TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63.2K photos
1.62K videos
218 files
4.4K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#ItsMyDam #ItsOurDam #GERD

የኅዳሴ ግድብ ድርድር ሁሉም ወገኖች መደመጣቸውን፣ አሜሪካም ወገንተኛ አለመሆኗን ለማረጋገጥ ምን እያደረጋችሁ ነው ተብለው የተጠየቁት የአሜሪካ ግምዣ ቤት ሴክሬታሪ ስቴቨን ምኑችን ጥያቄውን በቀጥታ ሳይመልሱ ቀርተዋል።

የኔቫዳው የኮንግረስ አባል ስቴቨን ሖርስፎርድ ሚዛናዊ ብትሆኑ ኢትዮጵያ ወደ ድርድሩ ልትመለስ ትችላለች ብዬ አስባለሁ ሲሉ ለምኑችን ነግረዋቸዋል።

ከግብጽ በተጨማሪ ሱዳን ከስምምነት ሳይደረስ ግድቡ በውኃ ሊሞላ አይገባም የሚል አቋም እንዳላት ምኑችን በአሜሪካ ኮንግረስ Ways & Means Committee ኮሚቴ ተናግረዋል። ኮሚቴው ከውጭ ግንኙነት ጋር የማይቀራረብ የመንግሥት በጀት ላይ አተኩሮ የሚሰራ ነው።

#EsheteBekele #LamFilmona

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
👍1