TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.8K photos
1.61K videos
216 files
4.37K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#መምህራን #ትግራይ

" ጥያቄያችን የመኖር ጥያቄ ነው ፤ መሰረታዊ የመምህራን ጥያቄ በአግባቡ ይመለስ ፤ እጅግ ተቸግረናል የ17 ወራት ውዙፍ ደመወዛችን ይከፈለን " ሲሉ የእንዳ ስላሰ ሽረ ከተማና አከባቢዋ መምህራን  በሰላማዊ ሰልፍ ጠየቁ።

መምህራኑ " መሰረታዊ ጥያቄዎቻችን " ያሉዋቸው እንዲመለሱላቸው ታህሳስ 7/2016 ዓ.ም በሰላማዊ ሰልፍ ጠይቀዋል። 

መነሻቸው ሽረ ስታድዮም በማድረግ በከተማዋ ዋና ዋና መንገዶች በመዞር ድምፃቸው ያሰሙ መምህራኑ ፤ ያጋጠማቸው ማህበረ ኢኮኖሚያዊ ቀውስ ጊዜ አይሰጥም ብለዋል። 

" ጥያቄያችን የመኖር እና ያለመኖር ጥያቄ ነው " ያሉት መምህራኑ የ2014 እና የ2015 ዓ.ም የደመወዝና የጋዎን ልብስ ክፍያ #እንዲከፈላቸው ጠይቀዋል። 

በተጨማሪ፦
- የስራ ግብር እንዲቀነስላቸው
- የደመወዝ እድገት እርከን እንዲሻሻልላቸው
- የቤት ኪራይ ክፍያ እንዲፈቀድላቸው የጠየቁት መምህራኑ ለደረሰባቸው ችግር #የሞራል_ካሳ እንዲሰጣቸው ጭምር በመፈክሮቻቸው ድምፃቸው አሰምተዋል። 

መምህራኑ በሰልፋቸው ያሳለፉት ከባድ የጦርነት ወቅት ፤ የተከሰተው የኑሮ ወድነትን የዋጋ ንረት ታሳቢ በማድረግ ከደደቢት ማይክሮፋይናንስ የወሰዱት የብድር ወለድ #እንዲሰረዝላቸው ጨምረው ጠይቀዋል።

የእንዳስላሰ ሽረ ከአዲስ አበባ በ1100 ፤ ከመቐለ በ300 ኪሎ ሜትር ርቀት የምትገኝ የትግራይ ሰሜናዊ ምእራብ ዞን ዋና ከተማ መሆንዋ የከተማዋ ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ፅህፈት ቤት በመጥቀስ የመቐለ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ዘግቧል።
                                   
@tikvahethiopia            
480😢122👏30😡23🕊16🙏13😭12😱11🥰7