TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63.1K photos
1.62K videos
217 files
4.39K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ንብ ኢንተርናሽናል ባንክ ንብተራ ኦንላይን መተግበሪያን ይፋ አደረገ !

ንብ ኢንተርናሽናል ባንክ አዲስ ይፋ ባደረገው የሦስት ዓመት ስትራቴጂ ዕቅድና የአምስት ዓመት ፍኖተ ካርታ ውስጥ ካቀዳቸው ዋና ዋና ተግባራት መካከል አንዱ የሆነውን ንብተራ ኦንላይን መተግበሪያ የማብሰሪያ መርሐ ግብር አካሄደ፡፡

ይህ ለደንበኞች የተሟላ፣ ምቹ፣ ቀላልና ቀልጣፋ አገልግሎት መስጠት የሚያስችለው ንብተራ ኦንላይን ሱፐር አፕ መተግበሪያ ከሐምሌ 05 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ሥራ ላይ እንዲውል ተደርጓል፡፡

መተግበርያው ደንበኞች ከባንክ አገልግልት በተጨማሪ ግብይቶችንና ክፍያዎችን በቀላሉ የእጅ ስልካቸውን ብቻ በመጠቀም መፈጸም እንደሚያስችላቸው በዚሁ የማብሰሪያ መርሃ ግብር ላይ ተገልጻል፡፡

በመርሐ ግብሩ ላይ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የባንኩ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ሔኖክ ከበደ ባስተላለፉት መልዕክት ባንኩ ለደንበኞቹ ዘመኑ የሚፈልገውን ቴክኖሎጂ በመጠቀም በውጤት የታጀበ አገልግልት ለመስጠት ጥረቱን አጠናክሮ እንደሚቀጥል የገለጹ ሲሆን አዲሱ የሦስት ዓመት ስትራቴጂክ ዕቅድም ከባለድርሻ አካላትና ከመላው ደንበኞቹ ጋር በመሆን የላቀ ውጤት የሚመዘገብበት ይሆናል ብለዋል፡፡

በመጨረሻም ይህ በውስጥ አቅም በልጽጎ ወደ ተግባር የገባው ንብተራ ኦንላይን መተግበሪያና አዲሱ የሶስት አመት ስትራቴጂክ ዕቅድ በአጭር ጊዜ ውስጥ በማበልፀግና ወደ ሥራ እንዲገባ ላደረጉ የባንኩ ሠራተኞችና የሥራ ኃላፊዎች ምሰጋና ያቀረቡት የባንኩ ሥራ አስፈጻሚ ቦርድ ሊ/መንበር አቶ ሺሰማ ሸዋነካ አዲሱ የስትራቴጂክ ዕቅድ ላይ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ምክክር አድርገውበትና ጸድቆ ወደ ሥራ መግባቱን አመልክተዋል፡፡

በይፋዊ የንብተራ ኦንላይን መተግበሪያ መርሃ ግብሩ ላይ የባንኩ ሥራ አስፈጻሚ ቦርድ አባላት፣ ደንበኞች፣ የባንኩ የስራ ኃላፊዎችና ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል፡፡

ለበለጠ መረጃ፡- https://www.nibbanksc.com/wp-content/uploads/2025/07/Press-release-NIB-Tera.pdf

ይሠሯል ከልብ፣ እንደ ንብ!

#Nib #DigitalBanking #Nibinternationalbank #nibbank #nibtera #nibsuperapp

Facebook  / Instagram / linkedin / X / Youtube / Tiktok / Website
370👏38😡16🥰7😢4😭3