TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63K photos
1.61K videos
216 files
4.38K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ከቢሾፍቱ የአይን እማኝ...

"ከኪዳነ ምህረት ቤተክርስቲያን መንገድ ላይ ስንደርስ ያልተፈቀደ አርማ ያለበትን ልብስ ለብሳችኃል/ይዛችኃል/ በሚል አታልፉም አሉን/የፀጥታ አካላት/። አረንጓዴ ቢጫ ቀይ የለበሱም ነበሩ እሱን እንዲህ ሆነን ማለፍ እንደማንችል ተነገረን። መዘምራንም ጭምር። ይሄን አርማ ይዛችሁ እና ለብሳችሁ ማለፍ አትችሉም አሉን። እዛው የነበርነው ሰዎች እንደዛ ከሆነ እዛው ኪዳነ ምህረት እናበራለን ብለን ተመለስን። ወደኪዳነ ምህረት ስንመለስ ወደአዳባባይ የሄዱት ሰዎች አንድ ደብር ጎሎ #አናበራም ብለው ሁሉም ተሰብስቦ ወደ ኪዳነ ምህረት እየተመለሰ ነበር #አደባባይ ያለውን ሳያበሩ ቀርተው። ግማሹ ኪዳነ ምህረት ከሄደ በኃላ እላይ ያለውን ወደታች እንዳይወርድ ታች ያለውን ወደ ላይ እንዳይወጣ ከለከሉ። ሰዎች ወደቤት አንሄድም አሉ። ሰዎችን አሳምነውም ወደአደባባይ ለመውሰድ እና ደመራው እንዲበራ ለማድረግ ጥረት አድርገው ነበር ግን ሰው አልተስማማ። እየዘመርን ወደቤታች እንመለሳለን ብሎ እኛ ወደቤታችን ሄደናል።"

ቢሾፍቱ ስለተፈጠረው ጉዳይ ምላሽ ለማግኘት ጥረት አድርጌ ነበር አልተሳካም። #BISHOFTU #ቢሾፍቱ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
👍1