TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63.1K photos
1.61K videos
217 files
4.38K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#NewsAlert “ኢትዮጵያ ውስጥ #ጥላቻና ብጥብጥ ከሚቀሰቅሱ የዳያስፖራ አባላት የተወሰኑት ዩናየትድ ስቴትስ የሚገኙ ናቸው” ሲሉ አዲስ አበባ የሚገኙት የአሜሪካ አምባሳደር ተናግረዋል።

“ዩናይትድ ስቴትስ ውስጥ በሚገኙበት ምቾትና ደኅንነት ውስጥ ሆነው እዚህ ኢትዮጵያ ውስጥ ጥላቻና ብጥብጥ ያነሳሳሉ” ብለዋል አምባሳደር ማይክ ራይነር።

ሰሞኑን በተመሣሣይ ጉዳይ ላይ የተናገሩት ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አሕመድ “ጥላቻና ብጥብጥ ያነሳሳሉ” ያሏቸውን “አንዳንድ” የኢትዮጵያ ዳያስፖራ አባላት “የእውነት አምላክ ይፍረድባቸው” ሲሉ አማርረዋል።

የሚባሉትን #ኢትዮጵያዊያን አስመልክቶ በሁለቱ ሃገሮች መካከል የተደረገ ንግግር ስለመኖር አለመኖሩ የታወቀ ነገር የለም።

Via #VOA
@tsegabwolde @tikvahethiopia