TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63.1K photos
1.62K videos
217 files
4.39K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ATTENTION🚨

ከፍተኛ ጥንቃቄ የሚያስፈልገው መልዕክት !

በኢትዮጵያ በርካታ አካባቢዎች ለአብነትም አዋሽ ወንዝን ተከትሎ የሚኖሩ ከመካከለኛው የሀገሪቱ ክፍል ከኦሮሚያ ክልል ከደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን ወረዳዎች ጀምሮ እስከ ታችኛው አዋሽ አካባቢዎች በተለይም ፦
- በአፋር ክልል በአዋሽ ወንዝ ዳር የሚገኙ ወረዳዎች፣
- በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ዳሰች ወረዳ ሆሞራቴ ከተማን ጨምሮ፣
- በጋምቤላ ክልል ጋምቤላ ከተማ እና ሌሎች በባሮ ወንዝ ተጋላጭ ሊሆኑ የሚችሉት ወረዳዎች፣
- በዋቤ ሸበሌ ወንዝ ሊጠቁ የሚችሉ የሶማሌ ክልል ወረዳዎች፣
- በአማራ ክልል በጣና ሀይቅ አቅራቢያ የሚገኙ አንዳንድ የክልሉ አካባቢዎች በዚህ የክረምት ወቅት ለጎርፍ አደጋ ተጋላጭ እና የተጎጂ ይሆናሉ ተብሎ ተለይቷል፡፡

በተጨማሪም የክረምት ወቅት ዝናብ ተጠቃሚ የአገሪቱ አከባቢዎችና ከተሞች በሙሉ ከባድ ዝናብ በሚኖርበት ወቅት በየትኛዉም ጊዜ በቅፅበታዊ ጎርፍ አደጋ ሊጠቁ የሚችሉ ሲሆን በአንዳንድ አካባቢዎች ባልታሰቡ ክስተቶች እና ትናንሽ ወንዞች ምክንያት የጎርፍ አደጋ ሊከሰት ይችላል፡፡

የ2017 ክረምት ወቅት የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት እና ዓለም አቀፍ ትንበያዎች እንደሚያመለክቱት በእነዚህ ክልሎች እና ሌሎችም ከመደበኛ በላይ የሆነ ዝናብ የሚጠበቅ ነዉ፡፡

የጎርፍ አደጋ ስጋት ተጋላጭ የሆኑ አካባቢዎች የትኞቹ ናቸው ?

➡️ በተፋሰስና ወንዝ ዳርቻ (አዋሽ ፣ ዋቤ ሸበሌ፣ ተከዜ፣ ባሮ፣ ኦሞ፣ የከተሞች ወንዞች፣ ወ.ዘ.ተ….)፣

➡️ በግድቦች ማስተንፈሻ አካባቢዎች (ተንዳሆና ቀሰም፣ ግልገል ጊቤ ፣ ተከዜ፣ ገናሌ፣ ዳዋ ፣ ፊንጫ፣ ቆቃ ወ.ዘ.ተ...)፣

➡️ የክረምት ዝናብ ተጠቃሚ የሆነ አከባቢዎችና ከተሞች ሙሉ በሙሉ ከባድ ዝናብ በሚኖርበት ወቅት በየትኛዉም ጊዜ ቅፅበታዊ ጎርፍ ሊጠቁ ይችላሉ።

ማህበረሰቡ፣ የሚመለከታቸው ተቋማት እና የአስተዳደር መዋቅሮች አስፈላጊውን ጥንቃቄና በክትትል ላይ ተመሰረተ እርምጃዎች እንዲወስዱ የኢትዮጵያ አደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን አሳስቧል።

(ዝርዝር መረጀዎች ከላይ ተያይዟል)

⚠️መልዕክቱን ለሌሎች ያጋሩ!

#EDRMC

#TikvahEthiopiaFamliyAA

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
1.42K🙏267🕊56😭38😢30👏22🥰17😡11🤔10😱4💔1