TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63K photos
1.61K videos
216 files
4.38K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
🏷የ12ኛ ክፍል የፈተና #ዉጤት አስመልክቶ በተለያዩ ማህበረዊ ሚዲያዎች የሚለቀቁ መረጃዎች #ሀሰት መሆናቸውን የፈተናዎች ኤጀንሲ አስታወቀ፡፡ ሀገር አቀፍ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች ኤጀንሲ እንዳስታወቀዉ የ12ኛ ክፍል ዉጤት #በቅርቡ ይለቃቃል የሚለዉ መረጃ መሰረተ ቢስ ነዉ ብሏል። የኤጀንሲዉ የሕዝብ ግንኙነት ሃላፊ አቶ ረዲ ሺፋ ለኢትዮኤፍኤም እንዳረጋገጡት ኤጀንሲዉ የፈተናዎቹ ዉጤት ይፋ የሚሆንበትን ቀን አልወሰነም ብለዋል፡፡

በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያዎች ዉጤቱ ተለቋል በዚህ ቀን ይለቀቃልና ሌሎች መሰል መረጃዎች ሀሰት እንደሆኑ አቶ ረዲ ተናግረዋል፡፡ ተማሪዎቹም ሆነ ህብረተሰቡ ከተሳሳተ መረጃ እራሱን እንዲጠብቅ ሃላፊዉ ጠይቀዋል፡፡ በቀጣይ ኤጀንሲዉ የ10ኛ እና የ12ኛ ክፍል የፈተና ዉጤት ይፋ የሚሆንበትን ቀን ለመገናኛ ብዙሃን በይፋ ያሳውቃል ብለዋል፡፡

Via #ኢትዮኤፍኤም
@tsegabwolde @tikvahethiopia