#Pagume
የአዲስ ዓመት አቀባበልን አስመልክቶ “ጳጉሜን ፌስቲቫል” በሚል ስያሜ የተዘጋጀው ፕሮግራም ካለፈው ዓርብ ጀምሮ በጉለሌ እፅዋት ማእከል በመካሄድ ላይ ነው። ዝግጅቱ በስድስቱም የጳጉሜን ቀናት በልዩ ልዩ ዝግጅቶች የሚከበር ሲሆን የተለያዩ የብሄር ብሄረሰቦች ባህላዊ ጨዋታዎች፣ ባህላዊ ምግቦች አሰራርና አመጋገብ፣ አልባሳት ኤግዚቢሽንና ሽያጭ፣ የፎቶ ግራፍ አውደ ርእይና ሌሎች በየክልሉ የሚገኙ ባህላዊ እሴቶች በዝግጅቱ ላይ ለእይታ እየቀረቡ ይገኛሉ። የ“ጳጉሜን ፌስቲቫል” ድርጅት ሀሳብ አፍላቂ፣ መስራችና ሥራ አስኪያጅ የሆኑት አቶ ሀይለአብ መረሳ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደገለፁት፣ የዚህ ድርጅት ሀሳብ የመነጨው የዛሬ አሥር ዓመት ገደማ ሲሆን ሁሉንም ነገር አጠናቅቆ ወደ ሥራ የገባው የዛሬ ሁለት ዓመት ነው። ይህ አሁን እየተከበረ ያለው ሁለተኛው “ጳጉሜን ፌስቲቫል” ዝግጅት ሲሆን ከአምናው ዘንድሮ በተሻለ ሁኔታና በድምቀት በመከበር ላይ ነው ብለዋል።
Via #EPA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የአዲስ ዓመት አቀባበልን አስመልክቶ “ጳጉሜን ፌስቲቫል” በሚል ስያሜ የተዘጋጀው ፕሮግራም ካለፈው ዓርብ ጀምሮ በጉለሌ እፅዋት ማእከል በመካሄድ ላይ ነው። ዝግጅቱ በስድስቱም የጳጉሜን ቀናት በልዩ ልዩ ዝግጅቶች የሚከበር ሲሆን የተለያዩ የብሄር ብሄረሰቦች ባህላዊ ጨዋታዎች፣ ባህላዊ ምግቦች አሰራርና አመጋገብ፣ አልባሳት ኤግዚቢሽንና ሽያጭ፣ የፎቶ ግራፍ አውደ ርእይና ሌሎች በየክልሉ የሚገኙ ባህላዊ እሴቶች በዝግጅቱ ላይ ለእይታ እየቀረቡ ይገኛሉ። የ“ጳጉሜን ፌስቲቫል” ድርጅት ሀሳብ አፍላቂ፣ መስራችና ሥራ አስኪያጅ የሆኑት አቶ ሀይለአብ መረሳ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደገለፁት፣ የዚህ ድርጅት ሀሳብ የመነጨው የዛሬ አሥር ዓመት ገደማ ሲሆን ሁሉንም ነገር አጠናቅቆ ወደ ሥራ የገባው የዛሬ ሁለት ዓመት ነው። ይህ አሁን እየተከበረ ያለው ሁለተኛው “ጳጉሜን ፌስቲቫል” ዝግጅት ሲሆን ከአምናው ዘንድሮ በተሻለ ሁኔታና በድምቀት በመከበር ላይ ነው ብለዋል።
Via #EPA
@tsegabwolde @tikvahethiopia