TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.8K photos
1.61K videos
216 files
4.37K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
"ኢትዮጵያን #የሚያጠፏት እኔ አውቅላችኃለሁ ባዮች ናቸው" ፕሮፌሰር ደጀኔ አየለ
.
.
የአሁኑ ትውልድ ራሱን ከጥላቻ ንግግሮች በማራቅ በአንድነት፤ በፍቅር ኢትዮጵያን እንዲገነባ የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዘዳንት ጥሪ አቀረቡ። ፕሮፌሰሩ ጥሪውን ያቀረቡት TIKVAH-ETH በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ባዘጋጀው #StopHateSpeech/የፀረ ጥላቻ ንግግር/ ዘመቻ መድረክ ላይ ነው።

ወጣትነት ማለት ያልተለኮሰ ሻማ ነው ያሉት ፕሮፌሰር ደጀኔ -- ሰይጣን ሲለኩሰው የጥፋት እና የውድመት ኃይል ይሆናል፤ በመልካምነት እና በበጎነት ሲለኮስ ደግሞ ሀገር ይገነባል፤ ሀገር ይታደጋል ብለዋል። አክለውም ሁሉም ወጣት የእርስ በእርስ ግጭት ተፈጥሮባቸው ከነበሩት ሀገራት #በመማር ከጥላቻ ንግግሮች በመቆጠብ፤ በሰላም በፍቅር እና በአንድነት ለኢትዮጵያ እንዲሰራ ሀገራዊ ጥሪ አቅርበዋል።

በመጨረሻም ፕሮፌሰር ደጀኔ የTIKVAH-ETH ቤተሰብ አባላትን ያመሰገኑ ሲሆን ለሰላም እና ለፍቅር የሚደረገውን ጉዞ #እንደሚደግፉ ገልፀዋል፤ በ#StopHateSpeech ጉዞ ተሳታፊ የሆኑ ወጣቶችንም ያበረታቱ ሲሆን "ነገ ታሪክ ያስታውሳችኃል ጉዟቹን ቀጥሉ ሁሉም ከእናተ ዘንድ ይሰለፋል" ብለዋል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia