TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.8K photos
1.61K videos
216 files
4.37K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#የዩኒቨርሲቲ_መውጫ_ፈተና

የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ትምህርት ሚኒስቴር ፤ ከሁሉም መንግስት ዩኒቨርሲቲዎች የሚመረቁ ተማሪዎች በሰለጠኑባቸው ሙያዎች ብቁ መሆናቸውን ለማረጋገጥ እንዲወስዱ የሚጠበቀውን የመውጫ ፈተና ወደ ተግባር እንዲገባ ዝግጅት መደረጉን አስታውቋል።

የመውጫ ፈተናውን በተመለከተ የመንግስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ፕሬዝዳንቶች በተገኙበት በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ምክክር እየተደረገ ይገኛል።

የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች የምክክር መድረክ ባዘጋጀው ውይይት የመውጫ ፈተናው አስፈላጊነት፤ የፈተናው አወጣጥና አፈታተን እንዲሁም በተያያዥ ጉዳዮች ዙሪያ ምክክር እየተደረገበት ነው።

የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ሳሙኤል ክፍሌ ፤ መንግስት በመጪዎቹ አምስት ዓመታት የትምህርት ጥራትን ለማሻሻል ጠንካራ ትግበራ እና ርምጃዎችን እንደሚወስድ አንስተዋል።

በቀጣይ አምስት ዓመታት አዲስ የመንግስት ዩኒቨርሲቲ እንደማይኖር የገለጹት ሚኒስትር ዴኤታው፤ ይልቁንም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አቅም እና ጥራት ማሻሻል ላይ በትኩረት ይሰራል ብለዋል።

በሁሉም የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች የሚገኙ ተመራቂ ተማራዎች ፈተናዉን እንዲወስዱ በቂ ዝግጅት መደረጉን ጠቁመዋል።

የመውጫ ፈተናው በእያንዳንዱ ዩኒቨርሲቲ በየሙያው እና ትምህርት ዘርፍ ተዘጋጅቶ የሚሰጥ ሲሆን ለዚህም ትግበራ ፖሊሲና ዝርዝር ማስፈፀሚያ መመሪያ መዘጋጀቱን ገልጸዋል።

በህግና በህክምና ሙያ የሚሰጠው የመውጫ ፈተናና የብቃት ማረጋገጫ ፍተሻ እንደ ልምድ ይወሰዳል ተብሏል።

ምንጭ፦ አዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ

@tikvahuniversity
👎1.27K👍93453😱47😢38👏26🥰18😭1