TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63K photos
1.61K videos
216 files
4.38K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update የአዲስ አበባ ፖሊስ አስጠነቀቀ⬇️

የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን በከተማዋ ሚስማር የተተከለበትን ዱላ የያዘ አንድም ሰው #እንዳልመለከት ብሏል፡፡

ምክትል ኮሚሽነር ዘላለም መንግስቴ በመዲናዋ የተከሰተውን አለመግባባት በተመለከተ ከሚመለከታቸው ጋር እየሰራሁ ነው ሲሉ ገልፀዋል፡፡

በህዝብ መገልገያ ንብረት፣ በመናፈሻዎች፣ በግንቦች፣ በአውቶብስ መጠበቂያዎች እና በአጠቃላይ ባንዲራ መቀባት #ፈፅሞ የተከለከለ እንደሆነ ፖሊስ ኮሚሽኑ ለሸገር ተናግሯል፡፡

የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን በከተማዋ ሚስማር የተተከለበትን ዱላ የያዙ ግለሰቦችን እንደተመለከተና #እርምጃ እንደተወሰደ ተናግረዋል፡፡

ከዚህ በኋላም ፖሊስ ኮሚሽኑ አላስፈላጊ የሆኑ ድርጊቶችን ከተመለከተ ፖሊሳዊ እርምጃ እንደሚወስድ አሳውቋል፡፡

የዲፕሎማት መቀመጫ ትልልቅ ጉባኤዎች የሚሰሙባት እና የአፍሪካ መዲና ለሆነችው አዲስ አበባ ደረጃዋን የጠበቀ ሰላምና ፀጥታ እንዲፈጠር ፖሊስ ኮሚሽኑ ከሚመለከታቸው ጋር እየሰራ እንደሆነ ለሸገር ተናግሯል፡፡

©Sheger FM 102.1
@tsegabwolde @tikvahethiopia