TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.8K photos
1.61K videos
216 files
4.37K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ‼️

ማሳሰቢያ፦

የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የ2011 ዓ.ም የመደበኛ ተማሪዎች ቅበላ ከጥቅምት 10 እስከ 14/2011 ዓ.ም ድረስ ማካሄዱ ይታወሳል፡፡

ዩኒቨርሲቲው የምዝገባ ስርዓቱን አጠናቆ መደበኛ የመማር ማስተማር ሂደት ውስጥ የገባ ሲሆን ለሠላማዊ የመማር ማስተማር መስፈን ከውጫዊና ውስጣዊ ባለድረሻ አካላት ጋር በቁርጠኝነት እየሰራ ይገኛል፡፡

ነገር ግን ዩኒቨርሲቲው በሚገኝበት አካባቢ ምንም አይነት የፀጥታ እና የደህንነት ስጋት ሳይኖር ተማሪዎችን ሆን ብሎ ለማወክና በዩኒቨርሲቲው ቅጥር ግቢ ውስጥ #ረብሻ እንደተከሰተ ተደርጎ በማህበራዊ ድረ ገፅ #እየተወራ ይገኛል፡፡

በመሆኑም ይህ መሰረተ ቢስ #ወሬ እንደ ሆነ ታውቆ ተማሪዎችና የተማሪ ወላጆች አንዳች #ስጋት እንዳይገባቸሁ ተቋሙ #ያሳስባል፡፡

መደበኛ የመማር ማስተማር ስራው ሳይስተጓጎል ተጠናክሮ እንዲቀጥል ባለድርሻ አካላት የተለመደ ትብብራቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉ እና አስፈላጊውን ትብብር ሁሉ እንዲያደርጉ ዩኒቨርሲቲው ያሳስባል፡፡

ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ
ጥቅምት 23/2011 ዓ.ም.
@tsegabwolde @tikvahethiopia