ፎቶ📸በዛሬው ዕለት በዓዲግራት ከተማ እየተከበረ ያለው #ደማቅ የመስቀል በዓል ምክንያት በማድረግ የተካሄደው ታላቅ ሩጫ #መስቀል_ዓጋመ #ADIGRAT #ETHIOPIA
PHOTO: JOHN/TIKVAH-ETHIOIA
@tsegabwolde @tikvahethioia
PHOTO: JOHN/TIKVAH-ETHIOIA
@tsegabwolde @tikvahethioia
👍1
#Adigrat
በጦርነቱ ምክንያት ከ70 ከመቶ በላይ ውድመት የደረሰበት " የዓዲግራት አዲስ የመድሃኒት ፋብሪካ " አግግሞ እስከ 110 የሚደርሱ የተለያዩ በሽታዎች የሚፈውሱ መድሃኒቶች በማምረት ላይ እንደሚገኝ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።
የፋብሪካው ዋና ስራ አስፈፃሚ ሃይለ ገ/ሚካኤል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል ፥ የመድሃኒት ፋብሪካው ጦርነቱ በጀመረ ማግስት በኤርትራ ወታደሮች ቁጥጥር ስር ውሎ ነበር።
በእነዚህ የኤርትራ ወታደሮችም 7 ሰራተኞቹ በሞት መነጠቁንና በርካቶችም መቁሰላቸውን አስታውሰዋል፡፡
የመድሃኒት ፋብሪካው ከህዳር እስከ የካቲት 2013 ዓ.ም ባሉት ሶስት ወራት የኤርትራ ወታደሮች እንደ #ካምፕ ሲገለገሉበት እንደነበር ገልጸዋል።
" ወታደሮቹ ማሽነሪዎች ጨምሮ የተለያዩ የፅህፈት ቤት እቃዎች ዘርፈው መውሰዳቸውንና መውሰድ ያልቻሉት ፈንጅ በማጥመድ አጋይቶውታል " ብለዋል፡፡
ፋብሪካው ሚያዝያ ወር 2013 ዓ.ም በኢትዮጵያ ሀገር መከላከያ ወታደሮች ቁጥጥር ስር ከዋለ በኋላ በተነፃፃሪ የጥበቃ ከለላ ስር የተወሰኑ የጥገና ስራዎች ጀምሮ ነበር ሲሉ ገልጸዋል።
ነገር ግን በውቅቱ በነበረው የተወሳሰበ ውግያና የፀጥታ መድፍረስ ሳይሳካለት ቀርቶ 1500 ቀዋሚና ጊዚያዊ ሰራተኞቹ ለመበተን መገደዱን አመልክተዋል።
ፋብሪካው ከጥቅምት 2015 የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ማግስት የጥገና ስራዎች በማካሄድ ከፌደራል የመድሃኒትና የምግብ ቁጥጥር ባለስልጣን መልሶ ለማምረት የሚያስችለው የብቃት ማረጋገጫ ማግኘቱ አቶ ሃይለ ገልፀዋል፡፡
ያንብቡ ፦ https://telegra.ph/Tikvah-Ethiopia-05-11
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
በጦርነቱ ምክንያት ከ70 ከመቶ በላይ ውድመት የደረሰበት " የዓዲግራት አዲስ የመድሃኒት ፋብሪካ " አግግሞ እስከ 110 የሚደርሱ የተለያዩ በሽታዎች የሚፈውሱ መድሃኒቶች በማምረት ላይ እንደሚገኝ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።
የፋብሪካው ዋና ስራ አስፈፃሚ ሃይለ ገ/ሚካኤል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል ፥ የመድሃኒት ፋብሪካው ጦርነቱ በጀመረ ማግስት በኤርትራ ወታደሮች ቁጥጥር ስር ውሎ ነበር።
በእነዚህ የኤርትራ ወታደሮችም 7 ሰራተኞቹ በሞት መነጠቁንና በርካቶችም መቁሰላቸውን አስታውሰዋል፡፡
የመድሃኒት ፋብሪካው ከህዳር እስከ የካቲት 2013 ዓ.ም ባሉት ሶስት ወራት የኤርትራ ወታደሮች እንደ #ካምፕ ሲገለገሉበት እንደነበር ገልጸዋል።
" ወታደሮቹ ማሽነሪዎች ጨምሮ የተለያዩ የፅህፈት ቤት እቃዎች ዘርፈው መውሰዳቸውንና መውሰድ ያልቻሉት ፈንጅ በማጥመድ አጋይቶውታል " ብለዋል፡፡
ፋብሪካው ሚያዝያ ወር 2013 ዓ.ም በኢትዮጵያ ሀገር መከላከያ ወታደሮች ቁጥጥር ስር ከዋለ በኋላ በተነፃፃሪ የጥበቃ ከለላ ስር የተወሰኑ የጥገና ስራዎች ጀምሮ ነበር ሲሉ ገልጸዋል።
ነገር ግን በውቅቱ በነበረው የተወሳሰበ ውግያና የፀጥታ መድፍረስ ሳይሳካለት ቀርቶ 1500 ቀዋሚና ጊዚያዊ ሰራተኞቹ ለመበተን መገደዱን አመልክተዋል።
ፋብሪካው ከጥቅምት 2015 የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ማግስት የጥገና ስራዎች በማካሄድ ከፌደራል የመድሃኒትና የምግብ ቁጥጥር ባለስልጣን መልሶ ለማምረት የሚያስችለው የብቃት ማረጋገጫ ማግኘቱ አቶ ሃይለ ገልፀዋል፡፡
ያንብቡ ፦ https://telegra.ph/Tikvah-Ethiopia-05-11
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
👏580❤105🙏43🕊35😭19🥰7😢7🤔5😱1
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Adigrat
🚨 " በር ሰብረው ነው የገቡት " - አቶ ኪዱ ገብረ ፃድቅ (የትግራይ ክልል ምስራቃዊ ዞን የፀጥታ ኃላፊ)
➡️ " እኛ በር ሰብረን አልገባንም ህዝቡ ግቡ ብሎ በሰልፍ ስለመጣ ነው " - አቶ ረዳኢ ገ/እግዚአብሔር
ከዚህ ቀደም የዓዲግራት ከተማ ሁለት ከንቲባዎች (አንድ በጊዜያዊ አስተዳደሩ አንድም እነ ዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል በሚመሩት ህወሓት) እንደተሾሙባት ይታወቃል።
ማክሰኞ በደብረፅዮን (ዶ/ር) ህወሓት ቡድን የተሾሙት ከንቲባ በሰራዊት ኃይል በመታገዝ በኃይል በር በመስበር ፅ/ቤቱን እንደያዙት የምስራቃዊ ዞን የፀጥታ ኃላፊ አቶ ኪዱ ገብረ ፃድቅ አሳውቀዋል።
አቶ ኪዱ ገብረ ፃድቅ ምን አሉ ?
" የሰራዊቱ አመራሮች ' በምክር ቤት ለተመረጠው ከንቲባ አስረክቡ ' በማለት ወደ ከተማዋ ሰራዊት አስገብተዋል። ወደ ከንቲባ ፅ/ቤትም በኃይል ገብተዋል። ቁልፍ የላቸውም ሰብረው ነው የገቡት " ብለዋል።
አቶ ኪዱ ሰኞ ዕለት በዓዲግራት መግቢያ ቤተ ሓርያት በተባለ አካባቢው " ወጣቶች እያደራጃቹ ነው " በሚል በፀጥታ ኃይሎች ለ 4 ሰዓታት ታግተው ነው የተለቀቁት።
ማክሰኞ ቁልፍ ሳይኖራቸው በሩን ሰብረው ገብተዋል የተባሉት አቶ ረዳኢ ገ/እግዚአብሔር ፤ " ሰብረን አልንገባንም " ብለዋል።
አቶ ረዳኢ ገ/እግዚአብሔር ምን አሉ ?
" በህዝብ ሳይመረጥ በራስ ፍላጎት ብቻ በስልጣን ላይ የመቆየት ፍላጎት ስለነበረ ህዝቡ አገልግሎት አጥቶ ለሶስት ወራት ቆይቷል።
እኔ በምክር ቤት ተሹሜ ለሶስት ወራት ፅ/ቤት ሳልገባ መንገድ ዳር ነበርኩኝ። ችግሮች እንዳይፈጠሩ ስላሰብን ነው እስካሁን የቆየነው። አሁን ሰብረን አይደለም የገባነው የከተማው ህዝብ ከየአቅጣጫው ወጥቶ ' በሩ ይከፈት ' ብሎ ጠየቀ መልስ በማጣቱ ገፍቶ ነው የገባው በዚህም ወደ ፅ/ቤት ገብተናል " ብለዋል።
የፀጥታ ኃይሎች በአካባቢው የፀጥታ ችግር እንዳይፈጠር ራቅ ብለው ይከታተሉ ነበር እንጂ ወደ አስተዳደሩ ቅጥር ግቢ አልገቡም ሲሉ አክለዋል።
#VOATIGRIGNA
@tikvahethiopia
🚨 " በር ሰብረው ነው የገቡት " - አቶ ኪዱ ገብረ ፃድቅ (የትግራይ ክልል ምስራቃዊ ዞን የፀጥታ ኃላፊ)
➡️ " እኛ በር ሰብረን አልገባንም ህዝቡ ግቡ ብሎ በሰልፍ ስለመጣ ነው " - አቶ ረዳኢ ገ/እግዚአብሔር
ከዚህ ቀደም የዓዲግራት ከተማ ሁለት ከንቲባዎች (አንድ በጊዜያዊ አስተዳደሩ አንድም እነ ዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል በሚመሩት ህወሓት) እንደተሾሙባት ይታወቃል።
ማክሰኞ በደብረፅዮን (ዶ/ር) ህወሓት ቡድን የተሾሙት ከንቲባ በሰራዊት ኃይል በመታገዝ በኃይል በር በመስበር ፅ/ቤቱን እንደያዙት የምስራቃዊ ዞን የፀጥታ ኃላፊ አቶ ኪዱ ገብረ ፃድቅ አሳውቀዋል።
አቶ ኪዱ ገብረ ፃድቅ ምን አሉ ?
" የሰራዊቱ አመራሮች ' በምክር ቤት ለተመረጠው ከንቲባ አስረክቡ ' በማለት ወደ ከተማዋ ሰራዊት አስገብተዋል። ወደ ከንቲባ ፅ/ቤትም በኃይል ገብተዋል። ቁልፍ የላቸውም ሰብረው ነው የገቡት " ብለዋል።
አቶ ኪዱ ሰኞ ዕለት በዓዲግራት መግቢያ ቤተ ሓርያት በተባለ አካባቢው " ወጣቶች እያደራጃቹ ነው " በሚል በፀጥታ ኃይሎች ለ 4 ሰዓታት ታግተው ነው የተለቀቁት።
ማክሰኞ ቁልፍ ሳይኖራቸው በሩን ሰብረው ገብተዋል የተባሉት አቶ ረዳኢ ገ/እግዚአብሔር ፤ " ሰብረን አልንገባንም " ብለዋል።
አቶ ረዳኢ ገ/እግዚአብሔር ምን አሉ ?
" በህዝብ ሳይመረጥ በራስ ፍላጎት ብቻ በስልጣን ላይ የመቆየት ፍላጎት ስለነበረ ህዝቡ አገልግሎት አጥቶ ለሶስት ወራት ቆይቷል።
እኔ በምክር ቤት ተሹሜ ለሶስት ወራት ፅ/ቤት ሳልገባ መንገድ ዳር ነበርኩኝ። ችግሮች እንዳይፈጠሩ ስላሰብን ነው እስካሁን የቆየነው። አሁን ሰብረን አይደለም የገባነው የከተማው ህዝብ ከየአቅጣጫው ወጥቶ ' በሩ ይከፈት ' ብሎ ጠየቀ መልስ በማጣቱ ገፍቶ ነው የገባው በዚህም ወደ ፅ/ቤት ገብተናል " ብለዋል።
የፀጥታ ኃይሎች በአካባቢው የፀጥታ ችግር እንዳይፈጠር ራቅ ብለው ይከታተሉ ነበር እንጂ ወደ አስተዳደሩ ቅጥር ግቢ አልገቡም ሲሉ አክለዋል።
#VOATIGRIGNA
@tikvahethiopia
😁420🕊114❤102😭39🤔33😡16👏11🙏11😢9🥰3