TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63K photos
1.61K videos
217 files
4.38K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#ICRC #Tigray የዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል ኮሚቴ (ICRC) በተለያዩ ክልሎች በግጭት ለተጎዱ ወገኖች ድጋፍ ማድረጉን ቀጥሏል። ኮሚቴው #በትግራይ_ክልል በግጭት የተጎዱ አርሶ አደሮችን ምርታማነት ለማሳደግ ፦ 👉 በማዕከላዊ፣ 👉 በምስራቅ ፣ 👉 በደቡብ ምስራቅ እና በደቡብ ዞኖች ለሚገኙ ለ20,000 አባውራዎች (120,000 ግለሰቦች) የአፈር ማዳበሪያ በማከፋፈል ላይ እንደሚገኝ ዛሬ አሳውቋል።…
#ICRC

ICRC ለተፈናቃይ አባወራዎች የገንዘብ ድጋፍ አደረገ።

የዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል ኮሚቴ ፤ በኢትዮጵያ ውስጥ በግጭት የተፈናቀሉ አብዛኛዎቹ ሰዎች በሕይወት ለመቆየት በሰብአዊ እርዳታ ላይ ጥገኛ መሆናቸውን አመልክቷል።

በመጠለያ ካምፖች ውስጥ ያሉ ተፈናቃይ ሰዎች ደግሞ ምንም አይነት አስተማማኝ የኢኮኖሚ ምንጭ የላቸውም ሲል ገልጿል።

በዚህም ምክንያት በአማራ ክልል ፦ ሰሜን ወሎ ዞን፣ ሃብሩ ወረዳ፣ ጃራ የተፈናቃዮች መጠለያ ካምፕ ለሚገኙ 3,674 #ተፈናቃይ_አባወራዎች (22,044 ግለሰቦች) መሰረታዊ ፍላጎቶችን ለማሟላት የሚያግዝ የገንዘብ ድጋፍ ማድረጉን አሳውቋል።

@tikvahethiopia
👍24916👏12😢5🥰3🙏3