TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.9K photos
1.61K videos
216 files
4.37K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
የምክትል ከንቲባው ምስጋና~ለአዲስ አበቤዎች!

ክብረትና ጤና ይስጥልኝ፦

ዛሬ #በመስቀል_አደባባይ በነበረን ቆይታ እጅግ ደስ ብሎኛል። የሃሴቴ ምንጭ ለጋራ የጤና ጥበቃ እና የመንፈስ መታደስ የታደምነው አዲስአበቤዎች ቁጥራችን ብዙ ስለነበረ ብቻ አይደለም። በጋራ መቆማችን፣ የነበረን ፍቅርን እና ጨዋታ ነው ይበልጥ ያስደሰተኝ።

ሶስት ወራትን ያስቆጠረው የጋራ ስፖርት እንቅስቃሴያችን ካለምነው በላይ ህያው የሆነ ትሩፋት እያጎናፀፈን፣ ለቀጣዩ ወር ይዞት ለሚመጣው ድንቃድንቅ እያጓጓን መጥቷል።

ወንድም እህቶቼ፣ እርስ በእርስ ለመደጋገፍ እና ለጤናችን #መትጋታችንን እንቀጥል። ለሰርከስ፣ ለጂምናስቲክስ፣ ለማርሻል አርት ትርኢት አቅራቢዎች፣ ለጋራ ስፖርት አሰልጣኞች እነሆ የተለየ ምስጋና። #እንደሁሌውም ለምታኮሩኝ አስደናቂዎቹ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ጤና እና ክብረት ይስጥልኝ።

ኢንጂነር ታከለ ኡማ

@tsegabwolde @tikvahethiopia
👍1