አዳማ🔝
ከየካቲት 5 እስከ 7 ቀን 2011 ዓ.ም በአዳማ ከተማ ሲካሄድ የቆየው 32ኛው የኢትዮ-ኬንያ የጋራ የድንበር ኮሚሽን ስብሳባ ውሳኔዎች በማሳለፍ ተጠናቀቀ።
በስብሰባው የድንበር አካባቢ ማህበረሰቦች የፖለቲካ፣ የፀጥታ፣ የኢኮኖሚና ማህበራዊ ጉዳዮች ላይ ውይይት በማካሄድ በቀጣይ የሁለቱን አገሮች ግንኙነት ለማሻሻል የሚያግዙ ውሳኔዎች ተላልፈዋል፡፡
ኢትዮጵያ እና ኬንያ በአዋሳኝ ድንበሮቻቸው አካባቢ ያላቸውን ዘርፈ-ብዙ ግንኙነት ይበልጥ #ለማጠናከር እንደሚሰሩ የጋራ የድንበር ኮሚሽን ስብሰባ ላይ #ከመግባባት ላይ ተደርሷል። በተጨማሪም በድንበር አካባቢ ለሰላም እና ፀጥታ ችግር ሊሆኑ የሚችሉ ጉዳዮች በጋራ ለመፍታት ከሚመለከታቸው የሁለቱ አገራት መ/ቤቶች እና የተጋሪ ድንበር አካባቢ አስተዳዳሪዎች የአገር ሽማግሌዎች የተውጣጣ የሰላም ኮሚቴ ተቋቁሞ ወደ ስራ አንዲገባ ከስምምነት ላይ ተደርሷል።
ሁለቱም ወገኖች ስምምነቶቹን ለመተግበር የሚያስችል በልዑካን ቡድን መሪዎቻቸው አማካኝነት ቃለ ጉባኤ ተፈራርመዋል።
ምንጭ፦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ጽህፈት ቤት
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ከየካቲት 5 እስከ 7 ቀን 2011 ዓ.ም በአዳማ ከተማ ሲካሄድ የቆየው 32ኛው የኢትዮ-ኬንያ የጋራ የድንበር ኮሚሽን ስብሳባ ውሳኔዎች በማሳለፍ ተጠናቀቀ።
በስብሰባው የድንበር አካባቢ ማህበረሰቦች የፖለቲካ፣ የፀጥታ፣ የኢኮኖሚና ማህበራዊ ጉዳዮች ላይ ውይይት በማካሄድ በቀጣይ የሁለቱን አገሮች ግንኙነት ለማሻሻል የሚያግዙ ውሳኔዎች ተላልፈዋል፡፡
ኢትዮጵያ እና ኬንያ በአዋሳኝ ድንበሮቻቸው አካባቢ ያላቸውን ዘርፈ-ብዙ ግንኙነት ይበልጥ #ለማጠናከር እንደሚሰሩ የጋራ የድንበር ኮሚሽን ስብሰባ ላይ #ከመግባባት ላይ ተደርሷል። በተጨማሪም በድንበር አካባቢ ለሰላም እና ፀጥታ ችግር ሊሆኑ የሚችሉ ጉዳዮች በጋራ ለመፍታት ከሚመለከታቸው የሁለቱ አገራት መ/ቤቶች እና የተጋሪ ድንበር አካባቢ አስተዳዳሪዎች የአገር ሽማግሌዎች የተውጣጣ የሰላም ኮሚቴ ተቋቁሞ ወደ ስራ አንዲገባ ከስምምነት ላይ ተደርሷል።
ሁለቱም ወገኖች ስምምነቶቹን ለመተግበር የሚያስችል በልዑካን ቡድን መሪዎቻቸው አማካኝነት ቃለ ጉባኤ ተፈራርመዋል።
ምንጭ፦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ጽህፈት ቤት
@tsegabwolde @tikvahethiopia