TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.8K photos
1.61K videos
216 files
4.37K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#NewsAlert አቶ አህመድ ቡህ #የድሬዳዋ_ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሆነው ተሾሙ። የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት አቶ አህመድ ቡህን የአስተዳደሩ ምክትል ከንቲባ አድርጎ ሾመ።

የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት 2ኛ የስራ ዘመን 6ኛ አስቸኳይ ጉባኤውን በዛሬው እለት አካሂዷል። ምክር ቤቱ በዛሬው እለት ባካሄደው አስቸኳይ ጉባኤው ካለፈው መጋቢት ወር 2011 ዓ.ም መጀመሪያ ጀምሮ በከንቲባነት ያገለገሉትን የአቶ መሐዲ ጊሬን መልቀቂያ ተቀብሏል። በምትካቸውም አቶ አህመድ ቡህን የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ አድርጎ ሹሟል፡፡

በተጨማሪም ምክር ቤቱ በአስቸኳይ ጉባዔው የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት የአፈ ጉባኤ አብደላ አህመድን መልቀቂያ መቀበሉም ተገልጿል። በምትካቸውም ወይዘሮ ፈጡም ሙስጣፋን የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት የአፈ ጉባኤ አድርጎ ሾሟል።

Via #fbc
@tsegabwolde @tikvahethiopia