TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63K photos
1.61K videos
217 files
4.38K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
‹‹በማህበራዊ ሚዲያ #የጥላቻ ንግግሮችን ለሚያወጡ ሰዎች #ህግ እያወጣን ነው፡፡››

◾️▪️ጠ/ሚ ዶክተር ዐብይ አህመድ▪️◾️
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ፌስቡክ የጥላቻ ንግግሮችን እያስወገደ ነው...

ፌስቡክ በስድስት ወራት ውስጥ 3 ቢሊዮን የሀሰት አካውንቶችን ማጥፋቱን አስታወቀ፡፡ ከሰባት ሚሊዮን በላይ #የጥላቻ_ንግግሮችን በማስወገድም በታሪኩ ከፍተኛ የተባለለትን እርምጃ ወስዷልም ተብሏል፡፡

ፌስቡክ ጥላቻ ንግግርና በሀሰተኛ መረጃዎች እየቀረበበት ያለውን ወቀሳ ተከትሎ ለጀመሪያ ጊዜ ምን ያህል ሀሰተኛ አካውንቶችንና ልጥፎችን ጭምር እንዳጠፋ በግምገማዊ ሪፖርቱ አስታውቋል፡፡

የፌስ ቡክ ዋና አስተዳዳሪው #ማርክ_ዙከርበርግ በትላንተናው ዕለት ፌስቡክን ለመቆጣጠር በተለያየ መልኩ ተከፋፍሎ እንዲደራጅ ለቀረቡለት ጥሪዎች ችግሩን ለመፍታት አሰራሮችን ማዘመን ብቸኛው መፍትሄ ነው ሲል መልሷል፡፡

እንዲወገዱ የተደረጉት የሀሰተኛ አካውንቶች ሁሉም በሚባል ደረጃ በማኅበራዊ አውታር "ንቁ" ተጠቃሚዎች እንዲሆኑ ዕድል ከማግኘታቸው በፊት ካለፈው ጥቅምት እስከ መጋቢት ድረስ እርምጃው እንደተወሰደባቸው ተመልክቷል፡፡

ፌስቡክ እንዳለው ሪፖርቱ የሚያሳየው የኩባንያውን ግልጽነትና ለተጠቃሚዎቻችን ተጠያቂነታችንን እና ምላሽ ሰጭነታችንን ለማሳየትና እምነት ለመገንባት የሚያስችለን ነው፡፡

ምንጭ፡- ቢቢሲ
@tsegabwolde @tikvahethiopia