TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.8K photos
1.61K videos
216 files
4.37K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ብሔራዊ_ባንክ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ከጥር 10 ጀምሮ ለብሔራዊ ባንክ ገዥ ሹመት ሰጥተዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ የብሔራዊ ባንክ ገዥ በሆኑት ዶ/ር ይናገር ደሴ ምትክ አቶ ማሞ ምህረቱን በቦታው ላይ ሹመዋል።

አቶ ማሞ ምህረቱ ፤ የጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ #ከፍተኛ_የኢኮኖሚ አማካሪና ዋና የንግድ ተደራዳሪ እንዲሁም የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግ ዋና ስራ አስፈፃሚ በመሆን ሰርተዋል።

የብሔራዊ ባንክ ገዢ ዶ/ር ይነገር ደሴ በፈቃዳቸው ቦታቸውን ይልቀቁ ፣ ከባንኩ ገዢነት በመንግሥት ይነሱ ወይም ደግሞ ለሌላ ኃላፊነት/ስልጣን ታጭተው እንደሆነ እስካሁን ምንም የተባለ ነገር የለም።

ዶ/ር ይናገር ደሴ የብሔራዊ ባንክ ገዢ ሆነው ተሾሙት ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ወደ ሥልጣን ከመጡ ከወራት በኋላ በ2011 ዓ.ም ነበር።

@tikvahethiopia
👍716👎123🥰24🤔24😢2016🙏16🕊9😱8