TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63.1K photos
1.62K videos
217 files
4.39K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ለጥንቃቄ

በአዲስ አበባ ከተማ ቂርቆስ ክ/ከተማ በተለያየ ቦታ እየተንቀሳቀሱ የመኪና ስፖኪዮ በመስረቅ ወንጀል የተጠረጠሩ 4 ግለሰቦች (ታዳጊ ልጆች) በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የቂርቆስ ክ/ከተማ ፖሊስ መምሪያ ገልጿል።

ተጠርጣሪዎቹ ሚያዚያ 23 እና 24/ 2016 ዓ.ም ወረዳ 2 ጋዜቦ አደባባይ እና ወረዳ 9 አካባቢ ነው የተያዙት ተብሏል።

ተጠርጣሪዎቹ #ከመስቀል፣አደባባይ ወደ #ቦሌ በሚወስደው መንገድ ላይ የትራፊክ መብራቶችና ተሽከርካሪ በሚቆምባቸው ሌሎች ቦታዎች ላይ በመንቀሳቀስ ስፖኪዮ ሲሰርቁ እንደነበር ፖሊስ አመልክቷል።

በዚህ የወንጀል ድርጊት ለይ ተሳትፈው የተገኙት ህፃናቶች መሆናቸውን ገልጿል።

በዚህ መነሻ በተደረገ ምርመራ ለህፃናቱ ስምሪት የሚሰጡ የተደራጁ ወንጀለኞች መኖራቸውን ፖሊስ ማረጋገጡን አሳውቋል።

" አንዳንድ ህፃናት መኪና የሚጠብቁ እንዲሁም ደግሞ እርዳታ የሚፈልጉ መስለው በመቅረብ የወንጀል ተግባራት እንደሚፈፅሙ አሽከርካሪዎች ተገንዝበው በትራፊክ መብራቶችም ሆነ የትራፊክ ፍሰት በሚበዛባቸው ሌሎች ቦታዎች ላይ ሲቆሙ እና በዝግታ ሲያሽከረክሩ ተገቢውን ጥንቃቄ ሊያደርጉ ይገባል " ሲል ፖሊስ መልዕክት አስተላልፏል።

#AddisAbabaPolice

@tikvahethiopia
👏32978😢73😱23😡23😭22🙏17🕊11🥰3🤔3