TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.9K photos
1.61K videos
216 files
4.37K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#COVID19

በኢትዮጵያ እስካሁን በኮሮና ቫይረስ የተጠቃ ሰው ባይኖርም በሽታውን ለመከላከል ማኅበረሰቡ የግል ንጽሕናውን በአግባቡ በመጠበቅ የራሱን ቅድመ ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚገባው የኢትዮጵያ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት አስታውቋል።

በሽታው ወደ ሀገር ቢገባ ከሚደረጉ ቅድመ ጥንቃቄዎች መካከል የተለያዩ ማእከላትን ግብዓት በማሟላት አስፈላጊ ዝግጅቶች እየተደረጉ መሆኑንም የኢትዮጵያ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ኤባ አባተ ተናግረዋል።

በአሁን ሰዓት የቫይረሱ ምልክት ታይቶባቸው በማቆያ ማእከላት ውስጥ አምስት ግለሰቦች የሚገኙ ሲሆን፣ ከዚህ ቀደም በማእከሉ ክትትል ሲደረግባቸው የነበሩ ከ900 በላይ ሰዎች ክትትላቸውን ጨርሰው መውጣታቸውንም ዋና ዳይሬክተሩ አስታውቀዋል።

#ኢቢሲ #የህብረተሰብጤናኢንስቲትዩት
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia