TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63K photos
1.61K videos
217 files
4.38K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update ጅግጅጋ⬇️

በጅግጅጋ ከተማ የሚገኙ አገልግሎት መስጫ ተቋማት ከዛሬ ጀምሮ ወደ መደበኛ አገልግሎት እንዲገቡ ተጠየቀ።

በሶማሌ ክልል በተለይም በጅግጅጋ ከተማ ከሃምሌ 28 ቀን 2010 ዓ.ም ጀምሮ ከተፈጠረው ሁከትና ብጥብጥ በኋላ ቅዳሜ እለት የሰላም ኮንፈረንስ ተካሂዷል።

በሰላም ኮንፈረንሱ ላይ የጅግጅጋ ከተማ ነዋሪ ተወካዮች፣ የሀገር ሽማግሌዎች እና የጎሳ መሪዎች የተሳተፉ ሲሆን፥ ድርጊቱ #በተደራጀ መንገድ በመዋቅር ተመርቶ የተፈፀመ መሆኑን ተሳታፊዎቹ ተናግረዋል።

#ድርጊቱ በክልሉ መንግስት አመራሮች የተመራና ክልሉን ለመበጥበጥ የተፈጸመ መሆኑንም አንስተዋል።

በኢፌዴሬ መከላከያ ሚኒስቴር የመረጃ ሃላፊ ሌተናል ጀኔራል ሃሰን ኢብራሂም ለተፈጸመው ችግር የክልሉ አመራሮች ተጠያቂ መሆናቸውን ገልጸዋል።

ለጥቂት ሰዎች #ስልጣን ተብሎ የክልሉ ሰላምና ፀጥታ መደፍረስ እንደሌለበት ያነሱት ሃላፊው፥ መከላከያ ሰራዊት ወደ ክልሉ ሰላም ለማስከበር ብቻ መግባቱንም ነው የተናገሩት።

ከዚህ ውጭ ግን ከሶማሌ ክልል ልዩ ሃይል ጋር ሊዋጋ ነው በሚል የሚናፈሰው ወሬ #ሃሰት መሆኑንም ጠቅሰዋል።

የደቡብ ምስራቅ ዕዝ ዋና አዛዥ ሜጀር ጀኔራል በላይ ስዩም በበኩላቸው የኢፌዴሪ መከላከያ እና የሶማሌ ክልል ልዩ ሃይል በሰሩት ስራ አሁን ላይ አንጻራዊ ሰላም መታየቱን አንስተዋል።

ከመከላከያ ሰራዊት፣ ከክልሉ ልዩ ሃይልና ከክልሉን ፖሊስ የተውጣጣ ኮማንድ ፖስት መቋቋሙን በጥቀስ።

በጅግጅጋ ከተማ ሰላም በመታየቱ ሁሉም ሁሉም የገንዘብ እና የንግድ ተቋማት ወደ ስራ እንዲገቡም ተጠይቋል።

ከዚህ ባለፈም የሃገር ሽማግሌዎች ስለ ሰላም እንዲሰብኩና ወጣቶችም ከጥፋት ድርጊት በመታቀብ ለሰላም ዘብ እንዲቆሙም ተጠይቋል።

©FBC
@tseagabwolde @tikvahethiopia