TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63K photos
1.61K videos
217 files
4.38K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ሰበር ዜና-አብዴፓ‼️

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከአፋር ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥትና ከአፋር ብሔራዊ ዲሞክራሲዊ ፓርቲ የማዕከላዊ ኮሚቴ አመራር ጋር ባለፈዉ ሳምንት የጀመሩትን ዉይይት ዛሬ ህዳር 11 ቀን 2011 ዓ.ም. ቀጥለዋል፡፡

በዚህ ዉይይት በአገር አቀፍ ደረጃ በመካሄድ ላይ ያለውን ለውጥ በክልል ደረጃ እንዴት መካሄድ እንዳለበት ትኩረቱን ተደርጎበታል፡፡ በውይይቱ መጨረሻ ለውጡን የበለጠ ለማሳካት እንዲቻል ነባር የፓርቲ አመራሮች በአዲስ አመራሮች #እንዲተኩ ተወስንዋል።

ከዚህም በተጨማሪ የክልሉን ሰላምና ፀጥታ በበለጠ #በማጠናከር ህዝቡ የልማት ተጠቃሚነቱን የበለጠ ለማረጋገጥ እንዲቻል ሁሉም አመራር በጋር ለመስራት ስምምነት ላይ ተደርሷል፡፡

በሌላም በኩል የክልሉን ወጣቶችን ይበልጥ በማሳተፍ የህዝቡን የልማትና የዲሞክራሲ ጥያቄዎች ለመመለስ አመራሮቹ ቃል ገብተዋል፡፡

ምንጭ፦ የጠ/ሚ ፅ/ቤት
@tsegabwolde @tikvahethiopia