TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63K photos
1.61K videos
217 files
4.38K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ሆሳዕና‼️

በሆሳዕና ከተማ በአንድ ግለሰብ ሱቅ ውስጥ 10 ቱርክ ሰራሽ #ሽጉጦች ከ358 #ጥይቶች ጋር ተደብቀው መገኘታቸውን የሃዲያ ዞን ፖሊስ መምሪያ አስታወቀ።

የመምሪያው አዛዥ ኮማንደር #ደሳለኝ_ሽጉጤ ለኢዜአ እንደገለፁት ፖሊስ ህገ-ወጥ የጦር መሳሪያውን ሊይዝ የቻለው ከህብረተሰቡ በተደረገ ጥቆማ አማካኝነት ነው።

በከተማው ሴች ዱና ቀበሌ ከተያዘው የጦር መሳሪያ ጋር ባለ ሱቁን ጨምሮ እጃቸው አለበት በሚል የተጠረጠሩ አራት ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ማዋላቸውንም ኮማንደሩ ተናግረዋል፡፡

ህብረተሰቡ ላከናወነው ተግባር ያመሰገኑት ኮማንደር ደሳለኝ ሰላምን የሚያደፈርስና የሚያጠራጥር መሰል ድርጊት ሲያጋጥም ለፖሊስ መጠቆሙን አጠናክሮ እንዲቀጥልም ጠይቀዋል።

ምንጭ፦ ኢዜአ
@tsegabwolde @tikvahethiopia