TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.9K photos
1.61K videos
216 files
4.37K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
የአዲስ አበባ ካቢኔ ምን ውሳኔዎች አሳለፈ ?

የአዲስ አበ ባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ ባካሄደው 4ተኛ አመት 7ኛ መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳልፏል።

የመጀመሪያው በከተማዉ አስተዳደር በጀት ተመድቦላቸዉ የተገነቡ እና በመጠናቀቅ ያሉትን አዳዲስ ሆስፒታሎችን የሚመለከት ነው።

በዚህም ሆስፒታሎቹ ዘመኑን በዋጀ ህክምና መሳሪያ ለማሟላት እና አለም አቀፍ ደረጃን የሚያሟላ አገልግሎት መስጠት ያስችላቸው ዘንድ በዘርፉ ትልቅ ልምድ ካከበቱ
#የግል_ሴክተር ጋር በአጋርነት ለመስራት ዉሳኔ አሳልፏል።

ሁለተኛ አንዳንድ የመንግስት አገልግሎቶችን በውል
#ለ3ተኛ_ወገን ለማስራት የወጣውን ረቂቅ ደንብ መርምሮ በማየት ካቢኔዉ አፅድቋል።

በሶስተኛ ደረጀ የተለያዩ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ ላላቸው እና ተኪ ምርቶችን ለሚያመርቱ ኢንዲስትሪዎች ባቀረቡት
#የማስፋፊያ_ቦታ ጥያቄዎች ላይ በመወያየት እና የአተገባበር አቅጣጫ በማስቀመጥ ካቢኔው በሙሉ ድምፅ አፅድቋል።

አራተኛ የኮሪደር ልማት ውጤት ከሆኑት ሥራዎች አንዱ የብዙሀን ትራንስፖርት መሠረተ ልማት ችግሮች የሚያቃልል እና የትራፊክ ፍስቱን የሚያሻሽለው የብስክሌት መጋራት አገልግሎት እና የብስክሌት መስመር አጠቃቀም ደንብን በመመርመር ማፅደቁን ከከተማ አስተዳደሩ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

@tikvahethiopia
😡447168🤔25🕊24🙏21😭12🥰8👏7😢1