TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63K photos
1.61K videos
217 files
4.38K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ከትምህርት ሚኒስቴር⬇️

ሰሞኑን ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ለቀጣዩ 15 ዓመት የሚሆን የትምህርትና ሥልጠና ፍኖተ-ካርታ ረቂቅ የጥናት ሰነድ ላይ የመጀመሪያውን #ውይይት እያካሄደ መሆኑ እየታወቀ አንዳንድ የማህበራዊ ድረ-ገፅ ተጠቃሚዎች ግን ጥናት አጥኝዎች ለውይይት ያቀረቡትን ሃሳብ ብቻ በመያዝ #መላው የሃገራችን ህዝብ ውይይት አድርጎ ይሁንታ ባላገኘውና ባልፀደቀው ሃሳብ በመንተራስ ለህብረተሰቡ መረጃ እያሰራጩ መሆኑ ታይቷል ።

ስለዚህ ህብረተሰቡ በመረጃው ሳይዛባ በተጠናው ረቂቅ ሰነድ መነሻነት በባለቤትነት #በመሳተፍ ለሃገራችን የትምህርትና ሥልጠና ፍትሃዊ
ተደራሽነት፣ አግባብነትና ጥራት መረጋገጥ የበኩሉን እንዲወጣ በዚህ አጋጣሚ በድጋሜ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን ።

በመጨረሻም ውይይቱ #ከመስከረም መጀመሪያ ጀምሮ እስከ #ታችኛው የህብረተስብ ክፍል የሚተገበር ይሆናል። በሚደረገው ውይይትም መግባባት ሲደረስ የ15 ዓመት የፍኖተ-ካርታው ዝግጅት ተጠናቆ በሚመለከተው አካል #መፅደቅ ሲችል ብቻ ተግባራዊ እንደሚሆን ትምህርት ሚኒስቴር ያሳውቃል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia