TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63.2K photos
1.62K videos
218 files
4.39K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#የጤና_ሚኒስቴር_ማስጠንቀቂያ !

የኢፌዴሪ ጤና ሚኒስቴር ፥ የኮቪድ-19 ክትባትን ከመንግስት የጤና ተቋማት ውጪ የሚሰጡ አካላት ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ አስጠነቀቀ።

በሚኒስቴሩ የብሄራዊ ክትባት አስተባባሪ የሆኑት አቶ ዮሃንስ ላቀው ፥ የኮቪድ 19 ክትባትን በግል እያስከፈሉ የሚሰጡ አካላት ህገ ወጥ በመሆናቸው ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡና ህብረተሰቡም ይሄንን ተከትሎ ራሱን ለአደጋ ማጋለጥ እንደሌለበት ተናግረዋል።

አቶ ዮሃንስ ክትባቶቹ በእርዳታ የገቡ መሆናቸውን አስታውሰው፣ ለህብረተሰቡ በመንግስታዊ ጤና ተቋማት ብቻ በነፃ የሚሰጡ ሆነው ሳለ ክፍያ እየተጠየቀ እንደሚሰጥ ሰምተን እያጣራን ነው ብለዋል፡፡

ከዚህም በተጨማሪ በህገ ወጥ መንገድ ክትባቶቹን ለመገበያየት መሞከር በአያያዙና በአወሳሰዱ ላይ እክል የሚፈጥር በመሆኑ ጉዳቱ የከፋ መሆኑን ነው የገለጹት፡፡

እስካሁን ለየተኛውም የግል ተቋም የኮቪድ 19 ክትባትን መስጠት እንዲችል ያልተከፋፈለ መሆኑንና ፈቃድም እንዳልተሰጣቸው በማሳሰብ ለወደፊት በግል ጤና ተቋማት መሰጠት ሲጀመር ቀድመን የምናሳውቅ ይሆናል ብለዋል። እስካሁን ግን ክትባት እንዲሰጥ ፈቃድ የተሰጠዉ የግል የህክምና ተቋም የለም ሲሉ አስገንዝበዋል።

መረጃው የኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 ነው።

@tikvahethiopia
👍2