TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63.1K photos
1.61K videos
217 files
4.38K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ጨዋ ሰራዊት ነው...

"ለደንብ ልብስ #ክፍያ የሚፈጽም ጨዋ ሠራዊት ነው!! የመከላከያ ሠራዊቱ አባላት የሚለብሱትን የደንብ ልብስ ሲያገኙ የነበረው በክፍያ ነበር ያውቃሉ ? አንድ የሠራዊቱ አባል የተሟላ የደንብ ልብስ ለማግኘት 900 ብር መክፈል ይጠበቅበት ነበር። ከሁሉም በላይ የሚያሳዝነው የመከላከያ ሠራዊቱ አባላት የወር ደሞዝ እጅግ ዝቅተኛ ሆኖ ሳለ ወታደራዊ የደንብ ልብሱን ለማሟላት ከደሞዙ ላይ ቆርጦ ይገዛ ነበር። ከዘንድሮው ዓመት ጀምሮ ግን ይህ እንዲቀር ተወስኖ ወታደራዊ የደንብ ልብሱን መንግስት በነፃ ማቅረብ ጀምሯል። እና ምን ለማለት ነው ?የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ሀገሪቱ ከፍ እና ዝቅ ባለችባቸው ጊዜያት በሙሉ በታላቅ ሀላፊነት ረግቶ የተቀመጠ ስነ ስርዓት ያለው ሰራዊት ነው ፤ ክብር ይገባዋል ሲባል ተረት ተረት አይደለም። እናም ለሠራዊቱ ከፍ ያለ ክብር ይገባል ፣ በተለይም ተራው የሠራዊቱን አባላት ሳስብ የበለጠ ከፍ ያለ ክብር እሰጣለው።" #YohannesAnberbir

@tsegabwolde @tikvahethiopia