ዘምዘም ማለትም መካ የሚገኘው ምንጭ በቃዴስ እና በባሬድ መካከል ሲሆን እዚህ ቦታ አብርሃም ምን እንዳደረገ ባይብል አይናገርም፦
ዘፍጥረት 16፥7 የእግዚአብሔር መልአክም በውኃ ምንጭ አጠገብ በበረሀ አገኛት፤ *ምንጩም ወደ ሱር በምትወስደው መንገድ አጠገብ ነው*።
ዘፍጥረት 16፥14 ስለዚህም *የዚያ ጕድጓድ ስም ብኤርለሃይሮኢ* ተብሎ ተጠራ፤ እርሱም *በቃዴስ እና በባሬድ* መካከል ነው።
በቃዴስ እና በሱር መካከል ያለው ቦታ ሲና፣ ሴይር፣ ፋራን፣ ሳባ ወዘተ ናቸው፤ የሳባ ንግሥት የሰሎሞንን ጥበብ ለመስማት ከደቡብ መጥታለች፤ “ንግሥተ ዓዜብ” ማለት “የአዜብ ንግሥት” ወይም “የደቡብ ንግሥት” ማለት ነው፦
ማቴዎስ 12፥42 *ንግሥተ ዓዜብ* በፍርድ ቀን ከዚህ ትውልድ ጋር ተነሥታ ትፈርድበታለች፤ *የሰሎሞንን ጥበብ ለመስማት ከምድር ዳር መጥታለችና*፥
ታዲያ ከእስራኤል በስተ ደቡብ ያለችዋ ሳባ የምትባለው አገር ማን ናት? ባይብል በቃዴስ እና በሱር መካከል ያለው ቦታ ካለን የታሪክ ምሁራን ደግሞ ሳባ ደቡባዊ የዐረብ ክፍል የሆነችው የመን ስለመሆኗ ቁልጭ አርገው በወርቃማ ብዕራቸው አስፍረዋል፤ ይህቺን የሳባ ንግሥት የመኖች “ቢልቂሥ” بلقيس ይሏታል፤ የእኛ አገር ሰዎች “ማክዳ” ይሏታል፤ ግራም ነፈሰ ቀኝ የባይብል፣ የግብጽ፣ የየመን፣ የአይሁድ ሆነ የዓለም ታሪክ ላይ ይህቺ ንግሥት የየመን ንግሥት እንደነበረች ያትታል፤ የኢትዮጵያ ንግሥት ነበረች የሚለው ዲቃላ ትረካ ሁሌም ሁሉ የእኔ በምትለው በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ በተቀነባበረው በክብረ ነገሥት ላይ የተቀመጠ ትረካ ነው፤ ክብረ ነገሥት እንደ ጎርጎሮሳውያን አቆጣጠር 1225 AD ላይ በንቡረ እድ ይስሐቅ የተቀነባበረ ታሪክ ነው።
እንደ ጎርጎሮሳውያን አቆጣጠር 1270 AD ላይ የሰለሞን ስርወ-መንግሥት ተብሎ የሚጠራውን የመሰረተው ይኩኖ አምላክ ከ 900-1270 AD ላሊበላ ላይ ማእከል ያደረገውን የዛጉዌ ስርወ-መንግሥት ከገረሰሰ በኃላ ነው፤ ይኩኖ አምላክ በተክለ ሃይማኖት ትምህርት በማደጉ በዚህ ጊዜ ነው ንግሥት ሳባ የኢትዮጵያ ንግሥት ሆና ከንጉሥ ሰለሞን ጋር ተራክቦ አርጋ ቀዳማይ ሚኒሊክ የሚባል ልጅ ወልዳ እስከ 1974 AD ሀይለ ሥላሴ ድረስ ያሉት ነገሥታት “ንጉሠ ነገሥት” ማለትም “የነገሥታት ንጉሥ” እየተባሉ ከእነዚህ የነገሥታት ንጉሥ “ሞዓ አንበሳ ዘእምነገደ- ይሁዳ” ማለትም “ከይሁዳ ነገድ የሚሆነው አንበሳ” ይመጣል ተብሎ ይጠበቅ ነበር፦
ዘፍጥረት 49፥9-10 ይሁዳ የአንበሳ ደቦል ነው፤ ልጄ ሆይ፥ ከአደንህ ወጣህ፤ እንደ አንበሳ አሸመቀ፥ እንደ ሴት አንበሳም አደባ፤ ያስነሣውስ ዘንድ ማን ይችላል? በትረ መንግሥት ከይሁዳ አይጠፋም፥ የገዥም ዘንግ ከእግሮቹ መካከል፥ ገዥ የሆነው እስኪመጣ ድረስ፤ የአሕዛብ መታዘዝም ለእርሱ ይሆናል።
“ከይሁዳ ነገድ የሚሆነው አንበሳ” ግን መሲሑ እንደሆነ ቅቡል ቢሆንም ቅሉ ግን ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ “ሥዩመ እግዚአብሔር እና ንጉሠ ነገሥት” ሆነው ተሹመዋል፦
ራእይ 5፥5 ከሽማግሌዎቹም አንዱ፦ አታልቅስ፤ እነሆ፥ *ከይሁዳ ነገድ የሆነው አንበሳ* እርሱም የዳዊት ሥር መጽሐፉን ይዘረጋ ዘንድ ሰባቱንም ማኅተም ይፈታ ዘንድ ድል ነሥቶአል፡ አለኝ።
ከይሁዳ ነገድ የሆነው አንበሳ መሲሑ ኢየሱስ ሆኖ ሳለ ግን ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ “ሥዩመ እግዚአብሔር”፣ “ንጉሠ ነገሥት” እና “ከይሁዳ ነገድ የሚሆነው አንበሳ” ለምን ማለትስ አስፈለገ? ዛሬ ለራስተፈሪያን እምነት መመስረት ተጠያቂዎቹ የክብረ ነገስት ጸሐፊ፣ ይኩኖ አምላክ እና ተክለ ሃይማኖት ናቸው።
ዘፍጥረት 16፥7 የእግዚአብሔር መልአክም በውኃ ምንጭ አጠገብ በበረሀ አገኛት፤ *ምንጩም ወደ ሱር በምትወስደው መንገድ አጠገብ ነው*።
ዘፍጥረት 16፥14 ስለዚህም *የዚያ ጕድጓድ ስም ብኤርለሃይሮኢ* ተብሎ ተጠራ፤ እርሱም *በቃዴስ እና በባሬድ* መካከል ነው።
በቃዴስ እና በሱር መካከል ያለው ቦታ ሲና፣ ሴይር፣ ፋራን፣ ሳባ ወዘተ ናቸው፤ የሳባ ንግሥት የሰሎሞንን ጥበብ ለመስማት ከደቡብ መጥታለች፤ “ንግሥተ ዓዜብ” ማለት “የአዜብ ንግሥት” ወይም “የደቡብ ንግሥት” ማለት ነው፦
ማቴዎስ 12፥42 *ንግሥተ ዓዜብ* በፍርድ ቀን ከዚህ ትውልድ ጋር ተነሥታ ትፈርድበታለች፤ *የሰሎሞንን ጥበብ ለመስማት ከምድር ዳር መጥታለችና*፥
ታዲያ ከእስራኤል በስተ ደቡብ ያለችዋ ሳባ የምትባለው አገር ማን ናት? ባይብል በቃዴስ እና በሱር መካከል ያለው ቦታ ካለን የታሪክ ምሁራን ደግሞ ሳባ ደቡባዊ የዐረብ ክፍል የሆነችው የመን ስለመሆኗ ቁልጭ አርገው በወርቃማ ብዕራቸው አስፍረዋል፤ ይህቺን የሳባ ንግሥት የመኖች “ቢልቂሥ” بلقيس ይሏታል፤ የእኛ አገር ሰዎች “ማክዳ” ይሏታል፤ ግራም ነፈሰ ቀኝ የባይብል፣ የግብጽ፣ የየመን፣ የአይሁድ ሆነ የዓለም ታሪክ ላይ ይህቺ ንግሥት የየመን ንግሥት እንደነበረች ያትታል፤ የኢትዮጵያ ንግሥት ነበረች የሚለው ዲቃላ ትረካ ሁሌም ሁሉ የእኔ በምትለው በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ በተቀነባበረው በክብረ ነገሥት ላይ የተቀመጠ ትረካ ነው፤ ክብረ ነገሥት እንደ ጎርጎሮሳውያን አቆጣጠር 1225 AD ላይ በንቡረ እድ ይስሐቅ የተቀነባበረ ታሪክ ነው።
እንደ ጎርጎሮሳውያን አቆጣጠር 1270 AD ላይ የሰለሞን ስርወ-መንግሥት ተብሎ የሚጠራውን የመሰረተው ይኩኖ አምላክ ከ 900-1270 AD ላሊበላ ላይ ማእከል ያደረገውን የዛጉዌ ስርወ-መንግሥት ከገረሰሰ በኃላ ነው፤ ይኩኖ አምላክ በተክለ ሃይማኖት ትምህርት በማደጉ በዚህ ጊዜ ነው ንግሥት ሳባ የኢትዮጵያ ንግሥት ሆና ከንጉሥ ሰለሞን ጋር ተራክቦ አርጋ ቀዳማይ ሚኒሊክ የሚባል ልጅ ወልዳ እስከ 1974 AD ሀይለ ሥላሴ ድረስ ያሉት ነገሥታት “ንጉሠ ነገሥት” ማለትም “የነገሥታት ንጉሥ” እየተባሉ ከእነዚህ የነገሥታት ንጉሥ “ሞዓ አንበሳ ዘእምነገደ- ይሁዳ” ማለትም “ከይሁዳ ነገድ የሚሆነው አንበሳ” ይመጣል ተብሎ ይጠበቅ ነበር፦
ዘፍጥረት 49፥9-10 ይሁዳ የአንበሳ ደቦል ነው፤ ልጄ ሆይ፥ ከአደንህ ወጣህ፤ እንደ አንበሳ አሸመቀ፥ እንደ ሴት አንበሳም አደባ፤ ያስነሣውስ ዘንድ ማን ይችላል? በትረ መንግሥት ከይሁዳ አይጠፋም፥ የገዥም ዘንግ ከእግሮቹ መካከል፥ ገዥ የሆነው እስኪመጣ ድረስ፤ የአሕዛብ መታዘዝም ለእርሱ ይሆናል።
“ከይሁዳ ነገድ የሚሆነው አንበሳ” ግን መሲሑ እንደሆነ ቅቡል ቢሆንም ቅሉ ግን ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ “ሥዩመ እግዚአብሔር እና ንጉሠ ነገሥት” ሆነው ተሹመዋል፦
ራእይ 5፥5 ከሽማግሌዎቹም አንዱ፦ አታልቅስ፤ እነሆ፥ *ከይሁዳ ነገድ የሆነው አንበሳ* እርሱም የዳዊት ሥር መጽሐፉን ይዘረጋ ዘንድ ሰባቱንም ማኅተም ይፈታ ዘንድ ድል ነሥቶአል፡ አለኝ።
ከይሁዳ ነገድ የሆነው አንበሳ መሲሑ ኢየሱስ ሆኖ ሳለ ግን ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ “ሥዩመ እግዚአብሔር”፣ “ንጉሠ ነገሥት” እና “ከይሁዳ ነገድ የሚሆነው አንበሳ” ለምን ማለትስ አስፈለገ? ዛሬ ለራስተፈሪያን እምነት መመስረት ተጠያቂዎቹ የክብረ ነገስት ጸሐፊ፣ ይኩኖ አምላክ እና ተክለ ሃይማኖት ናቸው።
ቁርአን የአምላካችን የአላህ ንግግር ነው፤ ከነብያችን”ﷺ” በፊት ያለው ድርጊት “አል-ገይቡል ማዲ” الغيبه المادي ሲሆን ያለፈ ክስተት ነው፤ ይህም ድርጊቱ ከዚህ በፊት አላፊ የሆነ ነገር ነው፤ ከፍጡራን በፊት ያሉትን የሩቅ ወሬዎች አላህ ብቻ ነው በትክክል የሚያውቃቸው፤ አላህ ይህንን የሩቅ ወሬ “ነቁስሱ አለይከ” نَقُصُّ عَلَيْكَ “እንተርክልሃለን” በማለት ለነብያችን”ﷺ” ይናገራል፦
11:120 ከመልክተኞቹም “ወሬዎች” ተፈላጊውን ሁሉንም ልብህን በእርሱ የምናረካበትን “*እንተርክልሃለን*፤ በዚህችም እውነቱ ነገር ለምእምናን ግሳጼ እና ማስታወሻ መጥቶልሃል፡፡ وَكُلًّۭا نَّقُصُّ عَلَيْكَ مِنْ أَنۢبَآءِ ٱلرُّسُلِ مَا نُثَبِّتُ بِهِۦ فُؤَادَكَ ۚ وَجَآءَكَ فِى هَٰذِهِ ٱلْحَقُّ وَمَوْعِظَةٌۭ وَذِكْرَىٰ لِلْمُؤْمِنِينَ
አላህ ለነብያችን”ﷺ” የሚተርክበት ምክንያት ለምእምናን ግሳጼ እና ማስታወሻ ነው እንጂ እከሌ እከሌን ወለደ ብሎ የሚናገር የቀበሌ አሊያም የእድር መዝገብ አይደለም፤ እኛ እንድንማርበት ከተረከን አንዱ የሰበእ ማለትም የሳባ ንግሥት ታሪክ ነው፤ ይህም በሱረቱል ነምል 27፥22-44 ላይ አለ፦
27፥22 ወፉ ዕሩቅ ያልኾነንም ጊዜ ቆዬ፡፡ አለም «ያላወቅከውን ነገር አወቅኩ፡፡ *ከሰበእም እርግጠኛን ወሬ አመጣሁልህ*፡፡ فَمَكَثَ غَيْرَ بَعِيدٍۢ فَقَالَ أَحَطتُ بِمَا لَمْ تُحِطْ بِهِۦ وَجِئْتُكَ مِن سَبَإٍۭ بِنَبَإٍۢ يَقِينٍ
27፥23 «እኔ የምትገዛቸው የኾኑችን ሴት ከነገሩም ሁሉ የተሰጠችኝ አገኘሁ፡፡ ለእርሷም ታላቅ ዙፋን አልላት፡፡ إِنِّى وَجَدتُّ ٱمْرَأَةًۭ تَمْلِكُهُمْ وَأُوتِيَتْ مِن كُلِّ شَىْءٍۢ وَلَهَا عَرْشٌ عَظِيمٌۭ
አምላካችን አላህ ይህንን የተረከበት ጭብጥ የሱለይማን ተልዕኮ እርሷን ውደ ዲኑል ኢስላም መጥራት ነው፤ እርሷም፦ “ለዓለማት ጌታ ለአላህ ታዘዝኩ” በማለት መልሳለች፦
27፥30 «እርሱ ከሱለይማን ነው፡፡ እርሱም *በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩኅ በጣም አዛኝ በኾነው*፡፡ إِنَّهُۥ مِن سُلَيْمَٰنَ وَإِنَّهُۥ بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ
27፥31 «በእኔ ላይ አትኩሩ፡፡ *ታዛዦችም* ኾናችሁ ወደ እኔ ኑ የሚል ነው፡፡ أَلَّا تَعْلُوا۟ عَلَىَّ وَأْتُونِى مُسْلِمِينَ
27፥43 *ከአላህ ሌላ ታመልከውው የነበረችውንም ከለከላት፡፡ እርሷ ከከሓዲዎች ሕዝቦች ነበረችና*፡፡ وَصَدَّهَا مَا كَانَت تَّعْبُدُ مِن دُونِ ٱللَّهِ ۖ إِنَّهَا كَانَتْ مِن قَوْمٍۢ كَٰفِرِينَ
27፥44 ሕንጻውን ግቢ ተባለች፡፡ ባየቺውም ጊዜ ባሕር ነው ብላ ጠረጠረችው፡፡ ከባቶችዋም ገለጠች፡፡ «እርሱ ከመስተዋት የተለሰለሰ ሕንጻ ነው» አላት፡፡ «ጌታዬ ሆይ! እኔ ነፍሴን በደልኩ፡፡ ከሱለይማንም ጋር ሆኜ *ለዓለማት ጌታ ለአላህ ታዘዝኩ*» አለች፡፡ قِيلَ لَهَا ٱدْخُلِى ٱلصَّرْحَ ۖ فَلَمَّا رَأَتْهُ حَسِبَتْهُ لُجَّةًۭ وَكَشَفَتْ عَن سَاقَيْهَا ۚ قَالَ إِنَّهُۥ صَرْحٌۭ مُّمَرَّدٌۭ مِّن قَوَارِيرَ ۗ قَالَتْ رَبِّ إِنِّى ظَلَمْتُ نَفْسِى وَأَسْلَمْتُ مَعَ سُلَيْمَٰنَ لِلَّهِ رَبِّ ٱلْعَٰلَمِينَ
አላህ ስለ ሳቢያን ህዝቦች በረከትና ቅጣት በሱረቱል ሰበእ 34፥15-20 ነግሮናል፤ በተጨማሪም ሳቢያን በአላህ እና በመጨረሻው ቀን አምነው መልካም ከሰሩ መልካም ምንዳ እንዳላቸው እና በመጨረሻው ቀን በእነርሱ መካከል እንደሚፈርድ ተናግሯል፦
34፥15 *ለሰበእ በመኖሪያቸው በእውነት አስደናቂ ምልክት ነበራቸው*፡፡ ከግራና ከቀኝ ሁለት አትክልቶች ነበሯቸው፡፡ «ከጌታችሁ ሲሳይ ብሉ፡፡ ለእርሱም አመስግኑ፡፡ አገራችሁ ውብ አገር ናት፡፡ ጌታችሁ መሓሪ ጌታም ነው» ተባሉ፡፡ لَقَدْ كَانَ لِسَبَإٍۢ فِى مَسْكَنِهِمْ ءَايَةٌۭ ۖ جَنَّتَانِ عَن يَمِينٍۢ وَشِمَالٍۢ ۖ كُلُوا۟ مِن رِّزْقِ رَبِّكُمْ وَٱشْكُرُوا۟ لَهُۥ ۚ بَلْدَةٌۭ طَيِّبَةٌۭ وَرَبٌّ غَفُورٌۭ
2፥62 እነዚያ ያመኑ እነዚያም ይሁዳውያን የኾኑ፣ ክርስቲያኖችም፣ *ሳቢያኖችም ከእነርሱ በአላህና በመጨረሻው ቀን ያመነ መልካምንም ሥራ የሠራ ለነርሱ በጌታቸው ዘንድ ምንዳቸው አላቸው*፡፡ በነርሱም ላይ ፍርሃት የለባቸውም፤ እነሱም አያዝኑም፡፡ إِنَّ الَّذِينَ آمَنُوا وَالَّذِينَ هَادُوا وَالنَّصَارَىٰ وَالصَّابِئِينَ مَنْ آمَنَ بِاللَّهِ وَالْيَوْمِ الْآخِرِ وَعَمِلَ صَالِحًا فَلَهُمْ أَجْرُهُمْ عِندَ رَبِّهِمْ وَلَا خَوْفٌ عَلَيْهِمْ وَلَا هُمْ يَحْزَنُونَ
22፥17 እነዚያ ያመኑት፣ እነዚያም ይሁዳውያን *ሳቢያኖችም*፣ ክርስቲያኖችም፣ መጁሶችም እነዚያም ያጋሩ *አላህ በትንሣኤ ቀን በመካከላቸው በፍርድ ይለያል*፡፡ አላህ በነገሩ ሁሉ ላይ በእርግጥ ዐዋቂ ነውና፡፡ إِنَّ الَّذِينَ آمَنُوا وَالَّذِينَ هَادُوا وَالصَّابِئِينَ وَالنَّصَارَىٰ وَالْمَجُوسَ وَالَّذِينَ أَشْرَكُوا إِنَّ اللَّهَ يَفْصِلُ بَيْنَهُمْ يَوْمَ الْقِيَامَةِ ۚ إِنَّ اللَّهَ عَلَىٰ كُلِّ شَيْءٍ شَهِيدٌ
✍ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሰላሙ አለይኩም
11:120 ከመልክተኞቹም “ወሬዎች” ተፈላጊውን ሁሉንም ልብህን በእርሱ የምናረካበትን “*እንተርክልሃለን*፤ በዚህችም እውነቱ ነገር ለምእምናን ግሳጼ እና ማስታወሻ መጥቶልሃል፡፡ وَكُلًّۭا نَّقُصُّ عَلَيْكَ مِنْ أَنۢبَآءِ ٱلرُّسُلِ مَا نُثَبِّتُ بِهِۦ فُؤَادَكَ ۚ وَجَآءَكَ فِى هَٰذِهِ ٱلْحَقُّ وَمَوْعِظَةٌۭ وَذِكْرَىٰ لِلْمُؤْمِنِينَ
አላህ ለነብያችን”ﷺ” የሚተርክበት ምክንያት ለምእምናን ግሳጼ እና ማስታወሻ ነው እንጂ እከሌ እከሌን ወለደ ብሎ የሚናገር የቀበሌ አሊያም የእድር መዝገብ አይደለም፤ እኛ እንድንማርበት ከተረከን አንዱ የሰበእ ማለትም የሳባ ንግሥት ታሪክ ነው፤ ይህም በሱረቱል ነምል 27፥22-44 ላይ አለ፦
27፥22 ወፉ ዕሩቅ ያልኾነንም ጊዜ ቆዬ፡፡ አለም «ያላወቅከውን ነገር አወቅኩ፡፡ *ከሰበእም እርግጠኛን ወሬ አመጣሁልህ*፡፡ فَمَكَثَ غَيْرَ بَعِيدٍۢ فَقَالَ أَحَطتُ بِمَا لَمْ تُحِطْ بِهِۦ وَجِئْتُكَ مِن سَبَإٍۭ بِنَبَإٍۢ يَقِينٍ
27፥23 «እኔ የምትገዛቸው የኾኑችን ሴት ከነገሩም ሁሉ የተሰጠችኝ አገኘሁ፡፡ ለእርሷም ታላቅ ዙፋን አልላት፡፡ إِنِّى وَجَدتُّ ٱمْرَأَةًۭ تَمْلِكُهُمْ وَأُوتِيَتْ مِن كُلِّ شَىْءٍۢ وَلَهَا عَرْشٌ عَظِيمٌۭ
አምላካችን አላህ ይህንን የተረከበት ጭብጥ የሱለይማን ተልዕኮ እርሷን ውደ ዲኑል ኢስላም መጥራት ነው፤ እርሷም፦ “ለዓለማት ጌታ ለአላህ ታዘዝኩ” በማለት መልሳለች፦
27፥30 «እርሱ ከሱለይማን ነው፡፡ እርሱም *በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩኅ በጣም አዛኝ በኾነው*፡፡ إِنَّهُۥ مِن سُلَيْمَٰنَ وَإِنَّهُۥ بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ
27፥31 «በእኔ ላይ አትኩሩ፡፡ *ታዛዦችም* ኾናችሁ ወደ እኔ ኑ የሚል ነው፡፡ أَلَّا تَعْلُوا۟ عَلَىَّ وَأْتُونِى مُسْلِمِينَ
27፥43 *ከአላህ ሌላ ታመልከውው የነበረችውንም ከለከላት፡፡ እርሷ ከከሓዲዎች ሕዝቦች ነበረችና*፡፡ وَصَدَّهَا مَا كَانَت تَّعْبُدُ مِن دُونِ ٱللَّهِ ۖ إِنَّهَا كَانَتْ مِن قَوْمٍۢ كَٰفِرِينَ
27፥44 ሕንጻውን ግቢ ተባለች፡፡ ባየቺውም ጊዜ ባሕር ነው ብላ ጠረጠረችው፡፡ ከባቶችዋም ገለጠች፡፡ «እርሱ ከመስተዋት የተለሰለሰ ሕንጻ ነው» አላት፡፡ «ጌታዬ ሆይ! እኔ ነፍሴን በደልኩ፡፡ ከሱለይማንም ጋር ሆኜ *ለዓለማት ጌታ ለአላህ ታዘዝኩ*» አለች፡፡ قِيلَ لَهَا ٱدْخُلِى ٱلصَّرْحَ ۖ فَلَمَّا رَأَتْهُ حَسِبَتْهُ لُجَّةًۭ وَكَشَفَتْ عَن سَاقَيْهَا ۚ قَالَ إِنَّهُۥ صَرْحٌۭ مُّمَرَّدٌۭ مِّن قَوَارِيرَ ۗ قَالَتْ رَبِّ إِنِّى ظَلَمْتُ نَفْسِى وَأَسْلَمْتُ مَعَ سُلَيْمَٰنَ لِلَّهِ رَبِّ ٱلْعَٰلَمِينَ
አላህ ስለ ሳቢያን ህዝቦች በረከትና ቅጣት በሱረቱል ሰበእ 34፥15-20 ነግሮናል፤ በተጨማሪም ሳቢያን በአላህ እና በመጨረሻው ቀን አምነው መልካም ከሰሩ መልካም ምንዳ እንዳላቸው እና በመጨረሻው ቀን በእነርሱ መካከል እንደሚፈርድ ተናግሯል፦
34፥15 *ለሰበእ በመኖሪያቸው በእውነት አስደናቂ ምልክት ነበራቸው*፡፡ ከግራና ከቀኝ ሁለት አትክልቶች ነበሯቸው፡፡ «ከጌታችሁ ሲሳይ ብሉ፡፡ ለእርሱም አመስግኑ፡፡ አገራችሁ ውብ አገር ናት፡፡ ጌታችሁ መሓሪ ጌታም ነው» ተባሉ፡፡ لَقَدْ كَانَ لِسَبَإٍۢ فِى مَسْكَنِهِمْ ءَايَةٌۭ ۖ جَنَّتَانِ عَن يَمِينٍۢ وَشِمَالٍۢ ۖ كُلُوا۟ مِن رِّزْقِ رَبِّكُمْ وَٱشْكُرُوا۟ لَهُۥ ۚ بَلْدَةٌۭ طَيِّبَةٌۭ وَرَبٌّ غَفُورٌۭ
2፥62 እነዚያ ያመኑ እነዚያም ይሁዳውያን የኾኑ፣ ክርስቲያኖችም፣ *ሳቢያኖችም ከእነርሱ በአላህና በመጨረሻው ቀን ያመነ መልካምንም ሥራ የሠራ ለነርሱ በጌታቸው ዘንድ ምንዳቸው አላቸው*፡፡ በነርሱም ላይ ፍርሃት የለባቸውም፤ እነሱም አያዝኑም፡፡ إِنَّ الَّذِينَ آمَنُوا وَالَّذِينَ هَادُوا وَالنَّصَارَىٰ وَالصَّابِئِينَ مَنْ آمَنَ بِاللَّهِ وَالْيَوْمِ الْآخِرِ وَعَمِلَ صَالِحًا فَلَهُمْ أَجْرُهُمْ عِندَ رَبِّهِمْ وَلَا خَوْفٌ عَلَيْهِمْ وَلَا هُمْ يَحْزَنُونَ
22፥17 እነዚያ ያመኑት፣ እነዚያም ይሁዳውያን *ሳቢያኖችም*፣ ክርስቲያኖችም፣ መጁሶችም እነዚያም ያጋሩ *አላህ በትንሣኤ ቀን በመካከላቸው በፍርድ ይለያል*፡፡ አላህ በነገሩ ሁሉ ላይ በእርግጥ ዐዋቂ ነውና፡፡ إِنَّ الَّذِينَ آمَنُوا وَالَّذِينَ هَادُوا وَالصَّابِئِينَ وَالنَّصَارَىٰ وَالْمَجُوسَ وَالَّذِينَ أَشْرَكُوا إِنَّ اللَّهَ يَفْصِلُ بَيْنَهُمْ يَوْمَ الْقِيَامَةِ ۚ إِنَّ اللَّهَ عَلَىٰ كُلِّ شَيْءٍ شَهِيدٌ
✍ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሰላሙ አለይኩም
መስቀል
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
41፥37 ሌሊትና ቀንም ፀሐይና ጨረቃም ከምልክቶቹ ናቸው፡፡ ለፀሐይና ለጨረቃ “አትስገዱ”፡፡ ለእዚያም ለፈጠራቸው አላህ “ስገዱ” ፡፡ እርሱን ብቻ “የምታመልኩ” እንደ ኾናችሁ *”ለሌላ አትስገዱ”*፡፡
"በቅዱስ ቁርኣን" “ሡጁድ” سُّجُود የሚለው ቃል “ሠጀደ” سَجَدَ ማለት “ሰገደ” ወይም “ታዘዘ” ከሚል ግስ የተገኘ ሲሆን “ስግደት” ወይም “መታዘዝ” ማለት ነው፤ ሡጁድ ደግሞ በሁለት ይከፈላል፦ አንዱ “ሡጁዱል ዒባዳ” سُّجُود العبادة ማለትም “የአምልኮ ስግደት” ሲሆን ሌላው “ሡጁዱ አተሒያ” سُّجُود التحيه ማለትም “የአክብሮት ስግደት” ነው፤ ነገር ግን ይህ አክብሮት አቅጣጫውን ቀይሮ አምልኮ እየሆነ ስላለ ከሰላምታ ውጪ በሱጁድ ለፍጡራን ማጎብደድ፣ መተናነስ፣ ማሸርገድ ቁርአን ሲወርድ ቆሟል፤ የአክብሮት ስግደት ከአምልኮ ስግደት ጋር እንዳይደባለቅ የተከለከለው በነብያችን”ﷺ” ጊዜ ነው፤ አላህም ሁሉን ለፈጠረው ለእርሱ እንጂ ለሌላ አትስገዱ ብሎናል፤ ከአላህ ሌላ የሚገዙት ግኡዛን ነገር የገሀነም ማገዶዎች ናቸው፦
41፥37 ሌሊትና ቀንም ፀሐይና ጨረቃም ከምልክቶቹ ናቸው፡፡ ለፀሐይና ለጨረቃ “አትስገዱ”፡፡ ለእዚያም ለፈጠራቸው አላህ “ስገዱ” ፡፡ እርሱን ብቻ “የምታመልኩ” እንደ ኾናችሁ *”ለሌላ አትስገዱ”*፡፡
21፥8 እናንተ ከአላህ ሌላ የምትገዟቸውም የገሀነም ማገዶዎች ናችሁ፡፡ እናንተ ለእርሷ ወራጆች ናችሁ إِنَّكُمْ وَمَا تَعْبُدُونَ مِن دُونِ ٱللَّهِ حَصَبُ جَهَنَّمَ أَنتُمْ لَهَا وَٰرِدُونَ ፡፡
ማገዶዎች በሚለው ቃላት “ማ” َمَا የሚለው አንፃራዊ ተውላጠ-ስም አቅል የሌላቸውን ጣኦታት ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ ነው፤ አቅል ያላቸውን ማንነቶች “መን” مَّن የሚል አንፃራዊ ተውላጠ-ስም የሚጠቀመው፤ ግን እዚህ አንቀፅ ላይ “ማ” የሚል አንፃራዊ ተውላጠ-ስም መጠቀሙ አቅል የሌላቸውን ጣኦታት ፍንትው አድርጎ የሚያሳይ ነው፤ ከአላህ ውጪ የሚደረግ ባዕድ አምልኮ “ጣጉት” لطَّاغُوتِ ይባላል፤ ይህም ጣዖት በሁለት ይከፈላል፤ አንዱ “አውሳን” أَوْثَٰن ሲሆን ሁለተኛው “አስናም” أَصْنَام ነው፤ “አውሳን” ማለት ከድንጋይ ተቀርፀው አምልኮ ለሚቀርብላቸው ሲሆን፤ “አስናም” ደግሞ ከእንጨት፣ ብር፣ ነሐስ ተሰርተው አምልኮ ለሚቀርብላቸው ነው፤ እነዚህ ሁለቱም በቁርአን ተጠቅሰዋል፦
1.”አውሳን”
29:17 ከአላህ ሌላ የምታመልኩት “ጣዖታትን” أَوْثَانًا ብቻ ነው፤ ውሸትንም ትቀጣጥፋላችሁ፤ እነዚያ ከአላህ ሌላ የምታመልኩአቸው ለእናንተ ሲሳይን ሊሰጧችሁ አይችሉም፤
2. “አስናም”
6:74 ኢብራሒምም ለአባቱ ለአዘር “ጣዖታትን” أَصْنَامًا አማልክት አድርገህ ትይዛለህን እኔ አንተንም ሕዝቦችህንም በግልጽ መሳሳት ውስጥ ኾናችሁ አያችኋለሁ» ባለ ጊዜ አስታውስ።
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
41፥37 ሌሊትና ቀንም ፀሐይና ጨረቃም ከምልክቶቹ ናቸው፡፡ ለፀሐይና ለጨረቃ “አትስገዱ”፡፡ ለእዚያም ለፈጠራቸው አላህ “ስገዱ” ፡፡ እርሱን ብቻ “የምታመልኩ” እንደ ኾናችሁ *”ለሌላ አትስገዱ”*፡፡
"በቅዱስ ቁርኣን" “ሡጁድ” سُّجُود የሚለው ቃል “ሠጀደ” سَجَدَ ማለት “ሰገደ” ወይም “ታዘዘ” ከሚል ግስ የተገኘ ሲሆን “ስግደት” ወይም “መታዘዝ” ማለት ነው፤ ሡጁድ ደግሞ በሁለት ይከፈላል፦ አንዱ “ሡጁዱል ዒባዳ” سُّجُود العبادة ማለትም “የአምልኮ ስግደት” ሲሆን ሌላው “ሡጁዱ አተሒያ” سُّجُود التحيه ማለትም “የአክብሮት ስግደት” ነው፤ ነገር ግን ይህ አክብሮት አቅጣጫውን ቀይሮ አምልኮ እየሆነ ስላለ ከሰላምታ ውጪ በሱጁድ ለፍጡራን ማጎብደድ፣ መተናነስ፣ ማሸርገድ ቁርአን ሲወርድ ቆሟል፤ የአክብሮት ስግደት ከአምልኮ ስግደት ጋር እንዳይደባለቅ የተከለከለው በነብያችን”ﷺ” ጊዜ ነው፤ አላህም ሁሉን ለፈጠረው ለእርሱ እንጂ ለሌላ አትስገዱ ብሎናል፤ ከአላህ ሌላ የሚገዙት ግኡዛን ነገር የገሀነም ማገዶዎች ናቸው፦
41፥37 ሌሊትና ቀንም ፀሐይና ጨረቃም ከምልክቶቹ ናቸው፡፡ ለፀሐይና ለጨረቃ “አትስገዱ”፡፡ ለእዚያም ለፈጠራቸው አላህ “ስገዱ” ፡፡ እርሱን ብቻ “የምታመልኩ” እንደ ኾናችሁ *”ለሌላ አትስገዱ”*፡፡
21፥8 እናንተ ከአላህ ሌላ የምትገዟቸውም የገሀነም ማገዶዎች ናችሁ፡፡ እናንተ ለእርሷ ወራጆች ናችሁ إِنَّكُمْ وَمَا تَعْبُدُونَ مِن دُونِ ٱللَّهِ حَصَبُ جَهَنَّمَ أَنتُمْ لَهَا وَٰرِدُونَ ፡፡
ማገዶዎች በሚለው ቃላት “ማ” َمَا የሚለው አንፃራዊ ተውላጠ-ስም አቅል የሌላቸውን ጣኦታት ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ ነው፤ አቅል ያላቸውን ማንነቶች “መን” مَّن የሚል አንፃራዊ ተውላጠ-ስም የሚጠቀመው፤ ግን እዚህ አንቀፅ ላይ “ማ” የሚል አንፃራዊ ተውላጠ-ስም መጠቀሙ አቅል የሌላቸውን ጣኦታት ፍንትው አድርጎ የሚያሳይ ነው፤ ከአላህ ውጪ የሚደረግ ባዕድ አምልኮ “ጣጉት” لطَّاغُوتِ ይባላል፤ ይህም ጣዖት በሁለት ይከፈላል፤ አንዱ “አውሳን” أَوْثَٰن ሲሆን ሁለተኛው “አስናም” أَصْنَام ነው፤ “አውሳን” ማለት ከድንጋይ ተቀርፀው አምልኮ ለሚቀርብላቸው ሲሆን፤ “አስናም” ደግሞ ከእንጨት፣ ብር፣ ነሐስ ተሰርተው አምልኮ ለሚቀርብላቸው ነው፤ እነዚህ ሁለቱም በቁርአን ተጠቅሰዋል፦
1.”አውሳን”
29:17 ከአላህ ሌላ የምታመልኩት “ጣዖታትን” أَوْثَانًا ብቻ ነው፤ ውሸትንም ትቀጣጥፋላችሁ፤ እነዚያ ከአላህ ሌላ የምታመልኩአቸው ለእናንተ ሲሳይን ሊሰጧችሁ አይችሉም፤
2. “አስናም”
6:74 ኢብራሒምም ለአባቱ ለአዘር “ጣዖታትን” أَصْنَامًا አማልክት አድርገህ ትይዛለህን እኔ አንተንም ሕዝቦችህንም በግልጽ መሳሳት ውስጥ ኾናችሁ አያችኋለሁ» ባለ ጊዜ አስታውስ።
ወደ ባይብል ስንመጣ “ስግደት” የሚለው ቃል በዕብራይስጥ “ሻኻህ” שָׁחָה ሲሆን በግሪክ ደግሞ “ፕሩስኩኔኦ” προσκυνέω ይባላል፤ ይህም ለተለያየ ምንነት ሆነ ማንነት በኒያ”intention” የሚቀርብ አምልኮን”Adoration” ወይም አክብሮትን”prostration” ነው ለማመልከት በባይብል ተጠቅሞበታል፤ የአምልኮት ስግደት በባህርይ የአንድ አምላክ ሃቅና ገንዘብ ሲሆን የአክብሮት ስግደት ደግሞ በፀጋ ለህያዋን ማንነት ማክበርን ያመለክታል፤ ግን ለግኡዛን ነገሮች አምልኮም ይሁን ስግደት ተከልክሏል፤ በዕብራይስጥ “ኤሊል” אֱלִיל ማለት “ምስል”፣ “ቅርፅ”፣ “ጣዖት” ማለት ሲሆን በግሪክ ደግሞ “ኤዶሎን” εἴδωλον ነው፤ ትርጉሙ ተመሳሳይ ነው። የሙሴ አምላክ ለሙሴ “”ለእናንተ ጣዖት አታድርጉ፥ የተቀረጸም ምስል ወይም ሐውልት አታቁሙ፤ ትሰግዱለትም ዘንድ በምድራችሁ ላይ የተቀረጸ ድንጋይ አታኑሩ፣ የማናቸውንም ምሳሌ፥ የተቀረጸውንም ምስል ለአንተ አታድርግ፣ አትስገድላቸው፥ አታምልካቸውምም”” ብሎ ተናግሯል፤ እንደውም ለተቀረጸ ምስል የሚሰግዱ ሁሉ ይፈሩ ይላል፦
ዘሌዋውያን 26፥1 እኔ ያህዌህ አምላካችሁ ነኝና ለእናንተ *”ጣዖት አታድርጉ፥ የተቀረጸም ምስል ወይም ሐውልት አታቁሙ”*፤ ትሰግዱለትም ዘንድ በምድራችሁ ላይ የተቀረጸ ድንጋይ አታኑሩ።
ዘጸአት 20፥4 በላይ በሰማይ ካለው፥ በታችም በምድር ካለው፥ ከምድርም በታች በውኃ ካለው ነገር *”የማናቸውንም ምሳሌ፥ የተቀረጸውንም ምስል ለአንተ አታድርግ፤ አትስገድላቸው፥ አታምልካቸውምም”*፤
መዝሙር 97፥7 *”ለተቀረጸ ምስል የሚሰግዱ ሁሉ፥ በጣዖቶቻቸውም የሚመኩ ይፈሩ*”፤ መላእክቱ ሁሉ ስገዱለት።
ታዲያ ነጥብህ ምንድን ነው? ከመስቀል ጋር ምን የሚያገናኘው ነገር አለ? ትሉ ይሆናል፤ መስቀል እኮ በሃውልት ድንጋይ፣ እንጨት፣ ወርቅ፣ ብር፣ ብረት፣ ነሐስ ወዘተ ነው፤ ይህ ግኡዝ ነገር በአበይት ክርስቲያኖች ይሰገድለታል ምስጋና ይቀርበለታል፤ ይህ በተግባር ሲሆን በጽሑፍ የዘወትር ፀሎት ላይ ደግሞ እንዲህ ይነበባል፦
ግዕዙ፦
“እሰግድ “ለ”መስቀለ እግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ ዘተቀደሰ በደሙ ክቡር”
ትርጉም፦
“ዓለምን ለማዳን ሲል ኢየሱስ ክርስቶስ “ለ”ተሰቀለበት መስቀል እሰግዳለው”
ግዕዙ፦
“ስብሐት “ለ”መስቀለ እግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ በምህረቱ ይዘከረነ”
ትርጉም፦
” “ለ”ኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል ምስጋና ይገባዋል”
ምን ትፈልጋለህ? “ለ”ተቀረጸ ምስል የሚሰግዱ ሁሉ ይፈሩ እየተባለ ለምንድን ነው ለግኡዝ ነገር የፀጋ ስግደት የሚሰገድለት? ምስጋናስ የሚቅብለት የሚሰማበት ዐቅል የት አለውና ነው? መስቀል መሳለም ሆነ በመስቀል ማሳለም የትኛው ነብይና ሃዋርያ አደረገስ አድርጉስ አለ? እኔስ ኢሳይያስ የተናገረው ትንቢት ትዝ አለኝ፦
ኢሳይያስ 44፥15-19 ለሰውም ማገዶ ይሆናል፤ ከእርሱም ወስዶ ይሞቃል፥ አንድዶም እንጀራ ይጋግርበታል፤ ከእርሱም አምላክ አበጅቶ ይሰግድለታል፥ የተቀረጸውንም ምስል ሠርቶ በእርሱ ፊት ይንበረከካል። ግማሹን በእሳት ያቃጥላል፥ በዚያ በግማሹ ሥጋ ይበላል፥ ሥጋም ይጠብስበትና ይጠግባል፤ ይሞቃልና፦ እሰይ ሞቅሁ፥ እሳቱን አይቻለሁ ይላል። የቀረውንም እንጨት አምላክ አድርጎ ምስል ይቀርጽበታል፤ በፊቱም ተጐንብሶ ይሰግዳል ወደ እርሱም እየጸለየ፦ አምላኬ ነህና አድነኝ ይላል። አያውቁም፥ አያስቡም፤ እንዳያዩ ዓይኖቻቸውን፥ እንዳያስተውሉ ልቦቻቸውን ጨፍነዋል። በልቡም ማንም አያስብም፦ ግማሽዋን በእሳት አቃጥያለሁ፥ በፍምዋም ላይ እንጀራን ጋግሬአለሁ፥ ሥጋም ጠብሼ በልቻለሁ፤ የቀረውንም አስጸያፊ ነገር አደርጋለሁን? ለዛፍስ ግንድ እሰግዳለሁን? እንዲልም እውቀትና ማስተዋል የለውም።
ከአላህ በቀር የምትጠሯቸው ሊረዷችሁ አይችሉም፤ እራሳቸውንም አይረዱምና ወደ አላህ በንስሃ ተመለሱ፦
7፥197 እነዚያም ከእርሱ በቀር የምትጠሯቸው ሊረዷችሁ አይችሉም፤ እራሳቸውንም አይረዱም وَٱلَّذِينَ تَدْعُونَ مِن دُونِهِۦ لَا يَسْتَطِيعُونَ نَصْرَكُمْ وَلَآ أَنفُسَهُمْ يَنصُرُونَ ፡፡
ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሰላሙ አለይኩም
ዘሌዋውያን 26፥1 እኔ ያህዌህ አምላካችሁ ነኝና ለእናንተ *”ጣዖት አታድርጉ፥ የተቀረጸም ምስል ወይም ሐውልት አታቁሙ”*፤ ትሰግዱለትም ዘንድ በምድራችሁ ላይ የተቀረጸ ድንጋይ አታኑሩ።
ዘጸአት 20፥4 በላይ በሰማይ ካለው፥ በታችም በምድር ካለው፥ ከምድርም በታች በውኃ ካለው ነገር *”የማናቸውንም ምሳሌ፥ የተቀረጸውንም ምስል ለአንተ አታድርግ፤ አትስገድላቸው፥ አታምልካቸውምም”*፤
መዝሙር 97፥7 *”ለተቀረጸ ምስል የሚሰግዱ ሁሉ፥ በጣዖቶቻቸውም የሚመኩ ይፈሩ*”፤ መላእክቱ ሁሉ ስገዱለት።
ታዲያ ነጥብህ ምንድን ነው? ከመስቀል ጋር ምን የሚያገናኘው ነገር አለ? ትሉ ይሆናል፤ መስቀል እኮ በሃውልት ድንጋይ፣ እንጨት፣ ወርቅ፣ ብር፣ ብረት፣ ነሐስ ወዘተ ነው፤ ይህ ግኡዝ ነገር በአበይት ክርስቲያኖች ይሰገድለታል ምስጋና ይቀርበለታል፤ ይህ በተግባር ሲሆን በጽሑፍ የዘወትር ፀሎት ላይ ደግሞ እንዲህ ይነበባል፦
ግዕዙ፦
“እሰግድ “ለ”መስቀለ እግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ ዘተቀደሰ በደሙ ክቡር”
ትርጉም፦
“ዓለምን ለማዳን ሲል ኢየሱስ ክርስቶስ “ለ”ተሰቀለበት መስቀል እሰግዳለው”
ግዕዙ፦
“ስብሐት “ለ”መስቀለ እግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ በምህረቱ ይዘከረነ”
ትርጉም፦
” “ለ”ኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል ምስጋና ይገባዋል”
ምን ትፈልጋለህ? “ለ”ተቀረጸ ምስል የሚሰግዱ ሁሉ ይፈሩ እየተባለ ለምንድን ነው ለግኡዝ ነገር የፀጋ ስግደት የሚሰገድለት? ምስጋናስ የሚቅብለት የሚሰማበት ዐቅል የት አለውና ነው? መስቀል መሳለም ሆነ በመስቀል ማሳለም የትኛው ነብይና ሃዋርያ አደረገስ አድርጉስ አለ? እኔስ ኢሳይያስ የተናገረው ትንቢት ትዝ አለኝ፦
ኢሳይያስ 44፥15-19 ለሰውም ማገዶ ይሆናል፤ ከእርሱም ወስዶ ይሞቃል፥ አንድዶም እንጀራ ይጋግርበታል፤ ከእርሱም አምላክ አበጅቶ ይሰግድለታል፥ የተቀረጸውንም ምስል ሠርቶ በእርሱ ፊት ይንበረከካል። ግማሹን በእሳት ያቃጥላል፥ በዚያ በግማሹ ሥጋ ይበላል፥ ሥጋም ይጠብስበትና ይጠግባል፤ ይሞቃልና፦ እሰይ ሞቅሁ፥ እሳቱን አይቻለሁ ይላል። የቀረውንም እንጨት አምላክ አድርጎ ምስል ይቀርጽበታል፤ በፊቱም ተጐንብሶ ይሰግዳል ወደ እርሱም እየጸለየ፦ አምላኬ ነህና አድነኝ ይላል። አያውቁም፥ አያስቡም፤ እንዳያዩ ዓይኖቻቸውን፥ እንዳያስተውሉ ልቦቻቸውን ጨፍነዋል። በልቡም ማንም አያስብም፦ ግማሽዋን በእሳት አቃጥያለሁ፥ በፍምዋም ላይ እንጀራን ጋግሬአለሁ፥ ሥጋም ጠብሼ በልቻለሁ፤ የቀረውንም አስጸያፊ ነገር አደርጋለሁን? ለዛፍስ ግንድ እሰግዳለሁን? እንዲልም እውቀትና ማስተዋል የለውም።
ከአላህ በቀር የምትጠሯቸው ሊረዷችሁ አይችሉም፤ እራሳቸውንም አይረዱምና ወደ አላህ በንስሃ ተመለሱ፦
7፥197 እነዚያም ከእርሱ በቀር የምትጠሯቸው ሊረዷችሁ አይችሉም፤ እራሳቸውንም አይረዱም وَٱلَّذِينَ تَدْعُونَ مِن دُونِهِۦ لَا يَسْتَطِيعُونَ نَصْرَكُمْ وَلَآ أَنفُسَهُمْ يَنصُرُونَ ፡፡
ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሰላሙ አለይኩም
ሰላም
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
4፥86 *በሰላምታ በተከበራችሁም ጊዜ ከእርሷ ይበልጥ ባማረ “ሰላምታ” አክብሩ፤ ወይም እርሷኑ መልሷት*። وَإِذَا حُيِّيتُم بِتَحِيَّةٍ فَحَيُّوا بِأَحْسَنَ مِنْهَا أَوْ رُدُّوهَا
በቁርአን ከተገለጹት የአላህ ስሞች አንዱ "አሥ-ሠላም" السَّلَام ሲሆን ትርጉሙ የሰላም ባለቤት"the source of peace" ማለት ነው፤ ሰላም ከአላህ ዘንድ ነው፦
59፥23 እርሱ አላህ ነው፡፡ ያ ከእርሱ በቀር ሌላ አምላክ የሌለ፣ ንጉሡ ከጉድለት ሁሉ የጠራው፣ *የሰላም ባለቤቱ*፣ ጸጥታን ሰጪው፣ ባሮቹን ጠባቂው፣ አሸናፊው፣ ኀያሉ፣ ኩሩው ነው፡፡ አላህ ከሚያጋሩት ሁሉ ጠራ፡፡ هُوَ اللَّهُ الَّذِي لَا إِلَـٰهَ إِلَّا هُوَ الْمَلِكُ الْقُدُّوسُ السَّلَامُ الْمُؤْمِنُ الْمُهَيْمِنُ الْعَزِيزُ الْجَبَّارُ الْمُتَكَبِّرُ ۚ سُبْحَانَ اللَّهِ عَمَّا يُشْرِكُونَ
ሱነን ኢብኑ ማጃህ መጽሐፍ 5, ሐዲስ 977
ዓኢሻህ"ረ.ዐ." የአላህ መልእክተኛ"ﷺ" በሚያሰላምቱ ጊዜ፦ *"አላህ ሆይ! አንተ የሰላም ባለቤት ነህ፤ ሰላም ከአንተ ዘንድ ነው፤ የግርማ እና የክብር ባለቤት ሆይ! ብሩክ ነህ" በማለት እንጂ አይቀመጡ ነበር*። عَنْ عَائِشَةَ، قَالَتْ كَانَ رَسُولُ اللَّهِ ـ صلى الله عليه وسلم ـ إِذَا سَلَّمَ لَمْ يَقْعُدْ إِلاَّ مِقْدَارَ مَا يَقُولُ " اللَّهُمَّ أَنْتَ السَّلاَمُ وَمِنْكَ السَّلاَمُ تَبَارَكْتَ يَا ذَا الْجَلاَلِ وَالإِكْرَامِ
"ሠላም" سَلَٰم የሚለው ቃል "ሠለመ" سَلَّمَ ማለትም "ሰላምታ ሰጠ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "ሰላም" ማለት ነው፤ የአላህን ሰላም አንዱ አማኝ በሌላው አማኝ ላይ እንዲሆን መመኘት የሙስሊም ሰላምታ ነው፤ "ተሥሊም" تَسْلِيم ማለት "ሰላምታ" ማለት ነው፦
4፥61 *ቤቶችንም በገባችሁ ጊዜ፤ ከአላህ ዘንድ የኾነችን የተባረከች መልካም ሰላምታ በነፍሶቻችሁ ላይ ሰላም በሉ*፡፡ فَإِذَا دَخَلْتُم بُيُوتًا فَسَلِّمُوا عَلَىٰ أَنفُسِكُمْ تَحِيَّةً مِّنْ عِندِ اللَّهِ مُبَارَكَةً طَيِّبَة
ሠሊሙ" سَلِّمُوا ማለት "ሰላም በሉ" ማለት ሲሆን ትእዛዛዊ ግስ ነው፤ ይህም ሰላምታ "አሠላሙ አለይኩም" السَّلَامُ عَلَيْكُم ነው፤ ትርጉሙ "የአላህ ሰላም በእናንተ ላይ ይሁን" ማለት ነው።
አንድ ሙስሊም መጥቶ "አሠላሙ አለይኩም" ቢለን፥ እርሱ ካለን ይበልጥ ባማረ መልኩ "ወአለይኩም አሥ-ሠላም፣ ወራሕመቱላሂ ወበረካቱህ" السَّلاَمُ عَلَيْكُمْ وَرَحْمَةُ اللهِ وَبَرَكَاتُهُ ማለትም "የአላህ ሰላም፣ ምህረት፣ በረከት በእናንተ ላይ ይሁን" ብለን እንመልሳለን፤ ወይንም እራሷኑ "ወአለይኩም አሥ-ሠላም" وَعَلَيْكُم السَّلَام ብለን እንመልሳለን፦
4፥86 *በሰላምታ በተከበራችሁም ጊዜ ከእርሷ ይበልጥ ባማረ “ሰላምታ” አክብሩ፤ ወይም እርሷኑ መልሷት*። وَإِذَا حُيِّيتُم بِتَحِيَّةٍ فَحَيُّوا بِأَحْسَنَ مِنْهَا أَوْ رُدُّوهَا
"በሰላምታ በተከበራችሁም ጊዜ" የሚለው ሃይለ-ቃል ይሰመርበት፤ አንድ ሙሥሊም ሙሥሊም ያልሆነን ሰው አሠላሙ አለይኩም አይልም፤ ምክንያቱም ይህ የሙስሊም ሰላምታ ነውና፤ ከዛ ይልቅ እንደ አገሩ ባህል "ጤና ይስጥልኝ" "ሰላም" "እንደምን ዋልክ" ወዘተ.. ማለት ይችላል፤ ነገር ግን ሙስሊም ያልሆነ ሰው አሠላሙ አለይኩም ካለን አላህ፦ "እርሷኑ መልሷት" ስላለ "ወአለይኩም" وَعَلَيْكُمْ ብለን እንመልሳለን፦
አል-አደበል ሙፍረድ መጽሐፍ 44, ሐዲስ 2
አቢ በስረል ጊፋሪይ እንደተረከው፦ "ነብዩም"ﷺ" አሉ፦ *"ነገ ወደ አንድ አይሁድ እጓዛለው፤ በመጀመሪያ ሰላም(አሠላሙ አለይኩም) አትበሏቸው፤ አሠላም አለይኩም ቢሏችሁ ግን ወአለይኩም በሉ*። عَنْ أَبِي بَصْرَةَ الْغِفَارِيِّ، عَنِ النَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم قَالَ: إِنِّي رَاكِبٌ غَدًا إِلَى يَهُودَ، فَلاَ تَبْدَأُوهُمْ بِالسَّلاَمِ، فَإِذَا سَلَّمُوا عَلَيْكُمْ فَقُولُوا: وَعَلَيْكُمْ.
አል-አደበል ሙፍረድ መጽሐፍ 44, ሐዲስ 3
አቢ ሁረይራህ እንደተረከው፦ "ነብዩም"ﷺ" አሉ፦ *"የመጽሐፉ ሰዎችን ቅድሚያ ሰላም(አሠላሙ አለይኩም) አትበሏቸው*። عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ، عَنِ النَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم قَالَ: أَهْلُ الْكِتَابِ لاَ تَبْدَأُوهُمْ بِالسَّلاَمِ
ሱነን ኢብኑ ማጃህ መጽሐፍ 33, ሐዲስ 41
ዐነሥ ኢብኑ ማሊክ እንደተረከው፦ "የአላህ መልእክተኛም"ﷺ" አሉ፦ *"ማንም ከመጽሐፉ ሰዎች ሠላም(አሠላሙ አለይኩም) ብሎ ሰላምታ ከሳጣችሁ፥ "ወአለይኩም" በሉ*። عَنْ أَنَسِ بْنِ مَالِكٍ، قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ ـ صلى الله عليه وسلم ـ " إِذَا سَلَّمَ عَلَيْكُمْ أَحَدٌ مِنْ أَهْلِ الْكِتَابِ فَقُولُوا وَعَلَيْكُمْ.
የአላህ ሰላም የሚገኘው አላህን በኢኽላስ በመታዘዝ ብቻ ነው፤ "ኢሥላም" إِسْلَٰم የሚለው ቃል "አሥለመ" أَسْلَمَ ማለትም "ታዘዘ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "መታዘዝ" ማለት ነው። “ሠለም” سَلَم ማለት ደግሞ “ታዛዥነት” ማለት ነው።
"ሙሥሊም" مُسْلِم ማለት "ታዛዥ" ማለት ነው፤ አንድ ሙስሊም አላህን በፍጹም ሲታዘዝ የአላህ ሰላም ከእርሱ ጋር ይሆናል፤ ያኔ ውስጡ "ሠሊም" سَلِيم ማለትም "ንፁህ" ይሆናል፤ እርሱም "ሠሊሙን" سَٰلِمُون ማለትም "ሰላማዊ" ይሆናል። አምላካችን አላህ እርሱን በመታዘዝ የውስጥ ሰላም ከሚያገኙት ሰላማውያን ያድርገን! አሚን።
✍ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሰላሙ አለይኩም
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
4፥86 *በሰላምታ በተከበራችሁም ጊዜ ከእርሷ ይበልጥ ባማረ “ሰላምታ” አክብሩ፤ ወይም እርሷኑ መልሷት*። وَإِذَا حُيِّيتُم بِتَحِيَّةٍ فَحَيُّوا بِأَحْسَنَ مِنْهَا أَوْ رُدُّوهَا
በቁርአን ከተገለጹት የአላህ ስሞች አንዱ "አሥ-ሠላም" السَّلَام ሲሆን ትርጉሙ የሰላም ባለቤት"the source of peace" ማለት ነው፤ ሰላም ከአላህ ዘንድ ነው፦
59፥23 እርሱ አላህ ነው፡፡ ያ ከእርሱ በቀር ሌላ አምላክ የሌለ፣ ንጉሡ ከጉድለት ሁሉ የጠራው፣ *የሰላም ባለቤቱ*፣ ጸጥታን ሰጪው፣ ባሮቹን ጠባቂው፣ አሸናፊው፣ ኀያሉ፣ ኩሩው ነው፡፡ አላህ ከሚያጋሩት ሁሉ ጠራ፡፡ هُوَ اللَّهُ الَّذِي لَا إِلَـٰهَ إِلَّا هُوَ الْمَلِكُ الْقُدُّوسُ السَّلَامُ الْمُؤْمِنُ الْمُهَيْمِنُ الْعَزِيزُ الْجَبَّارُ الْمُتَكَبِّرُ ۚ سُبْحَانَ اللَّهِ عَمَّا يُشْرِكُونَ
ሱነን ኢብኑ ማጃህ መጽሐፍ 5, ሐዲስ 977
ዓኢሻህ"ረ.ዐ." የአላህ መልእክተኛ"ﷺ" በሚያሰላምቱ ጊዜ፦ *"አላህ ሆይ! አንተ የሰላም ባለቤት ነህ፤ ሰላም ከአንተ ዘንድ ነው፤ የግርማ እና የክብር ባለቤት ሆይ! ብሩክ ነህ" በማለት እንጂ አይቀመጡ ነበር*። عَنْ عَائِشَةَ، قَالَتْ كَانَ رَسُولُ اللَّهِ ـ صلى الله عليه وسلم ـ إِذَا سَلَّمَ لَمْ يَقْعُدْ إِلاَّ مِقْدَارَ مَا يَقُولُ " اللَّهُمَّ أَنْتَ السَّلاَمُ وَمِنْكَ السَّلاَمُ تَبَارَكْتَ يَا ذَا الْجَلاَلِ وَالإِكْرَامِ
"ሠላም" سَلَٰم የሚለው ቃል "ሠለመ" سَلَّمَ ማለትም "ሰላምታ ሰጠ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "ሰላም" ማለት ነው፤ የአላህን ሰላም አንዱ አማኝ በሌላው አማኝ ላይ እንዲሆን መመኘት የሙስሊም ሰላምታ ነው፤ "ተሥሊም" تَسْلِيم ማለት "ሰላምታ" ማለት ነው፦
4፥61 *ቤቶችንም በገባችሁ ጊዜ፤ ከአላህ ዘንድ የኾነችን የተባረከች መልካም ሰላምታ በነፍሶቻችሁ ላይ ሰላም በሉ*፡፡ فَإِذَا دَخَلْتُم بُيُوتًا فَسَلِّمُوا عَلَىٰ أَنفُسِكُمْ تَحِيَّةً مِّنْ عِندِ اللَّهِ مُبَارَكَةً طَيِّبَة
ሠሊሙ" سَلِّمُوا ማለት "ሰላም በሉ" ማለት ሲሆን ትእዛዛዊ ግስ ነው፤ ይህም ሰላምታ "አሠላሙ አለይኩም" السَّلَامُ عَلَيْكُم ነው፤ ትርጉሙ "የአላህ ሰላም በእናንተ ላይ ይሁን" ማለት ነው።
አንድ ሙስሊም መጥቶ "አሠላሙ አለይኩም" ቢለን፥ እርሱ ካለን ይበልጥ ባማረ መልኩ "ወአለይኩም አሥ-ሠላም፣ ወራሕመቱላሂ ወበረካቱህ" السَّلاَمُ عَلَيْكُمْ وَرَحْمَةُ اللهِ وَبَرَكَاتُهُ ማለትም "የአላህ ሰላም፣ ምህረት፣ በረከት በእናንተ ላይ ይሁን" ብለን እንመልሳለን፤ ወይንም እራሷኑ "ወአለይኩም አሥ-ሠላም" وَعَلَيْكُم السَّلَام ብለን እንመልሳለን፦
4፥86 *በሰላምታ በተከበራችሁም ጊዜ ከእርሷ ይበልጥ ባማረ “ሰላምታ” አክብሩ፤ ወይም እርሷኑ መልሷት*። وَإِذَا حُيِّيتُم بِتَحِيَّةٍ فَحَيُّوا بِأَحْسَنَ مِنْهَا أَوْ رُدُّوهَا
"በሰላምታ በተከበራችሁም ጊዜ" የሚለው ሃይለ-ቃል ይሰመርበት፤ አንድ ሙሥሊም ሙሥሊም ያልሆነን ሰው አሠላሙ አለይኩም አይልም፤ ምክንያቱም ይህ የሙስሊም ሰላምታ ነውና፤ ከዛ ይልቅ እንደ አገሩ ባህል "ጤና ይስጥልኝ" "ሰላም" "እንደምን ዋልክ" ወዘተ.. ማለት ይችላል፤ ነገር ግን ሙስሊም ያልሆነ ሰው አሠላሙ አለይኩም ካለን አላህ፦ "እርሷኑ መልሷት" ስላለ "ወአለይኩም" وَعَلَيْكُمْ ብለን እንመልሳለን፦
አል-አደበል ሙፍረድ መጽሐፍ 44, ሐዲስ 2
አቢ በስረል ጊፋሪይ እንደተረከው፦ "ነብዩም"ﷺ" አሉ፦ *"ነገ ወደ አንድ አይሁድ እጓዛለው፤ በመጀመሪያ ሰላም(አሠላሙ አለይኩም) አትበሏቸው፤ አሠላም አለይኩም ቢሏችሁ ግን ወአለይኩም በሉ*። عَنْ أَبِي بَصْرَةَ الْغِفَارِيِّ، عَنِ النَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم قَالَ: إِنِّي رَاكِبٌ غَدًا إِلَى يَهُودَ، فَلاَ تَبْدَأُوهُمْ بِالسَّلاَمِ، فَإِذَا سَلَّمُوا عَلَيْكُمْ فَقُولُوا: وَعَلَيْكُمْ.
አል-አደበል ሙፍረድ መጽሐፍ 44, ሐዲስ 3
አቢ ሁረይራህ እንደተረከው፦ "ነብዩም"ﷺ" አሉ፦ *"የመጽሐፉ ሰዎችን ቅድሚያ ሰላም(አሠላሙ አለይኩም) አትበሏቸው*። عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ، عَنِ النَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم قَالَ: أَهْلُ الْكِتَابِ لاَ تَبْدَأُوهُمْ بِالسَّلاَمِ
ሱነን ኢብኑ ማጃህ መጽሐፍ 33, ሐዲስ 41
ዐነሥ ኢብኑ ማሊክ እንደተረከው፦ "የአላህ መልእክተኛም"ﷺ" አሉ፦ *"ማንም ከመጽሐፉ ሰዎች ሠላም(አሠላሙ አለይኩም) ብሎ ሰላምታ ከሳጣችሁ፥ "ወአለይኩም" በሉ*። عَنْ أَنَسِ بْنِ مَالِكٍ، قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ ـ صلى الله عليه وسلم ـ " إِذَا سَلَّمَ عَلَيْكُمْ أَحَدٌ مِنْ أَهْلِ الْكِتَابِ فَقُولُوا وَعَلَيْكُمْ.
የአላህ ሰላም የሚገኘው አላህን በኢኽላስ በመታዘዝ ብቻ ነው፤ "ኢሥላም" إِسْلَٰم የሚለው ቃል "አሥለመ" أَسْلَمَ ማለትም "ታዘዘ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "መታዘዝ" ማለት ነው። “ሠለም” سَلَم ማለት ደግሞ “ታዛዥነት” ማለት ነው።
"ሙሥሊም" مُسْلِم ማለት "ታዛዥ" ማለት ነው፤ አንድ ሙስሊም አላህን በፍጹም ሲታዘዝ የአላህ ሰላም ከእርሱ ጋር ይሆናል፤ ያኔ ውስጡ "ሠሊም" سَلِيم ማለትም "ንፁህ" ይሆናል፤ እርሱም "ሠሊሙን" سَٰلِمُون ማለትም "ሰላማዊ" ይሆናል። አምላካችን አላህ እርሱን በመታዘዝ የውስጥ ሰላም ከሚያገኙት ሰላማውያን ያድርገን! አሚን።
✍ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሰላሙ አለይኩም
ተህሊል
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
47፥19 *እነሆ ከአላህ ሌላ አምላክ አለመኖሩንም ዕወቅ*፡፡ فَاعْلَمْ أَنَّهُ لَا إِلَـٰهَ إِلَّا اللَّهُ
“ተህሊል” تهليل ማለት “ላ ኢላሀ ኢለልሏህ ” لَا إِلَـٰهَ إِلَّا الله ማለትም “ከአላህ በቀር በእውነት የሚመለክ አምላክ የለም” ማለት ነው፤ አላህ ጥንት ለነበሩት ነቢያቱ ወሕይ የሚያወርድላቸው የነበረው “ላ ኢላሃ ኢልላ አና” لَا إِلَٰهَ إِلَّا أَنَا ማለትም “ከኔ በቀር ሌላ አምላክ የለም” የሚል ነው፦
21፥25 ከአንተ በፊትም እነሆ *”ከእኔ ሌላ አምላክ የለምና አምልኩኝ”* በማለት ወደ እርሱ የምናወርድለት ቢኾን እንጅ ከመልክተኛ አንድንም አልላክንም፡፡ وَمَآ أَرْسَلْنَا مِن قَبْلِكَ مِن رَّسُولٍ إِلَّا نُوحِىٓ إِلَيْهِ أَنَّهُۥ لَآ إِلَٰهَ إِلَّآ أَنَا۠ فَٱعْبُدُونِ
16፥2 ከባሮቹ በሚሻው ሰው ላይ መላእክትን ከራእይ ጋር በፈቃዱ ያወርዳል ከሓዲዎችን በቅጣት አስጠንቅቁ፤ እነሆ *”ከእኔ በቀር ሌላ አምላክ የለም፤ ፍሩኝም”* ማለትን አስታውቁ በማለት ያወርዳል፡፡ يُنَزِّلُ ٱلْمَلَٰٓئِكَةَ بِٱلرُّوحِ مِنْ أَمْرِهِۦ عَلَىٰ مَن يَشَآءُ مِنْ عِبَادِهِۦٓ أَنْ أَنذِرُوٓا۟ أَنَّهُۥ لَآ إِلَٰهَ إِلَّآ أَنَا۠ فَٱتَّقُونِ
የዕውቀት መጀመሪያ ከአላህ ሌላ አምላክ አለመኖሩንም ማወቅ ነው፦
47፥19 *እነሆ ከአላህ ሌላ አምላክ አለመኖሩንም ዕወቅ*፡፡ فَاعْلَمْ أَنَّهُ لَا إِلَـٰهَ إِلَّا اللَّهُ
11፥14 ለእናንተም ጥሪውን ባይቀበሏችሁ የተወረደው በአላህ እውቀት ብቻ መሆኑን እና *ከእርሱ ሌላ አምላክ አለመኖሩን ዕወቁ፡፡ ታዲያ እናንተ የምትሰልሙ ናችሁን?* በላቸው፡፡ فَإِلَّمْ يَسْتَجِيبُوا لَكُمْ فَاعْلَمُوا أَنَّمَا أُنزِلَ بِعِلْمِ اللَّهِ وَأَن لَّا إِلَـٰهَ إِلَّا هُوَ ۖ فَهَلْ أَنتُم مُّسْلِمُونَ
ከአላህ በቀር ሌላ አምላክ የለም ብሎ ትምህርት ኢስላም ይባላል፤ “ከእርሱ ሌላ አምላክ አለመኖሩን ዕወቁ፡፡ ታዲያ እናንተ የምትሰልሙ ናችሁን?” የሚለው ይሰመርበት፦
40፥66 *እኔ ከጌታዬ አስረጂዎች በመጡልኝ ጊዜ* እነዚያን ከአላህ ሌላ የምትጠሯዋቸውን እንዳላመልክ ተከልክያለሁ፡፡ ለዓለማት ጌታም *እንድገዛ* ታዝዣለሁ» በላቸው፡፡ قُلْ إِنِّي نُهِيتُ أَنْ أَعْبُدَ الَّذِينَ تَدْعُونَ مِن دُونِ اللَّهِ لَمَّا جَاءَنِيَ الْبَيِّنَاتُ مِن رَّبِّي وَأُمِرْتُ أَنْ أُسْلِمَ لِرَبِّ الْعَالَمِينَ
6፥71 «የአላህ መንገድ እርሱ ቀጥተኛው መንገድ ነው፡፡ ለዓለማት ጌታ *ልንገዛም* ታዘዝን» በላቸው፡፡ قُلْ إِنَّ هُدَى ٱللَّهِ هُوَ ٱلْهُدَىٰ ۖ وَأُمِرْنَا لِنُسْلِمَ لِرَبِّ ٱلْعَٰلَمِينَ
27፥44 «ጌታዬ ሆይ! እኔ ነፍሴን በደልኩ፡፡ ከሱለይማንም ጋር ሆኜ ለዓለማት ጌታ ለአላህ *ታዘዝኩ*» አለች፡፡ قَالَتْ رَبِّ إِنِّى ظَلَمْتُ نَفْسِى وَأَسْلَمْتُ مَعَ سُلَيْمَٰنَ لِلَّهِ رَبِّ ٱلْعَٰلَمِينَ
“እንድገዛ” ለሚለው ቃል የተቀመጠው “ኡሥሊመ” أُسْلِمَ ሲሆን “ልንገዛ” ለሚለው ደግሞ “ሊኑሥሊመ” لِنُسْلِمَ ነው፤ የሳባ ንግሥት “ታዘዝኩኝ” ለሚለው ቃል “አሥለምቱ” َأَسْلَمْتُ ማለቷ አንባቢ ልብ ይለዋል፤ ሙስሊም ማለት ለዓለማቱ ጌታ የሚገዛ ማለት ነው፦
43፥69-70 *እነዚያ በአንቀጾቻችን ያመኑ እና ፍጹም ታዛዦች የነበሩ* «ገነትን ግቡ እናንተም ጥንዶቻችሁም ትደሰታላችሁ ትከበሩማላችሁ» ይባላሉ፡፡ الَّذِينَ آمَنُوا بِآيَاتِنَا وَكَانُوا مُسْلِمِينَ ادْخُلُوا الْجَنَّةَ أَنتُمْ وَأَزْوَاجُكُمْ تُحْبَرُونَ
እዚህ ላይ “ታዛዦች” ለሚለው ቃል የተቀመጠው “ሙስሊሚን” مُسْلِمِينَ ነው፤ እነዚያ የካዱት በትንሣኤ ቀን ሙስሊሞች በኾኑ ኖሮ በብዛት ይመኛሉ፦
15፥2 *እነዚያ የካዱት በትንሣኤ ቀን ሙስሊሞች በኾኑ ኖሮ በብዛት ይመኛሉ*፡፡ رُّبَمَا يَوَدُّ الَّذِينَ كَفَرُوا لَوْ كَانُوا مُسْلِمِينَ
ምክንያቱም ሙስሊም “ከአላህ ሌላ አምላክ የለም” ብሎ የተቀበለ ስለሆነ ከሃድያን “ከአላህ ሌላ አምላክ የለም” ሲባሉ ይኮሩ ስለነበር በትንሣኤ ቀን ሙስሊሞች በኾኑ ኖሩ በብዛት ይመኛሉ፦
37፥35 እነርሱ *ከአላህ ሌላ አምላክ የለም* በተባሉ ጊዜ ይኮሩ ነበሩ፡፡ إِنَّهُمْ كَانُوا إِذَا قِيلَ لَهُمْ لَا إِلَـٰهَ إِلَّا اللَّهُ يَسْتَكْبِرُونَ
አላህ ሙስሊም ሆነው ከሚሞቱት ባሮቹ ያድርገን።
✍ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሰላሙ አለይኩም
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
47፥19 *እነሆ ከአላህ ሌላ አምላክ አለመኖሩንም ዕወቅ*፡፡ فَاعْلَمْ أَنَّهُ لَا إِلَـٰهَ إِلَّا اللَّهُ
“ተህሊል” تهليل ማለት “ላ ኢላሀ ኢለልሏህ ” لَا إِلَـٰهَ إِلَّا الله ማለትም “ከአላህ በቀር በእውነት የሚመለክ አምላክ የለም” ማለት ነው፤ አላህ ጥንት ለነበሩት ነቢያቱ ወሕይ የሚያወርድላቸው የነበረው “ላ ኢላሃ ኢልላ አና” لَا إِلَٰهَ إِلَّا أَنَا ማለትም “ከኔ በቀር ሌላ አምላክ የለም” የሚል ነው፦
21፥25 ከአንተ በፊትም እነሆ *”ከእኔ ሌላ አምላክ የለምና አምልኩኝ”* በማለት ወደ እርሱ የምናወርድለት ቢኾን እንጅ ከመልክተኛ አንድንም አልላክንም፡፡ وَمَآ أَرْسَلْنَا مِن قَبْلِكَ مِن رَّسُولٍ إِلَّا نُوحِىٓ إِلَيْهِ أَنَّهُۥ لَآ إِلَٰهَ إِلَّآ أَنَا۠ فَٱعْبُدُونِ
16፥2 ከባሮቹ በሚሻው ሰው ላይ መላእክትን ከራእይ ጋር በፈቃዱ ያወርዳል ከሓዲዎችን በቅጣት አስጠንቅቁ፤ እነሆ *”ከእኔ በቀር ሌላ አምላክ የለም፤ ፍሩኝም”* ማለትን አስታውቁ በማለት ያወርዳል፡፡ يُنَزِّلُ ٱلْمَلَٰٓئِكَةَ بِٱلرُّوحِ مِنْ أَمْرِهِۦ عَلَىٰ مَن يَشَآءُ مِنْ عِبَادِهِۦٓ أَنْ أَنذِرُوٓا۟ أَنَّهُۥ لَآ إِلَٰهَ إِلَّآ أَنَا۠ فَٱتَّقُونِ
የዕውቀት መጀመሪያ ከአላህ ሌላ አምላክ አለመኖሩንም ማወቅ ነው፦
47፥19 *እነሆ ከአላህ ሌላ አምላክ አለመኖሩንም ዕወቅ*፡፡ فَاعْلَمْ أَنَّهُ لَا إِلَـٰهَ إِلَّا اللَّهُ
11፥14 ለእናንተም ጥሪውን ባይቀበሏችሁ የተወረደው በአላህ እውቀት ብቻ መሆኑን እና *ከእርሱ ሌላ አምላክ አለመኖሩን ዕወቁ፡፡ ታዲያ እናንተ የምትሰልሙ ናችሁን?* በላቸው፡፡ فَإِلَّمْ يَسْتَجِيبُوا لَكُمْ فَاعْلَمُوا أَنَّمَا أُنزِلَ بِعِلْمِ اللَّهِ وَأَن لَّا إِلَـٰهَ إِلَّا هُوَ ۖ فَهَلْ أَنتُم مُّسْلِمُونَ
ከአላህ በቀር ሌላ አምላክ የለም ብሎ ትምህርት ኢስላም ይባላል፤ “ከእርሱ ሌላ አምላክ አለመኖሩን ዕወቁ፡፡ ታዲያ እናንተ የምትሰልሙ ናችሁን?” የሚለው ይሰመርበት፦
40፥66 *እኔ ከጌታዬ አስረጂዎች በመጡልኝ ጊዜ* እነዚያን ከአላህ ሌላ የምትጠሯዋቸውን እንዳላመልክ ተከልክያለሁ፡፡ ለዓለማት ጌታም *እንድገዛ* ታዝዣለሁ» በላቸው፡፡ قُلْ إِنِّي نُهِيتُ أَنْ أَعْبُدَ الَّذِينَ تَدْعُونَ مِن دُونِ اللَّهِ لَمَّا جَاءَنِيَ الْبَيِّنَاتُ مِن رَّبِّي وَأُمِرْتُ أَنْ أُسْلِمَ لِرَبِّ الْعَالَمِينَ
6፥71 «የአላህ መንገድ እርሱ ቀጥተኛው መንገድ ነው፡፡ ለዓለማት ጌታ *ልንገዛም* ታዘዝን» በላቸው፡፡ قُلْ إِنَّ هُدَى ٱللَّهِ هُوَ ٱلْهُدَىٰ ۖ وَأُمِرْنَا لِنُسْلِمَ لِرَبِّ ٱلْعَٰلَمِينَ
27፥44 «ጌታዬ ሆይ! እኔ ነፍሴን በደልኩ፡፡ ከሱለይማንም ጋር ሆኜ ለዓለማት ጌታ ለአላህ *ታዘዝኩ*» አለች፡፡ قَالَتْ رَبِّ إِنِّى ظَلَمْتُ نَفْسِى وَأَسْلَمْتُ مَعَ سُلَيْمَٰنَ لِلَّهِ رَبِّ ٱلْعَٰلَمِينَ
“እንድገዛ” ለሚለው ቃል የተቀመጠው “ኡሥሊመ” أُسْلِمَ ሲሆን “ልንገዛ” ለሚለው ደግሞ “ሊኑሥሊመ” لِنُسْلِمَ ነው፤ የሳባ ንግሥት “ታዘዝኩኝ” ለሚለው ቃል “አሥለምቱ” َأَسْلَمْتُ ማለቷ አንባቢ ልብ ይለዋል፤ ሙስሊም ማለት ለዓለማቱ ጌታ የሚገዛ ማለት ነው፦
43፥69-70 *እነዚያ በአንቀጾቻችን ያመኑ እና ፍጹም ታዛዦች የነበሩ* «ገነትን ግቡ እናንተም ጥንዶቻችሁም ትደሰታላችሁ ትከበሩማላችሁ» ይባላሉ፡፡ الَّذِينَ آمَنُوا بِآيَاتِنَا وَكَانُوا مُسْلِمِينَ ادْخُلُوا الْجَنَّةَ أَنتُمْ وَأَزْوَاجُكُمْ تُحْبَرُونَ
እዚህ ላይ “ታዛዦች” ለሚለው ቃል የተቀመጠው “ሙስሊሚን” مُسْلِمِينَ ነው፤ እነዚያ የካዱት በትንሣኤ ቀን ሙስሊሞች በኾኑ ኖሮ በብዛት ይመኛሉ፦
15፥2 *እነዚያ የካዱት በትንሣኤ ቀን ሙስሊሞች በኾኑ ኖሮ በብዛት ይመኛሉ*፡፡ رُّبَمَا يَوَدُّ الَّذِينَ كَفَرُوا لَوْ كَانُوا مُسْلِمِينَ
ምክንያቱም ሙስሊም “ከአላህ ሌላ አምላክ የለም” ብሎ የተቀበለ ስለሆነ ከሃድያን “ከአላህ ሌላ አምላክ የለም” ሲባሉ ይኮሩ ስለነበር በትንሣኤ ቀን ሙስሊሞች በኾኑ ኖሩ በብዛት ይመኛሉ፦
37፥35 እነርሱ *ከአላህ ሌላ አምላክ የለም* በተባሉ ጊዜ ይኮሩ ነበሩ፡፡ إِنَّهُمْ كَانُوا إِذَا قِيلَ لَهُمْ لَا إِلَـٰهَ إِلَّا اللَّهُ يَسْتَكْبِرُونَ
አላህ ሙስሊም ሆነው ከሚሞቱት ባሮቹ ያድርገን።
✍ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሰላሙ አለይኩም
ወንድማማችነት
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
49፥10 *ምእመናኖች ወንድማመቾች ናቸው፡፡ በሁለት ወንድሞቻችሁም መካከል አስታርቁ*፡፡ ይታዘንላችሁም ዘንድ አላህን ፍሩ፡፡ إِنَّمَا الْمُؤْمِنُونَ إِخْوَةٌ فَأَصْلِحُوا بَيْنَ أَخَوَيْكُمْ ۚ وَاتَّقُوا اللَّهَ لَعَلَّكُمْ تُرْحَمُونَ
በአማርኛችን ላይ “ወንድማማችነት”brotherhood” እና “እህትማማችነት”sisterhood” የሚሉትን የሚያቅፍ አንድ ቃል የለም። ነገር ግን ቁርኣኑ ላይ ሁለቱንም የሚያቅፍ “ኢኽወቱን” إِخْوَةٌ የሚል ቃል አለ። እንግዲህ እኔ ሆነ አማርኛው የቁርኣን ትርጉም በዚህ አርስት ላይ “ወንድማማችነት” ስል ሁለቱንም ጾታ ያቀፈ መሆኑን አንባቢ ልብ ይለዋል። አምላካችን አላህ በቁርኣን ወንድማማች የሚላቸው በሦስት ዋና ዋና ክፍል ይከፈላሉ፦
ነጥብ አንድ
“ሰብአዊ ወንድማማችነት”
የሰው ልጆች ባጠቃላይ ኑባሪያችን ሰው ነን፤ ሰብአዊነት ያገኘነው ከአባታችን አደም እና ከእናታችን ሐዋ ነው፤ ሁላችንንም የአዳም ልጆች ነን፤ አላህ ሰዎችን ሁሉ ከአንድ የአደም ስብዕና እና ከመቀናጃው ከሐዋ ብዙ ወንዶችንና ሴቶች የበተነውን ነው፦
7፥27 *የአዳም ልጆች ሆይ! ሰይጣን አባትና እናታችሁን* ኀፍረተ ገላቸውን ሊያሳያቸው ልብሶቻቸውን ከነሱ የገፈፋቸው ሲኾን ከገነት እንዳወጣቸው ሁሉ እናንተን አይሞክራችሁ፡፡ يَا بَنِي آدَمَ لَا يَفْتِنَنَّكُمُ الشَّيْطَانُ كَمَا أَخْرَجَ أَبَوَيْكُم مِّنَ الْجَنَّةِ يَنزِعُ عَنْهُمَا لِبَاسَهُمَا لِيُرِيَهُمَا سَوْآتِهِمَا ۗ إِنَّهُ يَرَاكُمْ هُوَ وَقَبِيلُهُ مِنْ حَيْثُ لَا تَرَوْنَهُمْ ۗ إِنَّا جَعَلْنَا الشَّيَاطِينَ أَوْلِيَاءَ لِلَّذِينَ لَا يُؤْمِنُونَ
4፥1 *እናንተ ሰዎች ሆይ! ያንን ከአንዲት ነፍስ የፈጠራችሁን ከእርስዋም መቀናጆዋን የፈጠረውን ከእነርሱም ብዙ ወንዶችንና ሴቶች የበተነውን ጌታችሁን ፍሩ*፡፡ يَا أَيُّهَا النَّاسُ اتَّقُوا رَبَّكُمُ الَّذِي خَلَقَكُم مِّن نَّفْسٍ وَاحِدَةٍ وَخَلَقَ مِنْهَا زَوْجَهَا وَبَثَّ مِنْهُمَا رِجَالًا كَثِيرًا وَنِسَاءً ۚ وَاتَّقُوا اللَّهَ الَّذِي تَسَاءَلُونَ بِهِ وَالْأَرْحَامَ ۚ إِنَّ اللَّهَ كَانَ عَلَيْكُمْ رَقِيبًا
በዚህ ወንድማማችነት ከሃድያንም ወንድምና እህት ናቸው፤ ምክንያቱም እነርሱ ድመት፣ ውሻ፣ ዝንጀሮ ሳይሆኑ ሰው ስለሆኑ፤ አምላካችን አላህ ከሃድያንን በወገን ደረጃ ለአማንያን “ወንድማቸው” በማለት ይናገራል፦
26፥106 *ወንድማቸው ኑሕ* ለእነርሱ ባላቸው ጊዜ «አትጠነቀቁምን? إِذْ قَالَ لَهُمْ أَخُوهُمْ نُوحٌ أَلَا تَتَّقُونَ
7፥56 ወደ ዓድም *ወንድማቸውን ሁድን ላክን*፡፡ «ወገኖቼ ሆይ! አላህን ተገዙ፡፡ ከእርሱ ሌላ ምንም አምላክ የላችሁም፡፡ የአላህን ቅጣት አትፈሩምን» አላቸው፡፡ وَإِلَىٰ عَادٍ أَخَاهُمْ هُودًا ۗ قَالَ يَا قَوْمِ اعْبُدُوا اللَّهَ مَا لَكُم مِّنْ إِلَـٰهٍ غَيْرُهُ ۚ أَفَلَا تَتَّقُونَ
11፥61 *ወደ ሰሙዶችም ወንድማቸውን ሷሊህን ላክን*፡፡ «ሕዝቦቼ ሆይ! አላህን ተገዙ፡፡ ከእርሱ ሌላ ለእናንተ አምላክ የላችሁም፡፡ وَإِلَىٰ ثَمُودَ أَخَاهُمْ صَالِحًا ۚ قَالَ يَا قَوْمِ اعْبُدُوا اللَّهَ مَا لَكُم مِّنْ إِلَـٰهٍ غَيْرُهُ ۖ هُوَ أَنشَأَكُم مِّنَ الْأَرْضِ وَاسْتَعْمَرَكُمْ فِيهَا فَاسْتَغْفِرُوهُ ثُمَّ تُوبُوا إِلَيْهِ ۚ إِنَّ رَبِّي قَرِيبٌ مُّجِيبٌ
26፥161 *ወንድማቸው ሉጥ ለእነርሱ ባለ ጊዜ «አትጠነቀቁምን?* إِذْ قَالَ لَهُمْ أَخُوهُمْ لُوطٌ أَلَا تَتَّقُونَ
11፥84 *ወደ መድየንም ወንድማቸውን ሹዐይብን ላክን*፡፡ አላቸው «ሕዝቦቼ ሆይ! አላህን ተገዙ፡፡ ከእርሱ ሌላ ለናንተ አምላክ የላችሁም፡፡ وَإِلَىٰ مَدْيَنَ أَخَاهُمْ شُعَيْبًا ۚ قَالَ يَا قَوْمِ اعْبُدُوا اللَّهَ مَا لَكُم مِّنْ إِلَـٰهٍ غَيْرُهُ ۖ وَلَا تَنقُصُوا الْمِكْيَالَ وَالْمِيزَانَ ۚ إِنِّي أَرَاكُم بِخَيْرٍ وَإِنِّي أَخَافُ عَلَيْكُمْ عَذَابَ يَوْمٍ مُّحِيطٍ
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
49፥10 *ምእመናኖች ወንድማመቾች ናቸው፡፡ በሁለት ወንድሞቻችሁም መካከል አስታርቁ*፡፡ ይታዘንላችሁም ዘንድ አላህን ፍሩ፡፡ إِنَّمَا الْمُؤْمِنُونَ إِخْوَةٌ فَأَصْلِحُوا بَيْنَ أَخَوَيْكُمْ ۚ وَاتَّقُوا اللَّهَ لَعَلَّكُمْ تُرْحَمُونَ
በአማርኛችን ላይ “ወንድማማችነት”brotherhood” እና “እህትማማችነት”sisterhood” የሚሉትን የሚያቅፍ አንድ ቃል የለም። ነገር ግን ቁርኣኑ ላይ ሁለቱንም የሚያቅፍ “ኢኽወቱን” إِخْوَةٌ የሚል ቃል አለ። እንግዲህ እኔ ሆነ አማርኛው የቁርኣን ትርጉም በዚህ አርስት ላይ “ወንድማማችነት” ስል ሁለቱንም ጾታ ያቀፈ መሆኑን አንባቢ ልብ ይለዋል። አምላካችን አላህ በቁርኣን ወንድማማች የሚላቸው በሦስት ዋና ዋና ክፍል ይከፈላሉ፦
ነጥብ አንድ
“ሰብአዊ ወንድማማችነት”
የሰው ልጆች ባጠቃላይ ኑባሪያችን ሰው ነን፤ ሰብአዊነት ያገኘነው ከአባታችን አደም እና ከእናታችን ሐዋ ነው፤ ሁላችንንም የአዳም ልጆች ነን፤ አላህ ሰዎችን ሁሉ ከአንድ የአደም ስብዕና እና ከመቀናጃው ከሐዋ ብዙ ወንዶችንና ሴቶች የበተነውን ነው፦
7፥27 *የአዳም ልጆች ሆይ! ሰይጣን አባትና እናታችሁን* ኀፍረተ ገላቸውን ሊያሳያቸው ልብሶቻቸውን ከነሱ የገፈፋቸው ሲኾን ከገነት እንዳወጣቸው ሁሉ እናንተን አይሞክራችሁ፡፡ يَا بَنِي آدَمَ لَا يَفْتِنَنَّكُمُ الشَّيْطَانُ كَمَا أَخْرَجَ أَبَوَيْكُم مِّنَ الْجَنَّةِ يَنزِعُ عَنْهُمَا لِبَاسَهُمَا لِيُرِيَهُمَا سَوْآتِهِمَا ۗ إِنَّهُ يَرَاكُمْ هُوَ وَقَبِيلُهُ مِنْ حَيْثُ لَا تَرَوْنَهُمْ ۗ إِنَّا جَعَلْنَا الشَّيَاطِينَ أَوْلِيَاءَ لِلَّذِينَ لَا يُؤْمِنُونَ
4፥1 *እናንተ ሰዎች ሆይ! ያንን ከአንዲት ነፍስ የፈጠራችሁን ከእርስዋም መቀናጆዋን የፈጠረውን ከእነርሱም ብዙ ወንዶችንና ሴቶች የበተነውን ጌታችሁን ፍሩ*፡፡ يَا أَيُّهَا النَّاسُ اتَّقُوا رَبَّكُمُ الَّذِي خَلَقَكُم مِّن نَّفْسٍ وَاحِدَةٍ وَخَلَقَ مِنْهَا زَوْجَهَا وَبَثَّ مِنْهُمَا رِجَالًا كَثِيرًا وَنِسَاءً ۚ وَاتَّقُوا اللَّهَ الَّذِي تَسَاءَلُونَ بِهِ وَالْأَرْحَامَ ۚ إِنَّ اللَّهَ كَانَ عَلَيْكُمْ رَقِيبًا
በዚህ ወንድማማችነት ከሃድያንም ወንድምና እህት ናቸው፤ ምክንያቱም እነርሱ ድመት፣ ውሻ፣ ዝንጀሮ ሳይሆኑ ሰው ስለሆኑ፤ አምላካችን አላህ ከሃድያንን በወገን ደረጃ ለአማንያን “ወንድማቸው” በማለት ይናገራል፦
26፥106 *ወንድማቸው ኑሕ* ለእነርሱ ባላቸው ጊዜ «አትጠነቀቁምን? إِذْ قَالَ لَهُمْ أَخُوهُمْ نُوحٌ أَلَا تَتَّقُونَ
7፥56 ወደ ዓድም *ወንድማቸውን ሁድን ላክን*፡፡ «ወገኖቼ ሆይ! አላህን ተገዙ፡፡ ከእርሱ ሌላ ምንም አምላክ የላችሁም፡፡ የአላህን ቅጣት አትፈሩምን» አላቸው፡፡ وَإِلَىٰ عَادٍ أَخَاهُمْ هُودًا ۗ قَالَ يَا قَوْمِ اعْبُدُوا اللَّهَ مَا لَكُم مِّنْ إِلَـٰهٍ غَيْرُهُ ۚ أَفَلَا تَتَّقُونَ
11፥61 *ወደ ሰሙዶችም ወንድማቸውን ሷሊህን ላክን*፡፡ «ሕዝቦቼ ሆይ! አላህን ተገዙ፡፡ ከእርሱ ሌላ ለእናንተ አምላክ የላችሁም፡፡ وَإِلَىٰ ثَمُودَ أَخَاهُمْ صَالِحًا ۚ قَالَ يَا قَوْمِ اعْبُدُوا اللَّهَ مَا لَكُم مِّنْ إِلَـٰهٍ غَيْرُهُ ۖ هُوَ أَنشَأَكُم مِّنَ الْأَرْضِ وَاسْتَعْمَرَكُمْ فِيهَا فَاسْتَغْفِرُوهُ ثُمَّ تُوبُوا إِلَيْهِ ۚ إِنَّ رَبِّي قَرِيبٌ مُّجِيبٌ
26፥161 *ወንድማቸው ሉጥ ለእነርሱ ባለ ጊዜ «አትጠነቀቁምን?* إِذْ قَالَ لَهُمْ أَخُوهُمْ لُوطٌ أَلَا تَتَّقُونَ
11፥84 *ወደ መድየንም ወንድማቸውን ሹዐይብን ላክን*፡፡ አላቸው «ሕዝቦቼ ሆይ! አላህን ተገዙ፡፡ ከእርሱ ሌላ ለናንተ አምላክ የላችሁም፡፡ وَإِلَىٰ مَدْيَنَ أَخَاهُمْ شُعَيْبًا ۚ قَالَ يَا قَوْمِ اعْبُدُوا اللَّهَ مَا لَكُم مِّنْ إِلَـٰهٍ غَيْرُهُ ۖ وَلَا تَنقُصُوا الْمِكْيَالَ وَالْمِيزَانَ ۚ إِنِّي أَرَاكُم بِخَيْرٍ وَإِنِّي أَخَافُ عَلَيْكُمْ عَذَابَ يَوْمٍ مُّحِيطٍ
ነጥብ ሁለት
“አብራካዊ ወንድማማችነት”
በአንድ ማህጸን የተኙ ወንድምና እህት ወይም ከአንድ አባት የሚወለዱ የአብራክ ክፋይ ወንድምና እህት ይባላሉ፦
12፥5 አባቱም አለ «ልጄ ሆይ! ሕልምህን *ለወንድሞችህ* አታውራ፡፡ ላንተ ተንኮልን ይሰሩብሃልና፡፡ ሰይጣን ለሰው ግልጽ ጠላት ነውና፡፡» قَالَ يَا بُنَيَّ لَا تَقْصُصْ رُؤْيَاكَ عَلَىٰ إِخْوَتِكَ فَيَكِيدُوا لَكَ كَيْدًا ۖ إِنَّ الشَّيْطَانَ لِلْإِنسَانِ عَدُوٌّ مُّبِينٌ
7፥151 ሙሳም፡- «ጌታዬ ሆይ! *ለእኔም ለወንድሜም ማር*፡፡ በእዝነትህም ውስጥ አግባን፡፡ አንተም ከአዛኞች ሁሉ ይበልጥ አዛኝ ነህ» አለ፡፡ قَالَ رَبِّ اغْفِرْ لِي وَلِأَخِي وَأَدْخِلْنَا فِي رَحْمَتِكَ ۖ وَأَنتَ أَرْحَمُ الرَّاحِمِينَ
ነጥብ ሦስት
“መንፈሳዊ ወንድማማችነት”
በሊላሂ መንገድ የአላህን ገመድ የያዝን አማንያን በጸጋው የሃይማኖት ወንድማማች ነን፦
9፥11 ቢጸጸቱም፣ ሶላትንም ቢሰግዱ፣ ዘካንም ቢሰጡ *የሃይማኖት ወንድሞቻችሁ ናቸው*፡፡ ለሚያውቁ ሕዝቦችም አንቀጾችን እናብራራለን፡፡ فَإِن تَابُوا وَأَقَامُوا الصَّلَاةَ وَآتَوُا الزَّكَاةَ فَإِخْوَانُكُمْ فِي الدِّينِ ۗ وَنُفَصِّلُ الْآيَاتِ لِقَوْمٍ يَعْلَمُونَ
3፥103 *የአላህንም ገመድ ሁላችሁም ያዙ፡፡ አትለያዩም፡፡ ጠበኞችም በነበራችሁ ጊዜ በእናንተ ላይ የዋለውን የአላህን ጸጋ አስታውሱ፡፡ በልቦቻችሁም መካከል አስማማ፡፡ በጸጋውም ወንድማማቾች ኾናችሁ*፡፡ وَاعْتَصِمُوا بِحَبْلِ اللَّهِ جَمِيعًا وَلَا تَفَرَّقُوا ۚ وَاذْكُرُوا نِعْمَتَ اللَّهِ عَلَيْكُمْ إِذْ كُنتُمْ أَعْدَاءً فَأَلَّفَ بَيْنَ قُلُوبِكُمْ فَأَصْبَحْتُم بِنِعْمَتِهِ إِخْوَانًا وَكُنتُمْ عَلَىٰ شَفَا حُفْرَةٍ مِّنَ النَّارِ فَأَنقَذَكُم مِّنْهَا ۗ كَذَٰلِكَ يُبَيِّنُ اللَّهُ لَكُمْ آيَاتِهِ لَعَلَّكُمْ تَهْتَدُونَ
33፥5 ለአባቶቻቸው በማስጠጋት ጥሯቸው፡፡ እርሱ አላህ ዘንድ ትክክለኛ ነው፡፡ አባቶቻቸውንም ባታውቁ *በሃይማኖት ወንድሞቻችሁና ዘመዶቻችሁ ናቸው*፡፡ ادْعُوهُمْ لِآبَائِهِمْ هُوَ أَقْسَطُ عِندَ اللَّهِ ۚ فَإِن لَّمْ تَعْلَمُوا آبَاءَهُمْ فَإِخْوَانُكُمْ فِي الدِّينِ وَمَوَالِيكُمْ ۚ وَلَيْسَ عَلَيْكُمْ جُنَاحٌ فِيمَا أَخْطَأْتُم بِهِ وَلَـٰكِن مَّا تَعَمَّدَتْ قُلُوبُكُمْ ۚ وَكَانَ اللَّهُ غَفُورًا رَّحِيمًا
49፥10 *ምእመናኖች ወንድማመቾች ናቸው፡፡ በሁለት ወንድሞቻችሁም መካከል አስታርቁ*፡፡ ይታዘንላችሁም ዘንድ አላህን ፍሩ፡፡ إِنَّمَا الْمُؤْمِنُونَ إِخْوَةٌ فَأَصْلِحُوا بَيْنَ أَخَوَيْكُمْ ۚ وَاتَّقُوا اللَّهَ لَعَلَّكُمْ تُرْحَمُونَ
ይህ የባህርይ መመሳሰል ለምሳሌ አባካኞች የሰይጣናት ወንድሞች ናቸውና፦
17፥27 *አባካኞች የሰይጣናት ወንድሞች ናቸውና*፡፡ ሰይጣንም ለጌታው ብርቱ ከሓዲ ነው፡፡ إِنَّ الْمُبَذِّرِينَ كَانُوا إِخْوَانَ الشَّيَاطِينِ ۖ وَكَانَ الشَّيْطَانُ لِرَبِّهِ كَفُورًا
✍ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሰላሙ አለይኩም
“አብራካዊ ወንድማማችነት”
በአንድ ማህጸን የተኙ ወንድምና እህት ወይም ከአንድ አባት የሚወለዱ የአብራክ ክፋይ ወንድምና እህት ይባላሉ፦
12፥5 አባቱም አለ «ልጄ ሆይ! ሕልምህን *ለወንድሞችህ* አታውራ፡፡ ላንተ ተንኮልን ይሰሩብሃልና፡፡ ሰይጣን ለሰው ግልጽ ጠላት ነውና፡፡» قَالَ يَا بُنَيَّ لَا تَقْصُصْ رُؤْيَاكَ عَلَىٰ إِخْوَتِكَ فَيَكِيدُوا لَكَ كَيْدًا ۖ إِنَّ الشَّيْطَانَ لِلْإِنسَانِ عَدُوٌّ مُّبِينٌ
7፥151 ሙሳም፡- «ጌታዬ ሆይ! *ለእኔም ለወንድሜም ማር*፡፡ በእዝነትህም ውስጥ አግባን፡፡ አንተም ከአዛኞች ሁሉ ይበልጥ አዛኝ ነህ» አለ፡፡ قَالَ رَبِّ اغْفِرْ لِي وَلِأَخِي وَأَدْخِلْنَا فِي رَحْمَتِكَ ۖ وَأَنتَ أَرْحَمُ الرَّاحِمِينَ
ነጥብ ሦስት
“መንፈሳዊ ወንድማማችነት”
በሊላሂ መንገድ የአላህን ገመድ የያዝን አማንያን በጸጋው የሃይማኖት ወንድማማች ነን፦
9፥11 ቢጸጸቱም፣ ሶላትንም ቢሰግዱ፣ ዘካንም ቢሰጡ *የሃይማኖት ወንድሞቻችሁ ናቸው*፡፡ ለሚያውቁ ሕዝቦችም አንቀጾችን እናብራራለን፡፡ فَإِن تَابُوا وَأَقَامُوا الصَّلَاةَ وَآتَوُا الزَّكَاةَ فَإِخْوَانُكُمْ فِي الدِّينِ ۗ وَنُفَصِّلُ الْآيَاتِ لِقَوْمٍ يَعْلَمُونَ
3፥103 *የአላህንም ገመድ ሁላችሁም ያዙ፡፡ አትለያዩም፡፡ ጠበኞችም በነበራችሁ ጊዜ በእናንተ ላይ የዋለውን የአላህን ጸጋ አስታውሱ፡፡ በልቦቻችሁም መካከል አስማማ፡፡ በጸጋውም ወንድማማቾች ኾናችሁ*፡፡ وَاعْتَصِمُوا بِحَبْلِ اللَّهِ جَمِيعًا وَلَا تَفَرَّقُوا ۚ وَاذْكُرُوا نِعْمَتَ اللَّهِ عَلَيْكُمْ إِذْ كُنتُمْ أَعْدَاءً فَأَلَّفَ بَيْنَ قُلُوبِكُمْ فَأَصْبَحْتُم بِنِعْمَتِهِ إِخْوَانًا وَكُنتُمْ عَلَىٰ شَفَا حُفْرَةٍ مِّنَ النَّارِ فَأَنقَذَكُم مِّنْهَا ۗ كَذَٰلِكَ يُبَيِّنُ اللَّهُ لَكُمْ آيَاتِهِ لَعَلَّكُمْ تَهْتَدُونَ
33፥5 ለአባቶቻቸው በማስጠጋት ጥሯቸው፡፡ እርሱ አላህ ዘንድ ትክክለኛ ነው፡፡ አባቶቻቸውንም ባታውቁ *በሃይማኖት ወንድሞቻችሁና ዘመዶቻችሁ ናቸው*፡፡ ادْعُوهُمْ لِآبَائِهِمْ هُوَ أَقْسَطُ عِندَ اللَّهِ ۚ فَإِن لَّمْ تَعْلَمُوا آبَاءَهُمْ فَإِخْوَانُكُمْ فِي الدِّينِ وَمَوَالِيكُمْ ۚ وَلَيْسَ عَلَيْكُمْ جُنَاحٌ فِيمَا أَخْطَأْتُم بِهِ وَلَـٰكِن مَّا تَعَمَّدَتْ قُلُوبُكُمْ ۚ وَكَانَ اللَّهُ غَفُورًا رَّحِيمًا
49፥10 *ምእመናኖች ወንድማመቾች ናቸው፡፡ በሁለት ወንድሞቻችሁም መካከል አስታርቁ*፡፡ ይታዘንላችሁም ዘንድ አላህን ፍሩ፡፡ إِنَّمَا الْمُؤْمِنُونَ إِخْوَةٌ فَأَصْلِحُوا بَيْنَ أَخَوَيْكُمْ ۚ وَاتَّقُوا اللَّهَ لَعَلَّكُمْ تُرْحَمُونَ
ይህ የባህርይ መመሳሰል ለምሳሌ አባካኞች የሰይጣናት ወንድሞች ናቸውና፦
17፥27 *አባካኞች የሰይጣናት ወንድሞች ናቸውና*፡፡ ሰይጣንም ለጌታው ብርቱ ከሓዲ ነው፡፡ إِنَّ الْمُبَذِّرِينَ كَانُوا إِخْوَانَ الشَّيَاطِينِ ۖ وَكَانَ الشَّيْطَانُ لِرَبِّهِ كَفُورًا
✍ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሰላሙ አለይኩም
ጠንካራ ዘለበት
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፤
31፥22 እርሱ መልካም ሠሪ ሆኖ ፊቱን ወደ አላህ የሚሰጥም ሰው *ጠንካራን ዘለበት* በእርግጥ ጨበጠ፡፡ የነገሩም ሁሉ ፍጻሜ ወደ አላህ ነው፡፡ وَمَن يُسْلِمْ وَجْهَهُ إِلَى اللَّهِ وَهُوَ مُحْسِنٌ فَقَدِ اسْتَمْسَكَ بِالْعُرْوَةِ الْوُثْقَىٰ ۗ وَإِلَى اللَّهِ عَاقِبَةُ الْأُمُورِ
“ጠንካራ ዘለበት” የተባለው “ላ ኢላሃ ኢለ ሏህ” لَا إِلَٰهَ إِلَّا اللَّهُ ማለትም “ከአሏህ በቀር ሌላ አምላክ የለም” የሚለው ቃለ-ምስክርነት ነው፤ ይህ ቃለ-ምስክርነት ሁለት ማዕዘናት አለው፤ አንደኛው “ነፍይ” ሲሆን ሁለተኛ “ኢሥባት” ነው፦
“ነፍይ” نفي ማለት “አፍራሽ” ሲሆን አሉታዊ ቃል ነው፤ ይህም አሉታዊ ቃል፦ “ላ ኢላሃ” لَا إِلَٰهَ ማለትም “ሌላ አምላክ የለም” ብለን ስንል ማንኛውንም ጣኦታት ውድቅ የምናደርግበት ነው፤ በቁርአን ከአላህ ውጪ የሚደረግ ባዕድ አምልኮ “ጣጉት” لطَّاغُوتِ ይባላል።
“ኢሥባት” إثبات ማለት ደግሞ “ማፅደቅ” ሲሆን አውንታዊ ቃል ነው፤ ይህም አውንታዊ ቃል፦ “ኢለ ሏህ” إِلَّا اللَّهُ ማለትም “ከአላህ በቀር” ብለን ስንል አንዱን አምላክ በብቸኝነትና በእውነት ልናመልከው የምናፀድቅበት ነው፤ በእርግጥም በጣዖትም የሚክድና በአላህ የሚያምን ሰው ለእርሷ መበጠስ የሌላትን *ጠንካራ ዘለበት* በእርግጥ ጨበጠ፦
2፥256 በሃይማኖት ማስገደድ የለም፡፡ ቅኑ መንገድ ከጠማማው በእርግጥ ተገለጠ፡፡ በጣዖትም የሚክድና በአላህ የሚያምን ሰው ለርሷ መበጠስ የሌላትን *ጠንካራ ዘለበት* በእርግጥ ጨበጠ፡፡ አላህም ሰሚ ዐዋቂ ነው፡፡ لَا إِكْرَاهَ فِي الدِّينِ ۖ قَد تَّبَيَّنَ الرُّشْدُ مِنَ الْغَيِّ ۚ فَمَن يَكْفُرْ بِالطَّاغُوتِ وَيُؤْمِن بِاللَّهِ فَقَدِ اسْتَمْسَكَ بِالْعُرْوَةِ الْوُثْقَىٰ لَا انفِصَامَ لَهَا ۗ وَاللَّهُ سَمِيعٌ عَلِيمٌ
ይህንን ጠንካራ ዘለበት የምንጨብጠው ሁለንተናን ለአላህ በመስጠት ነው፦
31፥22 እርሱ መልካም ሠሪ ሆኖ ፊቱን ወደ አላህ የሚሰጥም ሰው *ጠንካራን ዘለበት* በእርግጥ ጨበጠ፡፡ የነገሩም ሁሉ ፍጻሜ ወደ አላህ ነው፡፡ وَمَن يُسْلِمْ وَجْهَهُ إِلَى اللَّهِ وَهُوَ مُحْسِنٌ فَقَدِ اسْتَمْسَكَ بِالْعُرْوَةِ الْوُثْقَىٰ ۗ وَإِلَى اللَّهِ عَاقِبَةُ الْأُمُورِ
“ፊት” ተብሎ የተቀመጠው ቃል “ወጅህ” وَجْه ሲሆን “ሁለንተና” ማለት ነው፦
3፥20 ቢከራከሩህም፦ *«ፊቴን ለአላህ ሰጠሁ*፤ የተከተሉኝም ሰዎች እንደዚሁ ለአላህ ሰጡ» በላቸው፡፡ فَإِنْ حَاجُّوكَ فَقُلْ أَسْلَمْتُ وَجْهِيَ لِلَّهِ وَمَنِ اتَّبَعَن
6፥79 «እኔ ለዚያ ሰማያትንና ምድርን *ለፈጠረው አምላክ ቀጥተኛ ስኾን ፊቴን አዞርኩ*፡፡ እኔም ከአጋሪዎቹ አይደለሁም» አለ። إِنِّي وَجَّهْتُ وَجْهِيَ لِلَّذِي فَطَرَ السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضَ حَنِيفًا ۖ وَمَا أَنَا مِنَ الْمُشْرِكِينَ
4፥125 እርሱ መልካም ሠሪ ኾኖ *ፊቱን ለአላህ ከሰጠ* እና የኢብራሂምንም መንገድ ቀጥተኛ ሲኾን ከተከተለ ሰው ይበልጥ ሃይማኖቱ ያማረ ማን ነው? አላህም ኢብራሂምን ፍጹም ወዳጅ አድርጐ ያዘው፡፡ وَمَنْ أَحْسَنُ دِينًا مِّمَّنْ أَسْلَمَ وَجْهَهُ لِلَّهِ وَهُوَ مُحْسِنٌ وَاتَّبَعَ مِلَّةَ إِبْرَاهِيمَ حَنِيفًا ۗ وَاتَّخَذَ اللَّهُ إِبْرَاهِيمَ خَلِيلًا
“ሰጠሁ” ተብሎ የተቀመጠበት ቃል “አስለምቱ” أَسْلَمْتُ ሲሆን “ታዘዝኩ” ማለት ነው፤ “ሰጠ” ተብሎ የተቀመጠበት ደግሞ “አስለመ” أَسْلَمَ ሲሆን “ታዘዘ” ማለት ነው፤ “ኢሥላም” إِسْلَٰم የሚለው ቃል “አሥለመ” أَسْلَمَ “ታዘዘ” “ተገዛ” ” አመለከ” ከሚል ግስ የመጣ ሲሆን ትርጉሙ “መታዘዝ” “መገዛት” “ማምለክ” ማለት ነው፤ አላህ ለኢብራሂም “አስሊም” أَسْلِمْ ማለትም “ታዘዝ” ብሎ ሲለው እርሱም ለዓለማት ጌታ “አስለምቱ” أَسْلَمْتُ ማለትም “ታዘዝኩ” አለ፤ አንድ ሁለንተናውን ለአላህ የሰጠ “ሙስሊም” مُسْلِم ማለትም “አምላኪ” “ተገዢ” “ታዛዥ” ይባላል፦
2፥131 ጌታው ለእርሱ *”ታዘዝ”* ባለው ጊዜ መረጠው፡፡ ለዓለማት ጌታ *”ታዘዝኩ”* አለ፡፡ إِذْ قَالَ لَهُۥ رَبُّهُۥٓ أَسْلِمْ ۖ قَالَ أَسْلَمْتُ لِرَبِّ ٱلْعَٰلَمِينَ
2፥139 እኛም *ለእርሱ ፍጹም ታዛዦች* ስንኾን “በአላህ ሃይማኖት” ትከራከሩናላችሁን? በላቸው፡፡ قُلْ أَتُحَآجُّونَنَا فِى ٱللَّهِ وَهُوَ رَبُّنَا وَرَبُّكُمْ وَلَنَآ أَعْمَٰلُنَا وَلَكُمْ أَعْمَٰلُكُمْ وَنَحْنُ لَهُۥ مُخْلِصُونَ
“ታዛዦች” ተብሎ የተቀመጠው ቃል “ሙስሊሙን” مُسْلِمُونَ ሲሆን “ሙስሊም” مُسْلِم ለሚለው ብዙ ቁጥር ነው፤ በእርግጥም ሁለመናውን ለአላህ የሰጠ ሰው ለእርሱ በጌታው ዘንድ ምንዳው አለው፡፤ በእርሱም ላይ ፍርሃት የለበትም፤ እርሱም አያዝንም፦
2፥112 አይደለም እርሱ በጎ ሠሪ ኾኖ *ፊቱን ለአላህ የሰጠ* ሰው ለእርሱ በጌታው ዘንድ ምንዳ አለው፡፡ በእነሱም ላይ ፍርሃት የለባቸውም፤ እነሱም አያዝኑም፡፡ بَلَىٰ مَنْ أَسْلَمَ وَجْهَهُ لِلَّهِ وَهُوَ مُحْسِنٌ فَلَهُ أَجْرُهُ عِندَ رَبِّهِ وَلَا خَوْفٌ عَلَيْهِمْ وَلَا هُمْ يَحْزَنُونَ
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፤
31፥22 እርሱ መልካም ሠሪ ሆኖ ፊቱን ወደ አላህ የሚሰጥም ሰው *ጠንካራን ዘለበት* በእርግጥ ጨበጠ፡፡ የነገሩም ሁሉ ፍጻሜ ወደ አላህ ነው፡፡ وَمَن يُسْلِمْ وَجْهَهُ إِلَى اللَّهِ وَهُوَ مُحْسِنٌ فَقَدِ اسْتَمْسَكَ بِالْعُرْوَةِ الْوُثْقَىٰ ۗ وَإِلَى اللَّهِ عَاقِبَةُ الْأُمُورِ
“ጠንካራ ዘለበት” የተባለው “ላ ኢላሃ ኢለ ሏህ” لَا إِلَٰهَ إِلَّا اللَّهُ ማለትም “ከአሏህ በቀር ሌላ አምላክ የለም” የሚለው ቃለ-ምስክርነት ነው፤ ይህ ቃለ-ምስክርነት ሁለት ማዕዘናት አለው፤ አንደኛው “ነፍይ” ሲሆን ሁለተኛ “ኢሥባት” ነው፦
“ነፍይ” نفي ማለት “አፍራሽ” ሲሆን አሉታዊ ቃል ነው፤ ይህም አሉታዊ ቃል፦ “ላ ኢላሃ” لَا إِلَٰهَ ማለትም “ሌላ አምላክ የለም” ብለን ስንል ማንኛውንም ጣኦታት ውድቅ የምናደርግበት ነው፤ በቁርአን ከአላህ ውጪ የሚደረግ ባዕድ አምልኮ “ጣጉት” لطَّاغُوتِ ይባላል።
“ኢሥባት” إثبات ማለት ደግሞ “ማፅደቅ” ሲሆን አውንታዊ ቃል ነው፤ ይህም አውንታዊ ቃል፦ “ኢለ ሏህ” إِلَّا اللَّهُ ማለትም “ከአላህ በቀር” ብለን ስንል አንዱን አምላክ በብቸኝነትና በእውነት ልናመልከው የምናፀድቅበት ነው፤ በእርግጥም በጣዖትም የሚክድና በአላህ የሚያምን ሰው ለእርሷ መበጠስ የሌላትን *ጠንካራ ዘለበት* በእርግጥ ጨበጠ፦
2፥256 በሃይማኖት ማስገደድ የለም፡፡ ቅኑ መንገድ ከጠማማው በእርግጥ ተገለጠ፡፡ በጣዖትም የሚክድና በአላህ የሚያምን ሰው ለርሷ መበጠስ የሌላትን *ጠንካራ ዘለበት* በእርግጥ ጨበጠ፡፡ አላህም ሰሚ ዐዋቂ ነው፡፡ لَا إِكْرَاهَ فِي الدِّينِ ۖ قَد تَّبَيَّنَ الرُّشْدُ مِنَ الْغَيِّ ۚ فَمَن يَكْفُرْ بِالطَّاغُوتِ وَيُؤْمِن بِاللَّهِ فَقَدِ اسْتَمْسَكَ بِالْعُرْوَةِ الْوُثْقَىٰ لَا انفِصَامَ لَهَا ۗ وَاللَّهُ سَمِيعٌ عَلِيمٌ
ይህንን ጠንካራ ዘለበት የምንጨብጠው ሁለንተናን ለአላህ በመስጠት ነው፦
31፥22 እርሱ መልካም ሠሪ ሆኖ ፊቱን ወደ አላህ የሚሰጥም ሰው *ጠንካራን ዘለበት* በእርግጥ ጨበጠ፡፡ የነገሩም ሁሉ ፍጻሜ ወደ አላህ ነው፡፡ وَمَن يُسْلِمْ وَجْهَهُ إِلَى اللَّهِ وَهُوَ مُحْسِنٌ فَقَدِ اسْتَمْسَكَ بِالْعُرْوَةِ الْوُثْقَىٰ ۗ وَإِلَى اللَّهِ عَاقِبَةُ الْأُمُورِ
“ፊት” ተብሎ የተቀመጠው ቃል “ወጅህ” وَجْه ሲሆን “ሁለንተና” ማለት ነው፦
3፥20 ቢከራከሩህም፦ *«ፊቴን ለአላህ ሰጠሁ*፤ የተከተሉኝም ሰዎች እንደዚሁ ለአላህ ሰጡ» በላቸው፡፡ فَإِنْ حَاجُّوكَ فَقُلْ أَسْلَمْتُ وَجْهِيَ لِلَّهِ وَمَنِ اتَّبَعَن
6፥79 «እኔ ለዚያ ሰማያትንና ምድርን *ለፈጠረው አምላክ ቀጥተኛ ስኾን ፊቴን አዞርኩ*፡፡ እኔም ከአጋሪዎቹ አይደለሁም» አለ። إِنِّي وَجَّهْتُ وَجْهِيَ لِلَّذِي فَطَرَ السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضَ حَنِيفًا ۖ وَمَا أَنَا مِنَ الْمُشْرِكِينَ
4፥125 እርሱ መልካም ሠሪ ኾኖ *ፊቱን ለአላህ ከሰጠ* እና የኢብራሂምንም መንገድ ቀጥተኛ ሲኾን ከተከተለ ሰው ይበልጥ ሃይማኖቱ ያማረ ማን ነው? አላህም ኢብራሂምን ፍጹም ወዳጅ አድርጐ ያዘው፡፡ وَمَنْ أَحْسَنُ دِينًا مِّمَّنْ أَسْلَمَ وَجْهَهُ لِلَّهِ وَهُوَ مُحْسِنٌ وَاتَّبَعَ مِلَّةَ إِبْرَاهِيمَ حَنِيفًا ۗ وَاتَّخَذَ اللَّهُ إِبْرَاهِيمَ خَلِيلًا
“ሰጠሁ” ተብሎ የተቀመጠበት ቃል “አስለምቱ” أَسْلَمْتُ ሲሆን “ታዘዝኩ” ማለት ነው፤ “ሰጠ” ተብሎ የተቀመጠበት ደግሞ “አስለመ” أَسْلَمَ ሲሆን “ታዘዘ” ማለት ነው፤ “ኢሥላም” إِسْلَٰم የሚለው ቃል “አሥለመ” أَسْلَمَ “ታዘዘ” “ተገዛ” ” አመለከ” ከሚል ግስ የመጣ ሲሆን ትርጉሙ “መታዘዝ” “መገዛት” “ማምለክ” ማለት ነው፤ አላህ ለኢብራሂም “አስሊም” أَسْلِمْ ማለትም “ታዘዝ” ብሎ ሲለው እርሱም ለዓለማት ጌታ “አስለምቱ” أَسْلَمْتُ ማለትም “ታዘዝኩ” አለ፤ አንድ ሁለንተናውን ለአላህ የሰጠ “ሙስሊም” مُسْلِم ማለትም “አምላኪ” “ተገዢ” “ታዛዥ” ይባላል፦
2፥131 ጌታው ለእርሱ *”ታዘዝ”* ባለው ጊዜ መረጠው፡፡ ለዓለማት ጌታ *”ታዘዝኩ”* አለ፡፡ إِذْ قَالَ لَهُۥ رَبُّهُۥٓ أَسْلِمْ ۖ قَالَ أَسْلَمْتُ لِرَبِّ ٱلْعَٰلَمِينَ
2፥139 እኛም *ለእርሱ ፍጹም ታዛዦች* ስንኾን “በአላህ ሃይማኖት” ትከራከሩናላችሁን? በላቸው፡፡ قُلْ أَتُحَآجُّونَنَا فِى ٱللَّهِ وَهُوَ رَبُّنَا وَرَبُّكُمْ وَلَنَآ أَعْمَٰلُنَا وَلَكُمْ أَعْمَٰلُكُمْ وَنَحْنُ لَهُۥ مُخْلِصُونَ
“ታዛዦች” ተብሎ የተቀመጠው ቃል “ሙስሊሙን” مُسْلِمُونَ ሲሆን “ሙስሊም” مُسْلِم ለሚለው ብዙ ቁጥር ነው፤ በእርግጥም ሁለመናውን ለአላህ የሰጠ ሰው ለእርሱ በጌታው ዘንድ ምንዳው አለው፡፤ በእርሱም ላይ ፍርሃት የለበትም፤ እርሱም አያዝንም፦
2፥112 አይደለም እርሱ በጎ ሠሪ ኾኖ *ፊቱን ለአላህ የሰጠ* ሰው ለእርሱ በጌታው ዘንድ ምንዳ አለው፡፡ በእነሱም ላይ ፍርሃት የለባቸውም፤ እነሱም አያዝኑም፡፡ بَلَىٰ مَنْ أَسْلَمَ وَجْهَهُ لِلَّهِ وَهُوَ مُحْسِنٌ فَلَهُ أَجْرُهُ عِندَ رَبِّهِ وَلَا خَوْفٌ عَلَيْهِمْ وَلَا هُمْ يَحْزَنُونَ
“ዲን” دِين ማለት ደግሞ “ሃይማኖት” “ፍትህ” “ፍርድ” “ሕግ” “መርህ” ማለት ነው፤ “ዲን” ደግሞ ሦስት ደረጃ አሉት፦ “ኢሥላም” إِسْلَٰم ፣ “ኢማን” إِيمَٰن እና “ኢሕሣን” إِحْسَٰن ናቸው፤ “ኢሥላም” ማለት “አንዱን አምላክ ብቻ ማምለክ” ሲሆን “ኢማን” ማለት ግን “እምነት” ማለት ነው፤ “ኢሕሣን” ማለት “አላህን እንደምታየው አርገህ ማምለክ፤ አሊያም አላህ እንደሚያይህ አርገህ ማምለክ ነው”፤ ሃይማኖትን ለአላህ ብቻ ያጠራን ኾነን ስናመልከው ይህ ጠንካራ ዘለበት ነው፦
39፥11 በል *«እኔ አላህን ሃይማኖትን ለእርሱ ያጠራሁ ኾኜ እንዳመልከው ታዘዝኩ፡፡ قُلْ إِنِّي أُمِرْتُ أَنْ أَعْبُدَ اللَّهَ مُخْلِصًا لَّهُ الدِّينَ
39፥2 እኛ ወደ አንተ መጽሐፉን በእውነት የተመላ ሲኾን አወረድነው፡፡ አላህንም *ሃይማኖትን ለእርሱ ብቻ ያጠራህ ኾነህ አምልከው*፡፡ إِنَّا أَنزَلْنَا إِلَيْكَ الْكِتَابَ بِالْحَقِّ فَاعْبُدِ اللَّهَ مُخْلِصًا لَّهُ الدِّينَ
40፥65 እርሱ ብቻ ሁል ጊዜ ሕያው ነው፤ ከእርሱ ሌላ አምላክ የለም፤ *ሃይማኖትንም ለእርሱ ያጠራችሁ ስትኾኑ* «ምስጋና ለዓለማት ጌታ ለአላህ ይኹን» የምትሉ ኾናችሁ አምልኩት፡፡ هُوَ الْحَيُّ لَا إِلَـٰهَ إِلَّا هُوَ فَادْعُوهُ مُخْلِصِينَ لَهُ الدِّينَ ۗ الْحَمْدُ لِلَّهِ رَبِّ الْعَالَمِينَ
7፥29 ጌታዬ በማስተካከል አዘዘ፤ በየመስጊዱም ዘንድ ፊቶቻችሁን እርሱን ለመገዛት አስተካክሉ፤ *ሃይማኖትንም ለእርሱ ፍጹም አድርጋችሁ አምልኩት*፡፡ እንደጀመራችሁ ትመለሳላችሁ» በላቸው፡፡ قُلْ أَمَرَ رَبِّي بِالْقِسْطِ ۖ وَأَقِيمُوا وُجُوهَكُمْ عِندَ كُلِّ مَسْجِدٍ وَادْعُوهُ مُخْلِصِينَ لَهُ الدِّينَ ۚ كَمَا بَدَأَكُمْ تَعُودُونَ
✍ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሰላሙ አለይኩም
39፥11 በል *«እኔ አላህን ሃይማኖትን ለእርሱ ያጠራሁ ኾኜ እንዳመልከው ታዘዝኩ፡፡ قُلْ إِنِّي أُمِرْتُ أَنْ أَعْبُدَ اللَّهَ مُخْلِصًا لَّهُ الدِّينَ
39፥2 እኛ ወደ አንተ መጽሐፉን በእውነት የተመላ ሲኾን አወረድነው፡፡ አላህንም *ሃይማኖትን ለእርሱ ብቻ ያጠራህ ኾነህ አምልከው*፡፡ إِنَّا أَنزَلْنَا إِلَيْكَ الْكِتَابَ بِالْحَقِّ فَاعْبُدِ اللَّهَ مُخْلِصًا لَّهُ الدِّينَ
40፥65 እርሱ ብቻ ሁል ጊዜ ሕያው ነው፤ ከእርሱ ሌላ አምላክ የለም፤ *ሃይማኖትንም ለእርሱ ያጠራችሁ ስትኾኑ* «ምስጋና ለዓለማት ጌታ ለአላህ ይኹን» የምትሉ ኾናችሁ አምልኩት፡፡ هُوَ الْحَيُّ لَا إِلَـٰهَ إِلَّا هُوَ فَادْعُوهُ مُخْلِصِينَ لَهُ الدِّينَ ۗ الْحَمْدُ لِلَّهِ رَبِّ الْعَالَمِينَ
7፥29 ጌታዬ በማስተካከል አዘዘ፤ በየመስጊዱም ዘንድ ፊቶቻችሁን እርሱን ለመገዛት አስተካክሉ፤ *ሃይማኖትንም ለእርሱ ፍጹም አድርጋችሁ አምልኩት*፡፡ እንደጀመራችሁ ትመለሳላችሁ» በላቸው፡፡ قُلْ أَمَرَ رَبِّي بِالْقِسْطِ ۖ وَأَقِيمُوا وُجُوهَكُمْ عِندَ كُلِّ مَسْجِدٍ وَادْعُوهُ مُخْلِصِينَ لَهُ الدِّينَ ۚ كَمَا بَدَأَكُمْ تَعُودُونَ
✍ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሰላሙ አለይኩም
Telegram
ወሒድ የዕቅበተ ኢሥላም መጣጥፍት"Wahid Articles of Islamic Apologetics"
ዳዒ ወሒድ በኢሥላም እና በክርስትና መካከል ያለውን ልዩነት እና አንድነት በንጽጽር የሚያስቀምጥ ወንድም ነው። ለዚህም የቋንቋ፣ የሰዋስው፣ የዐውድ፣ የተዛማች እና የሥነ አመክንዮ ሙግት በማቅረብ የሚታወቅ ተሟጋች እና ጦማሪ ነው። ለሙግቱ ነጥብ በዋነኝነት የሚጠቀምባቸው ቋንቋ ዐማርኛ፣ ግዕዝ፣ እንግሊዝኛ፣ ዐረቢኛ፣ ዕብራይስጥ እና ግሪክ ናቸው። መልካም የንባብ፣ የጥናት፣ የማነጻጸር ጊዜ ይሁንልዎ!
መሸወድ እስከመቸ.pdf
4.2 MB
መሸወድ እስከ መቼ!?
በተለያዩ ጊዜያት ሙስሊም ባልሆኑ ወገኖቻችን ለተጠየቁ ጥያቄዎች መልስ የያዘ pdf
https://tttttt.me/Wahidcom
https://tttttt.me/Wahidcom
በተለያዩ ጊዜያት ሙስሊም ባልሆኑ ወገኖቻችን ለተጠየቁ ጥያቄዎች መልስ የያዘ pdf
https://tttttt.me/Wahidcom
https://tttttt.me/Wahidcom
አካል እና መንፈስ
ክፍል አንድ
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
መግቢያ
በማህበራዊ ሚድያ ላይ፦ አላህ ምንድን ነው? አካል ወይስ መንፈስ የሚል አለሌ እና ቅሪላ ጥያቄ ይጠየቃል፤ ለዚህ አንኮላ እና እንኩቶ ቃላት መልሳችን አላህ ምንድን ነው? ብለን ስንጠየቅ ህላዌን ታሳቢ እና ዋቢ ያደረገ ነው፤ “ዛት” ذات ማለት “ህላዌ”essence” ማለት ሲሆን “ምንድን” ተብሎ በመጠይቅ ተውላጠ-ስም የሚቀመጥ “ክዋኔ-ምንነት” ሲሆን የቅዋሜ-ማንነት መሰረት ነው።
በስነ-ኑባሬ ጥናት”ontology” ውስጥ “ኢስም” ٱسْم ማለትም “ስም” ባህርይ የተሰየመበት መጠሪያ ሲሆን “ሲፋ” صِفَة ማለትም “ባህርይ” ደግሞ የህላዌ መግለጫ“description” ነው፣ አላህ ምንድን ነው? ለሚለው የህላዌ ጥያቄ መልሱን የምናገኘው በባህርይ ነው፣ አላህ ምንድን ነው ለሚለው ጥያቄ የህላዌ መገለጫ የሆኑትን ባህርያት እራሱ አላህ በተከበረው ከሊማ ይነግረናል፤ አሏህ ﺍﻟﻠﻪ ማለት፦ አር- ረህማን ﺍﻟﺮﺣﻤﻦ ነው፣ አር-ረሂም ﺍﻟﺮﺣﻴﻢ ነው፣ አል-ሙልክ ﺍﻟﻤﻠﻚ ነው፣ አል-ቅዱስ ﺍﻟﻘﺪﻭﺱ ነው፣ አስ-ሰላም ﺍﻟﺴﻼﻡ ነው፣ አል-ኻሊቅ ﺍﻟﺨﺎﻟﻖ ነው፣ አል-ዓሊም ﺍﻟﻌﻠﻴﻢ ነው እያልን ባህርያት የተሰየሙበትን መልካም ስሞቹን እንዘረዝራለን፤ አላህ ከፍጡራኑ ጋር የማይመሳሰል “አስማኡል ሁስና” الْأَسْمَاءُ الْحُسْنَىٰ ማለትም “መልካም ስሞች” አሉት፦
59:24 እርሱ አላህ ፈጣሪው ከኢምንት አስገኚው ቅርጽን አሳማሪው ነው፤ ለእርሱ “መልካም ስሞች” الْأَسْمَاءُ الْحُسْنَىٰ አሉት፤
20:8 አላህ ከእርሱ ሌላ አምላክ የለም ለእርሱ “መልካም የሆኑ ስሞች” الْأَسْمَاءُ الْحُسْنَىٰ አሉት።
17:110 ፦አላህን ጥሩ፤ ወይም አልረሕማንን ጥሩ፤ ማንኛውንም ብትጠሩ፣ መልካም ነው፤ ለእርሱ “መልካም ስሞች” الْأَسْمَاءُ الْحُسْنَىٰ አሉትና በላቸው፤
7:180 ለአላህም “መልካም ስሞች” الْأَسْمَاءُ الْحُسْنَىٰ አሉት፤ ስትጸልዩ በርሷም ጥሩት እነዚያንም ስሞቹን የሚያጣምሙትን ተውዋቸው፤
ከላይ ለቀረበው የሽሙጥና የለበጣ ጥያቄ ይህ ምላሽ በቂ ቢሆንም ሞኝ የያዘው ፈሊጥ ውሻ የደፋው ሊጥ ይባላልና አላህ አካል እና መንፈስ ነውን? ተብሎ ለተጠየቀው ቅጥ አንባሩ ለጠፋበት ጥያቄ አካል እና መንፈስ ምን እንደሆኑ ነጥብ በነጥብ ቅድሚያ እናያለን፦
ነጥብ አንድ
“አካል”
“ጀሰድ” جَسَد”የሚለው ቃል “አካል”body” ማለት ሲሆን ፈሳሽ”liquid”፣ ጠጣር”solid” እና ጋዝ”gas” ነው፤ ይህም ግዙፍ ነገር ነው፤ አለቃ ኪዳነ-ወልድ ክፍሌ 1948 መጽሐፈ ሰዋስው ወግስ ወመዝገበ ቃላት ላይ፦ “አካል” ማለት አፍአዊ ወይም ውጫዊ ትርጉሙ ጀማትና አጥንትን የያዘ ተክለ-ሰውነት ወይም ገላ አሊያም ግዝፈተ-ስጋ”body” ማለት ነው፤ ይህንን ሃሳብ ደስታ ተክለ-ወልድ መዝገበ ቃላት ሆነ ከሳቴ-ብርሃን ተሰማ መዝገበ ቃላት ተመሳሳይ ፍቺ አስቀምጠዋል፤ “ጀሰድ” የሚለው ቃል በቁርአን ውስጥ 4 ጊዜ ተጠቅሷል፤ ይህም ቃል በሁለት ይከፈላል፦
አንደኛው ህያው አካል ነው፤ ህያው አካል ማለት ሩህ ያለው ማለት ሲሆን የሚበላ እና የሚጠጣ ነው፦
21፥8 ምግብን የማይበሉ “አካልም” አላደረግናቸውም፡፡ ዘውታሪዎችም አልነበሩም وَمَا جَعَلْنَٰهُمْ جَسَدًۭا لَّا يَأْكُلُونَ ٱلطَّعَامَ وَمَا كَانُوا۟ خَٰلِدِينَ ፡፡
ሁለተኛው ደግሞ ግኡዝ አካል ነው፤ ግኡዝ አካል ማለት ሩህ የሌለው ማለት ነው፦
7፥148 የሙሳም ሕዝቦች ከእርሱ መኼድ በኋላ ከጌጦቻቸው ወይፈንን “”አካልን”” ለእርሱ ማግሳት ያለውን ያዙ፡፡ እርሱ የማያናግራቸው መንገድንም የማይመራቸው መኾኑን አይመለከቱምን? አምላክ አድርገው ያዙት፡፡ በዳዮችም ኾኑ وَٱتَّخَذَ قَوْمُ مُوسَىٰ مِنۢ بَعْدِهِۦ مِنْ حُلِيِّهِمْ عِجْلًۭا جَسَدًۭا لَّهُۥ خُوَارٌ ۚ أَلَمْ يَرَوْا۟ أَنَّهُۥ لَا يُكَلِّمُهُمْ وَلَا يَهْدِيهِمْ سَبِيلًا ۘ ٱتَّخَذُوهُ وَكَانُوا۟ ظَٰلِمِينَ ፡፡
20፥88 ለእነሱም “”አካል”” የኾነ ጥጃን ለእርሱ መጓጎር ያለውን አወጣላቸው፡፡ ተከታዮቹ «ይህ አምላካችሁ የሙሳም አምላክ ነው ግን ረሳው» አሉም فَأَخْرَجَ لَهُمْ عِجْلًۭا جَسَدًۭا لَّهُۥ خُوَارٌۭ فَقَالُوا۟ هَٰذَآ إِلَٰهُكُمْ وَإِلَٰهُ مُوسَىٰ فَنَسِىَ ፡፡
38፥34 ሱለይማንንም በእርግጥ ፈተንነው፡፡ በመንበሩም ላይ “አካልን” ጣልን፡፡ ከዚያም በመጸጸት ተመለሰ وَلَقَدْ فَتَنَّا سُلَيْمَٰنَ وَأَلْقَيْنَا عَلَىٰ كُرْسِيِّهِۦ جَسَدًۭا ثُمَّ أَنَابَ ፡፡
ስለዚህ በኢስላም አላህ ህያው ወይም ግኡዝ አካል የለውም፤ “አካል” ፍጡር ነውና። ወደ ባይብል ስንመጣ በብሉይ ግሪክ ሰፕቱጀንት እና በአዲስ ግሪክ ኮይኔ ውስጥ “ሶማ” σῶμα ማለት “አካል” ማለት ሲሆን ሌንስ የያዘ አይን፣ ሃመር የያዘ ጆሮ፣ እግር ወዘተ የያዘው የብልት ጥርቅም እንደሆነ ያስቀምጣል፦
1ኛ ቆሮንቶስ 12፥14-16 “አካል” ብዙ ብልቶች እንጂ አንድ ብልት አይደለምና። እግር። እኔ እጅ አይደለሁምና የአካል ክፍል አይደለሁም ብትል፥ ይህን በማለትዋ የአካል ክፍል መሆንዋ ይቀራልን? ጆሮም። እኔ ዓይን አይደለሁምና የአካል ክፍል አይደለሁም ቢል፥ ይህን በማለቱ የአካል ክፍል መሆኑ ይቀራልን? አካል ሁሉ ዓይን ቢሆን መስማት ወዴት በተገኘ? ሁሉም መስማት ቢሆን ማሽተት ወዴት በተገኘ?።
ዘሌዋውያን 21፥18 ዕውር፥ ወይም አንካሳ፥ ወይም አፍንጫ ደፍጣጣ፥ ወይም ትርፍ “አካል” ያለው፥
ዘዳግም 14፥1-2 ስለ ሞተው ሰው “አካላችሁን” አትንጩ፥
መዝሙር 139፥15-136 እኔ በስውር በተሠራሁ ጊዜ፥ “አካሌም” በምድር ታች በተሠራ ጊዜ፥ አጥንቶቼ ከአንተ አልተሰወሩም። ያልተሠራ “አካሌን” ዓይኖችህ አዩኝ፤ የተፈጠሩ ቀኖቼ ሁሉ አንድ ስንኳ ሳይኖር በመጽሐፍህ ተጻፉ።
ክፍል አንድ
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
መግቢያ
በማህበራዊ ሚድያ ላይ፦ አላህ ምንድን ነው? አካል ወይስ መንፈስ የሚል አለሌ እና ቅሪላ ጥያቄ ይጠየቃል፤ ለዚህ አንኮላ እና እንኩቶ ቃላት መልሳችን አላህ ምንድን ነው? ብለን ስንጠየቅ ህላዌን ታሳቢ እና ዋቢ ያደረገ ነው፤ “ዛት” ذات ማለት “ህላዌ”essence” ማለት ሲሆን “ምንድን” ተብሎ በመጠይቅ ተውላጠ-ስም የሚቀመጥ “ክዋኔ-ምንነት” ሲሆን የቅዋሜ-ማንነት መሰረት ነው።
በስነ-ኑባሬ ጥናት”ontology” ውስጥ “ኢስም” ٱسْم ማለትም “ስም” ባህርይ የተሰየመበት መጠሪያ ሲሆን “ሲፋ” صِفَة ማለትም “ባህርይ” ደግሞ የህላዌ መግለጫ“description” ነው፣ አላህ ምንድን ነው? ለሚለው የህላዌ ጥያቄ መልሱን የምናገኘው በባህርይ ነው፣ አላህ ምንድን ነው ለሚለው ጥያቄ የህላዌ መገለጫ የሆኑትን ባህርያት እራሱ አላህ በተከበረው ከሊማ ይነግረናል፤ አሏህ ﺍﻟﻠﻪ ማለት፦ አር- ረህማን ﺍﻟﺮﺣﻤﻦ ነው፣ አር-ረሂም ﺍﻟﺮﺣﻴﻢ ነው፣ አል-ሙልክ ﺍﻟﻤﻠﻚ ነው፣ አል-ቅዱስ ﺍﻟﻘﺪﻭﺱ ነው፣ አስ-ሰላም ﺍﻟﺴﻼﻡ ነው፣ አል-ኻሊቅ ﺍﻟﺨﺎﻟﻖ ነው፣ አል-ዓሊም ﺍﻟﻌﻠﻴﻢ ነው እያልን ባህርያት የተሰየሙበትን መልካም ስሞቹን እንዘረዝራለን፤ አላህ ከፍጡራኑ ጋር የማይመሳሰል “አስማኡል ሁስና” الْأَسْمَاءُ الْحُسْنَىٰ ማለትም “መልካም ስሞች” አሉት፦
59:24 እርሱ አላህ ፈጣሪው ከኢምንት አስገኚው ቅርጽን አሳማሪው ነው፤ ለእርሱ “መልካም ስሞች” الْأَسْمَاءُ الْحُسْنَىٰ አሉት፤
20:8 አላህ ከእርሱ ሌላ አምላክ የለም ለእርሱ “መልካም የሆኑ ስሞች” الْأَسْمَاءُ الْحُسْنَىٰ አሉት።
17:110 ፦አላህን ጥሩ፤ ወይም አልረሕማንን ጥሩ፤ ማንኛውንም ብትጠሩ፣ መልካም ነው፤ ለእርሱ “መልካም ስሞች” الْأَسْمَاءُ الْحُسْنَىٰ አሉትና በላቸው፤
7:180 ለአላህም “መልካም ስሞች” الْأَسْمَاءُ الْحُسْنَىٰ አሉት፤ ስትጸልዩ በርሷም ጥሩት እነዚያንም ስሞቹን የሚያጣምሙትን ተውዋቸው፤
ከላይ ለቀረበው የሽሙጥና የለበጣ ጥያቄ ይህ ምላሽ በቂ ቢሆንም ሞኝ የያዘው ፈሊጥ ውሻ የደፋው ሊጥ ይባላልና አላህ አካል እና መንፈስ ነውን? ተብሎ ለተጠየቀው ቅጥ አንባሩ ለጠፋበት ጥያቄ አካል እና መንፈስ ምን እንደሆኑ ነጥብ በነጥብ ቅድሚያ እናያለን፦
ነጥብ አንድ
“አካል”
“ጀሰድ” جَسَد”የሚለው ቃል “አካል”body” ማለት ሲሆን ፈሳሽ”liquid”፣ ጠጣር”solid” እና ጋዝ”gas” ነው፤ ይህም ግዙፍ ነገር ነው፤ አለቃ ኪዳነ-ወልድ ክፍሌ 1948 መጽሐፈ ሰዋስው ወግስ ወመዝገበ ቃላት ላይ፦ “አካል” ማለት አፍአዊ ወይም ውጫዊ ትርጉሙ ጀማትና አጥንትን የያዘ ተክለ-ሰውነት ወይም ገላ አሊያም ግዝፈተ-ስጋ”body” ማለት ነው፤ ይህንን ሃሳብ ደስታ ተክለ-ወልድ መዝገበ ቃላት ሆነ ከሳቴ-ብርሃን ተሰማ መዝገበ ቃላት ተመሳሳይ ፍቺ አስቀምጠዋል፤ “ጀሰድ” የሚለው ቃል በቁርአን ውስጥ 4 ጊዜ ተጠቅሷል፤ ይህም ቃል በሁለት ይከፈላል፦
አንደኛው ህያው አካል ነው፤ ህያው አካል ማለት ሩህ ያለው ማለት ሲሆን የሚበላ እና የሚጠጣ ነው፦
21፥8 ምግብን የማይበሉ “አካልም” አላደረግናቸውም፡፡ ዘውታሪዎችም አልነበሩም وَمَا جَعَلْنَٰهُمْ جَسَدًۭا لَّا يَأْكُلُونَ ٱلطَّعَامَ وَمَا كَانُوا۟ خَٰلِدِينَ ፡፡
ሁለተኛው ደግሞ ግኡዝ አካል ነው፤ ግኡዝ አካል ማለት ሩህ የሌለው ማለት ነው፦
7፥148 የሙሳም ሕዝቦች ከእርሱ መኼድ በኋላ ከጌጦቻቸው ወይፈንን “”አካልን”” ለእርሱ ማግሳት ያለውን ያዙ፡፡ እርሱ የማያናግራቸው መንገድንም የማይመራቸው መኾኑን አይመለከቱምን? አምላክ አድርገው ያዙት፡፡ በዳዮችም ኾኑ وَٱتَّخَذَ قَوْمُ مُوسَىٰ مِنۢ بَعْدِهِۦ مِنْ حُلِيِّهِمْ عِجْلًۭا جَسَدًۭا لَّهُۥ خُوَارٌ ۚ أَلَمْ يَرَوْا۟ أَنَّهُۥ لَا يُكَلِّمُهُمْ وَلَا يَهْدِيهِمْ سَبِيلًا ۘ ٱتَّخَذُوهُ وَكَانُوا۟ ظَٰلِمِينَ ፡፡
20፥88 ለእነሱም “”አካል”” የኾነ ጥጃን ለእርሱ መጓጎር ያለውን አወጣላቸው፡፡ ተከታዮቹ «ይህ አምላካችሁ የሙሳም አምላክ ነው ግን ረሳው» አሉም فَأَخْرَجَ لَهُمْ عِجْلًۭا جَسَدًۭا لَّهُۥ خُوَارٌۭ فَقَالُوا۟ هَٰذَآ إِلَٰهُكُمْ وَإِلَٰهُ مُوسَىٰ فَنَسِىَ ፡፡
38፥34 ሱለይማንንም በእርግጥ ፈተንነው፡፡ በመንበሩም ላይ “አካልን” ጣልን፡፡ ከዚያም በመጸጸት ተመለሰ وَلَقَدْ فَتَنَّا سُلَيْمَٰنَ وَأَلْقَيْنَا عَلَىٰ كُرْسِيِّهِۦ جَسَدًۭا ثُمَّ أَنَابَ ፡፡
ስለዚህ በኢስላም አላህ ህያው ወይም ግኡዝ አካል የለውም፤ “አካል” ፍጡር ነውና። ወደ ባይብል ስንመጣ በብሉይ ግሪክ ሰፕቱጀንት እና በአዲስ ግሪክ ኮይኔ ውስጥ “ሶማ” σῶμα ማለት “አካል” ማለት ሲሆን ሌንስ የያዘ አይን፣ ሃመር የያዘ ጆሮ፣ እግር ወዘተ የያዘው የብልት ጥርቅም እንደሆነ ያስቀምጣል፦
1ኛ ቆሮንቶስ 12፥14-16 “አካል” ብዙ ብልቶች እንጂ አንድ ብልት አይደለምና። እግር። እኔ እጅ አይደለሁምና የአካል ክፍል አይደለሁም ብትል፥ ይህን በማለትዋ የአካል ክፍል መሆንዋ ይቀራልን? ጆሮም። እኔ ዓይን አይደለሁምና የአካል ክፍል አይደለሁም ቢል፥ ይህን በማለቱ የአካል ክፍል መሆኑ ይቀራልን? አካል ሁሉ ዓይን ቢሆን መስማት ወዴት በተገኘ? ሁሉም መስማት ቢሆን ማሽተት ወዴት በተገኘ?።
ዘሌዋውያን 21፥18 ዕውር፥ ወይም አንካሳ፥ ወይም አፍንጫ ደፍጣጣ፥ ወይም ትርፍ “አካል” ያለው፥
ዘዳግም 14፥1-2 ስለ ሞተው ሰው “አካላችሁን” አትንጩ፥
መዝሙር 139፥15-136 እኔ በስውር በተሠራሁ ጊዜ፥ “አካሌም” በምድር ታች በተሠራ ጊዜ፥ አጥንቶቼ ከአንተ አልተሰወሩም። ያልተሠራ “አካሌን” ዓይኖችህ አዩኝ፤ የተፈጠሩ ቀኖቼ ሁሉ አንድ ስንኳ ሳይኖር በመጽሐፍህ ተጻፉ።
የሚገርመው የባይብል አምላክ መንፈስ ነው እየተባለ ይዶስኮርለት እንጂ አካል የያዘውን ላባና ክንፍ፣ ከንፈርና ምላስ፣ ዓይንና ቅንድብ፣ አፍንጫና አፍ እና እግር ከነጫማው እንዳለው ተቀምጧል።
ላባና ክንፍ፦
መዝሙር 91፥4 *በላባዎቹ ይጋርድሃል፥ በክንፎቹም* በታች ትተማመናለህ
ከንፈርና ምላስ፦
ኢሳይያስ 30፥27 እነሆ፥ የእግዚአብሔር ስም ከሚነድድ ቍጣ ከሚትጐለጐልም ጢስ ጋር ከሩቅ ይመጣል፤ *ከንፈሮቹም* ቍጣን የሞሉ ናቸው፥ *ምላሱም* እንደምትበላ እሳት ናት፤
ዓይንና ቅንድብ፦
መዝሙር 11፥4 እግዚአብሔር በተቀደሰው መቅደሱ ነው፤ እግዚአብሔር፥ ዙፋኑ በሰማይ ነው፤ “ዓይኖቹ” ወደ ድሃ ይመለከታሉ፥ *ቅንድቦቹም* የሰው ልጆችን ይመረምራሉ።
አፍንጫና አፍ፦
ዘጸአት 15፥8 *በአፍንጫህ* እስትንፋስ ውኆች ተከመሩ፥
መዝሙር 33:6 በእግዚአብሔር ቃል ሰማዮች ጸኑ፥ ሠራዊታቸውም ሁሉ *”በአፉ”* እስትንፋስ፤”
ክንድና ብብት፦
ኢሳይያስ 40፥11 መንጋውን እንደ እረኛ ያሰማራል፥ ጠቦቶቹን *በክንዱ ሰብስቦ በብብቱ* ይሸከማል፥ የሚያጠቡትንም በቀስታ ይመራል።
እግርና ጫማ፦
ሕዝቅኤል 43:7 እንዲህም አለኝ። የሰው ልጅ ሆይ፥ በእስራኤል ልጆች መካከል ለዘላለም የምቀመጥበት የዙፋኔ ስፍራና “የእግሬ ጫማ” መረገጫ ይህ ነው።
መንፈስ ማለት የማይታይ ነው ከተባለ የእስራኤል አምላክን ሰዎች አይተውታል ይለናል፦
ዘጸአት 24:10 የእስራኤልንም አምላክ “”አዩ””፤ “ከእግሩም” በታች እንደ ሰማይ መልክ የሚያበራ እንደ ብሩህ ሰንፔር ድንጋይ የሚመስል ወለል ነበረ።
አይን፣ እጅ፣ እግር፣ ጆሮ ስጋዊ ሳይሆን መለኮታዊ ነው ይሉናል፦
ኢዮብ 10፥4 በውኑ የሥጋ ዓይን አለህን?
ወይስ ሰው እንደሚያይ ታያለህን?
አየህ አይን፣ እጅ፣ እግር፣ ጆሮ ስጋዊ ሳይሆን መለኮታዊ ከሆነ ፈጣሪ አፍአዊ ወይም ውጫዊ ትርጉሙ ያለው ጀማትና አጥንትን የያዘ ተክለ-ሰውነት ወይም ገላ አሊያም ግዝፈተ-ስጋ”body” የለውም ማለት ነው። ነገር ግን ውሳጣዊ ወይም ውስጣዊ ትርጉም ቅዋሜ-ማንነት እገሌ ተብሎ በእኔነት፣ “በአንተነት”፣ “በእርሱነት” የሚገለጥ ነባቢ ባለቤት”person” ብሎ አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ አሌፍ 218 ገፅ 218 ላይ እና በተመሳሳይ አለቃ ደስታ ተክለ ወልድ አሌፍ 97 ገፅ 97 ላይ ያስቀመጠውን ነባቢ ማንነት ፈጣሪ አለው፤ ፍፁም ገፅ ማለትም መታወቂያ”identity” ፍፁም መልክ ማለትም መለያ ወይም መገለጫ”intity” አለው። ይህ በኢስላም “ሸኽስ” شخص ይባላል፤ “ሸኽስ” ዛትን “በእኔነት” ወይም “በማንነት” የሚገልጥ ሲሆን “ማን” ተብሎ በመጠይቅ ተውላጠ-ስም የሚቀመጥ “ቅዋሜ-ማንነት” አለው፤ “ሸኽስ” የሚለውን ቃል በግሪክ “ፕሮሶፓን” πρόσωπον ሲሆን ፐርሰን”person” የሚለው የኢንግሊሹ ቃል እና ፐርሶና የሚለው የላቲኑ ቃል ከግሪኩ ፕሮሶፓን የመጣ ሲሆን “ቅዋሜ-ማንነት” ማለት ነው፤ ይህንን ቃል በአማርኛ ቃል ሲጠፋለት አለቃ ኪዳነ-ወልድ ክፍሌ መዝገበ ቃላት፣ ደስታ ተክለ-ወልድ መዝገበ ቃላት ሆነ ከሳቴ-ብርሃን ተሰማ መዝገበ ቃላት “አካል” ብለውታል፤።
“ሸኽስ” የሚለው ቃል “አሐድ” ለሚለው ቃል ተለዋዋጭ ነው፤ “አሐድ” أَحَد የሚለው ቃል “ላ “አሐደ” አግየሩ ሚነልላህ” لاَ أَحَدَ أَغْيَرُ مِنَ اللَّهِ ተብሎ በኢማም ቡኻሪይ ላይ ሲዘገብ “ሸኽስ” شخص ደግሞ “ወላ “ሸኽሰ” አግየሩ ሚነልላህ” وَلاَ شَخْصَ أَغْيَرُ مِنَ اللَّهِ ተብሎ በኢማም ሙስሊም ላይ በተመሳሳይ ሰዋስው ተዘግቧል፦
ኢማም ቡኻሪይ መፅሐፍ 65, ሐዲስ 4637
لاَ أَحَدَ أَغْيَرُ مِنَ اللَّهِ، فَلِذَلِكَ حَرَّمَ الْفَوَاحِشَ مَا ظَهَرَ مِنْهَا وَمَا بَطَنَ، وَلاَ أَحَدَ أَحَبُّ إِلَيْهِ الْمِدْحَةُ مِنَ اللَّهِ، فَلِذَلِكَ مَدَحَ نَفْسَهُ
ኢማም ሙስሊም መፅሐፍ 19, ሐዲስ 22
وَلاَ شَخْصَ أَغْيَرُ مِنَ اللَّهِ وَلاَ شَخْصَ أَحَبُّ إِلَيْهِ الْعُذْرُ مِنَ اللَّهِ مِنْ أَجْلِ ذَلِكَ بَعَثَ اللَّهُ الْمُرْسَلِينَ مُبَشِّرِينَ وَمُنْذِرِينَ وَلاَ شَخْصَ أَحَبُّ إِلَيْهِ الْمِدْحَةُ مِنَ اللَّهِ مِنْ أَجْلِ ذَلِكَ وَعَدَ اللَّهُ الْجَنَّةَ
ስለዚህ አላህ የራሱ ዛትን “በእኔነት” ወይም “በማንነት” የሚገልጥ፣ “ማን” ተብሎ በመጠይቅ ተውላጠ-ስም የሚቀመጥ “ቅዋሜ-ማንነት” አለው፤ የእርሱ እውቀት፣ እይታ፣ መስማት እና መናገር ከፍጡራን ጋር የማይመሳሰል መለኮዊዉ እንጂ ሰዋዊ አይደለም፦
60:1 #እኔ የምትደብቁትንና የምትገልጹትን #የማውቅ ስሆን ወደ እነርሱ በፍቅር ትመሣጠራላችሁ?፤
34:11 #እኔ የምትሠሩትን ነገር ሁሉ ተመልካች ነኝና።
2:186 ባሮቼም ከእኔ በጠየቁህ ጊዜ፡- #እኔ ቅርብ ነኝ፡፡ የለማኝን ጸሎት በለመነኝ ጊዜ #እቀበለዋለሁ፡፡ ስለዚህ ለኔ ይታዘዙ፤ በእኔም ይመኑ፤ እነርሱ ሊመሩ ይከጀላልና፡፡
21:92 “#እኔም” ጌታችሁ #ነኝ እና “አምልኩኝ”።
አላህ ዛት እንዳለው በሐዲስ ተገልጿል፦
ኢማም ቡኻሪይ መጽሐፍ 60, ሐዲስ 38:
አቢ ሁረይራህ”ረዳየሏሁ ዐንሁ” እንደተረከው፦ “ኢብራሒም አልቀጠፈም በሶስት ጉዳይ ላይ ቢሆን እንጂ፤ ሁለቱ ለአላህ “ዛት” ذَاتِ ብሎ፦ እኔ አሞኛል እና እኔ አልሰራሁም ግን ትልቁ ጣዖት ይህንን ሰራ ባለበት ጊዜ ሲሆን፤ ሶስተኛው እርሱ እና ሳራ በተጓዙ ጊዜ عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ ـ رضى الله عنه ـ قَالَ لَمْ يَكْذِبْ إِبْرَاهِيمُ ـ عَلَيْهِ السَّلاَمُ ـ إِلاَّ ثَلاَثَ كَذَبَاتٍ ثِنْتَيْنِ مِنْهُنَّ فِي ذَاتِ اللَّهِ عَزَّ وَجَلَّ، قَوْلُهُ {إِنِّي سَقِيمٌ } وَقَوْلُهُ {بَلْ فَعَلَهُ كَبِيرُهُمْ هَذَا}، وَقَالَ بَيْنَا هُوَ ذَاتَ يَوْمٍ وَسَارَةُ إِذْ أَتَى عَلَى جَبَّارٍ مِنَ الْجَبَابِرَةِ فَقِيلَ لَهُ إِنَّ هَا هُنَا رَجُلاً مَعَهُ امْرَأَةٌ مِنْ أَحْسَنِ النَّاسِ ።
ኢንሻላህ ስለ መንፈስ በክፍል ሁለት ይቀጥላል….
✍ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሰላሙ አለይኩም
ላባና ክንፍ፦
መዝሙር 91፥4 *በላባዎቹ ይጋርድሃል፥ በክንፎቹም* በታች ትተማመናለህ
ከንፈርና ምላስ፦
ኢሳይያስ 30፥27 እነሆ፥ የእግዚአብሔር ስም ከሚነድድ ቍጣ ከሚትጐለጐልም ጢስ ጋር ከሩቅ ይመጣል፤ *ከንፈሮቹም* ቍጣን የሞሉ ናቸው፥ *ምላሱም* እንደምትበላ እሳት ናት፤
ዓይንና ቅንድብ፦
መዝሙር 11፥4 እግዚአብሔር በተቀደሰው መቅደሱ ነው፤ እግዚአብሔር፥ ዙፋኑ በሰማይ ነው፤ “ዓይኖቹ” ወደ ድሃ ይመለከታሉ፥ *ቅንድቦቹም* የሰው ልጆችን ይመረምራሉ።
አፍንጫና አፍ፦
ዘጸአት 15፥8 *በአፍንጫህ* እስትንፋስ ውኆች ተከመሩ፥
መዝሙር 33:6 በእግዚአብሔር ቃል ሰማዮች ጸኑ፥ ሠራዊታቸውም ሁሉ *”በአፉ”* እስትንፋስ፤”
ክንድና ብብት፦
ኢሳይያስ 40፥11 መንጋውን እንደ እረኛ ያሰማራል፥ ጠቦቶቹን *በክንዱ ሰብስቦ በብብቱ* ይሸከማል፥ የሚያጠቡትንም በቀስታ ይመራል።
እግርና ጫማ፦
ሕዝቅኤል 43:7 እንዲህም አለኝ። የሰው ልጅ ሆይ፥ በእስራኤል ልጆች መካከል ለዘላለም የምቀመጥበት የዙፋኔ ስፍራና “የእግሬ ጫማ” መረገጫ ይህ ነው።
መንፈስ ማለት የማይታይ ነው ከተባለ የእስራኤል አምላክን ሰዎች አይተውታል ይለናል፦
ዘጸአት 24:10 የእስራኤልንም አምላክ “”አዩ””፤ “ከእግሩም” በታች እንደ ሰማይ መልክ የሚያበራ እንደ ብሩህ ሰንፔር ድንጋይ የሚመስል ወለል ነበረ።
አይን፣ እጅ፣ እግር፣ ጆሮ ስጋዊ ሳይሆን መለኮታዊ ነው ይሉናል፦
ኢዮብ 10፥4 በውኑ የሥጋ ዓይን አለህን?
ወይስ ሰው እንደሚያይ ታያለህን?
አየህ አይን፣ እጅ፣ እግር፣ ጆሮ ስጋዊ ሳይሆን መለኮታዊ ከሆነ ፈጣሪ አፍአዊ ወይም ውጫዊ ትርጉሙ ያለው ጀማትና አጥንትን የያዘ ተክለ-ሰውነት ወይም ገላ አሊያም ግዝፈተ-ስጋ”body” የለውም ማለት ነው። ነገር ግን ውሳጣዊ ወይም ውስጣዊ ትርጉም ቅዋሜ-ማንነት እገሌ ተብሎ በእኔነት፣ “በአንተነት”፣ “በእርሱነት” የሚገለጥ ነባቢ ባለቤት”person” ብሎ አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ አሌፍ 218 ገፅ 218 ላይ እና በተመሳሳይ አለቃ ደስታ ተክለ ወልድ አሌፍ 97 ገፅ 97 ላይ ያስቀመጠውን ነባቢ ማንነት ፈጣሪ አለው፤ ፍፁም ገፅ ማለትም መታወቂያ”identity” ፍፁም መልክ ማለትም መለያ ወይም መገለጫ”intity” አለው። ይህ በኢስላም “ሸኽስ” شخص ይባላል፤ “ሸኽስ” ዛትን “በእኔነት” ወይም “በማንነት” የሚገልጥ ሲሆን “ማን” ተብሎ በመጠይቅ ተውላጠ-ስም የሚቀመጥ “ቅዋሜ-ማንነት” አለው፤ “ሸኽስ” የሚለውን ቃል በግሪክ “ፕሮሶፓን” πρόσωπον ሲሆን ፐርሰን”person” የሚለው የኢንግሊሹ ቃል እና ፐርሶና የሚለው የላቲኑ ቃል ከግሪኩ ፕሮሶፓን የመጣ ሲሆን “ቅዋሜ-ማንነት” ማለት ነው፤ ይህንን ቃል በአማርኛ ቃል ሲጠፋለት አለቃ ኪዳነ-ወልድ ክፍሌ መዝገበ ቃላት፣ ደስታ ተክለ-ወልድ መዝገበ ቃላት ሆነ ከሳቴ-ብርሃን ተሰማ መዝገበ ቃላት “አካል” ብለውታል፤።
“ሸኽስ” የሚለው ቃል “አሐድ” ለሚለው ቃል ተለዋዋጭ ነው፤ “አሐድ” أَحَد የሚለው ቃል “ላ “አሐደ” አግየሩ ሚነልላህ” لاَ أَحَدَ أَغْيَرُ مِنَ اللَّهِ ተብሎ በኢማም ቡኻሪይ ላይ ሲዘገብ “ሸኽስ” شخص ደግሞ “ወላ “ሸኽሰ” አግየሩ ሚነልላህ” وَلاَ شَخْصَ أَغْيَرُ مِنَ اللَّهِ ተብሎ በኢማም ሙስሊም ላይ በተመሳሳይ ሰዋስው ተዘግቧል፦
ኢማም ቡኻሪይ መፅሐፍ 65, ሐዲስ 4637
لاَ أَحَدَ أَغْيَرُ مِنَ اللَّهِ، فَلِذَلِكَ حَرَّمَ الْفَوَاحِشَ مَا ظَهَرَ مِنْهَا وَمَا بَطَنَ، وَلاَ أَحَدَ أَحَبُّ إِلَيْهِ الْمِدْحَةُ مِنَ اللَّهِ، فَلِذَلِكَ مَدَحَ نَفْسَهُ
ኢማም ሙስሊም መፅሐፍ 19, ሐዲስ 22
وَلاَ شَخْصَ أَغْيَرُ مِنَ اللَّهِ وَلاَ شَخْصَ أَحَبُّ إِلَيْهِ الْعُذْرُ مِنَ اللَّهِ مِنْ أَجْلِ ذَلِكَ بَعَثَ اللَّهُ الْمُرْسَلِينَ مُبَشِّرِينَ وَمُنْذِرِينَ وَلاَ شَخْصَ أَحَبُّ إِلَيْهِ الْمِدْحَةُ مِنَ اللَّهِ مِنْ أَجْلِ ذَلِكَ وَعَدَ اللَّهُ الْجَنَّةَ
ስለዚህ አላህ የራሱ ዛትን “በእኔነት” ወይም “በማንነት” የሚገልጥ፣ “ማን” ተብሎ በመጠይቅ ተውላጠ-ስም የሚቀመጥ “ቅዋሜ-ማንነት” አለው፤ የእርሱ እውቀት፣ እይታ፣ መስማት እና መናገር ከፍጡራን ጋር የማይመሳሰል መለኮዊዉ እንጂ ሰዋዊ አይደለም፦
60:1 #እኔ የምትደብቁትንና የምትገልጹትን #የማውቅ ስሆን ወደ እነርሱ በፍቅር ትመሣጠራላችሁ?፤
34:11 #እኔ የምትሠሩትን ነገር ሁሉ ተመልካች ነኝና።
2:186 ባሮቼም ከእኔ በጠየቁህ ጊዜ፡- #እኔ ቅርብ ነኝ፡፡ የለማኝን ጸሎት በለመነኝ ጊዜ #እቀበለዋለሁ፡፡ ስለዚህ ለኔ ይታዘዙ፤ በእኔም ይመኑ፤ እነርሱ ሊመሩ ይከጀላልና፡፡
21:92 “#እኔም” ጌታችሁ #ነኝ እና “አምልኩኝ”።
አላህ ዛት እንዳለው በሐዲስ ተገልጿል፦
ኢማም ቡኻሪይ መጽሐፍ 60, ሐዲስ 38:
አቢ ሁረይራህ”ረዳየሏሁ ዐንሁ” እንደተረከው፦ “ኢብራሒም አልቀጠፈም በሶስት ጉዳይ ላይ ቢሆን እንጂ፤ ሁለቱ ለአላህ “ዛት” ذَاتِ ብሎ፦ እኔ አሞኛል እና እኔ አልሰራሁም ግን ትልቁ ጣዖት ይህንን ሰራ ባለበት ጊዜ ሲሆን፤ ሶስተኛው እርሱ እና ሳራ በተጓዙ ጊዜ عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ ـ رضى الله عنه ـ قَالَ لَمْ يَكْذِبْ إِبْرَاهِيمُ ـ عَلَيْهِ السَّلاَمُ ـ إِلاَّ ثَلاَثَ كَذَبَاتٍ ثِنْتَيْنِ مِنْهُنَّ فِي ذَاتِ اللَّهِ عَزَّ وَجَلَّ، قَوْلُهُ {إِنِّي سَقِيمٌ } وَقَوْلُهُ {بَلْ فَعَلَهُ كَبِيرُهُمْ هَذَا}، وَقَالَ بَيْنَا هُوَ ذَاتَ يَوْمٍ وَسَارَةُ إِذْ أَتَى عَلَى جَبَّارٍ مِنَ الْجَبَابِرَةِ فَقِيلَ لَهُ إِنَّ هَا هُنَا رَجُلاً مَعَهُ امْرَأَةٌ مِنْ أَحْسَنِ النَّاسِ ።
ኢንሻላህ ስለ መንፈስ በክፍል ሁለት ይቀጥላል….
✍ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሰላሙ አለይኩም
አካል እና መንፈስ
ክፍል ሁለት
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
17:85 ከሩሕም ይጠይቁሃል፤ ሩሕ *ከ* ጌታዬ ነገር مِنْ أَمْرِ رَبِّي ነው፤ ከዕውቀትም ጥቂትን እንጂ አልተሰጣችሁም፤ በላቸው።
ነጥብ ሁለት
“መንፈስ”
“ሩሕ” رُوح የሚለው ቃል “መንፈስ” ማለት ሲሆን በቁርአን 21 ጊዜ ተጠቅሷል፤ ይህም ቃል እንደየ አውዱ ለተለየየ አጠቃቀም ይጠቀምበታል፤ ለምሳሌ ቁርአን “መንፈስ” ተብሏል፦
42፥52 እንደዚሁም ወደ አንተ ከትእዛዛችን ሲኾን “መንፈስን” አወረድን፡፡ መጽሐፉም እምነቱም ምን እንደኾነ የምታውቅ አልነበርክም፡፡ ግን ከባሮቻችን የምንሻውን ሰው በእርሱ የምንመራበት “ብርሃን” አደረግነው፡፡ አንተም ወደ ቀጥተኛው መንገድ በእርግጥ ትመራለህ وَكَذَٰلِكَ أَوْحَيْنَآ إِلَيْكَ رُوحًۭا مِّنْ أَمْرِنَا ۚ مَا كُنتَ تَدْرِى مَا ٱلْكِتَٰبُ وَلَا ٱلْإِيمَٰنُ وَلَٰكِن جَعَلْنَٰهُ نُورًۭا نَّهْدِى بِهِۦ مَن نَّشَآءُ مِنْ عِبَادِنَا ۚ وَإِنَّكَ لَتَهْدِىٓ إِلَىٰ صِرَٰطٍۢ مُّسْتَقِيمٍۢ ፡፡
እዚህ አንቀፅ ላይ “መንፈስ” እና “ብርሃን” ተለዋዋጭ ቃል ሆነው ገብተዋል፤ ብርሃን የሃይድሮጂን፣ የሂልየም እና የአርገን ብርሃን ማለት እንዳልሆን ሁሉ መንፈስ የተባለውም አካል ህያው የሚሆንበት ንጥረ-ነገር ሳይሆን ቁርአን ነው፤ “መንፈስ” እና “ብርሃን” እዚህ ጋር “ሒስሲይ” ማለትም “እማሬአዊ” ሳይሆን “መዕነዊይ” ማለትም “ፍካሬአዊ” ነው። በተጨማሪም ጂብሪል *ታማኙ መንፈስ* እና *ቅዱሱ መንፈስ* ተብላል፦
26:192-194 እርሱም ቁርአን በእርግጥ ከዓለማት ጌታ የተወረደ ነው፡፡ እርሱን #ታማኙ* #መንፈስ* አወረደው፤ ከአስጠንቃቂዎቹ ትኾን ዘንድ #በልብህ* ላይ አወረደው፡፡
19:17 ከእነሱም መጋረጃን አደረገች፣ #መንፈሳችንንም (ጂብሪልን) ወደርሷ ላክን፤ ለእርሷም ትክክለኛ ሰው ሆኖ ተመሰለላት።
16:102 እነዚያን ያመኑትን ለማረጋጋት ሙስሊሞቹንም ለመምራትና ለማብሰር ቁርአንን #ቅዱሱ* #መንፈስ*(ጂብሪል) እውነተኛ ሲሆን #ከጌታህ* مِنْ رَبِّكَ *አወረደው* በላቸው።
ክፍል ሁለት
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
17:85 ከሩሕም ይጠይቁሃል፤ ሩሕ *ከ* ጌታዬ ነገር مِنْ أَمْرِ رَبِّي ነው፤ ከዕውቀትም ጥቂትን እንጂ አልተሰጣችሁም፤ በላቸው።
ነጥብ ሁለት
“መንፈስ”
“ሩሕ” رُوح የሚለው ቃል “መንፈስ” ማለት ሲሆን በቁርአን 21 ጊዜ ተጠቅሷል፤ ይህም ቃል እንደየ አውዱ ለተለየየ አጠቃቀም ይጠቀምበታል፤ ለምሳሌ ቁርአን “መንፈስ” ተብሏል፦
42፥52 እንደዚሁም ወደ አንተ ከትእዛዛችን ሲኾን “መንፈስን” አወረድን፡፡ መጽሐፉም እምነቱም ምን እንደኾነ የምታውቅ አልነበርክም፡፡ ግን ከባሮቻችን የምንሻውን ሰው በእርሱ የምንመራበት “ብርሃን” አደረግነው፡፡ አንተም ወደ ቀጥተኛው መንገድ በእርግጥ ትመራለህ وَكَذَٰلِكَ أَوْحَيْنَآ إِلَيْكَ رُوحًۭا مِّنْ أَمْرِنَا ۚ مَا كُنتَ تَدْرِى مَا ٱلْكِتَٰبُ وَلَا ٱلْإِيمَٰنُ وَلَٰكِن جَعَلْنَٰهُ نُورًۭا نَّهْدِى بِهِۦ مَن نَّشَآءُ مِنْ عِبَادِنَا ۚ وَإِنَّكَ لَتَهْدِىٓ إِلَىٰ صِرَٰطٍۢ مُّسْتَقِيمٍۢ ፡፡
እዚህ አንቀፅ ላይ “መንፈስ” እና “ብርሃን” ተለዋዋጭ ቃል ሆነው ገብተዋል፤ ብርሃን የሃይድሮጂን፣ የሂልየም እና የአርገን ብርሃን ማለት እንዳልሆን ሁሉ መንፈስ የተባለውም አካል ህያው የሚሆንበት ንጥረ-ነገር ሳይሆን ቁርአን ነው፤ “መንፈስ” እና “ብርሃን” እዚህ ጋር “ሒስሲይ” ማለትም “እማሬአዊ” ሳይሆን “መዕነዊይ” ማለትም “ፍካሬአዊ” ነው። በተጨማሪም ጂብሪል *ታማኙ መንፈስ* እና *ቅዱሱ መንፈስ* ተብላል፦
26:192-194 እርሱም ቁርአን በእርግጥ ከዓለማት ጌታ የተወረደ ነው፡፡ እርሱን #ታማኙ* #መንፈስ* አወረደው፤ ከአስጠንቃቂዎቹ ትኾን ዘንድ #በልብህ* ላይ አወረደው፡፡
19:17 ከእነሱም መጋረጃን አደረገች፣ #መንፈሳችንንም (ጂብሪልን) ወደርሷ ላክን፤ ለእርሷም ትክክለኛ ሰው ሆኖ ተመሰለላት።
16:102 እነዚያን ያመኑትን ለማረጋጋት ሙስሊሞቹንም ለመምራትና ለማብሰር ቁርአንን #ቅዱሱ* #መንፈስ*(ጂብሪል) እውነተኛ ሲሆን #ከጌታህ* مِنْ رَبِّكَ *አወረደው* በላቸው።
ስለዚህ አላህ ማለት ግኡዛን ነገሮችን ህያው የሚያደርግበት ንጥረ-ነገር አይደለም። አላህ ፈጣሪ እንጂ ፍጡር አይደለም። ስለዚህ ሩህ እውቀት የተሰጠን እውቀት አናሳ ነው፤ ዋናው ሩህ ከአፈር ሳይሆን ከጌታ ነገር መሆኑን መቀበል ነው፦
17:85 ከሩሕም ይጠይቁሃል፤ ሩሕ *ከ* ጌታዬ ነገር مِنْ أَمْرِ رَبِّي ነው፤ ከዕውቀትም ጥቂትን እንጂ አልተሰጣችሁም፤ በላቸው።
ይህንን ካየን በባይብል መንፈስ የሚለው ቃል በዕብራይስጥ “ሩዋህ” ר֫וּחַ በግሪክ ደግሞ “ኑማ” πνεῦμα ሲሆን ፈጣሪ አደምን ከምድር አፈር ሰርቶ በአፍንጫውም “የሕይወት እስትንፋስን የሆነውን መንፈስ እፍ ሲልበት አደም ህያው ነፍስ ሆነ፤ ይህንን መንፈስ በአካል ውስጥ ሰራው፦
ዘፍጥረት 2፥7 እግዚአብሔር አምላክም ሰውን ከምድር አፈር አበጀው፤ በአፍንጫውም “የሕይወት እስትንፋስን እፍ”” አለበት ሰውም ሕያው ነፍስ ሆነ። NIV
ዘካርያስ 12፥1 ስለ እስራኤል የተነገረ የእግዚአብሔር ቃል ሸክም ይህ ነው። ሰማያትን የዘረጋ፥ ምድርንም የመሠረተ፥ “”የሰውንም መንፈስ በውስጡ የሠራ”” እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦
ይህም መንፈስ ከአምላክ እንደተሰጠ በሞት ጊዜ ወደ አምላክ ይመለሳል፦
መክብብ 12፥7 አፈርም ወደ ነበረበት ምድር ሳይመለስ፥ “መንፈስም” ר֫וּחַ ወደ ሰጠው ወደ እግዚአብሔር ሳይመለስ ፈጣሪህን አስብ። NIV
ይህ የሰው መንፈስ የእግዚአብሔር መብራት ነው፦
ምሳሌ 20፥27 የሰው መንፈስ የእግዚአብሔር መብራት ነው የሆዱን ጕርጆች ሁሉ የሚመረምር።
ሌላው መላእክት መንፈስ ናቸው፦
መዝሙር 104፥4 “መላእክቱን መንፈስ የሚያደርግ”፥ አገልጋዮቹንም የእሳት ነበልባል።
ራእ 4፥5 ከዙፋኑም መብረቅና ድምፅ ነጐድጓድም ይወጣል፤ በዙፋኑም ፊት ሰባት የእሳት መብራቶች ይበሩ ነበር፥ እነርሱም ሰባቱ “”የእግዚአብሔር መናፍስት”” ናቸው።
ራእ 5፥6 ሰባትም ቀንዶችና ሰባት ዓይኖች ነበሩት እነርሱም ወደ ምድር ሁሉ የተላኩ “የእግዚአብሔር መናፍስት” ናቸው።
“ቄስ” በብዜት “ቄሶች” ለማለት “ቀሳውስት” እንደሚባል፣ “አምላክ” በብዜት “አምላኮች” ለማለት “አማልክት” እንደሚባል ሁሉ “መንፈስ” በብዜት “መንፈሶች” ለማለት “መናፍስት” ይባላል፤ እነዚህም ሰባት የእግዚአብሔር መንፈሶች ሰባቱም የእግዚአብሔር መላእክት ናቸው፦
ራእ 16፥1 #ለሰባቱም መላእክት”። ሄዳችሁ የእግዚአብሔርን ቁጣ ጽዋዎች በምድር ውስጥ አፍስሱ የሚል ታላቅ ድምፅ ከመቅደሱ ሰማሁ።
ራእ 8፥2 በእግዚአብሔርም ፊት የሚቆሙትን #ሰባቱን መላእክት” አየሁ፥ ሰባትም መለከት ተሰጣቸው።
ሌላው “እግዚአብሔር መንፈስ ነው” ማለት “ሥጋና አጥንት የለውም” ማለት ነው እንጂ መንፈስ ማለት የማይታይ ረቂቅ ማለት ብቻ አይደለም፦
ዮሐንስ 4:24 “እግዚአብሔር መንፈስ ነው”፥ የሚሰግዱለትም በመንፈስና በእውነት ሊሰግዱለት ያስፈልጋቸዋል።
ሉቃስ 24:39 እኔ ራሴ እንደ ሆንሁ እጆቼንና እግሮቼን እዩ፤ በእኔ እንደምታዩት፥ “መንፈስ ሥጋና አጥንት የለውምና” እኔን ዳስሳችሁ እዩ አላቸው።
ምክንያቱም እግዚአብሔር በዚህ ዓለም ሆነ በትንሳኤ ቀን እንደሚታይ ስለሚናገር፦
ዘጸአት 24:10 የእስራኤልንም አምላክ “”አዩ””፤ “ከእግሩም” በታች እንደ ሰማይ መልክ የሚያበራ እንደ ብሩህ ሰንፔር ድንጋይ የሚመስል ወለል ነበረ።
ማቴዎስ 18፥10 ከነዚህ ከታናናሾቹ አንዱን እንዳትንቁ ተጠንቀቁ፤ መላእክቶቻቸው በሰማያት ዘወትር በሰማያት ያለውን “”የአባቴን ፊት ያያሉ”” እላችኋለሁና።
ኢዮብ 19፥ 26-27 ይህ ቁርበቴም ከጠፋ በኋላ፥ በዚያን ጊዜ ከሥጋዬ ተለይቼ “”እግዚአብሔርን እንዳይ”” አውቃለሁ። እኔ ራሴ አየዋለሁ፥ “”ዓይኖቼም ይመለከቱታል””፥
ራእይ 22፥3 ከእንግዲህም ወዲህ መርገም ከቶ አይሆንም። የእግዚአብሔርና የበጉም ዙፋን በእርስዋ ውስጥ ይሆናል፥ ባሪያዎቹም ያመልኩታል፥ “”ፊቱንም ያያሉ””፥
ሲጀመር “እግዚአብሔር መንፈስ ነው” የሚለው ቃል ኢየሱስ ይናገረው አይናገረው እርግጠኛ አይደለንም። ምክንያቱም አራቱ ወንጌላት ላይ አሉ የሚባሉት የኢየሱስ ንግግር ከመቶ 82% የኢየሱስ አይደለም የሚል የአዲስ ኪዳን ምሁር የዶክተር ሄርማን ሙግት ስላለም ጭምር።
ሲቀጥል “እግዚአብሔር መንፈስ ነው” ማለት ሥጋና አጥንት የለውም” ነው፤ ለምሳሌ አምላክ እሳት ነው ተብሏል፦
ዘዳግም 4፥24 አምላክህ እግዚአብሔር “የሚበላ እሳት” ቀናተኛም አምላክ ነውና።
ዕብራውያን 12:29 አምላካችን በእውነት የሚያጠፋ እሳት ነውና።
ዘዳግም 9፥3 አምላክህም እግዚአብሔር “እንደሚበላ እሳት” ሆኖ በፊትህ እንዲያልፍ ዛሬ እወቅ፤ እርሱ ያጠፋቸዋል፥
እግዚአብሔር “እንደሚበላ እሳት” ስለሚያጠፋ እሳት ተባለ እንጂ ነበልባል የሆነ ኦክሲዴሽን ማለት እንዳልሆነ ሁሉ መንፈስ ነው ማለት ልክ እንደ መንፈስ ሥጋና አጥንት የለውም ማለት እንጂ ንጥረ-ነገር የሆነ መንፈስ ነው ማለት አይደለም።
ሲሰልስ መንፈስ በእግዚአብሔርም ፊት ቆሞ መናገሩ እና መላኩ መንፈስ እርሱ ከእግዚአብሔር ይለያል፦
1ኛ ነገሥት 22፥20-23 እግዚአብሔርም፦ ወጥቶ በሬማት ዘገለዓድ ይወድቅ ዘንድ አክዓብን የሚያሳስት ማን ነው? አለ። አንዱም እንዲህ ያለ ነገር፥ ሌላውም እንዲያ የለ ነገር ተናገረ። መንፈስም ወጣ “”በእግዚአብሔርም ፊት ቆሞ””፦ እኔ አሳስተዋለሁ አለ። እግዚአብሔርም፦ በምን? አለው እርሱም፦ ወጥቼ በነቢያቶቹ ሁሉ አፍ ሐሰተኛ መንፈስ እሆናለሁ አለ። እግዚአብሔርም፦ ማሳሳትስ ታሳስተዋለህ፥ ይሆንልሃልም ውጣ፥ እንዲሁም አድርግ አለ። አሁንም፦ እነሆ፥ እግዚአብሔር በእነዚህ በነቢያትህ ሁሉ አፍ ሐሰተኛ መንፈስ አድርጎአል፤ እግዚአብሔርም በላይህ ክፉ ተናግሮብሃል።
2ኛ ነገሥት 19፥7 እነሆ፥ በላዩ “”መንፈስን እሰድዳለሁ””፥ ወሬንም ይሰማል፥ ወደ ምድሩም ይመለሳል፤ በምድሩም በሰይፍ እንዲወድቅ አደርገዋለሁ በሉት አላቸው።
መደምደሚያ
መንፈስ ከጌታችን “ነገር” ነው፦
17:85 ከሩሕም ይጠይቁሃል፤ ሩሕ *ከ* ጌታዬ ነገር مِنْ أَمْرِ رَبِّي ነው፤ ከዕውቀትም ጥቂትን እንጂ አልተሰጣችሁም፤ በላቸው።
መንፈስ ከነገር አንዱ ከሆነ ነገር ሁሉ ፍጡር ነው፦
39:62 አላህ “የነገሩ ሁሉ ፈጣሪ ነው”፤ እርሱም በነገሩ ሁሉ ላይ አስተናባሪ ነው።
40:62 ይሃችሁ፣ ጌታችሁ አላህ ነው፤ “የነገር ሁሉ ፈጣሪ ነው”፤ ከርሱ ሌላ አምላክ የለም፤ ታዲያ ከእምነት ወዴት ትመለሳላችሁ?።
6:102 ይህ ጌታችሁ አላህ ነው፡፡ ከእርሱ በቀር አምላክ የለም፡፡ “ነገርን ሁሉ ፈጣሪ” ነው፡፡ ስለዚህ አምልኩት፤ እርሱም በነገሩ ሁሉ ላይ ተጠባባቂ ነው፡፡
ስለዚህ አላህ ነገር ሳይሆን የነገር ፈጣሪ ስለሆነ ፍጡር የሆኑትን አካል እና መንፈስ ነገር ስለሆኑ አላህ አካል እና መንፈስ አይደለም። አላህ መንፈስ ነው ወይስ አካል ነው? ብሎ መሞገት መደዴነት ነው፤ አላህ መለኮት ነው፤ መለኮታዊ ማንነትና ምንነት አለው፤ ማንና ምንድን እንደሆነ ቁርአን ላይ ጥልልና ጥንፍፍ ባለ መልኩ ተቀምጧል፤ ለመጣጥፉ እርዝመት ይቅርታ እጠይቃለው።
✍ ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሰላሙ አለይኩም
17:85 ከሩሕም ይጠይቁሃል፤ ሩሕ *ከ* ጌታዬ ነገር مِنْ أَمْرِ رَبِّي ነው፤ ከዕውቀትም ጥቂትን እንጂ አልተሰጣችሁም፤ በላቸው።
ይህንን ካየን በባይብል መንፈስ የሚለው ቃል በዕብራይስጥ “ሩዋህ” ר֫וּחַ በግሪክ ደግሞ “ኑማ” πνεῦμα ሲሆን ፈጣሪ አደምን ከምድር አፈር ሰርቶ በአፍንጫውም “የሕይወት እስትንፋስን የሆነውን መንፈስ እፍ ሲልበት አደም ህያው ነፍስ ሆነ፤ ይህንን መንፈስ በአካል ውስጥ ሰራው፦
ዘፍጥረት 2፥7 እግዚአብሔር አምላክም ሰውን ከምድር አፈር አበጀው፤ በአፍንጫውም “የሕይወት እስትንፋስን እፍ”” አለበት ሰውም ሕያው ነፍስ ሆነ። NIV
ዘካርያስ 12፥1 ስለ እስራኤል የተነገረ የእግዚአብሔር ቃል ሸክም ይህ ነው። ሰማያትን የዘረጋ፥ ምድርንም የመሠረተ፥ “”የሰውንም መንፈስ በውስጡ የሠራ”” እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦
ይህም መንፈስ ከአምላክ እንደተሰጠ በሞት ጊዜ ወደ አምላክ ይመለሳል፦
መክብብ 12፥7 አፈርም ወደ ነበረበት ምድር ሳይመለስ፥ “መንፈስም” ר֫וּחַ ወደ ሰጠው ወደ እግዚአብሔር ሳይመለስ ፈጣሪህን አስብ። NIV
ይህ የሰው መንፈስ የእግዚአብሔር መብራት ነው፦
ምሳሌ 20፥27 የሰው መንፈስ የእግዚአብሔር መብራት ነው የሆዱን ጕርጆች ሁሉ የሚመረምር።
ሌላው መላእክት መንፈስ ናቸው፦
መዝሙር 104፥4 “መላእክቱን መንፈስ የሚያደርግ”፥ አገልጋዮቹንም የእሳት ነበልባል።
ራእ 4፥5 ከዙፋኑም መብረቅና ድምፅ ነጐድጓድም ይወጣል፤ በዙፋኑም ፊት ሰባት የእሳት መብራቶች ይበሩ ነበር፥ እነርሱም ሰባቱ “”የእግዚአብሔር መናፍስት”” ናቸው።
ራእ 5፥6 ሰባትም ቀንዶችና ሰባት ዓይኖች ነበሩት እነርሱም ወደ ምድር ሁሉ የተላኩ “የእግዚአብሔር መናፍስት” ናቸው።
“ቄስ” በብዜት “ቄሶች” ለማለት “ቀሳውስት” እንደሚባል፣ “አምላክ” በብዜት “አምላኮች” ለማለት “አማልክት” እንደሚባል ሁሉ “መንፈስ” በብዜት “መንፈሶች” ለማለት “መናፍስት” ይባላል፤ እነዚህም ሰባት የእግዚአብሔር መንፈሶች ሰባቱም የእግዚአብሔር መላእክት ናቸው፦
ራእ 16፥1 #ለሰባቱም መላእክት”። ሄዳችሁ የእግዚአብሔርን ቁጣ ጽዋዎች በምድር ውስጥ አፍስሱ የሚል ታላቅ ድምፅ ከመቅደሱ ሰማሁ።
ራእ 8፥2 በእግዚአብሔርም ፊት የሚቆሙትን #ሰባቱን መላእክት” አየሁ፥ ሰባትም መለከት ተሰጣቸው።
ሌላው “እግዚአብሔር መንፈስ ነው” ማለት “ሥጋና አጥንት የለውም” ማለት ነው እንጂ መንፈስ ማለት የማይታይ ረቂቅ ማለት ብቻ አይደለም፦
ዮሐንስ 4:24 “እግዚአብሔር መንፈስ ነው”፥ የሚሰግዱለትም በመንፈስና በእውነት ሊሰግዱለት ያስፈልጋቸዋል።
ሉቃስ 24:39 እኔ ራሴ እንደ ሆንሁ እጆቼንና እግሮቼን እዩ፤ በእኔ እንደምታዩት፥ “መንፈስ ሥጋና አጥንት የለውምና” እኔን ዳስሳችሁ እዩ አላቸው።
ምክንያቱም እግዚአብሔር በዚህ ዓለም ሆነ በትንሳኤ ቀን እንደሚታይ ስለሚናገር፦
ዘጸአት 24:10 የእስራኤልንም አምላክ “”አዩ””፤ “ከእግሩም” በታች እንደ ሰማይ መልክ የሚያበራ እንደ ብሩህ ሰንፔር ድንጋይ የሚመስል ወለል ነበረ።
ማቴዎስ 18፥10 ከነዚህ ከታናናሾቹ አንዱን እንዳትንቁ ተጠንቀቁ፤ መላእክቶቻቸው በሰማያት ዘወትር በሰማያት ያለውን “”የአባቴን ፊት ያያሉ”” እላችኋለሁና።
ኢዮብ 19፥ 26-27 ይህ ቁርበቴም ከጠፋ በኋላ፥ በዚያን ጊዜ ከሥጋዬ ተለይቼ “”እግዚአብሔርን እንዳይ”” አውቃለሁ። እኔ ራሴ አየዋለሁ፥ “”ዓይኖቼም ይመለከቱታል””፥
ራእይ 22፥3 ከእንግዲህም ወዲህ መርገም ከቶ አይሆንም። የእግዚአብሔርና የበጉም ዙፋን በእርስዋ ውስጥ ይሆናል፥ ባሪያዎቹም ያመልኩታል፥ “”ፊቱንም ያያሉ””፥
ሲጀመር “እግዚአብሔር መንፈስ ነው” የሚለው ቃል ኢየሱስ ይናገረው አይናገረው እርግጠኛ አይደለንም። ምክንያቱም አራቱ ወንጌላት ላይ አሉ የሚባሉት የኢየሱስ ንግግር ከመቶ 82% የኢየሱስ አይደለም የሚል የአዲስ ኪዳን ምሁር የዶክተር ሄርማን ሙግት ስላለም ጭምር።
ሲቀጥል “እግዚአብሔር መንፈስ ነው” ማለት ሥጋና አጥንት የለውም” ነው፤ ለምሳሌ አምላክ እሳት ነው ተብሏል፦
ዘዳግም 4፥24 አምላክህ እግዚአብሔር “የሚበላ እሳት” ቀናተኛም አምላክ ነውና።
ዕብራውያን 12:29 አምላካችን በእውነት የሚያጠፋ እሳት ነውና።
ዘዳግም 9፥3 አምላክህም እግዚአብሔር “እንደሚበላ እሳት” ሆኖ በፊትህ እንዲያልፍ ዛሬ እወቅ፤ እርሱ ያጠፋቸዋል፥
እግዚአብሔር “እንደሚበላ እሳት” ስለሚያጠፋ እሳት ተባለ እንጂ ነበልባል የሆነ ኦክሲዴሽን ማለት እንዳልሆነ ሁሉ መንፈስ ነው ማለት ልክ እንደ መንፈስ ሥጋና አጥንት የለውም ማለት እንጂ ንጥረ-ነገር የሆነ መንፈስ ነው ማለት አይደለም።
ሲሰልስ መንፈስ በእግዚአብሔርም ፊት ቆሞ መናገሩ እና መላኩ መንፈስ እርሱ ከእግዚአብሔር ይለያል፦
1ኛ ነገሥት 22፥20-23 እግዚአብሔርም፦ ወጥቶ በሬማት ዘገለዓድ ይወድቅ ዘንድ አክዓብን የሚያሳስት ማን ነው? አለ። አንዱም እንዲህ ያለ ነገር፥ ሌላውም እንዲያ የለ ነገር ተናገረ። መንፈስም ወጣ “”በእግዚአብሔርም ፊት ቆሞ””፦ እኔ አሳስተዋለሁ አለ። እግዚአብሔርም፦ በምን? አለው እርሱም፦ ወጥቼ በነቢያቶቹ ሁሉ አፍ ሐሰተኛ መንፈስ እሆናለሁ አለ። እግዚአብሔርም፦ ማሳሳትስ ታሳስተዋለህ፥ ይሆንልሃልም ውጣ፥ እንዲሁም አድርግ አለ። አሁንም፦ እነሆ፥ እግዚአብሔር በእነዚህ በነቢያትህ ሁሉ አፍ ሐሰተኛ መንፈስ አድርጎአል፤ እግዚአብሔርም በላይህ ክፉ ተናግሮብሃል።
2ኛ ነገሥት 19፥7 እነሆ፥ በላዩ “”መንፈስን እሰድዳለሁ””፥ ወሬንም ይሰማል፥ ወደ ምድሩም ይመለሳል፤ በምድሩም በሰይፍ እንዲወድቅ አደርገዋለሁ በሉት አላቸው።
መደምደሚያ
መንፈስ ከጌታችን “ነገር” ነው፦
17:85 ከሩሕም ይጠይቁሃል፤ ሩሕ *ከ* ጌታዬ ነገር مِنْ أَمْرِ رَبِّي ነው፤ ከዕውቀትም ጥቂትን እንጂ አልተሰጣችሁም፤ በላቸው።
መንፈስ ከነገር አንዱ ከሆነ ነገር ሁሉ ፍጡር ነው፦
39:62 አላህ “የነገሩ ሁሉ ፈጣሪ ነው”፤ እርሱም በነገሩ ሁሉ ላይ አስተናባሪ ነው።
40:62 ይሃችሁ፣ ጌታችሁ አላህ ነው፤ “የነገር ሁሉ ፈጣሪ ነው”፤ ከርሱ ሌላ አምላክ የለም፤ ታዲያ ከእምነት ወዴት ትመለሳላችሁ?።
6:102 ይህ ጌታችሁ አላህ ነው፡፡ ከእርሱ በቀር አምላክ የለም፡፡ “ነገርን ሁሉ ፈጣሪ” ነው፡፡ ስለዚህ አምልኩት፤ እርሱም በነገሩ ሁሉ ላይ ተጠባባቂ ነው፡፡
ስለዚህ አላህ ነገር ሳይሆን የነገር ፈጣሪ ስለሆነ ፍጡር የሆኑትን አካል እና መንፈስ ነገር ስለሆኑ አላህ አካል እና መንፈስ አይደለም። አላህ መንፈስ ነው ወይስ አካል ነው? ብሎ መሞገት መደዴነት ነው፤ አላህ መለኮት ነው፤ መለኮታዊ ማንነትና ምንነት አለው፤ ማንና ምንድን እንደሆነ ቁርአን ላይ ጥልልና ጥንፍፍ ባለ መልኩ ተቀምጧል፤ ለመጣጥፉ እርዝመት ይቅርታ እጠይቃለው።
✍ ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሰላሙ አለይኩም
ሙስሊም
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
3፥102 እናንተ ያመናችሁ ሆይ! አላህን ተገቢውን መጠንቀቅ ተጠንቀቁት፡፡ እናንተም *”ሙስሊሞች ኾናችሁ እንጅ አትሙቱ”* ፡፡ يَٰٓأَيُّهَا ٱلَّذِينَ ءَامَنُوا۟ ٱتَّقُوا۟ ٱللَّهَ حَقَّ تُقَاتِهِۦ وَلَا تَمُوتُنَّ إِلَّا وَأَنتُم مُّسْلِمُونَ
መግቢያ
“ሙሥሊም” مُسْلِم የሚለው ቃል “አሥለመ” أَسْلَمَ “ታዘዘ”፣ “ተገዛ”፣ ” አመለከ” “ሁሉ ነገሩን ሰጠ” ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን ትርጉሙ “አቢድ” عَابِدُ ማለትም “አምላኪ” አሊያም “ቃኒት” قَانِتِ ማለትም “ታዛዥ” ማለት ነው፤ አላህ ለኢብራሂም “አሥሊም” أَسْلِمْ ማለትም “ታዘዝ” ብሎ ሲለው እርሱም ለዓለማት ጌታ “አሥለምቱ” أَسْلَمْتُ ማለትም “ታዘዝኩ” አለ፦
2፥131 ጌታው ለእርሱ *”ታዘዝ”* ባለው ጊዜ መረጠው፡፡ ለዓለማት ጌታ *”ታዘዝኩ”* አለ፡፡ إِذْ قَالَ لَهُۥ رَبُّهُۥٓ أَسْلِمْ ۖ قَالَ أَسْلَمْتُ لِرَبِّ ٱلْعَٰلَمِينَ
22፥34 *አምላካችሁም አንድ አምላክ ብቻ ነው፡፡ ለእርሱም ብቻ ታዘዙ*፡፡ ለአላህ ተዋራጆችንም አብስራቸው፡፡ فَإِلَـٰهُكُمْ إِلَـٰهٌ وَاحِدٌ فَلَهُ أَسْلِمُوا ۗ وَبَشِّرِ الْمُخْبِتِينَ
39፥54 «ቅጣቱም ወደእናንተ ከመምጣቱና ከዚያም የማትርረዱ ከመኾናችሁ በፊት ወደ ጌታችሁ በመጸጸት ተመለሱ፡፡ *ለእርሱም ታዘዙ*፡፡ وَأَنِيبُوا إِلَىٰ رَبِّكُمْ وَأَسْلِمُوا لَهُ مِن قَبْلِ أَن يَأْتِيَكُمُ الْعَذَابُ ثُمَّ لَا تُنصَرُونَ
“ታዘዙ” ለሚለው ቃል የመጣው “አሥሊሙ” أَسْلِمُوا ሲሆን “ሙስሊም” ማለት አንዱን አምላክ የሚታዘዝ ታዛዥ ማለት ነው። ስለዚህ ሙስሊም ማለት የዓለማቱን ጌታ አንዱን አምላክ በብቸኝነት የሚያመልክና የሚታዘዝ ማለት ነው። “ኢሥላም” إِسْلَٰم ደግሞ ሃይማኖቱ ሲሆን “ሢልም” سِّلْم ማለትም “መታዘዝ” ወይም “መገዛት” ማለት ነው፦
2፥208 እናንተ ያመናችሁ ሆይ! ሁላችሁም *”በመታዘዝ”* ውስጥ ግቡ፡፡ يَٰٓأَيُّهَا ٱلَّذِينَ ءَامَنُوا۟ ٱدْخُلُوا۟ فِى ٱلسِّلْمِ كَآفَّةًۭ
ይህ “መታዘዝ” ደግሞ በዲን ይመጣል፤ “ዲን” دِين ማለት “ሃይማኖት” “ፍትህ” “ፍርድ” “ሕግ” “መርህ” ማለት ነው፤ አላህ ዘንድ ያለው ሃይማኖት ኢስላም ብቻ ነው፤ ከኢስላም ሌላ ሃይማኖትን የሚፈልግ ሰው ፈጽሞ ተቀባይ የለውም፤ እርሱም በመጨረሻይቱ ዓለም ከከሳሪዎቹ ነው፦
3፥19 አላህ ዘንድ የተወደደ ሃይማኖት *“ኢስላም”* ብቻ ነው፡፡ إِنَّ ٱلدِّينَ عِندَ ٱللَّهِ ٱلْإِسْلَٰمُ
3፥85 *”ከኢስላም ሌላ ሃይማኖትን የሚፈልግ ሰው ፈጽሞ ከርሱ ተቀባይ የለውም”*፡፡ እርሱም በመጨረሻይቱ ዓለም ከከሳሪዎቹ ነው፡፡ وَمَن يَبْتَغِ غَيْرَ ٱلْإِسْلَٰمِ دِينًۭا فَلَن يُقْبَلَ مِنْهُ وَهُوَ فِى ٱلْـَٔاخِرَةِ مِنَ ٱلْخَٰسِرِينَ
“ሠለም” سَلَم ማለት ደግሞ “ታዛዥነት” በሚል መጥቷል፦
16፥87 አጋሪዎቹ በዚያ ቀንም *ታዛዥነታቸውን* ወደ አላህ ያቀርባሉ፡፡ ይቀጣጥፉት የነበሩትም ሁሉ ከእነርሱ ይጠፋቸዋል፡፡ وَأَلْقَوْا إِلَى اللَّهِ يَوْمَئِذٍ السَّلَمَ ۖ وَضَلَّ عَنْهُم مَّا كَانُوا يَفْتَرُون
ታዲያ “ሙስሊም” ማለት አንዱን አምላክ በብቸኝነት ማምለክ ከሆነ እስልምና የተጀመረው መቼ ነው? አንዳንድ ስለ እስልምና እሳቤው የሌላቸው ሰዎች በነብያችን”ﷺ” የተጀመረ ይመስላቸዋል፤ ነገር ግን እውነታው እስልምና ነብያችን”ﷺ” ከመላካቸው በፊት የነበሩት ሰዎች፣ ጂንዎች እና መላእክትም ሙስሊም ናቸው፤ እንዲህ ሲባል እንደው እውርና ድንብር የሆነ ፀለምተኛ ሙግት ሳይሆን ከቋንቋ ሙግት እና ከአምላካችን ከአላህ ንግግር ተነስቼ ነው፤ ይህንን ነጥብ በነጥብ እናያለን፦
ነጥብ አንድ
“መላእክት”
በሰማያት ያሉት መላእክት ለዓለማቱ ጌታ ለአላህ የታዘዙ ናቸው፦
3፥83 በሰማያትና በምድር *”ያሉት ሁሉ”* በውድም በግድም ለእርሱ *”የታዘዙ”* ወደርሱም የሚመለሱ ሲኾኑ ከሓዲዎች ከአላህ ሃይማኖት ሌላን ይፈልጋሉን? أَفَغَيْرَ دِينِ ٱللَّهِ يَبْغُونَ وَلَهُۥٓ أَسْلَمَ مَن فِى ٱلسَّمَٰوَٰتِ وَٱلْأَرْضِ طَوْعًۭا وَكَرْهًۭا وَإِلَيْهِ يُرْجَعُونَ
“የታዘዙ” ተብሎ የተቀመጠው ቃል “አስለመ” أَسْلَمَ ሲሆን “ሙስሊም” مُسْلِم የሚለው ቃል የመጣበት ስርወ-ግንድ ነው፣ ስለዚህ በሰማያት ያሉት መላእክት ለዓለማቱ ጌታ ለአላህ የታዘዙ ሲሆኑ እርሱን ከመገዛት አይኮሩም፤ አይሰለቹም፦
21:19 በሰማያትና በምድር ያለው ሁሉም የእርሱ ነው፡፡ እርሱ ዘንድ ያሉትም መላእክት *”እርሱን ከመገዛት አይኮሩም፤ አይሰለቹም”*፡፡ وَلَهُۥ مَن فِى ٱلسَّمَٰوَٰتِ وَٱلْأَرْضِ ۚ وَمَنْ عِندَهُۥ لَا يَسْتَكْبِرُونَ عَنْ عِبَادَتِهِۦ وَلَا يَسْتَحْسِرُونَ
ይህ እስልምና ውስጡ ሡጁድ ያቀፈ ሲሆን ይህም ሡጁድ “ሡጁዱል ዒባዳ” سُّجُود العبادة ማለትም “የአምልኮ ስግደት” ነው፦
16:49 ለአላህም በሰማያት ያለው ከተንቀሳቃሽም በምድር ያለው ሁሉ፣ *”መላእክትም ይሰግዳሉ፤ እነርሱም አይኮሩም”*፡፡ وَلِلَّهِ يَسْجُدُ مَا فِى ٱلسَّمَٰوَٰتِ وَمَا فِى ٱلْأَرْضِ مِن دَآبَّةٍۢ وَٱلْمَلَٰٓئِكَةُ وَهُمْ لَا يَسْتَكْبِرُونَ
16፥50 ጌታቸውን ከበላያቸው ሲኾን ይፈሩታል፡፡ *”የታዘዙትንም”* ሁሉ ይሠራሉ፡፡ يَخَافُونَ رَبَّهُم مِّن فَوْقِهِمْ وَيَفْعَلُونَ مَا يُؤْمَرُونَ ۩
7፥206 እነዚያ እጌታህ ዘንድ ያሉት መላእክት እርሱን *“ከማምለክ” አይኮሩም፤ ያወድሱታልም፤ “ለእርሱም ብቻ ይሰግዳሉ”* ። إِنَّ ٱلَّذِينَ عِندَ رَبِّكَ لَا يَسْتَكْبِرُونَ عَنْ عِبَادَتِهِۦ وَيُسَبِّحُونَهُۥ وَلَهُۥ يَسْجُدُونَ ۩
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
3፥102 እናንተ ያመናችሁ ሆይ! አላህን ተገቢውን መጠንቀቅ ተጠንቀቁት፡፡ እናንተም *”ሙስሊሞች ኾናችሁ እንጅ አትሙቱ”* ፡፡ يَٰٓأَيُّهَا ٱلَّذِينَ ءَامَنُوا۟ ٱتَّقُوا۟ ٱللَّهَ حَقَّ تُقَاتِهِۦ وَلَا تَمُوتُنَّ إِلَّا وَأَنتُم مُّسْلِمُونَ
መግቢያ
“ሙሥሊም” مُسْلِم የሚለው ቃል “አሥለመ” أَسْلَمَ “ታዘዘ”፣ “ተገዛ”፣ ” አመለከ” “ሁሉ ነገሩን ሰጠ” ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን ትርጉሙ “አቢድ” عَابِدُ ማለትም “አምላኪ” አሊያም “ቃኒት” قَانِتِ ማለትም “ታዛዥ” ማለት ነው፤ አላህ ለኢብራሂም “አሥሊም” أَسْلِمْ ማለትም “ታዘዝ” ብሎ ሲለው እርሱም ለዓለማት ጌታ “አሥለምቱ” أَسْلَمْتُ ማለትም “ታዘዝኩ” አለ፦
2፥131 ጌታው ለእርሱ *”ታዘዝ”* ባለው ጊዜ መረጠው፡፡ ለዓለማት ጌታ *”ታዘዝኩ”* አለ፡፡ إِذْ قَالَ لَهُۥ رَبُّهُۥٓ أَسْلِمْ ۖ قَالَ أَسْلَمْتُ لِرَبِّ ٱلْعَٰلَمِينَ
22፥34 *አምላካችሁም አንድ አምላክ ብቻ ነው፡፡ ለእርሱም ብቻ ታዘዙ*፡፡ ለአላህ ተዋራጆችንም አብስራቸው፡፡ فَإِلَـٰهُكُمْ إِلَـٰهٌ وَاحِدٌ فَلَهُ أَسْلِمُوا ۗ وَبَشِّرِ الْمُخْبِتِينَ
39፥54 «ቅጣቱም ወደእናንተ ከመምጣቱና ከዚያም የማትርረዱ ከመኾናችሁ በፊት ወደ ጌታችሁ በመጸጸት ተመለሱ፡፡ *ለእርሱም ታዘዙ*፡፡ وَأَنِيبُوا إِلَىٰ رَبِّكُمْ وَأَسْلِمُوا لَهُ مِن قَبْلِ أَن يَأْتِيَكُمُ الْعَذَابُ ثُمَّ لَا تُنصَرُونَ
“ታዘዙ” ለሚለው ቃል የመጣው “አሥሊሙ” أَسْلِمُوا ሲሆን “ሙስሊም” ማለት አንዱን አምላክ የሚታዘዝ ታዛዥ ማለት ነው። ስለዚህ ሙስሊም ማለት የዓለማቱን ጌታ አንዱን አምላክ በብቸኝነት የሚያመልክና የሚታዘዝ ማለት ነው። “ኢሥላም” إِسْلَٰم ደግሞ ሃይማኖቱ ሲሆን “ሢልም” سِّلْم ማለትም “መታዘዝ” ወይም “መገዛት” ማለት ነው፦
2፥208 እናንተ ያመናችሁ ሆይ! ሁላችሁም *”በመታዘዝ”* ውስጥ ግቡ፡፡ يَٰٓأَيُّهَا ٱلَّذِينَ ءَامَنُوا۟ ٱدْخُلُوا۟ فِى ٱلسِّلْمِ كَآفَّةًۭ
ይህ “መታዘዝ” ደግሞ በዲን ይመጣል፤ “ዲን” دِين ማለት “ሃይማኖት” “ፍትህ” “ፍርድ” “ሕግ” “መርህ” ማለት ነው፤ አላህ ዘንድ ያለው ሃይማኖት ኢስላም ብቻ ነው፤ ከኢስላም ሌላ ሃይማኖትን የሚፈልግ ሰው ፈጽሞ ተቀባይ የለውም፤ እርሱም በመጨረሻይቱ ዓለም ከከሳሪዎቹ ነው፦
3፥19 አላህ ዘንድ የተወደደ ሃይማኖት *“ኢስላም”* ብቻ ነው፡፡ إِنَّ ٱلدِّينَ عِندَ ٱللَّهِ ٱلْإِسْلَٰمُ
3፥85 *”ከኢስላም ሌላ ሃይማኖትን የሚፈልግ ሰው ፈጽሞ ከርሱ ተቀባይ የለውም”*፡፡ እርሱም በመጨረሻይቱ ዓለም ከከሳሪዎቹ ነው፡፡ وَمَن يَبْتَغِ غَيْرَ ٱلْإِسْلَٰمِ دِينًۭا فَلَن يُقْبَلَ مِنْهُ وَهُوَ فِى ٱلْـَٔاخِرَةِ مِنَ ٱلْخَٰسِرِينَ
“ሠለም” سَلَم ማለት ደግሞ “ታዛዥነት” በሚል መጥቷል፦
16፥87 አጋሪዎቹ በዚያ ቀንም *ታዛዥነታቸውን* ወደ አላህ ያቀርባሉ፡፡ ይቀጣጥፉት የነበሩትም ሁሉ ከእነርሱ ይጠፋቸዋል፡፡ وَأَلْقَوْا إِلَى اللَّهِ يَوْمَئِذٍ السَّلَمَ ۖ وَضَلَّ عَنْهُم مَّا كَانُوا يَفْتَرُون
ታዲያ “ሙስሊም” ማለት አንዱን አምላክ በብቸኝነት ማምለክ ከሆነ እስልምና የተጀመረው መቼ ነው? አንዳንድ ስለ እስልምና እሳቤው የሌላቸው ሰዎች በነብያችን”ﷺ” የተጀመረ ይመስላቸዋል፤ ነገር ግን እውነታው እስልምና ነብያችን”ﷺ” ከመላካቸው በፊት የነበሩት ሰዎች፣ ጂንዎች እና መላእክትም ሙስሊም ናቸው፤ እንዲህ ሲባል እንደው እውርና ድንብር የሆነ ፀለምተኛ ሙግት ሳይሆን ከቋንቋ ሙግት እና ከአምላካችን ከአላህ ንግግር ተነስቼ ነው፤ ይህንን ነጥብ በነጥብ እናያለን፦
ነጥብ አንድ
“መላእክት”
በሰማያት ያሉት መላእክት ለዓለማቱ ጌታ ለአላህ የታዘዙ ናቸው፦
3፥83 በሰማያትና በምድር *”ያሉት ሁሉ”* በውድም በግድም ለእርሱ *”የታዘዙ”* ወደርሱም የሚመለሱ ሲኾኑ ከሓዲዎች ከአላህ ሃይማኖት ሌላን ይፈልጋሉን? أَفَغَيْرَ دِينِ ٱللَّهِ يَبْغُونَ وَلَهُۥٓ أَسْلَمَ مَن فِى ٱلسَّمَٰوَٰتِ وَٱلْأَرْضِ طَوْعًۭا وَكَرْهًۭا وَإِلَيْهِ يُرْجَعُونَ
“የታዘዙ” ተብሎ የተቀመጠው ቃል “አስለመ” أَسْلَمَ ሲሆን “ሙስሊም” مُسْلِم የሚለው ቃል የመጣበት ስርወ-ግንድ ነው፣ ስለዚህ በሰማያት ያሉት መላእክት ለዓለማቱ ጌታ ለአላህ የታዘዙ ሲሆኑ እርሱን ከመገዛት አይኮሩም፤ አይሰለቹም፦
21:19 በሰማያትና በምድር ያለው ሁሉም የእርሱ ነው፡፡ እርሱ ዘንድ ያሉትም መላእክት *”እርሱን ከመገዛት አይኮሩም፤ አይሰለቹም”*፡፡ وَلَهُۥ مَن فِى ٱلسَّمَٰوَٰتِ وَٱلْأَرْضِ ۚ وَمَنْ عِندَهُۥ لَا يَسْتَكْبِرُونَ عَنْ عِبَادَتِهِۦ وَلَا يَسْتَحْسِرُونَ
ይህ እስልምና ውስጡ ሡጁድ ያቀፈ ሲሆን ይህም ሡጁድ “ሡጁዱል ዒባዳ” سُّجُود العبادة ማለትም “የአምልኮ ስግደት” ነው፦
16:49 ለአላህም በሰማያት ያለው ከተንቀሳቃሽም በምድር ያለው ሁሉ፣ *”መላእክትም ይሰግዳሉ፤ እነርሱም አይኮሩም”*፡፡ وَلِلَّهِ يَسْجُدُ مَا فِى ٱلسَّمَٰوَٰتِ وَمَا فِى ٱلْأَرْضِ مِن دَآبَّةٍۢ وَٱلْمَلَٰٓئِكَةُ وَهُمْ لَا يَسْتَكْبِرُونَ
16፥50 ጌታቸውን ከበላያቸው ሲኾን ይፈሩታል፡፡ *”የታዘዙትንም”* ሁሉ ይሠራሉ፡፡ يَخَافُونَ رَبَّهُم مِّن فَوْقِهِمْ وَيَفْعَلُونَ مَا يُؤْمَرُونَ ۩
7፥206 እነዚያ እጌታህ ዘንድ ያሉት መላእክት እርሱን *“ከማምለክ” አይኮሩም፤ ያወድሱታልም፤ “ለእርሱም ብቻ ይሰግዳሉ”* ። إِنَّ ٱلَّذِينَ عِندَ رَبِّكَ لَا يَسْتَكْبِرُونَ عَنْ عِبَادَتِهِۦ وَيُسَبِّحُونَهُۥ وَلَهُۥ يَسْجُدُونَ ۩
ነጥብ ሁለት
“ጅኒ”
“ጂን” جِنّ የሚለው ቃል “ጀንነ” جَنَّ “ተሰወረ” ወይም “ተደበቀ” ከሚል ግስ የመጣ ሲሆን “ስውር” ወይም “ድብቅ” ማለት ነው፤ “ጅኒ” جني ደግሞ የጂን ብዙ ቁጥር ነው፤ ጂኒዎች የተፈጠሩት ከሰው በፊት ነው፦
15:27 *”ጃንንም”* ከሰው በፊት ከእሳት ነበልባል ፈጠርነው፡፡ وَٱلْجَآنَّ خَلَقْنَٰهُ مِن قَبْلُ مِن نَّارِ ٱلسَّمُومِ
2:21 እናንተ ሰዎች ሆይ! የፈጠራችሁን እነዚያንም ከእናንተ በፊት *”የነበሩትን”* የፈጠረውን ጌታችሁን አምልኩ፤ يَٰٓأَيُّهَا ٱلنَّاسُ ٱعْبُدُوا۟ رَبَّكُمُ ٱلَّذِى خَلَقَكُمْ وَٱلَّذِينَ مِن قَبْلِكُمْ لَعَلَّكُمْ تَتَّقُونَ
26:184 «ያንንም የፈጠራችሁን *”የቀድሞዎቹንም ፍጡሮች”* የፈጠረውን ፍሩ፡፡» وَٱتَّقُوا۟ ٱلَّذِى خَلَقَكُمْ وَٱلْجِبِلَّةَ ٱلْأَوَّلِينَ
ጂኒዎች እንደ ሰው ነፃ ፈቃድ ያላቸው ፍጡሮች ናቸው፤ እንደ ሰው አላህ ሊያመልኩ የተፈጠሩት ፍጡሮች ናቸው፤ ከእነርሱ መካከል በነጻ ፈቃዳቸው በአላህ ላይ የሚያሻርኩ በደለኞች አሉ፤ አላህን በብቸኝነት የሚያመልኩ ሙስሊሞች አሉ፦
51:56 *″ጂን”* እና ሰውን *”ሊያመልኩኝ”* እንጅ ለሌላ አልፈጠርኳቸውም። وَمَا خَلَقْتُ ٱلْجِنَّ وَٱلْإِنسَ إِلَّا لِيَعْبُدُونِ
72፥14 «እኛም ከእኛ ውስጥ *”ሙስሊሞች አሉ”*፡፡ ከእኛም ውስጥ *”በዳዮች አሉ”*፡፡ የሰለሙም ሰዎች እነዚያ ቅንን መንገድ መረጡ፡፡» وَأَنَّا مِنَّا ٱلْمُسْلِمُونَ وَمِنَّا ٱلْقَٰسِطُونَ ۖ فَمَنْ أَسْلَمَ فَأُو۟لَٰٓئِكَ تَحَرَّوْا۟ رَشَدًۭا
ነጥብ ሶስት
“ሰዎች”
ሰው ሲፈጠር የሚፈጠርበት አላማ አንዱን አምላክ አላህን በብቸኝነት እንዲያመልክ ብቻ ነው፤ አላህ ሰዎችን የፈጠረበት ሃይማኖት ኢስላም ብቻ ነው፦
51:56 ጂን እና *”ሰውን ሊያመልኩኝ”* እንጅ ለሌላ አልፈጠርኳቸውም። وَمَا خَلَقْتُ ٱلْجِنَّ وَٱلْإِنسَ إِلَّا لِيَعْبُدُونِ
30፥30 ወደ እውነት ተዘንባይ ኾነህም ፊትህን ለሃይማኖት ቀጥ አድርግ፡፡ የአላህን ፍጥረት ያችን *”አላህ ሰዎችን በእርስዋ ላይ የፈጠረባትን ሃይማኖት ያዟት”*፡፡ فَأَقِمْ وَجْهَكَ لِلدِّينِ حَنِيفًۭا ۚ فِطْرَتَ ٱللَّهِ ٱلَّتِى فَطَرَ ٱلنَّاسَ عَلَيْهَا ۚ لَا تَبْدِيلَ لِخَلْقِ ٱللَّهِ ۚ ذَٰلِكَ ٱلدِّينُ ٱلْقَيِّمُ وَلَٰكِنَّ أَكْثَرَ ٱلنَّاسِ لَا يَعْلَمُونَ
3፥19 አላህ ዘንድ የተወደደ ሃይማኖት *“ኢስላም”* ብቻ ነው፡፡ إِنَّ ٱلدِّينَ عِندَ ٱللَّهِ ٱلْإِسْلَٰمُ
ኢስላም የተፈጥሮ ሀይማኖት፤ አላህ ከአደም ልጆች ከጀርቦቻቸው ዘሮቻቸውን ባወጣ ጊዜ «ጌታችሁ አይደለሁምን?» በማለት ጥያቄ ያቀርባል፤ እኛም «ጌታችን ነህ መሰከርን» እንላለን፦
7:172 ጌታህም ከአደም ልጆች ከጀርቦቻቸው *ዘሮቻቸውን ባወጣ”* እና «ጌታችሁ አይደለሁምን» ሲል በነፍሶቻቸው ላይ *”ባስመሰከራቸው”* ጊዜ የኾነውን አስታውስ፡፡ *«ጌታችን ነህ መሰከርን»* አሉ፡፡ «በትንሣኤ ቀን ከዚህ ኪዳን ዘንጊዎች ነበርን እንዳትሉ፡፡» وَإِذْ أَخَذَ رَبُّكَ مِنۢ بَنِىٓ ءَادَمَ مِن ظُهُورِهِمْ ذُرِّيَّتَهُمْ وَأَشْهَدَهُمْ عَلَىٰٓ أَنفُسِهِمْ أَلَسْتُ بِرَبِّكُمْ ۖ قَالُوا۟ بَلَىٰ ۛ شَهِدْنَآ ۛ أَن تَقُولُوا۟ يَوْمَ ٱلْقِيَٰمَةِ إِنَّا كُنَّا عَنْ هَٰذَا غَٰفِلِينَ
አላህ ስንፈጠር በማስመስከር ቃል ያስገባን እርሱ ብቻ ጌታ ሆኖ እንድናመልከው ነው፤ ይህ አምልኮ ኢስላም ይባላል፤ እኛም ሙስሊሞች ነን፤ “ጌታችን ነህ መሰከርን” ብለናል፤ አላህ የሰውን ዘር የፈጠረው ከጀርባ እና ከእርግብግብቶች መካከል የሚወጣ ከሆነ ተስፈንጣሪ ውሃ “Spurt of water” ሲሆን፤ ይህም ውሃ ሲመን”semen” ነው፦
32:7-8 ያ የፈጠረውን ነገር ሁሉ ያሳመረው፣ የሰውንም ፍጥረት ከጭቃ የጀመረው፥ ነው፤ ከዚያም *“ዘሮቹን፣ ከተጣለለ ከደካማ ውሃ”* ያደረገ፣ ነው።
86:5 ሰውም ከምን እንደተፈጠረ ይመልከት። ከተስፈንጣሪ ውሃ ተፈጠረ። *”ከጀርባ እና ከእርግብግብቶች መካከል የሚወጣ ከሆነ ውሃ”*።
ይህ ተስፈንጣሪ ውሃ የፍትወት ጠብታ”sperm-drop” ሆኖ ከሴት የእንቁላል ህዋስ ጋር ሲገናኝ ሰው ይፈጠራል፦
53:45-46 እርሱም ሁለቱን ዓይነቶች ወንድና ሴትን ፈጠረ። *”ከፍትወት ጠብታ በማኅፀን ውስጥ በምትፈስስ ጊዜ”*፤
56:57-59 እኛ ፈጠርናችሁ፤ አታምኑምን? *”በማኅፀኖች የምታፈሱትን አያችሁትን”*? እናንተ ትፈጥሩታላችሁን? ወይስ እኛ ፈጣሪዎቹ ነን።
እንግዲህ የሰው ልጅ ሙስሊም ሆኖ የሚፈጠረው በዚህ ጊዜ ነው፤ ነብያችንም”ﷺ” ኢስላም የተፈጥሮ ሃይማኖት መሆኑን እንዲህ ያስረዱናል፦
ኢማም ሙስሊም መፅሐፍ 040, ቁጥር 6853
ከአቢ ሁረይራህ”ረ.ዐ” እንደተላለፈው የአላህ መልእክተኛ”ﷺ” እንዲህ አሉ፡- *“ማንም የሚወለድ ሰው “በፊጥራ”(በኢስላም) ላይ ሆኖ እንጂ አይወለድም”*፤ ወላጆቹ ግን አይሁዳዊ ያደርጉታል፣ ወይም ክርስቲያን ያደርጉታል ወይም ዞሮስተርያን ያደርጉታል እንጂ عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ رَضِيَ اللَّهُ عَنْهُ، قَالَ: قَالَ النَّبِيُّ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ: «كُلُّ مَوْلُودٍ يُولَدُ عَلَى الفِطْرَةِ، فَأَبَوَاهُ يُهَوِّدَانِهِ، أَوْ يُنَصِّرَانِهِ، أَوْ يُمَجِّسَانِهِ….» رواه البخاري ومسلم وغيرهما.፤
ሙስሊም ሲፈጠር የሚጠመቅበት የሃይማኖት ጥምቀት ኢስላም ነው፣ ይህ ጥምቀት በ 40 ቀን ወይም በ 80 ቀን አሊያም ለአቅመ አዳም እና ለአቅመ ሔዋን ስንደሪስ የምንጠመቀው ሳይሆን የተፈጥሮ ጥምቀት ነው፣ አጥማቂውን ቄስ አሊያም ፓስተር ሳይሆን አላህ ነው፦
2:138َ የአላህን *”የተፈጥሮ ጥምቀት”* ያዙ፡፡ በማጥመቅም ከአላህ ይበልጥ ያማረ ማነው? ማንም የለም፤ እኛም *”ለእርሱ ብቻ ተገዢዎች ነን”* በሉ። صِبْغَةَ اللَّـهِ ۖ وَمَنْ أَحْسَنُ مِنَ اللَّـهِ صِبْغَةً ۖ وَنَحْنُ لَهُ عَابِدُون ፡፡
“ጅኒ”
“ጂን” جِنّ የሚለው ቃል “ጀንነ” جَنَّ “ተሰወረ” ወይም “ተደበቀ” ከሚል ግስ የመጣ ሲሆን “ስውር” ወይም “ድብቅ” ማለት ነው፤ “ጅኒ” جني ደግሞ የጂን ብዙ ቁጥር ነው፤ ጂኒዎች የተፈጠሩት ከሰው በፊት ነው፦
15:27 *”ጃንንም”* ከሰው በፊት ከእሳት ነበልባል ፈጠርነው፡፡ وَٱلْجَآنَّ خَلَقْنَٰهُ مِن قَبْلُ مِن نَّارِ ٱلسَّمُومِ
2:21 እናንተ ሰዎች ሆይ! የፈጠራችሁን እነዚያንም ከእናንተ በፊት *”የነበሩትን”* የፈጠረውን ጌታችሁን አምልኩ፤ يَٰٓأَيُّهَا ٱلنَّاسُ ٱعْبُدُوا۟ رَبَّكُمُ ٱلَّذِى خَلَقَكُمْ وَٱلَّذِينَ مِن قَبْلِكُمْ لَعَلَّكُمْ تَتَّقُونَ
26:184 «ያንንም የፈጠራችሁን *”የቀድሞዎቹንም ፍጡሮች”* የፈጠረውን ፍሩ፡፡» وَٱتَّقُوا۟ ٱلَّذِى خَلَقَكُمْ وَٱلْجِبِلَّةَ ٱلْأَوَّلِينَ
ጂኒዎች እንደ ሰው ነፃ ፈቃድ ያላቸው ፍጡሮች ናቸው፤ እንደ ሰው አላህ ሊያመልኩ የተፈጠሩት ፍጡሮች ናቸው፤ ከእነርሱ መካከል በነጻ ፈቃዳቸው በአላህ ላይ የሚያሻርኩ በደለኞች አሉ፤ አላህን በብቸኝነት የሚያመልኩ ሙስሊሞች አሉ፦
51:56 *″ጂን”* እና ሰውን *”ሊያመልኩኝ”* እንጅ ለሌላ አልፈጠርኳቸውም። وَمَا خَلَقْتُ ٱلْجِنَّ وَٱلْإِنسَ إِلَّا لِيَعْبُدُونِ
72፥14 «እኛም ከእኛ ውስጥ *”ሙስሊሞች አሉ”*፡፡ ከእኛም ውስጥ *”በዳዮች አሉ”*፡፡ የሰለሙም ሰዎች እነዚያ ቅንን መንገድ መረጡ፡፡» وَأَنَّا مِنَّا ٱلْمُسْلِمُونَ وَمِنَّا ٱلْقَٰسِطُونَ ۖ فَمَنْ أَسْلَمَ فَأُو۟لَٰٓئِكَ تَحَرَّوْا۟ رَشَدًۭا
ነጥብ ሶስት
“ሰዎች”
ሰው ሲፈጠር የሚፈጠርበት አላማ አንዱን አምላክ አላህን በብቸኝነት እንዲያመልክ ብቻ ነው፤ አላህ ሰዎችን የፈጠረበት ሃይማኖት ኢስላም ብቻ ነው፦
51:56 ጂን እና *”ሰውን ሊያመልኩኝ”* እንጅ ለሌላ አልፈጠርኳቸውም። وَمَا خَلَقْتُ ٱلْجِنَّ وَٱلْإِنسَ إِلَّا لِيَعْبُدُونِ
30፥30 ወደ እውነት ተዘንባይ ኾነህም ፊትህን ለሃይማኖት ቀጥ አድርግ፡፡ የአላህን ፍጥረት ያችን *”አላህ ሰዎችን በእርስዋ ላይ የፈጠረባትን ሃይማኖት ያዟት”*፡፡ فَأَقِمْ وَجْهَكَ لِلدِّينِ حَنِيفًۭا ۚ فِطْرَتَ ٱللَّهِ ٱلَّتِى فَطَرَ ٱلنَّاسَ عَلَيْهَا ۚ لَا تَبْدِيلَ لِخَلْقِ ٱللَّهِ ۚ ذَٰلِكَ ٱلدِّينُ ٱلْقَيِّمُ وَلَٰكِنَّ أَكْثَرَ ٱلنَّاسِ لَا يَعْلَمُونَ
3፥19 አላህ ዘንድ የተወደደ ሃይማኖት *“ኢስላም”* ብቻ ነው፡፡ إِنَّ ٱلدِّينَ عِندَ ٱللَّهِ ٱلْإِسْلَٰمُ
ኢስላም የተፈጥሮ ሀይማኖት፤ አላህ ከአደም ልጆች ከጀርቦቻቸው ዘሮቻቸውን ባወጣ ጊዜ «ጌታችሁ አይደለሁምን?» በማለት ጥያቄ ያቀርባል፤ እኛም «ጌታችን ነህ መሰከርን» እንላለን፦
7:172 ጌታህም ከአደም ልጆች ከጀርቦቻቸው *ዘሮቻቸውን ባወጣ”* እና «ጌታችሁ አይደለሁምን» ሲል በነፍሶቻቸው ላይ *”ባስመሰከራቸው”* ጊዜ የኾነውን አስታውስ፡፡ *«ጌታችን ነህ መሰከርን»* አሉ፡፡ «በትንሣኤ ቀን ከዚህ ኪዳን ዘንጊዎች ነበርን እንዳትሉ፡፡» وَإِذْ أَخَذَ رَبُّكَ مِنۢ بَنِىٓ ءَادَمَ مِن ظُهُورِهِمْ ذُرِّيَّتَهُمْ وَأَشْهَدَهُمْ عَلَىٰٓ أَنفُسِهِمْ أَلَسْتُ بِرَبِّكُمْ ۖ قَالُوا۟ بَلَىٰ ۛ شَهِدْنَآ ۛ أَن تَقُولُوا۟ يَوْمَ ٱلْقِيَٰمَةِ إِنَّا كُنَّا عَنْ هَٰذَا غَٰفِلِينَ
አላህ ስንፈጠር በማስመስከር ቃል ያስገባን እርሱ ብቻ ጌታ ሆኖ እንድናመልከው ነው፤ ይህ አምልኮ ኢስላም ይባላል፤ እኛም ሙስሊሞች ነን፤ “ጌታችን ነህ መሰከርን” ብለናል፤ አላህ የሰውን ዘር የፈጠረው ከጀርባ እና ከእርግብግብቶች መካከል የሚወጣ ከሆነ ተስፈንጣሪ ውሃ “Spurt of water” ሲሆን፤ ይህም ውሃ ሲመን”semen” ነው፦
32:7-8 ያ የፈጠረውን ነገር ሁሉ ያሳመረው፣ የሰውንም ፍጥረት ከጭቃ የጀመረው፥ ነው፤ ከዚያም *“ዘሮቹን፣ ከተጣለለ ከደካማ ውሃ”* ያደረገ፣ ነው።
86:5 ሰውም ከምን እንደተፈጠረ ይመልከት። ከተስፈንጣሪ ውሃ ተፈጠረ። *”ከጀርባ እና ከእርግብግብቶች መካከል የሚወጣ ከሆነ ውሃ”*።
ይህ ተስፈንጣሪ ውሃ የፍትወት ጠብታ”sperm-drop” ሆኖ ከሴት የእንቁላል ህዋስ ጋር ሲገናኝ ሰው ይፈጠራል፦
53:45-46 እርሱም ሁለቱን ዓይነቶች ወንድና ሴትን ፈጠረ። *”ከፍትወት ጠብታ በማኅፀን ውስጥ በምትፈስስ ጊዜ”*፤
56:57-59 እኛ ፈጠርናችሁ፤ አታምኑምን? *”በማኅፀኖች የምታፈሱትን አያችሁትን”*? እናንተ ትፈጥሩታላችሁን? ወይስ እኛ ፈጣሪዎቹ ነን።
እንግዲህ የሰው ልጅ ሙስሊም ሆኖ የሚፈጠረው በዚህ ጊዜ ነው፤ ነብያችንም”ﷺ” ኢስላም የተፈጥሮ ሃይማኖት መሆኑን እንዲህ ያስረዱናል፦
ኢማም ሙስሊም መፅሐፍ 040, ቁጥር 6853
ከአቢ ሁረይራህ”ረ.ዐ” እንደተላለፈው የአላህ መልእክተኛ”ﷺ” እንዲህ አሉ፡- *“ማንም የሚወለድ ሰው “በፊጥራ”(በኢስላም) ላይ ሆኖ እንጂ አይወለድም”*፤ ወላጆቹ ግን አይሁዳዊ ያደርጉታል፣ ወይም ክርስቲያን ያደርጉታል ወይም ዞሮስተርያን ያደርጉታል እንጂ عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ رَضِيَ اللَّهُ عَنْهُ، قَالَ: قَالَ النَّبِيُّ صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ: «كُلُّ مَوْلُودٍ يُولَدُ عَلَى الفِطْرَةِ، فَأَبَوَاهُ يُهَوِّدَانِهِ، أَوْ يُنَصِّرَانِهِ، أَوْ يُمَجِّسَانِهِ….» رواه البخاري ومسلم وغيرهما.፤
ሙስሊም ሲፈጠር የሚጠመቅበት የሃይማኖት ጥምቀት ኢስላም ነው፣ ይህ ጥምቀት በ 40 ቀን ወይም በ 80 ቀን አሊያም ለአቅመ አዳም እና ለአቅመ ሔዋን ስንደሪስ የምንጠመቀው ሳይሆን የተፈጥሮ ጥምቀት ነው፣ አጥማቂውን ቄስ አሊያም ፓስተር ሳይሆን አላህ ነው፦
2:138َ የአላህን *”የተፈጥሮ ጥምቀት”* ያዙ፡፡ በማጥመቅም ከአላህ ይበልጥ ያማረ ማነው? ማንም የለም፤ እኛም *”ለእርሱ ብቻ ተገዢዎች ነን”* በሉ። صِبْغَةَ اللَّـهِ ۖ وَمَنْ أَحْسَنُ مِنَ اللَّـهِ صِبْغَةً ۖ وَنَحْنُ لَهُ عَابِدُون ፡፡
መደምደሚያ
እምላካችን አላህ ሰዎች ወደ ኢስላም እንዲመጡ ነብያት ልኳል፤ ሙስሊሞች ሳንሆን እንዳንሞት ነግሮናል፦
3፥102 እናንተ ያመናችሁ ሆይ! አላህን ተገቢውን መጠንቀቅ ተጠንቀቁት፡፡ እናንተም *”ሙስሊሞች ኾናችሁ እንጅ አትሙቱ”* ፡፡ يَٰٓأَيُّهَا ٱلَّذِينَ ءَامَنُوا۟ ٱتَّقُوا۟ ٱللَّهَ حَقَّ تُقَاتِهِۦ وَلَا تَمُوتُنَّ إِلَّا وَأَنتُم مُّسْلِمُونَ
ከሞትን በኃላ ግን በትንሣኤ ቀን ሙስሊሞች በሆንን ብሎ መቆጨት እርባና የለውምና እናንተ ከሃድያን ሆይ በተውበት ወደ አላህ ተመለሱ፦
15፥2 እነዚያ የካዱት በትንሣኤ ቀን *”ሙስሊሞች በኾኑ ኖሩ በብዛት ይመኛሉ”*፡፡ رُّبَمَا يَوَدُّ ٱلَّذِينَ كَفَرُوا۟ لَوْ كَانُوا۟ مُسْلِمِينَ
✍ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሰላሙ አለይኩም
እምላካችን አላህ ሰዎች ወደ ኢስላም እንዲመጡ ነብያት ልኳል፤ ሙስሊሞች ሳንሆን እንዳንሞት ነግሮናል፦
3፥102 እናንተ ያመናችሁ ሆይ! አላህን ተገቢውን መጠንቀቅ ተጠንቀቁት፡፡ እናንተም *”ሙስሊሞች ኾናችሁ እንጅ አትሙቱ”* ፡፡ يَٰٓأَيُّهَا ٱلَّذِينَ ءَامَنُوا۟ ٱتَّقُوا۟ ٱللَّهَ حَقَّ تُقَاتِهِۦ وَلَا تَمُوتُنَّ إِلَّا وَأَنتُم مُّسْلِمُونَ
ከሞትን በኃላ ግን በትንሣኤ ቀን ሙስሊሞች በሆንን ብሎ መቆጨት እርባና የለውምና እናንተ ከሃድያን ሆይ በተውበት ወደ አላህ ተመለሱ፦
15፥2 እነዚያ የካዱት በትንሣኤ ቀን *”ሙስሊሞች በኾኑ ኖሩ በብዛት ይመኛሉ”*፡፡ رُّبَمَا يَوَدُّ ٱلَّذِينَ كَفَرُوا۟ لَوْ كَانُوا۟ مُسْلِمِينَ
✍ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://tttttt.me/Wahidcom
ወሰላሙ አለይኩም
ኢስላም እና ነብያት
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
21፥25 ከአንተ በፊትም እነሆ *”ከእኔ ሌላ አምላክ የለምና አምልኩኝ”* በማለት ወደ እርሱ የምናወርድለት ቢኾን እንጅ ከመልክተኛ አንድንም አልላክንም፡፡ وَمَآ أَرْسَلْنَا مِن قَبْلِكَ مِن رَّسُولٍ إِلَّا نُوحِىٓ إِلَيْهِ أَنَّهُۥ لَآ إِلَٰهَ إِلَّآ أَنَا۠ فَٱعْبُدُونِ
መግቢያ
የኢስላምን መሰረትና ውቅር፣ ዋልታና ማገር፣ ጥልቀትና ስፋት፣ ድርና ማግ “ላ-ኢላሀ ኢልለሏህ” لا اله الاّ الله ነው፣ የነብያት ዐቂዳህ አስኳሉ “ላ-ኢላሀ ኢልለሏህ” ነው፤ አላህ ጥንት ለነበሩት ነቢያቱ ወሕይ የሚያወርድላቸው የነበረው “ላ ኢላሃ ኢልላ አና” لَا إِلَٰهَ إِلَّا أَنَا ማለትም “ከኔ በቀር ሌላ አምላክ የለም” የሚል ነው፦
21፥25 ከአንተ በፊትም እነሆ *”ከእኔ ሌላ አምላክ የለምና አምልኩኝ”* በማለት ወደ እርሱ የምናወርድለት ቢኾን እንጅ ከመልክተኛ አንድንም አልላክንም፡፡ وَمَآ أَرْسَلْنَا مِن قَبْلِكَ مِن رَّسُولٍ إِلَّا نُوحِىٓ إِلَيْهِ أَنَّهُۥ لَآ إِلَٰهَ إِلَّآ أَنَا۠ فَٱعْبُدُونِ
16፥2 ከባሮቹ በሚሻው ሰው ላይ መላእክትን ከራእይ ጋር በፈቃዱ ያወርዳል ከሓዲዎችን በቅጣት አስጠንቅቁ፤ እነሆ *”ከኔ በቀር ሌላ አምላክ የለም፤ ፍሩኝም”* ማለትን አስታውቁ በማለት ያወርዳል፡፡ يُنَزِّلُ ٱلْمَلَٰٓئِكَةَ بِٱلرُّوحِ مِنْ أَمْرِهِۦ عَلَىٰ مَن يَشَآءُ مِنْ عِبَادِهِۦٓ أَنْ أَنذِرُوٓا۟ أَنَّهُۥ لَآ إِلَٰهَ إِلَّآ أَنَا۠ فَٱتَّقُونِ
ወደ ሰዎች ሲልካቸውም “ማ ለኩም ሚን ኢላሂ ገይሩሁ” مَا لَكُمْ مِنْ إِلَٰهٍ غَيْرُهُ ማለትም “ከእርሱ በቀር ሌላ አምላክ የላችሁም” ብለው እንዲናገሩ ነው፦
23:32 በውስጣቸውም ከእነርሱ የኾነን መልክተኛ አላህን አምልኩ *”ከእርሱ በቀር ሌላ አምላክ የላችሁም”* مَا لَكُمْ مِنْ إِلَٰهٍ غَيْرُهُ አትጠነቀቁምን በማለት ላክን፡፡
7:59 ኑሕን ወደ ወገኖቹ በእርግጥ ላክነው፤ አላቸው፦ወገኖቼ ሆይ! አላህን አምልኩ፤ ለእናንተ *ከእርሱ በቀር ሌላ ምንም አምላክ የላችሁም* مَا لَكُمْ مِنْ إِلَٰهٍ غَيْرُهُ፤
11:50 ወደ ዓድም ወንድማቸውን ሁድን ላክን አላቸው ፦ ወገኖቼ ሆይ አላህን አምልኩ *ከእርሱ ሌላ በቀር ምንም አምላክ የላችሁም* مَا لَكُمْ مِنْ إِلَٰهٍ غَيْرُهُ ፤
11:61 ወደ ሠሙዶችም ወንድማቸውን ሷሊህን ላክን፤ ፦ሕዝቦቼ ሆይ አላህን አምልኩ፤ *ከእርሱ በቀር ሌላ ለናንተ አምላክ፣ የላችሁም* مَا لَكُمْ مِنْ إِلَٰهٍ غَيْرُهُ ፤
11:84 ወደ መድየንም ወንድማችውን ሹዐይብን፣ ላክን፤ አላቸው ሕዝቦቼ ሆይ! አላህን አምልኩ፤ *ከእርሱ በቀር ሌላ ለናንተ አምላክ የላችሁም* مَا لَكُمْ مِنْ إِلَٰهٍ غَيْرُهُ፤
ለናሙና ያክል ከላይ ያሉትን ጠቀስን እንጂ አላህ በየሕዝቡም ሁሉ ውስጥ እርሱን እንዲያመልኩ እና ጣዖትንም እንዲርቁ መልክተኛን በእርግጥ ልኳል፤ ከእነርሱ አላህ ለእኛ አስፈላጊ ያላቸውን በነብያችን”ﷺ” ላይ የተረካቸው አሉ፤ ከእነርሱም ለእኛ አስፈላጊ ያልሆኑትን በነብያችን”ﷺ” ላይ ያልተረካቸው አሉ፦
16:36 በየሕዝቡም ሁሉ ውስጥ *”አላህን አምልኩ፤ ጣዖትንም ራቁ”*፤ በማለት መልክተኛን በእርግጥ ልከናል፤ وَلَقَدْ بَعَثْنَا فِى كُلِّ أُمَّةٍۢ رَّسُولًا أَنِ ٱعْبُدُوا۟ ٱللَّهَ وَٱجْتَنِبُوا۟ ٱلطَّٰغُوتَ
40:78 *”ከአንተ በፊትም መልክተኞችን በእርግጥ ልከናል፤ ከእነርሱ በአንተ ላይ የተረክንልህ አለ፤ ከእነርሱም በአንተ ላይ ያልተረክነው አለ”*፤ وَلَقَدْ أَرْسَلْنَا رُسُلًۭا مِّن قَبْلِكَ مِنْهُم مَّن قَصَصْنَا عَلَيْكَ وَمِنْهُم مَّن لَّمْ نَقْصُصْ عَلَيْكَ
እነዚህ ነብያት አምላካችን አላህ ወሕይ የሚያወርድላቸው ጭብጥ ይህ እስልምና ነው፤ እስቲ እነዚህ ነብያት በተናጥል እንመልከት፦
ነጥብ አንድ
“አደም”
አላህ ወደ አደም ወህይ አውርዷል፤ አደምም ከእርሱ ቃላት ተቀብሏል፦
20:115 ወደ አደምም ከዚህ በፊት *“ኪዳንን በእርግጥ አወረድን”*፤ ረሳም፡፡ ለእርሱም ቆራጥነትን አላገኘንለትም وَلَقَدْ عَهِدْنَآ إِلَىٰٓ ءَادَمَ مِن قَبْلُ فَنَسِىَ وَلَمْ نَجِدْ لَهُۥ عَزْمًۭا ፡፡
2:37 አደምም *“ከጌታው ቃላትን ተቀበለ”*፡፡ በርሱ ላይም ጌታው ጸጸትን በመቀበል ተመለሰለት፤ እነሆ እርሱ ጸጸትን ተቀባይ አዛኝ ነውና فَتَلَقَّىٰٓ ءَادَمُ مِن رَّبِّهِۦ كَلِمَٰتٍۢ فَتَابَ عَلَيْهِ ۚ إِنَّهُۥ هُوَ ٱلتَّوَّابُ ٱلرَّحِيمُ ፡፡
ወደ ነብያት የሚወርደው የኢስላም አስኳሉ የሆነው “ላ ኢላሃ ኢልለሏህ” ከሆነ ነብያችንም”ﷺ” በግልፅና በማያሻማ አደም የመጀመሪያው ነብይ መሆኑን ነግረውናል፦
ሙስነድ አህመድ መጽሐፍ 5, ሐዲስ 1781
አቡ ዘር ነብዩን የአላህ ነብይ”ﷺ” ሆይ የመጀመሪያው ነብይ ማን ነው? ብሎ ጠየቃቸው፤ ነብዩም አደም”አ.ሰ.” ነው አሉ፤ እርሱም፦ እርሱ ነብይ ነበረ? ብሎ ጠየቀ፤ ነብዩም፦ አዎ አላህ በእጁ የፈጠረውና ሩህ የነፋበት ነበር፤ አሉት قال : قلت : يا نبي الله ! فأي الأنبياء كان أول ? قال : آدم عليه السلام . قال : قلت : يا نبي الله ! أو نبي كان آدم ? قال : نعم , نبي مكلم , خلقه الله بيده , ثم نفخ فيه من روحه ።
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
21፥25 ከአንተ በፊትም እነሆ *”ከእኔ ሌላ አምላክ የለምና አምልኩኝ”* በማለት ወደ እርሱ የምናወርድለት ቢኾን እንጅ ከመልክተኛ አንድንም አልላክንም፡፡ وَمَآ أَرْسَلْنَا مِن قَبْلِكَ مِن رَّسُولٍ إِلَّا نُوحِىٓ إِلَيْهِ أَنَّهُۥ لَآ إِلَٰهَ إِلَّآ أَنَا۠ فَٱعْبُدُونِ
መግቢያ
የኢስላምን መሰረትና ውቅር፣ ዋልታና ማገር፣ ጥልቀትና ስፋት፣ ድርና ማግ “ላ-ኢላሀ ኢልለሏህ” لا اله الاّ الله ነው፣ የነብያት ዐቂዳህ አስኳሉ “ላ-ኢላሀ ኢልለሏህ” ነው፤ አላህ ጥንት ለነበሩት ነቢያቱ ወሕይ የሚያወርድላቸው የነበረው “ላ ኢላሃ ኢልላ አና” لَا إِلَٰهَ إِلَّا أَنَا ማለትም “ከኔ በቀር ሌላ አምላክ የለም” የሚል ነው፦
21፥25 ከአንተ በፊትም እነሆ *”ከእኔ ሌላ አምላክ የለምና አምልኩኝ”* በማለት ወደ እርሱ የምናወርድለት ቢኾን እንጅ ከመልክተኛ አንድንም አልላክንም፡፡ وَمَآ أَرْسَلْنَا مِن قَبْلِكَ مِن رَّسُولٍ إِلَّا نُوحِىٓ إِلَيْهِ أَنَّهُۥ لَآ إِلَٰهَ إِلَّآ أَنَا۠ فَٱعْبُدُونِ
16፥2 ከባሮቹ በሚሻው ሰው ላይ መላእክትን ከራእይ ጋር በፈቃዱ ያወርዳል ከሓዲዎችን በቅጣት አስጠንቅቁ፤ እነሆ *”ከኔ በቀር ሌላ አምላክ የለም፤ ፍሩኝም”* ማለትን አስታውቁ በማለት ያወርዳል፡፡ يُنَزِّلُ ٱلْمَلَٰٓئِكَةَ بِٱلرُّوحِ مِنْ أَمْرِهِۦ عَلَىٰ مَن يَشَآءُ مِنْ عِبَادِهِۦٓ أَنْ أَنذِرُوٓا۟ أَنَّهُۥ لَآ إِلَٰهَ إِلَّآ أَنَا۠ فَٱتَّقُونِ
ወደ ሰዎች ሲልካቸውም “ማ ለኩም ሚን ኢላሂ ገይሩሁ” مَا لَكُمْ مِنْ إِلَٰهٍ غَيْرُهُ ማለትም “ከእርሱ በቀር ሌላ አምላክ የላችሁም” ብለው እንዲናገሩ ነው፦
23:32 በውስጣቸውም ከእነርሱ የኾነን መልክተኛ አላህን አምልኩ *”ከእርሱ በቀር ሌላ አምላክ የላችሁም”* مَا لَكُمْ مِنْ إِلَٰهٍ غَيْرُهُ አትጠነቀቁምን በማለት ላክን፡፡
7:59 ኑሕን ወደ ወገኖቹ በእርግጥ ላክነው፤ አላቸው፦ወገኖቼ ሆይ! አላህን አምልኩ፤ ለእናንተ *ከእርሱ በቀር ሌላ ምንም አምላክ የላችሁም* مَا لَكُمْ مِنْ إِلَٰهٍ غَيْرُهُ፤
11:50 ወደ ዓድም ወንድማቸውን ሁድን ላክን አላቸው ፦ ወገኖቼ ሆይ አላህን አምልኩ *ከእርሱ ሌላ በቀር ምንም አምላክ የላችሁም* مَا لَكُمْ مِنْ إِلَٰهٍ غَيْرُهُ ፤
11:61 ወደ ሠሙዶችም ወንድማቸውን ሷሊህን ላክን፤ ፦ሕዝቦቼ ሆይ አላህን አምልኩ፤ *ከእርሱ በቀር ሌላ ለናንተ አምላክ፣ የላችሁም* مَا لَكُمْ مِنْ إِلَٰهٍ غَيْرُهُ ፤
11:84 ወደ መድየንም ወንድማችውን ሹዐይብን፣ ላክን፤ አላቸው ሕዝቦቼ ሆይ! አላህን አምልኩ፤ *ከእርሱ በቀር ሌላ ለናንተ አምላክ የላችሁም* مَا لَكُمْ مِنْ إِلَٰهٍ غَيْرُهُ፤
ለናሙና ያክል ከላይ ያሉትን ጠቀስን እንጂ አላህ በየሕዝቡም ሁሉ ውስጥ እርሱን እንዲያመልኩ እና ጣዖትንም እንዲርቁ መልክተኛን በእርግጥ ልኳል፤ ከእነርሱ አላህ ለእኛ አስፈላጊ ያላቸውን በነብያችን”ﷺ” ላይ የተረካቸው አሉ፤ ከእነርሱም ለእኛ አስፈላጊ ያልሆኑትን በነብያችን”ﷺ” ላይ ያልተረካቸው አሉ፦
16:36 በየሕዝቡም ሁሉ ውስጥ *”አላህን አምልኩ፤ ጣዖትንም ራቁ”*፤ በማለት መልክተኛን በእርግጥ ልከናል፤ وَلَقَدْ بَعَثْنَا فِى كُلِّ أُمَّةٍۢ رَّسُولًا أَنِ ٱعْبُدُوا۟ ٱللَّهَ وَٱجْتَنِبُوا۟ ٱلطَّٰغُوتَ
40:78 *”ከአንተ በፊትም መልክተኞችን በእርግጥ ልከናል፤ ከእነርሱ በአንተ ላይ የተረክንልህ አለ፤ ከእነርሱም በአንተ ላይ ያልተረክነው አለ”*፤ وَلَقَدْ أَرْسَلْنَا رُسُلًۭا مِّن قَبْلِكَ مِنْهُم مَّن قَصَصْنَا عَلَيْكَ وَمِنْهُم مَّن لَّمْ نَقْصُصْ عَلَيْكَ
እነዚህ ነብያት አምላካችን አላህ ወሕይ የሚያወርድላቸው ጭብጥ ይህ እስልምና ነው፤ እስቲ እነዚህ ነብያት በተናጥል እንመልከት፦
ነጥብ አንድ
“አደም”
አላህ ወደ አደም ወህይ አውርዷል፤ አደምም ከእርሱ ቃላት ተቀብሏል፦
20:115 ወደ አደምም ከዚህ በፊት *“ኪዳንን በእርግጥ አወረድን”*፤ ረሳም፡፡ ለእርሱም ቆራጥነትን አላገኘንለትም وَلَقَدْ عَهِدْنَآ إِلَىٰٓ ءَادَمَ مِن قَبْلُ فَنَسِىَ وَلَمْ نَجِدْ لَهُۥ عَزْمًۭا ፡፡
2:37 አደምም *“ከጌታው ቃላትን ተቀበለ”*፡፡ በርሱ ላይም ጌታው ጸጸትን በመቀበል ተመለሰለት፤ እነሆ እርሱ ጸጸትን ተቀባይ አዛኝ ነውና فَتَلَقَّىٰٓ ءَادَمُ مِن رَّبِّهِۦ كَلِمَٰتٍۢ فَتَابَ عَلَيْهِ ۚ إِنَّهُۥ هُوَ ٱلتَّوَّابُ ٱلرَّحِيمُ ፡፡
ወደ ነብያት የሚወርደው የኢስላም አስኳሉ የሆነው “ላ ኢላሃ ኢልለሏህ” ከሆነ ነብያችንም”ﷺ” በግልፅና በማያሻማ አደም የመጀመሪያው ነብይ መሆኑን ነግረውናል፦
ሙስነድ አህመድ መጽሐፍ 5, ሐዲስ 1781
አቡ ዘር ነብዩን የአላህ ነብይ”ﷺ” ሆይ የመጀመሪያው ነብይ ማን ነው? ብሎ ጠየቃቸው፤ ነብዩም አደም”አ.ሰ.” ነው አሉ፤ እርሱም፦ እርሱ ነብይ ነበረ? ብሎ ጠየቀ፤ ነብዩም፦ አዎ አላህ በእጁ የፈጠረውና ሩህ የነፋበት ነበር፤ አሉት قال : قلت : يا نبي الله ! فأي الأنبياء كان أول ? قال : آدم عليه السلام . قال : قلت : يا نبي الله ! أو نبي كان آدم ? قال : نعم , نبي مكلم , خلقه الله بيده , ثم نفخ فيه من روحه ።