TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63K photos
1.61K videos
216 files
4.38K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
አሳሳቢ የምግብ እጥረት...#ኢትዮጵያ

በደቡብ ኢትዮጵያ አንዳንድ አካባቢዎች አሳሳቢ #የምግብ_እጥረት እንዳለ ዓለም አቀፉ ድንበር የለሽ የሐኪሞች ቡድን አሳሰበ። ቡድኑ በተለይ የጎሳ ግጭት አንድ ሚሊዮን የሚጠጉ ሰዎችን ባፈናቀለበት በደቡብ ክልል በምግብ እጥረት ይበልጡን የተጠቁት ህጻናት መሆናቸውን ዐስታውቋል። ባለፉት ሁለት ሳምንታት በጌድኦ በምግብ እጥረት እጅግ የተጎዱ ከ200 የሚበልጡ ህጻናትን ማከሙን ቡድኑ ይፋ አድርጓል። የቡድኑ የመስክ ሥራ አስተባባሪ ማርኩስ ቦይኒንግን ጠቅሶ የፈረንሳይ ዜና አገልግሎት እንደዘገበው ወላጆች ህጻናትን ወደ ክሊኒካቸው ይዘው የሚመጡት እጅግ ዘግይተው ነው። አንዳንዶቹም የሞት አፋፍ ላይ የሚገኙ ናቸው። ቶሎ ክሊኒኩ ባለመድረሳቸው ሕይወታቸው የሚያልፍ ህጻናት እንዳሉ ቡድኑ ተናግሯል። ሆኖም ቡድኑ የሞቱ ህጻናትን ቁጥር አልገለጸም። ጌድኦ የሚገኙት የተፈናቃዮች ማቆያ ሥፍራዎች ውስጥ የመጠለያ ኹኔታ፣ የውኃ አቅርቦት እና የንጽህና አጠባበቅ እጅግ አሳሳቢ መሆናቸውን ቦይኒንግ አስረድተዋል።

Via የጀርመን ራድዮ
@tsegabwolde @tikvahethiopia