TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63K photos
1.61K videos
216 files
4.38K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update ኢንጂነር አይሻ⬇️

ኢትዮጵያ የመጀመሪያዋን ሴት የአገር መከላከያ ሚኒስትር ሾመች። ኢንጂነር #አይሻ_መሃመድ በኢትዮጵያ ታሪክ የመጀመሪያዋ የአገር መከላከያ ሚኒስትር ሆነው ተሹመዋል።

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው መደበኛ ሰብሰባ ኢንጂነር አይሻ መሃመድን #የአገር_የመከላከያ_ሚኒስትር አድርጓቸዋል።

ኢንጂነር አይሻ የአፋር ክልል ተወላጅ ሲሆኑ የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን በሲቪል ኢንጂነሪንግ፣ ሁለተኛ ዲግሪያቸውን ደግሞ በትራንስፎርሜሽናል ሊደር ሺፕ ኤንድ ቼንጅ አግኝተዋል።

በአፋር ክልል የአደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና ቢሮ ሃላፊ በመሆን ያገለገሉ ሲሆን የባህልና ቱሪዝም ሚኒስትርም ነበሩ። በአሁኑ ወቅትም የኮንስትራክሽን ሚኒስትር ሆነው በማገልገል ላይ ነበሩ።

በዛሬው የምክር ቤቱ መደበኛ ስብሰባም የመጀመሪያዋ የኢትዮጵያ ሴት የአገር መከላከያ ሚኒስትር ሆነው ተሹመዋል።

ዛሬ በጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ከተሾሙት 20 የካቢኔ አባላት መካከል አስሩ ሴቶች ናቸው።

ምንጭ፦ መንግስት ኮሚኒኬሽን
@tsegabwolde @tikvahethiopia