَّلًا حَتَّى يَخْرُجَ إلَيْهِمْ

ቅድሚያ ውስጣቸን ካለው ዘረኝነት፣ ጎጠኝነት፣ ጠርዘኝነት፣ ቡድንተኝነት ጋር መፋለም አለብን። ይህ ጂሃዱ አን-ነፍሥ ሲሆን ሁለተኛ ጂሃድ ከኩፋር እና ከሙናፊቂ ጋር የሚደረግ ጂሃድ ነው። ይህ ጂሃድ ከኢማን ቀጥሎ ያለው የተሻለ ሥራ ነው፦
ኢማም ቡኻሪይ መጽሐፍ 25 , ሐዲስ 7:
አቢ ሁረይራህ”ረ.ዐ” እንደተረከው፦ *“ነቢዩ”ﷺ” የትኛው ነው የተሻለ ድርጊት? ተብለው ተጠይቀው ነበር፥ እርሳቸውም፦ “በአላህ እና በመልእክተኛው ማመን” አሉ። በመቀጠልስ? ተብለው ተጠየቁ፥ እርሳቸውም፦ “በአላህ መንገድ ጂሃድ ላይ መሳተፍ” አሉ። በመቀጠልስ? ተብለው ተጠየቁ፥ እርሳቸውም፦ “ሐጅ መብሩር” አለ*። عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ ـ رضى الله عنه ـ قَالَ سُئِلَ النَّبِيُّ صلى الله عليه وسلم أَىُّ الأَعْمَالِ أَفْضَلُ قَالَ ‏”‏ إِيمَانٌ بِاللَّهِ وَرَسُولِهِ ‏”‌‏.‏ قِيلَ ثُمَّ مَاذَا قَالَ ‏”‏ جِهَادٌ فِي سَبِيلِ اللَّهِ ‏”‌‏.‏ قِيلَ ثُمَّ مَاذَا قَالَ ‏”‏ حَجٌّ مَبْرُورٌ ‏”‌‏.‏
ሡነን አቢ ዳውድ መጽሐፍ 15, ሐዲስ 28
አነሥ እንደተረከው፦ “ነቢዩም”ﷺ” አሉ፦ *”በንብረታችሁ፣ በነፍሶቻችሁ እና በአንደበታችሁ ሙሽሪኮችን ታገሉ”*። عَنْ أَنَسٍ، أَنَّ النَّبِيَّ صلى الله عليه وسلم قَالَ ‏:‏ ‏ “‏ جَاهِدُوا الْمُشْرِكِينَ بِأَمْوَالِكُمْ وَأَنْفُسِكُمْ وَأَلْسِنَتِكُمْ ‏

"ጃሂዱ" جَاهِدُوا የሚለው ኃይለ-ቃል ይሰመርበት። ይህም ጂሃድ ወሰን አልፈው ለሚመጡ ሁሉ በአላህ መንገድ መጋደል ነው፦
2፥190 *እነዚያንም የሚጋደሉዋችሁን በአላህ መንገድ ተጋደሉ፡፡ ወሰንንም አትለፉ፤ አላህ ወሰን አላፊዎን አይወድምና*፡፡ وَقَاتِلُوا فِي سَبِيلِ اللَّهِ الَّذِينَ يُقَاتِلُونَكُمْ وَلَا تَعْتَدُوا ۚ إِنَّ اللَّهَ لَا يُحِبُّ الْمُعْتَدِينَ
2፥218 *እነዚያ ያመኑትና እነዚያም ከአገራቸው የተሰደዱት በአላህም መንገድ ላይ የተጋደሉት እነዚያ የአላህን እዝነት ይከጅላሉ*፡፡ አላህም እጅግ መሓሪ አዛኝ ነው፡፡ إِنَّ الَّذِينَ آمَنُوا وَالَّذِينَ هَاجَرُوا وَجَاهَدُوا فِي سَبِيلِ اللَّهِ أُولَـٰئِكَ يَرْجُونَ رَحْمَتَ اللَّهِ ۚ وَاللَّهُ غَفُورٌ رَّحِيمٌ
2፥193 *ሁከት እስከማይገኝ እና ሃይማኖት ለአላህ ብቻ እስከሚኾን ድረስ ተጋደሉዋቸው፡፡ ቢከለክሉም ወሰንን ማለፍ በበዳዮች ላይ እንጂ የለም ወሰን አትለፉባቸው*፡፡ وَقَاتِلُوهُمْ حَتَّىٰ لَا تَكُونَ فِتْنَةٌ وَيَكُونَ الدِّينُ لِلَّهِ ۖ فَإِنِ انتَهَوْا فَلَا عُدْوَانَ إِلَّا عَلَى الظَّالِمِينَ
ይህ የሚሆነው ሰላም ሆኖ ሁከት እስከሚጠፋ ድረስ እና ሃይማኖት ለአላህ እስከሚሆን ድረስ ነው። “እነዚያንም የሚጋደሉዋችሁን በአላህ መንገድ ተጋደሉ” እስከ መቼ? “ሃይማኖት ለአላህ ብቻ እስከሚኾን ድረስ” እስከ ትንሳኤ ቀን ድረስ ወሰን አልፎ በሚመጣው ላይ ለእነዚያ ለሚገደሉት ምእመናን እነርሱ የተበደሉ በመኾናቸው መጋደል ተፈቀደላቸው፦
22፥39 *ለእነዚያ ለሚገደሉት ምእመናን እነርሱ የተበደሉ በመኾናቸው መጋደል ተፈቀደላቸው*፡፡ أُذِنَ لِلَّذِينَ يُقَاتَلُونَ بِأَنَّهُمْ ظُلِمُوا ۚ وَإِنَّ اللَّهَ عَلَىٰ نَصْرِهِمْ لَقَدِيرٌ

መጋደል ከሌለ ገዳማት፣ ቤተክርስቲያኖችም፣ ምኩራቦችም በውስጣቸው የአላህ ስም በብዛት የሚወሳባቸው መስጊዶችም ይፈርሳሉ፦
22፥40 *ለእነዚያ «ጌታችን አላህ ነው» ከማለታቸው በስተቀር ያለ አግባብ ከአገራቸው የተባረሩ ለሆኑት ተፈቀደ፡፡ አላህ ሰዎችን ከፊላቸውን በከፊሉ መገፍተሩ ባልነበረ ኖሮ ገዳማት፣ ቤተክርስቲያኖችም፣ ምኩራቦችም በውስጣቸው የአላህ ስም በብዛት የሚወሳባቸው መስጊዶችም፤ በተፈረሱ ነበር*፡፡ አላህም ሃይማኖቱን የሚረዳውን ሰው በእርግጥ ይረዳዋል፡፡ አላህ ብርቱ አሸናፊ ነውና፡፡ الَّذِينَ أُخْرِجُوا مِن دِيَارِهِم بِغَيْرِ حَقٍّ إِلَّا أَن يَقُولُوا رَبُّنَا اللَّهُ ۗ وَلَوْلَا دَفْعُ اللَّهِ النَّاسَ بَعْضَهُم بِبَعْضٍ لَّهُدِّمَتْ صَوَامِعُ وَبِيَعٌ وَصَلَوَاتٌ وَمَسَاجِدُ يُذْكَرُ فِيهَا اسْمُ اللَّهِ كَثِيرًا ۗ وَلَيَنصُرَنَّ اللَّهُ مَن يَنصُرُهُ ۗ إِنَّ اللَّهَ لَقَوِيٌّ عَزِيزٌ

በአላህ መንገድ ከጠላት ጋር የሚደረግ ጂሃድ ሦስት አይነት ነው፥ እርሱም በእጅ የሚደረግ፣ በምላስ የሚደረግ እና በልብ የሚደረግ ነው፦
ሪያዱ አስ-ሷሊሒን መጽሐፍ 1, ሐዲስ 184
አቢ ሠዒድ አል-ኹድሪይ”ረ.ዐ.” እንደተረከው፦ “የአላህ መልክተኛ”ﷺ” እንዲህ ሲሉ ሰምቻቸዋለሁ፦ *“ከእናንተ ውስጥ እኩይ ነገር ያየ በእጁ ይቀይረው፣ ካልቻለ በምላሱ ያውግዝ፣ ይህንንም ካልቻለ በልቡ ይጥላው። በልብ መጥላት ደካማው ኢማን ነው”*። عن أبي سعيد الخدري رضي الله عنه قال‏:‏ سمعت رسول الله صلى الله عليه وسلم يقول‏:‏ ‏ “‏من رأى الخد منكرًا فليغيره بيده ، فإن لم يستطع فبلسانه، فإن لم يستطع فبقلبه وذلك أضعف الإيمان

ሡናውን የሚይዙ እና በትእዛዙ የሚመሩ ቀደምት ሠለፎች ጂሃድን መንሃጃቸው አርገው አልፈዋል፥ የሚያሳዝነው ዛሬ ያለነው "ከእነርሱ በኃላ የማያደርጉትን የሚናገሩ እና ያልታዘዙትን የሚያደርጉ ተተኪዎች ይመጣሉ" የተባልነው ትውልድ ነን፦
ኢማም ሙሥሊም መጽሐፍ 1, ሐዲስ 86
ዐብደላህ ኢብኑ መሥዑድ እንደተረከው፦ "የአላህ መልእክተኛ"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ *"አላህ ከእኔ ሕዝብ በፊት ከነቢይ አንድንም አላከም፥ ሡናውን የሚይዙ እና በትእዛዙ የሚመሩ ሐዋርያት እና ባልደረቦች ከሕዝቡ ቢያደርግለት እንጂ። ከዚያም ከእነርሱ በኃላ የማያደርጉትን የሚናገሩ እና ያልታዘዙትን የሚያደርጉ ተተኪዎች ይመጣሉ። እነርሱን በእጁ የታገላቸው እርሱ አማኝ ነው፣ በምላሱ የታገላቸው እርሱ አማኝ ነው፣ በልቡ የታገላቸው እርሱ አማኝ ነው። ከዚህ ውጪ የጎመንዘር ያህል ኢማን የለም"*። عَنْ عَبْدِ اللَّهِ بْنِ مَسْعُودٍ، أَنَّ رَسُولَ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم قَالَ‏ "‏ مَا مِنْ نَبِيٍّ بَعَثَهُ اللَّهُ فِي أُمَّةٍ قَبْلِي إِلاَّ كَانَ لَهُ مِنْ أُمَّتِهِ حَوَارِيُّونَ وَأَصْحَابٌ يَأْخُذُونَ بِسُنَّتِهِ وَيَقْتَدُونَ بِأَمْرِهِ ثُمَّ إِنَّهَا تَخْلُفُ مِنْ بَعْدِهِمْ خُلُوفٌ يَقُولُونَ مَا لاَ يَفْعَلُونَ وَيَفْعَلُونَ مَا لاَ يُؤْمَرُونَ فَمَنْ جَاهَدَهُمْ بِيَدِهِ فَهُوَ مُؤْمِنٌ وَمَنْ جَاهَدَهُمْ بِلِسَانِهِ فَهُوَ مُؤْمِنٌ وَمَنْ جَاهَدَهُمْ بِقَلْبِهِ فَهُوَ مُؤْمِنٌ وَلَيْسَ وَرَاءَ ذَلِكَ مِنَ الإِيمَانِ حَبَّةُ خَرْدَلٍ ‏

በእጅ፣ በምላስ እና በልቡ ያልታገለ የጎመንዘር ያህል ኢማን የለውም። ምእምናን ማለት በገንዘቦቻቸው እና በነፍሶቻቸውም በአላህ መንገድ የታገሉት ብቻ ናቸው፥ እነዚያ እነርሱ እውነተኞቹ ናቸው። አላህ እኛን ውርደት ያከናነበን ከጂሃድ በመራቃችን ነው፦
49፥15 *ምእምናን እነዚያ በአላህ እና በመልእከተኛው ያመኑት ከዚያም ያልተጠራጠሩት “በገንዘቦቻቸው እና በነፍሶቻቸውም በአላህ መንገድ የታገሉት ብቻ ናቸው”፡፡ እነዚያ እነርሱ እውነተኞቹ ናቸው*፡፡ إِنَّمَا الْمُؤْمِنُونَ الَّذِينَ آمَنُوا بِاللَّهِ وَرَسُولِهِ ثُمَّ لَمْ يَرْتَابُوا وَجَاهَدُوا بِأَمْوَالِهِمْ وَأَنفُسِهِمْ فِي سَبِيلِ اللَّهِ ۚ أُولَـٰئِكَ هُمُ الصَّادِقُونَ
ሡነን አቢ ዳውድ መጽሐፍ 24, ሐዲስ 47
ኢብኑ ዑመር"ረ.ዐ." እንደተረከው፦ የአላህ መልእክተኛ"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ *"በሪባ በተገበያያቹህ ጊዜ፣ ከብቶችን በተከትላችሁ ጊዜ፣ እርሻኝ በወዳዳቹህ ጊዜ እና ጂሃድን በተዋቹህ ጊዜ አላህ ውርደት ያከናንባችኃል፥ ይህንንም ውርደት ወደ ዲናቹህ እስካልተመለሳቹህ ድረስ ከእናንተ አያነሳም"*። عَنِ ابْنِ عُمَرَ، قَالَ سَمِعْتُ رَسُولَ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم يَقُولُ ‏ "‏ إِذَا تَبَايَعْتُمْ بِالْعِينَةِ وَأَخَذْتُمْ أَذْنَابَ الْبَقَرِ وَرَضِيتُمْ بِالزَّرْعِ وَتَرَكْتُمُ الْجِهَادَ سَلَّطَ اللَّهُ عَلَيْكُمْ ذُلاًّ لاَ يَنْزِعُهُ حَتَّى تَرْجِعُوا إِلَى دِينِكُمْ

መሣጂዶች ሲፈርሱና ሲቃጠሉ በእጃችን ካተከላከልን ወይም በምላሳችን ካልተቃወምን አሊያም በልባችን ጉዳዩን ካልጠላን የእኛ ዲነኛ መሆን ፋይዳው ምኑ ላይ ነው? አላህ በእርሱን መንገድ የሚታገሉ ሙጃሂድ ያድርገን! አሚን።

ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
ቅድስት ሥላሴ

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ፥ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።

4፥171 *”እናንተ የመጽሐፉ ሰዎች ሆይ! በሃይማኖታችሁ ወሰንን አትለፉ፡፡ በአላህም ላይ እውነትን እንጅ አትናገሩ”*፡፡ .. *”«ሦስት ናቸው» አትበሉም”*፡፡ ተከልከሉ፤ ለእናንተ የተሻለ ይኾናልና፡፡ *”አላህ አንድ አምላክ ብቻ ነው”*፡፡ يَٰٓأَهْلَ ٱلْكِتَٰبِ لَا تَغْلُوا۟ فِى دِينِكُمْ وَلَا تَقُولُوا۟ عَلَى ٱللَّهِ إِلَّا ٱلْحَقَّ ۚ إِنَّمَا ٱلْمَسِيحُ عِيسَى ٱبْنُ مَرْيَمَ رَسُولُ ٱللَّهِ وَكَلِمَتُهُۥٓ أَلْقَىٰهَآ إِلَىٰ مَرْيَمَ وَرُوحٌۭ مِّنْهُ ۖ فَـَٔامِنُوا۟ بِٱللَّهِ وَرُسُلِهِۦ ۖ وَلَا تَقُولُوا۟ ثَلَٰثَةٌ ۚ ٱنتَهُوا۟ خَيْرًۭا لَّكُمْ ۚ إِنَّمَا ٱللَّهُ إِلَٰهٌۭ وَٰحِدٌۭ ۖ سُبْحَٰنَهُۥٓ أَن يَكُونَ لَهُۥ وَلَدٌۭ ۘ لَّهُۥ مَا فِى ٱلسَّمَٰوَٰتِ وَمَا فِى ٱلْأَرْضِ ۗ وَكَفَىٰ بِٱللَّهِ وَكِيلًۭا

አምላካችን አላህ በቁርኣን ከተገለጹት ስሞቹ አንዱ "አል-ቁዱሥ" الْقُدُّوس ሲሆን ትርጉሙ "ቅዱሱ" ወይም "ከጉድለት ሁሉ የጠራው" ማለት ነው፦
59፥23 እርሱ አላህ ነው፡፡ ያ ከእርሱ በቀር ሌላ አምላክ የሌለ፣ ንጉሡ፣ *ቅዱሱ*፣ የሰላም ባለቤቱ፣ ጸጥታን ሰጪው፣ ባሮቹን ጠባቂው፣ አሸናፊው፣ ኀያሉ፣ ኩሩው ነው፡፡ አላህ ከሚያጋሩት ሁሉ ጠራ፡፡ هُوَ اللَّهُ الَّذِي لَا إِلَـٰهَ إِلَّا هُوَ الْمَلِكُ الْقُدُّوسُ السَّلَامُ الْمُؤْمِنُ الْمُهَيْمِنُ الْعَزِيزُ الْجَبَّارُ الْمُتَكَبِّرُ ۚ سُبْحَانَ اللَّهِ عَمَّا يُشْرِكُونَ
62፥1 በሰማያት ያለው በምድርም ያለው ሁሉ ለአላህ ንጉሥ፣ *ቅዱስ*፣ አሸናፊ፣ ጥበበኛ ለኾነው ያሞግሳል፡፡ يُسَبِّحُ لِلَّهِ مَا فِي السَّمَاوَاتِ وَمَا فِي الْأَرْضِ الْمَلِكِ الْقُدُّوسِ الْعَزِيزِ الْحَكِيمِ

በባይብልም ከሄድን አንዱ አምላክ "ቅዱስ" ተብሏል፥ እንደ እርሱ ያለ ቅዱስ የለም፦
1ኛ ሳሙኤል 2፥2 *“እንደ ያህዌህ ቅዱስ የለምና”፥ እንደ አምላካችንም ጻድቅ የለምና፤ “ከአንተ በቀር ቅዱስ” የለም*።
ራእይ 15፥4 *“አንተ ብቻ ቅዱስ” ነህና*፥

“አንተ” የሚለው ነጠላ ተውላጠ-ስም አንድ ነጠላ ማንነት ብቻ ቅዱስ እንደተባለ ፍትውና ቁልጭ አድርጎ ያስረዳል፥ ሶስት ማንነትቶች ቢሆኑ ኖሮ “እናንተ” ተብሎ ይቀመጥ ነበር። “ከእናንተ” በቀር ቅዱስ የለም” ቢል ኖሮ ለሶስት አካላት ያዋጣ ነበር፥ ቅሉ ግን "አንተ ብቻ ቅዱስ ነህ" ተብሏል። እርሱ ቅዱስ የተባለው ፍጡራን በተባሉበት ስሌትና ቀመር አይደለም፥ ለምሳሌ ሰው እና መላእክት ቅዱሳን ተብለዋል፦
ዘሌዋውያን 11፥45 *እንግዲህ “እኔ ቅዱስ ነኝ እና እናንተ ቅዱሳን”* ሁኑ።
ኢዮብ 15፥15 እነሆ፥ *በቅዱሳኑ ስንኳ አይታመንም*፤ ሰማያትም በፊቱ ንጹሐን አይደሉም።

"ቅዱስ" ነጠላ ተባዕታይ መደብ ሲሆን የቅዱስ ብዙ ቁጥር "ቅዱሳን" ነው። የሥላሴ አማንያን"Trinitarian"፦ "መላእክት አንዱን አምላክ ሦስት ጊዜ “ቅዱስ፥ ቅዱስ፥ ቅዱስ” ማለታቸው ሦስት አካላት እንዳሉ ማሳያ ነው" የሚል ስሁት ሙግት አላቸው፦
ኢሳይያስ 6፥3 አንዱም ለአንዱ፦ *“ቅዱስ፥ ቅዱስ፥ ቅዱስ፥” የሠራዊት ጌታ ያህዌህ፤ ምድር ሁሉ ከክብሩ ተሞልታለች እያለ ይጮኽ ነበር*።
ራእይ 4፥8 *“ቅዱስ፥ ቅዱስ፥ ቅዱስ” የነበረውና ያለ የሚመጣውም ሁሉንም የሚገዛ ጌታ አምላክ እያሉ ቀንና ሌሊት አያርፉም*።

ይህ ሙግት ውኃ የማያነሳ እና የማይቋጥር ሙግት ነው። ምክንያቱም አንድ ነገር ሦስት ጊዜ መጠቀሱ ያንን ነገር ሦስት ካደረገው ኤርሚያስ ምድርን ሦስት ጊዜ “ምድር ሆይ፥ ምድር ሆይ፥ ምድር ሆይ” ብሎ ጠርቷል፦
ኤርምያስ 22፥29 *“ምድር ሆይ፥ ምድር ሆይ፥ ምድር ሆይ”*፥ የእግዚአብሔርን ቃል ስሚ።

ምድር ሦስት ጊዜ መጠራቷ ምድር ሦስት አካላት ናት ያሰኛልን? በተጨማሪ ኤርሚያስ የእግዚአብሔርን መቅደስ ሦስት ጊዜ “የእግዚአብሔር መቅደስ፥ የእግዚአብሔር መቅደስ፥ የእግዚአብሔር መቅደስ” ብሎ ጠርቷል፦
ኤርሚያስ 7፥4 *የእግዚአብሔር መቅደስ፥ የእግዚአብሔር መቅደስ፥ የእግዚአብሔር መቅደስ ይህ ነው እያላችሁ በሐሰት ቃል አትታመኑ*።

የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ሦስት ጊዜ መጠራቱ የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ሦስት አካላት ነው ያሰኛልን? ሌላ ናሙና የይሁዳ ምድር ባድማ እንደሚያደርጋት ሦስት ጊዜ ተናግሯል፦
ሕዝቅኤል 21፥27 *ባድማ፥ ባድማ፥ ባድማ አደርጋታለሁ*።

ባድማ እንደሚያደርግ ሦስት ጊዜ መናገሩ ሦስት ጊዜ ማድረጉን ያሰኛልን? መጽሐፈ ኩፋሌ የሚባለው የኦርቶዶክስ የቀኖና መጽሐፍ ላይ ደግሞ አብርሃምን ሦስት ጊዜ አብርሃም፥ አብርሃም፥ አብርሃም” ይለዋል፦
ኩፋሌ 14፥5 “እግዚአብሔርም *አብርሃምን፥ “አብርሃም፥ አብርሃም፥ አብርሃም” ብሎ ጠራው፥ አብርሃምም “አቤት አለሁ”አለ*።

አብርሃም ሦስት ጊዜ መጠራቱ አብርሃም ሦስት አካላት ነው ያሰኛልን? መልክአ ኢየሱስ የሚባለው የኦርቶዶክስ መጽሐፍ ላይ ኢየሱስን ሦስት ጊዜ “ኢየሱስ፥ ኢየሱስ፥ ኢየሱስ" ይለዋል፦
*“ኢየሱስ ኢየሱስ፥ ኢየሱስ”* ክርስቶስ ዘሰረጽከ እመቤተ ሌዊ ኮሬባዊ መለኮታዊ ቃል ሰማያዊ እም ድንግል ተወለደ።

ኢየሱስ የሚለው ቃል ሦስት ጊዜ መደገሙ ከድንግል የተወለደው ኢየሱስ ሦስት አካላት ነውን? ዘፍጥረት ላይ ደግሞ አብርሃም ሁለቴ ስሙ ተደግሟል፦
ዘፍጥረት 22፥11የእግዚአብሔር መልአክም ከሰማይ ጠራና። *“አብርሃም፥ አብርሃም”* አለው።
አብርሃም ሁለት አካል ነውን? ኢየሱስን ሁለት ጊዜ “ጌታ ሆይ ጌታ ሆይ” ይሉታል፦
ማቴዎስ 7፥21 *“ጌታ ሆይ፥ ጌታ ሆይ”* የሚለኝ ሁሉ መንግስተ ሰማያት የሚገባ አይደለም።

ኢየሱስ ሁለት አካል ነውን? ሙሴ ሁለት ጊዜ “ሙሴ ሙሴ፥ ሙሴ ሙሴ” ተብሏል፦
ዘጽአት 3፥4 “እግዚአብሔር ከቁጥቋጦው ውስጥ እርሱን ጠርቶ፦ *ሙሴ፥ ሙሴ ሆይ አለ*።

ሙሴ ሁለት አካል ነውን? እንዳትሰክሩ ብለን እንጂ ማስረጃ በቁና ሰፍረን መስጠት እንችላለን። አይሁዶች በሥላሴ አያምኑም፥ ታዲያ ለምን አንድ ጉዳይ ሶስት ጊዜ ተደጋገመ? ለሚለው መልሳቸው "አንድ ስም ከአንድ በላይ ጊዜ መጠራት ጉዳዩን አጽንዖትና አንክሮት ለመስጠት እንጂ ያንን ስም ብዙ አካል አያደርገውም" ይላሉ።
ሲቀጥል “ቅዱስ” ተባታይ ሲሆን “ቅድስት” አንስታይ ነው፥ ሥላሴ ልክ እንደ “አጋእዝት” ማለትም “ጌቶች” ተብለው እንደሚጠቀሙበት “ቅዱሳን” ተብሎ መጠራት ነበረባቸው እንጂ እንደ ሴት “ቅድስት” እንዴት ይባላሉ? ሥላሴ ሴት ናት እንዴ “ቅድስት” የተባለችው? "አይ አዛኝ “ስለሆኑ” ነው" ብሎ አንድ ክርስቲያን ወገን የቋንቋ፣ የሰዋስው ወይም የባይብል መረጃ የሌለው የጨበጣ መልስ ሰቶኛል። “ስለሆነ” ተብሎ የሚመለክ እንጂ “ስለሆኑ” ተብለው የሚመለኩ ሦስት ቅዱሳን የሉም።

ሢሰልስ "ቅድስት" ለብዙ ቁጥር ወይም ለማኅበር ይውላል፥ ለዛ ነው "ሥሉስ ቅዱስ" ማለትም "ሦስት ቅዱስ" የሚሉት። "ሦስት ቅዱስ አለ" ብሎ ማመን የጤንነት ነውን? በሦስነቱ ሲቀደስ እና ሢሰለስ የሚኖር አምላክ በባይብል ሽታው የለም። ከዚህ በተቃራኒ ውዳሴ ማርያም ይወድስዋ ላይ መልአኩ ማርያምን ሦስት ቅዱስ እንዳለና ወልድ "ከሦስቱ ቅዱስ አንዱ ቅዱስ ነው" ይለናል፦
"መልአኩም እንዲህ አላት፦ "መንፈስ ቅዱስ ይጠብቅሻል የልዑል ኃይልም ያድርብሻል፥ *ይህ የሚወለደው ከሦስቱ ቅዱስ አንዱ ቅዱስ ነው*።

"ይህ የሚወለደው ከሦስቱ ቅዱስ አንዱ ቅዱስ ነው" የሚለው ኃይለ-ቃል ሉቃስ ላይ አለመኖሩ በራሱ የተጭበረበረ ሐረግ ነው። እናንተ የመጽሐፉ ሰዎች ሆይ! በአላህም ላይ እውነትን እንጅ አትናገሩ፡፡ ፈጣሪን «ሦስት ናቸው» አትበሉም፥ ተከልከሉ። ለእናንተ የተሻለ ይኾናልና፡፡ አላህ በአንድነቱ ላይ ሦስትነት የሌለበት አንድ አምላክ ብቻ ነው፦
4፥171 *”እናንተ የመጽሐፉ ሰዎች ሆይ! በሃይማኖታችሁ ወሰንን አትለፉ፡፡ በአላህም ላይ እውነትን እንጅ አትናገሩ”*፡፡ .. *”«ሦስት ናቸው» አትበሉም”*፡፡ ተከልከሉ፤ ለእናንተ የተሻለ ይኾናልና፡፡ *”አላህ አንድ አምላክ ብቻ ነው”*፡፡ يَٰٓأَهْلَ ٱلْكِتَٰبِ لَا تَغْلُوا۟ فِى دِينِكُمْ وَلَا تَقُولُوا۟ عَلَى ٱللَّهِ إِلَّا ٱلْحَقَّ ۚ إِنَّمَا ٱلْمَسِيحُ عِيسَى ٱبْنُ مَرْيَمَ رَسُولُ ٱللَّهِ وَكَلِمَتُهُۥٓ أَلْقَىٰهَآ إِلَىٰ مَرْيَمَ وَرُوحٌۭ مِّنْهُ ۖ فَـَٔامِنُوا۟ بِٱللَّهِ وَرُسُلِهِۦ ۖ وَلَا تَقُولُوا۟ ثَلَٰثَةٌ ۚ ٱنتَهُوا۟ خَيْرًۭا لَّكُمْ ۚ إِنَّمَا ٱللَّهُ إِلَٰهٌۭ وَٰحِدٌۭ ۖ سُبْحَٰنَهُۥٓ أَن يَكُونَ لَهُۥ وَلَدٌۭ ۘ لَّهُۥ مَا فِى ٱلسَّمَٰوَٰتِ وَمَا فِى ٱلْأَرْضِ ۗ وَكَفَىٰ بِٱللَّهِ وَكِيلًۭا

አላህ ሂዳያ ይስጣችሁ፥ እኛንም በተውሒድ ያጽናን! አሚን።

ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
ታላቁ ታምር

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

6:124 "ታምርም" በመጣላቸው ጊዜ፡- «የአላህ መልክተኞች የተሰጡትን ብጤ እስክንሰጥ ድረስ በፍጹም አናምንም» አሉ وَإِذَا جَآءَتْهُمْ ءَايَةٌۭ قَالُوا۟ لَن نُّؤْمِنَ حَتَّىٰ نُؤْتَىٰ مِثْلَ مَآ أُوتِىَ رُسُلُ ٱللَّهِ ۘ ٱللَّهُ أَعْلَمُ حَيْثُ يَجْعَلُ رِسَالَتَهُۥ ۗ سَيُصِيبُ ٱلَّذِينَ أَجْرَمُوا۟ صَغَارٌ عِندَ ٱللَّهِ وَعَذَابٌۭ شَدِيدٌۢ بِمَا كَانُوا۟ يَمْكُرُونَ ፡፡

ቁርኣን ለነቢያችን ነቢይነት ማረጋገጫ ይሆን ዘንድ ከተሰጣቸው ተአምራት ውስጥ ታላቁ እና ዋነኛው ነው፣ የቁርኣን ተአምራዊነት ከቀደምት ነቢያት ተአምራት በሁለት መልኩ ይለያል፦
አንደኛ የቀደምት ነቢያት ተአምራት በአይን የሚታይ፣ በእጅ የሚዳሰስ ነው፣ ይህም ታምር ”ሒስሲይ” ይባላል፣ የቀደምት ነቢያት ተአምር ከነቢይነት ዘመናቸው ጋር ብቻ የተቆራኘ ነው፣ ከእነርሱ ሞት በኋላ ያበቃል፣ ይህም ታምር ”ወቅቲይ” ማለትም ጊዜአዊ ይሰኛል፡፡
ሁለተኛ ለነቢያችን ነቢይነት እንደ ማስረጃ የተሰጣቸው ቁርኣን ግን ህሊናን የሚያናግር፡ አእምሮን የሚቆጣጠርና ልብን የሚገዛ፣ በሚያስተላልፋቸው መልእክቱ ሰዎችን ለለውጥ የሚዳርግ ነው፣ ይህም ታምር ”መዕነዊይ” ይባላል፣ ቁርኣን ከነቢያችን ሞት በኋላ እንኳ ተአምራዊነቱ አላከተመም፣ እስከ ቂያማ ድረስ በነበረው ተአምራዊነቱ ይቀጥላል፤ በዚህም ”አበዲይ” ይሰኛል፡፡ እስቲ ይህንን ታላቅ ታምር በወረደበት ወቅት ሰዎች እንዴት እንዳስተባበሉት እንመልከት፦

ነጥብ አንድ
"የአላህ ታምራት"
ቁርአን በወረደ ጊዜ ሰዎች፦ "ከጌታውም በእርሱ ላይ ለምን ተዓምር አልተወረደም" አሉ፤ አምላካችን አላህም፦ "አላህ ተአምርን በማውረድ ላይ ቻይ ነው" በላቸው ብሎ መለሰ ሰጠ፦
6:37 *«ከጌታውም በእርሱ ላይ ለምን ተዓምር አልተወረደም»* አሉ፡፡ *«አላህ ተአምርን በማውረድ ላይ ቻይ ነው» በላቸው*፡፡ ግን አብዛኞቻቸው አያውቁም፡፡

አላህ ቁርኣንን ታምር አድርጎ ለነቢያችን ነቢይነት ማረጋገጫ ይሆን ዘንድ እንዳወረደው ይናገራል፦
3:108 ይህች በአንተ ላይ በእዉነት የምናነባት ስትሆን የአላህ *ታምራት* آيَاتُ ናት፤
45:6 እነዚህ፣ በአንተ ላይ በእውነት የምናነባቸው ሲኾኑ *የአላህ ታምራት* آيَاتُ ናቸው፤ ከአላህና *ከታምራቶቹም* وَآيَاتِهِ ወዲያ በየትኛው ንግግር ያምናሉ?
2:252 እነዚህ በእውነት በአንተ ላይ የምናነባቸው ሲኾኑ *የአላህ ታምራት* آيَاتُ ናቸው፤
3:58 ይህ *ከታምራቶች"* الْآيَاتِ እና ጥበብን ከያዘዉ ተግሣጥ ሲሆን በአንተ ላይ እናነበዋለን።

አላህ የሚነበብ ሆኖ ቁርአን መወረዱ ታምር እንደሆነ እንደነገረን ሁሉ ነብያችንም ቁርአን ለእሳቸው ነብይነት ታምር እንደሆነ በአጽንኦትና በአንክሮት ነግረውናል፦
ኢማም ቡኻሪይ መጽሐፍ 66 , ሐዲስ 3:
አቢ ሁረይራህ"ረ.ዐ." እንደተረከው፦ ነብዩ"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ ማንኛውም ነብይ ህዝቦቹ ያምኑበት ዘንድ ታምር ተሰጠውታል፣ ነገር ግን ለእኔ የተሰጠኝ ታምር አላህ ወደ እኔ ያወረደው ወህይ ነው عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ، قَالَ قَالَ النَّبِيُّ صلى الله عليه وسلم ‏ "‏ مَا مِنَ الأَنْبِيَاءِ نَبِيٌّ إِلاَّ أُعْطِيَ مَا مِثْلُهُ آمَنَ عَلَيْهِ الْبَشَرُ، وَإِنَّمَا كَانَ الَّذِي أُوتِيتُ وَحْيًا أَوْحَاهُ اللَّهُ إِلَىَّ فَأَرْجُو أَنْ أَكُونَ أَكْثَرَهُمْ تَابِعًا يَوْمَ الْقِيَامَةِ ‏" ።

ነጥብ ሁለት
"ማስተባበያ"
ሰዎች ቁርአን ታምር ሆኖ በመጣላቸው ጊዜ፡- "የአላህ መልክተኞች የተሰጡትን ብጤ እስክንሰጥ ድረስ በፍጹም አናምንም" ወይም "ለሙሳ የተሰጠው ቢጤ አይሰጠውም ኖሯልን ” ብለው ይህንን ታምር አስተባበሉ፦
6:124 *"ታምርም በመጣላቸው ጊዜ"*፡- «የአላህ መልክተኞች የተሰጡትን ብጤ እስክንሰጥ ድረስ በፍጹም አናምንም» አሉ፡፡
28:48 እውነቱም ከእኛ ዘንድ በመጣላቸው ጊዜ “ለሙሳ የተሰጠው ቢጤ አይሰጠውም ኖሯልን ” አሉ ። ከዚህ በፊት ሙሳ በተሰጠው አልካዱምን? አሉም “የተረዳዱ ሁለት ድግምተኞች ናቸው” ፤ አሉም “እኛ በሁለቱም ከሀዲዎች ነን”።

ለሙሳ የተሰጠው ግልጽ የሆኑን "ዘጠኝ ታምራቶች" ናቸው፦
17:101 ለሙሳም ግልጽ የሆኑን "ዘጠኝ ታምራቶች" በእርግጥ ሰጠነው፤

አላህ ታምር ብሎ "ዘጠኝ ታምራቶች" ቢያሳይም በወቅቱ ሙሳና ሃሩንን "የተረዳዱ ሁለት ድግምተኞች ናቸው” አሉ፤ ከዚህ ታምር ይልቅ "ሙሳ ሆይ አላህን በግልጽ እስከምናይልህ ድረስ ለአንተ በፍጹም አናምንልህም" አሉ፦
2:55 ሙሳ ሆይ አላህን በግልጽ እስከምናይልህ ድረስ በአንተ በፍጹም አናምንልህም ”

በወቅቱ የነበሩ ሰዎች ስለ ነብያችን፦ "ለሙሳ የተሰጠው ቢጤ አይሰጠውም ኖሯልን ” አሉ፤ አላህም፦ "ከዚህ በፊት ሙሳ በተሰጠው አልካዱምን?" በማለት ያ የተባለው ታምር ተመልሶ ቢመጣ አሁን ማስተባበላቸውን እንደማይቀር ተናግሯል።
ነጥብ ሶስት
"አስጠንቃቂ"
እነዚያም የካዱት፦ "በእርሱ ላይ ከጌታው ታምር ለምን አልተወረደለትም?" ብለው የጠየቁት ታምር የአላህ መልክተኞች የተሰጡትን ብጤ አይነት ታምር ነው፤ ይህንን ታምር ነብያችን በራሳቸው ማምጣት አይችሉም፤ እርሳቸው አስጠንቃቂ እንጂ በፍላጎታቸው ታምር እውራጅ አይደሉም፤ ታምር አውራጅ አላህ ነው፤ ስለሆነም ቁርአን በእርሳቸው ላይ ታምር አድርጎ አውርዷል፦
13:7 እነዚያም የካዱት፦ "በእርሱ ላይ ከጌታው ታምር ለምን አልተወረደለትም?" ይላሉ፤ አንተ "አስጠንቃቂ" ብቻ ነህ ለሕዝብም ሁሉ መሪ አላቸው።
10:20 በእርሱ ላይም ከጌታው የሆነች ታምር ለምን አትወረድለትም ይላሉ፡፡ «ሩቅ ነገርም ሁሉ የአላህ ብቻ ነው፡፡ ተጠባበቁም፤ እኔ ከናንተ ጋር ከሚጠባበቁት ነኝና» በላቸው፡፡
6:37 «ከጌታውም በእርሱ ላይ ለምን ተዓምር አልተወረደም» አሉ፡፡ «አላህ ተአምርን በማውረድ ላይ ቻይ ነው» በላቸው፡፡

በእርግጥም አንድ መልእክተኛ ሲመጣ አላህ በፈቃዱ ከሚሰጠው ታምር በራሱ ሊያመጣ አይችል፦
13:38 ለማንኛውም *መልክተኛ በአላህ ፈቃድ እንጂ፥ ታምር ሊያመጣ አይገባውም*፤
40:78 ለማንኛውም *መልክተኛ በአላህ ፈቃድ ካልሆነ ታምርን ሊያመጣ አይገባውም*።

መደምደሚያ
በኢየሱስ ዘመንም ኢየሱስ ብዙ ታምር እያደረገ በዘመኑ የነበሩ ሰዎች የሚጠይቁት ታምር ግን ከሰማይ ነው፤ ኢየሱስም እነርሱን የጠየቁትን ታምር ከመፈፀም ይልቅ "ለዚህ ትውልድ *"ምልክት አይሰጠውም"* ብሎ መለሰ፦
ማርቆስ 8፥11-12 ፈሪሳውያንም ወጡና ሊፈትኑት *"ከሰማይ ምልክት"* ከእርሱ ፈልገው ከእርሱ ጋር ይከራከሩ ጀመር። በመንፈሱም እጅግ ቃተተና፦ ይህ ትውልድ ስለ ምን *"ምልክት"* ይፈልጋል? እውነት እላችኋለሁ፥ ለዚህ ትውልድ *"ምልክት አይሰጠውም"* አለ።
ማቴዎስ 16:4 ክፉና አመንዝራ ትውልድ *"ምልክት"* ይሻል፥ ከነቢዩም ከዮናስ ምልክት በቀር *"ምልክት አይሰጠውም"*። *ትቶአቸውም ሄደ*።

ኢየሱስ፦ "ለዚህ ትውልድ ምልክት አይሰጠውም" ማለቱ ሰዎች የፈለጉት ከሰማይ ምልክት አላደርግም ማለት እንጂ ምልክት አለማድረግን አያሳይም፣ እነርሱ የፈለጉት ምልክት ከሰማይ ምልክት ነው፣ ነገር ግን ኢየሱስ እነርሱ ከጠየቁት ታምር በተቃራኒው ያደረገውን ታምር በፊታቸው ምንም ቢያደርግ በእርሱ አላመኑም፦
ዮሐንስ 12፥37-38 ነገር ግን ይህን ያህል *"ምልክት በፊታቸው ምንም ቢያደርግ"* ነቢዩ ኢሳይያስ፦ ጌታ ሆይ፥ ማን ምስክርነታችንን አመነ? የእግዚአብሔርስ ክንድ ለማን ተገለጠ? ብሎ የተናገረው ቃል ይፈጸም ዘንድ *"በእርሱ አላመኑም"*።

በተመሳሳይም በነቢያችን ዘመን የነበሩት ሰዎች ታምር ብለው የሚሉትና አላህ ታምር የሚለው ሁለት ለየቅል ነው፣ የቁርአንን ታላቅ ታምርነት በወቅቱ የነበሩት ሰዎች እነርሱ በሚፈልጉት መልኩ ባይመጣም ለሰው የሚበጅ ታምር ማምጣት የሚችለው አላህ ብቻ ነው፤ ከላይ የቀረበውን ነጥብ በኢየሱስ ታምር ማሳያነት በቀላሉ መረዳት ይቻላል።

ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom

ወሠላሙ ዐለይኩም
ፊዳከ አቢ ወኡሚ ያ ረሱሉሏህ!

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ፥ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

94፥4 *መወሳትህንም ለአንተ ከፍ አድርገንልሃል*፡፡ وَرَفَعْنَا لَكَ ذِكْرَكَ

አምላካች አላህ እኛ አማንያን ነቢያችንን"ﷺ" በሸሃደተይን፣ በዒቃም፣ በአዛን፣ በተሸሁድ ጊዜ እና ስማቸው ሲጠራ ሶለዋት በማውረድ እንደናወሳቸው አድርጓል፦
94፥4 *መወሳትህንም ለአንተ ከፍ አድርገንልሃል*፡፡ وَرَفَعْنَا لَكَ ذِكْرَكَ

በተጨማሪም መወሳትን ከፍ ለማድረግ "ፊዳከ አቢ ወኡሚ ያ ረሱሉሏህ" فِدَاكَ أَبِي وَأُمِّي يَا رَسُولَ اللَّه ማለትም "አባቴ እና እናቴ ለእርሶ ቤዛ ይሁንልዎ" እንላለን። እዚህ መወሳት ላይ ሚሽነሪዎች ረብጣ በሆነ ዕውቀት እጦት ሁለት ዐበይት ጥያቄ ያነሳሉ። አንዱ "መስዋዕት ለዛውም ሰው የሆኑ አባት እና እናት መስዋዕት እንዴት ለፍጡር ይቀርባል? ሲሆን ሁለተኛው "አንድ ማንነት በሌለበት በሁለተኛ መደብ "ሆይ" በማለት ማናገር ዱዓእ አይደለምን? በማለት ይጠይቃሉ። እነዚህ ጥያቄዎች በሰላና በሰከነ አእምሮ ለመመለስ ሁለት የሙግት ነጥቦችን እንመልከት፦

ነጥብ አንድ
"ቤዛ"
"ፊዳእ" فِدَاء የሚለው ቃል "ፈዳ" فَدَى ማለትም "ቤዘወ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "ቤዛ" "ዋቢ" "ዋስ" "ተያዥ" ማለት ነው። እኛ ነቢያችንን"ﷺ" "ፊዳከ አቢ ወኡሚ" የምንልበት እሳቸውን ዋቢ ለማድረግ እንጂ ለእርሳቸው መስዋዕት ማቅረባችንን በፍጹም አያሳይም። ምክንያቱም እራሳቸውን ነቢያችን"ﷺ" ባልደረባቸውን "ፊዳከ አቢ ወኡሚ" ብለውታል፦
ሡነን ኢብኑ ማጃህ መጽሐፍ 1, ሐዲስ 1
ዐሊይ እንደተረከው፡- "የአላህ መልእክተኛ"ﷺ" ወላጆቹን በመሰብሰብ ለሰዕድ ኢብኑ ማሊክ እንዳሉት ለማንም ሲሉ አልሰማኋቸውም፥ እኔ የኡሑድ ዘመቻ ቀን እንዲህ ሲሉ ሰማኋቸው፡፦ "ሰዕድ ሆይ! በጠላት ላይ በትርህን ወርውር! *"አባቴ እና እናቴ ቤዛ ይሁኑልክ"*። عَنْ عَلِيٍّ، قَالَ مَا رَأَيْتُ رَسُولَ اللَّهِ ـ صلى الله عليه وسلم ـ جَمَعَ أَبَوَيْهِ لأَحَدٍ غَيْرِ سَعْدِ بْنِ مَالِكٍ فَإِنَّهُ قَالَ لَهُ يَوْمَ أُحُدٍ ‏ "‏ ارْمِ سَعْدُ فِدَاكَ أَبِي وَأُمِّي ‏

እዚህ ሐዲስ ላይ "ቤዛ" የሚለውን "መስዋዕት" በሚል ብቻ ብንረዳው ነቢያችን"ﷺ" ለሰዕድ ኢብኑ ማሊክ መስዋዕት ያቀርቡ ነበር ይባል ነበር፥ ቅሉ ግን እንደዛ አይደለም። ምክንያቱም የሰው መስዋዕት አይደለም ለሰው ለአምላክ አይቀርብም። ሲቀጥል የነቢያችን"ﷺ" አባት እና እናት በሕይወት የሉም ፥ የሌሉትን "ቤዛ ይሁኑልክ" ማለት "ዋቢ ይሁኑልክ" "ዋስ ይሁኑልክ" ማለት እንጂ "የእርድ መስዋዕት ይሁኑልክ" ማለት በፍጹም አይደለም። ይህ ፍቅርን የሚገልጹበት ዘይቤአዊ አንጋገር ነው። ሢሰልስ “መስዋዕት” የሚለው ቃል “ኑሡክ” نُسُك ሲሆን ለአላህ ብቻ የሚቀርብ "እርድ" ነው፦
22፥34 *ለሕዝብም ሁሉ ወደ አላህ መስዋዕት ማቅረብን ደነገግን*፡፡ ከቤት እንስሳት በሰጣቸው ሲሳይ ላይ የአላህን ስም ብቻ ያወሱ ዘንድ አዘዝናቸው፡፡ وَلِكُلِّ أُمَّةٍ جَعَلْنَا مَنسَكًا لِّيَذْكُرُوا اسْمَ اللَّهِ عَلَىٰ مَا رَزَقَهُم مِّن بَهِيمَةِ الْأَنْعَامِ
6፥162 *«ስግደቴ፣ መስዋዕቴም፣ ሕይወቴም፣ ሞቴም ለዓለማት ጌታ ለአላህ ነው»* በል፡፡ قُلْ إِنَّ صَلَاتِي وَنُسُكِي وَمَحْيَايَ وَمَمَاتِي لِلَّهِ رَبِّ الْعَالَمِينَ

“ሀድይ” هَدْي ማለት “የእርድ እንስሳ” ሲሆን ጊደር፣ በግ፣ ፍየል፣ ጥጃ፣ ግመል ነው፥ ይህ ለአላህ የሚቀርበው መስዋዕት “ቁርባን” ይባላል። “ቁርባን” قُرْبَان የሚለው ቃል “ቀረበ” قَرَّبَ ማለትም “ቀረበ” ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን “መቃረቢያ” “አምኃ” “እጅ መንሻ” ማለት ነው።
"ቤዛ" ማለት የግድ "መስዋዕት" ማለት ብቻ ነው ብሎ መተርጎም ክፉኛ ስህተት ነው፥ "ቤዛ" በሚለው ቃል ዙሪያ የቋንቋ ምሁራን "ዋቢ" "ዋስ" "ተያዥ" ማለት ነው ብለው አስቀምጠዋል። የተለያዩ ሙዳየ-ቃላት ይመልከቱ፦
1. አለቃ ኪዳነ ወልደ ክፍሌ 1948 ድኅረ-ልደት ገጽ 266.
2. ከሣቴ ብርሃን ተሰማ 1951 ድኅረ-ልደት ገጽ 532.

ይህንን ሙግት ወደ ባይብል በማነጻጸር ስንመለከት "ቤዛ" ማለት የግድ "መስዋዕት" ማለት ከሆነ ሀብት ለሰው ነፍስ መስዋዕት ነው ማለት ነው፦
ምሳሌ13፥8 *ለሰው ነፍስ ቤዛው ሀብቱ ነው*፤ ድሀ ግን ተግሣጽን አይሰማም።

ሀብት ለሰው ነፍስ ዋስትና ነው ማለት እንጂ ልክ እንደ በግ፣ በሬ፣ ፍየል ለፈጣሪ የሚቀርብ እርድ ነው ማለት እንዳልሆነ እሙን ነው፦
ምሳሌ 21፥18 *ኀጥእ የጻድቅ ቤዛ ነው፥ በደለኛም የቅን ሰው ቤዛ ነው*።
ኢሳይያስ 43፥3 *ግብጽን ለአንተ ቤዛ አድርጌ፥ ኢትዮጵያንና ሳባንም ለአንተ ፋንታ ሰጥቻለሁ*።

"ኀጥእ የጻድቅ ቤዛ ነው፣ በደለኛ የቅን ሰው ቤዛ ነው፣ ግብጽን ለእስራኤል ቤዛ ነው" ማለት "ኀጥእ የጻድቅ መስዋዕት ነው፣ በደለኛ የቅን ሰው መስዋዕት ነው፣ ግብጽ ለእስራኤል መስዋዕት ነው" ማለት እንደልሆነ ቅቡል ነው፦
የሐዋርያት ሥራ7፥35 በመልአኩ እጅ እግዚአብሔር ሹምና *ቤዛ አድርጎ ላከው*።

"ሙሴ ለእስራኤል ቤዛ ነው" ማለት "ሙሴ ለእስራኤል መስዋዕት ነው" ማለት አይደለም። እኛ ነቢያችንን"ﷺ" "ፊዳከ አቢ ወኡሚ" ማለታችን በዚህ ስሌትና ቀመር ተረዱት። ይህንን የሙግት ዚቅ በስሜት ሳይሆን በስሌት፥ በሙቀት ሳይሆን በዕውቀት ለመረዳት ሞክሩ።