TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.9K photos
1.61K videos
216 files
4.38K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ሀዋሳ🔝በሀዋሳ ከተማ #የነዳጅ_እጥረት በመከሰቱ አሽከርካሪዎች መቸገራቸውን ለTIKVAH-ETH በላኩት መልዕክት ገልፀዋል። የሚመለከተው አካል ችግሩን እንዲፈታ ጥሪ አቅርበዋል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ሀዋሳ🔝

በሀዋሳ ከተማ የተከሰተው #የነዳጅ_እጥረት መፍትሄ አላገኘም። ዛሬም በከተማይቱ ረጃጅም የተሽከርካሪ ሰልፎች ይታያሉ።

በሀዋሳ ከተማ የሚገኝ የTIKVAH-ETH ቤተሰብ አባል ስለ ነዳጅ እጥረቱ እንዲህ ብሏል...

"ከሌሊቱ 10 ሰአት #ተሰልፈን እስከ አሁን 1:45 ነዳጅ መቅዳት አልተጀመረም ከተማው ወስጥ 3 ማደያዎች ቤንዚል ቢኖራቸው #ማኔጅ የሚያደርግ አካል የለም በጣም ተቸግረናል።"

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ሀዋሳ🔝በከተማይቱ ያለው #የነዳጅ እጥረት እስካሁን መፍትሄ አላገኘም። ዛሬ ከማለዳው አንስቶ ረጃጅም የተሽከርካሪ ሰልፎች በተለያዩ ነዳጅ ማደያ ጣቢያዎች ለማየት ተችሏል።

#TIKVAHETHIOPIA(የሀዋሳ ቤተሰብ አባላት)
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ወላይታ ሶዶ🔝

በወላይታ ሶዶ ከተማ ለጥቂት ቀናትም ቢሆን ተቃሎ የነበረው #የነዳጅ_እጥረት ዳግም ማገርሸቱን በከተማይቱ የሚኖሩ የTIKVAH-ETH ቤተሰብ አባላት ገልፀዋል። መንግስት ችግሩ የሚቃለልበትን መንገድም እንዲፈልግ ጠይቀዋል።
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የነዳጅ እጥረት በአዲስ አበባ‼️

በአዲስ አበባ ከተማ የተፈጠረው #የነዳጅ_እጥረት በአሽከርካሪዎች ላይ ጫና መፍጠሩን የታክሲና የባጃጅ አሽከርካሪዎች ገለጹ። የኢትዮጵያ ነዳጅ አቅራቢ ድርጅት ያጋጠመውን ወቅታዊ የነዳጅ አቅርቦት ችግር በቀጣዮቹ ሁለት ቀናት እንደሚፈታ አመልክቷል። የትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ ታክሲዎችና ባለሶስት እግር ተሽከርካሪዎች (ባጃጅ) አሽከርካሪዎች ከነዳጅ ማደያ ቤንዚን ለማግኘት በመቸገራቸው በእለት ኑሯቸው ላይ ጫና ማሳደሩን ጠቁመዋል። የእለት ገቢ እያገኙ ቤተሰቦቻቸውን የሚያስተዳድሩ በመሆኑ ረጅም ሰዓት በነዳጅ ማደያ ተሰልፈው በማሳለፋቸው ገቢ እያገኙ እንዳልሆነ ለኢዜአ ገልጸዋል።

ምንጭ፦ ኢዜአ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ጅማ🔝በጅማ ከተማ #የነዳጅ_እጥረት መከሱትን የTIKVAH-ETH ቤተሰብ አባላት ገልፀዋል። መንግስት ችግሩን እንዲቀርፍም ጠይቀዋል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ፌደራል ፖሊስ~ድሬዳዋ ቅርንጫፍ‼️

በሕገ-ወጥ መንገድ ከድሬዳዋ ተጭኖ ወደ ሐርጌሌ ሊጓጓዝ የነበረ ነዳጅና አምስት #ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ሥር ማዋሉን የፌዴራል ፖሊስ የድሬዳዋ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ገለጸ።

የጽህፈት ቤቱ የወንጀል ምርመራ ባለሙያ አቶ #ሞገስ_አያሌው ለኢዜአ እንዳመለከቱት ከከተማው ሊወጣ ሲል የተያዘው 20ሺህ ሊትር ናፍጣ፣ 16 ጀሪካን የሞተር ዘይትና በድርጊቱ የተጠረጠሩት ግለሰቦች ናቸው፡፡ በተለይ ነዳጁ የተያዘው በአንድ የጭነት መኪና ከነተሳቢው በጄሪካን ተጭኖ እንደነበር አስረድተዋል፡፡

ነዳጁን በከተማው ከሚገኝ አንድ ነዳጅ ማደያ ገዝተው ሊያጓጓዙ የነበሩት ግለሰብና ከጉዳዩ ጋር ግንኙነት ያላቸው የተባሉ አራት ተጠርጣሪዎች መያዛቸውን ገልጸዋል፡፡ ለግለሰቡ  ከፍተኛ መጠን ያለው ነዳጅ መሰጠቱ አግባብ  አለመሆኑን ያስረዱት ባለሙያው፣ በሕገ-ወጥ መንገድ ነዳጅን ጥቅም ላይ ለማዋል የሚከናወነውን እንቅስቃሴ በተቀናጀ መንገድ ለመከላከል እየተሰራ መሆኑን አስረድተዋል፡፡ ኅብረተሰቡ ማንኛውንም ሕገ-ወጥ ተግባር ለፖሊስ በማሳወቅ ትብብሩን እንዲቀጥልም ጠይቀዋል፡፡

ነዳጁ በቁጥጥር ሥር እንዲውል ጥቆማ ከሰጡት አንዱ ለኢ ዜ አ  እንዳስታወቁት በከተማዋ #የነዳጅ_እጥረት የሚከሰተው በሕገ ወጥ መንገድ በሚካሄደው ንግድ ነው፡፡ ”የቤንዚኑ ችግር ሳይፈታ ናፍጣ ቢወደድ ሌላ ችግር ስለሚፈጥር ጉዳዩን ጠርጥረን ለፖሊስ አሳውቀናል። ትብብራችንም ይቀጥላል”ብሏል፡፡

#ሐርጌሌ በሶማሌ ክልል ከድሬዳዋ በአንድ ሺህ ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የምትገኝ ከተማ ናት። የድሬዳዋ አስተዳደር ፖሊስ ኮሚሽን ከሁለት ወራት በፊት በተመሳሳይ መንገድ ሊጓዝ የነበረ ነዳጅ በቁጥጥር ሥር ማዋሉ ይታወሳል፡፡

ምንጭ፦ ኢዜአ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
የነዳጅ ዋጋ📈 የነዳጅ ዋጋ በበርሜል ከ100 ዶላር በላይ አሻቅቧል። የሩሲያ ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን በምሥራቃዊ ዩክሬን ላይ “ወታደራዊ ዘመቻ” መጀመሩን መግለጻቸውን ተከትሎ የነዳጅ ዋጋ በከፍተኛ ሁኔታ መጨመሩን ቢቢሲ ዘግቧል። በዚህም ሳቢያ በ7 ዓመታት ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ የነዳጅ ዘይት ዋጋ በበርሜል ከ100 ዶላር በላይ አሻቅቧል። ውጥረት እና ግጭቱ የሚቀጥል ከሆነ የነዳጅ ዋጋ ከዚህም በላይ…
የሩስያ እና ዩክሬን ፍጥጫ #እንደኛ ባሉ አዳጊ ሀገራት ላይ ሊያሳድር የሚችለው ተፅእኖ ምንድነው ?

[በዓለም አቀፉ ጋዜጠኛ ኤልያስ መሰረት የቀረበ]

- #የምግብ_ዋጋ_መናር : ኢትዮጵያ ስንዴ የምትገዛባቸው ሶስት ዋና ዋና ሀገራት ሩስያ፣ ዩክሬን እና አውስትራሊያ ናቸው። በተለይ ሩስያ እና ዩክሬን በአለም ላይ ካለው የስንዴ ገበያ አንድ አራተኛውን ይሸፍናሉ። ዩክሬን 40 % የሚሆነውን የስንዴ ምርቷን ለመካከለኛው ምስራቅ እና እንደ ኢትዮጵያ ላሉ አዳጊ ሀገራት በሽያጭ ታቀርባለች። ታድያ ይህ አቅርቦት በጦርነት ምክንያት ሲስተጓጎል የምርት/ምግብ አቅርቦት መስተጓጎሉ አይቀርም። ይህም በአንዳንድ ሀገራት የሚታየውን የዋጋ ግሽበት አባብሶ ህዝባዊ ቁጣ ሊቀሰቅስ ይችላል።

- #የነዳጅ_ዋጋ_መጨመር : የሩስያ እና ዩክሬንን ፍጥጫ ተከትሎ አሁን ላይ የነዳጅ ዋጋ ከ100 ዶላር በላይ እንዳሻቀበ የሚወጡ ሪፖርቶች ያሳያሉ፣ ይህ ዋጋ ከዚህም በላይ በፍጥነት ሊጨምር ይችላል የሚል ግምት አለ። ሩስያ በአለም ላይ የተፈጥሮ ጋዝ እና ነዳጅ በማምረት ከፍተኛውን ድርሻ ከሚይዙ ሀገራት መሀል ትመደባለች። ታድያ ይህ ግጭት የአለም የነዳጅ ዋጋን እጅጉን እያናረው ይገኛል፣ ይህም በተለይ እንደ ሀገራችን ላሉ ነዳጅ ገዢ ሀገራት እጅጉን ፈታኝ ግዜ እንደሚያመጣ ግልፅ እየሆነ ነው።

- #የእርዳታ_መቀነስ : ብዙ ግዜ እንደሚታየው አንድ ቦታ ላይ ትልቅ ችግር ሲከሰት ትኩረት ወደዛ ይዞራል። ለምሳሌ በሶርያ፣ የመን፣ ኢራቅ፣ አፍጋኒስታን ወዘተ ችግሮች ሲከሰቱ ከረጂ ሀገራት የሚገኘው ድጋፍ እዚህም፣ እዛም ይከፋፈል እና ይቀንሳል። አሁን ደግሞ ሀገራችን በጦርነት እና ድርቅ ምክንያት ከፍተኛ አለም አቀፍ ድጋፍ የምትሻበት ግዜ ነው፣ ነገር ግን ይህ እየተባባሰ የመጣ ፍጥጫ ትኩረት እንዳያሳጣን ስጋት አለ።

@tikvahethiopia
👍671😢216👎53😱53👏2316🥰9
#የነዳጅ_ዋጋ !

አሁን በዓለም ገበያ 1 በርሜል ብሬንት ድፍድፍ ነዳጅ 106.6 ዶላር እየተሸጠ የሚገኝ ሲሆን በአሜሪካ ነዳጅ ገበያ እንደመለኪያ በሚታየው ዌስት ቴክሳስ ኢንተርሚዴት አንድ በርሜል ነዳጅ 104.3 ዶላር በሆነ ዋጋ እየተሸጠ ይገኛል።

#OilPrice

@tikvahethiopia
2👍2😱1
TIKVAH-ETHIOPIA
#ሚያዚያ የቤንዚን እና የናፍጣ ምርቶች ዋጋ ባለበት ይቀጥላል። የንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ፥ የሚያዚያ ወር የቤንዚን እና የናፍጣ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በመጋቢት ወር ላይ ሲሸጥበት በነበረው እንደሚቀጥል አስታውቋል። የአውሮፕላን ነዳጅ ፣ የከባድ ጥቁር ናፍጣ እና የቀላል ጥቁር ናፍጣ የመሸጫ ዋጋ በዓለም አቀፍ ዋጋ መሰረት ተሰልቶ የመጣው ወደ ተጠቃሚው እንዲተላለፍ መወሰኑን ኤፍ ቢ…
#የነዳጅ_ዋጋ_ጭማሪ

ከነገ ሚያዚያ 30 ጀምሮ የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ላይ ጭማሪ ተደርጓል።

በዚህም ፦

👉 ቤንዚን በሊትር 36 ብር ከ87 ሳንቲም ፣
👉 ነጭ ናፍጣ በሊትር 35 ብር ከ43 ሳንቲም፣
👉 ኬሮሲን በሊትር 35 ብር ከ43 ሳንቲም፣
👉 ቀላል ጥቁር ናፍጣ በሊትር 52 ብር ከ45 ሳንቲም፣
👉 ከባድ ጥቁር ናፍጣ በሊትር 51 ብር ከ78 ሳንቲም
👉 የአውሮፕላን ነዳጅ በሊትር 78 ብር ከ87 ሳንቲም እንዲሆን መወሰኑን የንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታውቋል።

ዝርዝሩን ያንብቡ : https://telegra.ph/ETHIOPIA-05-07

@tikvahethiopia
👍81
TIKVAH-ETHIOPIA
" ባጃጅ ታግዷል " በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከነገ የካቲት 30 ጀምሮ የባጃጅ ትራንስፖርት አገልግሎት ታገደ። ከነገ ጀምሮ በከተማዋ በየትኛውም አካባቢ ላልተወሰነ ጊዜ የባጃጅ አገልግሎት መታገዱን የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ አስታውቋል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትራንስፖርት ቢሮ " የባጃጅ ትራንስፖርት አገልግሎት አሰጣጥን በተሻለ መልክ ለመምራት እንዲያስችል አሰራር ማሻሻያ ስራዎችን…
#ባጃጅ

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር  የባለ ሶስት እግር ተሽከርካሪዎች / ባጃጅ መታገዱን በተመለከተ ዛሬ ባወጣው መግለጫ አጭር ማብራሪያ ሰጥቷል።

በማብራሪያው ፤ " መንግስት የህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪዎችን #የነዳጅ_ድጎማ ተጠቃሚ እንዲሆን ማድረጉ እየታወቀ የባለሶስት ጎማ ወይም በተለምዶ አጠራራቸው የባጃጅ አሽከርካሪዎች ያልተገባ የዋጋ ጭማሪ በማድረግ እንዲሁም የተወሰኑት በወንጀል ድርጊቶች ላይ በመሰማራት የከተማችን ነዋሪ የቅሬታ ምንጭ ሆነዋል " ብሏል።

የከተማ አስተዳደሩ የባጃጅ አገልግሎትን ስርዓት ለማስያዝ የአሰራር ማስተካከያ እያደረገ መሆኑን ገልጾ ይህ ተግባራዊ እስከሚሆን ድረስ በከተማድ ሁሉም አካባቢዎች የባጃጅ ትራንስፖርት አገልግሎት #እንዲቆም መወሰኑን ገልጿል።

የተሸርካሪዎቹ ከስራ መውጣት በነዋሪው ላይ የትራንስፖርት ጫና እንዳያሳድር አስተዳደሩ ሌሎቹ የትራንስፖርት አገልግሎቶች በሙሉ አቅማቸውና በቅንጅት አገልግሎት የሚሰጡበትን ሁኔታ መመቻቸቱን አመላክቷል።

(የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሌሎች ጉዳዮችንም ያነሳበት የዛሬ መጋቢት 1 ቀን 2015 ዓ.ም መግለጫ ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia
👎1.47K👍79532🤔25😱17🙏17🕊14🥰2😢1
#የWFP_ማጠንቀቂያ

የተመድ ዓለም ምግብ ፕሮግራም ለረሃብ የተጋለጡ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎችን ለመመገብ በቢሊዮኖች የሚቆጠር የገንዘብ ድጋፍ ማግኘት ካልተቻለ በሚቀጥሉት ከ12 እስከ 18 ወራት ውስጥ ዓለም፥ የጅምላ ስደትን፣ መረጋጋት የጎደላቸውን ሀገራት እና በረኀብ የተጠቁ ሕፃናትንና አዋቂዎችን ማየት እንደሚጀምር አስጠንቅቋል።

የድርጅቱ ዋና ኃላፊ ዴቪድ ቤስሊ ባለፈው ዐርብ  ቃለ ምልልስ ሰጥተው ነበር።

ቤስሊ ምን አሉ ?

- ለረሃብ የተጋለጡ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎችን ለመመገብ #በቢሊዮኖች የሚቆጠር የገንዘብ ድጋፍ ማግኘት ካልተቻለ በሚቀጥሉት ከ12 እስከ 18 ወራት ውስጥ ዓለም፥ የጅምላ ስደትን፣ መረጋጋት የጎደላቸውን ሀገራት እና በረሃብ የተጠቁ ሕፃናትንና አዋቂዎችን ማየት ይጀምራል።

- ባለፈው ዓመት፣ ከአሜሪካና ከጀርመን የተገኘውን ተጨማሪ ድጋፍ ይደነቃል ፤ ቻይና፣ የባሕረ ሠላጤው ሀገራት፣ ቢሊየነር ባዕለ ጸጋዎች እና ሌሎችም ሀገራት፣ ከምንጊዜውም በላይ አሁን ድጋፋቸውን ሊያፋጥኑ ይገባል።

- በ49 ሀገራት ውስጥ አስቸኳይ የሆነ #የምግብ ርዳታ የሚያስፈልጋቸውን 350 ሚሊዮን ሰዎች ለመርዳት 23 ቢሊየን ዶላር ሲሆን ይህ ገንዘብ ላያገኝ ይችላል ፤ ይህ ደግሞ በከፍተኛ ኹኔታ አስጨንቆኛል።

- አሜሪካ የምትሰጠውን የገንዘብ ርዳታ ከ3.5 ቢሊዮን ዶላር ወደ 7.4 ቢሊዮን አሳድጋለች፤ በተመሳሳይ ጀርመንም ከ350 ሚሊየን ዶላር ወደ 1.7 ቢሊዮን ከፍ አድርጋለች ፤ በዓለም ሁለተኛ ትልቁ የሆነውን ኢኮኖሚ የያዘችው ቻይና ባለፈው ዓመት ለተቋሙ የሰጠችው ገንዘብ 11 ሚሊየን ዶላር ብቻ በመሆኑ ድጋፏን ልታሳድግ ይገባል።

- #የነዳጅ_ዋጋ በከፍተኛ ሁኔታ ከመጨመሩ ጋራ ተያይዞ የባሕረ ሠላጤው ሀገራት የበለጠ እገዛ ሊያደርጉ ይችላሉ። በተለይ ከምሥራቅ አፍሪካ፣ ከሰሐራ እና ከሌሎች የመካከለኛው ምሥራቅ ሀገራት ጋራ ግንኙነት ያላቸው የሙስሊም ሀገራት የተሻለ አስተዋፅኦ ማድረግ ይችላሉ።

- ቅድሚያ ሊሰጣቸው የሚገባቸው በአፍሪካ የሳሕል ክልል የሚገኙ ሀገራትና ምሥራቅ ሶማሊያ ፣ ሰሜናዊ ኬንያ ፣ ደቡብ ሱዳን ፣  #ኢትዮጵያ 🇪🇹 ይገኙባቸዋል።

- የዓለም መሪዎች፣ ከፍተኛ የሆነ አለመረጋጋትን ሊያስከትሉ የሚችሉ የሰብአዊ ርዳታ ክፍተቶች ለአሉባቸው ሀገራት ቅድሚያ ሊሰጡ ይገባል።

ዴቪድ ቤስሊ በዓለም ትልቁ ሰብአዊ ርዳታ ሰጪ በሆነው ተቋም የነበራቸውን ሥልጣን በመጪው ሳምንት ለአሜሪካ አምባሳደር ሲንዲ ማኬይን ያስረክባሉ።

#VOA

@tikvahethiopia
👍1.05K😢174120👎69🕊23😱20🙏20🥰7
ዓለም አቀፍ የነዳጅ ዋጋ ላይ ጭማሪ ታይቷል ፤ ለምን ?

ባለተጠበቀ ሁኔታ የዓለማችን ከፍተኛ የነዳጅ አምራች አገራት #የነዳጅ_ምርትን_ለመቀነስ ከተስማሙ በኋላ የነዳጅ ዋጋ ጭማሪ አሳይቷል።

በዚህም የብሬንት አንድ በርሜል ድፍድፍ ነዳጅ በ5 የአሜሪካ ዶላር ወይም በ7 በመቶ ጨማሪ አሳይቶ ከ85 ዶላር በላይ እየተሸጠ ይገኛል።

የነዳጅ ዋጋ ጭማሪው የመጣው ፦ሳዑዲ አረቢያ፣ ኢራቅ እና ሌሎች በርካታ የባህረ ሰላጤው አገራት በቀን የአንድ ሚሊዮን በርሜል ነዳጅ ምርት ቅነሳ እናደርጋለን ካሉ በኋላ ነው።

የምርት ቅነሳውን ያደረጉት ኦፔክ+ የሚባሉት ነዳጅ አምራች አገራት ሲሆኑ ለዓለም ገበያ ከሚቀርበው የነዳጅ መጠን 40 በመቶውን ይሸፍናሉ።

ሳዑዲ አረቢያ የቀን ምርቷን በ500 ሺህ በርሜል የምትቀንስ ሲሆን ኢራቅ ደግሞ በ211 ሺህ በርሜል የዕለት ምርቷን ትቀንሳለች። የተባበሩት አረብ ኤሜሬቶች፣ ኩዌት፣ አልጄሪያ እና ኦማን ሌሎች የምርት ቅነሳ የሚያደርጉ አገራት ናቸው።

ነዳጅ አምራች አገራቱ የምርት ቅነሳ ማድረጋቸውን ካሳወቁ በኋላ የአሜሪካ ብሔራዊ ደኅንነት ም/ቤት “ የገበያ መረጋጋት በሌለበት በዚህ ወቅት የምርት ቅነሳ ማድረጉ የሚመከር አይደለም - ይህን ግልጽ አድርገናል ” ሲል አሳውቋል።

የሳዑዲ የኢነርጂ ሚኒስቴር ፤ የነዳጅ ምርት ላይ ቅናሽ ማድረግ ያስፈለገው " የነዳጅ ገበያ መረጋጋት ለመፍጥር የተወሰደ የቅድመ ጥናቃቄ እርምጃ ነው " ብሏል።

ናታን ፓይፐር የተባሉ የዘርፉ ተንታኝ በበኩላቸው ነዳጅ አምራቾች ምርታቸውን የቀነሱት በዓለም ምጣኔ ሃብት መቀዛዝ ምክንያት የነዳጅ ዋጋ በበርሜል #ከ80_ዶላር_በታች_እንዳይወርድ በማሰብ ነው ብለዋል።

መረጃው የቢቢሲ ነው።

@tikvahethiopia
👍524👎8965😢33😱19🕊9🥰6🙏5
TIKVAH-ETHIOPIA
#ሩስያ ሩስያ ላልተወሰነ ጊዜ ነዳጅ (ቤንዚን እና ናፍጣ) ወደ ውጭ መላክ አቆመች ፤ ይህ ተከትሎ የዓለም የነዳጅ ዋጋ ላይ ተፅእኖ ይኖራል ተብሎ ተሰግቷል። ሩስያ ፤ " የሀገር ውስጥ ገበያን ለማረጋጋት እንዲሁም የሀገር ውስጥ የነዳጅ ፍላጎትን ለማሻሻል " በሚል ከአራት የቀድሞ የሶቪየት ሕብረት አባላት ውጭ ወደ #ሁሉም_ሀገራት የነዳጅ ምርቶችን ቤንዚን እና ናፍጣ መላክን ለጊዜው አግዳለች። እገዳው…
#የነዳጅ_ዋጋ !

በዓለም ገበያ 1 በርሜል ብሬንት ድፍድፍ ነዳጅ ዋጋ ከ3 ወራት በፊት 74 የአሜሪካ ዶላር የነበረ ሲሆን አሁን 94.8 የአሜሪካ ዶላር ገብቷል።

የብሬንት ድፍድፍ ነዳጅ ዋጋ ከቀን ወደ ቀን እያሻቀበ ይገኛል። ትላንት 97 ዶላር ደርሶም ነበር። ይህም እኤአ ከህዳር 2022 ወዲህ ከፍተኛው ጭማሪ ሆኖ ተመዝግቧል።

የዚህ ከፍተኛ የሆነ የዋጋ ጭማሪ #ምክንያት የፍላጎት መጨመር እና የድፍድፍ ዘይት አቅርቦቶች በከፍተኛ ሁኔታ በመቀነሱ ነው ተብሏል።

ለአቅርቦት መቀነሱና ለዋጋ ንረቱ ደግሞ የ " OPEC+ " አባላት የሆኑት ሳዑዲ አረቢያና ሩስያ ከዚህ ቀደም ያሳለፏቸው ውሳኔዎች ትልቁን ድርሻ ይይዛል ተብሏል።

በርካታ በዘርፉ ላይ ያሉ ተንታኞች ዋጋው በቅርብ ጊዜ ከ100 ዶላር በላይ ሊደርስ እንደሚችል እየገለፁ ናቸው።

@tikvahethiopia
😱530😢177105😡71🕊40🙏38🥰15😭1