TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63.2K photos
1.62K videos
218 files
4.4K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#UNITED_NATION

በትግራይ ያለውን የሰብዓዊ መብቶች የአያያዝ ሁኔታ የሚገመግሙ 2 ቡድኖቹ ወደ ክልሉ መግባታቸውን የተ.መ.ድ. የሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን አስታውቋል፡፡

የኮሚሽኑ ሃላፊ ሚሼል ባሸሌት የኢትዮጵያ መንግስት በተደረሰው ስምምነት መሰረት ያልተቆራረጡ ሰብዓዊ አቅርቦቶች እንዲኖሩ መፍቀዱን መቀበላቸውን አስታውቀዋል፡፡

ሆኖም ሰብዓዊ አቅርቦቶቹ በጦርነቱ የተጎዱ ሁሉንም የትግራይ አካባቢዎች ሊያዳርሱ እንደሚገባ ነው ያሳሰቡት፡፡

ሚሼል ባሸሌት ከዓለም አቀፍ ህግጋት በተጣረሰ መልኩ በተሰባሰበ ህዝብ ላይ የመተኮስ፣ ሆን ብሎ ንጹሃንን ዒላማ የማድረግ፣ የግድያ እና ዝርፊያ ድርጊቶች ጭምር እንዳሉ የሚያለክቱ መረጃዎች ደርሰውናል ብለዋል፡፡

ይህም በ2ቱም ወገኖች ንጹሃን ዜጎችን ለመጠበቅ አለመቻላቸውን የሚያሳይ ነው ያሉም ሲሆን ጦርነቱ በክልሉ ሰሜናዊ ፣ ማዕከላዊ እና ደቡባዊ አካባቢዎች ቀጥሏል መባሉ ይበልጥ እንዳሳሰባቸውም ነው ኮሚሽነሯ የገለጹት፡፡ #AlAin

የተመድ OHCHR ሙሉ መረጃ 👇
https://www.ohchr.org/EN/NewsEvents/Pages/DisplayNews.aspx?NewsID=26623&LangID=E

@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia