TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.8K photos
1.61K videos
216 files
4.37K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#የእሳት_አደጋ_በሀዲያ_ዞን

በሀዲያ ዞን ምሻ ወረዳ በሶስት ቀበሌዎች ፦
- ኤራ ጌሜዶ፣
- ኩናፋ
- ጉና ሜጋቾ በደረሰ እሳት አደጋ 4 መቶ 36 የቤተሰብ አባላት መፈናቀላቸውን የዞኑ የአደጋ ስጋት ሥራ አመራር ጽ/ቤት አሳውቋል።

ፅህፈት ቤቱ አደጋው የተፈጥሮ እሳት አደጋ ነው ብሏል።

በደረሰው አደጋ ከ23 ሚሊየን ብር በላይ የሚገመት ንብረት መዉደሙ ተጠቁሟል፡፡

በአደጋው በሰው ህይወት ላይ የደረሰ ጉዳት የለም።

128 ዶሮዎች፣ 243 ኩንታል የተለያዩ የእህል ዘሮች ፣ 18 የንብ ቀፎዎች፣ የተለያዩ የቤት ቁሳቁሶች እና በአካባቢው የነበሩ የጓሮ አትክልቶች በድምሩ ከ23 ሚሊየን ብር በላይ የሚገመት ንብረት ወድሟል።

በሌላ መረጃ ፦

በምዕራብ ሶሮ ወረዳ በጃቾ ከተማ በደረሰ የእሳት አደጋ ከ250 ሺህ ብር በላይ የሚገመት ንብረት ወድሟል።

አደጋው ታህሳስ 18 ከምሽቱ 2፡30 በመብራት ኮንታክት የደረሰ መሆኑን የወረደው ፖሊስ ጽ/ቤት አስታውቋል።

አደጋው ህብረተሰቡና የፖሊስ አካላት ባደረጉት ርብርብ ወደ ሌሎች ሱቆችና መኖርያ ቤቶች ሳይሻገር በቁጥጥር ስር መዋሉን ተገልጿል።

(ሀዲያ ዞን ኮሚኒኬሽን)
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia