"የሀዋሳ ከተማ ሰላም አስተማማኝ ደረጃ ላይ ደርሷል!" የሆቴል ባለሀብቶችና ስራ አስኪያጆች
.
.
የሀዋሳ ከተማ #ሰላም አስተማማኝ ደረጃ ላይ በመድረሱ ተጠቃሚነታቸው እየጨመረ መምጣቱን በሀዋሳ የሆቴል ባለሀብቶችና ስራ አስኪያጆች ገለፁ።
በቱሪስት አገልግሎት ዘርፍ የሚስተዋሉ #ተግዳሮቶችን ለመፍታት ያለመ የምክክር መድረክ በሀዋሳ ከተማ ከሚገኙ የሆቴል ባለሀብቶችና ስራ አስኪያጆች ጋር በትላንትናው ዕለት ተካሂዷል፡፡
የሀዋሳ ከተማ ምክትል ከንቲባ አቶ ጥራቱ በየነ በመሩት በዚህ መድረክ የተሳተፉት የሆቴል ባለሀብቶች እና ስራ አስኪያጆች ቀድሞ የነበረውን የከተማዋን ሰላም ጠብቆ የማቆየት እና አስተማማኝ ደረጃ የማድረስ ኃላፊነት የመንግስት ብቻ ሳይሆን የሁሉም ህብረተሰብ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡
ለቱሪዝም ዘርፉ ተግዳሮት የሆኑ ጉዳዮችን በጋራ ለመፍታት እንሰራለን ያሉት የመድረኩ ተሳታፊዎች የከተማዋ ሰላም አስተማማኝ ደረጃ ላይ የደረሰ በመሆኑ ተጠቃሚነታችን ተረጋግጧልም ብለዋል፡፡
አቶ ጥራቱ በየነ የሀዋሳ ከተማ ም/ከንቲባ በበኩላቸው አስተዳደሩ ሰላምን በማረጋገጥ እና ሁሉን አቀፍ ለውጥ በማምጣት የከተማዋን የቱሪስት መስህብነት ከምንጊዜውም በላይ እውን ለማድረግ እንደሚሰራም አመላክተዋል፡፡
Via Hawassa City Administration Public Relation Office
@tsegabwolde @tikvahethiopia
.
.
የሀዋሳ ከተማ #ሰላም አስተማማኝ ደረጃ ላይ በመድረሱ ተጠቃሚነታቸው እየጨመረ መምጣቱን በሀዋሳ የሆቴል ባለሀብቶችና ስራ አስኪያጆች ገለፁ።
በቱሪስት አገልግሎት ዘርፍ የሚስተዋሉ #ተግዳሮቶችን ለመፍታት ያለመ የምክክር መድረክ በሀዋሳ ከተማ ከሚገኙ የሆቴል ባለሀብቶችና ስራ አስኪያጆች ጋር በትላንትናው ዕለት ተካሂዷል፡፡
የሀዋሳ ከተማ ምክትል ከንቲባ አቶ ጥራቱ በየነ በመሩት በዚህ መድረክ የተሳተፉት የሆቴል ባለሀብቶች እና ስራ አስኪያጆች ቀድሞ የነበረውን የከተማዋን ሰላም ጠብቆ የማቆየት እና አስተማማኝ ደረጃ የማድረስ ኃላፊነት የመንግስት ብቻ ሳይሆን የሁሉም ህብረተሰብ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡
ለቱሪዝም ዘርፉ ተግዳሮት የሆኑ ጉዳዮችን በጋራ ለመፍታት እንሰራለን ያሉት የመድረኩ ተሳታፊዎች የከተማዋ ሰላም አስተማማኝ ደረጃ ላይ የደረሰ በመሆኑ ተጠቃሚነታችን ተረጋግጧልም ብለዋል፡፡
አቶ ጥራቱ በየነ የሀዋሳ ከተማ ም/ከንቲባ በበኩላቸው አስተዳደሩ ሰላምን በማረጋገጥ እና ሁሉን አቀፍ ለውጥ በማምጣት የከተማዋን የቱሪስት መስህብነት ከምንጊዜውም በላይ እውን ለማድረግ እንደሚሰራም አመላክተዋል፡፡
Via Hawassa City Administration Public Relation Office
@tsegabwolde @tikvahethiopia
👍1