TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.9K photos
1.61K videos
216 files
4.37K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update ኢህአዴግ የደርግ መሰል #የቤት_ልማት_ፖሊስ ተግባራዊ ሊያደርግ ነው ተብሏል። በሀዋሳ በተደረገው የድርጅቱ 11ኛ ጉባኤ ላይ በቀረበው ሰነድ መሰረት #የመጠለያ ችግርን ከመቅረፍ አንፃር መሬት እና ፋይናንስ በማቅረብ ዜጎች ቤታቸውን #በራሳቸው ገንብተው የቤት ባለቤት የሚሆኑበት አሰራር ተግባራዊ ይደረጋል። መንግስት ቤት በራሱ ገንብቶ ለህብረተሰቡ ተደራሽ አደርጋለሁ ሲል ቢቆይም ከፍላጎት አንፃር መሄድ ያልቻለ እና #በሙስና እና #ብልሹ አሰራር የተተበተበ መሆኑ ሲያስተቸው መቆየቱ አይዘነጋም። በአዲሱ እቅድ መሬት እና ብድር ተመቻችቶ ቤት ፈላጊዎች በራሳቸው ይገነባሉ። ይህ አሠራር ደርግ እስከ መውደቂያው እለት ሲተገብረው የነበረ እና በርካቶችን እንዳ አቅማቸው የቤት ባለቤት እንዲሆኑ ያደረገበት ፖሊሲ እንደነበር ይታወሳል።

ምንጭ፦Muluken Yewondwossen,ENF
@tsegabwolde @tikvahethiopia
👍1